#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
...“በጣም ጎበዝ ያቤዝ፡፡ ስለ አለብህ የጤና ችግር ለማውቅ መፈለግ በጣም ጉብዝና ነው፡፡ በተጨማሪም ብዙ ጥቅም አለው፡፡ ባይፖላር ዲስኦርደር ማለት፣ ሰዎች ሁለት የስሜት ዋልታዎች መፈራረቅን ተከትሎ፣ተደጋጋሚ የሚመጣ የባህሪ መለዋወጥ ሲያጋጥማቸው ነው።
መለዋወጦቹም፧ በስሜት ከፍታዎች እና በስሜት ዝቅታዎች መካከል የሚከሰት ነው:: በመሆኑም ይህ ችግር ያለበት ሰው፣ ባለበት የስሜት ከፍታ ወይም ዝቅታ መሰረት አሰተሳሰቡ፣ ውሳኔ አሰጣጡ፣ በነገሮች ላይ የሚኖረው ፍላጎት፣ ድርጊቶችን ለማድረግ የሚኖረው ሀይልና ጉልበት፣ በአጠቃላይ የህይወት አመለካከቱና አረዳዱ በሰዐቱ እንዳለው
የስሜት ሁኔታ የተለያየ ነው፡፡ በተጨማሪም፣ የዚህ ችግር ተጠቂ የሆኑ
ሰዎች ውስጣዊ ለውጦች ሊኖራቸው፣ አካባቢያቸው የተለወጠ ስለሚመስላቸው የሚሰጡት ምላሽ የተሳሳተ ሊሆን ይችላል፡፡
የዚህ ችግር ተጠቂዎች የስሜት ከፍታ ሲኖራቸው ማኒያ ወይም ሃይፖማኒያ ይባላል፡፡ ማኒያ ከሃይፖማኒያ ተመሳሳይ ምልክት ቢኖረውም፣ ማኒያ በህመም ደረጃው ከበድ ያለ በሽታ ነው፡፡ ይህ
የባህሪዎች መለዋወጥ፣ ችግሩ ያለባቸውን ሰዎች በስራ፣ በትምህርት፣
በማህበራዊ እንቅስቃሴያቸው እና ግንኙነቶቻቸው ላይ ችግሮች
ማወቅ እንዲከሰቱ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ የስሜት ከፍታ ላይ ሲሆኑ፤ በፊት
ብዙም ትኩረት ማይሰጡትን ጉዳይ የማየት፣ የመስማትና የማወቅ ፍላጎት መጨመርን ያሳያሉ፤ ከነበራቸው ማህበራዊ መግባባት የጨመረ
የመቀራረብና የመግባባት ባህሪ ያሳያሉ፣ የማይጨበጡ፣ ወይም
ቶሎቶሎ ሚቀያየሩ አዳዲስ ሀሳቦችንና ንድፎችን በማምጣት ያወራሉ፤አንድ ቦታና አንድ ሃሳብ ላይ በጥልቀት ማስብ ስለሚያስጨንቃቸው ቶሎ ከሃሳብ ወደ ሃሳብ ይቀያይራሉ፣ በጥቃቅን ነገሮች አክርረው ይጨቃጨቃሉ፣ ነገሮቹ ከነርሱ ህይወት ጋር ጠቃሚ ግንኙነት ባይኖራቸውም፣ ስለሚሰሟቸው ነገር ከፍተኛ የማወቅ ፍፈላጎት ያሳያሉ፤ ለነገሮች ከተገቢው በላይ ይናደዳሉ፣ ይበሳጨሉ፣ ከብሰጭት ስሜት መውጣት ይቸገራሉ፣ የተጋነነ በራስ የመተማመን ስሜት ይኖራቸዋል፤ የሚያመጧቸውን ሀሳቦች ፍፁም አድርገው ያስባሉ፡፡
ትችትና አስተያየት መቀበል ይከብዳቸዋል እንደሚተገብሯቸው እርግጠኛ መሆን፡፡ የእንቅልፍ ፍላጎት መቀነስ፤ በፊት ከሚተኙበት ሰዓት ዘግይቶ መተኛትና ባልተለመደ ንቁ መሆን፤ ያልተለመደ
ወሬኛነት፤ ከማይግባቧቸውና ከማያቋቸው ሰዎች ጋር ጭምር
ያልተለመደ የማውራት ፍላጎት፤ ነገሮችን አብዝቶ ማቅለል፤ ደካማ ውሳኔ መስጠት ያስከትላል፡፡ የመሳስሉትን ምልክቶች የሚያሳዩ ሰዎች ሃይፖማኒያ ይባላል፡፡”
“ስለዚህ ዶክ፣ አንድ ሰው የተዘረዘሩት ምልክቶች በሙሉ ሊኖርበት ነው ይሄ ችግሩ አለበት ሚባለው?”
“ኖኖ! እንደዛ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ከላይ ከዘረዘርኳቸው ውስጥ፣ ሶስቱን ወይም ከዚያ በላይ ምልክቶች ካሳየና በሃኪም
ከተረጋገጠ ሃይፖማኒያ አለበት ልንል እንችላለን፡፡” በውስጤ አሰላሰልኩ፡፡ እነዚህ ስሜቶች ሶስቱ ሳይሆን ሁሉም ግዜ ጠብቀው፣እብደቴ ሲነሳ በደስታ ማስተናግዳቸው ሲሜቶች ናቸው፡፡
“ዶክ ከእነዚህ ስሜቶች አብዛኞቹ በተደጋጋ እኔን ሲስሙኝ ኖረዋል። ታዲያ ሃይፖማንያ ሳይሆን ለምን ባይፖላር አለብህ አልከኝ?”
ትክክል ነህ ያቤዝ፡፡ አንተ እነዚህ ስሜቶች ሲሰሙህ እንደከረሙ ነግረኸኛል፡፡ ነገር ግን፣ ሃይፖማንያ ሚባሉት እነዚህን
ስሜቶች ብቻ ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ አንተ ግን፣ እነዚህ ስሜቶች ብቻ አይደሉም ሲሰሙህ የነበረው፡፡ ሌላም ስሜቶች ነበሩህ፡፡”
“ሌላ ስሜትም ስትለኝ፣ ሌላ ምን አይነት ስሜት?"
