አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
575 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#አርፋጅ

አንድ ሰፈር ነው ያደግነው፡፡ አንድ ዩኒቨርስቲ ተማርን። ብሩክ ፈታ ያለ ነው፣ ጨዋታ ያደምቃል፣ ጨዋታም ያውቃል። እሱ ካለ የሳቅ ድምጽ አይጠፋም። ስድስተኛ ክፍል አልፈልግህም ተብሎ የተላከለትን ደብዳቤ አባቱ አግቶበት
የመታውን ጠረባ፣ ለፍቺም ደርሰህልኛላ እያለ የሚጦልበውን ጡለባዎችን እየቀመመ ሲያጫውት አፉን ከፍቶ የማይስቅ አልነበረም።

ታላቅ ወንድሙ ላይ የሚሠራውን ተንኮል፣ የግድያ ሙከራ የሚመስሉ ድብደባዎችን ኮስተር ብሎ በፌዛም ፊቱ እያወጋ ያዝናናን ነበር። ግሬድ ሲሰቅልም፣ ሲሾቅም ማላገጡ የሚጠበቅ ነው። በዙሪያው የማንጠፋው ፍሬንዶቹ ላይ እንዳይደብረን አድርጎ ለጨዋታ ፐርፐዝ ብቻ ይቀልድብናል።

ብሩክ እንደ ጃካራንዳ ዛፍ በዙሪያው ሚያጅበው አይጠፋም፣ ሰው ይወደዋል። ከሰው ጋ እይጋጭም፣ መከባበር የማይደራደርበት ዋነኛ ፖሊሲው እንደሆነ በደንብ የሚቀርበው ሁሉ ያውቃል፣ የጠበቀ ወዳጅነት ያለን ደግሞ በይበልጥ እናውቃለን።

ብሩክ ለእኔ ወንድሜ ነው የማልለው ባልጀራነትን ማሳነስ ስለሚመስለኝ ነው። ብዙ ሳቅ እና ጭንቀቶችን ተጋርተናል። በድዬ ሳለሁ ለእኔ አግዞልኛል፣ እስከ ድክመቱ ተቀብየዋለሁ፤ ጓደኛዬ ነው፣ ምንም ሳይኖረን ጊዜ ብቻ እያለን ነው ነፍሳችን የተናበበው፤ የጓደኝነት ትርጉም መተንተን ሳንጀምር ነው የተወዳጀነው።

እኔ ታላቅ ወንድሜ የጀመረውን ቢዚነስ ተቀላቅዬ በሂደት ብዙ ሳንቲም ማግበስበስ ጀመርኩ። ብዙ ሀብት ባገኘሁ ቁጥር መፍጨርጨሬ ጠነከረ፣ ነገሮችን በውሎዬ ስለምመዝን እነጫነጫለሁ፣ ብሩክ ነገሮችን ከእሱ አንጻር ስለሚያይ መነጫነጬ አይገባውም።

ብሩክ ቀልደኝነቱ መፍዘዝ ጀመረና መገለጫው ያልሆነ ጨለምተኝነት ወረሰው። ምሬቱን ቀልቤን ሰብስቤ አሰላስዬ አላውቅም፣ መንገዱን ለመደልደል አልጣርኩም። ከእጮኛው ጋ የሚያጋጥመውን ግጭት በምሬት ሲነግረኝ ቀልቤን ሰብስቤ ከጊዜያዊ ስሜት የገዘፈ ይሆናል ብዬ አላሰብኩም።

የድሃ ልጅ መሆኑ፣ አይዞህ የሚለው አለመኖሩን ሲጠቅስ አብሬው ከማሸብሸብ የዘለለ ጊዜ ሰጥቸው ምን ላግዘው? ከእኔ ምን ይጠበቃል? ብዬ ለአፍታ አሰላስዬ አላውቅም።

እድገት ላይ በመመሰጤ ያሉኝን በረከቶች ለማስተዋል አልተቻለኝም ነበር። ያሉንን እየጣልን የምናመጣው አዲስ ስኬት እንደምን የምንፈልገውን ደስታ ሊያመጣልን ይቻለው ይሆን??

ለሥራ ኔትወርክ የማይሰራበት ቦታ ከርሜ ስመጣ እንድንጠጣ፣ እንድንስቅ ደወልኩለት ግን ስልኩ ዝግ ነው። ደጋግሜ ደወልኩ፤ አሁንም ስልኩ ዝግ ነው። ስልክ ማጥፋት፣ ስልክ አለማንሳት፣ ለብቻው መሆን አዲስ ያመጣው ፋሽኑ መሆን ጀምሯል። ቤቱ ልሄድ ተነሳሁ።

ፀሐዩ ሀሩር ነው፤ ዘንድሮ ፀሐዩን ለማምለጥ እንደዝናብ መጠለል እና መሮጥ መጀመራችን አይቀርም። የድሮ ሰፈሬ ደረስኩ፣ የነ ብሩኬ ደጅ ላይ ድንኳን ተደኩኗል፤ ብሩኬ አያቱ ጠንካራ ሕመም እያንገላታቸው እንደሆነ ነገሮኝ ነበር።

አያቱ በሕይወቱ ደማቅ ስፍራ አላቸው፤ ይወዳቸዋል፡፡ እንደ ወንድሙ ነበር የሚያዋራቸው፣ እንደ ጓደኛቸው ነበር የሚያጫውቱት። ከልጅነት ጀምሮ የምናቀውን ሰው ማጣት ሕመሙ ብርቱ ነው። ድብርት እና ምሬት ሳይጣባው አያቱ ሳይተኙ ለመድረስ ነበር የሚሮጠው።

እርምጃዬን ቀስ እያደረኩ ወደ ድንኳኑ ስሄድ የሰፈራችን ለቀስተኞች አይን እኔ ላይ አረፈ፣ አጎነበስኩ። ቀስ ብዬ የድንኳኑ መግቢያ በር ላይ ያገኘሁት ወንበር ላይ ቁጭ አልኩ፣ በቀስታ ቀና ብዬ ብሩኬን በአይኔ ሳስሰው ወንበርተደርድሮ በተቀመጠ ፍራሽ ላይ የደከሙ አያቱን አየኋቸው፤ ፍጥጥ ብዬ እንዳየኋቸው አስታውሳለሁ።

ከአጠገባቸው እናቱን አየኋት፣ በጥሩ መንፈስ አላየችኝም፤ አይኔ ወደ ተሰቀለው ፎቶ ተምዘገዘገ። ከዛ ሰዓት በኋላ የሆነውን ብዙ አላስታውስም። ለቀበሌ መታወቂያ ብሎ አብረን ሄደን የተነሳነው የብሩኬ ፎቶ ተሰቅሏል። በጣም እንደጮህኩ አስታውሳለሁ፤ እናቱን ሂሩቴን እየወደቅኩ፣ እየተነሳሁ የሆነውን ለመጠየቅ ፍራሹ ጋ ለመሄድ መሞከሬንም አልረሳሁትም። የሆነውን ሁሉ ፡ አለማወቄ ተገለጸላቸው፡፡ ረጭ ያለው ለቅሶ ቤት ታወከ፤ ሁኔታዬ ያሳዘናቸው ሰዎች አብረውኝ ያለቀሱ ይመስለኛል።

አያቱን አንቄ ጋሽ በላይ ጓደኛዎት የት ሄደ፣ ብሩኬ የት ሄደ? አልኳቸው። በዛለ እጃቸው አቅፈውኝ በትኩስ እንባ ታጅበው እጁን በእጁ በላ አሉኝ። እግሬ አልጸና ያለ ይመስለኛል፤ ብዙ ሰዎች ያዙኝ፤ ክንዴን ክንዴን ብዬ ጮህኩኝ፤ ሰው ለካ እንዲህ ደካማ ነው፤ የቻልኩት መጮህ እና የሆነውን መካድ ነበር።

በቀን ብዛት ተበረታታሁ ያወራነውን ሳሰላስለው ኋላ መቅረት ሲንጠው እንደነበር ገባኝ። ጨለምተኝነቱ ለመኖር ያለውን ፍላጎት ቀድሞ እንደገደለበት ገባኝ። ለካስ ማስተዋል አቅቶኝ ነው እንጂ ሁሉም ነገሩ ይገባ ነበር። አብረን ብንሆንም ለካ ተለያይተን ነበር፤ ለካ እሱ ነበር ጓደኛዬ እንጂ እኔ ጓደኛው አልነበርኩም። አናቱ ላይ በፍጥነት የወረረውን ሽበት ከ"stress"፤ ከመብሰልሰል የተፈጠረ መሆኑን አልጠረጠርኩም ነበር።

ተሳክቶለታል የምባለው እኔ ነገሮች ሲጠሙብኝ፣ አንዳንድ ነገሮች ሲከፉብኝ ይቺ ዓለም እንደምትሰለቸኝ አውርቼው አላውቅም።

ራሴን ልገድለው እንደነበር ነግሬው አላውቅም። ሽራፊ ፈገግታ በሀሩር ፀሐይ ጤዛ እንደመፈለግ ሆኖብኝ ሳለ፣ የሞከርኩት ሙከራዎች ሲከሽፉ፣ ከሰው ሁሉ አነስኩኝ ስሜቴ ሲበላኝ፣ ብቻ መሆን ሲጨፍርብኝ፣ አለመፈለግ ስሜት ሲወዘውዘኝ፣ ያለኝን ነገር ሁሉ ያፈሰስኩበት ተስፋዬ ሲጠፋ፣ ሕልሜ ሰፍቶኝ ስንከላወስ፣ የምሸሸግበት ጥግ ሳጣ፣ በማምነው ሰው ስካድ፣ ዕድለቢስነት እንዳልጠራጠር አድርጎ ሲመሰክርብኝ ራሴን ልገለው ዳድቶኝ ነበር። መዳዳቴን እንዴት ድል እነደነሳሁት ሳልነግረው!

