#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ድክምክም ብሎታል፡፡ግን ደግሞ አልጋው ላይ ተኝቷ በሀሳብ እየተንገላታ ነው፡፡ ሰለሞን በሁለት በኩል ስለት ባለው ሰይፍ የሚጫወት ህፃን አይነት ሰው እንደሆነ እየተሰማው ነው፡፡ሞያውን በተመለከተ ለሶስት አመት በከፍተኛ የፕሮፌሽናል ደረጃ በምድረ-አሜሪካ ሲሰራ አንድም ጊዜ እንደዚህ አይነት ክፍተት ተከስቶበት አያውቅም..በዛም በራሱ ሲመካና ሲኮራ ኖሮ ነበር፡፡አሁን ግን ወደሀገሩ ተመልሶ ባጋጠሙት የመጀመሪያ ደንበኞቹ ከፍተኛ የሚባል ሽንቁር ተከስቶበታል፡፡አንድ ባለሞያ የሞያውን ስነምግባር አክብሮ ስራውን መስራት የሚገደደው ለደንበኞች ደህንነትንና ጥቅም ሲባል ብቻ አይደለም…ለራሱ ለሞያው ክብርና ተቀባይነትም እያንዳንዱ ባለሞያ የስራ-አፈፃፀም ሁኔታ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡በሙስናና በጥቅማጥቅም የሚታለሉ ዳኞችና አቃቢ-ህጎች በሞሉበት ሀገር ፍርድቤት ሊከበርና ሊታመን አይችልም፡፡ሌላውም ሞያ እንደዛው ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረ ያጋጠመችው ትልቋ ደንበኛው በፀሎት ነች፡፡እርግጥ ቀጥታ ደንበኛው እሷ ሳትሆን ወላጆቾ ናቸው፡፡ከእነሱ ጋር እየሰራ ያለውን ስራ የሞያው ስነምግባር በሚፈቅደው መንገድ ጥርትና ጥልል አድርጎ እየሰራ ነው፡፡ቢሆንም ቀጥታ ቀጣሪው ልጃቸው በፀሎት ነች፡፡እሷ ፍላጎቱን ተረድታ አፈቅርሀለው ብትለው እንኳን ፍቅሯ እሱ ለወላጆቾ በሚያደርገው የሞያ ድጋፍ ተፅዕኖ ስር የወደቀ ወይንም በይሉኝታ ስሜት የተቀነበበ ሊሆን ይችላል…ይሄንን ማንም በእርግጠኝነት ማወቅ አይችልም…በዚህም ምክንያት ከእሷ ጋር ደግሞ ያለው ግንኙነት እየሄደ ያለበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል፡፡ከሞያ ስነምግባር ውጭም እንደሆነ ያምናል፡፡ይሄ ጉዳይ ነው በጣም እያስጨነቀው ያለው፡፡ ከበፀሎት ጋር የፍቅር ስሜት በተሰማበት ቅፅበት ሁለት ምርጫ ነበረው፡፡አንድም በእሷ ቀጣሪነት ወላጆቾን ለማከም የተዋዋለውን የስራ ውል አፍርሶ ነፃ መውጣትና.. ከልሆነም ልቡን ገስፆ እና ፍቅሩን በውስጡ አክስሞ ስራው ላይ ብቻ አትኩሮ መቀጠል፡፡ቢያንስ ስራውን በተዋዋለው መሰረት ሙሉ በሙሉ አጠናቆ እስኪጨርስ ድረስ እንደዛ ነበር ማድረግ ያለበት፡፡ግን ይሄው ሁለቱንም ማድረግ አልቻለም፡፡ ‹‹ግን እኮ ይሄ በስራ አለም ቆይታዬ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀምኩት የሞያ ስነምግባር ጥሰት ነው››ሲል እራሱን ለማፅናናት ሞከረ…..፡፡ንግግሩ ግን እራሱንም ሊያሳምነው አልቻለም፡፡ ‹‹ስህተት የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻ ያው ስህተት ነው››የገዛ አእምሮ መልሶ የነገረው ነበር፡፡ ‹‹አሁን ወደኃላ መመለስ አልችልም…ይሄንን ጉዳይ ከዳር ላድርስና ..ከእሷ ጋር ያለኝ የፍቅር ግንኙነት የሚደርስበትን ከፍታ አይቼ ውጤታማ የሚሆን ከሆነ ምን አልባት ሞያውን በክብር ብለቅና ወደሌላ ዘርፍ ብሸጋገር እንኳን ያዋጣኛል››ሲል ለጊዜው የታየውን መፍትሄ አስቀመጠ…የገዛ አእምሮው ግን ወዲያው ነበር አፍራሽ የሆነ ሀሳብ የሰጠው‹‹ሰውዬ ምን ነካህ..?ይሄንን ሞያ ለቀህ…ነጋዴም ብትሆን …ወይም ደራሲ… ሁሉም ሞያ አይነቱ እና ተጋላጭነቱ በመጠኑ ይለያይ እንደሆን እንጂ የራሱ ህጋዊም ሆኑ ሞራላዊ የስነምግባር ገደቦች አሉበት…በተለይ ፍቅርን በተመለከተ ሁሉም ሞያ ይፈተናል…አስተማሪ ብትሆን ተማሪህ ላይ አይንህን መጣል የለብህም…ማናጀር ሆነህ ፀሀፊህን መጎነታተል ስህተት ነው፡፡ሞያህን ሳይሆን አመለካከትህን ነው መቀየር ያለብህ… ራስህን አታሞኝ፡፡››አለው…. ለጊዜው በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በላይ ማሰብ አልፈለገም….ጉዳዩን ለጊዜ አሳልፎ ሰጠና ብድርብሱን ተከናንቦ እራሱን ለእንቅልፉን አሳልፎ ሰጠ ....ወዲያው ነበር ያሸለበው…የሚገርመው ደግሞ አይኖቹ በተከደኑ ከሁለት ደቂቃ በኃላ ነበር በፀሎት ነጭ ቬሎ ለብሳ ጭንቅላቷ ላይ የሚያብረቀርቅ የወርቅ አክሊል አጥልቃ ግራና ቀኝ ጎኗ ላይ የበቀሉ ውብ ክንፏቾን እያማታች ከሰማዩ ላይ ሰንጥቃ መጥታ እቅፉ ውስጥ ስትገባ በህልሙ ያየው፡፡
///
በፀሎትና ለሊሴ ከወንጪ ከተመለሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡መሽተዋል…አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው…በፀሎት እና ፊራኦል ግቢው ውስጥ ካለ ግዙፍ የመንጎ ዛፍ ስር ጎን ለጎን ቁጭ ብለው እያወሩ ነው፡፡
‹‹እንዴት ነበር ወንጪ?››
‹‹ውይ ሲዊዘርላድ በለው፡፡››
‹‹እኔ ወንጪን እንጂ ሲዊዘርላንድን አላውቃትም፡፡››
‹‹አኔ ደግሞ አውቃታለዋ ለዛ ነው ያነፃፀርኩልህ..ደግሞ ዘመዶቻችን እንዴት ደግና ቀሽት መሰሉህ?፡፡››
‹‹የእኔም ዘመዶች እኮ ናቸው አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ቢሆንም ..አንተ ምንአልባት ከልጅነትህ ጀምሮ ስለምታውቃቸው …ብዙም ጣእም ላይሰጥህ ይችላል..ማለት ሁለም ሰው እንደእነሱ አይነት ዘመድ ያለው ስለሚመስልህ ተራ ነገር አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ….እንደእኔ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አይነት ዘመድ ሲኖርህ ግን በቃ ..ከአሁኑ እንዴት እንደናፈቁኝ ብታውቅ››
‹‹ገና በሁለት ቀን››
‹‹አዎ በሁለት ቀን››
‹‹አሁን ከእኛ ስትለይና ወደቤትሽ ስትሄጂ እንናፍቅሻለን ..?ማለት እኔ ናፍቅሻለሁ?››ለቀናት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው….?ወደየትኛው ቤቴ ነው የምሄደው?››
‹‹ወደቦሌው ቤትሽ››
‹‹ምን….ለሊሴ ነገረችህ››
‹‹እሷ ታውቃለች እንዴ?››
‹‹እሷ ካልነገረችሽ ታዲያ ማን ነገረህ?››
‹‹እራሴ ነኝ የደሰረስኩበት ..ወደ ወንጪ ከመሄዳችሁ በፊት ነው ያወቅኩት››
‹‹እኮ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?››
‹‹ያው እንዳልኩሽ የእህቴን ልብ ከተቀበልሽ በኃላ በሩቅ ሆኜ ለረጅም ጊዜ ስከታተልሽ ነበር..ስለዚህ በደንብ አውቅሻለው…እዚህ ቤት ከመጣሽ ከሳምንት በኃላ ጀምሮ ከፍተኛ ጥርጣሬ አድሮብኝ ነበር..ከዛ ምን አደረኩ አንድ ቀን ስትተኚ ሻርፕሽን ሙሉ በሙሉ ከፊትሽ ላይ ገፍፌ ተመለከትኩሽ…እና ኦርጅናለዋ በፀሎት መሆንሽን አረጋገጥኩ፡፡
‹‹ትገርማለህ..ከዛ ፀጥ አልክ?››
‹‹ምን ላድርግ…ምንም ማለትና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወቅኩም ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ አወቅክ?››
‹‹አይ….አንቺ ንገርኝ እስኪ …ምን ልታደርጊ ነው…?እስከመቼ ነው ከወላጆችሽ ምትደበቂው?››
‹‹ወላጆቼን በቀደም አግኝቼቸዋለው..እዚህ መሆኔን ያውቃሉ››ብላ ያልጠበቀውን ዜና ነገረችው፡፡
‹‹ጥሩ..እሺ እነአባዬን እንዴት ልታደርጊ ነው….?እንደዋሸሻቸው ሲያውቅ በጣም ነው የሚያዝኑብሽ…በአንቺ ብቻ ሳይሆን እኛም አውቀን ከነሱ ደብቀን ዝም በማለታችን ምን እንደሚወጥን አላውቅም? በጣም ጨንቆኛል›ብሎ እውነተኛ ስሜቱን ነገራት፡፡
‹‹ይቅርታ ፊራኦል..እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ስላስገባዋችሁ በጣም አዝናልው…ግን በዚህ ሁለት ሶስት ቀን ውስጥ እፈተዋለው…ማለት እናንተ ቀድማችሁ እንደምታውቁ ሳላሳውቅ እፈተዋለው››
‹‹እስኪ እናያለን…››
‹‹እኔ የእህትህን ልብ የተሸክምኩ በፀሎት መሆኔን እርግጠኛ ስትሆን ምን ተሰማህ?››
‹‹ግማሽ ሀዘን ግማሽ ደስታ››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ለረጂም ጊዜ ላናግርሽና ቀርቤ ላወራሽ የምመኝሽ የእህቴን ከፊል አካል የተሸከምሽው በፀሎት የገዛ ቤቴ መጥተሸ ከእኔ ጋር አንድ መአድ እየቆረሽ መሆንሽን ሳውቅ ፍጽም ድስታ ነው የተሰማኝ…በሌላ ጎኑ ደግሞ ያችኛዋን በፀሎት አፍቅሬት ስለነበር….ሌላ በፀሎት እንዳልሆንሽ ሳውቅ ቅር ብሎኛል››
‹‹ከመቀመጫዋ ተነሳችና እላዩ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመችው‹‹….የእኔ ወንድም
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ድክምክም ብሎታል፡፡ግን ደግሞ አልጋው ላይ ተኝቷ በሀሳብ እየተንገላታ ነው፡፡ ሰለሞን በሁለት በኩል ስለት ባለው ሰይፍ የሚጫወት ህፃን አይነት ሰው እንደሆነ እየተሰማው ነው፡፡ሞያውን በተመለከተ ለሶስት አመት በከፍተኛ የፕሮፌሽናል ደረጃ በምድረ-አሜሪካ ሲሰራ አንድም ጊዜ እንደዚህ አይነት ክፍተት ተከስቶበት አያውቅም..በዛም በራሱ ሲመካና ሲኮራ ኖሮ ነበር፡፡አሁን ግን ወደሀገሩ ተመልሶ ባጋጠሙት የመጀመሪያ ደንበኞቹ ከፍተኛ የሚባል ሽንቁር ተከስቶበታል፡፡አንድ ባለሞያ የሞያውን ስነምግባር አክብሮ ስራውን መስራት የሚገደደው ለደንበኞች ደህንነትንና ጥቅም ሲባል ብቻ አይደለም…ለራሱ ለሞያው ክብርና ተቀባይነትም እያንዳንዱ ባለሞያ የስራ-አፈፃፀም ሁኔታ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡በሙስናና በጥቅማጥቅም የሚታለሉ ዳኞችና አቃቢ-ህጎች በሞሉበት ሀገር ፍርድቤት ሊከበርና ሊታመን አይችልም፡፡ሌላውም ሞያ እንደዛው ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረ ያጋጠመችው ትልቋ ደንበኛው በፀሎት ነች፡፡እርግጥ ቀጥታ ደንበኛው እሷ ሳትሆን ወላጆቾ ናቸው፡፡ከእነሱ ጋር እየሰራ ያለውን ስራ የሞያው ስነምግባር በሚፈቅደው መንገድ ጥርትና ጥልል አድርጎ እየሰራ ነው፡፡ቢሆንም ቀጥታ ቀጣሪው ልጃቸው በፀሎት ነች፡፡እሷ ፍላጎቱን ተረድታ አፈቅርሀለው ብትለው እንኳን ፍቅሯ እሱ ለወላጆቾ በሚያደርገው የሞያ ድጋፍ ተፅዕኖ ስር የወደቀ ወይንም በይሉኝታ ስሜት የተቀነበበ ሊሆን ይችላል…ይሄንን ማንም በእርግጠኝነት ማወቅ አይችልም…በዚህም ምክንያት ከእሷ ጋር ደግሞ ያለው ግንኙነት እየሄደ ያለበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል፡፡ከሞያ ስነምግባር ውጭም እንደሆነ ያምናል፡፡ይሄ ጉዳይ ነው በጣም እያስጨነቀው ያለው፡፡ ከበፀሎት ጋር የፍቅር ስሜት በተሰማበት ቅፅበት ሁለት ምርጫ ነበረው፡፡አንድም በእሷ ቀጣሪነት ወላጆቾን ለማከም የተዋዋለውን የስራ ውል አፍርሶ ነፃ መውጣትና.. ከልሆነም ልቡን ገስፆ እና ፍቅሩን በውስጡ አክስሞ ስራው ላይ ብቻ አትኩሮ መቀጠል፡፡ቢያንስ ስራውን በተዋዋለው መሰረት ሙሉ በሙሉ አጠናቆ እስኪጨርስ ድረስ እንደዛ ነበር ማድረግ ያለበት፡፡ግን ይሄው ሁለቱንም ማድረግ አልቻለም፡፡ ‹‹ግን እኮ ይሄ በስራ አለም ቆይታዬ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀምኩት የሞያ ስነምግባር ጥሰት ነው››ሲል እራሱን ለማፅናናት ሞከረ…..፡፡ንግግሩ ግን እራሱንም ሊያሳምነው አልቻለም፡፡ ‹‹ስህተት የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻ ያው ስህተት ነው››የገዛ አእምሮ መልሶ የነገረው ነበር፡፡ ‹‹አሁን ወደኃላ መመለስ አልችልም…ይሄንን ጉዳይ ከዳር ላድርስና ..ከእሷ ጋር ያለኝ የፍቅር ግንኙነት የሚደርስበትን ከፍታ አይቼ ውጤታማ የሚሆን ከሆነ ምን አልባት ሞያውን በክብር ብለቅና ወደሌላ ዘርፍ ብሸጋገር እንኳን ያዋጣኛል››ሲል ለጊዜው የታየውን መፍትሄ አስቀመጠ…የገዛ አእምሮው ግን ወዲያው ነበር አፍራሽ የሆነ ሀሳብ የሰጠው‹‹ሰውዬ ምን ነካህ..?ይሄንን ሞያ ለቀህ…ነጋዴም ብትሆን …ወይም ደራሲ… ሁሉም ሞያ አይነቱ እና ተጋላጭነቱ በመጠኑ ይለያይ እንደሆን እንጂ የራሱ ህጋዊም ሆኑ ሞራላዊ የስነምግባር ገደቦች አሉበት…በተለይ ፍቅርን በተመለከተ ሁሉም ሞያ ይፈተናል…አስተማሪ ብትሆን ተማሪህ ላይ አይንህን መጣል የለብህም…ማናጀር ሆነህ ፀሀፊህን መጎነታተል ስህተት ነው፡፡ሞያህን ሳይሆን አመለካከትህን ነው መቀየር ያለብህ… ራስህን አታሞኝ፡፡››አለው…. ለጊዜው በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በላይ ማሰብ አልፈለገም….ጉዳዩን ለጊዜ አሳልፎ ሰጠና ብድርብሱን ተከናንቦ እራሱን ለእንቅልፉን አሳልፎ ሰጠ ....ወዲያው ነበር ያሸለበው…የሚገርመው ደግሞ አይኖቹ በተከደኑ ከሁለት ደቂቃ በኃላ ነበር በፀሎት ነጭ ቬሎ ለብሳ ጭንቅላቷ ላይ የሚያብረቀርቅ የወርቅ አክሊል አጥልቃ ግራና ቀኝ ጎኗ ላይ የበቀሉ ውብ ክንፏቾን እያማታች ከሰማዩ ላይ ሰንጥቃ መጥታ እቅፉ ውስጥ ስትገባ በህልሙ ያየው፡፡
///
በፀሎትና ለሊሴ ከወንጪ ከተመለሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡መሽተዋል…አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው…በፀሎት እና ፊራኦል ግቢው ውስጥ ካለ ግዙፍ የመንጎ ዛፍ ስር ጎን ለጎን ቁጭ ብለው እያወሩ ነው፡፡
‹‹እንዴት ነበር ወንጪ?››
‹‹ውይ ሲዊዘርላድ በለው፡፡››
‹‹እኔ ወንጪን እንጂ ሲዊዘርላንድን አላውቃትም፡፡››
‹‹አኔ ደግሞ አውቃታለዋ ለዛ ነው ያነፃፀርኩልህ..ደግሞ ዘመዶቻችን እንዴት ደግና ቀሽት መሰሉህ?፡፡››