“አንተ የሃይፖኒያ ስሜቶች ብቻ ሳይሆን የነበረህ፣ ግዜን ጠብቆ ሚፈራረቅ የስሜት ዝቅታ ወይም የዲፕረሽን ምልክቶችም ነበሩህ፡፡”
“የስሜት ዝቅታ /የዲፕረሽን/ ምልክቶችስ ምን ምን ናቸው?"
“የዲፕረሽን ምልክቶች የምንላቸው፤ ከፍተኛ ብስጭት፣ማህበራዊ መነጠል፣ ብቸኝነት ማብዛት፤ ከፍተኛ ምክንያት የለሽ የድካም ስሜት፧ የጡንቻ መዛል፤ ቁርጥማት፣ የጀርባ ህመም፤ የመረበሽ
ስሜት ፣ በስራ፣ በትምህርትና ቤተሰባዊ ሃላፊነቶች ከተገቢው በላይ መጨነቅ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፍላጎት መቀነስ፣ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የመዝናናት የፍላጎት ማጣት፣ እንዲሁም፣ የጥፋተኝነት ስሜቶች፣ ዋጋቢስ እና ተገቢ ያልሆነ ራስን መቅጣት፣ በራስ የመተማመን ስሜት መቀነስ፣ ደካማ እና የቀነሰ ትኩረት፣ አፍራሽ እና መጥፎ ሃሳቦችን በተደጋጋሚ ማሰብ፣ ራስን የማጥፋት አስተሳሰብ እና ራስን የመጉዳት ወይም ራስን የመግደል ሙከራዎች እና የመሳሰሉት ምልክቶች ካሉበት፤ የዲፕረሽን ችግር አለበት ይባላል”
እነዚህ የበሽታ ምልክቶች ከሆኑማ
ታምሜያለሁ፣ሲፈራረቁብኝ ኖረዋል፡፡ ነገር ግን፣ ብዙ ሰው እንደዛ ሚሰማው
ይመስለኛል፡፡ ሃኒ በአምሮዬ ውልብ አለች፡፡ ትበሳጭ ነበር፤ ትናደድ ነበር፤ ብቻዋን መደበቅ ፈልጋ ስትመጣ ነው የተገናኘነው፣ እራሷን አጥፍታለች። እና ሃኒም እንደኔ የዲፕረሽን ታማሚ ነበረች ማለት ነው?፣ እራሷን ለማጥፋት ያደረሳት ይህ ህመም አልባ በሽታ ነበር ማለት ነው?
“እና ዲፕረሽን አሁን ከጠቀስካቸው ምልክት ሶስቱን ማሳየት ማለት ነው?”
“አይደለም፡፡ ዲፕረሽን እንደ ሃይፖ ማንያ በሶስት ምልክት ብቻ አይደለም፡፡ ከእነዚህ ምልክቶች መካከል አምስቱን ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑት አንድ ስው ደጋግሞ ሲኖረውና የእለት ተለት ህይወቱን እንዳይመራ ተፅእኖ ሊኖራቸው ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህን በሽታዎች
ሃኪም ሳያማክሩ ምልክት በመቁጠር ብቻ እንዲህ ነኝ እንዲያ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ግን ምልክቶቹ ከተደጋገሙና ከቆዩ ሃኪም ማማከር አስፈላጊ ነው፡፡”
“እነዚህም ምልክቶች እኮ በደንብ እንደነበሩኝ ነግሬሃለው ዶክተር፡፡ ታድያ ለምን ዲፕረሽንም አለብህ አላልከኝም? ህይወቴን እዚህ ያደረሱት እኮ አሁን የጠቀስካቸው ምልክቶች ሲስሙኝ ነው። ያማል፣ያላምጣል፣ ያመነዥካል፣ ሞት እንደ ጣፋጭ መድሃኒት ይናፍቃ፡ ዶክ፣
ስለዚህ እኔ ያለብኝ ችግር እንደውም ዲፕረሽን ነው፡፡”
“አየህ ያቤዝ፣ ቅድም ለዛ ነበር ሃኪም ሳያማክሩ ምልክቶችን ቆጥሮ ይሄ ነው፣ ያ ነው ያለብኝ፣ ማለት አይቻልም ያልኩህ፡፡ አንተ የሃይፖማንያም የዲፕረሽንም ምልክቶች እየተቀያየሩብህ አሳይተሃል፡፡
አንድ ስው የሃይፖማንያ ምልክት ብቻ ካለው፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ ሃይፖማንያ አለበት ይባላል፤ የድባቴ ምልክቶች ብቻ ካሉበት፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ የድባቴ ችግር አለበት ይባላል፤ የሁለቱ በሽታዎች ምልክት እየተፈራረቁ ከተሰሙት ደግሞ፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ የባይፖላር ችግር አለበት ይባላል፡፡”
አሁን ለቀናት ሳነብ አልገለጥልህ ያለኝ ተገለጠልኝ፡፡ አይኔ በራ፡፡ዶክተር እያወራ ነው፡፡ “ባይፖላር ዲስኦርደር የዕድሜ ልክ ሁኔታ ቢሆንም፣ሕክምና በመከታተል የስሜት መለዋወጥን እና ሌሎች
ምልክቶችን በመቆጣጠርና መሰናክሎችን በማስቀረት በህይወት ስኬታማ መሆን ይቻላል፡፡ ባይፖላር
ዲስኦርደር በስነ ልቦና ምክር (ሳይኮቴራፒ)እና በመድኃኒቶች ይታከማል፡፡
በግማሽ ልቤ ነው ማዳምጠው፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ተወሽቄያለሁ።ወደኋላ ተመልሼ በሃሳብ እየተብሰለሰልኩ ነው፡፡ ዶክተር እውነቱን ነው::ቅድም የጠቀሳቸው ስሜቶች ብዙ ግዜ ተፈራርቀውብኛል። ባይፖላር ዲስኦርደር፣ በጋና ክረምት የሚመሰሉ ስሜቶች መፈራረቅን ተከትሎ
