#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
“እና ደግሞ ጭራ
“የምን ጭራ? "
“ጭራ ነዋ፤ የዝንብ ማባረሪያ ጭራ፡፡”
ደግሞ ጭራ ምን ይሰራልሃል?
“ነገርኩሽኮ፡፡ ቄስ መምሰል ነው የምፈልገው::
ወር ሆነው ዘውዲቱ ቤት ዘግቶ ከተቀመጠ፡፡ ድንገት ሲሰወር
ደብዛው ሲጠፋ አውሬው እያጓራ በየስርቻው እንደሚያነፈንፍ ገምቷል፡፡
ቢሆንም አንድ ቦታ አድብቶ ጊዜ እስከወሰደ ድረስ መልሰው ጭራውን
ለመያዝ ይቸገራሉ። በዛ ጊዜ ውስጥ ራሱን ለመቀየር ጊዜ ያገኛል።
ከውዲቱ ጋር በሂሣብ ተስማምተው እዛው ሰነበተ:: . አብሯት የሚያድር ደንበኛ ያገኘች ሌሊት እፎይ ብሎ አንዴ በጀርባው አንዴ በደረቱ እየተገላበጠ ደልቶት እየተኛ ያልቀናት : ሌሊት ደግሞ የማታ ማታ እየተጎተተች መጥታ በዛችው ጠባብ ታጣፊ አልጋ ላይ እየተጋፉ ወር
አለፈ ፤ እንደምንም::
ገና ቤቷን በተከራየ በአራተኛው ቀን ነበር አላስችል ብሏት የጠየቀችው:: የጠበቀው ጥያቄ ነበር! መምጣቱ አላስደነገጠውም
አላስበረገገውም:: ተዘጋጅቷል፤ ምን እንደሚመልስላት ያውቅ ነበር፡፡
"ጺምህን ለምን አትላጨውም? ደግሞ ለምን ወጣ አትልም? ከጠዋት ጀምረህ እስከ ማታ በር ዘግተህ ምንድነው? የጤና ነው?” አለችው ጠዋት ከደንበኛ ጋር ኣድራ አረፋፍንዳ ስትመጣ ቤት ስታገኘው፡፡
“አዎ፡፡” አላት ነገሩን በአጭሩ ለመቅጨት፡፡
“ምን ማለት ነው አዎ?” አለች የምታበጥረውን ፀጉሯን ለቃ
ቁለቁል በተቀመጠበት እየተመለከታችሁ
“አዎ ነዋ፡፡” አለ ይበልጥ ገፍታ ገፍታ እስክትመጣ ወጥራ እስክትይዘው፡፡
ሁኔታው እንዳላማራት በግልጽ ታስታውቃለች። ቀሚሷን በጭንቅላቷ አውልቃ አልጋው ላይ ወርወር አደረገችውና ከፊት ለፊቷ
ያለውን ቁም ሳጠን ከፈተች፡፡
“እየው ወንድም” አለች ከቁም ሳጥኑ ውስጥ የታሰቀላ ልብስ ማውረዷን ሳታቋርጥ ፊቷን ወደሱ መልሳ፡፡ «እየው ወንድም ብሬ እስካልተቋረጠ ድረስ ዓመትም ተግተህ ብትቆይ ግድ የለኝም:: ግን ደግሞ ችግር አልፈልግም፡፡ ከፖሊስ ነው የተደበቅኽው አይደል?”
“ምን ማለትሽ ነው? እንዴት ከፖሊስ?” ደነገጠ፡፡
ተው ባክህ አለች ከቁምሳጥኗ ያወረደችውን ቀሚስ እያጠለቀች፡፡ “አሁን ማን ይሙት ዓለም በቃኝ ብለህ እኔ ጎጆ ውስጥ ሱባዔ የገባኸው ለነፍስህ ነው?”