‹‹የእኔም ዘመዶች እኮ ናቸው አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ቢሆንም ..አንተ ምንአልባት ከልጅነትህ ጀምሮ ስለምታውቃቸው …ብዙም ጣእም ላይሰጥህ ይችላል..ማለት ሁለም ሰው እንደእነሱ አይነት ዘመድ ያለው ስለሚመስልህ ተራ ነገር አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ….እንደእኔ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አይነት ዘመድ ሲኖርህ ግን በቃ ..ከአሁኑ እንዴት እንደናፈቁኝ ብታውቅ››
‹‹ገና በሁለት ቀን››
‹‹አዎ በሁለት ቀን››
‹‹አሁን ከእኛ ስትለይና ወደቤትሽ ስትሄጂ እንናፍቅሻለን ..?ማለት እኔ ናፍቅሻለሁ?››ለቀናት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው….?ወደየትኛው ቤቴ ነው የምሄደው?››
‹‹ወደቦሌው ቤትሽ››
‹‹ምን….ለሊሴ ነገረችህ››
‹‹እሷ ታውቃለች እንዴ?››
‹‹እሷ ካልነገረችሽ ታዲያ ማን ነገረህ?››
‹‹እራሴ ነኝ የደሰረስኩበት ..ወደ ወንጪ ከመሄዳችሁ በፊት ነው ያወቅኩት››
‹‹እኮ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?››
‹‹ያው እንዳልኩሽ የእህቴን ልብ ከተቀበልሽ በኃላ በሩቅ ሆኜ ለረጅም ጊዜ ስከታተልሽ ነበር..ስለዚህ በደንብ አውቅሻለው…እዚህ ቤት ከመጣሽ ከሳምንት በኃላ ጀምሮ ከፍተኛ ጥርጣሬ አድሮብኝ ነበር..ከዛ ምን አደረኩ አንድ ቀን ስትተኚ ሻርፕሽን ሙሉ በሙሉ ከፊትሽ ላይ ገፍፌ ተመለከትኩሽ…እና ኦርጅናለዋ በፀሎት መሆንሽን አረጋገጥኩ፡፡
‹‹ትገርማለህ..ከዛ ፀጥ አልክ?››
‹‹ምን ላድርግ…ምንም ማለትና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወቅኩም ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ አወቅክ?››
‹‹አይ….አንቺ ንገርኝ እስኪ …ምን ልታደርጊ ነው…?እስከመቼ ነው ከወላጆችሽ ምትደበቂው?››
‹‹ወላጆቼን በቀደም አግኝቼቸዋለው..እዚህ መሆኔን ያውቃሉ››ብላ ያልጠበቀውን ዜና ነገረችው፡፡
‹‹ጥሩ..እሺ እነአባዬን እንዴት ልታደርጊ ነው….?እንደዋሸሻቸው ሲያውቅ በጣም ነው የሚያዝኑብሽ…በአንቺ ብቻ ሳይሆን እኛም አውቀን ከነሱ ደብቀን ዝም በማለታችን ምን እንደሚወጥን አላውቅም? በጣም ጨንቆኛል›ብሎ እውነተኛ ስሜቱን ነገራት፡፡
‹‹ይቅርታ ፊራኦል..እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ስላስገባዋችሁ በጣም አዝናልው…ግን በዚህ ሁለት ሶስት ቀን ውስጥ እፈተዋለው…ማለት እናንተ ቀድማችሁ እንደምታውቁ ሳላሳውቅ እፈተዋለው››
‹‹እስኪ እናያለን…››
‹‹እኔ የእህትህን ልብ የተሸክምኩ በፀሎት መሆኔን እርግጠኛ ስትሆን ምን ተሰማህ?››
‹‹ግማሽ ሀዘን ግማሽ ደስታ››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ለረጂም ጊዜ ላናግርሽና ቀርቤ ላወራሽ የምመኝሽ የእህቴን ከፊል አካል የተሸከምሽው በፀሎት የገዛ ቤቴ መጥተሸ ከእኔ ጋር አንድ መአድ እየቆረሽ መሆንሽን ሳውቅ ፍጽም ድስታ ነው የተሰማኝ…በሌላ ጎኑ ደግሞ ያችኛዋን በፀሎት አፍቅሬት ስለነበር….ሌላ በፀሎት እንዳልሆንሽ ሳውቅ ቅር ብሎኛል››
‹‹ከመቀመጫዋ ተነሳችና እላዩ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመችው‹‹….የእኔ ወንድም
👍66❤14🥰2👏2
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
==================
ተው በአያትህ አትፍረድ…ማንኛውም በቃኝ መመልኮስ ፈልጋለው ብሎ እራሱን ከአለም ለመለየት የወሰነ ሰው ማድረግ ያለበት ልክ እሷቸው እንዳደረጉት ነው፡፡የምልኩስና ህይወትን ለመንፈሳዊ መንገድ ራስን አሳልፎ መስጠት ነው፡፡ከአለም ሆነ ከገዛ ዘመድ ምንም ነገር አለመጠበቅ ነው፡፡ከዛም አልፎ ለአለምም ሆነ ለገዛ ዘመድ ምንም አይነት ኃላፊነት አለመቀበል ማለት ነው፡፡አንድ ሰው ከመለኮሰ ልጄ ለምን ሳይጦረኝ ወንድሜ ለምን ሳይጠይቀኝ ብሎ የመጠየቅም ሆነ የመውቀስ መብት የለውም..በዛውም ልክ እናቴን መጦር ነበረብኝ..ወንድሜን መርዳት ይጠበቅብኛል..የልጅ ልጆቼን መንከባከብ የእኔ ኃላፊነት ነው ከሚለው ማህበራዊ ኃላፊነቶችም ራሱን ነፃ ማድረግ አለበት፡፡
ሙሉ ትኩረቱ መንፈሳዊ ብልፅግና እራስን ማጎልበት ላይ መሆን አለበት፡፡ለዘመዱም ሆነ ለመላ አለሙ እኩል ፀሎት ማድረግ ነው የሚጠበቅባቸው፡፡ስለክርስቶስ ፍቅር መትጋት ፤ዳቢሎስ ለመጥላትና ለመርገም ግን ጊዜ ከማባከን መቆጠብ ነው ከእነሱ የምጠበቀው…ምክንያቱም በአንድ ንፅህ ልብ ፍቅርና ጥላቻ እውነትና ሀሰት ክፋትና መልካምነት ተጎራብተው መኖር አይቻላቸውምና፡፡ሁለቱንም አቻችሎ እያኖረ ያለ ልብ የመንፈሳዊ ሰው ልብ ሊባል አይችልም፡፡እና በአያትህ ውሳኔና ድርጊት ቅንጣት ያህል ቅሬታ እንዳያድርብህ ..እንደውም በተቃራኒው በረከታቸው እንዲጠብቅህ ብቻ ነው መመኘት ያለብህ››
‹‹ትክክል ነሽ እቴቴ…ለማንኛውም አንቺን ደጋግሜ አመሰግናለሁ››
‹‹እኔም አመሰግናለው ልጄ….ይሄ ፀባይህ መቼም እንዳይቀየር .አሁን ምን ማድረግ እንዳለብህ የምትወስነው አንተ ነህ…እንደእኔ እንደእኔ ኮሌጅ ገብተህ የሙያ ትምህርት ለመማር በመወሰንህ በጣም ጥሩ ነው…ሞያ ያለው ሰው ወድቆ አይወድቅም…ቢያንስ የሆነ ተባራሪ ስራ ሰርቶ ወይም የሆነ ነገር ጠጋግኖ የእለት ጉርሱን ያገኛል..ቀስ እያልክ ደግሞ በሂደት የራስህን ድርጅት የማቋቋም እድልም ይኖርሀል….እና እኔ እናትህ ሁሌም በውሳኔህ አብሬህ ነኝ፡፡››
‹‹አቴቴ አታስቢ ከሰሎሜና ከአላዛር ጋር ተነጋግረን ወስነናል…የሆነ ሞያ እንማራለን ››
‹‹ጎሽ ልጄ እንደዛ ነው…ሰሎሜንም ስለምትንከባከባት አመሰግናለሁ››
‹‹እንዴ እቴቴ እህቴ አይደለችም እንዴ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…እንደውም ትልቁ ላመሰግንህ የሚገባው እሷን በተመለከተ ነው…እናንተ ላትሰሙ ትችላላችሁ ፡፡ከጎረመሰችና ለአቅመ አዳምና ሄዋን ከደረሳችሁ በኃላ የሰፈሩ ሰው በሰበብ አስባብ እያደረገ…‹‹ይሄ ጎረምሳ ልጇን አስረግዞ ጉድ ያደርጋታል….››ሲሉኝ፡፡‹‹እንዚህ ልጆች እንዳይሳሳቱና አጉል ችግር ውስጥ እንዳይከቱሽ›› እያሉ ሲመክሩኝ፡፡እኔ ግን ከልጄ ይልቅ በአንተ ላይ ሙሉ እምነት ነበረኝ…አለማየሁማ እኔ እናቱን እንዳፍርና አንገቴን አንቄ እራሴን እንዳጠፋ አያደርገኝም….የገዛ እህቱን የሆነ ነገር አድርጎ የሰፈርተኛውን ሟርት እውን በማድረግ እኔ እናቱን ወደመቃብር አይልከኝም››የሚል ፅኑ እምነት ነበረኝ፡፡እናም ቤተክርስቲያን ስሄድ ጌታ ሆይ ለሁለቱም ልጆቼ ልቦና ስጥልኝ ብዬ ከመፀለይ ውጭ በእናንተ ላይ ምንም አይነት ተፅእኖም ሆነ ክትትል አድርጌ አላውቅም ፤ወደፊትም ስለማምናችሁ ስጋት የለብኝም…እና ለዚህም አመሰግናለው፡፡
አለማየሁ አቴቴ ስለእሱና ስለሰሎሜ እያንዳንዱን ቃላት ከአንደበታቸው አውጥተው በተናገሩት ቁጥር ከልቡ የተወሰነ አካሉ እየተሸራረፈ ሲረግፍ ይታወቀው ነበር..በቃ የአላዛር የእንጀራ እናት ከቀናት በፊት የሰነጣጠቀችው ልቡን አሁን ሙሉ በሙሉ ተሰባበረ፡፡ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሁለቱም የፍቅር ክንፎቹ ተቆርጦ ሲወድቅበት ..መቋቋም ከሚችለው በላይ ፍፅም ተስፋ መቁረት ውስጥ ነው የገባው፡፡‹‹እቴቴ ..ይሄን ሁሉ ሰቀቀን ስላሳለፍሽ ቅርታ….አይዞሽ አታስቢ …እኔ ልጅሽ ነኝ ልጅሽም እንደሆንኩ እቀጥላለሁ፡፡››ሲል ነበር በደመነፍስ ቃል የገባላቸው፡፡
በዚህ ሁኔታ ነበር ሁለቱም ተመሰጋግነውና ተላቅሰው ከቤተክርሰቲያን የተመለሱት፡፡
ከዛ በኃላ ግን አለማየሁ ሁሉም ነገሩ ነው የተመሰቃቀለበት፡፡ማትሪክ ውጤት አይቶ ዩኒቨርሲቲ መግባት እንደማይችል ያወቀ ሰሞን እንኳን እንዲህ መላ ነገሩ አልተተረማመሰም፡፡ከአላዛር እንጀራ እናት በተለያየበት ቀንም የተወሰነ የሚመረኮዘው ተስፋ ነበርው…ከቴቴ ጋር ካወራ በኃላ ግን በቃል ታስሮል….ከሚወዱትና ከሚያከብሩት ሰው አንደበት የወጣ ቃል ደግሞ ከፖሊስ ካቴና የጠበቀ ቀፍድዶ የሚያስር ነው፡፡አሁን ለአስራዘጠኝ አመት ሲንከባከበውና ሲፋለምለት ከነበረው የፍቅር ሀዲድ ተገፍትሮ ወጥቷል…፡፡የሰሎሜን ፍቅር ከልቡ አውጥቶ በአንደበቱ ማወጅ አይችልም…፡፡እንደዛ ካደረገ እናቷን ማሳዘን አንገት ማስደፋት እንደሆነ ገብቷታል፡፡ከሁለት አንዱን መምረጥ ያለበት ጊዜ ላይ እንደሆነ አውቆል፡፡
ልክ የሀይስኩል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቀ. ለሰሎሜ ያለውን ፍቅር ለማፈንዳትና እሷን ከተቀናቃኞቹ ሁሴንና አላዛር ፈልቅቆ ራሱ ለማድረግ የአመታት እቅድ ነበረው…ያ ቀን እስኪደርስ በመመኘት ብዙ ቀን እንቅልፍ አጥቶል፡፡ በስንት ጣር ቀኑ ሲደርስ ግን እናቷ ያልጠበቀውን ዱብ እዳ ነገሩት፡፡እሱ እንደውም ይሰጋ የነበረው እንዲህ አይነት ነገር ተፈጥሮ ከሰሎሜ ፍቅር ይነጥለኛል ብሎ ሳይሆን ከአስካለ ጋር የነበረው የድብቅ ፍቅር ሰሎሜ ጆሮ ገብቶ እሷን ያሳጣኝ ይሆን ብሎ ነበር፡፡
ግን ይሄው ጨርሶ ባልጠበቀው መንገድ አሳዳጊ እናቱ እቴቴ እሱና ሰሎሜ በእህት እና ወንድም ስሌት እንዲቀጥሉ እንጂ ፍቅር የሚባል ነገር በመሀከላቸው እንዲበቅል ምንም ፍላጎት እንደሌላቸውና እንደውም እስከሞት ሚያደርስ ሀዘን ላይ እንደሚጥላቸው ግልፅ ባለ አማርኛ ነገርውታል፡፡
እሱ ብቻ ሳይሆን የገዛ ጓደኞቹ አላዛርና ሁሴንም እንደሚያፈቅሯትን በቅርብ በማንኛውም ጊዜ ፍቅራቸውን እንደሚናዘዙላት ያውቃል፡፡ለዚህ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ሶስቱም እሷን እንደሚያፈቅሮት ስለሚያውቁና እርስ በርስም ለዘመናት ሲነጋገሩና ሲወያዩ በመኖራቸው…‹‹.ስንጠይቃት ለየት ያለ ዝግጅት አዘጋጅተን..ሶስታችንም በአንድ ቃል..ሰሎሜ እኛ ሶስቱ ጓደኞችሽ አንቺን ከልጅነታችን ጀምሮ እናፈቅርሻለኝ… ሶስታችንም የእኛ እንድትሆኚ እንፈልጋለን፡፡አንቺ ከሶስታችንን ማንን ትመርጫለሽ…?በውሳኔሽ እንስማማለን፡፡አስበሽበት ከሶስታችን ማንኛችንን እንደምትመርጪ አሳውቂን ››ብለው ሰርፕራይዝ ሊያደርጓትና የመምረጡን እድል ለእሷ ሊሰጡ ገና ዘጠነኛ ክፍል እያሉ ነበር ቃል የተገባቡት፡፡
እና ከእቴቴ ጋር ከማውራቱ ከሳምንት በፊት በሁሴን ሽኝት ላይ ይሄንን ጉዳይ አንስተው ደግሞው ተነጋገርውበት ነበር፡፡ሁሴንም‹‹በቃ አንድ ሴሚስተር ተምሬ ከጨረስኩ በኃላ በሴሚስተር ዝግ ስመጣ እንደተባባልነው እናዳርጋለን›› ብሏቸዋል…እነሱም በሀሳቡ ተስማምተው ነበር፡፡ እስከዛ ማንም አፈቅርሻለው ብሎ እንዳይነግራት ተማምለው ከእንደገና ቃላቸውን አድሰው ነበር፡፡እና በዚህ ሁሉ ውይይትና ንግግር ሰሎሜ አሱን እንደምትመርጥ ከእነሱ በላይ ሰባና ሰማኒያ ፐርሰንት እድል እንዳለው ያምን ነበር..እንደዛ እንዲያስብ ያደረገው ደግሞ ከጓደኝነታቸውም በላይ እንደእህትና ወንድም አንድ ቤት በመኖራቸው..ቀን ብቻ ሳይሆን ምሽትም ለሊትም አንድ ቤት ውስጥ ስለሚሆኑ …ታፋው ላይ ያለውን ጠባሳ ስለምታውቅና ከጡቷ ዝቅ ብሎ ያለውን የማሪያም ስሞሽ ሰልሚያውቅ…ጭምር ነበር የእሷ ተመራጭ እሱ እንደሚሆን እርግጠኛ የሆነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
==================
ተው በአያትህ አትፍረድ…ማንኛውም በቃኝ መመልኮስ ፈልጋለው ብሎ እራሱን ከአለም ለመለየት የወሰነ ሰው ማድረግ ያለበት ልክ እሷቸው እንዳደረጉት ነው፡፡የምልኩስና ህይወትን ለመንፈሳዊ መንገድ ራስን አሳልፎ መስጠት ነው፡፡ከአለም ሆነ ከገዛ ዘመድ ምንም ነገር አለመጠበቅ ነው፡፡ከዛም አልፎ ለአለምም ሆነ ለገዛ ዘመድ ምንም አይነት ኃላፊነት አለመቀበል ማለት ነው፡፡አንድ ሰው ከመለኮሰ ልጄ ለምን ሳይጦረኝ ወንድሜ ለምን ሳይጠይቀኝ ብሎ የመጠየቅም ሆነ የመውቀስ መብት የለውም..በዛውም ልክ እናቴን መጦር ነበረብኝ..ወንድሜን መርዳት ይጠበቅብኛል..የልጅ ልጆቼን መንከባከብ የእኔ ኃላፊነት ነው ከሚለው ማህበራዊ ኃላፊነቶችም ራሱን ነፃ ማድረግ አለበት፡፡
ሙሉ ትኩረቱ መንፈሳዊ ብልፅግና እራስን ማጎልበት ላይ መሆን አለበት፡፡ለዘመዱም ሆነ ለመላ አለሙ እኩል ፀሎት ማድረግ ነው የሚጠበቅባቸው፡፡ስለክርስቶስ ፍቅር መትጋት ፤ዳቢሎስ ለመጥላትና ለመርገም ግን ጊዜ ከማባከን መቆጠብ ነው ከእነሱ የምጠበቀው…ምክንያቱም በአንድ ንፅህ ልብ ፍቅርና ጥላቻ እውነትና ሀሰት ክፋትና መልካምነት ተጎራብተው መኖር አይቻላቸውምና፡፡ሁለቱንም አቻችሎ እያኖረ ያለ ልብ የመንፈሳዊ ሰው ልብ ሊባል አይችልም፡፡እና በአያትህ ውሳኔና ድርጊት ቅንጣት ያህል ቅሬታ እንዳያድርብህ ..እንደውም በተቃራኒው በረከታቸው እንዲጠብቅህ ብቻ ነው መመኘት ያለብህ››
‹‹ትክክል ነሽ እቴቴ…ለማንኛውም አንቺን ደጋግሜ አመሰግናለሁ››
‹‹እኔም አመሰግናለው ልጄ….ይሄ ፀባይህ መቼም እንዳይቀየር .አሁን ምን ማድረግ እንዳለብህ የምትወስነው አንተ ነህ…እንደእኔ እንደእኔ ኮሌጅ ገብተህ የሙያ ትምህርት ለመማር በመወሰንህ በጣም ጥሩ ነው…ሞያ ያለው ሰው ወድቆ አይወድቅም…ቢያንስ የሆነ ተባራሪ ስራ ሰርቶ ወይም የሆነ ነገር ጠጋግኖ የእለት ጉርሱን ያገኛል..ቀስ እያልክ ደግሞ በሂደት የራስህን ድርጅት የማቋቋም እድልም ይኖርሀል….እና እኔ እናትህ ሁሌም በውሳኔህ አብሬህ ነኝ፡፡››
‹‹አቴቴ አታስቢ ከሰሎሜና ከአላዛር ጋር ተነጋግረን ወስነናል…የሆነ ሞያ እንማራለን ››
‹‹ጎሽ ልጄ እንደዛ ነው…ሰሎሜንም ስለምትንከባከባት አመሰግናለሁ››
