#የእግዜር_የአደራ_ልጅ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
❤55
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጁኒዬር አለምን ይዞ ወደ ወላጆቹ ቤት ሲደርስ ሳሎን ያለው አባቱ ብቻ ነው፡፡አቶ ፍሰሀ ከመቀመጫቸው ተነስተው እጇን እየጨበጡ"ጁኒየር ስላገኘሽ እና እንድትመጪም ስላሳመነሽ ደስ ብሎኛል" አላት፡፡
"እኔም እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።"
"ደህና….ተቀመጪ››
ተቀመጠች፡፡
"ምን ትጠጫለሽ?"ሲል ጁኒዬር ጠየቃት፡፡ "ነጭ ወይን ካለ ደስ ይለኛል…. እባክህ" አለች.
አቶ ፍሰሀ በጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ እያያት "ነጭ ወይን,? እንዳጋጣሚ ባለቤቴም የነጭ ወይን አፍቃሪ ስለሆነች ከእኛ ቤት ጠፍቶ አያውቅም… አሁን ትመጣና ትቀላለናለች
፡፡››አላት
ጁኒየር መጥሪያውን ሲጫን የቤቱ አገልጋይ ከውስጠኛው ክፍል እየሮጠች መጣች…ነጭ ወይን አምጥታ ለአለም እንድትቀዳላት አዘዛት፡፡ወይኑ መጣና ተቀዳላት..አቶ ፍሰሀና ልጃቸው ጁኒዬር ቢራ ያዙ፡፡
‹‹ጁኒዬር ወደቤት ይዞሽ እንዲመጣ ጠይቄው ነበር..እንዲህ በፍጥነት ይሳካለታል አላልኩም ነበር፡፡››
አለም ግራ ተገባች..እናም ወደ ጁኒዬር ዞር ብላ‹‹ወደእዚህ እንድመጣ ያንተ ፍላጎት መስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እሱማ የእኔም ፍላጎት ነው››አላት በእፍረት አንገቱን አቀርቅሮ፡፡ አለምም ወደ ፍሰሀ ዞራ "እሺ ለምን ነበር የፈለከኝ?"አለችው፡፡
በእሷ ቀጥተኛነት ለጊዜው ያልተደሰተ ይመስላል፣ ቢሆን እሱም በተመሳሳይ መንገድ መለሰላት
"ጠላቶች እንድንሆን… አንቺን በደንብ ማወቅ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"እኔም የመጣሁት ለዚህ ነው አቶ ፍሰሀ።"አለችው ፍርጥም ብላ፡፡
እሷን ትንሽ ጊዜ ወስዷ ሊያጠናት ሞከረ። "እንዴት ጠበቃ ለመሆን ፈለግሽ?"የተለመደ ግን ደግሞ ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"የእናቴን ግድያ ለመመርመር ወንጀለኛውን ለፍርድ ለማቅረብ እንድችል.››
መልሱ በድንገት ወደ ከንፈሮቿ የመጣ ነው፣ ይህም መልሷ እንሱን ብቻ ሳይሆን አለምን እራሷን አስገርሟታል። እሷ ከዚህ በፊት የእናቷን ገዳይ መፈለግ ዋና ግቧ እንደሆነ ተናግራ አታውቅም።በዚህ የእናቷ ግድያ ወንጀል ላይ እሷ ራሷም በአያቷ ዘንድ ይፋዊ ተጠርጣሪ ሆና መቅረቧ ነገሩን በቁርጠኝነት እንድትይዘው ገፊ ምክንያት ሆኗታል፡፡ በመጨረሻ ሞት አፋፍ ላይ የምትገኝ አያቷ ለእናቷ ሞት ዋና ተጠያቂ እሷ እንደሆንች በግልፅ ቃል ደጋግማ ነግራታለች።አያቷ የተናገረችው ስህተት እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሌላ ማስረጃ እስካላገኘች ድረስ ጥፋቱን እስከ ህይወቷ ድረስ ይዛ ለመኖር ትገደዳለች ። እና አሁን ከሻሸመኔ ከተማ ሃያሎቹ ጋር ተፋጣ የምትገኝት ዋና ምክንያት ራሷን ነፃ ለማውጣት ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ "ባል የለሽም? ልጆችስ?"ሲል ሌላ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"አይ የለኝም።
" "ለምን?"