የሚለው ጠፍቶት ዝም ብሎ ተመለከታት፡፡
“ሰርቀህ ነው! አይደል? ሰርቀህ ነው የተደሰቅኸው?“
“አይደለም… አይደለም::” አለ ፈጠን ብሎ፡፡ ለፖሊስ እንዳታሳጣው
ሰጋ፡፡
“ታዲያ ምንድነው? ወይስ ፍቅር ያዘህ ከኔ!” አለች ድንገት ስቃ፡፡
“እየው እኔ ግድ የለኝም:: ሌባ ቀርቶ የፈለከውን መሆን ትችላለህ፡፡ ግን
ልምከርህ፡፡ ከፖሊስ ከሆነ የተደበቅኸው እዚህ ተከተህ አታመልጣቸውም፡፡
አንድ ቀን ወጣ ያልክ ቀን ጋማህን ያብቱሃል፡፡ ራቅ ብለህ ሂድ፡፡ ድሬድዋ
ወይ ጅማ! እንደገንዘቡ እንደሰረቅከው ገንዘብ ብዛት፡፡”
ከተቀመጠበት ኣልጋ ላይ ተነስቶ
“ሰርቄ አይደለም ዘውዲቱ በጠባቧ ክፍል ጎርደድ ማለት ያዘ፡፡
“ታዲያ እኔ ቤት ውስጥ እናትህን ቀብረሃል? ”እይኖቿ አብረው
እየተንጎራደዱ ወገቧን ይዛ ጠየቀችው፡፡
ጊዜው እንደሚደርስ ቀድሞውኑም ገብቶታል፡፡ እንደምትጠይቀው ወጥራ እንደመትይዘው ገብቶታል፡፡የሚያሳምን ምክንያት መስጠት እንዳለበትም ተረድቷል፡፡ አለበለዚያ ለሳምንታት ቤቷ ውስጥ ተደብቆ ሊቆይ አይችልም፡፡ በአጭሩ የቤትሽን ኪራይ እስካላቋረጥኩ ድረስ አያገባሽም፡፡ ብሎ ዝም ሊያሰኛት ይችላል። ግን ደግሞ ልትፈራ ትችላለች! ወንጀል ፈጽሞ ከቤቷ የተሸሸገ ሊመስላት ይችላል:: “ውጣ!” ብትለውስ? ፖሊስ ይዛ
ከተፍ ብትልስ?ለዚህ ነው ቀደም ብሎ የሚላትን ያዘጋጀው፡፡ “ሊያስደነግጣት
አይገባም፡፡ ግን ደግሞ ልታዝንለት ይገባል። ችግሩን ተረድታ ልትረዳው
ፈቃደኛ መሆን አለባት፡፡ ቀስ ብሎ ማግባባት አለበት፡፡
“ምን መሰለሽ ዘውድዬ.…አለ ቀረብ ብሎ ግራ ክንፏን ያዝ አደረገና፡፡ “ግን አደራ…”
አይ ይሄን ያህል የሚያስጨንቅህ ከሆነ አትንገረኝ፡፡ ምን መሰለህ ከብዬ በሰላም መኖር ስለምፈልግ ብቻ ነው፡፡ ገላዬን ሽጨ የኖርኩት አንሶኝ ተባበርሽ ምንትስዬ ተብዬ ዘብጥያ መውረድ አልፈለግም፡፡ ይገባሃል አይደል?ልጅ አለኝ፡፡ የምወደው የምቀልበው ወንድ ልጅ፡፡ነገ የሚሸረሙጥ” ፈገግ አለች፡፡
ልታስከፋው እንዳልፈለገች ከሁኔታዋ ያስታውቃል፡፡ባለፉት ቀናቶች
ሳይታወቃቸው በመሃላቸው የመግባባት ስሜት ተፈጥሯል፡፡ስሙን ስትጠይቀው 'ከበደ' ብሎ እንደዋሻት ብትረዳም አላስጨነቀችውም፤ ስቃ ተወችው
ተወችው።ተከትለዋት እቤቷ ድረስ መጥተው ተጨማልቀው አጨማልቀዋት
ሳንቲም ወርውረውላት እንደሚሄዱ ደንበኛቿ እንዳልሆነ ግን ተረድታዋለች፡፡
የመጀመሪያው ማታ አብሬሽ
አልተኛም ሲላት ለይስሙላ ነበር የመሰላት፡፡ አጋጥመዎታላ! የገዛ ገንዘባቸውን ከፍለው መጥተው ተለማመጡን የሚሉ፤ ካላንቆለጳጰሳችሁን የሚሉ፤ “ያው የገዛችሁት ዕቃ” ሲባሉ የሚግደረደሩ።
ያን ቀን ማታ በል የውስጥ ልብሴን አቀብለኝ ብላው ያለችውን አቀብሏት : መብራቱን አጥፍቶ ከጎኗ አልጋው ውስጥ ሲገባ ይዘግይ እንጅ ያው እንደ አውሬ ወንድሞቹ የማታ የማታ ዘሎ እንደሚያንቃት አልተጠራጠረችም ነበር፡፡ አልጋዋ ወስጥ ገብቶ በጀርባው ተኝቶ