‹‹እንዴ እቴቴ እህቴ አይደለችም እንዴ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…እንደውም ትልቁ ላመሰግንህ የሚገባው እሷን በተመለከተ ነው…እናንተ ላትሰሙ ትችላላችሁ ፡፡ከጎረመሰችና ለአቅመ አዳምና ሄዋን ከደረሳችሁ በኃላ የሰፈሩ ሰው በሰበብ አስባብ እያደረገ…‹‹ይሄ ጎረምሳ ልጇን አስረግዞ ጉድ ያደርጋታል….››ሲሉኝ፡፡‹‹እንዚህ ልጆች እንዳይሳሳቱና አጉል ችግር ውስጥ እንዳይከቱሽ›› እያሉ ሲመክሩኝ፡፡እኔ ግን ከልጄ ይልቅ በአንተ ላይ ሙሉ እምነት ነበረኝ…አለማየሁማ እኔ እናቱን እንዳፍርና አንገቴን አንቄ እራሴን እንዳጠፋ አያደርገኝም….የገዛ እህቱን የሆነ ነገር አድርጎ የሰፈርተኛውን ሟርት እውን በማድረግ እኔ እናቱን ወደመቃብር አይልከኝም››የሚል ፅኑ እምነት ነበረኝ፡፡እናም ቤተክርስቲያን ስሄድ ጌታ ሆይ ለሁለቱም ልጆቼ ልቦና ስጥልኝ ብዬ ከመፀለይ ውጭ በእናንተ ላይ ምንም አይነት ተፅእኖም ሆነ ክትትል አድርጌ አላውቅም ፤ወደፊትም ስለማምናችሁ ስጋት የለብኝም…እና ለዚህም አመሰግናለው፡፡
አለማየሁ አቴቴ ስለእሱና ስለሰሎሜ እያንዳንዱን ቃላት ከአንደበታቸው አውጥተው በተናገሩት ቁጥር ከልቡ የተወሰነ አካሉ እየተሸራረፈ ሲረግፍ ይታወቀው ነበር..በቃ የአላዛር የእንጀራ እናት ከቀናት በፊት የሰነጣጠቀችው ልቡን አሁን ሙሉ በሙሉ ተሰባበረ፡፡ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሁለቱም የፍቅር ክንፎቹ ተቆርጦ ሲወድቅበት ..መቋቋም ከሚችለው በላይ ፍፅም ተስፋ መቁረት ውስጥ ነው የገባው፡፡‹‹እቴቴ ..ይሄን ሁሉ ሰቀቀን ስላሳለፍሽ ቅርታ….አይዞሽ አታስቢ …እኔ ልጅሽ ነኝ ልጅሽም እንደሆንኩ እቀጥላለሁ፡፡››ሲል ነበር በደመነፍስ ቃል የገባላቸው፡፡
በዚህ ሁኔታ ነበር ሁለቱም ተመሰጋግነውና ተላቅሰው ከቤተክርሰቲያን የተመለሱት፡፡
ከዛ በኃላ ግን አለማየሁ ሁሉም ነገሩ ነው የተመሰቃቀለበት፡፡ማትሪክ ውጤት አይቶ ዩኒቨርሲቲ መግባት እንደማይችል ያወቀ ሰሞን እንኳን እንዲህ መላ ነገሩ አልተተረማመሰም፡፡ከአላዛር እንጀራ እናት በተለያየበት ቀንም የተወሰነ የሚመረኮዘው ተስፋ ነበርው…ከቴቴ ጋር ካወራ በኃላ ግን በቃል ታስሮል….ከሚወዱትና ከሚያከብሩት ሰው አንደበት የወጣ ቃል ደግሞ ከፖሊስ ካቴና የጠበቀ ቀፍድዶ የሚያስር ነው፡፡አሁን ለአስራዘጠኝ አመት ሲንከባከበውና ሲፋለምለት ከነበረው የፍቅር ሀዲድ ተገፍትሮ ወጥቷል…፡፡የሰሎሜን ፍቅር ከልቡ አውጥቶ በአንደበቱ ማወጅ አይችልም…፡፡እንደዛ ካደረገ እናቷን ማሳዘን አንገት ማስደፋት እንደሆነ ገብቷታል፡፡ከሁለት አንዱን መምረጥ ያለበት ጊዜ ላይ እንደሆነ አውቆል፡፡
ልክ የሀይስኩል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቀ. ለሰሎሜ ያለውን ፍቅር ለማፈንዳትና እሷን ከተቀናቃኞቹ ሁሴንና አላዛር ፈልቅቆ ራሱ ለማድረግ የአመታት እቅድ ነበረው…ያ ቀን እስኪደርስ በመመኘት ብዙ ቀን እንቅልፍ አጥቶል፡፡ በስንት ጣር ቀኑ ሲደርስ ግን እናቷ ያልጠበቀውን ዱብ እዳ ነገሩት፡፡እሱ እንደውም ይሰጋ የነበረው እንዲህ አይነት ነገር ተፈጥሮ ከሰሎሜ ፍቅር ይነጥለኛል ብሎ ሳይሆን ከአስካለ ጋር የነበረው የድብቅ ፍቅር ሰሎሜ ጆሮ ገብቶ እሷን ያሳጣኝ ይሆን ብሎ ነበር፡፡
ግን ይሄው ጨርሶ ባልጠበቀው መንገድ አሳዳጊ እናቱ እቴቴ እሱና ሰሎሜ በእህት እና ወንድም ስሌት እንዲቀጥሉ እንጂ ፍቅር የሚባል ነገር በመሀከላቸው እንዲበቅል ምንም ፍላጎት እንደሌላቸውና እንደውም እስከሞት ሚያደርስ ሀዘን ላይ እንደሚጥላቸው ግልፅ ባለ አማርኛ ነገርውታል፡፡
እሱ ብቻ ሳይሆን የገዛ ጓደኞቹ አላዛርና ሁሴንም እንደሚያፈቅሯትን በቅርብ በማንኛውም ጊዜ ፍቅራቸውን እንደሚናዘዙላት ያውቃል፡፡ለዚህ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ሶስቱም እሷን እንደሚያፈቅሮት ስለሚያውቁና እርስ በርስም ለዘመናት ሲነጋገሩና ሲወያዩ በመኖራቸው…‹‹.ስንጠይቃት ለየት ያለ ዝግጅት አዘጋጅተን..ሶስታችንም በአንድ ቃል..ሰሎሜ እኛ ሶስቱ ጓደኞችሽ አንቺን ከልጅነታችን ጀምሮ እናፈቅርሻለኝ… ሶስታችንም የእኛ እንድትሆኚ እንፈልጋለን፡፡አንቺ ከሶስታችንን ማንን ትመርጫለሽ…?በውሳኔሽ እንስማማለን፡፡አስበሽበት ከሶስታችን ማንኛችንን እንደምትመርጪ አሳውቂን ››ብለው ሰርፕራይዝ ሊያደርጓትና የመምረጡን እድል ለእሷ ሊሰጡ ገና ዘጠነኛ ክፍል እያሉ ነበር ቃል የተገባቡት፡፡
እና ከእቴቴ ጋር ከማውራቱ ከሳምንት በፊት በሁሴን ሽኝት ላይ ይሄንን ጉዳይ አንስተው ደግሞው ተነጋገርውበት ነበር፡፡ሁሴንም‹‹በቃ አንድ ሴሚስተር ተምሬ ከጨረስኩ በኃላ በሴሚስተር ዝግ ስመጣ እንደተባባልነው እናዳርጋለን›› ብሏቸዋል…እነሱም በሀሳቡ ተስማምተው ነበር፡፡ እስከዛ ማንም አፈቅርሻለው ብሎ እንዳይነግራት ተማምለው ከእንደገና ቃላቸውን አድሰው ነበር፡፡እና በዚህ ሁሉ ውይይትና ንግግር ሰሎሜ አሱን እንደምትመርጥ ከእነሱ በላይ ሰባና ሰማኒያ ፐርሰንት እድል እንዳለው ያምን ነበር..እንደዛ እንዲያስብ ያደረገው ደግሞ ከጓደኝነታቸውም በላይ እንደእህትና ወንድም አንድ ቤት በመኖራቸው..ቀን ብቻ ሳይሆን ምሽትም ለሊትም አንድ ቤት ውስጥ ስለሚሆኑ …ታፋው ላይ ያለውን ጠባሳ ስለምታውቅና ከጡቷ ዝቅ ብሎ ያለውን የማሪያም ስሞሽ ሰልሚያውቅ…ጭምር ነበር የእሷ ተመራጭ እሱ እንደሚሆን እርግጠኛ የሆነው፡፡
👍68❤11
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
ወንጀሉ በተፈፀመ በ15ተኛው ቀን ለአለማየሁ ደውሎለት ነበር፡፡
‹‹ሄሎ አሌክስ..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ..አንተስ..?ሰፍር ?እነሰሎሜ ደህና ናቸው?››
‹‹ሁሉም ሰላም ነው….አንተ ጋርስ? ስልጠናው እንዴት ነው?››
‹‹ከባድ ነው.. ግን ያው ስፖርት ስለምወድ…ለእኔ ብዙም አልከበደኝም፡፡››
‹‹ጥሩ…..››
‹‹ምነው የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ ?ድምፅህ እኮ ጥሩ አይደለም…ሰሎሜ ምን ሆነች?››
‹‹አይ እሷ ደህና ነች..አባቴ ነው፡፡››
‹‹አባትህ ምን ሆኑ?
አመማቸው?››
‹‹አልታመመም..ግን የሆነ ወንጀል ሰርቷል..ያንን ወንጀል መስራቱን እኔ ብቻ ነኝ ማውቀው..አሳልፌ ለፖሊስ ልስጠው ወይስ ዝም ብዬ ልቀመጥ? ግራ ገብቷኛል…ምክር እንድትሰጠኝ ነው የደወልኩት..በዚህ ጉዳይ ላይ አንተን ብቻ ነው የማምነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ወንጀል ?ከባድ ነው?››
‹‹በጣም ከባድ….እጅግ በጣም ከባድ…በእድሜ ልክ ወይም በሞት የሚያስቃጣ ወንጀል፡፡››
‹‹ግን እኮ አላዛር..አባትህ ትልቅ ሰው ናቸው..በዚህ እድሜቸው የእስር ቤትን ህይወት አይችሉም ..ወዲያው ነው የሚሞቱት…ለመሆኑ ወንጀሉ ምንድነው?››
‹‹የእንጀራ እናቴን ታስታውሳታለህ?››
አላዛር ስለእንጀራ እናቱ ሲያነሳ አለማየሁ ጠቅላላ ሰውነት ጆሮ ነው የሆነው፡፡ፈራ ተባ እያለ‹‹አዎ አስታውሳታለው..ምን ሆነች?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹አርግዛ ነበር››
የሚያውቀው ነገር ቢሆንም በተሳሰረና በተወለካከፈ ድምፅ ‹‹በእውነት….?እሱን አላውቅም ነበር››አለው፡፡
‹‹አዎ እኔም አላውቅም ነበር…እና ያረገዘችው ከሌላ ሰው ነው፡፡››
‹‹ከሌላ ሰው ?ከማን …?›
‹‹እሱን እኔ አላውቅም ..አባቴም የሚያውቅ አይመስለኝም….››
በሚርገበገብ ድምፁ በፍራቻ ‹‹እና ምን ተፈጠረ…?››ሲል ጠየቀው፡
‹‹አባቴ ልጁ የእሱ እንዳልሆነ በምን መንገድ እንደሆነ አላውቅም አወቀና ..እርጉዟን ሚስቱን ገደላት››
‹‹ምን ?ገደላት….››
‹‹አዎ ገድሎ የማላውቀው ቦታ ቀብሮታል….አሁን እሱም ሀገር ጥሎ ጠፍቶል..እና ምን እንዳደርግ ትመክረኛለህ?፡፡››
አለማየሁ በሰማው መርዶ የደነገጠው ድንጋጤ መጠን የሌለው ነው..እናትና አባቱ የሞቱ ሰሞን እንኳን እንደዛ አይነት ፍፅም ቀዝቃዛ ሀዘን አልተሰማውም ነበር ‹‹እሳቸው ሳይሆኑ እኔ ነኝ የገደልኩሽ፡፡››ሲል አሰበ፡፡
ድምፅ የጠፋበት አላዛር‹‹አሌክስ እየሰማሀኝ ነው?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹አላዛር ይቅርታ ይሄ ጉዳይ ከባድ ስለሆነ ላስብበትና ነገ ልደውልልህ?››አለው፡፡ከንግግሩ ድምፀት የስሜቱን መሰባበርን መረዳት ይቻላል፡፡
‹‹እሺ በቃ በደንብ አስብበት..ወንድሜ በጣም ተጨንቄልሀለው፡፡››
‹‹እሺ ጠንከር በል አይዞህ…ቸው፡፡››
አለማየሁ ስልኩን እንደዛጋ ወዲያው ያደረገው ነገር ሲሙ ላይ ያሉትን አድራሻ ወደቀፎው በማስተላለፍ ስልኩን ከፍቶ ሲሙን አውጥቶ መሰባበር ነው፡፡
ይሄ የእሱ ጥፋትና መዘዝ ስለሆነ ማንም ላይ ለመፍረድ ሆነ ለማንም ምክር ለመስጠት መብትም ሆነ ብቃት እደሌለው አምኗል፡፡በህይወት ውስጥ ያለውን እድል አሰበና ምርር ብሎ ነበር ያለቀሰው ፡፡መቼም ቢሆን ከማንም ሴት ጋር ፍቅር ፍቅር ላለመጫወትና ረዘም ያለ ግንኙነት ውስጥ ላለመግባት ወሰነ፡፡ከአላዛርም ሆነ ከሰሎሜ ከዛም አልፎ ከአደገበት አካባቢ ከሚያውቃቸው ሰዎች ጋር ያለውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ አቋረጠ…በብቸኝነት በሶስት ወርም ሆነ በስድስት ወር አንዴ ደውሎ እንዴት ነሽ? ሚለው አሳዳጊ እናቱን እቴቴን ብቻ ነበር፡፡
አላዛር ግን ከአለማየሁ ምንም አይነት መልስም ሆነ ምክር ባያገኝም ከፀፀቱ ጋር ህይወቱን ቀጠለ….አባትዬውም በሄዱበት የት እንደገቡ ሳይታወቅ ጠፉ፡፡አላዛር አንገቱን ደፍቶ ትኩረቱን ስራው ላይ አደረገ፡፡በንግዱ ጠንካራ ሰራተኛ ሆነ..፡፡
ከማትሪክ በኃላ ወደተግባረ እድ የሞያ ማሰልጠኛ ተቋም ገብቶ የጀመረውን ኮንስትራክሽን ትምህርት አጥብቆ ገፋበት ..ከሰሎሜ ጋር የነበራቸውም ጓደኝነት ልክ እንደወትሮ ግለቱን እንደጠበቀ ቀጠለ፡፡ እንደውም ከአራት ጓደኛሞች ሁለት ብቻ ስለቀሩ በተሻለ መተሳሰብና በመረዳዳት ትምህርታቸውን መማር ብቻ ሳይሆን በህይወትም መተጋገዝና መረዳዳት ቀጠሉ፡፡እሷ ብቸኛ ስራዋ የጀመረችን የአካውንቲንግ ትምህርት መማር ብቻ ሲሆን እሱ ግን ልክ እንደተለመደው ሁለት ኃላፊነት ነበረበት፤ እየተማረ ንግዱንም በጎን ማስኬድ ፡፡ ሱቁ እየሰራ..በጎንም ሌሎች ተባራሪ ስራዎች እየሰራ ቀጠለ፡፡እንዲህ እንዲህ እያለ ጊዜ መብረር ጀመረ ፡፡
በዚህ ጊዜ ሁሉ ሁሴን በአመት አንድ ጊዜ እየመጣ በክረምቱ የዩኒቨርሲቲ ዝግ ወቅት ለአንድ ወር አብሮቸው ያሳልፍ ነበር፡፡በዛን ጊዜ ታዲያ ነገሮች ሁሉ የተለየ ገፅታ ይኖራቸዋል፡፡ከበፊቱ በተለየ አብረው ማሳለፍ..ብዙ መዝናኛ ቦታዎች አብረው መሄድ ..ሌሎች ለወደፊት ትዝታ የሚሆኑ ኩነቶችን መፍጠር በአጠቃላይ አሪፍ በሚባል ጣፋጭ ጊዜ ያሳልፈና መልሰው ወደዩኒቨርሲቲ ይልኩታል፡፡
የሆነ የህይወት ጉዞ መጀመር ነው እንጂ ሚከብደው አንዴ ቆራጥ ውሳኔ ወስነው መንገድ ውስጥ ገብተው እግር ማንቀሳቀስ ከጀመሩ እንቅፋትና ኮረኮንች ከመሀከል ቢያስቸግርም መንገዱ ማለቁና ካሰቡት መዳረሻ መደረሱ አይቀርም ፡፡በተለይ በዚህ ዘመን ሳዕታት እንዴት እንደሚስፈነጠረሩ… ቀናቶች እንዴት እንደሚከንፉ ወርና አመታት እንዴት እንደሚበሩ አይታወቅም፡፡መስከረም፤ጥቅምት….ብለን ሀምሌና ነሀሴ ላይ እንዴት እንደምንደርስ ያስገርማል፡፡ እናም አላዛርና ሰሎሜም የጀመሩትን የኮሌጅ ትምህርት ብዙም ሳይሰላቹና መቼ ባለቀ ሳይሉ ለምረቃት በቁ፡፡ …ሁሴንም እረፍቱን አስታኮ ለምርቃታቸው አዲስአበባ ነው የሚገኘው፡በዛም ምክንያት ምርቃታቸው በጣም ደማቅና በማይረሳ ትዝታ የታጨቀበት ሆኖ እንዲያልፍ ሆኗል…ሶስቱም በየልባቸው አለማየሁም በሆነ ምክንየት ስለምርቃታቸው ሰምቶ ሰርፕራይዝ ሊያደርጋቸው ሶስት አመት ከተደበቀበት ድንገት ብቅ ብሎ ያስደምመናል ብለው ይጠብቁ ነበር፡፡ያ ምኞታቸው ግን እውነት ሊሆን አልቻለም፡፡በተለይ ሰሎሜ አለማየሁን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ተስፋ የቆረጠችበት ወቅት ነበር፡፡‹‹በቃ በዚህ ጊዜ ሊያየን ካልመጣ መቼም ወደህይወታችን ተመልሶ ላለመምጣት ወስኗል ማለት ነው፡››ስትል ደመደመች፡፡…በዛም ምክንያት እሷም እስከወዲያኛው ስለእሱ ረስታ ህይወቷን ወደፊት መቀጠል እንዳለባት ወሰነች፡፡፡ሁሴን ምርቃታቸውን በደስታና በፈንጠዝያ አብሮቸው አክብሮ ወደዩኒርሲቲው ሊመለስ ቀናቶች ነው ቀሩት፡፡ ከመሄዱ በፊት ግን ብዙ ጊዜውን ሁለት ጓደኞቹ ጋር ነው የሚያሳልፈው፡፡አሁን በምሽት ከአላዛር ጋር ሆቴል ተቀምጠው እየተዝናኑ ነው፡፡ሰሎሜ አብራቸው የለችም፡፡
‹‹ሁሴኖ በእውነት ምርቃታችንን በጣም ነው ያደመቅክልን….› አለው አላዛር፡፡የተናገረው ከልቡ ነው፡፡እስከአሁን ምርቃታቸውን በተመለከተ ያደረገላቸውን ነገር አንስቶ የማመስገኑን እድል አላገኘም ነበር፡፡
‹‹ምን ነካህ ወንድሜ..አንተም አንተ ነህ..ሰሎሜም ያው የምታውቃት ነች…ቢቻል ለእናንተ…››
‹‹አይዞኝ በሚቀጥለው አመት በዚህን ጊዜ ያንተን ምርቃት ደረጃውን በጠበቀና በሚመጥንህ መልኩ ነው የምናከብረው፡፡››
‹‹አይ ..እኔ ተመርቄ የደካማ እናቴ ህይወት ለማስተካከል እንጂ ለምርቃቱ ጋጋታ ምንም አይነት ኢንተረስት የለኝም››ሲል ትክክለኛ ፍላጎቱን ሳይደብቅ ነገረው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
ወንጀሉ በተፈፀመ በ15ተኛው ቀን ለአለማየሁ ደውሎለት ነበር፡፡
‹‹ሄሎ አሌክስ..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ..አንተስ..?ሰፍር ?እነሰሎሜ ደህና ናቸው?››
‹‹ሁሉም ሰላም ነው….አንተ ጋርስ? ስልጠናው እንዴት ነው?››
‹‹ከባድ ነው.. ግን ያው ስፖርት ስለምወድ…ለእኔ ብዙም አልከበደኝም፡፡››
‹‹ጥሩ…..››
‹‹ምነው የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ ?ድምፅህ እኮ ጥሩ አይደለም…ሰሎሜ ምን ሆነች?››
‹‹አይ እሷ ደህና ነች..አባቴ ነው፡፡››
‹‹አባትህ ምን ሆኑ?