አምላኬ ጋር ሙጥኝ እያልኩ፤

አንዳንዴ በረከቶቼን ፈልፍዬ ለራሴ እየተረኩ፣

አንዳንደ ጭላንጭል ብርሃኔ ላይ ተመስጬ፣

ብሞት የምሰብራቸውን ሰዎች አዝኜላቸው።

አንዳንዴ ክችች ያልኩበትን ጉዳይ እያላላሁ፣ አንዳንዴ ግትርነቱን እየገሰጽኩ፣ አንዳንዴ ሆስፒታል ያሉ አካላቸው የማይታዘዝላቸው ነፍሶችን እየረዳሁ፣ አንዳንዴ እስረኞችን እየጠየቅኩ ነው ራሴ ላይ የራራሁት ሳልለው
ይሄ ትግሌ ለብሩኬ ትርጉም ሊሰጠው እንደሚችል ማሰብ አልተቻለኝም ነበር። የምንወዳቸውን ሰዎች ምን ያህል እንደምንወዳቸው ካለ እጦት እንዴት መረዳት ያቅተናል? ለራስ ሰው አለመድረስን ያህል አርፋጅነት የለም።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
38😢13👍11
#እግዜር_አደራውን_ሲበላ

ግርግር ከማይወዱ ጓደኞቼ ዛብሎን አንደኛው "ነው። እይታዎቹ በወፍ በረር የተኮረጁ አይደሉም፤ ስለማያውቀው ነገር ከተወራ ይሰማል ረጋ ብሎ ስለሚያወራ፣ ስለሚያውቀው ነገር ብቻ ስለሚያወራ እያዳመጠ ስለሚያወራ፣ መናገር .. ሲጀምር የማይሰማው የለም።

ጨዋታው ብዙ ሰው ላይ ያለው እመነኝ፣ ቅዱስ ነኝ ዓይነት ስብከት የለበትም።

ክላስ አለው!!

አጠገቡ ያለ ሰው ስለማያውቀው ነገር ሲቀባጥር፣ ዛብሎን ደግሞ ስለጉዳዩ በደንብ እውቀት ካለው ለስለስ አድርጎ ቀባጣሪው የቀባጣሪነት ስሜትን ሳያሳድርበት ደርበብ ባለ መልኩ ሐሳቡ ላይ ብቻ አተኩሮ ሙግት ውስጥ ሳይገባ ስለሚያውቀው ነገር ይናገራል። እንደዚህ ዓይነት ግለሰብ ሰውዬው የበታችነት ሳይሰማው፣ አላዋቂነት ሳይታገለው የያዘውን መረጃ አልያም አቋም እንዲመረምር ያስችላል።

ዛብሎን ጺሜ አደገ፣ ጸጉሬ ተንጨባረረ ብሎ ጸጉር ቤት እንደማይሄድ የጸጉሩ መንጨባረር እና የጺሙ መንዥርገግ ምስክር ናቸው። ዘናጭ አይደለም ግን ንፁሕ ነው። ከሁሉ የሚገርመኝ ካላሳቀው አይስቅም። በጋራ ተሰብስበን ሁላችንም እየሳቅን በእርጋታ ሳቃችን እስክንጨርስ ጠብቆ በትንሽ ፈገገግታ አልገባኝም ብሎ ስለሳቅንበት ነገር ማብራሪያ ይጠይቃል፤ ተጨብጭቦለታል ብለን ለምናጨበጭብ ሰዎች አጀብ ነው ይሄ፡፡

ካፌ ውስጥ እንደተቀመጥን ዛብሎን አስተናጋጇን በምልክት ጠራትና መጥታ

'ምን ልታዘዝ'

"ተቆራጭ አምጭልኝ" አስናጋጇ ስትሄድ ጠብቄ

የገና ጾም አትጾምም እንዴ?

“አልጾምም!“

ለምን?

“እናቴ ስትሞት ነው ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር ያለኝ ቁርኝት የተፋታሁ፤ ተስፋ ቆረጥኩ፣ የምለፋበት ምክንያት አጣሁኝ። ድሮ ቤተክርስትያን ስሄድ ነጭ ሐበሻ ቀሚስ የለበሱ፣ ሹርባ የተሠሩ እናቶች ሳይ፣ ሥራ ስይዝ ለእናቴ እንዲህ እገዛለሁ እለው ነበር እግዚአብሔርን። ቆርበው ከቤተክርስትያን በር ላይ መኪና የሚጠብቃቸው እናቶችን ሳይ እኔ ለእናቴ እንዲህ እንደምንሆን ለእግዚአብሔር ፈገግ እያልኩ አጫውተው ነበር። ስማር እንቅልፌ እየመጣ እግሬን ውሃ ውስጥ ዘፍዝፌ የማጠናው ከእግዜር ጋር የተጨዋወትነውን ምኞቴን ለማሳካት ነበር። እሱ እኮ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ነው የሚለው እያልኩ።

ሱሰኛ ያልነበርኩት እናቴ ልጄ እኮ እንደዚህ ዓይነት ነገር አይወድም፤ የእኔ ልጅ እኮ ብላ እንድትጎርር ነበር። ሕልሜን ከእናቴ ጋ ብቻ ማቆራኘት አልነበረብኝም። ግን እኮ ወድጄ አይደለም፤ ቤተሰቦቿ አረገዝሽ ብለው ሲያባርሯት፣ አባትየው ሲክዳት፣ ምድረ በዳ ላይ ተነጥሎ እንደቀረ ሰው እኔን አገሯ፣ ዓለሟ አድርጋ የተዋደቀችልኝ ናት"

ፊቱ ቅዝቅዝ አለ... ትኩስ እንባ አይኑ ላይ ቅርርር ሲል አየሁ። ከዚህ በፊት አስተውየዋለሁ፤ ስለ አምላክ ሲወራ አስተያየት አይጎጥም። በቤተክርስቲያን ስናልፍ በእጃችን እያማተብን ከጉልበታችን ሸብረክ ስንል እሱ ግን ልክ መንገድ ላይ የምናውቀውን ሰው አግኝተን ሰላም ስንል ስለማያውቀው ብቻ እልፍ ብሎ እንደሚሄደው ልክ እንደሱ አልፎ ይሄዳል።

ውለታ የዋለለትን ሰው የእግዜር ስምን እያጠቀሰ ሲመርቀው አሜን አይልም። ተመጽዋች ምጽዋት ሲጠይቀን ከሌለን እኛ እግዜር ይስጥልን እንላለን ወደ እሱ ዞሮ ሲለምነው የለኝም ይላል።

እግዚአብሄሩን አኩርፎት እንደሆነ ካስተዋልኩ ቆየሁ። በዙሪያው የሚያፈቅረው የለም፤ አለማፍቀሩ ከፍቅር ሾልከው የሚመጡ ስጋት፣ ተስፋ እና ስስት የሚባሉትን ከውስጡ አሽሽቶለታል። አንድ ቀንም ለእግዜር ስሞታም፣ ውዳሴም ሲያቀርብ አይቼው አላውቅም። ዝም ብዬ ሳየው በለሆሳስ ብቻውን ከእግዚአብሄሩ ጋር የሚዋቀስ ነው የሚመስለኝ።

ሳየው በዝምታ እግዜሩን ለምን አደራኽን በላህ የሚለው ነው የሚመስለኝ!!!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
28🤔8👍1
#ኀሰሳችን_ከሽፎ_እንጂ

ጥዑም ጊዜ ላይ ነበርን። ወይን እየተጎነጨን፣ እየተሳሳምን፣ ድንገት ሳላቅድ፣ ሳልቀምር፣ ሳላስብበት ከአንደበቴ የውስጤ እውነት አመለጠኝ፡፡

ትክ ብዬ ሳያት ፈገግ ብላ “እችን የመሰለች ልጅ ጠበስክኣ?" አለችኝ ወደ ራሷ እያመለከተች፤ በትንሹ ፈገግ አልኩ። ፈገግታዬን እንደ መስማማት ቆጥራ በሚያምር ፈገግታዋ እያየችኝ "እናትህማ መርቀውሃል" ስትለኝ ይሄኔ ነበር የልቤ እውነት ያመለጠኝ።