የሚመጣ የባህሪ መለዋወጥ ነው፡፡ በጋ፣ ብርሀን ነው ፧ ተስፋ ነው ፤ በጋ ሙቀት ነው ፤ ሀይል ነው፤ መቦረቅ ነው፡፡ ክረምት ግን፣ ብርድ ነው ፤መሸሸግ፣ መኮራመት ነው፡፡ አዎ! የኔ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
...“በጣም ጎበዝ ያቤዝ፡፡ ስለ አለብህ የጤና ችግር ለማውቅ መፈለግ በጣም ጉብዝና ነው፡፡ በተጨማሪም ብዙ ጥቅም አለው፡፡ ባይፖላር ዲስኦርደር ማለት፣ ሰዎች ሁለት የስሜት ዋልታዎች መፈራረቅን ተከትሎ፣ተደጋጋሚ የሚመጣ የባህሪ መለዋወጥ ሲያጋጥማቸው ነው።
መለዋወጦቹም፧ በስሜት ከፍታዎች እና በስሜት ዝቅታዎች መካከል የሚከሰት ነው:: በመሆኑም ይህ ችግር ያለበት ሰው፣ ባለበት የስሜት ከፍታ ወይም ዝቅታ መሰረት አሰተሳሰቡ፣ ውሳኔ አሰጣጡ፣ በነገሮች ላይ የሚኖረው ፍላጎት፣ ድርጊቶችን ለማድረግ የሚኖረው ሀይልና ጉልበት፣ በአጠቃላይ የህይወት አመለካከቱና አረዳዱ በሰዐቱ እንዳለው
የስሜት ሁኔታ የተለያየ ነው፡፡ በተጨማሪም፣ የዚህ ችግር ተጠቂ የሆኑ
ሰዎች ውስጣዊ ለውጦች ሊኖራቸው፣ አካባቢያቸው የተለወጠ ስለሚመስላቸው የሚሰጡት ምላሽ የተሳሳተ ሊሆን ይችላል፡፡
የዚህ ችግር ተጠቂዎች የስሜት ከፍታ ሲኖራቸው ማኒያ ወይም ሃይፖማኒያ ይባላል፡፡ ማኒያ ከሃይፖማኒያ ተመሳሳይ ምልክት ቢኖረውም፣ ማኒያ በህመም ደረጃው ከበድ ያለ በሽታ ነው፡፡ ይህ
የባህሪዎች መለዋወጥ፣ ችግሩ ያለባቸውን ሰዎች በስራ፣ በትምህርት፣
በማህበራዊ እንቅስቃሴያቸው እና ግንኙነቶቻቸው ላይ ችግሮች
ማወቅ እንዲከሰቱ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ የስሜት ከፍታ ላይ ሲሆኑ፤ በፊት
ብዙም ትኩረት ማይሰጡትን ጉዳይ የማየት፣ የመስማትና የማወቅ ፍላጎት መጨመርን ያሳያሉ፤ ከነበራቸው ማህበራዊ መግባባት የጨመረ
የመቀራረብና የመግባባት ባህሪ ያሳያሉ፣ የማይጨበጡ፣ ወይም
ቶሎቶሎ ሚቀያየሩ አዳዲስ ሀሳቦችንና ንድፎችን በማምጣት ያወራሉ፤አንድ ቦታና አንድ ሃሳብ ላይ በጥልቀት ማስብ ስለሚያስጨንቃቸው ቶሎ ከሃሳብ ወደ ሃሳብ ይቀያይራሉ፣ በጥቃቅን ነገሮች አክርረው ይጨቃጨቃሉ፣ ነገሮቹ ከነርሱ ህይወት ጋር ጠቃሚ ግንኙነት ባይኖራቸውም፣ ስለሚሰሟቸው ነገር ከፍተኛ የማወቅ ፍፈላጎት ያሳያሉ፤ ለነገሮች ከተገቢው በላይ ይናደዳሉ፣ ይበሳጨሉ፣ ከብሰጭት ስሜት መውጣት ይቸገራሉ፣ የተጋነነ በራስ የመተማመን ስሜት ይኖራቸዋል፤ የሚያመጧቸውን ሀሳቦች ፍፁም አድርገው ያስባሉ፡፡
ትችትና አስተያየት መቀበል ይከብዳቸዋል እንደሚተገብሯቸው እርግጠኛ መሆን፡፡ የእንቅልፍ ፍላጎት መቀነስ፤ በፊት ከሚተኙበት ሰዓት ዘግይቶ መተኛትና ባልተለመደ ንቁ መሆን፤ ያልተለመደ
ወሬኛነት፤ ከማይግባቧቸውና ከማያቋቸው ሰዎች ጋር ጭምር
ያልተለመደ የማውራት ፍላጎት፤ ነገሮችን አብዝቶ ማቅለል፤ ደካማ ውሳኔ መስጠት ያስከትላል፡፡ የመሳስሉትን ምልክቶች የሚያሳዩ ሰዎች ሃይፖማኒያ ይባላል፡፡”
“ስለዚህ ዶክ፣ አንድ ሰው የተዘረዘሩት ምልክቶች በሙሉ ሊኖርበት ነው ይሄ ችግሩ አለበት ሚባለው?”
“ኖኖ! እንደዛ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ከላይ ከዘረዘርኳቸው ውስጥ፣ ሶስቱን ወይም ከዚያ በላይ ምልክቶች ካሳየና በሃኪም
ከተረጋገጠ ሃይፖማኒያ አለበት ልንል እንችላለን፡፡” በውስጤ አሰላሰልኩ፡፡ እነዚህ ስሜቶች ሶስቱ ሳይሆን ሁሉም ግዜ ጠብቀው፣እብደቴ ሲነሳ በደስታ ማስተናግዳቸው ሲሜቶች ናቸው፡፡
“ዶክ ከእነዚህ ስሜቶች አብዛኞቹ በተደጋጋ እኔን ሲስሙኝ ኖረዋል። ታዲያ ሃይፖማንያ ሳይሆን ለምን ባይፖላር አለብህ አልከኝ?”
ትክክል ነህ ያቤዝ፡፡ አንተ እነዚህ ስሜቶች ሲሰሙህ እንደከረሙ ነግረኸኛል፡፡ ነገር ግን፣ ሃይፖማንያ ሚባሉት እነዚህን
ስሜቶች ብቻ ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ አንተ ግን፣ እነዚህ ስሜቶች ብቻ አይደሉም ሲሰሙህ የነበረው፡፡ ሌላም ስሜቶች ነበሩህ፡፡”
“ሌላ ስሜትም ስትለኝ፣ ሌላ ምን አይነት ስሜት?"