"አባ" አለ ጁኒየር በአባቱ እፍረት ማጣት አፍሮ ‹‹አለም ልተዝናና እንጂ በጥያቅህ እንድታጨናንቃት ይዣት አልመጣሁም››
" ጁኒየር ምንም ችግር የለውም። ይህ የተለመደ ጥያቄ ነው።"አለች አለም፡፡
" እሺ እንደዛ ካልሽ መልስሽ ምንድነው?"አቶ ፍሰሀ ጠየቃት፡፡
"ጊዜ ወይም ዝንባሌ የለኝም."
"በዚህ በእኛ አካባቢም ተመሳሳይ ብዙ ጊዜ እና በቂ ዝንባሌ የለንም."
ጁኒየር በጠወለገ እይታ አባቱን ተመለከተው።የተነገረው አሽሙር እሱን የሚመለከት እንደሆነ ያውቃል"አባዬ የከሸፉብኝን ትዳሮቼን እየጠቀሰ ነው።››በማለት አብራራላት፡፡
"ጋብቻዎች? ስንት ነበሩ?"አለም በጉጉት ጠየቀች
"ሶስት" በማለት ተናዘዘ።
"እና አንዳቸውም እኔን አያት የማድረግ ፍላጎቱም ሆነ ብቃት አልነበራቸውም››አቶ ፍሰሀ ዋና ቅሬታውን ተናገረ፡፡
በዚህ መካከል ከፎቁ ወደታች የሚወርድ የጫማ ኳኳታ ሰሙና በተመሳሳይ ሦስቱም ዞሩ። አንዲት ሴት በተከፈተው በር ላይ ቆማ ነበር። አለም የአቶ ፍሰሀ ሚስት እና የጁኒዬር እናት መሆኗን አወቀች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ ድረስ ምን እንደምትመስል አእምሮአዊ ምስል ቀርጾ ነበር። ወይዘሮዋ ግን የአለምን አእምሮአዊ ምስል ተቃራኒ ነበረች።
ጁኒዬር እናቴ ጀማይካዊት ነች ስላላት..የሆነች ፈርጣም ..ጠቆር ያለች.. ከንፈረ ትልልቅ…የፀጉሯ ድሬድ መቀመጫዋን የሚነካ አይነት አድርጋ ነበር የሳለቻት…እሷ ግን ቅንጥስጥስ ያለች ቀጭን…ቀይ ቆንጆ ግን ደግሞ ስልችት ያለው ፊት ያየዘች…ሀበሻ መሳይ
ሴት ነች፡፡ጁኒዬር ያንን አፍዛዣ መሳይ ውበቱን እና ለስላሳ ባህሪውን ከማን እንደወረሰው አሁን በግልፅ ገባት ፡፡
"ሃኒ ይህቺ አለም ጎበና ነች" አለ አቶ ፍሰሀ ።
የጁኒዬር እናት ባለቤቷን ችላ ብላ ፈካ ያለ ፊቷ አብርቶ ቀጥ ያለ ቀጭን ከንፈሯ ወደቀኝ በመጠምዘዝ ‹‹አለም ወደቤታችን እንኳን በሰላም መጣሽ…ሳራ እባላለው..የጁኒዬር እናት ነኝ
››አለችና ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡
አለም ከሴትዬዋ ንግግር የፍሰሀ ባለቤት ከመሆኗ በላይ የጁኒዬር እናት በመሆኗ ኩራት እንደሚሰማት ነው የተረዳችው፡፡
"አመሰግናለሁ።"ስትል መለሰች፡፡
ጁኒየር ከተቀመጠበት ተነሳና አንድ ብርጭቆ ነጭ ወይን ቀዳና ለእናቱ አቀበላት.. ። በሚያብረቀርቅ ፈገግታ‹‹አመሰግናለው የእኔ ልጅ››በማለት ተቀበለችው፡፡
እሱም ጎንበስ ብሎ እናቱን የለሰለሰ ስርጉድ ጉንጯን ሳመ። "ራስ ምታትሽ እንዴት ነው?"