ታውቂያለሽ ግን አንቺ ሕልሜ እንዳልሆንሽ፤ የመጣሽበት መንገድ፣ ዕቅድሽ፣ መርሕሽ ከእኔ ጋ መች ይሄዳል? አልኳት።

ሽማግሌ ከላክሁኝ በኋላ፣ በጋራ ስለምንወልዳቸው ልጆቻች ስናወራ ከርመን እንዴት እንዲህ ይባላል? ሁሉ እውነት እንዴት ይወራል? የልብ እውነት ሁሉ ይዘረዘራል?! ትበሳጫለች ብዬ ነበር ግን ደግሞ የጠበኩትን የፊት መለዋወጥ አላየሁም። ረጋ እንዳለች፣ ፊቷ ሳይለዋወጥ ትክ ብላ አየችኝ፤ ቅፍፍፍ የሚል  ስሜት ዋጠኝ፤ ምን አለ አስማተኛ በሆንኩ እና እንዳልሰማች ማድረግ አልያም እንዳልተናገርኩ መሆን ብችል።

ቃላቱን እርግጥ አድርጋ

“ትክክል!! ጊዜው አሳዝኖን ነው አብረን የሆነው፤ አብረን ሆነን በስሱ ሌላ የፍለጋ ሙከራ ስላልተሳካልን ነው የምንጋባው። አንዲት ቀን 'Messenger ህን ከፍቼ አይቻለሁ፡፡ የምታወራቸውን እንስቶች ቀልብ ለመግዛት የምትሄድባቸውን መንገዶች፣ መሻፈዶች፣ ላጤ ነኝ ጨዋታዎች፣ ብልግናዎች ተመልክቻለሁ፤ ሁሉም ከእኔ ጋ አንድ ዓይነት ነበሩ። የማደርገውን ነበር የምታደርገው፤ ከፍቶኝ ነበር እንዳላኮርፍ፣ እንዳልጨቀጭቅህ፣ እንዳልጣላህ ካንተ አለመሻሌ አሸማቀቀኝ። የብዙ ሰዎች ትዳር እንዲህ እንደሆነ አይቻለሁ፤ ከገቡ በኋላ በልጆቻቸው ይጽናናሉ፤ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሚስትና እና ባላቸውን እየከሰሱ ኑሮን ይገፉታል።

ለዛ ነው እንከን የለሽ ትዳር የሚያስሱት ቆመው የሚቀሩት! በቆዩ ቁጥር መለኪያቸውን እየቀየሩ ካጣጣሉት፣ ከተጠየፉት የኑሮ ቀንበር ላይ ራሳቸውን ያገኙታል። ለዛ ነው እንደሚታረድ በግ ሁሉን እያወቅኩ ሽማግሌ ስትልክ፣ ቀለበት ስታጠልቅልኝ፣ የልቤን እውነት አፍኜ የምከተልህ።"

ሲዘበራረቅብኝ ይታወቅኛል። ግራ ገባኝ፤ የሕይወት አጋርን በዚህ ደረጃ አለማወቅ ምን ይባላል? እችን ልጅ ነገሮች በዚህ ደረጃ ይገባታል ብዬ አላሰብኩም። ሴት ልጅ ትታልልህልሀለች እንጂ አታታልላትም እኔ እንዲህ እንደሚሰማኝ እንጂ እሷ እንደዚህ እንደሚሰማት አላውቅም ነበር።

ለምን ታድያ አብረን እንሆናለን ሁለታችንም እንዲህ
ከተሰማን?

"እንሂድ"

ምን አልባት ጊዜያችን፤

ምን አልባት ዕድሜያችን አሳዝኖን?

ምን አልባትም በዙሪያችን ያለ ውትወታ?

ምን አልባት ዘራችንን ለመተካት ካለን ፍላጎት?

ምን አልባት መላመዳችን እንዳንለያይ አግቶን ይሆን?

ምን አልባት አንዳችን ለአንዳችን ካለን ውስጣዊ ስሜት ይሆን?

ምን አልባት በዙሪያችን ካሉት ሰዎች የበለጠ ስለምንዋደድ??

ምን አልባት በስሱ ሌላ ለማግኘት ያሰስነው ኀሰሳ ስላልተሳካ??

ሰው የልቡን ሁሉ አለማውጣቱ ይሆን ቁርኝታችንን
ያላሳደፈው? ባለጋራችንን አለማወቅ ጠቀሜታ ይኖረው ይሆን? አንዳንድ ዕውቀት ምቾት አይሰጥም። ዕውቀት ትካዜን ታበዛለች እንዲል መጽሐፉ፤ አንዳንድ ውይይቶች ሽንቁር ያበጃሉ። የጀመርኩትን ወይኔን በአንድ ትንፋሽ ወደ ጉሮሮዬ አንቆረቆርኩት።

እንደዚህ ዓይነት ሎጂክ ተዘባዝቦ ግንኙነት፣ ትዳር መመሥረት ይቻል ይሆን? እንዳለችው ፍርሀት ነው? እጦት ነው? መላመድ ነው? ምንድን ይሆን በትክክል ያጋመደን?

ምን አስቸኮለን? ምን አሸበረን? ይሄን እውነታ ከተዘራዘሩ በኋላ እንዴት ጎጆ ይቀለሳል? ልጅ ሳይመጣ፣ ንብረት ሳናፈራ፣ ኑሮ ሳይንጠን የግንኙነታችንን መዓዘን መገምገም እንዳለብን ነው የገባኝ። አሁን የምጎዳት ነገ ከምሰብራት አይበልጥም፤ ዛሬ የሚሰማኝ ሕመም ነገ ከሚጋረጥብኝ መከራ አይበልጥም።

ማሬዋ ሰው ውድ ፍጡር ነው። ችኮላችን ብልጣብልጥነታችን፣ በራሳችን ማስተዋል መንጠልጠላችን የእኛ የራሳችን የሆኑት ሰዎች ጋ አንድንሸዋወድ ያደርገናል። ጊዜ እንውሰድ፣ ተነጣጥለን ዙሪያችንን፣ መንገዳችንን እንመርምር፤ ብልግናችንን ይቅር እንበለው። የቆምንባቸውን ስፍራዎች እንቃኛቸው፣ ከፈጸምናቸው ጥፋቶች ጋ እንፋጠጥ፣ እናርማቸው፣ እናበጃጃቸው። ብቸኝነት አባብቶን፣ አቻ ግፊት ወትውቶን፣ መላመድ አሳስሮን፣ የቤተሰብ ግፊት ገፈታትሮን ኑሮ አይመሰረትም። የሁሉም ጓዳ እንዲህ ነው ተብሎ አዲስ ጎጆ አይበጅም፤ ሁሉም ሄዷል ተብሎ እንኳን በስሕተት መንገድ በትክክለኛ መንገድ መሄድ ተገቢ አይደለም።

ከመጣንበት መንገድ የምንሄድበት ሩቅ ነው። ራሳችንን ከእርስ በእርሳችን ነጣጥለን እናጢነው። የአሰተውሎት መንገድ ደግሞ አሜን ካልነው ባሻገር ያለውን እውነታ መጋፈጥን ይጨምራል።

ያኔ የውስጣችን እውነት ፍንትው ብሎ ይታየናል፤ ለውሳኔም ይረዳናል። ስሕተታችንን ለማረም ከፍርሀት ጋ መጋፈጥ የመጀመሪያው እርምጃ ነው።

ከዚህ ሁሉ መንገድ በኋላ መመለስ እንዳስፈራት ታስታውቃለች። እኔም የወጠንኩትን፣ የለመድኩትን፣ የወሰንኩትን ዳግም ለመመርመር እና ለመከለስ ሳስብ ደስስ የማይል የሚቀረዝዝ ስሜት ሲወረኝ እየተሰማኝ ነው።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
29👍3
በየደቂቃው ከጭንቅላቴ የሚፈልቀውን ዝባዝንኬ ሳላስቀር፣ በአጠገቤ ውል ያለውን ሳይቀር ነበር የምተነፍስለት። እንዳልቆም አድርጎ ያፍረከረከኝ፤ ያሳለፍነውን፣ ያገዘፍኩትን ነገር አንድ ሳይቀር ነው አሳንሷት የሄደው፡፡ ትረካ የሌለው መለያየት፣ ውጣ ውረድ የሌለው ፍቺ፣ የማይተነፈስ ሕመም ለማይታይ ጠባሳ ይዳርጋል፡፡ እንዴት በዚህ መጠን ተራ ይሆናል? እንዴት እየተፍለቀለቅሁ የምተርከውን ትዝታዬን እንደዚህ ያባክነዋል?

እንዴት ጥሩ ምክንያት አይፈበርክም?

እንዴት አካሄዱን ወዝ አያላብሰውም?