“አንተ የሃይፖኒያ ስሜቶች ብቻ ሳይሆን የነበረህ፣ ግዜን ጠብቆ ሚፈራረቅ የስሜት ዝቅታ ወይም የዲፕረሽን ምልክቶችም ነበሩህ፡፡”
“የስሜት ዝቅታ /የዲፕረሽን/ ምልክቶችስ ምን ምን ናቸው?"
“የዲፕረሽን ምልክቶች የምንላቸው፤ ከፍተኛ ብስጭት፣ማህበራዊ መነጠል፣ ብቸኝነት ማብዛት፤ ከፍተኛ ምክንያት የለሽ የድካም ስሜት፧ የጡንቻ መዛል፤ ቁርጥማት፣ የጀርባ ህመም፤ የመረበሽ
ስሜት ፣ በስራ፣ በትምህርትና ቤተሰባዊ ሃላፊነቶች ከተገቢው በላይ መጨነቅ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፍላጎት መቀነስ፣ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የመዝናናት የፍላጎት ማጣት፣ እንዲሁም፣ የጥፋተኝነት ስሜቶች፣ ዋጋቢስ እና ተገቢ ያልሆነ ራስን መቅጣት፣ በራስ የመተማመን ስሜት መቀነስ፣ ደካማ እና የቀነሰ ትኩረት፣ አፍራሽ እና መጥፎ ሃሳቦችን በተደጋጋሚ ማሰብ፣ ራስን የማጥፋት አስተሳሰብ እና ራስን የመጉዳት ወይም ራስን የመግደል ሙከራዎች እና የመሳሰሉት ምልክቶች ካሉበት፤ የዲፕረሽን ችግር አለበት ይባላል”
እነዚህ የበሽታ ምልክቶች ከሆኑማ
ታምሜያለሁ፣ሲፈራረቁብኝ ኖረዋል፡፡ ነገር ግን፣ ብዙ ሰው እንደዛ ሚሰማው
ይመስለኛል፡፡ ሃኒ በአምሮዬ ውልብ አለች፡፡ ትበሳጭ ነበር፤ ትናደድ ነበር፤ ብቻዋን መደበቅ ፈልጋ ስትመጣ ነው የተገናኘነው፣ እራሷን አጥፍታለች። እና ሃኒም እንደኔ የዲፕረሽን ታማሚ ነበረች ማለት ነው?፣ እራሷን ለማጥፋት ያደረሳት ይህ ህመም አልባ በሽታ ነበር ማለት ነው?
“እና ዲፕረሽን አሁን ከጠቀስካቸው ምልክት ሶስቱን ማሳየት ማለት ነው?”
“አይደለም፡፡ ዲፕረሽን እንደ ሃይፖ ማንያ በሶስት ምልክት ብቻ አይደለም፡፡ ከእነዚህ ምልክቶች መካከል አምስቱን ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑት አንድ ስው ደጋግሞ ሲኖረውና የእለት ተለት ህይወቱን እንዳይመራ ተፅእኖ ሊኖራቸው ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህን በሽታዎች
ሃኪም ሳያማክሩ ምልክት በመቁጠር ብቻ እንዲህ ነኝ እንዲያ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ግን ምልክቶቹ ከተደጋገሙና ከቆዩ ሃኪም ማማከር አስፈላጊ ነው፡፡”
“እነዚህም ምልክቶች እኮ በደንብ እንደነበሩኝ ነግሬሃለው ዶክተር፡፡ ታድያ ለምን ዲፕረሽንም አለብህ አላልከኝም? ህይወቴን እዚህ ያደረሱት እኮ አሁን የጠቀስካቸው ምልክቶች ሲስሙኝ ነው። ያማል፣ያላምጣል፣ ያመነዥካል፣ ሞት እንደ ጣፋጭ መድሃኒት ይናፍቃ፡ ዶክ፣
ስለዚህ እኔ ያለብኝ ችግር እንደውም ዲፕረሽን ነው፡፡”
“አየህ ያቤዝ፣ ቅድም ለዛ ነበር ሃኪም ሳያማክሩ ምልክቶችን ቆጥሮ ይሄ ነው፣ ያ ነው ያለብኝ፣ ማለት አይቻልም ያልኩህ፡፡ አንተ የሃይፖማንያም የዲፕረሽንም ምልክቶች እየተቀያየሩብህ አሳይተሃል፡፡
አንድ ስው የሃይፖማንያ ምልክት ብቻ ካለው፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ ሃይፖማንያ አለበት ይባላል፤ የድባቴ ምልክቶች ብቻ ካሉበት፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ የድባቴ ችግር አለበት ይባላል፤ የሁለቱ በሽታዎች ምልክት እየተፈራረቁ ከተሰሙት ደግሞ፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ የባይፖላር ችግር አለበት ይባላል፡፡”
አሁን ለቀናት ሳነብ አልገለጥልህ ያለኝ ተገለጠልኝ፡፡ አይኔ በራ፡፡ዶክተር እያወራ ነው፡፡ “ባይፖላር ዲስኦርደር የዕድሜ ልክ ሁኔታ ቢሆንም፣ሕክምና በመከታተል የስሜት መለዋወጥን እና ሌሎች
ምልክቶችን በመቆጣጠርና መሰናክሎችን በማስቀረት በህይወት ስኬታማ መሆን ይቻላል፡፡ ባይፖላር
ዲስኦርደር በስነ ልቦና ምክር (ሳይኮቴራፒ)እና በመድኃኒቶች ይታከማል፡፡
በግማሽ ልቤ ነው ማዳምጠው፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ተወሽቄያለሁ።ወደኋላ ተመልሼ በሃሳብ እየተብሰለሰልኩ ነው፡፡ ዶክተር እውነቱን ነው::ቅድም የጠቀሳቸው ስሜቶች ብዙ ግዜ ተፈራርቀውብኛል። ባይፖላር ዲስኦርደር፣ በጋና ክረምት የሚመሰሉ ስሜቶች መፈራረቅን ተከትሎ
የሚመጣ የባህሪ መለዋወጥ ነው፡፡ በጋ፣ ብርሀን ነው ፧ ተስፋ ነው ፤ በጋ ሙቀት ነው ፤ ሀይል ነው፤ መቦረቅ ነው፡፡ ክረምት ግን፣ ብርድ ነው ፤መሸሸግ፣ መኮራመት ነው፡፡ አዎ! የኔ