"ሙሉ በሙሉ አልተወኝም፣ ነገር ግን እንቅልፍ ረድቶኛል። ስለጠየቅከኝ አመሰግናለሁ።"
አለም የሴትዬዋን እጇች ስታይ ተገረመች …እጇ ነጭ ሲሆኑ … በአውሎ ንፋስ እንደተመታ አበባ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል።
ባሏን " መቼስ ስለከብቶችና ፈረሶች እያወራህ እያሰለቸሀት ነው አይደል?"አለችው፡፡
"በራሴ ቤት ውስጥ፣ ስለምንስ ባወራ አንቺን ምን ጨነቀሽ?" አቶ ፍሰሀ ቱግ አለ፡፡ ጁኒየር ንግግራቸውን ከዛ በላይ እንዳይጠነክርና አለም ፊት እንዳያሳፍሩን ፈጠን ብሎ ጣልቃ ገባ፡፡
"እማዬ ስለ እርባታ አይደለም እያወራን ያለነው ። አባዬ ከሚስቶቼ ወራሽ የሚሆን ልጅ ለመውለድ ባለመቻሌ እየወቀሰኝ ነበር።"ሲል አብራራላት፡፡
"ጊዜው ሲደርስ ከትክክለኛ ሴት ጋር ልጆች ትወልዳለህ››.አለችና ወደ አለም ዘወር ብላ ጠየቀች፡- “ወ.ሪት አለም በፍፁም አላገባሁም ስትይ ሰምቻለሁ ልበል ?” ብላ ጠየቀችው።
"ልክ ነው"
"እንግዳ ነገር ነው…ቢያንስ የወንድ ጓደኛ ሊኖርሽ ይገባ ነበር፡፡››
"አለም የወንድ ጓደኛ የለኝም አላለችም እኮ
››ጁኒየር አስተካከላት. "በቃ መራጭ ነች"ሲል አከለበት፡፡
"አዎ ከጋብቻ እና ቤተሰብ ከመመሥረት ይልቅ ሙያዬን መርጫለሁ።ለጊዜው፣ ለማንኛውም ነገር ጊዜ የለኝም። ግን እናቴ የሆነ ሙያ ባለቤት ለመሆን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ታውቃለች?"
"እሷን እስከማውቃት ድረስ እንደዛ አይነት ምኞት አልነበራትም" ሲል ጁኒየር መለሰ፣ አለም በፀፀት ስሜት "በጣም ቀድማ በልጅነቷ ነበር የወለደችኝ" አለች።
"ምናልባት ያለዕድሜ ጋብቻ ውስጥ መግባቷ እና ልጅ መውለዷ ወደ ሥራ እንዳትገባ አግዷት ይሆናል….ሰሎሜ የራሷን ምርጫ ነው ተግባራዊ ያደረገችው."ሲል መለሰላት፡፡
"የምታውቀውን ስለነገርከኝ አመሰግናለሁ.››
‹‹ አንድ ጊዜ እኔ እሷና ጀማል ለመዝናናት ወደወንዶ ገነት ሄደን ነበር፡፡በፍል ውሀ ስንታጠብና ስንዋኝ ከዋልን በኃላ በጣም ደክሞን ዛፍ ጥላ ስር ሳሩ ላይ ተዘርረን ሰማዩን አንጋጠን ስለ ምኞታችን ስናወራ እንደነበር ትዝ ይለኛል…ሁላችንም የዋና ልብስ ብቻ ነበር የለበስነው…እና እሷም በመሀላችን ተኝታ ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጁኒዬር አለምን ይዞ ወደ ወላጆቹ ቤት ሲደርስ ሳሎን ያለው አባቱ ብቻ ነው፡፡አቶ ፍሰሀ ከመቀመጫቸው ተነስተው እጇን እየጨበጡ"ጁኒየር ስላገኘሽ እና እንድትመጪም ስላሳመነሽ ደስ ብሎኛል" አላት፡፡
"እኔም እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።"
"ደህና….ተቀመጪ››
ተቀመጠች፡፡
"ምን ትጠጫለሽ?"ሲል ጁኒዬር ጠየቃት፡፡ "ነጭ ወይን ካለ ደስ ይለኛል…. እባክህ" አለች.