በዚህ መጠን ተራ አድርጎኝ እንዴት ይሄዳል? ያውቅ የለ ማን እንዳሳደገኝ፤ ለክብሬ ለግንኙነታችን ያለኝን ቦታ እያወቀ።

እችን ብቻ ነበር የምናክለው?

አብረን ስንሆን የእኔ ነው ብዬ አይደል እርቃኔን የተንጎማለልኩት?

የነበረን ነገር ቢያይል አይደለ ድክመት እና ስጋቴን መግለጼ?

ያሳለፍነውን ውብ ጊዜያት ካለጥንቃቄ በአካሄዱ ተረማምዶበት ነው ያናወዘኝ፣ እንጂ'ማ መለያየት ተፈጥሯዊም አይደል? ነፍስስ ኵስጋ ይለይ የለ? መሄዱ አይደለም፣ አካሄዱ ነው መላቅጡ የጠፋ ዱካክ ውስጥ የዘፈቀኝ።

አወዳደቃችን ውስጥ የጠያችን ግዝፈት እና ተራነት አሻራ በጉልህ አለ፡፡ ምን አለ አለሳልሶ ቢጥለኝ? ምን አለ ሲተወኝ ይሉኝታ ቢስ ባይሆን፡፡ አብረን በነበረን ጊዜ እንደምወደው እያንዳንዱ ዳናዬ ምስክር ነበር። ሰው ለሚወደው አይደለም ላሸነፈው ጠላቱ እንኳ ይራራ የለ?

ምን አለ ራርቶልኝ ቢሆን...

ምን አልባት እኮ የእኔ ብቻዬን የመሆን ፍርሀት ሲያርደኝ መለማመጤን አይቶ ነው ለእኔ ያለው ስሜቱ የተከለለበት፤ ምን አልባት ከእኔ የተሻለ ሰው አግኝቶ በእጁ እስኪያረጋት ወረት አውሮት ነው።

ምን አልባት እንዲህ መሙለጭለጭ ማንነቱ ይሆን ይሆናል። እሱ እንዳልሄድበት ከመጣው መንገድ በላይ እኔስ አልሄድኩም? ለእናቴስ የጀመርኩትን የደበቅኋት፣ የማትወደውን የሆንኩት ነገ ስነግራት አታፍርብኝም ብዬ አይደል? ከራስ ሰው ጋ መንዘላዘል ትዝታውም ሁኔታውም ይጣፍጣል ብዬ አይደል ከእናቴ የዘወትር ስጋት ራሴን ጥዬ ያገኘሁት?

ይሂድ! መሄዱ አይደለም ያጎሳቆለኝ!

ይሄ ማለቂያ የሌለው የምን አልባት ጉዞ ነው ከሰውነት ተራ ያወጣኝ። ምን አልባት ቃል ገድፌ የማይወደውን ብዬ፣ ወይ ምን አልባት ያልዋልኩበትን ነግረውት ይሆን? ወይ የሆንኩትን አገዛዝፈው አሻክረውት ይሆን? ይሄ እና ሌሎች የምን አልባት መላምቴ ነው ጭንቅላቴን ያጣበበው፤ እንዲህ እንደባተልኩ አልቀርም፤ እረሳዋለሁ። ያኔ እዚህ የዘራውን እዛ ሲያጭድ መሰስ እያለ ይመጣል፤ ያኔ የእኔን የምን አልባት የመላምት ችንካርን ይቀምሰዋል።"

ተሾመ ረጋ ብሎ ነበር የሚመለከተኝ። ሶልያና ያለችውን ሳነብ አንዱም ቃል አልለሰለሰኝም። ልቤን የጥፋተኝነት ስሜት ሸቀሸቀኝ። እያነበብኩ እንባዬ ሲንከባለል ተሾመ ተረጋግቶ ከመቀመጥ በቀር ምንም አላደረገም። ስቃይህ ከስቃይዋ አይበልጥም ብሎ ይሆናል።

ሶልያና ሕመሟን ከመቼ ጀምሮ ነው እንዲህ ለሰው ማጋራት የጀመረችው? አንዳንድ በደል የሌለንን ማንነት እና ባሕሪ ይወልዳል ማለት ነው።

አለሌ ብሆንም ስንቴ እየወደድኩ ተትቻለሁ፤ እየለመንኩ ተረግጫለሁ፤ ከእኔ የተሻለ ጋ ሄዳለች ብዬ ናፍቆቴን ፊት ነስቻለሁ። ጭር ያለ ስፍራ ተሸጉጬ አልቅሻለሁ። በሌላ አሳብቤ ተነጫንጫለሁ። ስንት ጓደኛ ሽምግልና ልኬያለሁ፤ የኔ ያድርጋት ብዬ ጸልያለሁ፤ አለመፈለጌን ለመርታት አነቃቂ ንግግር ሰምቻለሁ፤ ሴት እንዲህ ነች ብዬ ተቦትርፌያለሁ። ጥላኝ ማን ጋ እንደሄደች እያሰብኩ አርሬያለሁ።

ቃሏን እያጣቀስኩ ከስሻለሁ፤ ናፍቄ ረግሜያታለሁ። ይሄ እንዲህ ሆኖ ሳለ የሚወዱትን በገዛ ፍቃድ እንደመተው ያለ ሕመም ግን የትም የለም!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢209
#አንዲት_ዕድሜ_ለስንት_ትሆናለች

በጨዋታችን መሀል "ባል ፈልግልኝ" አለችኝ ምን ዓይነት? አልኳት።

“ጥሩ ፀባይ ካለው ይበቃኛል።" የምሯን እንደሆነ ሁለ ነገሯ ይናገራል። ጉጉቷ አንጀቴን በላው።

ፍቅረኛ ኖሮሽ ያውቃል? አልኳት።

ጥያቄውን ለማለስለስ ስታገል በደረቁ ወጣብኝ።

“ዛሬ ነገ እያለ ሕልሙ ላይ ተመስጦ ድክመቴን እያጎላ፣ እያሳጣ ከዛሬ ነገ እንጋባለን እያለ ቀኔን ዕድሜዬን በልቶ ተልካሻ ምክንያቶችን ጠቃቅሶ ተለየኝ። አሁን ሌላ ከእኔ በአስር ዓመት የምታንስ ጉብል አግብቶ ወልዶ ይኖራል"

ምናለ ...

ካልወደድካት፣ ካላገባሃት ብትተዋት፤ ቀኗን ባታኝከው! ውበቷ ሳይደበዝዝ፣ የከጀለችውን አማርጣ በጊዜዋ ታግባ፡፡ ጊዜ ለሴት ልጅ ከወንድ ልጅ የበለጠ ትርጉም አለው።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍199🥰2
    ዓይንሽ እሳት ሳቅሽ እሳት እጀሽ እሳት
ታዲያ ምን ይገርማል ባንቺ ቃል ብሳሳት?
    አይንሽ ውኃ ሳቅሽ ውኃ እጀሽ ውኃ
  ታዲያ ምን ይገርማል ብሆንሽ አምሀ?
    በጋና ክረምቱ ዝናብና ውርጩ
ሳቅሽ ነው እላለሁ የአቡሻኽር ምንጩ?
                     እሰይ...

             ከቤቴ እወጣለሁ
             ከደጄ እወጣለሁ
            ዶፍ ይውረድ በላዬ
     ሳቅሽ እንደዝናብ ካሳደገኝ ብዬ ፡፡

            ደስታ ሲያስገመግም
             ሰኔ ሲያስገመግም
   ዮም ፍሰሐ ኮነ በኤልያስ ግርግም፡፡

ወረደልህ  ቢሉኝ ደመና በክስተት
    ዘነበልህ ቢሉኝ ወለላና ወተት
ሲደመም ቢኖርም እግዜርን ላመነው
            ታዲያ ለኔ ምነው
ሳቅሽ ተነጥሎ ተዓምር የሆነው?

             ስንት ለመዘነ
             ስንት ለፈተነ

ሲደመም ቢኖርም እግዜርን ላመነው
           ታዲያ ለኔ ምነው
ሳቅሽ ተነጥሎ ተዓምር የሆነው?

            ስንት ለመዘነ
            ስንት ለፈተነ
  ስንት ለወጠነ ለኔ አይነት አለቃ
ከዚህ ሁሉ ሜዳ እንዴት እጅሽ በቃ?

ሞትም ባንቺ ፉጨት አልሰማም ካልጠራኝ ህይወት ባንቺ ፉጨት አልሰማም ካልጠራኝ
    እስኪ ጠይቂልኝ ካንቺ እንደሰራኝ !!!