👍3😁1
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አቤል ወላጆቹን ትቶ ወደ ትዕግሥት በሐሳቡ መጓዝ ስለጀመረ ዐይኑን ቦዘዝ እንዳደረገ ዝም አለ ።
ምነው ? ”አሉ ዮናታን ፥ አንዳች ስሜቴን የሚጎዳ ነገር የተናገሩ መስሎአቸው ተደናግጠው ። ሐሳባቸው ዘሎ
ያረፈው እናቱ ወይም አባቱ ሞተዋል ከሚል ግምት ላይ ነበር ። ይህን ደግሞ ከአሁን በፊት አልነገራቸውም ፡ ግራ ተጋቡ።
“ ምንም አይደለም ”አላቸው ከሐሳቡ ባነነና ። እርስዎ ለእኔ ያለዎት ክብርና ፍቅር እየታሰበኝ ነው ።ለእኔ መድከምዎ አንሶ ወላጆቼን ሊረዱልኝ ሲያስቡ ... ”
“ ይህ ውለታ ሆኖ ካሳሰበህ ተሳስተሃል ” አሉት ዮናታን “ይህ ማንኛውም ዜጋ ሊያደርገው የሚገባ ነገርም ነው ። ማስተማር ለእኔ ግዴታ ሳይሆን ፥ የመንፈስ ክብርና ኩራት የሚሰጠኝ መስክ ነው ። እናም ጥሩ ተማሪዬን ጥሩ
ቦታ ወይም የሙያ ዘርፍ ላይ ለማየት እንጂ የማስተማር ግዴታዩን ለመወጣት ብቻ አይደለም የማስተምረው ። መረዳዳት ያስፈልጋል ። ደግሞም አጥብቀን አናስበውም እንጂ
ከመረዳዳት ውጪ የሆነ እንቅስቃሴ ምን ታገኛለህ ? ሁሉም የግል ጎጆ ቢቀልስም፡ የሕይወት እንቅስቃሴው የጋራ ነው። ማኅ
በረሰብ ከሌለ ግለሰብ የሚባል ነገር የለም " ምኑን ከምን አርጎ ሊንቀሳቀስ ? ነገሩ ይህ ሆኖ ሳለ ከግል ኑሮአችን በመነሳት የምናደርገው፥ ማኅበራዊ ግንኙነት ከመረዳዳት እንጻር
አጉልተን አናየውም እንጂ ኑሮአችን በመረዳዳት የተሳሰረ ነው።
ዮናታን ከልባቸው እየተመሰጡ ንግግራቸው እየጎላና እየረቀቁ ሲሔድ ፥ የአቤልን እንባ አደረቀው ። አፉን ከፍቶ
ነበር የሚያዳምጣቸው ።
“እሺ እንግዲህ 'እንዳሉት 'አሁን ያለኝ ምርጫ ትምህርቴን ማቋረጥ ነው ። እናም አቋርጠዋለሁ ” አለ የሜዝት
በሚመስል ጉልህ ድምፅ "
«« አዎ ! ቆራጥነት ያስፈልጋል አሉ ዮናታን
“ቆራጥ ካልሆንክና ውሳኔ መውሰድ ካልቻልክ ሕይወትህ የተመሰቃቀለ ይሆንብሃል ። አብዛኛውን ጊዜ ሕይወት የባለ ቤቷን ቆራጥነት ትፈታተናለች የቆራጥነትና ወሳኝነት ትርጉም የሚገባህ ውጤቱን ካየህ በሁዋላ ነው ። አይዞህ
በአንተም ሆነ በወላጆችህ ላይ የሚደርስ ጊዜያዊ ችግር ቢኖር በጋራ እንወጣዋለን አንተም ነገ ትልቅ ሰው እንደምትሆን
አትጠራጠር ። ”
በፊት ያንዣብብ የነበረው የጭንቀት ደመና ከአቤል ፊት ሳይ እየጠፋ መሔዱን ሲመለከቱ ዮናታን ደስታ ተሰማቸው
ጥረታቸው ዋጋ እንዳገኘ እድርገው ገመቱ።
“ እሺ ፤ ለማቋረጥ የሚያስፈልጉኝን ነገሮች ላሟላ ”ብሎ አቤል ከተቀመጠበት ተነሣ ።
“ ግሩም ! ” አሉ ዮናታን ሐሳቡን በመደግፍ ለማቋረጡ ተግባር የምረዳህ ነገር ካለ ብቅ ብለህ አማክረኝ ፡
አቤል እጅ ነሥቶ ሲወጣ በቆራጥነት ስሜት ግንባሩን አኮማትሮ ነበር ። በሐሳቡ የታየው ነገር ይህን “ የሥቃይ
ግቢ ” በአስቸኳይ ለቅቆ መውጣት ብቻ ነበር ። አንድ የሆነ ተቃራኒ ስሜት ጭንቅላቱን ቢከብደውም እስኪወጣ ድረስ ቀውል አልተከሠተለትም ።
ዮናታን ከደስታቸው ብዛት የሚይዙ የሚለቁትን አትተው ፊታቸው የተቀመጡትን ወረቀቶች ያለ ምንም ዓላማ ወዲያ ወዲህ ያገላብጡ ጀመር ፡ አቤል ሐሳባቸውን መቀበሉን የመጀመሪያው ደረጃ አድርገው ወሰዱት የዕቅዳቸው መጀመሪያ እንደ ተሳካ አድርገው በመገመት በጥረታቸው ረኩ ።
“ እሺ እንግዲህ ፡ ትምህርቱን አቋረጠ ። ከዚያ በኋላስ ምን መደረግ አለበት?” በማለት ዮናታን ፥ አቤልን ከተጠመደበት የዐይን ፍቅር ሕመም ለማዳን የሚቀጥለው ደረጃ ምን መሆን እንዳለበት ማሰብ ጀመሩ ። ይህን ሐሳብ በማውጣትና በማውረድ ላይ እንዳሉ በሩ ተከፈተ ።
ቀና ሲሉ አቤል ነው ፊቱ ከስሏል ዐይኖቹ ቀልተዋል በሆነ ስሜት ከራሱ ጋር የተጣላ ይመስላል ከኋላ እንደ ተባረረ ሰው እየቻኮለ ነበር በሩን የከፈተው።
ይቅርታ ያድርጉልኝ ለምን እንደ ዋሸሆዎት አላውቅም። ምናልባት ፈርቼዎት ይሆናል ትምህርቴን ማቋረጥ የለብኝም ብሞክርም አልችልም አላቸው ወደ ውስጥ ሳይገባ በሩ ላይ ቆሞ።
ዮናታን ግር አላቸው ምን ሰይጣን ነው በአንዴ ሐሳቡን ያስቀለበሰው ለጊዜው
የሚመልሱትም ሆነ የሚጠይቁት ነገር እልነበራቸውም።
አቤል ሐሳቡን የቀየረው በሩን ወጥቶ ገና ጥቂት እንኳን ሳይራመድ ነው ። ክፍል ውስጥ ሆኖ ከዮናታን ጋር ሲስማማ ከውስጡ ሲጫጫነውና ሲከብደው የነበረው ተቃራኒ ስሜት ገና ከመውጣ እውነት አሁን ትምህርትህን አቋርጠክ ይህን ትእግስት ያለችበትን ግቢ ልትለቅ ነው? እውነት ከትእግስት ጋር ሳትተያይ ውለህ ማደር የምትችል ይመስልሃል?