አቶ ፍሰሀ በጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ እያያት "ነጭ ወይን,? እንዳጋጣሚ ባለቤቴም የነጭ ወይን አፍቃሪ ስለሆነች ከእኛ ቤት ጠፍቶ አያውቅም… አሁን ትመጣና ትቀላለናለች
፡፡››አላት
ጁኒየር መጥሪያውን ሲጫን የቤቱ አገልጋይ ከውስጠኛው ክፍል እየሮጠች መጣች…ነጭ ወይን አምጥታ ለአለም እንድትቀዳላት አዘዛት፡፡ወይኑ መጣና ተቀዳላት..አቶ ፍሰሀና ልጃቸው ጁኒዬር ቢራ ያዙ፡፡
‹‹ጁኒዬር ወደቤት ይዞሽ እንዲመጣ ጠይቄው ነበር..እንዲህ በፍጥነት ይሳካለታል አላልኩም ነበር፡፡››
አለም ግራ ተገባች..እናም ወደ ጁኒዬር ዞር ብላ‹‹ወደእዚህ እንድመጣ ያንተ ፍላጎት መስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እሱማ የእኔም ፍላጎት ነው››አላት በእፍረት አንገቱን አቀርቅሮ፡፡ አለምም ወደ ፍሰሀ ዞራ "እሺ ለምን ነበር የፈለከኝ?"አለችው፡፡
በእሷ ቀጥተኛነት ለጊዜው ያልተደሰተ ይመስላል፣ ቢሆን እሱም በተመሳሳይ መንገድ መለሰላት
"ጠላቶች እንድንሆን… አንቺን በደንብ ማወቅ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"እኔም የመጣሁት ለዚህ ነው አቶ ፍሰሀ።"አለችው ፍርጥም ብላ፡፡
እሷን ትንሽ ጊዜ ወስዷ ሊያጠናት ሞከረ። "እንዴት ጠበቃ ለመሆን ፈለግሽ?"የተለመደ ግን ደግሞ ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"የእናቴን ግድያ ለመመርመር ወንጀለኛውን ለፍርድ ለማቅረብ እንድችል.››
መልሱ በድንገት ወደ ከንፈሮቿ የመጣ ነው፣ ይህም መልሷ እንሱን ብቻ ሳይሆን አለምን እራሷን አስገርሟታል። እሷ ከዚህ በፊት የእናቷን ገዳይ መፈለግ ዋና ግቧ እንደሆነ ተናግራ አታውቅም።በዚህ የእናቷ ግድያ ወንጀል ላይ እሷ ራሷም በአያቷ ዘንድ ይፋዊ ተጠርጣሪ ሆና መቅረቧ ነገሩን በቁርጠኝነት እንድትይዘው ገፊ ምክንያት ሆኗታል፡፡ በመጨረሻ ሞት አፋፍ ላይ የምትገኝ አያቷ ለእናቷ ሞት ዋና ተጠያቂ እሷ እንደሆንች በግልፅ ቃል ደጋግማ ነግራታለች።አያቷ የተናገረችው ስህተት እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሌላ ማስረጃ እስካላገኘች ድረስ ጥፋቱን እስከ ህይወቷ ድረስ ይዛ ለመኖር ትገደዳለች ። እና አሁን ከሻሸመኔ ከተማ ሃያሎቹ ጋር ተፋጣ የምትገኝት ዋና ምክንያት ራሷን ነፃ ለማውጣት ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ "ባል የለሽም? ልጆችስ?"ሲል ሌላ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"አይ የለኝም።
" "ለምን?"