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
13👍1
#አይሸጥም

እቤቴ ሊጠይቀኝ የመጣ ሁሉ፤ አጠገቤ ያለ ባለ ፎቅ ሁሉ፤ ባጋጣሚ የሚደልል እና በድለላ የሚኖርበት ሁሉ፤ ዘመድ አዝማድ ሁሉ፤ የመኖርያ ቤቴን ስፋት ከሰፈራችን መዘመን እና ከቦታ ዋጋው መናር ጋር እያስተያዩ “አትሸጪውም?” ይሉኛል፡፡

ብሸጠው የማገኘውን ሰምቼው የማላቀውን ገንዘብ መጠን ይነግሩኛል መልሴ ሳላወጣ ሳላወርድ አንድ ነው እሱም አ ል ሸ ጠ ው ም ብቻ እነሱ ግን ከመወትወት ሰንፈው አያቁም። አንዳንዱ “እሺ እማማ እርሶ ይሄን ያህል ይበሉን እና እንግዛዎት” ይሉኛል፤ ግን የእውነት... አክሱም ወይ ላሊበላ አልያ ደግሞ ፋሲለደስ በስንት ቢሸጥ ያዋጣል? ታሪክ ይሸጣል?

ይሄ ግቢ እኮ ባሌ ሽኮረመመ ጃጰማኘ ያጣጣምንበት፤ ፍቅር የዘራንበተ፤ፍቅር ያጨድንበት የተጨቃጨቅንበት የተኮራረፍንበት የተመካከርንበት ያቀድንበት ያዘንበት የሳቅንበት የወለድንበት ስፍራ ነው።

ይሄ ስፍራ እኮ የጸነስኩት ልጆቼ ያሳደኩበት፤ ልጆቼ ፀሐይ ያሞኩቅበት፤ ልጆቼን የገረፍኩበት፤ ልጆቼን ያስታረቅኩበት ልጆቼን የዳኘሁበት እዚህ ግቢ እዚ ቤት ነው!!

ቤትሽን ሽጭልኝ የሚሉኝ መስሏቸው ነው? አይደለም! ታሪክሽን ነው ልግዛሽ ያሉኝ! ይሄ ስፍራ ለኔ ጥዑም የትዝታዬ መዓዛ የሚያውደኝ ቦታ ነው፡፡ ከዋናው Vila ጎን ከዛ ከምትታየው ጥንጥዬ ክፍል ተነስተን ተካሰን ተበድረን ታግለን ነው ያስፋፋነው!!

አቅም የሆነኝ፣ የሕይወት ጣዕም ያልተሟጠጠብኝ ትላንቴ ላይ ተተክዬ ነው፡፡ ትላንትሽን ሽጭልኝ ነው የሚሉኝ፤ እኔ ከትላንቴ ውጪ ምን አለኝ?? እዚ እረጭ ያለ ግቢ ውስጥ የልጆቼ የጨቅላነት፣ ጩኸት እና የጨዋታቸው ጫጫታ ይሰማኛል፡፡

ይሄ ቤት ልክ እንደ ዋርካ ሥራሥር ትዝታዎቼ ውስጥ ጠልቋል። ጠዋት ጠዋት በሬ ላይ ቁጭ ብዬ የምሞቀው ፀሐይ ከየትም ስፍራ ካለችው ፀሐይ የበለጠ ምቾት አላት።

ከቤቴ ውስጥ ልጆቼን፣ ባሌን የማያስታውሰኝ የትኛው የቤት ክፍል ነው? የትኛው የግቢዬ ጠርዝ ይሆን?

የቱም!

ትላንቷ ላይ ለከተመች አሮጊት ታድያ ይሄ ምን ያህል ገንዘብ ይተካላታል?

ለዚህ ነው ትላንቴን የማልሸጠው!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
32👏4
#አንተ_የሌለህ_ጊዜ

ተማሪ እያለን ለብዙ ጊዜ የፍቅር ሕይወትን ተጋርተናል፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላ፣ ትልቅ ሰው ከሆንን፤ የተለያየ የሕይወት መሥመር ውስጥ ከሰመጥን፣ አጀንዳዎቻችን ከተቀየሩ፣ ፍላጎት እና ሕልማችን ሌላ ከሆነ በኋላ በድንገተኛ ግጥምጥሞሽ ሥራ አገናኘን፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ ከብዙ ዓመታት በኋላ ስንገናኝ አድገን፣ በስለን ስለነበረ የወዳጅነት ሰላምታ ሰላም ተባባልን፡፡ ሁለታችንም አይናችን የጣት ቀለበት ሲያስስ ተገጣጠምን፤ ሁለታችንም አግብተናል። ያገናኘን ሥራ ላይ ተጠመድን፣ ደጋግሞ ሥራ አገናኘን፤ ደጋግመን 'email' ተለዋወጥን።

አንድ ቀን ማኪያቶ እየጠጣን ከላይ ከላይ እየተጨዋወትን በሕይወቷ ስላለፈችበት ፈታኝ ጊዜ ማወቅ ፈለግሁ። ለምን የመጣችበትን አስቸጋሪ ሕይወቷን ለማወቅ እንደፈለግኩ አላውቅም።

የህይወትሽ አስቸጋሪ ጊዜ መቼ ነበር አልኳት?

አየችኝ፤ በትንሹ ፈገግ አለች፤ ፈገግ ስትል ዲምፕል አላት፤ ጥርሶቿ እንደ ድሮው ያምራሉ። ከፊት ለፊት በግንባሯ የመጡትን ዘለላ ጸጉሮቿን በቄንጥ ወደኋላ መለሰቻቸው።

ዝም ብዬ ስመለከታት...

“አንተ የሌለህ ጊዜ። ማለቴ የተውከኝ ለታ" አለችኝ። ስትቀልድ መስሎኝ ሳቅሁ። “እማ ትሙት" አለችኝ። በእናቷ ምላ ዋሽታ አታውቅም፡፡ ግርምቴን መደበቅ አልቻልኩም፤ ሁለ ነገሬ ጆሮ ሆነ

አየኋት

“ያ ጊዜ ላልበሰለችው ሄርሞን ፈታኝ ጊዜዋ ነበር። እወድህ ነበር፤ እያንዳንዱ ነገሬ ከአንተ ጋ ተሳስሮ ነበር። ውጤት መጣልኝ፣ ክፍለሀገር ተመደብኩኝ፤ ምክንያቱን ባላወቅኩት ምክንያት ራቅከኝ፤ ሁሉ ነገር ላይ ስልጣን የሰጠኸኝ ልጅ ገሸሽ ስታደርገኝ የማደርገው ጠፋኝ። በጨቅላ ጭንቅላቴ ቀልብህን እንደ ድሮ ወደ እኔ ለመመለስ ባተልኩ፤ ግን አልሆነም።

ወደ ተመደብኩበት ዩኒቨርስቲ ወደፊት መራመድ እንደመብረር እየከበደኝ ሄድኩ። ቀልቤን፣ ሳቄን ትቼ ነበር የሄድኩት። አዲስ ቦታ መልመድ ለእኔ ቀላል እንዳልሆነ ታውቃለህ፤ ሁሉ ነገሬን ላንተ እንደማነበንብ ታውቃለህ። ስላ'ንተ ለሁሉ እንደማወራ ታውቃለህ፤ ጓደኞቻችን ሁሉ የጋራ ነበሩ። ዶርም ሜቶቼ ለሚያወሩት ቋንቋ ባዳ ነበርኩ፤ አብሮነታቸው ሲደራ ባይተዋርነት አራቆተኝ፤ የማይወዱኝ ይመስለኛል።

“የካምፓስ ምግቡ አልተስማማኝም፤ አዲስ ዩንቨርስቲ በመሆኑ ሁሉም ነገር ገና ነበር፡፡ ናፍቆት ገላዬን በላው። ምግቡ ስለማይስማማኝም ብዙ አልበላም። ሰለልኩ፤ የጨጓራ ሕመም ጨፈረብኝ"

መቼ ደውለሽልኝ ታውቂያለሽ? በእኔ የምታውቂው ሰው ሆኖ ማን አለ ያልዘጋሽው? አልኳት ኮስተር ብዬ!

“እንደማትፈልገኝ ሁሉ ነገርህ ይናገር ነበር፤ ስልክህ ረጅም ሰዓት ይያዛል፤ በፍጥነት ተቀያየርክ፤ ለስሜቴ መጠንቀቅ አቆምክ። እንደቀለልኩብህ ድርጊትህ ይናገር ነበር። አንተ ላይ ስልጣን አልባ እንደሆንኩ አሳየኸኝ። ነገሮችን ለማስተካከል በአፍላ ጭንቅላቴ ተፍጨረጨርኩ። ጓደኞቼ ሊሰሙኝ እንጂ መንገድ ለማሳየት ጥበብ እና ልምዱ አልነበራቸውም። ታላላቆቼ ጋ በዛ ዕድሜዬ በዚህ ጉዳይ የማውራት ስልጣኔ አልዳበረም፤ ነውር ነበር።

ሸሸሁ!

የባሰ የቀዘቀዘ ድምጽ እንዳልሰማ ሸሸሁ፤ አዲስ የተወዳጀሃት ልጅ እንዳለች ስድስተኛ ስሜቴ አንሾካሾከልኝ። ስደውል በእሷ ፊት ተራ ጓደኛዬ ነች ዓይነት ወሬ እንዳታወራኝ ሰጋሁ። አትደውይልኝ እንዳትለኝ ስለሰጋሁ ሸሸሁ።

ላ'ንተ ያለኝ ፍቅር የባሰ አጣጥለኸኝ እንዳይቋጭ ስለሳሳው ሸሸሁ!