የዐይን ፍቅረኛህን ትተህ የት ልትደርስ? እያለ እንደ ጥላ ተከተለው ። አቋርጣለሁ እያለ ቀድሞ ሲፎክር የነበረው ሁሉ ባዶ ጩህት ሆኖ አገኘው ትእግሥትን ጥሎ
ወዴት ?
ለዮናታን ቃል መግባታ አሳዝነው ። እንዴት እንደሚያስተባብላቸወ በማሸበ ቆሞ ተጨነቀ። ሆኖም ዮናታን ያቋርጣል በሚል ተስፋ ልባቸውን ሞልተው እንዳይቀመጡ ቶሎ ተመልሶ ማስተባበል
ነበረበት እራሱን እየረገመ ነው የተመለሰው ምነው? ተስማምተን አልሔድክም እንዴ? ምን ነካህ? ” አሉት ዮናታን በተደናገጠ ስሜት።
አዎ በሃሳቦዎ ተስማምቼ ነበር የወጣሁት ነገር ግን አርቄ ሳስባት ፈተና ተፈትኜ ዕድሌን መሞከር አለብኝ ?” አላቸውና መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ ሔደ።
«ስማኝ እንጂ አቤል ! ቆይ እስቲ ?” አሉት ዮናታን ከተቀመጡበት ተነስተው ሊከተሉት እየሞከሩ ዝም ብሏቸው ካጠገባቸው መጭ አለ።
ዮናታን በብስጭት ፈዘው ቀሩ ለሰም ሰው እኔ ምን አስጨነቀኝ ? ” የሚል ተፈታታኝ ሐሳብ መጣባቸው
ተስፋ የመቁረረጥ ስሜት ተስማቸው አኳኋኑ አናደዳቸው ግን ሁኔታን ባስታወሱ ጊዜ ልባቸው ሊጨክን አልቻለም ። እድራጎቱ አንድም የልጅነት አሊያም የፍቅር ቡሶት ነው ደመደሙ።
ቢሮእቸውን ቆልፈው ቀጥታ ወደ አቶ ቢልልኝ ቢሮ አመሩ አረማመዳቸው የሩጫ ያህል ነበር ። በመንገዳቸው
ላይ ሦስት ያህል የሚያውቋቸው ሰዎች ሰላምታ ሳይሰጡ ማለፋቸው አልታወቃቸውም።
ከከባቢልልኝ ቢሮ እንደ ደረሱ ሰላምታ እንኳን ሳይለዋወጡ አረእስተ ጉዳያቸውን አነሱ።
«ቢልልኝ የዚያን ልጅ ጉዳይ ሁላችሁም ቸል ማለታችሁ ነው ?
አቶ ቢልልኝ ! የዮናታን አርእስቱ ስለ አቤል ጉዳይ መሆኑ ለመገመት ጊዜ አልወሰደባቸውም።
የአቤልን ነገር ነው ?...ችላ ማለት አይደለም ኮ እኔ በበኩሌ የዐቅሜን እየመበከርኩ ነው። ሆኖም የልጁ ሁንታ
አስቸኳይ መፍትሔ የሚገኝለት አልሆነም።
"እንዴት ? ” አሉ ዮናታን ፡ ለመቀመጥ ወንበሩን እየሳቡ።
እስቸኳይ መፍትሔ ለማግኘት ልጁ ምቹ አይደለም ቢልልኝ ወደ ጉዳዩ ጠልቀው ሲገቡ ፊታቸው እየተለዋወጠ አዎ አቤል ግልጽ አይደለም ። አንዳንዱ ሰው ሰላፈቀራት ሴት ላገኘው ሰው ሁሉ በየደቂቃው ካላወራ አይሆንለትም ፤ ሌላ አርዕስት የለውም ። ሁሌ ሰው ለሰ
ፍቅር መፍትሔ የሚፈልግለት ይመስለዋል አንዳንዴ ደግሞ ለማንም ሳያዋይ ፍቅሩን ራሱ ዋጥ አርጎ ውስጥ ውስጡን
መቃጠል ይመርጣል ። ሌላ ሰው ለሱ ፍቅር ጤናማ አመለካከት ያለው አይመስለውም የአቤል በደረጃ ከመለየቱ በቀር ይሄኛውን ይመስላል ሁሉም አይነት ግን አስተዳደግና አካባቢን የተመረኮዘ መሠረት ይኖረዋል።
"ታዲያ አሁን የአቤል ነገር እንዴት ይሻላል ?” አሉ ዮናታን ፥ በተጨነቀና በተቻኮለ ስሜት ።
“ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ መፍትሔ ያገኛል ” አሉ ቢልልኝ፡ “ ጊዜ ! ጊዜ ይወስዳል ። የሥነ ልቡና ጥናት
ሥራ ዘዴና ትዕግሥት ይጠይቃል አቤል ፥ ሌላው ቀርቶ የግል የሕይወት ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ አልሆነም
ስለዚህ ሥራችን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አቤል ወላጆቹን ትቶ ወደ ትዕግሥት በሐሳቡ መጓዝ ስለጀመረ ዐይኑን ቦዘዝ እንዳደረገ ዝም አለ ።
ምነው ? ”አሉ ዮናታን ፥ አንዳች ስሜቴን የሚጎዳ ነገር የተናገሩ መስሎአቸው ተደናግጠው ። ሐሳባቸው ዘሎ
ያረፈው እናቱ ወይም አባቱ ሞተዋል ከሚል ግምት ላይ ነበር ። ይህን ደግሞ ከአሁን በፊት አልነገራቸውም ፡ ግራ ተጋቡ።
“ ምንም አይደለም ”አላቸው ከሐሳቡ ባነነና ። እርስዎ ለእኔ ያለዎት ክብርና ፍቅር እየታሰበኝ ነው ።ለእኔ መድከምዎ አንሶ ወላጆቼን ሊረዱልኝ ሲያስቡ ... ”