አመማቸው?››
‹‹አልታመመም..ግን የሆነ ወንጀል ሰርቷል..ያንን ወንጀል መስራቱን እኔ ብቻ ነኝ ማውቀው..አሳልፌ ለፖሊስ ልስጠው ወይስ ዝም ብዬ ልቀመጥ? ግራ ገብቷኛል…ምክር እንድትሰጠኝ ነው የደወልኩት..በዚህ ጉዳይ ላይ አንተን ብቻ ነው የማምነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ወንጀል ?ከባድ ነው?››
‹‹በጣም ከባድ….እጅግ በጣም ከባድ…በእድሜ ልክ ወይም በሞት የሚያስቃጣ ወንጀል፡፡››
‹‹ግን እኮ አላዛር..አባትህ ትልቅ ሰው ናቸው..በዚህ እድሜቸው የእስር ቤትን ህይወት አይችሉም ..ወዲያው ነው የሚሞቱት…ለመሆኑ ወንጀሉ ምንድነው?››
‹‹የእንጀራ እናቴን ታስታውሳታለህ?››
አላዛር ስለእንጀራ እናቱ ሲያነሳ አለማየሁ ጠቅላላ ሰውነት ጆሮ ነው የሆነው፡፡ፈራ ተባ እያለ‹‹አዎ አስታውሳታለው..ምን ሆነች?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹አርግዛ ነበር››
የሚያውቀው ነገር ቢሆንም በተሳሰረና በተወለካከፈ ድምፅ ‹‹በእውነት….?እሱን አላውቅም ነበር››አለው፡፡
‹‹አዎ እኔም አላውቅም ነበር…እና ያረገዘችው ከሌላ ሰው ነው፡፡››
‹‹ከሌላ ሰው ?ከማን …?›
‹‹እሱን እኔ አላውቅም ..አባቴም የሚያውቅ አይመስለኝም….››
በሚርገበገብ ድምፁ በፍራቻ ‹‹እና ምን ተፈጠረ…?››ሲል ጠየቀው፡
‹‹አባቴ ልጁ የእሱ እንዳልሆነ በምን መንገድ እንደሆነ አላውቅም አወቀና ..እርጉዟን ሚስቱን ገደላት››
‹‹ምን ?ገደላት….››
‹‹አዎ ገድሎ የማላውቀው ቦታ ቀብሮታል….አሁን እሱም ሀገር ጥሎ ጠፍቶል..እና ምን እንዳደርግ ትመክረኛለህ?፡፡››
አለማየሁ በሰማው መርዶ የደነገጠው ድንጋጤ መጠን የሌለው ነው..እናትና አባቱ የሞቱ ሰሞን እንኳን እንደዛ አይነት ፍፅም ቀዝቃዛ ሀዘን አልተሰማውም ነበር ‹‹እሳቸው ሳይሆኑ እኔ ነኝ የገደልኩሽ፡፡››ሲል አሰበ፡፡
ድምፅ የጠፋበት አላዛር‹‹አሌክስ እየሰማሀኝ ነው?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹አላዛር ይቅርታ ይሄ ጉዳይ ከባድ ስለሆነ ላስብበትና ነገ ልደውልልህ?››አለው፡፡ከንግግሩ ድምፀት የስሜቱን መሰባበርን መረዳት ይቻላል፡፡
‹‹እሺ በቃ በደንብ አስብበት..ወንድሜ በጣም ተጨንቄልሀለው፡፡››
‹‹እሺ ጠንከር በል አይዞህ…ቸው፡፡››
አለማየሁ ስልኩን እንደዛጋ ወዲያው ያደረገው ነገር ሲሙ ላይ ያሉትን አድራሻ ወደቀፎው በማስተላለፍ ስልኩን ከፍቶ ሲሙን አውጥቶ መሰባበር ነው፡፡
ይሄ የእሱ ጥፋትና መዘዝ ስለሆነ ማንም ላይ ለመፍረድ ሆነ ለማንም ምክር ለመስጠት መብትም ሆነ ብቃት እደሌለው አምኗል፡፡በህይወት ውስጥ ያለውን እድል አሰበና ምርር ብሎ ነበር ያለቀሰው ፡፡መቼም ቢሆን ከማንም ሴት ጋር ፍቅር ፍቅር ላለመጫወትና ረዘም ያለ ግንኙነት ውስጥ ላለመግባት ወሰነ፡፡ከአላዛርም ሆነ ከሰሎሜ ከዛም አልፎ ከአደገበት አካባቢ ከሚያውቃቸው ሰዎች ጋር ያለውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ አቋረጠ…በብቸኝነት በሶስት ወርም ሆነ በስድስት ወር አንዴ ደውሎ እንዴት ነሽ? ሚለው አሳዳጊ እናቱን እቴቴን ብቻ ነበር፡፡
አላዛር ግን ከአለማየሁ ምንም አይነት መልስም ሆነ ምክር ባያገኝም ከፀፀቱ ጋር ህይወቱን ቀጠለ….አባትዬውም በሄዱበት የት እንደገቡ ሳይታወቅ ጠፉ፡፡አላዛር አንገቱን ደፍቶ ትኩረቱን ስራው ላይ አደረገ፡፡በንግዱ ጠንካራ ሰራተኛ ሆነ..፡፡
ከማትሪክ በኃላ ወደተግባረ እድ የሞያ ማሰልጠኛ ተቋም ገብቶ የጀመረውን ኮንስትራክሽን ትምህርት አጥብቆ ገፋበት ..ከሰሎሜ ጋር የነበራቸውም ጓደኝነት ልክ እንደወትሮ ግለቱን እንደጠበቀ ቀጠለ፡፡ እንደውም ከአራት ጓደኛሞች ሁለት ብቻ ስለቀሩ በተሻለ መተሳሰብና በመረዳዳት ትምህርታቸውን መማር ብቻ ሳይሆን በህይወትም መተጋገዝና መረዳዳት ቀጠሉ፡፡እሷ ብቸኛ ስራዋ የጀመረችን የአካውንቲንግ ትምህርት መማር ብቻ ሲሆን እሱ ግን ልክ እንደተለመደው ሁለት ኃላፊነት ነበረበት፤ እየተማረ ንግዱንም በጎን ማስኬድ ፡፡ ሱቁ እየሰራ..በጎንም ሌሎች ተባራሪ ስራዎች እየሰራ ቀጠለ፡፡እንዲህ እንዲህ እያለ ጊዜ መብረር ጀመረ ፡፡
በዚህ ጊዜ ሁሉ ሁሴን በአመት አንድ ጊዜ እየመጣ በክረምቱ የዩኒቨርሲቲ ዝግ ወቅት ለአንድ ወር አብሮቸው ያሳልፍ ነበር፡፡በዛን ጊዜ ታዲያ ነገሮች ሁሉ የተለየ ገፅታ ይኖራቸዋል፡፡ከበፊቱ በተለየ አብረው ማሳለፍ..ብዙ መዝናኛ ቦታዎች አብረው መሄድ ..ሌሎች ለወደፊት ትዝታ የሚሆኑ ኩነቶችን መፍጠር በአጠቃላይ አሪፍ በሚባል ጣፋጭ ጊዜ ያሳልፈና መልሰው ወደዩኒቨርሲቲ ይልኩታል፡፡
የሆነ የህይወት ጉዞ መጀመር ነው እንጂ ሚከብደው አንዴ ቆራጥ ውሳኔ ወስነው መንገድ ውስጥ ገብተው እግር ማንቀሳቀስ ከጀመሩ እንቅፋትና ኮረኮንች ከመሀከል ቢያስቸግርም መንገዱ ማለቁና ካሰቡት መዳረሻ መደረሱ አይቀርም ፡፡በተለይ በዚህ ዘመን ሳዕታት እንዴት እንደሚስፈነጠረሩ… ቀናቶች እንዴት እንደሚከንፉ ወርና አመታት እንዴት እንደሚበሩ አይታወቅም፡፡መስከረም፤ጥቅምት….ብለን ሀምሌና ነሀሴ ላይ እንዴት እንደምንደርስ ያስገርማል፡፡ እናም አላዛርና ሰሎሜም የጀመሩትን የኮሌጅ ትምህርት ብዙም ሳይሰላቹና መቼ ባለቀ ሳይሉ ለምረቃት በቁ፡፡ …ሁሴንም እረፍቱን አስታኮ ለምርቃታቸው አዲስአበባ ነው የሚገኘው፡በዛም ምክንያት ምርቃታቸው በጣም ደማቅና በማይረሳ ትዝታ የታጨቀበት ሆኖ እንዲያልፍ ሆኗል…ሶስቱም በየልባቸው አለማየሁም በሆነ ምክንየት ስለምርቃታቸው ሰምቶ ሰርፕራይዝ ሊያደርጋቸው ሶስት አመት ከተደበቀበት ድንገት ብቅ ብሎ ያስደምመናል ብለው ይጠብቁ ነበር፡፡ያ ምኞታቸው ግን እውነት ሊሆን አልቻለም፡፡በተለይ ሰሎሜ አለማየሁን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ተስፋ የቆረጠችበት ወቅት ነበር፡፡‹‹በቃ በዚህ ጊዜ ሊያየን ካልመጣ መቼም ወደህይወታችን ተመልሶ ላለመምጣት ወስኗል ማለት ነው፡››ስትል ደመደመች፡፡…በዛም ምክንያት እሷም እስከወዲያኛው ስለእሱ ረስታ ህይወቷን ወደፊት መቀጠል እንዳለባት ወሰነች፡፡፡ሁሴን ምርቃታቸውን በደስታና በፈንጠዝያ አብሮቸው አክብሮ ወደዩኒርሲቲው ሊመለስ ቀናቶች ነው ቀሩት፡፡ ከመሄዱ በፊት ግን ብዙ ጊዜውን ሁለት ጓደኞቹ ጋር ነው የሚያሳልፈው፡፡አሁን በምሽት ከአላዛር ጋር ሆቴል ተቀምጠው እየተዝናኑ ነው፡፡ሰሎሜ አብራቸው የለችም፡፡
‹‹ሁሴኖ በእውነት ምርቃታችንን በጣም ነው ያደመቅክልን….› አለው አላዛር፡፡የተናገረው ከልቡ ነው፡፡እስከአሁን ምርቃታቸውን በተመለከተ ያደረገላቸውን ነገር አንስቶ የማመስገኑን እድል አላገኘም ነበር፡፡
‹‹ምን ነካህ ወንድሜ..አንተም አንተ ነህ..ሰሎሜም ያው የምታውቃት ነች…ቢቻል ለእናንተ…››
‹‹አይዞኝ በሚቀጥለው አመት በዚህን ጊዜ ያንተን ምርቃት ደረጃውን በጠበቀና በሚመጥንህ መልኩ ነው የምናከብረው፡፡››
‹‹አይ ..እኔ ተመርቄ የደካማ እናቴ ህይወት ለማስተካከል እንጂ ለምርቃቱ ጋጋታ ምንም አይነት ኢንተረስት የለኝም››ሲል ትክክለኛ ፍላጎቱን ሳይደብቅ ነገረው፡፡
👍60❤13
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
================
ሰሎሜና ሂሩት እንደተባባሉት ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ .. ሂሩት በሰበቡ እነሱ ቤት እንደምታድር ለአላዛር ነግራው በሰዓቱ እንድትገኝ አደረገች፡፡እራት በልተው መጠጥ እየቀማመሱ ካመሹ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ከእናትዬው እንደተደወለላትና እንዳመማቸው በመናገር ብቻቸውን ትታቸው ሄደች፡፡ አላዛር ልከተልሽ ቢላትም እምቢ አለችው፡፡ቀጥታ እናቷ ቤት ሳይሆን ቀን ወደዘጋጀችው ከሰፈራቸው ብዙም የማይርቅ ሆቴል ነበር የሄደችው፡፡ቀጥታ የተከራየችው ቤርጎ ገብታ ምን ይፈጠር ይሆን እያለች ስትጨነቅና ስትገላበጥ አደረች፡፡እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር ነበር ንጊቱን የሚያበስሩ የወፎችን ዝማሬ የሰማችው…ሂሩትም ገና ሰማይና ምድሩ በቅጡ ሳይላቀቅ ከለሊቱ 12 ሰዓት አካበቢ ነበር የደወለችላት፡፡ወዲያው ክፍሏን ለቃ ወጣችና የሆቴሉ ፓርኪንግ ጋር ያቆመቻትን መኪና ውስጥ ገብታ ወደነገረቻት ቦታ ተፈተለከች፡፡በወቅቱ የተከፈተ ካፍቴሪያ ወይም ሆቴል ማግኘት ስላልቻሉ ሰሎሜ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው ነበር ያወሩት፡፡
ሶሎሜ ስታገኛት ፈክታና ተፍለቅልቃ አገኛታለሁ ብላ ነበር ያሰበችው..ግን አኩርፋና ለምቦጯን ጥላ ነው ያገኘቻት፡፡ይሄ ደግሞ ይበልጥ አስደነገጣት፡፡‹‹የሆነ ነገር ባይፈጠርማ እንደዚህ አትነፋፋም ነበር፡፡በቃ ተሳክቶላት አሳስተዋለች..በቃ ችግሩ ከእኔ ነው››ብላ ደመደመች፡፡ድምጽ አውጥታ ብትጮህ ወይም እንባዋን ዘርግፋ ብታለቅስ ደስ ይላት ነበር፡፡ግን እንደዛ በማድረግ ሂሩት ፊት ደካማ ሆና መታየት አልፈለገችም፡፡
ከአሁን አሁን አንደበቷን አላቃ የሆነ ነገር ትለኛለች ብላ ብትጠብቅ ዝም ብላ እንዳቀረቀረች የቀኝና የግራ እጇን መዳፎች አንድ ላይ አቆላልፋ እያፍተለተለች ነው፡፡እሷን እንድትናገር መጠበቁ አሰልቺ ሆኖ ስለታያት‹‹እሺ እንዴት ሆነ?››በማለት ቃል አወጣችና ጠየቀቻት፡፡
‹‹በፊትም ተይ ይቅርብኝ ያልኩሽ ይሄን ፈርቼ ነበር…››እንባዋን ዘረገፈችው፡፡
‹‹አይዞሽ ..ምንም የሚያስለቅስ ነገር እኮ የለም..ምንም ነገር ሊፀፅትሽ አይገባም…እኔ እራሴ ፈቅጄና ገፋፍቼ እኮ ነው እንድታደርጊ ያደረኩሽ…አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆኖልኛል…… ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ›› አለቻት፡፡
ከአንደበቷ እየተወረወረ የሚወጣው ቃል ለራሷ እራሱ ሻካራነቱ እየተሰማት ነበር..እስከዛሬ ለሌላ ሰው ከተናገረቻቸው ንግግሮች እጅግ መራሩ ንግግር ነው፡፡እንደውም ንግግር እንዲህ ሊመር እንደሚችል ሲሰማት የመጀመሪያ ቀን የህይወት ልምዷ ነበር፡፡
ሂሩት የሆነ ነገር ትላለች ብላ ስትጠብቅ እሷ ግን እጇን ወደኪሷ ከተተችና ሞባይሏን በማውጣት ከፈተችና ሰጠቻት፡፡
‹‹ምንድነው?››
‹‹እይው በቃል ከምነግርሽ በምስል ይሻላል ብዬ አንቺ ከወጣሽ በኃላ ያለውን ትእይንት ሁሉ እሱ ሳያውቅ ቀርጬዋለሁ››
‹‹ምን ሊያደርግልኝ ነው የማየው?‹‹ገና ስታስበው ዘገነናት…የገዛ ባሏ… ቀለበት እጣቷ ላይ አጥልቆ ያጫት፤ ቬሎ ሰውነቷ ላይ አልብሶ ያገባትና አንድ ቀን ጭኗን ፈልቅቆ ማያውቀው ሰው አሁን ፊት ለፊቷ የተቀመጠችውን የገዛ ጓደኛዋን እርቃን ሰውነቷን አቅፎ ፤ቅስር ጡቶቻን እየጠባ…መቀመጫዋን እየጨመቀ…ሲያስጮኸት…እላዮ ላይ ወጥቶ ..ሁለቱም በስሜት እሳት ግለው ነበልባሉ በዙሪያቸው ሲንበለበል በምናቧ ሳላችና ዝግንን አላት..እንደምንም የሰጠቻትን ሞባይል አስጠግታ የተቀረፀውን ማየት ጀመረች፡፡ከጠበቀችው ፈፅሞ ተቃራኒ የሆነ ነገር ነው እያየች ያለችው፡፡
ሂሩት እየደነሳች ተራ በታራ ልብሷን ስታወልቅ…አላዛር ፊቱን ስልኩ ላይ አቀርቅሮ እሷን ላለማየት ሲጠነቀቅና ሲሸማቀቅ…እርቃኗን ሔዳ ስልኩን ከእጁ ነጥቃ ወደሶፋው ወርውራ እላዩ ላይ ለመቀመጥ ስትሞክር፤ከላዩ ላይ ወርውሮ ወለል ላይ ጥሏት እየተንዘረዘረ ሲናገር‹‹አንቺ ምን አይነት ክፉ ሴት ነሽ..ጓደኛሽ አንቺን አምና እኮ ነው ባሏን ጥላልሽ የሄደችው…እኔ እንኳን ልሳሳት ፈቅጄ ባስቸግርሽ አንቺ ትሞክሪዋለሽ ብዬ አስቤ አላውቅም..ደግሞ ከነዛ ሀሉ ጓደኞቾ አንቺን መርጣ ሚዜ ማድረጓ..?አዝናለሁ..እኔ ሰሎሜን በጣም ነው የማፈቅራት ስልሽ እንዲሁ ተራ ፍቅር መስሎ እንዳይሰማሽ….ነፍስ ካወቅኩበት ቀን ጀምሮ ከእናቴ ቀጥሎ ስወድና ሳፈቅራት.. በየሄደችበት እየሄድኩ ሳጅባት… ስታለቅስ አልቅሼ ስትስቅ ስስቅ እድሜዬን የፈጀሁባት ..የማንነቴ ክፋይ ነች፡፡እሷን ከዳሁ ማለት እራሴን ከዳሁ ማለት ነው፡ያ ከሚሆን ደግሞ ህይወቴን ዛሬውኑ ባጣ ይሻለኛል….በይ ልብስሽን ልበሺና እንግዳ ቤት ገብተሸ ተኚ….ይሄንን ቅሌትሽን እንዳልተፈጠረ እንርሳው…ምክንያቱም የማፈቅራት ሚስቴ በጓደኛዋ መከዳቷን አውቃ እንድታዝና አልፈልግም…››ብሎ ጥሏት አንደኛ ወለል ላይ ወደሚገኘው መኝታ ቤታቸው በመንደርደር ሲወጣ ያሳይና ቪዴዬ ይቋረጣል፡፡
‹‹ታድዬ.!!.ይወደኛል ማለት ነው..?አሁንም ከእኔ ፍቅር እደያዘው ነው››…ተንደርድራ ጉንጯ ላይ ተጣበቀችባትና፡፡ አገላብጣ ሳመቻት‹‹ሂሩትዬ አመሰግናለው….ጋንግሪን ሆኖ ሲበላኝ ከከረመ ጨለማ ጥርጣሬ ነው የገላገልሺኝ››
‹‹ችግር የለውም ..በቃ አሁን ልሂድ››
‹‹እንዴ የት ነው የምትሄጂው.?.የምትሄጂበት ላድርስሽ››
‹‹አይ የመጣሁበት ታክሲ እኮ እየጠበቀኝ ነው››መኪናውን በራፍ ከፍታ ወጣች….፡፡
‹‹ወይኔ በጌታ ቁርስ እንኳን አብረን ሳንበላ?››
‹‹አይ ቤት ሄጄ ልብስ ቀያይሬ ወደስራ መሄድ አለብኝ….ሌላ ጊዜ››
ሰሎሜ ከዚህ በላይ ልትጫናት አልፈለገችም‹‹በቃ ሰሞኑን ደውልልሽና እናወራለን አመሰግናለሁ፡››
ሄሩት ሄደችና ከኋላ ቆማ የነበረችው ታክሲ ውስጥ ገባች፡፡
///
የሰው ልጅ ለህይወት ሚያስፈልጉትን ነገሮች በራሱ ለማድረግ በተደጋጋሚ ልምምድ ይማራል…ለምሳሌ ምግብ እንዴት መመገብ እንዳለበት በወላጆቹ ሶስት አራት አመት እያጎረሱት ያለማመዱታል…ከዛ እንዴት ተጠቅልሎ እና ተዝቆ መብላት እንዳለበት መሞከርና ይጀምራል… ከዛ ይችላል…ግራ ቀኙን ለይቶ በትክክለኛው ጫማ ማድረግም እንደዛለው ሁለት ሶስት አመት ይወስድበታል….