አንጋለወት እንደሄዱ ህፃን ጣሪያ ጣሪያውን ሲመለከት በጨለማው ውስጥ
ስታየው ደነቃት፣ቢሆንም አላመነችውም፡፡ ዘግይቶ ሊጓጉር ነው ብላ ደህና እደር አለችና በደረቷ ተገልብጣ ተኛች፡፡ እንቅልፍ ሊወስዳት ግን አልቻለም፡፡ ሰውነቷ አላርፍልሽ አላት:: . 'ከአሁን አሁን ዘሎ.. እያለች እላይ እታች የሚለውን ትንፋሹን ተከተለችው::
እንቅልፍ፡ እንዳልወሰደው እርግጠኛ ነበረች፡፡ እንዳሰበችው ሃሳቡን
ሳያቀያር ዘገየባት፡፡ ሲያነቃቃውና በጊዜ ብገላገል ብላ በእንቅልፍ ልቧ
እንዳለች ሁሉ ተወራጨችና በብርድ ልብሱ ውስጥ ክንዷን ሰድዳ አንድ
እጇን ጭኑ ላይ ጣል አደረገችው:: ተፈታተነች፡፡ ሲሸማቀቅ ተሰማት።
እጁን ሰድዶ እጇን ከላዩ ላይ አነሳና በቀስታ እራቅ አድርጎ አስቀመጠው፡፡
በእንቅልፍ ልቧ ያለች ሳይመስለው አልቀረም። ጃውሳው! በጉ! ተረጋጋች፡፡
ሳታውቀው ድብን ያለ አንቅልፍ ይዟት ጭልጥ አለ፡፡
በተከተሉት ቀናት ሳትጠይቀው ቀድሞ የተስማሙበትን የወር የቤት ኪራይ ሂሳብ ሰጣት፡፡ ከዛ በተረፈ ሆቴል እንድታመጣለት ገንዘብ እየሰጣት እራሱን ብቻ ሳይሆን እሷንም እየቀለበ ተቀመጠ፡፡ ተገኝቶ ነው?፡፡ ግን ደግሞ አቤት ብቅ አለማለቱ የተደበቀ ሰው አስመስሎታል፡፡ አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ ዘግቶ መቀመጥ ምን ማለት ነው? . ታዲያ ይና ዝም
ብሎ ማለፍ ይቻላል? እህእ ነገ አንዱ መርቶበት ቢያስይዘው አብራ መውረዷ እደደለም? የተካፈለች አብራ የገመጠች ይመስል ሆ!
“ልክ ነሽ! ልክ ነሽ! ይገባኛልኮ፡፡ ግን ሠርቄ አይደለም፡፡” አላት የያዛቸውን ክንዶቿን ለቆ አልጋው ላይ እየተቀመጠ፡፡
“እሺ ምንድነው ታድያ? ”
“እደው ምን መሰለሽ…” ያጠነጠነውን ይተረትር ጀመር፡፡ አራት ቀን መሉ ብቻውን በሚሆን ሰዓት እየተንጎራደደ ያጠናውን የተለማመደውን ዲስኩር ጀመረ፡፡
“በምስራበት መሥሪያ ቤት ውስጥ ረዳት የሂሣብ ክፍል ኃላፊ ሆኜ ነው የማገለግለው ዘውድዬ እኔ ትዳር ያለኝ ሰው ነኝ፤ የሁለት ልጆች አባት ነኝ:: ነገር አልሻም፤ በሠላም ሰርቼ ከቤቴ መግባት ከባለቤቱና ከልጆቼ ጋር ያገኘሁትን ተቋድሼ ማደር ነው የምሻ:: ምን መሰለሽ…” ትክ ብለው ቁልቁል የሚያዩት አይኖቿ ሰርስረውት ገቡ፡፡ ግንባሩን የምታነብ መሰሰው፡፡ሁለት እጆቹን አንስቶ ለአንድ አፍታ በመዳፎቹ ውስጥ ደበቀው ሰባራ ሳንተም አላነሳሁም ግን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
“እና ደግሞ ጭራ
“የምን ጭራ? "
“ጭራ ነዋ፤ የዝንብ ማባረሪያ ጭራ፡፡”
ደግሞ ጭራ ምን ይሰራልሃል?