"አባ" አለ ጁኒየር በአባቱ እፍረት ማጣት አፍሮ ‹‹አለም ልተዝናና እንጂ በጥያቅህ እንድታጨናንቃት ይዣት አልመጣሁም››
" ጁኒየር ምንም ችግር የለውም። ይህ የተለመደ ጥያቄ ነው።"አለች አለም፡፡
" እሺ እንደዛ ካልሽ መልስሽ ምንድነው?"አቶ ፍሰሀ ጠየቃት፡፡
"ጊዜ ወይም ዝንባሌ የለኝም."
"በዚህ በእኛ አካባቢም ተመሳሳይ ብዙ ጊዜ እና በቂ ዝንባሌ የለንም."
ጁኒየር በጠወለገ እይታ አባቱን ተመለከተው።የተነገረው አሽሙር እሱን የሚመለከት እንደሆነ ያውቃል"አባዬ የከሸፉብኝን ትዳሮቼን እየጠቀሰ ነው።››በማለት አብራራላት፡፡
"ጋብቻዎች? ስንት ነበሩ?"አለም በጉጉት ጠየቀች
"ሶስት" በማለት ተናዘዘ።
"እና አንዳቸውም እኔን አያት የማድረግ ፍላጎቱም ሆነ ብቃት አልነበራቸውም››አቶ ፍሰሀ ዋና ቅሬታውን ተናገረ፡፡
በዚህ መካከል ከፎቁ ወደታች የሚወርድ የጫማ ኳኳታ ሰሙና በተመሳሳይ ሦስቱም ዞሩ። አንዲት ሴት በተከፈተው በር ላይ ቆማ ነበር። አለም የአቶ ፍሰሀ ሚስት እና የጁኒዬር እናት መሆኗን አወቀች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ ድረስ ምን እንደምትመስል አእምሮአዊ ምስል ቀርጾ ነበር። ወይዘሮዋ ግን የአለምን አእምሮአዊ ምስል ተቃራኒ ነበረች።
ጁኒዬር እናቴ ጀማይካዊት ነች ስላላት..የሆነች ፈርጣም ..ጠቆር ያለች.. ከንፈረ ትልልቅ…የፀጉሯ ድሬድ መቀመጫዋን የሚነካ አይነት አድርጋ ነበር የሳለቻት…እሷ ግን ቅንጥስጥስ ያለች ቀጭን…ቀይ ቆንጆ ግን ደግሞ ስልችት ያለው ፊት ያየዘች…ሀበሻ መሳይ
ሴት ነች፡፡ጁኒዬር ያንን አፍዛዣ መሳይ ውበቱን እና ለስላሳ ባህሪውን ከማን እንደወረሰው አሁን በግልፅ ገባት ፡፡
"ሃኒ ይህቺ አለም ጎበና ነች" አለ አቶ ፍሰሀ ።
የጁኒዬር እናት ባለቤቷን ችላ ብላ ፈካ ያለ ፊቷ አብርቶ ቀጥ ያለ ቀጭን ከንፈሯ ወደቀኝ በመጠምዘዝ ‹‹አለም ወደቤታችን እንኳን በሰላም መጣሽ…ሳራ እባላለው..የጁኒዬር እናት ነኝ
››አለችና ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡
አለም ከሴትዬዋ ንግግር የፍሰሀ ባለቤት ከመሆኗ በላይ የጁኒዬር እናት በመሆኗ ኩራት እንደሚሰማት ነው የተረዳችው፡፡
"አመሰግናለሁ።"ስትል መለሰች፡፡
ጁኒየር ከተቀመጠበት ተነሳና አንድ ብርጭቆ ነጭ ወይን ቀዳና ለእናቱ አቀበላት.. ። በሚያብረቀርቅ ፈገግታ‹‹አመሰግናለው የእኔ ልጅ››በማለት ተቀበለችው፡፡
እሱም ጎንበስ ብሎ እናቱን የለሰለሰ ስርጉድ ጉንጯን ሳመ። "ራስ ምታትሽ እንዴት ነው?"