“ ይህ ውለታ ሆኖ ካሳሰበህ ተሳስተሃል ” አሉት ዮናታን “ይህ ማንኛውም ዜጋ ሊያደርገው የሚገባ ነገርም ነው ። ማስተማር ለእኔ ግዴታ ሳይሆን ፥ የመንፈስ ክብርና ኩራት የሚሰጠኝ መስክ ነው ። እናም ጥሩ ተማሪዬን ጥሩ
ቦታ ወይም የሙያ ዘርፍ ላይ ለማየት እንጂ የማስተማር ግዴታዩን ለመወጣት ብቻ አይደለም የማስተምረው ። መረዳዳት ያስፈልጋል ። ደግሞም አጥብቀን አናስበውም እንጂ
ከመረዳዳት ውጪ የሆነ እንቅስቃሴ ምን ታገኛለህ ? ሁሉም የግል ጎጆ ቢቀልስም፡ የሕይወት እንቅስቃሴው የጋራ ነው። ማኅ
በረሰብ ከሌለ ግለሰብ የሚባል ነገር የለም " ምኑን ከምን አርጎ ሊንቀሳቀስ ? ነገሩ ይህ ሆኖ ሳለ ከግል ኑሮአችን በመነሳት የምናደርገው፥ ማኅበራዊ ግንኙነት ከመረዳዳት እንጻር
አጉልተን አናየውም እንጂ ኑሮአችን በመረዳዳት የተሳሰረ ነው።
ዮናታን ከልባቸው እየተመሰጡ ንግግራቸው እየጎላና እየረቀቁ ሲሔድ ፥ የአቤልን እንባ አደረቀው ። አፉን ከፍቶ
ነበር የሚያዳምጣቸው ።
“እሺ እንግዲህ 'እንዳሉት 'አሁን ያለኝ ምርጫ ትምህርቴን ማቋረጥ ነው ። እናም አቋርጠዋለሁ ” አለ የሜዝት
በሚመስል ጉልህ ድምፅ "
«« አዎ ! ቆራጥነት ያስፈልጋል አሉ ዮናታን
“ቆራጥ ካልሆንክና ውሳኔ መውሰድ ካልቻልክ ሕይወትህ የተመሰቃቀለ ይሆንብሃል ። አብዛኛውን ጊዜ ሕይወት የባለ ቤቷን ቆራጥነት ትፈታተናለች የቆራጥነትና ወሳኝነት ትርጉም የሚገባህ ውጤቱን ካየህ በሁዋላ ነው ። አይዞህ
በአንተም ሆነ በወላጆችህ ላይ የሚደርስ ጊዜያዊ ችግር ቢኖር በጋራ እንወጣዋለን አንተም ነገ ትልቅ ሰው እንደምትሆን
አትጠራጠር ። ”
በፊት ያንዣብብ የነበረው የጭንቀት ደመና ከአቤል ፊት ሳይ እየጠፋ መሔዱን ሲመለከቱ ዮናታን ደስታ ተሰማቸው
ጥረታቸው ዋጋ እንዳገኘ እድርገው ገመቱ።
“ እሺ ፤ ለማቋረጥ የሚያስፈልጉኝን ነገሮች ላሟላ ”ብሎ አቤል ከተቀመጠበት ተነሣ ።
“ ግሩም ! ” አሉ ዮናታን ሐሳቡን በመደግፍ ለማቋረጡ ተግባር የምረዳህ ነገር ካለ ብቅ ብለህ አማክረኝ ፡
አቤል እጅ ነሥቶ ሲወጣ በቆራጥነት ስሜት ግንባሩን አኮማትሮ ነበር ። በሐሳቡ የታየው ነገር ይህን “ የሥቃይ
ግቢ ” በአስቸኳይ ለቅቆ መውጣት ብቻ ነበር ። አንድ የሆነ ተቃራኒ ስሜት ጭንቅላቱን ቢከብደውም እስኪወጣ ድረስ ቀውል አልተከሠተለትም ።
ዮናታን ከደስታቸው ብዛት የሚይዙ የሚለቁትን አትተው ፊታቸው የተቀመጡትን ወረቀቶች ያለ ምንም ዓላማ ወዲያ ወዲህ ያገላብጡ ጀመር ፡ አቤል ሐሳባቸውን መቀበሉን የመጀመሪያው ደረጃ አድርገው ወሰዱት የዕቅዳቸው መጀመሪያ እንደ ተሳካ አድርገው በመገመት በጥረታቸው ረኩ ።
“ እሺ እንግዲህ ፡ ትምህርቱን አቋረጠ ። ከዚያ በኋላስ ምን መደረግ አለበት?” በማለት ዮናታን ፥ አቤልን ከተጠመደበት የዐይን ፍቅር ሕመም ለማዳን የሚቀጥለው ደረጃ ምን መሆን እንዳለበት ማሰብ ጀመሩ ። ይህን ሐሳብ በማውጣትና በማውረድ ላይ እንዳሉ በሩ ተከፈተ ።
ቀና ሲሉ አቤል ነው ፊቱ ከስሏል ዐይኖቹ ቀልተዋል በሆነ ስሜት ከራሱ ጋር የተጣላ ይመስላል ከኋላ እንደ ተባረረ ሰው እየቻኮለ ነበር በሩን የከፈተው።
ይቅርታ ያድርጉልኝ ለምን እንደ ዋሸሆዎት አላውቅም። ምናልባት ፈርቼዎት ይሆናል ትምህርቴን ማቋረጥ የለብኝም ብሞክርም አልችልም አላቸው ወደ ውስጥ ሳይገባ በሩ ላይ ቆሞ።
ዮናታን ግር አላቸው ምን ሰይጣን ነው በአንዴ ሐሳቡን ያስቀለበሰው ለጊዜው
የሚመልሱትም ሆነ የሚጠይቁት ነገር እልነበራቸውም።
አቤል ሐሳቡን የቀየረው በሩን ወጥቶ ገና ጥቂት እንኳን ሳይራመድ ነው ። ክፍል ውስጥ ሆኖ ከዮናታን ጋር ሲስማማ ከውስጡ ሲጫጫነውና ሲከብደው የነበረው ተቃራኒ ስሜት ገና ከመውጣ እውነት አሁን ትምህርትህን አቋርጠክ ይህን ትእግስት ያለችበትን ግቢ ልትለቅ ነው? እውነት ከትእግስት ጋር ሳትተያይ ውለህ ማደር የምትችል ይመስልሃል?