“ነገርኩሽኮ፡፡ ቄስ መምሰል ነው የምፈልገው::
ወር ሆነው ዘውዲቱ ቤት ዘግቶ ከተቀመጠ፡፡ ድንገት ሲሰወር
ደብዛው ሲጠፋ አውሬው እያጓራ በየስርቻው እንደሚያነፈንፍ ገምቷል፡፡
ቢሆንም አንድ ቦታ አድብቶ ጊዜ እስከወሰደ ድረስ መልሰው ጭራውን
ለመያዝ ይቸገራሉ። በዛ ጊዜ ውስጥ ራሱን ለመቀየር ጊዜ ያገኛል።
ከውዲቱ ጋር በሂሣብ ተስማምተው እዛው ሰነበተ:: . አብሯት የሚያድር ደንበኛ ያገኘች ሌሊት እፎይ ብሎ አንዴ በጀርባው አንዴ በደረቱ እየተገላበጠ ደልቶት እየተኛ ያልቀናት : ሌሊት ደግሞ የማታ ማታ እየተጎተተች መጥታ በዛችው ጠባብ ታጣፊ አልጋ ላይ እየተጋፉ ወር
አለፈ ፤ እንደምንም::
ገና ቤቷን በተከራየ በአራተኛው ቀን ነበር አላስችል ብሏት የጠየቀችው:: የጠበቀው ጥያቄ ነበር! መምጣቱ አላስደነገጠውም
አላስበረገገውም:: ተዘጋጅቷል፤ ምን እንደሚመልስላት ያውቅ ነበር፡፡
"ጺምህን ለምን አትላጨውም? ደግሞ ለምን ወጣ አትልም? ከጠዋት ጀምረህ እስከ ማታ በር ዘግተህ ምንድነው? የጤና ነው?” አለችው ጠዋት ከደንበኛ ጋር ኣድራ አረፋፍንዳ ስትመጣ ቤት ስታገኘው፡፡
“አዎ፡፡” አላት ነገሩን በአጭሩ ለመቅጨት፡፡
“ምን ማለት ነው አዎ?” አለች የምታበጥረውን ፀጉሯን ለቃ
ቁለቁል በተቀመጠበት እየተመለከታችሁ
“አዎ ነዋ፡፡” አለ ይበልጥ ገፍታ ገፍታ እስክትመጣ ወጥራ እስክትይዘው፡፡
ሁኔታው እንዳላማራት በግልጽ ታስታውቃለች። ቀሚሷን በጭንቅላቷ አውልቃ አልጋው ላይ ወርወር አደረገችውና ከፊት ለፊቷ
ያለውን ቁም ሳጠን ከፈተች፡፡
“እየው ወንድም” አለች ከቁም ሳጥኑ ውስጥ የታሰቀላ ልብስ ማውረዷን ሳታቋርጥ ፊቷን ወደሱ መልሳ፡፡ «እየው ወንድም ብሬ እስካልተቋረጠ ድረስ ዓመትም ተግተህ ብትቆይ ግድ የለኝም:: ግን ደግሞ ችግር አልፈልግም፡፡ ከፖሊስ ነው የተደበቅኽው አይደል?”
“ምን ማለትሽ ነው? እንዴት ከፖሊስ?” ደነገጠ፡፡
ተው ባክህ አለች ከቁምሳጥኗ ያወረደችውን ቀሚስ እያጠለቀች፡፡ “አሁን ማን ይሙት ዓለም በቃኝ ብለህ እኔ ጎጆ ውስጥ ሱባዔ የገባኸው ለነፍስህ ነው?”