የጋራ ጓደኞቼ በልቤ ያለውን ፍርሀት እንዳይነገሩኝ ሁሉንም ዘጋኋቸው « አነባቸው የነበሩ ፍቅር ነክ ልብ-ወለድ ጽሑፎች ውስታዬን ተስቅሰው ናፍቆቴን እንዳያባብሱት ማንበብ አቆምኩ፤ የፍቅር ፊልሞች ትዝታዬን ገላልጠው እንዳያሳምሙኝ ማየት ተውኩ፤ ያች ሄርሞን ከመሸሽ ውጪ የመጋፈጥ አቅም አልነበራትምና ሸሸች።

የጀመርኩት የ"psychology" ትምህርት ካለ ምርጫዬ ስለነበር ችግር ሲገጥመኝ የምሸሸግብህ፣ የምታጽናናኝ አንተ ስትለወጥብኝ፣ ስትገፋኝ የልቤን የማጫውተው ጓደኛ አለመኖሩ፣ የምግቡ አለመስማማት፣ የጨጓራ ሕመሜ ኑሮዬን አጠየፈው። ኪዳነምህረት ቤተክርስትያን . ረጅም ሰዓት እቀመጣለሁ፣ ስብከት አዳምጣለሁ፣ ጉባኤ እከታተላለሁ::

ፆታዊ ፍቅር ስለሌለው፣ የሁሉ ነገር መሠረት ክርስቶስ እንደሆነ ስለሚነገር፣ በፈተናው የጸና የተባረከ ነው ስለሚባል፣ ብዙ ነገሮች በዲያቢሎስ ስለሚላከክ፣ የጭንቀታችን ችግር መፍቻ ጸሎት፣ ንሰሃ መሆኑን በአማረ፣ እና በሚጣፍጥ ቋንቋ ስለሚያስተምሩ ጣፈጠኝ። መጽሐፍ ቅዱስን የሙጥኝ አልኩ። ችግሮቼ እየቀለሉኝ መጡ። አዳዲስ ሃይማኖተኛ ጓደኞች ተወዳጀሁ።

የመጀመሪያ ዓመት ጨርሼ ስመጣ ግሬይ ሱሪ፣ ቀይ ቲሸርት አድርገህ ቆመህ አየሁህ። ሳይህ ከእስራቴ፣ ከሱሴ መላቀቄ ነው የተገለጠልኝ። የሆነ ቀጫጫ ልጅ፣ ኖርማል ወንድ፣ ለአይን የማይሞላ ልጅ አየሁኝ። ለካ ችግራችንን የምናይበት መንገድ የገዘፈ ስለሆነ ነው ከችግራችን በታች የምንሆነው።

ዕውቀትና ልምድ ያለው ሰው መውጫ መሰላሉን ስለማርዮን ነው ለካ እንቅፋታችን የሚፈነጭብን። ርግጥ ከስቃይ የምናገኘው ጥበብ ያበስለናል። ከስኬት ከምናገኘው እውቀት ከውድቀት የምናገኘው ጥበብ እጅግ ትልቅ ነው።

ያኔ ሳይህና ሰላም ስልህ የተሰማኝ ስሜት አስገረመኝ፤ እረስቼህ ነበር። አንድ የማውቀውን ሰው ሰላም እንደማለት ነበር ያ ወቅት የሕይወቴ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር፤ ነገር ግን በዛ ፈታኝ ወቅት ያዳበርኩት ብስለት ለቀሪው ሕይወቴ ጫንቃ እያበቀልኩበት ነበር።

ጸጥ አልኩ፣ ትንሽ ጸጸት፣ ትንሽ ግርምት፣ ትንሽ | ግርታ ተደማምሮ ሁካታ ቢሞላብኝም ፀጥ አልኩ።ዝምታ ከመላምት ውጪ የሚያስተላልፈው አንድም ተጨባጭ መልእክት የለምና ፀጥ አልኩ።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
27👍17
#አዲስ_መንገድ

ቁንጅናዋ ብዙ ሰው የሚስማማበት ዓይነት ነው። ቆንጆ እንደሆነች ታውቃለች፤ ግን ቆንጆ ስትባል ደስ ይላታል። ሴት ልጅ በየትኛውም ዕድሜ ቆንጆ መባልን አትጠላም፤ ሴት ልጅ መደነቅ ድክመቷ ነው መሰለኝ። በእርግጥ መደነቅ እና ትክክል መባል የሰው ሁሉ ድክመት ይመስለኛል።

ምንም እንኳን የገላዋ አሠራርም ለአድናቆት እንዲመች አድርጎ ያበጃጃት ቢሆንም፣ ሴቶች በሚወዷቸው እንደማይጨክኑ ኤልዳና እኔ እንዳላገኛት መንገድ አለመዝጋቷ ምስክር ነው። እኔ ሞኝ የምባል ዓይነት ሰው ነኝ መሰለኝ፤ ለቀልድ እንኳን ሞኝ ስባል አራስ ነብር ነው የምሆነው። እንዲሁ በቃ ክፍ...ት ነው የሚለኝ።

ሞኝነት ድክመቴ ባይሆን ሞኝ ስባል እስቅ አልነበር? አሁን ቀጫጫ አይደለሁም፣ ቀጫጫ ብባል ግን እስቃለሁ እንጂ አልናደድም፤ ስለዚህ ሞኝ ነኝ ማለት ነው እላለሁ። አንዳንዴ ደግሞ እንደዚህ ከተመራመርኩ እኮ ሞኝ አይደለሁም እላለሁ።

ዘይገርም!

አንዳንዴ ሰዎች ጭንቅላቴ ስል ሲሆንባቸው ትኩር ብለው ያዩኛል፤ በቂላቂልነቴ 'save' አድርገውኝ ባይሆን ኖሮ እንዴት እንደዚህ አሰበ ብለው ሲገረሙብኝ አይናቸው ላይ መች አስተውል ነበር? ሰው ድክመቱን ባያሻሽለው እንኳን

ጥንጥም ይገባዋል ማለት ነው፤ ያ ማለት ደግሞ he might be denying the hard fact deliberately

ኤልዳና ጋ ብዙ ቀን እደውላለሁ፣ ሲያሻት ብቻ ስልኬን ታነሳለች፤ ከደወለችልኝ የሆነ ነገር ፈልጋ ነው፤ ቢሆንም ደስስ ይለኛል! ኤልዳና ከእኔ ጋ ስታወራ አወራሯ ፆታዊ ነገር የለውም፣ መሽኮርመም ሆነ ደርባባነት አይታይባትም። ምንም ፆታዊ ፍላጎት ስለሌላት ይሆን?

አላውቅም!

አግኚኝ ስላት ሀገር እንደምታስተዳድር ዓይነት ነው ባተሌ መሆኗን የምትነገርኝ። የግል ዩኒቨርስቲ እያስተማርኩ፣ ትልቅ ፕሮጀክት እየመራሁ እኔ እንኳን እንደእሷ ስለመባተል አላወራም።

ተሳክቶልኝ ኦር ፈልጋኝ ያገኘችኝ ጊዜ ደግሞ ነጻ መሆን አልችልም። አክብጄ ስለማያት ጨዋታ አይመጣልኝም፡፡ ባገኘሁት አጋጣሚ ቀልቧን ለመሳብ እባዝናለሁ። በቃ እዛው ከእኔ ጋ እያለች ከሌላ ሰው ጋ ስልክ ታወራለች፡፡ ፊቴ ለምታወራው ወንድ ሲሆን ደግሞ ደርበብ እሽኩርምም ስትል አስተውላለሁ፡፡ ሞኝ ስለምመስላት ይሄን የምረዳ አይመስላትም ወይም ሳይታወቃት በደመ ነብስ ነው ሁኔታዋ እና አነጋገሯ የሚቀየርባት፤ አንዳንዴ ለምንፈልገው ነገርአድራጎታችን ከዕውቅናችን ውጪ ይሆን የለ።

ትንሽ ለመጫወት እሞክራለሁ፤ ቀላል ወሬ ታወራልኛለች። ከዛ የማይመለስ ብር ትበደረኛለች፣ ከዛ እንቅ አድርጋ ትስመኛለች፤ ደስስስስስ ይለኛል፡፡ ጓደኞቿ ጋ ሆና ካገኘኋት በጣም እንደምወዳት እሷ ደግሞ ከምንም እንደማትቆጥረኝ፤ ለብቻቸው የነገረቻቸውን በማስረጃ እያጣቀሰች እና እየቀለደችብኝ ታሳየቸዋለች። እነሱ ደግሞ አምነንሻል፣ ገብቶናል ለማለት ያሽካካሉ።

አሁን እንደው የሚወደን ሰው ላይ እማኝ አስቀምጦ ማልመጥ ምን የሚሉት ሥልጣኔ ነው?!