የሰው ልጅ ምንም ሳይማር ቀጥታ ወደማድረግ እንዲሸጋገር የሚጠበቅበት ብቸኛው ለህይወት ወሳኝ የሆነው ነገር ወሲብ ነው፡፡ወሲብ ምን እንደሆነ…?እንዴት መነቃቃት..?እንዴትስ ማነቃቃት እንደሚቻል…?እንዴት መሳም እንዴት መዳበስ እንደሚገባው..?በየት በኩል እንዴት አድርጎ እንደሚያደርግ ማንም የሚያስተምረው የለም፡፡በትምህርት ቤት እንኳን ሚሰጡ ትምህርቶች ወሲብን እንደመራቢያ እና መባዣ መንገድ ብቻ በማየት እና እሱ ላይ ብቻ በማተኮር የሚሰጥ ነው፡፡ለመዋለድ ደግሞ ምንም አይነት የወሲብ ጥበብ አይጠይቅም.. ወጣ ገባ ብቻ በማድረግ ትንሽ ገባ ብሎ ዘር መድፋት ብቻ በቂ ነው፡፡ያ ግን የወሲብ አንዱ ግንጥል ጥቅም ነው፡፡ደግሞ ያ አይደለም የሚገርመው…ያለምንም ልምድ ባገኛቸው ቅንጭብጫቢ ሹክሹክታ መሰል መረጃዋች ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ሲፈፅም ‹‹አይ የመጀመሪያው ስለሆነ ነው ብሎ ለብቃቱ ይቅርታ የሚያደርግለት የለም…በተለይ ወንዱ የዚህ ጉዳይ ተጠቂ ነው፡፡ከመጀመሪያዋ ቅፅበት ጀምሮ ፍፅምነት ይጠበቅበታል ካልተሳካለት እንዲሸማቀቅ ይደረጋል፤ከዛ ህመሙ እየባሰበት ይሄዳል፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
================
ሰሎሜና ሂሩት እንደተባባሉት ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ .. ሂሩት በሰበቡ እነሱ ቤት እንደምታድር ለአላዛር ነግራው በሰዓቱ እንድትገኝ አደረገች፡፡እራት በልተው መጠጥ እየቀማመሱ ካመሹ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ከእናትዬው እንደተደወለላትና እንዳመማቸው በመናገር ብቻቸውን ትታቸው ሄደች፡፡ አላዛር ልከተልሽ ቢላትም እምቢ አለችው፡፡ቀጥታ እናቷ ቤት ሳይሆን ቀን ወደዘጋጀችው ከሰፈራቸው ብዙም የማይርቅ ሆቴል ነበር የሄደችው፡፡ቀጥታ የተከራየችው ቤርጎ ገብታ ምን ይፈጠር ይሆን እያለች ስትጨነቅና ስትገላበጥ አደረች፡፡እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር ነበር ንጊቱን የሚያበስሩ የወፎችን ዝማሬ የሰማችው…ሂሩትም ገና ሰማይና ምድሩ በቅጡ ሳይላቀቅ ከለሊቱ 12 ሰዓት አካበቢ ነበር የደወለችላት፡፡ወዲያው ክፍሏን ለቃ ወጣችና የሆቴሉ ፓርኪንግ ጋር ያቆመቻትን መኪና ውስጥ ገብታ ወደነገረቻት ቦታ ተፈተለከች፡፡በወቅቱ የተከፈተ ካፍቴሪያ ወይም ሆቴል ማግኘት ስላልቻሉ ሰሎሜ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው ነበር ያወሩት፡፡
ሶሎሜ ስታገኛት ፈክታና ተፍለቅልቃ አገኛታለሁ ብላ ነበር ያሰበችው..ግን አኩርፋና ለምቦጯን ጥላ ነው ያገኘቻት፡፡ይሄ ደግሞ ይበልጥ አስደነገጣት፡፡‹‹የሆነ ነገር ባይፈጠርማ እንደዚህ አትነፋፋም ነበር፡፡በቃ ተሳክቶላት አሳስተዋለች..በቃ ችግሩ ከእኔ ነው››ብላ ደመደመች፡፡ድምጽ አውጥታ ብትጮህ ወይም እንባዋን ዘርግፋ ብታለቅስ ደስ ይላት ነበር፡፡ግን እንደዛ በማድረግ ሂሩት ፊት ደካማ ሆና መታየት አልፈለገችም፡፡
ከአሁን አሁን አንደበቷን አላቃ የሆነ ነገር ትለኛለች ብላ ብትጠብቅ ዝም ብላ እንዳቀረቀረች የቀኝና የግራ እጇን መዳፎች አንድ ላይ አቆላልፋ እያፍተለተለች ነው፡፡እሷን እንድትናገር መጠበቁ አሰልቺ ሆኖ ስለታያት‹‹እሺ እንዴት ሆነ?››በማለት ቃል አወጣችና ጠየቀቻት፡፡
‹‹በፊትም ተይ ይቅርብኝ ያልኩሽ ይሄን ፈርቼ ነበር…››እንባዋን ዘረገፈችው፡፡
‹‹አይዞሽ ..ምንም የሚያስለቅስ ነገር እኮ የለም..ምንም ነገር ሊፀፅትሽ አይገባም…እኔ እራሴ ፈቅጄና ገፋፍቼ እኮ ነው እንድታደርጊ ያደረኩሽ…አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆኖልኛል…… ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ›› አለቻት፡፡
ከአንደበቷ እየተወረወረ የሚወጣው ቃል ለራሷ እራሱ ሻካራነቱ እየተሰማት ነበር..እስከዛሬ ለሌላ ሰው ከተናገረቻቸው ንግግሮች እጅግ መራሩ ንግግር ነው፡፡እንደውም ንግግር እንዲህ ሊመር እንደሚችል ሲሰማት የመጀመሪያ ቀን የህይወት ልምዷ ነበር፡፡
ሂሩት የሆነ ነገር ትላለች ብላ ስትጠብቅ እሷ ግን እጇን ወደኪሷ ከተተችና ሞባይሏን በማውጣት ከፈተችና ሰጠቻት፡፡
‹‹ምንድነው?››
‹‹እይው በቃል ከምነግርሽ በምስል ይሻላል ብዬ አንቺ ከወጣሽ በኃላ ያለውን ትእይንት ሁሉ እሱ ሳያውቅ ቀርጬዋለሁ››
‹‹ምን ሊያደርግልኝ ነው የማየው?‹‹ገና ስታስበው ዘገነናት…የገዛ ባሏ… ቀለበት እጣቷ ላይ አጥልቆ ያጫት፤ ቬሎ ሰውነቷ ላይ አልብሶ ያገባትና አንድ ቀን ጭኗን ፈልቅቆ ማያውቀው ሰው አሁን ፊት ለፊቷ የተቀመጠችውን የገዛ ጓደኛዋን እርቃን ሰውነቷን አቅፎ ፤ቅስር ጡቶቻን እየጠባ…መቀመጫዋን እየጨመቀ…ሲያስጮኸት…እላዮ ላይ ወጥቶ ..ሁለቱም በስሜት እሳት ግለው ነበልባሉ በዙሪያቸው ሲንበለበል በምናቧ ሳላችና ዝግንን አላት..እንደምንም የሰጠቻትን ሞባይል አስጠግታ የተቀረፀውን ማየት ጀመረች፡፡ከጠበቀችው ፈፅሞ ተቃራኒ የሆነ ነገር ነው እያየች ያለችው፡፡
ሂሩት እየደነሳች ተራ በታራ ልብሷን ስታወልቅ…አላዛር ፊቱን ስልኩ ላይ አቀርቅሮ እሷን ላለማየት ሲጠነቀቅና ሲሸማቀቅ…እርቃኗን ሔዳ ስልኩን ከእጁ ነጥቃ ወደሶፋው ወርውራ እላዩ ላይ ለመቀመጥ ስትሞክር፤ከላዩ ላይ ወርውሮ ወለል ላይ ጥሏት እየተንዘረዘረ ሲናገር‹‹አንቺ ምን አይነት ክፉ ሴት ነሽ..ጓደኛሽ አንቺን አምና እኮ ነው ባሏን ጥላልሽ የሄደችው…እኔ እንኳን ልሳሳት ፈቅጄ ባስቸግርሽ አንቺ ትሞክሪዋለሽ ብዬ አስቤ አላውቅም..ደግሞ ከነዛ ሀሉ ጓደኞቾ አንቺን መርጣ ሚዜ ማድረጓ..?አዝናለሁ..እኔ ሰሎሜን በጣም ነው የማፈቅራት ስልሽ እንዲሁ ተራ ፍቅር መስሎ እንዳይሰማሽ….ነፍስ ካወቅኩበት ቀን ጀምሮ ከእናቴ ቀጥሎ ስወድና ሳፈቅራት.. በየሄደችበት እየሄድኩ ሳጅባት… ስታለቅስ አልቅሼ ስትስቅ ስስቅ እድሜዬን የፈጀሁባት ..የማንነቴ ክፋይ ነች፡፡እሷን ከዳሁ ማለት እራሴን ከዳሁ ማለት ነው፡ያ ከሚሆን ደግሞ ህይወቴን ዛሬውኑ ባጣ ይሻለኛል….በይ ልብስሽን ልበሺና እንግዳ ቤት ገብተሸ ተኚ….ይሄንን ቅሌትሽን እንዳልተፈጠረ እንርሳው…ምክንያቱም የማፈቅራት ሚስቴ በጓደኛዋ መከዳቷን አውቃ እንድታዝና አልፈልግም…››ብሎ ጥሏት አንደኛ ወለል ላይ ወደሚገኘው መኝታ ቤታቸው በመንደርደር ሲወጣ ያሳይና ቪዴዬ ይቋረጣል፡፡
‹‹ታድዬ.!!.ይወደኛል ማለት ነው..?አሁንም ከእኔ ፍቅር እደያዘው ነው››…ተንደርድራ ጉንጯ ላይ ተጣበቀችባትና፡፡ አገላብጣ ሳመቻት‹‹ሂሩትዬ አመሰግናለው….ጋንግሪን ሆኖ ሲበላኝ ከከረመ ጨለማ ጥርጣሬ ነው የገላገልሺኝ››
‹‹ችግር የለውም ..በቃ አሁን ልሂድ››
‹‹እንዴ የት ነው የምትሄጂው.?.የምትሄጂበት ላድርስሽ››
‹‹አይ የመጣሁበት ታክሲ እኮ እየጠበቀኝ ነው››መኪናውን በራፍ ከፍታ ወጣች….፡፡
‹‹ወይኔ በጌታ ቁርስ እንኳን አብረን ሳንበላ?››
‹‹አይ ቤት ሄጄ ልብስ ቀያይሬ ወደስራ መሄድ አለብኝ….ሌላ ጊዜ››
ሰሎሜ ከዚህ በላይ ልትጫናት አልፈለገችም‹‹በቃ ሰሞኑን ደውልልሽና እናወራለን አመሰግናለሁ፡››
ሄሩት ሄደችና ከኋላ ቆማ የነበረችው ታክሲ ውስጥ ገባች፡፡
///
የሰው ልጅ ለህይወት ሚያስፈልጉትን ነገሮች በራሱ ለማድረግ በተደጋጋሚ ልምምድ ይማራል…ለምሳሌ ምግብ እንዴት መመገብ እንዳለበት በወላጆቹ ሶስት አራት አመት እያጎረሱት ያለማመዱታል…ከዛ እንዴት ተጠቅልሎ እና ተዝቆ መብላት እንዳለበት መሞከርና ይጀምራል… ከዛ ይችላል…ግራ ቀኙን ለይቶ በትክክለኛው ጫማ ማድረግም እንደዛለው ሁለት ሶስት አመት ይወስድበታል….
የሰው ልጅ ምንም ሳይማር ቀጥታ ወደማድረግ እንዲሸጋገር የሚጠበቅበት ብቸኛው ለህይወት ወሳኝ የሆነው ነገር ወሲብ ነው፡፡ወሲብ ምን እንደሆነ…?እንዴት መነቃቃት..?እንዴትስ ማነቃቃት እንደሚቻል…?እንዴት መሳም እንዴት መዳበስ እንደሚገባው..?በየት በኩል እንዴት አድርጎ እንደሚያደርግ ማንም የሚያስተምረው የለም፡፡በትምህርት ቤት እንኳን ሚሰጡ ትምህርቶች ወሲብን እንደመራቢያ እና መባዣ መንገድ ብቻ በማየት እና እሱ ላይ ብቻ በማተኮር የሚሰጥ ነው፡፡ለመዋለድ ደግሞ ምንም አይነት የወሲብ ጥበብ አይጠይቅም.. ወጣ ገባ ብቻ በማድረግ ትንሽ ገባ ብሎ ዘር መድፋት ብቻ በቂ ነው፡፡ያ ግን የወሲብ አንዱ ግንጥል ጥቅም ነው፡፡ደግሞ ያ አይደለም የሚገርመው…ያለምንም ልምድ ባገኛቸው ቅንጭብጫቢ ሹክሹክታ መሰል መረጃዋች ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ሲፈፅም ‹‹አይ የመጀመሪያው ስለሆነ ነው ብሎ ለብቃቱ ይቅርታ የሚያደርግለት የለም…በተለይ ወንዱ የዚህ ጉዳይ ተጠቂ ነው፡፡ከመጀመሪያዋ ቅፅበት ጀምሮ ፍፅምነት ይጠበቅበታል ካልተሳካለት እንዲሸማቀቅ ይደረጋል፤ከዛ ህመሙ እየባሰበት ይሄዳል፡፡
👍52❤5👏3
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁ በቀጠሮው መሰረት ከአላዛርና አለማየሁ ጋር ከተገናኘ በኋላ ‹‹እሺ ባላና ሚስቶች ለምንድነው የፈለጋችሁኝ….?ለጥሩ ነገር እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡››ሲል የመጀመሪያ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
ሁለቱም እርስ በርስ ተያዩ..አንተ ንገረው አንቺ ንገሪው እየተባባሉ የሚገባበዙ ይመስላል አላዛር ቅድሚያውን ወሰደ‹‹በሚቀጥለው ሳምንት ሁሴን እንደሚመጣ ታውቃለህ አይደል?››
ያልጠበቀውን ርዕስ ነው ያነሳበት‹‹ትክክለኛውን ቀን አላውቅም እንጂ እንደሚመጣ አዎ በቀደም ደውሎልኝ ነበር..››
‹‹ጥሩ እንግዲህ ..እናቱም አባቱም እንደሞቱ ታውቃለህ…..እዚህ ሌላ ዘመድ የለውም ..ከፋም ለማም የልጅነት ጓደኞቹና የቅርቡ ሰዎች እኛ ሶስታችን ነን››
በውስጡ ‹‹የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች›› የሚለውን ተረት እየተረተበት ‹‹አዎ ትክክል››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እና እንዴት እንቀበለው የሚለውን ለመነጋገር ነው፡፡››
‹‹በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው፡፡ይሄ የድሮ ጓደኛችንን የመቀበል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን እኛም መልሰን ለአመታት ተራርቀን ከቆየንበት ለመቀራረብና መልሰን ጓደኝነታችንን ለማደስ ያግዘናል….››አለ
…እንደዛ ሲል በውስጡ ያለው ከአላዛር ወይም ከሁሴን ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ድሮ ጓፈደኛነታችው የመመለስ ጉጉት ኖሮት አይደለም..ከዛ ይልቅ ስለሰሎሜ በውስጡ እያሰበ ነው፡፡
‹‹በጥሩ ሁኔታ ብንቀበለው ደስ ይለኛል…እኔ የሚጠበቅብኝን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ….ዝግጅቱን እኔ ቤት ማድረግ እንችላለን››አለ…
‹‹አይ ከአንተ ቤት የእኛ ቤት ይሻል ይመስለኛል….ማለት የወንደላጤን ቤት ማድመቅ ይከብዳል›› ሰሎሜ ነች ተናጋሪዋ፡
‹‹እሺ እንዳልሽ…እኔ ቤት ብንቀበለው በዛውም የራሱን ነገር እስከሚያመቻች አኔ ጋር መቆየት ይችላል ብዬ ነው፡፡››
‹‹እኛ ጋርስ ለመቆየት ምን ይከለክለዋል…?እቤታችን እንደሆነ እንኳን እሱንና አንተም ብትጨመር በቂ ክፍት ክፍሎች አሉን ….እንደምታውቀው እዛ አፓርታማ ቤት ውስጥ እኔና እሱ ብቻ ነን....ልጅ የለን ምን የለን››
በሰሎሜ ንግግር አላዛር ሽምቅቅ አለ..ሆነ ብላ አስባበት የተናገረችው እንደሆነ ያውቃል….ግን ዋጥ አድርጎ በትዕግስት ከማሳለፍ ውጭ ምርጫ እንደሌለው ያውቃል፣ያደረገውም እንደዛ ነው፡፡
አለማየሁ‹‹በቃ እሺ እጅ ሰጥቼለው››ሲል በሀሳባቸው ተስማማ፡፡
‹‹ጥሩ በቃ …እንደዛ ከሆነ በፊታችን እሁድ ቤት ናና ስለዝርዝሩ እንነጋገርበታለን››
‹‹ጥሩ..እንደውም በሰበቡ ቤታችሁን አያለሁ››
‹‹አዎ ››
ከዛ በኃላ ብዙም ያወሩት ነገረ የለም ፡፡ተሰነባብተው ተለያዩ፡፡
‹‹አላዛር እና ሰሎሜ በአንድ መኪና ገብተው ወደቤታቸው እየተጓዙ ወሬ ጀመሩ‹‹ግን እርግጠኛ ነህ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምኑን?››
‹‹ማለቴ የሁሴን እኛ ቤት ማረፍ….ነው ወይስ አንድ ሁለት ቀን እኛ ጋር ካደረ በኃላ ሌላ ማረፊያ ፈልግ ልንለወው ነው፡?››
‹‹ለምን …አንቺን ካልደበረሽ እቤታቸን ሰፊ ነው…ሁሴን የማናውቀው ሰው አይደለም ….ለሁለታችንም ቅርብ የሆነ ሰው ነው፡፡››
‹‹ገባኝ….በደንብ አስበህበታል ወይ ለማለት ነው…?.እኔማ ደስ ይለኛል..ግን እወቅ እንደነገረኝ ከሆነ እስከሶስት ወር ሊቆይ ይችላል፡፡››
‹‹ችግር የለውም..ታውቂያለሽ የሆነ የእኛ የምንለው ሰው አብሮን እንዲኖር እንዴት እፈልግ እንደነበረ…እህቶቼም ሁለቱም ስላገቡ ወደቤታችን ላመጣቸው አልቻልኩም…የአንቺም እናት አሻፈረኝ ብላለች..እስኪ አሁን በጓደኛችን እንሞክረው፡፡››
‹‹እማዬ እኮ ከእናንተ ጋር አልኖርም አላለችም..እሷ ያለችው ልጅ ስትወልዱ እሱን ለማሳደግ መጣለሁ…አሁን ግን መጥቼ የእናንተ ሞግዚት መሆን አልፈልግም ነው ያለችው››።
‹‹እና በሞግዚት ኑሪ እንጂ ሞግዚት ሁኚን መች አልናት?››
‹‹ተወው አሁን… ለምን የማይሆን ጭቅጭቅ ውስጥ እንገባለን…ቁርጥ አድርጋ አቋሟን አሳውቃለች…መውለድ ስንችል ትመጣለች››
‹‹ይሁን እሺ… ለማንኛውም ስለሁሴን አትጨነቂ… ሁኔታዎች ካልተመቹት እኮ እራሱ አማራጭ ይፈልጋል፡፡››በማለት የተጣመመውን ርእስ እንደምንም ብሎ አቃናው፡፡
‹‹ጥሩ..ለእኛም ከብቸኝነት ጋር ከመታገል በተወሰነ መንገድ ይታደገናል…›› ስትል መለሰች፡፡
‹‹እኔም እሱን አስቤ ነው ››አላት..ግን ሁለቱም ስጋታቸው ሌላ እንደሆነ ግልፅ ነው…ሁሴን ልክ እንደአላዛር ሁሉ የሰሎሜ የልጅነት አፍቃሪዎ እንደሆነ ሁለቱም ያውቃሉ፡፡ለሁለቱም እኩል ጓደኛቸው ቢሆንም ለእሷ ግን በተለየ መልኩ አፍቃሪዋም ጭምር ነው…እና አሁን አንድ ቤት እሱን ጎትቶ ማምጣት ለዛውም አሁን ባልና ሚስቶቹ ባሉበት ሁኔታ ላይ አደጋ እንዳለውና የልታሰበ መዘዝ ሊያመጣ እንደሚችል…ለሁለቱም ግልፅ ነው….እና ሰሎሜ ደጋግማ ስለውሳኔው እርግጠኝነት እየጠየቀችው ያለው..ነገ አንድ ነገር ቢከሰት ኃላፊነቱን እንዲወስድ በማሰብ ነው፡፡