የሚለው ጠፍቶት ዝም ብሎ ተመለከታት፡፡
“ሰርቀህ ነው! አይደል? ሰርቀህ ነው የተደሰቅኸው?“
“አይደለም… አይደለም::” አለ ፈጠን ብሎ፡፡ ለፖሊስ እንዳታሳጣው
ሰጋ፡፡
“ታዲያ ምንድነው? ወይስ ፍቅር ያዘህ ከኔ!” አለች ድንገት ስቃ፡፡
“እየው እኔ ግድ የለኝም:: ሌባ ቀርቶ የፈለከውን መሆን ትችላለህ፡፡ ግን
ልምከርህ፡፡ ከፖሊስ ከሆነ የተደበቅኸው እዚህ ተከተህ አታመልጣቸውም፡፡
አንድ ቀን ወጣ ያልክ ቀን ጋማህን ያብቱሃል፡፡ ራቅ ብለህ ሂድ፡፡ ድሬድዋ
ወይ ጅማ! እንደገንዘቡ እንደሰረቅከው ገንዘብ ብዛት፡፡”
ከተቀመጠበት ኣልጋ ላይ ተነስቶ
“ሰርቄ አይደለም ዘውዲቱ በጠባቧ ክፍል ጎርደድ ማለት ያዘ፡፡
“ታዲያ እኔ ቤት ውስጥ እናትህን ቀብረሃል? ”እይኖቿ አብረው
እየተንጎራደዱ ወገቧን ይዛ ጠየቀችው፡፡
ጊዜው እንደሚደርስ ቀድሞውኑም ገብቶታል፡፡ እንደምትጠይቀው ወጥራ እንደመትይዘው ገብቶታል፡፡የሚያሳምን ምክንያት መስጠት እንዳለበትም ተረድቷል፡፡ አለበለዚያ ለሳምንታት ቤቷ ውስጥ ተደብቆ ሊቆይ አይችልም፡፡ በአጭሩ የቤትሽን ኪራይ እስካላቋረጥኩ ድረስ አያገባሽም፡፡ ብሎ ዝም ሊያሰኛት ይችላል። ግን ደግሞ ልትፈራ ትችላለች! ወንጀል ፈጽሞ ከቤቷ የተሸሸገ ሊመስላት ይችላል:: “ውጣ!” ብትለውስ? ፖሊስ ይዛ
ከተፍ ብትልስ?ለዚህ ነው ቀደም ብሎ የሚላትን ያዘጋጀው፡፡ “ሊያስደነግጣት
አይገባም፡፡ ግን ደግሞ ልታዝንለት ይገባል። ችግሩን ተረድታ ልትረዳው
ፈቃደኛ መሆን አለባት፡፡ ቀስ ብሎ ማግባባት አለበት፡፡
“ምን መሰለሽ ዘውድዬ.…አለ ቀረብ ብሎ ግራ ክንፏን ያዝ አደረገና፡፡ “ግን አደራ…”
አይ ይሄን ያህል የሚያስጨንቅህ ከሆነ አትንገረኝ፡፡ ምን መሰለህ ከብዬ በሰላም መኖር ስለምፈልግ ብቻ ነው፡፡ ገላዬን ሽጨ የኖርኩት አንሶኝ ተባበርሽ ምንትስዬ ተብዬ ዘብጥያ መውረድ አልፈለግም፡፡ ይገባሃል አይደል?ልጅ አለኝ፡፡ የምወደው የምቀልበው ወንድ ልጅ፡፡ነገ የሚሸረሙጥ” ፈገግ አለች፡፡
ልታስከፋው እንዳልፈለገች ከሁኔታዋ ያስታውቃል፡፡ባለፉት ቀናቶች
ሳይታወቃቸው በመሃላቸው የመግባባት ስሜት ተፈጥሯል፡፡ስሙን ስትጠይቀው 'ከበደ' ብሎ እንደዋሻት ብትረዳም አላስጨነቀችውም፤ ስቃ ተወችው
ተወችው።ተከትለዋት እቤቷ ድረስ መጥተው ተጨማልቀው አጨማልቀዋት
ሳንቲም ወርውረውላት እንደሚሄዱ ደንበኛቿ እንዳልሆነ ግን ተረድታዋለች፡፡
የመጀመሪያው ማታ አብሬሽ
አልተኛም ሲላት ለይስሙላ ነበር የመሰላት፡፡ አጋጥመዎታላ! የገዛ ገንዘባቸውን ከፍለው መጥተው ተለማመጡን የሚሉ፤ ካላንቆለጳጰሳችሁን የሚሉ፤ “ያው የገዛችሁት ዕቃ” ሲባሉ የሚግደረደሩ።