“ኮትህን የት ገዛኸው" አለችኝ አንድ ጓደኛዋ ሽሙጥ እንዳልሆነ እንዳያሳብቅ ፊቷን እየተቆጣጠረችው። አይን ደግሞ አይዋሽ፣ አይኗ ያስታውቃል፡፡ ለበኋላ የሚሆን ቧልት እያድቦለቦለች ነው።

ዝም አልኳት። አሁን ሰው መርጦ እና ወዶ በለበሰው ኮት የለበሰው ሰው ፊት ማላገጥ ትክክል ነው??

ጓደኞቿ እኔ ላይ ያላቸው ንቀት ምንጭ የምወዳት ኤልዳና መሆኗን ነጋሪም መስካሪም አያስፈለገኝም። ተሰብስበው ሳገኛቸው ከሚጨንቀኝ ነገሮች አንዱ እጄን የት እንማደርገው ነው። ኪሴ ውስጥ እከተዋለሁ ወይ አጣምራለሁ አልያም የግራ እና የቀኝ ጣቶቼን አቆላልፋለሁ፤ በእሱ ራሱ ይቀልዳሉ።

ፍቅር ተአምራዊ መሆኑ ማሳያዬ ይሄ ሁላ እየገባኝ አለመሸሼ ነው! እኔ ለእሷ ክፉ አይደለሁ! ከሁሉም ሰው በላይ ስለምወዳት አይደል የተበደረችኝን እንደረሳሁ ሆኜ ሌላ ቀን እንደገና የማትመልስልኝን ገንዘብ የማበድራት፤ ለዛውም ላይ ታች ብዬ የማመጣውን ገንዘቤን!!

መውደዱ የእውነት እንደሆነ የሚታወቅ ሰው ላይ ይሾፋል?

ሰው ላይ መቀለድ አራድነት ነው?

ስለማታውቀኝ ነው እኮ ማጣጣል እንደማይጥለኝ፣ ስንቴ በትግሎቼ እንደወደቅኩ፣ ወድቄ ሳለሁ ቆሜ ስለምታገለው እንደማሰላስል!

ለዚህ ነው ይሄ ሁላ ነገሯ እየገባኝ፣ አይኗ ሲከፈት ሞኝነቴ ጥበብ እንዳለው ትረዳለች ብዬ መጠበቄ፤ የድንቁርናዋ ምንጩ አለማስተዋል እንደሆነ የምረዳላት፤ ከብልግናዎቿ መሀል መልካምነቷን ለራሴ እንደምነግር አልገባትም። ክፉ ቀን ቢመጣባት አብራ ከምታላግጥብኝ ጓደኞቿ የበለጠ እንደምረዳት፤ ከአጠገቧ እንደማልጠፋ አልገባትም።

ሰው በረከቱ ላይ እንዴት ያላግጣል? መወደድ በረከት አይደለምን?

ፍቅር የሚወዱንን ብቻ መውደድ አይደለም፤ ለዛ ነው የምወዳት፤ የቀን ጉዳይ ነው እንጂ ፍቅሬ አንድ ቀን ይጋባባታል።

ያ አንድ ቀን እንዲመጣ ደግሞ ...

ትላንት ባልሞከርኩት መንገድ መምጣት አለብኝ፤ ለተመሳሳይ አወዳዳቅ ተመሳሳይ የአተጋገል ስልቶች ምክንያት ናቸው፡፡ ጥበብ ማለት የሚፋለመንን መረዳት ብቻ ሳይሆን መቅደምም ጭምር ነው። ከትላንት የተሻለ ውጤት መጠበቅ ያለብኝ ትላንት በሄድኩበት መንገድ ካልመጣሁ ብቻ ነው።

እጅ መስጠት ውስጥም ደማቅ ድል አለ!!!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
17👍12
#የዕውቀት_መንገድ

ገጣጣ ነች፤ ስትስቅ አፏን ከፍታ ነው፤ አሳሳቋን ከማንም ጋ ብትሆን አትቀይረውም። ስንት ቀን እኔ ባለሁበት የሚያምርጥርስ አይታ ስታደንቅ አይቻታለሁ። የሌለውን ያላጣጣለ እሱ ትልቅ ሰው ነው!!!

ፎቶ ላይ ገጣጣነቷን ለመደበቅ ጥረት ስታደርግ አይቻት አላውቅም። ራስን የመሆን እና ራስን የማወቅ ጥግ ራስን መቀበል ነው። አንድ ዕለት ሆን ብዬ ግንባሯ ላይ ፍንክት ስላለባት እና በሻሽ፣ በሻርፕ ስለምትደብቀው ልጅ ስነግራት "በዙሪያችን ያሉ ሰዎች እንዲቀበሉን እኛ ቀድመን ራሳችን መቀበል አለብን፤ ደካማ ሰው ነው ድክመት ላይ የሚመሰጠው፤ በራሱ የማይተማመን፣ የሚያሳቅቀው ነው ጉድለት የሚያስሰው። የማይለወጥ ነገርን መቀበል ከራስ ጋ ያዋሕዳል። ያየነውን ጥሩ ነገርበትክክለኛው ሰዓት ማንጸባረቅ በራስ መተማመን ይባላል።
በራሳቸው የማይተማመኑ ሰው ማሳነስ ላይ ሲረማመዱ የሚውሉ ናቸው::"

"በራሳቸው የማይተማመኑ ድኩማኖች አላግጠው አሸማቀዋት ነው ራሷን ያልተቀበለችው፡፡ አስተዳደጓ ላይ ራስን ስለመሆን፣ ራስን ስለማወቅ እና ራስን ስለማሸነፍ ማንም ስላላሰረጸባት ነው፡፡ ማንም በጀርባዬ ስለገጣጣነቴ ሲንሾካሾክ ባይ ውስጤ አይታወክም፣ ድብርት አይንጠኝም፤ ምክንያቱም ራሴን ተቀብዬዋለሁ። ድሃን ድሃ ስትለው ከተንጨረጨረ ድህነቱን እንዳይቀበል ትምህክተኝነቱ ጋርዶታል ማለት ነው። መስታወት ላይ ስቆም ጥርሴን ስደብቅ ምን እንደምመስል በከንፈሬ እየደበቅኩ ለማየት አልጥርም፡፡ በአደጋ፣ በበሽታ፣ በዕድሜ መግፋት አካል እንደሚዛነፍ፣ እንደሚጎድል እና እንደሚበላሽ አውቀዋለሁ። እንደዚህ እያልኩ ግን ተጽናንቼ አላውቅም፤ መጽናናትም አማራጭ የማጣት መንገድ ነውና። ተጽናንተህ፣ አለባብሰህ፣ ራስህን አሞኝተህ የተውከው ነገር ባስታወሱህ አልያም ባስታወስከው ቁጥር ምቾት አይሰጥህም። ዘለቄታዊ መፍትሔ ራስን መቀበል ነው፤ አስተዋጽኦ ባላበረከትኩበት ነገር ስለምን እመሰጣለሁ?" እያለች ስታወራኝ እርጋታ እና ትህትና ተላብሳ ነው፤ ዕውቀት ነጻ እንደሚያወጣ ይኸው

እውነቱን ለማውራት ገጣጣነት ያምርባታል።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
18👍9👏6🥰5
#ጥሎ_መሸነፍ

አስቤበት፣ አሰላስዬ ልተዋት፣ አልፈልግሽም ልላት አቅጄ አግኝቻት ችላ ስትለኝ ፍቅሬ ይጨምራል። ስለ ማንም ግድ እንደሌላት ስትጠቁመኝ እልህ እጋባለሁ።

ልበ ሙሉነቷ፣ ካለ'ኔ መቆም እንደምትችል ሳስብ ልቤ ይርዳል። አንዳች የማላውቀው ኃይል አብሪያት እንድሆን ይታገለኛል። አሁን በቀደም ፀሐይ ስትሸሸግ፣ ሰማዩ ሲጠቁር፤ ከባቢው ሲሰክን፤ አንዲት ለስላሳ ሙዚቃ ያለበት ሬስቶራንት አገኘኋት። አልዘነጠችም ፈታ ብላለች፤ ፈታ ብያለሁ።

አብሪያት መሆን እንደማልፈልግ ጫፍ ጫፉን አሳየኋት። ነገ የምንኖረው የጋራ ሕልም እንደሌለን ጠቆምኳት፤ ምንም ሳይመስላት በፈገግታ ደስ እንዳለህ አለችኝ። ደስስ አላለኝም፤ ሲደብራት አባብላታለሁ ያልኩት የቃላት ጋጋታ ሟሟ። ድብርት ሲያቀዘቅዘኝ ታውቆኛል። ቅዝቃዜውን ለመርታት ያዘዝኩትን አልኮል በአንድ ትንፋሽ ጨለጥኩ። በልቤ ያለውን እውነታ ለማን ብናገር ያምናል፤ ልጣላት መጥቼ፣ ለመጣላት ዳር ዳር ስል ምንም አልመሰላትም ብሎ ሐሳብ መቀየር ምን ይሉታል።