እሷ ያላወቀችው ግን የእሱን እቅድ ነው…እሱ ሁሴን ወደቤት እንዲመጣ ሲወስን መዘዙንም አስቦና አስልቶ ነው፡፡ምን አልባት የጀመረው የህክምና ጉዳይ ባይሳካለት ሊያደርግ የሚችለውን እቅድ አስቦና አስልቶ ጨርሷል..በቃ እራስ ወዳድ መሆን እንደሌለበት ገብቶታል…እየወደደም ቢሆን ከሰሎሜን ህይወት ሾልኳ መውጣት እንዳለበት ወስኗል.. ከህይወቱ ሲሸኛት ግን በተሰበረ ልብ ሆና ስነልቦናዋ ተጎድቶ መሆን እንደሌለበትም ነው የሚያምነው..ለእሱ መሆን ካልቻለች ከሁለት የልጅነት ጓደኞቾና ከልብ ከሚያፈቅሯት መቼም ቢሆን ሊጎዶት ለማይችሉት ለአንዱ ሊያስረክባት ነው ያሰበው….ለዛም ጥሪጊያ መንገድ ለመፍጠር ሁሴን በእንግድነት እሱ ቤት ማረፍ እንዳለበት ማድረግ እንዳለበት ተሰምቶታል፡፡፡ያንን ካደረገ ደግሞ አለማየሁም በተደጋጋሚ ወደእሱ ቤት ለመመላለስና ከሰሎሜ ጋር በተደጋጋሚ ጊዜ የመገናኘት እድል ይኖራዋል፣በሂደት ከሁለት አንዱ ከእሷ ጋር በተሻለ መቀራረብ ይፈጥሩና ልቧን ማግኘት ይችሉ ይሆናል….ከዛ አንዱ ያገኛታል ማለት ነው፡፡ከዛ እሱ ሀዘኑን ለብቻው ያዝናል..ማጣቱን በማስታመም ቀሪ የብቸኝነት ዘመኑን ይገፋል…….፡፡እግዚያብሄር ቀንቶት ከተፈወሰ ደግሞ በቃ ምን ይፈልጋል…እና አሁን እያደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ነው፡፡ይሄ ነው ሰሎሜን ያልገባት፡፡
ይሄ ጉዳይ ደግሞ ከሰሎሜ ይልቅ አለማየሁን ነው ፍፅም ግራ ያጋባው‹‹ሰውዬው ምን እየሰራ ነው?››የሚለው ሀሳብ በውስጡ መጉላላት የጀመረው ገና ከእነሱ እንደተለየ ነው፡፡እና ደግሞ አልተመቸውም….በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ ወሳኝ ወቅት የሁሴን ወደሀገር ቤት ተመልሶ መምጣት ደስ አላሰኘውም ነበር፡፡፡በእሱ እምነት አላዛር ካልተሳካለት ቀጥታ ሰሎሜን የእሱ የማድረጉን ትግል በብቸኝነት ለመወጣት ነበር ዕቅዱም ምኞቱም..ሁሴን ደውሎ እንደሚመጣ ከነገረው በኋላ ግን ሌላ ተፋላሚ እየመጣበት እንደሆነ ነው ወዲያው የገባው…እንደውም መምጣቱ እራሱ ያጋጣሚ ነገር ሳይሆን ሆነ ብሎ የታሰበበት እንደሆነ ነው የሚጠረጥረው…ሰሎሜ አላዛርን ከማግባቷ በፊት ከእሱ ጋር ለረጅም ጊዜ እንደምትደዋወል ነግራዋለች..በእሷ እና በባሏ መካከል ያለውን ቦንብ ሚስጥር ለእሱ በተገናኙበት በመጀመሪያው ቀን ከነገረችው…ለረጅም ጊዜ ስትደዋወል ለነበረው ለዛውም ከባህር ማዶ ላለው ሁሴን ላትነግረው የምትችልበት ምክንያት ምንም እየታየው አይደለም…እንደጠረጠረው ነግራው ከሆነ ደግሞ በተለይ የሰሞኑን ግር ግር አብራርታለት ከሆነ የሆነ ምክንያት ፈጥሮ አጋጣሚውን ለመጠቀም እንደመጣ ነው የሚያምነው..እና ከእሱ ጋር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁ በቀጠሮው መሰረት ከአላዛርና አለማየሁ ጋር ከተገናኘ በኋላ ‹‹እሺ ባላና ሚስቶች ለምንድነው የፈለጋችሁኝ….?ለጥሩ ነገር እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡››ሲል የመጀመሪያ ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
ሁለቱም እርስ በርስ ተያዩ..አንተ ንገረው አንቺ ንገሪው እየተባባሉ የሚገባበዙ ይመስላል አላዛር ቅድሚያውን ወሰደ‹‹በሚቀጥለው ሳምንት ሁሴን እንደሚመጣ ታውቃለህ አይደል?››
ያልጠበቀውን ርዕስ ነው ያነሳበት‹‹ትክክለኛውን ቀን አላውቅም እንጂ እንደሚመጣ አዎ በቀደም ደውሎልኝ ነበር..››
‹‹ጥሩ እንግዲህ ..እናቱም አባቱም እንደሞቱ ታውቃለህ…..እዚህ ሌላ ዘመድ የለውም ..ከፋም ለማም የልጅነት ጓደኞቹና የቅርቡ ሰዎች እኛ ሶስታችን ነን››
በውስጡ ‹‹የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች›› የሚለውን ተረት እየተረተበት ‹‹አዎ ትክክል››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እና እንዴት እንቀበለው የሚለውን ለመነጋገር ነው፡፡››
‹‹በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው፡፡ይሄ የድሮ ጓደኛችንን የመቀበል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን እኛም መልሰን ለአመታት ተራርቀን ከቆየንበት ለመቀራረብና መልሰን ጓደኝነታችንን ለማደስ ያግዘናል….››አለ
…እንደዛ ሲል በውስጡ ያለው ከአላዛር ወይም ከሁሴን ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ድሮ ጓፈደኛነታችው የመመለስ ጉጉት ኖሮት አይደለም..ከዛ ይልቅ ስለሰሎሜ በውስጡ እያሰበ ነው፡፡
‹‹በጥሩ ሁኔታ ብንቀበለው ደስ ይለኛል…እኔ የሚጠበቅብኝን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ….ዝግጅቱን እኔ ቤት ማድረግ እንችላለን››አለ…
‹‹አይ ከአንተ ቤት የእኛ ቤት ይሻል ይመስለኛል….ማለት የወንደላጤን ቤት ማድመቅ ይከብዳል›› ሰሎሜ ነች ተናጋሪዋ፡
‹‹እሺ እንዳልሽ…እኔ ቤት ብንቀበለው በዛውም የራሱን ነገር እስከሚያመቻች አኔ ጋር መቆየት ይችላል ብዬ ነው፡፡››
‹‹እኛ ጋርስ ለመቆየት ምን ይከለክለዋል…?እቤታችን እንደሆነ እንኳን እሱንና አንተም ብትጨመር በቂ ክፍት ክፍሎች አሉን ….እንደምታውቀው እዛ አፓርታማ ቤት ውስጥ እኔና እሱ ብቻ ነን....ልጅ የለን ምን የለን››
በሰሎሜ ንግግር አላዛር ሽምቅቅ አለ..ሆነ ብላ አስባበት የተናገረችው እንደሆነ ያውቃል….ግን ዋጥ አድርጎ በትዕግስት ከማሳለፍ ውጭ ምርጫ እንደሌለው ያውቃል፣ያደረገውም እንደዛ ነው፡፡
አለማየሁ‹‹በቃ እሺ እጅ ሰጥቼለው››ሲል በሀሳባቸው ተስማማ፡፡
‹‹ጥሩ በቃ …እንደዛ ከሆነ በፊታችን እሁድ ቤት ናና ስለዝርዝሩ እንነጋገርበታለን››
‹‹ጥሩ..እንደውም በሰበቡ ቤታችሁን አያለሁ››
‹‹አዎ ››
ከዛ በኃላ ብዙም ያወሩት ነገረ የለም ፡፡ተሰነባብተው ተለያዩ፡፡
‹‹አላዛር እና ሰሎሜ በአንድ መኪና ገብተው ወደቤታቸው እየተጓዙ ወሬ ጀመሩ‹‹ግን እርግጠኛ ነህ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምኑን?››
‹‹ማለቴ የሁሴን እኛ ቤት ማረፍ….ነው ወይስ አንድ ሁለት ቀን እኛ ጋር ካደረ በኃላ ሌላ ማረፊያ ፈልግ ልንለወው ነው፡?››
‹‹ለምን …አንቺን ካልደበረሽ እቤታቸን ሰፊ ነው…ሁሴን የማናውቀው ሰው አይደለም ….ለሁለታችንም ቅርብ የሆነ ሰው ነው፡፡››
‹‹ገባኝ….በደንብ አስበህበታል ወይ ለማለት ነው…?.እኔማ ደስ ይለኛል..ግን እወቅ እንደነገረኝ ከሆነ እስከሶስት ወር ሊቆይ ይችላል፡፡››
‹‹ችግር የለውም..ታውቂያለሽ የሆነ የእኛ የምንለው ሰው አብሮን እንዲኖር እንዴት እፈልግ እንደነበረ…እህቶቼም ሁለቱም ስላገቡ ወደቤታችን ላመጣቸው አልቻልኩም…የአንቺም እናት አሻፈረኝ ብላለች..እስኪ አሁን በጓደኛችን እንሞክረው፡፡››
‹‹እማዬ እኮ ከእናንተ ጋር አልኖርም አላለችም..እሷ ያለችው ልጅ ስትወልዱ እሱን ለማሳደግ መጣለሁ…አሁን ግን መጥቼ የእናንተ ሞግዚት መሆን አልፈልግም ነው ያለችው››።
‹‹እና በሞግዚት ኑሪ እንጂ ሞግዚት ሁኚን መች አልናት?››
‹‹ተወው አሁን… ለምን የማይሆን ጭቅጭቅ ውስጥ እንገባለን…ቁርጥ አድርጋ አቋሟን አሳውቃለች…መውለድ ስንችል ትመጣለች››
‹‹ይሁን እሺ… ለማንኛውም ስለሁሴን አትጨነቂ… ሁኔታዎች ካልተመቹት እኮ እራሱ አማራጭ ይፈልጋል፡፡››በማለት የተጣመመውን ርእስ እንደምንም ብሎ አቃናው፡፡
‹‹ጥሩ..ለእኛም ከብቸኝነት ጋር ከመታገል በተወሰነ መንገድ ይታደገናል…›› ስትል መለሰች፡፡
‹‹እኔም እሱን አስቤ ነው ››አላት..ግን ሁለቱም ስጋታቸው ሌላ እንደሆነ ግልፅ ነው…ሁሴን ልክ እንደአላዛር ሁሉ የሰሎሜ የልጅነት አፍቃሪዎ እንደሆነ ሁለቱም ያውቃሉ፡፡ለሁለቱም እኩል ጓደኛቸው ቢሆንም ለእሷ ግን በተለየ መልኩ አፍቃሪዋም ጭምር ነው…እና አሁን አንድ ቤት እሱን ጎትቶ ማምጣት ለዛውም አሁን ባልና ሚስቶቹ ባሉበት ሁኔታ ላይ አደጋ እንዳለውና የልታሰበ መዘዝ ሊያመጣ እንደሚችል…ለሁለቱም ግልፅ ነው….እና ሰሎሜ ደጋግማ ስለውሳኔው እርግጠኝነት እየጠየቀችው ያለው..ነገ አንድ ነገር ቢከሰት ኃላፊነቱን እንዲወስድ በማሰብ ነው፡፡
እሷ ያላወቀችው ግን የእሱን እቅድ ነው…እሱ ሁሴን ወደቤት እንዲመጣ ሲወስን መዘዙንም አስቦና አስልቶ ነው፡፡ምን አልባት የጀመረው የህክምና ጉዳይ ባይሳካለት ሊያደርግ የሚችለውን እቅድ አስቦና አስልቶ ጨርሷል..በቃ እራስ ወዳድ መሆን እንደሌለበት ገብቶታል…እየወደደም ቢሆን ከሰሎሜን ህይወት ሾልኳ መውጣት እንዳለበት ወስኗል.. ከህይወቱ ሲሸኛት ግን በተሰበረ ልብ ሆና ስነልቦናዋ ተጎድቶ መሆን እንደሌለበትም ነው የሚያምነው..ለእሱ መሆን ካልቻለች ከሁለት የልጅነት ጓደኞቾና ከልብ ከሚያፈቅሯት መቼም ቢሆን ሊጎዶት ለማይችሉት ለአንዱ ሊያስረክባት ነው ያሰበው….ለዛም ጥሪጊያ መንገድ ለመፍጠር ሁሴን በእንግድነት እሱ ቤት ማረፍ እንዳለበት ማድረግ እንዳለበት ተሰምቶታል፡፡፡ያንን ካደረገ ደግሞ አለማየሁም በተደጋጋሚ ወደእሱ ቤት ለመመላለስና ከሰሎሜ ጋር በተደጋጋሚ ጊዜ የመገናኘት እድል ይኖራዋል፣በሂደት ከሁለት አንዱ ከእሷ ጋር በተሻለ መቀራረብ ይፈጥሩና ልቧን ማግኘት ይችሉ ይሆናል….ከዛ አንዱ ያገኛታል ማለት ነው፡፡ከዛ እሱ ሀዘኑን ለብቻው ያዝናል..ማጣቱን በማስታመም ቀሪ የብቸኝነት ዘመኑን ይገፋል…….፡፡እግዚያብሄር ቀንቶት ከተፈወሰ ደግሞ በቃ ምን ይፈልጋል…እና አሁን እያደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ነው፡፡ይሄ ነው ሰሎሜን ያልገባት፡፡
ይሄ ጉዳይ ደግሞ ከሰሎሜ ይልቅ አለማየሁን ነው ፍፅም ግራ ያጋባው‹‹ሰውዬው ምን እየሰራ ነው?››የሚለው ሀሳብ በውስጡ መጉላላት የጀመረው ገና ከእነሱ እንደተለየ ነው፡፡እና ደግሞ አልተመቸውም….በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ ወሳኝ ወቅት የሁሴን ወደሀገር ቤት ተመልሶ መምጣት ደስ አላሰኘውም ነበር፡፡፡በእሱ እምነት አላዛር ካልተሳካለት ቀጥታ ሰሎሜን የእሱ የማድረጉን ትግል በብቸኝነት ለመወጣት ነበር ዕቅዱም ምኞቱም..ሁሴን ደውሎ እንደሚመጣ ከነገረው በኋላ ግን ሌላ ተፋላሚ እየመጣበት እንደሆነ ነው ወዲያው የገባው…እንደውም መምጣቱ እራሱ ያጋጣሚ ነገር ሳይሆን ሆነ ብሎ የታሰበበት እንደሆነ ነው የሚጠረጥረው…ሰሎሜ አላዛርን ከማግባቷ በፊት ከእሱ ጋር ለረጅም ጊዜ እንደምትደዋወል ነግራዋለች..በእሷ እና በባሏ መካከል ያለውን ቦንብ ሚስጥር ለእሱ በተገናኙበት በመጀመሪያው ቀን ከነገረችው…ለረጅም ጊዜ ስትደዋወል ለነበረው ለዛውም ከባህር ማዶ ላለው ሁሴን ላትነግረው የምትችልበት ምክንያት ምንም እየታየው አይደለም…እንደጠረጠረው ነግራው ከሆነ ደግሞ በተለይ የሰሞኑን ግር ግር አብራርታለት ከሆነ የሆነ ምክንያት ፈጥሮ አጋጣሚውን ለመጠቀም እንደመጣ ነው የሚያምነው..እና ከእሱ ጋር
👍60❤14😁4
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
..ፎጣዋን አገልድማ ስትወጣ እሱ ደግሞ ለመግባት እርቃን ሰውነቱን በፓንት ብቻ ሆኖ ወደእሷ አቅጣጫ ሲመጣ አየችው…ዞር ብላ መንገዱን ለቀቀችለት …ቀጥታ ወደውስጥ ገባና የሻወሩን በራፍ ዘጋው…
ባለቤቷን እንዲህ እርቃኑን ስታየው ሁሌ እንደአዲስ እንደገረማት ነው፡፡ሰለብሪቲ አክተር ወይም ታዋቂ ሞዴል እኮ ነው የሚመስለው፡፡እዚህ አካባቢ እንደዚህ ቢሆን የሚባል ቅር የሚያሰኝ የአካል ክፍል የለውም‹‹ሆሆ..ለናሙና የተፈጠረ እኮ ነው የሚመስለው››አለችና ሰውነቷን አደራርቃ በምሽቱ ሶስቱን የእድሜ ልክ አድናቂዎቾና አፍቃሪዎቾ ወንዶችን ያስደምማል ያለችውን አለባበስ ለበሰች፡፡ፀጉሯን አስተካከለች፡፡የተወሰነ ሜካፕ ተጠቀመችና ሽቶ እላዮ ላይ ነስንሳ ወደሳሎን ወጣች፡፡
አለማየሁ ሰማያዊ ቀለም ያለው ሙሉ ሱፍ ለብሶ ዝንጥ ብሎ ሳሎን ቁጭ ብሎ እስኪወጡ እየጠበቃቸው ነበር፡፡
እንዳየችው ‹‹እንዴ ኩማንደር….አምባሳደር መስለሀል፡፡›› አለችው፡፡
‹‹የወደፊት እጣ ፋንታዬ ምን አልባት አምባአሳደር ሊሆን ይችላል፡፡››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹ተስፋ አደርጋለሁ፡፡››
‹‹ምነው አፍጥጠህ አየሀኝ…ልብሱ አልሄደብኝም እንዴ?››ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት፡፡
‹‹አረ የሚያስደነግጥ አለባበስ ነው … እንከን አይወጣለትም ..በጣም ያምራል፡፡››
‹‹ልብሱ ብቻ ነው ሚያምረው?››ስትል ልስልስ በሆነ ቅንዝራም ድምፅ ጠየቀችው፡፡
‹‹ስለአንቺ አላዛር ሲመጣ ይነግርሻል….ያንን አስተያየት የመስጠት መብት ለጊዜው የእሱ ነው፡፡››
ግንባሯን ቋጠረች‹‹ለጊዜው ስትል…?››
‹‹ይሄ ጥያቄ ይዝለለኝ፡፡››
‹‹በጣም ተቀይረሀል ..ድሮ እንደዚህ አልነበርክም››
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹ከእኔ ጋር ለምትነጋገረው ነገር ስትጠነቀቅ አይቼህ አላውቅም ..እንደመጣልህ በነፃነት ነበር የምናወራው፡፡ትዝ ይልሀል ..አንተ እኮ ጓደኛዬ ብቻ አልነበርክም….አንድ ቤት ውስጥ አብረኸኝ ያደክ ወንድሜ ነህ፡፡››
‹‹አዎ..በልጆቼን በሞት ሳጣና አያቴም በቃኝ ብላ ገዳም ጥላኝ ስትገባ ..አንተም ልጄ ነህ ..ከልጄ ጋር አሳድግሀለው ብላ የወሰደችኝ እናትሽ እቴቴ ነች፡፡በእውነት ለእሷ በሚገባው መጠን አልተንከባከብኳትም…፡፡››
‹‹ተው ተው..እቴቴንማ በጣም ነው የተንከባከብካት፡፡.በየጊዜው ብር እንደምትልክላት ማላውቅ ይመስልሀል፡፡እዚህ ከተቀየርክ በኃላ እንኳን እሷን ደጋግመህ አግኝተህ እኛን ግን ለማግኘት ፍቃደኛ አልነበርክም፡፡ካንተ ደግሞ ይልቅ ደግሞ የሚገርመኝ የእሷ ያንተ ተባባሪ ሆና መደበቅ፡፡ …እንደውም አንዳንዴ ከእቴቴ ጋር ስንጣላ እኮ…‹‹ከአንቺ ይልቅ የእኔን እናትነት የተረዳው አለማየሁ ነው…››እያለች ታበሳጨኛለች፡፡እና እሷ በአንተ ደስተኛ ነች…ትንሽ ቅር ሚላት በየጊዜው በአካል ሄደህ ስለማትጠይቃት ነው፡፡በዛ ከአንተ እኔ እሻላለሁ….፡፡››
‹‹ቢሆንልኝ…ለእሷ ምንም ነገር ባደርግ ይገባታል፡፡››