ያን ቀን ማታ በል የውስጥ ልብሴን አቀብለኝ ብላው ያለችውን አቀብሏት : መብራቱን አጥፍቶ ከጎኗ አልጋው ውስጥ ሲገባ ይዘግይ እንጅ ያው እንደ አውሬ ወንድሞቹ የማታ የማታ ዘሎ እንደሚያንቃት አልተጠራጠረችም ነበር፡፡ አልጋዋ ወስጥ ገብቶ በጀርባው ተኝቶ
አንጋለወት እንደሄዱ ህፃን ጣሪያ ጣሪያውን ሲመለከት በጨለማው ውስጥ
ስታየው ደነቃት፣ቢሆንም አላመነችውም፡፡ ዘግይቶ ሊጓጉር ነው ብላ ደህና እደር አለችና በደረቷ ተገልብጣ ተኛች፡፡ እንቅልፍ ሊወስዳት ግን አልቻለም፡፡ ሰውነቷ አላርፍልሽ አላት:: . 'ከአሁን አሁን ዘሎ.. እያለች እላይ እታች የሚለውን ትንፋሹን ተከተለችው::
እንቅልፍ፡ እንዳልወሰደው እርግጠኛ ነበረች፡፡ እንዳሰበችው ሃሳቡን
ሳያቀያር ዘገየባት፡፡ ሲያነቃቃውና በጊዜ ብገላገል ብላ በእንቅልፍ ልቧ
እንዳለች ሁሉ ተወራጨችና በብርድ ልብሱ ውስጥ ክንዷን ሰድዳ አንድ
እጇን ጭኑ ላይ ጣል አደረገችው:: ተፈታተነች፡፡ ሲሸማቀቅ ተሰማት።
እጁን ሰድዶ እጇን ከላዩ ላይ አነሳና በቀስታ እራቅ አድርጎ አስቀመጠው፡፡
በእንቅልፍ ልቧ ያለች ሳይመስለው አልቀረም። ጃውሳው! በጉ! ተረጋጋች፡፡
ሳታውቀው ድብን ያለ አንቅልፍ ይዟት ጭልጥ አለ፡፡
በተከተሉት ቀናት ሳትጠይቀው ቀድሞ የተስማሙበትን የወር የቤት ኪራይ ሂሳብ ሰጣት፡፡ ከዛ በተረፈ ሆቴል እንድታመጣለት ገንዘብ እየሰጣት እራሱን ብቻ ሳይሆን እሷንም እየቀለበ ተቀመጠ፡፡ ተገኝቶ ነው?፡፡ ግን ደግሞ አቤት ብቅ አለማለቱ የተደበቀ ሰው አስመስሎታል፡፡ አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ ዘግቶ መቀመጥ ምን ማለት ነው? . ታዲያ ይና ዝም
ብሎ ማለፍ ይቻላል? እህእ ነገ አንዱ መርቶበት ቢያስይዘው አብራ መውረዷ እደደለም? የተካፈለች አብራ የገመጠች ይመስል ሆ!
“ልክ ነሽ! ልክ ነሽ! ይገባኛልኮ፡፡ ግን ሠርቄ አይደለም፡፡” አላት የያዛቸውን ክንዶቿን ለቆ አልጋው ላይ እየተቀመጠ፡፡
“እሺ ምንድነው ታድያ? ”
“እደው ምን መሰለሽ…” ያጠነጠነውን ይተረትር ጀመር፡፡ አራት ቀን መሉ ብቻውን በሚሆን ሰዓት እየተንጎራደደ ያጠናውን የተለማመደውን ዲስኩር ጀመረ፡፡
“በምስራበት መሥሪያ ቤት ውስጥ ረዳት የሂሣብ ክፍል ኃላፊ ሆኜ ነው የማገለግለው ዘውድዬ እኔ ትዳር ያለኝ ሰው ነኝ፤ የሁለት ልጆች አባት ነኝ:: ነገር አልሻም፤ በሠላም ሰርቼ ከቤቴ መግባት ከባለቤቱና ከልጆቼ ጋር ያገኘሁትን ተቋድሼ ማደር ነው የምሻ:: ምን መሰለሽ…” ትክ ብለው ቁልቁል የሚያዩት አይኖቿ ሰርስረውት ገቡ፡፡ ግንባሩን የምታነብ መሰሰው፡፡ሁለት እጆቹን አንስቶ ለአንድ አፍታ በመዳፎቹ ውስጥ ደበቀው ሰባራ ሳንተም አላነሳሁም ግን
👍3