የዐይን ፍቅረኛህን ትተህ የት ልትደርስ? እያለ እንደ ጥላ ተከተለው ። አቋርጣለሁ እያለ ቀድሞ ሲፎክር የነበረው ሁሉ ባዶ ጩህት ሆኖ አገኘው ትእግሥትን ጥሎ
ወዴት ?
ለዮናታን ቃል መግባታ አሳዝነው ። እንዴት እንደሚያስተባብላቸወ በማሸበ ቆሞ ተጨነቀ። ሆኖም ዮናታን ያቋርጣል በሚል ተስፋ ልባቸውን ሞልተው እንዳይቀመጡ ቶሎ ተመልሶ ማስተባበል
ነበረበት እራሱን እየረገመ ነው የተመለሰው ምነው? ተስማምተን አልሔድክም እንዴ? ምን ነካህ? ” አሉት ዮናታን በተደናገጠ ስሜት።
አዎ በሃሳቦዎ ተስማምቼ ነበር የወጣሁት ነገር ግን አርቄ ሳስባት ፈተና ተፈትኜ ዕድሌን መሞከር አለብኝ ?” አላቸውና መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ ሔደ።
«ስማኝ እንጂ አቤል ! ቆይ እስቲ ?” አሉት ዮናታን ከተቀመጡበት ተነስተው ሊከተሉት እየሞከሩ ዝም ብሏቸው ካጠገባቸው መጭ አለ።
ዮናታን በብስጭት ፈዘው ቀሩ ለሰም ሰው እኔ ምን አስጨነቀኝ ? ” የሚል ተፈታታኝ ሐሳብ መጣባቸው
ተስፋ የመቁረረጥ ስሜት ተስማቸው አኳኋኑ አናደዳቸው ግን ሁኔታን ባስታወሱ ጊዜ ልባቸው ሊጨክን አልቻለም ። እድራጎቱ አንድም የልጅነት አሊያም የፍቅር ቡሶት ነው ደመደሙ።
ቢሮእቸውን ቆልፈው ቀጥታ ወደ አቶ ቢልልኝ ቢሮ አመሩ አረማመዳቸው የሩጫ ያህል ነበር ። በመንገዳቸው
ላይ ሦስት ያህል የሚያውቋቸው ሰዎች ሰላምታ ሳይሰጡ ማለፋቸው አልታወቃቸውም።
ከከባቢልልኝ ቢሮ እንደ ደረሱ ሰላምታ እንኳን ሳይለዋወጡ አረእስተ ጉዳያቸውን አነሱ።
«ቢልልኝ የዚያን ልጅ ጉዳይ ሁላችሁም ቸል ማለታችሁ ነው ?
አቶ ቢልልኝ ! የዮናታን አርእስቱ ስለ አቤል ጉዳይ መሆኑ ለመገመት ጊዜ አልወሰደባቸውም።
የአቤልን ነገር ነው ?...ችላ ማለት አይደለም ኮ እኔ በበኩሌ የዐቅሜን እየመበከርኩ ነው። ሆኖም የልጁ ሁንታ
አስቸኳይ መፍትሔ የሚገኝለት አልሆነም።
"እንዴት ? ” አሉ ዮናታን ፡ ለመቀመጥ ወንበሩን እየሳቡ።
እስቸኳይ መፍትሔ ለማግኘት ልጁ ምቹ አይደለም ቢልልኝ ወደ ጉዳዩ ጠልቀው ሲገቡ ፊታቸው እየተለዋወጠ አዎ አቤል ግልጽ አይደለም ። አንዳንዱ ሰው ሰላፈቀራት ሴት ላገኘው ሰው ሁሉ በየደቂቃው ካላወራ አይሆንለትም ፤ ሌላ አርዕስት የለውም ። ሁሌ ሰው ለሰ
ፍቅር መፍትሔ የሚፈልግለት ይመስለዋል አንዳንዴ ደግሞ ለማንም ሳያዋይ ፍቅሩን ራሱ ዋጥ አርጎ ውስጥ ውስጡን
መቃጠል ይመርጣል ። ሌላ ሰው ለሱ ፍቅር ጤናማ አመለካከት ያለው አይመስለውም የአቤል በደረጃ ከመለየቱ በቀር ይሄኛውን ይመስላል ሁሉም አይነት ግን አስተዳደግና አካባቢን የተመረኮዘ መሠረት ይኖረዋል።
"ታዲያ አሁን የአቤል ነገር እንዴት ይሻላል ?” አሉ ዮናታን ፥ በተጨነቀና በተቻኮለ ስሜት ።
“ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ መፍትሔ ያገኛል ” አሉ ቢልልኝ፡ “ ጊዜ ! ጊዜ ይወስዳል ። የሥነ ልቡና ጥናት
ሥራ ዘዴና ትዕግሥት ይጠይቃል አቤል ፥ ሌላው ቀርቶ የግል የሕይወት ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ አልሆነም
ስለዚህ ሥራችን