‹‹ለእኔስ…ለስድስት አመት የት እንዳለህ እንኳን ደውለህ አሳውቀሐኝ አታውቅም…አለማየሁ ደወሎ እንዲህ አለ…አለማየሁ ደውሎ በባንክ ይሄንን ላከ ሲባል እንጂ አንድ ቀን ሰሎሜ ሰላም ብሎሻል…?ሰሎሜ አለማየሁ ሰለአንቺ እንዲህ ያስባል ብሎ የነገረኝ ሰው የለም..ሁል ጊዜ አእመሮዬን እንደበላኝ ነው…‹‹ምን አድርጌዋለው…?መቼ ቀን ነው ያስከፋሁት …?.የቱ ጋር ነው የተቀየመኝ? ብዬ እንደተከዝኩ ነበር..እወነቱን ለመናገር በጣም ተቀይሜህ ነበር ..ባገኝህ እንደማላናግርህ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር..ግን በእንደዛ አይነት ሁኔታ ስንገናኝ…ምንም ማድረግ አልቻልኩም...ተቀይሜህ እንደነበረ ራሱ ከእስር ተፈትቼ ቤቴ ከገባው በኃላ ነው ያስታወስኩት፡፡››
‹‹ጥሩ ነው፣ ቂመኛ አይደለሽም ማለት ነው…አንቺን ያላገኘሁሽ ግን ላላገኝሽ ስላልፈለኩ ሳይሆን ተገድጄ ነው››
‹‹ተገድጄ ስትል?››
‹‹ማለቴ….››ንግግሩን እንዳንጠለጠለ አላዛር ከእነሱ በበለጠ.. ልክ እንደእለቱ ሙሽራ ዝንጥ ብሎ ወደእነሱ ሲመጣ ስለተመለከተ ለንግግር የተከፈተ አፉን መልሶ ዘጋ፡፡
‹‹በሉ…እንሂድና …ቀደም ብለን እዛው አካባቢ ደርሰን ብንጠብቀው ይሻለል፡፡››
አለማየሁ አላዛር መጥቶ ማውራት ከማይፈልገው ነገር ስለገላገለው በመደሰት ‹‹ጥሩ …እንሂድ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡ርምጃውን ከአላዛር አስተካክሎ ወደውጭ መራመድ ጀመረ.፡፡ሰሎሜ ከኃላ ሁለቱንም በትኩረት እያየች ተከተለቻቸው፡፡ሁለቱም ፈርጣማና ወንዳወንድ የሚባሉ ናቸው፡፡ግን አላዛር ወደላይ የተሳበ መለሎ ነው፡፡
//
ከ30 ደቂቃ ጥበቃ በኋላ የተጠበቀው ሁሴን ግዙፍ ሻንጣውን በጋሪ እየገፋ ከተርሚናሉ ሲወጣ ሶስቱም በእኩል አዩት…በደስታና በጩኸት እንዲያያቸው እጃቸውን አውለበለቡለት…ሁሴን ከዛሬ ስድስት አመት በፊት እደሚያውቁት አይነት ነው፡፡ እንዳዛው ውልምጭምጭ ቀጫጫ…ባለትልቅ ጭንቅላትና ሉጫ ፀጉር…የህፃን የመሰለ ፍልቅልቅ ፊት…ነጭ ከሩቅ አይን የሚስብ በረዶ መሳይ ጥርስ ……
ሶስቱም በየተራ እየተጠመጠሙበት ሰላምታ ከሰጡትና ይዘው የመጡትን የእንኳን በሰላም መጣህ ምኞታቸውን የሚገልፅ አበባ አስታቀፉት፡፡ከዛ በኃላ አለማየሁና አላዘር ሻንጣውን ተቀብለው ወደመኪናው ወሰዱና ከኋላ ጫኑለት፡፡…በአላዛር ሹፌርነት ሰሎሜ ገቢና ከእሱ ጎን ተቀምጣ አለማየሁና ሁሴን ከኋላ ሆነው ወደቤት ጉዞ ጀመሩ፡፡
ድንገት‹‹ይገርማል…?››አለ ሁሴን፡፡
አለማየሁ‹‹ምኑ ነው የገረመህ?ከተማዋ ልደቷን የምታከብር የቢሊዬነር ብቸኛ ልጅ መሰለችህ አይደል…?››አለው፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹አሸብርቃና ተኳኩላ …በደማቅ መብራቷች ተንቆጥቁጣ ስታያት ገርሞህ እንደሆነ ብዬ ነዋ?››
‹‹..አዎ ያልከው ነገር በጣም አስገርሞኛል..ግን እኔ ለማውራት የፈለኩት ሶስታችሁን በአንድነት መጥታችሁ ትቀበሉኛላቹሁ የሚል ምንም አይነት ግምት ስላልነበረኝ በዛ መደነቄን ነው፡፡፡፡›
ልክ እንደሁሴን እሷም ሶስቱም የልጅነት እና የአፍላ ወጣትነት ጓደኞቾ እና አፍቃሪዎቾ ከበርካታ አመታት በኋላ እንዲህ አንድ ላይ ተሰብስበው አይናቸው እሷ ላይ ሲያቁለጨለጩ በመመለከቷ እየተገረመች‹‹ምን ማለት ነው? ሶስታችንም እኩል ጓደኞችህ አይደለንም እንዴ…?ለመሆኑ መጥቶ ይቀበለኛል ብለህ የገመትከው ማንን ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው አሌክስን ነበር፡፡እናንተን በማግስቱ ባገኛችሁ ብዬ ነበር ያሰብኩት፡፡››
‹‹አንተ …ከእኛ ይልቅ አሌክስ ቁምነገረኛ የሆነው ከመቼ ወዲህ ነው…?ነው ሰው ሀገር ከሄድክ በኃላ ፀባያችን ተምታታብህ››አለችው ሰሎሜ በመገረም፡፡
አለማየው በፈገግታ‹‹አንቺ …ሰው ሁሉ ስለእኔ ልክ እንደአንቺ የተሳሳተ ግምት ያለው ይመስልሻል እንዴ?››አላት፡፡
‹‹ተው ተው…ከመሀከላችንማ አንደኛው ቁምነገረኛና ኃላፊነትን የሚወስደው አላዛር ነው…አንተ እንደውም በዚህ ጉዳይ የመጨረሻው ሰው ነህ››አለው ሁሴን፡፡
‹‹አንተ ዲያስፖራ ለመሆኑ ዜግነትህን ቀይረሀል?››ሲል ጠየቀው፡፡
ያልጠበቀውን ጥያቄ ስለተጠየቀው ግራ ተጋባ‹‹አይ አልቀየርኩም…ግን ለምን ጠየቅከኝ?››
‹‹አይ ኢትዬጵያዊ ዲያስፖራ ከሆንክ የሚጮህልህ ኤምባሲ ስለሌለ ለዚህ ንግግርህ የሆነ ሰበብ ፈልጌ ከርቸሌ ልወረውርህ ነዋ….እንደድሮ አለማየሁ ብቻ አይደለሁም..ኩማንደር አለማየሁ ነኝ፡፡››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
================
..ፎጣዋን አገልድማ ስትወጣ እሱ ደግሞ ለመግባት እርቃን ሰውነቱን በፓንት ብቻ ሆኖ ወደእሷ አቅጣጫ ሲመጣ አየችው…ዞር ብላ መንገዱን ለቀቀችለት …ቀጥታ ወደውስጥ ገባና የሻወሩን በራፍ ዘጋው…
ባለቤቷን እንዲህ እርቃኑን ስታየው ሁሌ እንደአዲስ እንደገረማት ነው፡፡ሰለብሪቲ አክተር ወይም ታዋቂ ሞዴል እኮ ነው የሚመስለው፡፡እዚህ አካባቢ እንደዚህ ቢሆን የሚባል ቅር የሚያሰኝ የአካል ክፍል የለውም‹‹ሆሆ..ለናሙና የተፈጠረ እኮ ነው የሚመስለው››አለችና ሰውነቷን አደራርቃ በምሽቱ ሶስቱን የእድሜ ልክ አድናቂዎቾና አፍቃሪዎቾ ወንዶችን ያስደምማል ያለችውን አለባበስ ለበሰች፡፡ፀጉሯን አስተካከለች፡፡የተወሰነ ሜካፕ ተጠቀመችና ሽቶ እላዮ ላይ ነስንሳ ወደሳሎን ወጣች፡፡
አለማየሁ ሰማያዊ ቀለም ያለው ሙሉ ሱፍ ለብሶ ዝንጥ ብሎ ሳሎን ቁጭ ብሎ እስኪወጡ እየጠበቃቸው ነበር፡፡
እንዳየችው ‹‹እንዴ ኩማንደር….አምባሳደር መስለሀል፡፡›› አለችው፡፡
‹‹የወደፊት እጣ ፋንታዬ ምን አልባት አምባአሳደር ሊሆን ይችላል፡፡››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹ተስፋ አደርጋለሁ፡፡››
‹‹ምነው አፍጥጠህ አየሀኝ…ልብሱ አልሄደብኝም እንዴ?››ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት፡፡
‹‹አረ የሚያስደነግጥ አለባበስ ነው … እንከን አይወጣለትም ..በጣም ያምራል፡፡››
‹‹ልብሱ ብቻ ነው ሚያምረው?››ስትል ልስልስ በሆነ ቅንዝራም ድምፅ ጠየቀችው፡፡
‹‹ስለአንቺ አላዛር ሲመጣ ይነግርሻል….ያንን አስተያየት የመስጠት መብት ለጊዜው የእሱ ነው፡፡››
ግንባሯን ቋጠረች‹‹ለጊዜው ስትል…?››
‹‹ይሄ ጥያቄ ይዝለለኝ፡፡››
‹‹በጣም ተቀይረሀል ..ድሮ እንደዚህ አልነበርክም››
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹ከእኔ ጋር ለምትነጋገረው ነገር ስትጠነቀቅ አይቼህ አላውቅም ..እንደመጣልህ በነፃነት ነበር የምናወራው፡፡ትዝ ይልሀል ..አንተ እኮ ጓደኛዬ ብቻ አልነበርክም….አንድ ቤት ውስጥ አብረኸኝ ያደክ ወንድሜ ነህ፡፡››
‹‹አዎ..በልጆቼን በሞት ሳጣና አያቴም በቃኝ ብላ ገዳም ጥላኝ ስትገባ ..አንተም ልጄ ነህ ..ከልጄ ጋር አሳድግሀለው ብላ የወሰደችኝ እናትሽ እቴቴ ነች፡፡በእውነት ለእሷ በሚገባው መጠን አልተንከባከብኳትም…፡፡››
‹‹ተው ተው..እቴቴንማ በጣም ነው የተንከባከብካት፡፡.በየጊዜው ብር እንደምትልክላት ማላውቅ ይመስልሀል፡፡እዚህ ከተቀየርክ በኃላ እንኳን እሷን ደጋግመህ አግኝተህ እኛን ግን ለማግኘት ፍቃደኛ አልነበርክም፡፡ካንተ ደግሞ ይልቅ ደግሞ የሚገርመኝ የእሷ ያንተ ተባባሪ ሆና መደበቅ፡፡ …እንደውም አንዳንዴ ከእቴቴ ጋር ስንጣላ እኮ…‹‹ከአንቺ ይልቅ የእኔን እናትነት የተረዳው አለማየሁ ነው…››እያለች ታበሳጨኛለች፡፡እና እሷ በአንተ ደስተኛ ነች…ትንሽ ቅር ሚላት በየጊዜው በአካል ሄደህ ስለማትጠይቃት ነው፡፡በዛ ከአንተ እኔ እሻላለሁ….፡፡››
‹‹ቢሆንልኝ…ለእሷ ምንም ነገር ባደርግ ይገባታል፡፡››
‹‹ለእኔስ…ለስድስት አመት የት እንዳለህ እንኳን ደውለህ አሳውቀሐኝ አታውቅም…አለማየሁ ደወሎ እንዲህ አለ…አለማየሁ ደውሎ በባንክ ይሄንን ላከ ሲባል እንጂ አንድ ቀን ሰሎሜ ሰላም ብሎሻል…?ሰሎሜ አለማየሁ ሰለአንቺ እንዲህ ያስባል ብሎ የነገረኝ ሰው የለም..ሁል ጊዜ አእመሮዬን እንደበላኝ ነው…‹‹ምን አድርጌዋለው…?መቼ ቀን ነው ያስከፋሁት …?.የቱ ጋር ነው የተቀየመኝ? ብዬ እንደተከዝኩ ነበር..እወነቱን ለመናገር በጣም ተቀይሜህ ነበር ..ባገኝህ እንደማላናግርህ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር..ግን በእንደዛ አይነት ሁኔታ ስንገናኝ…ምንም ማድረግ አልቻልኩም...ተቀይሜህ እንደነበረ ራሱ ከእስር ተፈትቼ ቤቴ ከገባው በኃላ ነው ያስታወስኩት፡፡››
‹‹ጥሩ ነው፣ ቂመኛ አይደለሽም ማለት ነው…አንቺን ያላገኘሁሽ ግን ላላገኝሽ ስላልፈለኩ ሳይሆን ተገድጄ ነው››
‹‹ተገድጄ ስትል?››
‹‹ማለቴ….››ንግግሩን እንዳንጠለጠለ አላዛር ከእነሱ በበለጠ.. ልክ እንደእለቱ ሙሽራ ዝንጥ ብሎ ወደእነሱ ሲመጣ ስለተመለከተ ለንግግር የተከፈተ አፉን መልሶ ዘጋ፡፡
‹‹በሉ…እንሂድና …ቀደም ብለን እዛው አካባቢ ደርሰን ብንጠብቀው ይሻለል፡፡››
አለማየሁ አላዛር መጥቶ ማውራት ከማይፈልገው ነገር ስለገላገለው በመደሰት ‹‹ጥሩ …እንሂድ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡ርምጃውን ከአላዛር አስተካክሎ ወደውጭ መራመድ ጀመረ.፡፡ሰሎሜ ከኃላ ሁለቱንም በትኩረት እያየች ተከተለቻቸው፡፡ሁለቱም ፈርጣማና ወንዳወንድ የሚባሉ ናቸው፡፡ግን አላዛር ወደላይ የተሳበ መለሎ ነው፡፡
//
ከ30 ደቂቃ ጥበቃ በኋላ የተጠበቀው ሁሴን ግዙፍ ሻንጣውን በጋሪ እየገፋ ከተርሚናሉ ሲወጣ ሶስቱም በእኩል አዩት…በደስታና በጩኸት እንዲያያቸው እጃቸውን አውለበለቡለት…ሁሴን ከዛሬ ስድስት አመት በፊት እደሚያውቁት አይነት ነው፡፡ እንዳዛው ውልምጭምጭ ቀጫጫ…ባለትልቅ ጭንቅላትና ሉጫ ፀጉር…የህፃን የመሰለ ፍልቅልቅ ፊት…ነጭ ከሩቅ አይን የሚስብ በረዶ መሳይ ጥርስ ……
ሶስቱም በየተራ እየተጠመጠሙበት ሰላምታ ከሰጡትና ይዘው የመጡትን የእንኳን በሰላም መጣህ ምኞታቸውን የሚገልፅ አበባ አስታቀፉት፡፡ከዛ በኃላ አለማየሁና አላዘር ሻንጣውን ተቀብለው ወደመኪናው ወሰዱና ከኋላ ጫኑለት፡፡…በአላዛር ሹፌርነት ሰሎሜ ገቢና ከእሱ ጎን ተቀምጣ አለማየሁና ሁሴን ከኋላ ሆነው ወደቤት ጉዞ ጀመሩ፡፡
ድንገት‹‹ይገርማል…?››አለ ሁሴን፡፡
አለማየሁ‹‹ምኑ ነው የገረመህ?ከተማዋ ልደቷን የምታከብር የቢሊዬነር ብቸኛ ልጅ መሰለችህ አይደል…?››አለው፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹አሸብርቃና ተኳኩላ …በደማቅ መብራቷች ተንቆጥቁጣ ስታያት ገርሞህ እንደሆነ ብዬ ነዋ?››
‹‹..አዎ ያልከው ነገር በጣም አስገርሞኛል..ግን እኔ ለማውራት የፈለኩት ሶስታችሁን በአንድነት መጥታችሁ ትቀበሉኛላቹሁ የሚል ምንም አይነት ግምት ስላልነበረኝ በዛ መደነቄን ነው፡፡፡፡›
ልክ እንደሁሴን እሷም ሶስቱም የልጅነት እና የአፍላ ወጣትነት ጓደኞቾ እና አፍቃሪዎቾ ከበርካታ አመታት በኋላ እንዲህ አንድ ላይ ተሰብስበው አይናቸው እሷ ላይ ሲያቁለጨለጩ በመመለከቷ እየተገረመች‹‹ምን ማለት ነው? ሶስታችንም እኩል ጓደኞችህ አይደለንም እንዴ…?ለመሆኑ መጥቶ ይቀበለኛል ብለህ የገመትከው ማንን ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው አሌክስን ነበር፡፡እናንተን በማግስቱ ባገኛችሁ ብዬ ነበር ያሰብኩት፡፡››
‹‹አንተ …ከእኛ ይልቅ አሌክስ ቁምነገረኛ የሆነው ከመቼ ወዲህ ነው…?ነው ሰው ሀገር ከሄድክ በኃላ ፀባያችን ተምታታብህ››አለችው ሰሎሜ በመገረም፡፡
አለማየው በፈገግታ‹‹አንቺ …ሰው ሁሉ ስለእኔ ልክ እንደአንቺ የተሳሳተ ግምት ያለው ይመስልሻል እንዴ?››አላት፡፡
‹‹ተው ተው…ከመሀከላችንማ አንደኛው ቁምነገረኛና ኃላፊነትን የሚወስደው አላዛር ነው…አንተ እንደውም በዚህ ጉዳይ የመጨረሻው ሰው ነህ››አለው ሁሴን፡፡
‹‹አንተ ዲያስፖራ ለመሆኑ ዜግነትህን ቀይረሀል?››ሲል ጠየቀው፡፡
ያልጠበቀውን ጥያቄ ስለተጠየቀው ግራ ተጋባ‹‹አይ አልቀየርኩም…ግን ለምን ጠየቅከኝ?››
‹‹አይ ኢትዬጵያዊ ዲያስፖራ ከሆንክ የሚጮህልህ ኤምባሲ ስለሌለ ለዚህ ንግግርህ የሆነ ሰበብ ፈልጌ ከርቸሌ ልወረውርህ ነዋ….እንደድሮ አለማየሁ ብቻ አይደለሁም..ኩማንደር አለማየሁ ነኝ፡፡››
👍63❤8👎2🔥1🥰1
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
/////
እሱም ጃኬቱን ይዞ ተከተላት፡፡እራሱ እያሸከረከረ የምትፈልገው መስሪያ ቤት ድረስ ወሰዳት፡፡
‹‹እ…ትጠብቀኛለህ ወይስ ትሄዳለህ?››
‹‹ኸረ በፍፁም.. አብሬሸ እገባለው››
‹‹ተው እዚሁ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ..ከአንተ ጋር የሆነ ቦታ መሄድ እኳ በሴቶች አይን ክፉኛ መገረፍ ነው..ታውቃለህ የሰው አይን ደግሞ ያቃጥላል፡፡››
‹‹አረ ባክሽ…!!!››ሞተሩን አጠፋና ከመኪናው ወረዳ… እሷም ወረደች…ክንዷን ያዘና ወደውስጥ መራመድ ጀመረ..መራመድ አቅቷት እግሯቾ ተሳሰሩባት፡፡ግን ምርጫ አልነበራትም፡፡
ግቢ ውስጥ ገቡና ወደኢንፎሪሜሽን ዴስክ ሲደርሱ እሱን እንግዳ ማረፊያ ወንበር ላይ አስቀጠችውና እሷ ወደዛው አመራች…ከአስር ደቀቂቃ በኃላ ግን አንገቷን ደፍታ ወደእሱ ተመለሰችና ከጎኑ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ምነው ፍቅር…አገኘሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ ..ጠመሙብኝ …ሰውዬው ከአራት አመት በፊት የዚህ ቢሮ ዳሬክተር ዴሬክቶሬት ነበረ…አሁን የት እንዳለና ቢያንስ ስልኩን እንዲሰጡኝ ነበር የጠየቅኳቸው…››
‹‹ቆይ ሰውዬው ምንሽ ነው?››
‹‹ምኔም አይደለም..ጭራሽም አላውቀውም..ግን ስለአባቴ መረጃ እንዳለው በሆነ መንገድ አውቄለው…እሱን ካገኘው አባቴ ይሙት ይኑር ማወቅ እችላለው፡፡››
የነገረችውን ያለምንም ጥርጣሬ አመናት…አሳዘነችው፡፡‹‹የሰውዬው ስም ማን ነው?››
ሙሉ ስሙን ነገረችው፡፡
‹‹ቆይ እንደውም ተነሽ›› ብሎ እጇን ይዞ ወደኢንፎርሜሽን ዴስኩ መራመድ ጀመረ..እሷ ምን ሊያደርግ እንደሆነ ሳይገባት ዝም ብላ ተጎተተችለት፡፡እንደደረሰ በትንሿ መስኮት ጎንበስ ብሎ ሲመለከት ..ሁለት ልጅ እግር ሴቶች ታዩት
‹‹ጤና ይስጥልኝ?›› ሲላቸው ሁለቱም አፋቸውን ከፍተው ፀጥ አሉት፡፡