"ሙሉ በሙሉ አልተወኝም፣ ነገር ግን እንቅልፍ ረድቶኛል። ስለጠየቅከኝ አመሰግናለሁ።"
አለም የሴትዬዋን እጇች ስታይ ተገረመች …እጇ ነጭ ሲሆኑ … በአውሎ ንፋስ እንደተመታ አበባ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል።
ባሏን " መቼስ ስለከብቶችና ፈረሶች እያወራህ እያሰለቸሀት ነው አይደል?"አለችው፡፡
"በራሴ ቤት ውስጥ፣ ስለምንስ ባወራ አንቺን ምን ጨነቀሽ?" አቶ ፍሰሀ ቱግ አለ፡፡ ጁኒየር ንግግራቸውን ከዛ በላይ እንዳይጠነክርና አለም ፊት እንዳያሳፍሩን ፈጠን ብሎ ጣልቃ ገባ፡፡
"እማዬ ስለ እርባታ አይደለም እያወራን ያለነው ። አባዬ ከሚስቶቼ ወራሽ የሚሆን ልጅ ለመውለድ ባለመቻሌ እየወቀሰኝ ነበር።"ሲል አብራራላት፡፡
"ጊዜው ሲደርስ ከትክክለኛ ሴት ጋር ልጆች ትወልዳለህ››.አለችና ወደ አለም ዘወር ብላ ጠየቀች፡- “ወ.ሪት አለም በፍፁም አላገባሁም ስትይ ሰምቻለሁ ልበል ?” ብላ ጠየቀችው።
"ልክ ነው"
"እንግዳ ነገር ነው…ቢያንስ የወንድ ጓደኛ ሊኖርሽ ይገባ ነበር፡፡››
"አለም የወንድ ጓደኛ የለኝም አላለችም እኮ
››ጁኒየር አስተካከላት. "በቃ መራጭ ነች"ሲል አከለበት፡፡
"አዎ ከጋብቻ እና ቤተሰብ ከመመሥረት ይልቅ ሙያዬን መርጫለሁ።ለጊዜው፣ ለማንኛውም ነገር ጊዜ የለኝም። ግን እናቴ የሆነ ሙያ ባለቤት ለመሆን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ታውቃለች?"
"እሷን እስከማውቃት ድረስ እንደዛ አይነት ምኞት አልነበራትም" ሲል ጁኒየር መለሰ፣ አለም በፀፀት ስሜት "በጣም ቀድማ በልጅነቷ ነበር የወለደችኝ" አለች።
"ምናልባት ያለዕድሜ ጋብቻ ውስጥ መግባቷ እና ልጅ መውለዷ ወደ ሥራ እንዳትገባ አግዷት ይሆናል….ሰሎሜ የራሷን ምርጫ ነው ተግባራዊ ያደረገችው."ሲል መለሰላት፡፡
"የምታውቀውን ስለነገርከኝ አመሰግናለሁ.››
‹‹ አንድ ጊዜ እኔ እሷና ጀማል ለመዝናናት ወደወንዶ ገነት ሄደን ነበር፡፡በፍል ውሀ ስንታጠብና ስንዋኝ ከዋልን በኃላ በጣም ደክሞን ዛፍ ጥላ ስር ሳሩ ላይ ተዘርረን ሰማዩን አንጋጠን ስለ ምኞታችን ስናወራ እንደነበር ትዝ ይለኛል…ሁላችንም የዋና ልብስ ብቻ ነበር የለበስነው…እና እሷም በመሀላችን ተኝታ ነበር፡፡
❤44👍2