ሳምኳት ሳመችኝ ተሳሳምን አትወጅም እያልኩ መጨቅጨቅ ጀመርኩ፤ እወድሃለሁ በይኝ አልኳት እወድሃለሁ አለችኝ።

ቆይ ከወደደችኝ ለምን እንደማልፈልጋት ምልክት ስሰጣት አልከፋትም? ለምን እንደምታፈቅረኝ አልዘበዘበችም፤ ቅርአለኝ። አሽናፊነት የሚመጣው ተጋጣሚ የሚፈልገውን ባለመስጠት ነው። የምንፈልገውን የምናገኘው እራሳችንን ከምንፈልገው ነገር ባለማሳነስ ነው። እውነቷን ነው በልመና የምታስቀረው ፍቅረኛዋ ምን ይጠቅማታል። ራሷን ከእሱ በታች አድርጋ የእሷ የምታደርገው አጋሯ ምን ይበጃታል።

ነጋ፣ ፍቅር በልተን፣ ፍቅር ሰርተን ስንነሳ፣ ስንዋሃድ አትለየኝ ትለኛለች ብዬ ጠበቅኳት። በፍቅር ሳመችኝ፤ እንዳደረኳት ሆነችልኝ፤ እንደሳምኳት ሳመችኝ፤ ምንም አላለችኝም፡፡ ሳበኝ፤ የምፈልገውን አለመስጠቷ ሳበኝ፤ እንደምጠብቀው አለመሆኑ ውስጤ ሲሸነፍ ታውቆኛል።

ጭንቅላቴን ተቆጣጠረችው፡፡ ሰው ምን ዓይነት ውሻ ፍጡርነው ስል ተበሳጨሁ፤ አልፈልግም ብትለኝ፣ ብታለቅስ እንዴት ነበር የምታበየው? ስንት ሕግ ነበር የምደረድረው? እንዴት ነበር ከማማው ላይ ተፈናጥጬ ቁልቁል የማያት? እንዴት ነበር እኔ ትልቅ፣ ግዙፍ ሰው መሆኔን እዘበዝብላት የነበር? ጥበቧ እንዳልታበይባት ከለለኝ፣ ልበሙሉነት መሥመራችንን የማቅለል አቅሙ ግዙፍ ነው፡፡

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍179🔥8🎉1
                      ጭራሽ....
                 ደሞ ልብ እንዳለው
                ሴት ላፍቅር እላለው?
                 ደሞ ነፍስ እንዳለው
            ቅኖና ንስሀ ምናምን እላለው?
                   ደሞ ሰማሻቸው?
                  ለመልኩ ለዓይኑ
                 ግድ የለውም ሲሉ

                   ጎኑ ላለ ተድላ...
                   ጎኑ ላለ ለቅሶ...
                   ጎኑ ላለ ዕድር...
                   ጎኑ ላለ ዕቁብ...
               የለውም አንዳች ቁብ

                  ሲሉ ሰማሻቸው?
        ፂሙ ቢንዠረገግ መሬት ቢዘረጋ
     እሱ ግድ የለውም አፈር ቢሆን አልጋ

               ሲሉ ሰማሻቸው?
               ዝም አትበያቸው

               ዝም አትበያቸው
"በየትኛው ነብሱ ይሄን ሁሉ ያስብ?"
             ብለሽ ጠይቂያቸው

              ዝም አትበያቸው

               ዝም አትበያቸው
"በየትኛው ነብሱ ይሄን ሁሉ ያስብ?"
            ብለሽ ጠይቂያቸው

  በየትኛው ነፍሴ ከትላንቴ ልማር
  በየትኛው ነፍሴ ከትላንቴ ልማር
አንቺን አገኝ ብዬ አሲዤው በቁማር

          አስመልሺኝ እስቲ...

ደሞ ልብ እንዳለው ሴት ላፍቅር እላለው?!


🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍9🔥5
ውድነሽን ሲነካብኝ በልጅነት አጥንቴ ሳይጠነክር፣ ትከሻዬ ሳይሰፋ፣ አካሌ ሳይጎለማ ለመታገል እንደተዘጋጀሁ እረሳው። እግዜር ሊበቀለው የራሱን ፊት እንደሰጠኝ፣ የራሱን ጥጋብ እንዳወረሰኝ አልተገለጠለትም ነበር። እግዜር ሲቀጣ ሂደቱን የውጤቱ ቀን ነው የሚገልጸው።

ያነቅኩበትን አንዱን እጄን ለቅቄ፣ እጄን ጨብጬ በኃይል አራት ጊዜ ያህል ደጋግሜ ሰነዘርኩ። ቤቱ ተንቀጠቀጠ፣ እናቴ ጮኸች፣ ቤት ውስጥ የነበረው ሰው ሊይዘኝ ስለፈራ ለመነኝ...

በእርግጥ ቡጢዬን ያሳረፍኩት ከፊቱ ጎን ያለው ግድግዳ ላይ ነው፤ ግድግዳው ተሰነጣጠቀ፤ ግዝፈቴ ይሆን፣ ብስጭቴ ይሆን፣ ግድግዳችን ስለማይረባ ይሆን አላውቅም!!

“ተው ልጄ ተው" አለኝ...

ድሪባ ለካ መለመን ይችላል። ወይም ዕድሜ ሲገፋ፣ አቅሙ ሲደክም ልመና ለምዷል፤ መኖር ለካ ብዙ መገለጫችን ያልሆነ ነገርን ጨምሮ ያስለምዳል።

የተሰማኝን ማውራት ብችል ኖሮ ምን ታድርግህ? ምን አድርጊ ነው የምትላት? ዕድሜ አያስተምርህም?አይበቃህም? እለው ነበር። ማድረግ የቻልኩት ሸፋሽፍቴ ላይ የተሞጀረ እንባ ማሳየት ብቻ ነበር!!

ስላልታደለ እንጂ አውሬው ልጁ እሱን ነበር ሊከላከለው የሚገባው፤ ስላልታደልኩ እንጂ ያሳደገኝን ሰውዬ እንደጠላቴ አልቆጥረውም ነበር።

ለቀቅሁት... ለመጀመሪያ ጊዜ መግዘፌ አስጠላኝ። ትናንት አቅም አልባ እያለሁ እናቴን ለማዳን ስፍጨረጨር የነበረው ስሜት ይሻል ነበር። ፍቅር ማለት ለሚያፈቅሩት ሲሉ ከማይችሉት ጋ መታገል እንጂ የሚያሸንፉትን ማሸማቀቅ አይደለም። ስለቀው እንባው እንደ እኔ ሽፋሽፍቱ አልገደበውም አለቀሰ። ያ ሞገሳሙ ድሪባ፣ በድምጹ የሚያርበደብደው፣ ተነሳበት የሚባለው፣ የሚለመነው፣ የሚለምኑት ጎረቤቶች ፊት ሲለመንለት ጊዜ አለቀሰ።

ለካ አርጅቷል፣ ለካ አቅሙ እየከዳው ነበር፣ ለካ ማስበርገግ ሱስ ሆኖበት ነው። መለመን ምን ምን እንደሚል፤ መበርገግ በገዛ ልጁ ምን እንደሚመስል በጎፈነነ ስሜት ውስጥ ሆኖ አየው። ድሪባ ሲያለቅስ ሳየው ዘመናት ሙሉ ከሽፋሽፍቴ ወርዶ የማያውቀው እንባዬ ጉንጬ ላይ ሲሄድ ታወቀኝ። ለምን ይሄን ያህል እስኪያለቅስ አሳዝኜው፣ ተፈታትኜው አንቄው ሳለ ሽጉጡን አውጥቶ ካልገደልኩት ብሎ አልተገላገለም።

ውድነሽን ባይነካብኝ ኖሮ መቼ አዋርደው ነበር? ደግሞስ ምን አገባኝ ሚስቱ አይደለች? ደግሞ ሲያመው ትደነግጥ የለ፤ ሲያማት የእኔን ያህል መጨነቁ ይታይ የለ።


እሷስ መቼ እንደምትጠላው ሰምቼ አውቃለሁ ? መቼ ስለጥፋቱ ለልጆቿም ሆነ ለሌላ ስታወራ መቼ ሰማሁ ? መቼ አጠጣጥላው አይቻት አውቃለሁ...መቼ??

ከድሪባ ጋር በፀባይ የምንመሳሰል መስሎኝ ነበር እውነቱ ግን እኔ አውሬ ነኝ።

እንባዬ በጉንጬ እየወረደ ስልኬ ጠራ የሚስቴ እናት ናቸው አንስቼ ሄሎ ስል "ሮብሰን የወንድ ልጅ አባት ሆነካል። መልኩ ደሞ ቁርጥ አንተን መንታ ነው የምትመስሉት አለችኝ።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
13👏1