‹‹እባካችሁ የሆነ ነገር ላስቸግራችሁ ነበር››
‹‹ምን ፈለክ…?ምን እንርዳህ?››አንደኛዋ ከመቀመጫዋ ተነስታ በመንሰፍሰፍ ጠየቀችው፡፡
‹‹እሷ እህቴ ነች..ከኃላው ያለችውን ፀአዳን ተመለከተችና‹‹ማንን ነበር ያልሽን?››ስትል ድጋሚ ጠየቀቻት፡፡
ፀአዳ ነገረቻት፡፡‹‹ቆይ እስኪ ››አለችና በኋላው በራፍ በመውጣት ወደእነሱ መጣች..እስቲ ተከተሉኝ ጋሽ ይርጋ በደንብ ያውቃሉ፡፡ጋሽ ይርጋ ማለት እዚህ መስሪያ ቤት ለ30አመት የሰሩ የመዝገብት ቤት ሰራተኛ ናቸው፡፡››የምታወራውን እያዳመጡ ከኋላ ተከተሏት‹‹አስቸገርን አይደል..?››አላት፡፡
ወደኃላ ዞራ‹‹‹አረ ችግር የለውም…ለዛውም ላንተ..ባይ ዘወዌ በጣም አድናቂህ ነኝ››አለችው
‹‹አመሰግናለው››ትህትና ባልተለየው የድምፅ ቃና መለሰላት፡፡
ከ10 ደቂቃ በኃላ የሰውየውን ሙሉ አድራሻ ይዘው ከቢሮ ወጡ…መኪና ውስጥ ገብተው መጓዝ እንደጀመሩን‹‹አየሽ አንቺን ሰምቼ ከስርሽ ቀርቼ ቢሆን ኖረ ምን እንደሚያጋጥምሽ ተመልከቺ››አላት በኩራት፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..አድራሻውን እንዲህ በቀላሉ አላገኘውም ነበር›
‹‹እና ሽልማት የለኝም?››
‹‹አለህ..ምን ትፈልገለህ…?መክሰስ ልጋብዝህ?››
‹‹አዎ ግን ቤትሽ››
‹‹ቤትሽ?››ግራ በመጋባት አፍጥጣ አየችው፡፡
‹‹አዎ ምነው ላደርስሽ አይደል…አሁን አስር ተኩልነው… አስራሁለት ሰዓት ሳይሆን እዛ እንደርሳለን…ከዛ ቤትሽ መክሰስ ትጋብዢኛለሽ››
‹‹ለምን መክሰስ..እራት ቢሆንልህ አይሻልም….በዛውም ታድራለህ››
በፈገግታ ተሞልቶ‹‹አንቺ እኮ ምርጥ ነሽ…….››ሲል መለሰ
‹‹አረ አላደርገውም …..ጎረቤቶቼስ ምን ይሉኛል.?.››
‹‹ምንም ይበሉሽ……››
‹‹አይ አይቻልም ከፈለክ ውጭ ልጋብዝህ››
‹‹ውጭ አልፍግም….. ባይሆን እዛ እስክንደርስ አስቢበት››አላት፡
ቀጥታ ወደአዳማ እየነዳ ነው፡፡‹‹አሁን ታዲያ እንዴት ልታደርጊ ነው?››
‹‹ግራ ገብቶኛል..ግን ምን ቢሆን ነው አንድ አመት ሙሉ አማኑኤል ህክምና ላይ የቆየው››
‹‹ያው አማኑኤል ምን ሲኮን ነው የሚቆየው? ጭንቅላቱን አሟት ነዋ….፡፡››መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ከዛ ሲወጣ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ቤተሰቦቹ ጋር ቦንጋ እንደገባ ነው የነገሩን ..እንዴት እንደዛ አይነት ውሳኔ ወሰነ…?ይታይህ በአንድ ወቅት ትልቅ ስልጣን ላይ የነበረ ጉምቱ ባለስልጣን በዛ ላይ ዶ/ር ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ቦንጋ …ከቦንጋም ገጠር ጠቅልሎ ሲገባ አይገርምም፡፡
‹‹ይገርማል..ግን እደእኔ እንደእኔ የብልህ ውሳኔ ነው የወሰነው ..ይሄ ሰው ጭንቀትና የአእምሮ በሽታ ካለበት ትክክለኛ መረጋጊያ ቦታ ገጠር ነው..ይታይሽ እዚህ አዲስ አበባ እንኳን ለአእመሮ ህመምተኛ ለጤነኛው ሰው ትርምሱና ኳኳታው አስጨናቂ ነው…ይልቅ እኔ ያሳሰበኝ ….አሁን ምን ልታደርጊ ነው?፡፡የሚለው ነው፡፡
‹‹ቦታው ላይ ሄጄ እድሌን ሞክራለው››ስትል በእርግጠኝነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእውነት ?››አለ ደነግጦ፡፡
‹‹አዎ….ይሄ እኮ ሲሪዬስ ነገር ነው….››
‹‹አውቃለው ..ግን እዛ ደረስ ሄደሽ ምንም ሊነግርሽ ባይችልስ…..?ማለቴ ከጤናው አንፃር ምንም ነገር ባያስታውስስ?››
‹‹ምንም ይሁን ምን ሰውዬውን ፊት ለፊት አግኝቼው መሞከር እፈልጋለው….ካለበለዚያ,--እረፍት አላገኝም፡፡››ስትል መለሰችለት፡፡
///
አቶ ቅጣው አዲሱ ክፍሉ በጣም ተመችቶታል…እንደውም በፊት ካለበት ክፍል ጋር ሲነፃፀር ከሲኦል ወደገነት የመዘዋወር አይነት ነው፡፡መኝታ አልጋ ያለው ..በቂ ብርሀን የሚያስገባ ንፁህ ክፍል ነው ያስገቡት፡፡በዛ ላይ እግሩም ሆነ እጁ ከሰንሰለት እስር ነፃ ስለሆነና ምግብም ሰዓቱን ጠብቆ ስለሚመጣለት ሰውነቱ ተአምራዊ በሆነ መልኩ እያገገመ ነው፡፡ክፍል ውስጥም ቢሆን እንደፈለገው እየተንቀሳቀሰ ቀላል ስፖርቶችን መስራት ችሏል…በዛ ምክንያት መንፈሱም ሆነ አካሉ ልዩ ለውጥ አምጥቷል፡፡
አሁን ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቁዱስ እያነበበ ነው፡፡ይሄንን መፅሀፍ ቅዱስ ከ10 ቀን በፊት ነበር ጠያቂው እና መካሪው መነኩሴ ናቸው አምጥተው የሰጡት፡፡ወዲያው ግን ማንበብ አልቻለም ነበር…፡፡አይኖቹ ለወራት ጨለማ ክፍል ውስጥ ስለከረሙ በቀላሉ ከብዣታ አገግመው ፊደል እየለቀሙ ለማንበብ ተቸግረው ነበር…ከጥቂት ቀናት ወደዚህ ግን እንደምንም ለማንበብ ችሏል፡፡
መለኩሴው የመጡ ቀን እንደተለመደው..ጠያቂ አለህ ተብሎ ነበር ከክፍል የተወሰደው፡፡የሚጠብቁት ክፍል ውስጥ ሲገባ እንደወትሮ በሰንሰለት እጅና እግሮቹ ተጠፍሮ የተቀደደ እና የተቦጫጨቀ ልብስ ለብሶ ሳይሆን በተለየ ሁኔታ ነበር፡፡እና በዚህ ሁኔታ ይደነቃሉ ብሎ ጠብቆ የነበረ ቢሆንም መነኩሴው ግን ልክ እንደወትሮ በተመሳሳይ ስሜት ነበር ያተናገሩት
ልጄ ይህ ግንኙነታችን የመጨረሻችን ነው… ልሰናበትህ ነው የመጣውት..›› ሲሉት ከዚ በፊት ተሰምቶት የማያውቀው ብቸኝነት ነው የተሰማው፡፡
‹‹አባ ለምን…?መመላለሱን ሰለቹ እንዴ?››
‹‹አይደለም… ልጄ ልሄድ ነው››
‹‹ወዴት ነው የሚሄዱት?››
‹‹ወደአባቴ…ወደፈጣሪ››
ሌላ ድንጋጤ፣‹‹እንዴ ያሞታል እንዴ?››
ፈገግ አሉ‹‹ አይ ልጄ ወደፈጣሪ ለመሄድ እኮ የግድ መታመም የለብንም…አምላክ በቃ ወደእኔ ና ብሎኛል…የዛሬዋን የመጨረሻ ቀኔ አንተንና ሌሎች ልጆቼን ለመሰናብት ነው የሰጠኝ..መቼስ ፡እሱ ለቸርነቱ ዳርቻ የለው… እኔ ሀጥያተኛውን መሞቻ ቀኔን ነገሮች ለመሰናበቻ ሚሆን ቀን ፈቅዶልኝ…ተመስገን ነው ..ተመስገን፡፡››
መነኩሴው የሚያወሩትን ሊገባው አልቻለም፡፡‹‹አባ እኔ ሞት የተፈረደብኝ ሰው እያለው እርሶ…..››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
/////
እሱም ጃኬቱን ይዞ ተከተላት፡፡እራሱ እያሸከረከረ የምትፈልገው መስሪያ ቤት ድረስ ወሰዳት፡፡
‹‹እ…ትጠብቀኛለህ ወይስ ትሄዳለህ?››
‹‹ኸረ በፍፁም.. አብሬሸ እገባለው››
‹‹ተው እዚሁ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ..ከአንተ ጋር የሆነ ቦታ መሄድ እኳ በሴቶች አይን ክፉኛ መገረፍ ነው..ታውቃለህ የሰው አይን ደግሞ ያቃጥላል፡፡››
‹‹አረ ባክሽ…!!!››ሞተሩን አጠፋና ከመኪናው ወረዳ… እሷም ወረደች…ክንዷን ያዘና ወደውስጥ መራመድ ጀመረ..መራመድ አቅቷት እግሯቾ ተሳሰሩባት፡፡ግን ምርጫ አልነበራትም፡፡
ግቢ ውስጥ ገቡና ወደኢንፎሪሜሽን ዴስክ ሲደርሱ እሱን እንግዳ ማረፊያ ወንበር ላይ አስቀጠችውና እሷ ወደዛው አመራች…ከአስር ደቀቂቃ በኃላ ግን አንገቷን ደፍታ ወደእሱ ተመለሰችና ከጎኑ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ምነው ፍቅር…አገኘሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ ..ጠመሙብኝ …ሰውዬው ከአራት አመት በፊት የዚህ ቢሮ ዳሬክተር ዴሬክቶሬት ነበረ…አሁን የት እንዳለና ቢያንስ ስልኩን እንዲሰጡኝ ነበር የጠየቅኳቸው…››
‹‹ቆይ ሰውዬው ምንሽ ነው?››
‹‹ምኔም አይደለም..ጭራሽም አላውቀውም..ግን ስለአባቴ መረጃ እንዳለው በሆነ መንገድ አውቄለው…እሱን ካገኘው አባቴ ይሙት ይኑር ማወቅ እችላለው፡፡››
የነገረችውን ያለምንም ጥርጣሬ አመናት…አሳዘነችው፡፡‹‹የሰውዬው ስም ማን ነው?››
ሙሉ ስሙን ነገረችው፡፡
‹‹ቆይ እንደውም ተነሽ›› ብሎ እጇን ይዞ ወደኢንፎርሜሽን ዴስኩ መራመድ ጀመረ..እሷ ምን ሊያደርግ እንደሆነ ሳይገባት ዝም ብላ ተጎተተችለት፡፡እንደደረሰ በትንሿ መስኮት ጎንበስ ብሎ ሲመለከት ..ሁለት ልጅ እግር ሴቶች ታዩት
‹‹ጤና ይስጥልኝ?›› ሲላቸው ሁለቱም አፋቸውን ከፍተው ፀጥ አሉት፡፡
‹‹እባካችሁ የሆነ ነገር ላስቸግራችሁ ነበር››
‹‹ምን ፈለክ…?ምን እንርዳህ?››አንደኛዋ ከመቀመጫዋ ተነስታ በመንሰፍሰፍ ጠየቀችው፡፡
‹‹እሷ እህቴ ነች..ከኃላው ያለችውን ፀአዳን ተመለከተችና‹‹ማንን ነበር ያልሽን?››ስትል ድጋሚ ጠየቀቻት፡፡
ፀአዳ ነገረቻት፡፡‹‹ቆይ እስኪ ››አለችና በኋላው በራፍ በመውጣት ወደእነሱ መጣች..እስቲ ተከተሉኝ ጋሽ ይርጋ በደንብ ያውቃሉ፡፡ጋሽ ይርጋ ማለት እዚህ መስሪያ ቤት ለ30አመት የሰሩ የመዝገብት ቤት ሰራተኛ ናቸው፡፡››የምታወራውን እያዳመጡ ከኋላ ተከተሏት‹‹አስቸገርን አይደል..?››አላት፡፡
ወደኃላ ዞራ‹‹‹አረ ችግር የለውም…ለዛውም ላንተ..ባይ ዘወዌ በጣም አድናቂህ ነኝ››አለችው
‹‹አመሰግናለው››ትህትና ባልተለየው የድምፅ ቃና መለሰላት፡፡
ከ10 ደቂቃ በኃላ የሰውየውን ሙሉ አድራሻ ይዘው ከቢሮ ወጡ…መኪና ውስጥ ገብተው መጓዝ እንደጀመሩን‹‹አየሽ አንቺን ሰምቼ ከስርሽ ቀርቼ ቢሆን ኖረ ምን እንደሚያጋጥምሽ ተመልከቺ››አላት በኩራት፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..አድራሻውን እንዲህ በቀላሉ አላገኘውም ነበር›
‹‹እና ሽልማት የለኝም?››
‹‹አለህ..ምን ትፈልገለህ…?መክሰስ ልጋብዝህ?››
‹‹አዎ ግን ቤትሽ››
‹‹ቤትሽ?››ግራ በመጋባት አፍጥጣ አየችው፡፡
‹‹አዎ ምነው ላደርስሽ አይደል…አሁን አስር ተኩልነው… አስራሁለት ሰዓት ሳይሆን እዛ እንደርሳለን…ከዛ ቤትሽ መክሰስ ትጋብዢኛለሽ››
‹‹ለምን መክሰስ..እራት ቢሆንልህ አይሻልም….በዛውም ታድራለህ››
በፈገግታ ተሞልቶ‹‹አንቺ እኮ ምርጥ ነሽ…….››ሲል መለሰ
‹‹አረ አላደርገውም …..ጎረቤቶቼስ ምን ይሉኛል.?.››
‹‹ምንም ይበሉሽ……››
‹‹አይ አይቻልም ከፈለክ ውጭ ልጋብዝህ››
‹‹ውጭ አልፍግም….. ባይሆን እዛ እስክንደርስ አስቢበት››አላት፡
ቀጥታ ወደአዳማ እየነዳ ነው፡፡‹‹አሁን ታዲያ እንዴት ልታደርጊ ነው?››
‹‹ግራ ገብቶኛል..ግን ምን ቢሆን ነው አንድ አመት ሙሉ አማኑኤል ህክምና ላይ የቆየው››
‹‹ያው አማኑኤል ምን ሲኮን ነው የሚቆየው? ጭንቅላቱን አሟት ነዋ….፡፡››መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ከዛ ሲወጣ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ቤተሰቦቹ ጋር ቦንጋ እንደገባ ነው የነገሩን ..እንዴት እንደዛ አይነት ውሳኔ ወሰነ…?ይታይህ በአንድ ወቅት ትልቅ ስልጣን ላይ የነበረ ጉምቱ ባለስልጣን በዛ ላይ ዶ/ር ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ቦንጋ …ከቦንጋም ገጠር ጠቅልሎ ሲገባ አይገርምም፡፡
‹‹ይገርማል..ግን እደእኔ እንደእኔ የብልህ ውሳኔ ነው የወሰነው ..ይሄ ሰው ጭንቀትና የአእምሮ በሽታ ካለበት ትክክለኛ መረጋጊያ ቦታ ገጠር ነው..ይታይሽ እዚህ አዲስ አበባ እንኳን ለአእመሮ ህመምተኛ ለጤነኛው ሰው ትርምሱና ኳኳታው አስጨናቂ ነው…ይልቅ እኔ ያሳሰበኝ ….አሁን ምን ልታደርጊ ነው?፡፡የሚለው ነው፡፡
‹‹ቦታው ላይ ሄጄ እድሌን ሞክራለው››ስትል በእርግጠኝነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእውነት ?››አለ ደነግጦ፡፡
‹‹አዎ….ይሄ እኮ ሲሪዬስ ነገር ነው….››
‹‹አውቃለው ..ግን እዛ ደረስ ሄደሽ ምንም ሊነግርሽ ባይችልስ…..?ማለቴ ከጤናው አንፃር ምንም ነገር ባያስታውስስ?››
‹‹ምንም ይሁን ምን ሰውዬውን ፊት ለፊት አግኝቼው መሞከር እፈልጋለው….ካለበለዚያ,--እረፍት አላገኝም፡፡››ስትል መለሰችለት፡፡
///
አቶ ቅጣው አዲሱ ክፍሉ በጣም ተመችቶታል…እንደውም በፊት ካለበት ክፍል ጋር ሲነፃፀር ከሲኦል ወደገነት የመዘዋወር አይነት ነው፡፡መኝታ አልጋ ያለው ..በቂ ብርሀን የሚያስገባ ንፁህ ክፍል ነው ያስገቡት፡፡በዛ ላይ እግሩም ሆነ እጁ ከሰንሰለት እስር ነፃ ስለሆነና ምግብም ሰዓቱን ጠብቆ ስለሚመጣለት ሰውነቱ ተአምራዊ በሆነ መልኩ እያገገመ ነው፡፡ክፍል ውስጥም ቢሆን እንደፈለገው እየተንቀሳቀሰ ቀላል ስፖርቶችን መስራት ችሏል…በዛ ምክንያት መንፈሱም ሆነ አካሉ ልዩ ለውጥ አምጥቷል፡፡
አሁን ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቁዱስ እያነበበ ነው፡፡ይሄንን መፅሀፍ ቅዱስ ከ10 ቀን በፊት ነበር ጠያቂው እና መካሪው መነኩሴ ናቸው አምጥተው የሰጡት፡፡ወዲያው ግን ማንበብ አልቻለም ነበር…፡፡አይኖቹ ለወራት ጨለማ ክፍል ውስጥ ስለከረሙ በቀላሉ ከብዣታ አገግመው ፊደል እየለቀሙ ለማንበብ ተቸግረው ነበር…ከጥቂት ቀናት ወደዚህ ግን እንደምንም ለማንበብ ችሏል፡፡
መለኩሴው የመጡ ቀን እንደተለመደው..ጠያቂ አለህ ተብሎ ነበር ከክፍል የተወሰደው፡፡የሚጠብቁት ክፍል ውስጥ ሲገባ እንደወትሮ በሰንሰለት እጅና እግሮቹ ተጠፍሮ የተቀደደ እና የተቦጫጨቀ ልብስ ለብሶ ሳይሆን በተለየ ሁኔታ ነበር፡፡እና በዚህ ሁኔታ ይደነቃሉ ብሎ ጠብቆ የነበረ ቢሆንም መነኩሴው ግን ልክ እንደወትሮ በተመሳሳይ ስሜት ነበር ያተናገሩት
ልጄ ይህ ግንኙነታችን የመጨረሻችን ነው… ልሰናበትህ ነው የመጣውት..›› ሲሉት ከዚ በፊት ተሰምቶት የማያውቀው ብቸኝነት ነው የተሰማው፡፡
‹‹አባ ለምን…?መመላለሱን ሰለቹ እንዴ?››
‹‹አይደለም… ልጄ ልሄድ ነው››
‹‹ወዴት ነው የሚሄዱት?››
‹‹ወደአባቴ…ወደፈጣሪ››
ሌላ ድንጋጤ፣‹‹እንዴ ያሞታል እንዴ?››
ፈገግ አሉ‹‹ አይ ልጄ ወደፈጣሪ ለመሄድ እኮ የግድ መታመም የለብንም…አምላክ በቃ ወደእኔ ና ብሎኛል…የዛሬዋን የመጨረሻ ቀኔ አንተንና ሌሎች ልጆቼን ለመሰናብት ነው የሰጠኝ..መቼስ ፡እሱ ለቸርነቱ ዳርቻ የለው… እኔ ሀጥያተኛውን መሞቻ ቀኔን ነገሮች ለመሰናበቻ ሚሆን ቀን ፈቅዶልኝ…ተመስገን ነው ..ተመስገን፡፡››
መነኩሴው የሚያወሩትን ሊገባው አልቻለም፡፡‹‹አባ እኔ ሞት የተፈረደብኝ ሰው እያለው እርሶ…..››
👍61❤15😱1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
‹ከሃያ ደቂቃ በኋላ ቢሮዬ እንገናኝ።››
በእሺታ ራሷን ነቀነቀች፣ ከዚያም አልፋው ጥላው ሄደች፡፡
ከግማሽ ሰአት በኋላ ራሄል ቢሮው መጥታ ከጠረጴዛው ማዶ ተቀመጠች፣ በአንድ እጇ እስክሪብቶ፣ በሌላ እጇ ማስታወሻ ደብተር ይዛለች። ሁኔታዋ አስገረመው ፡፡
ዶ/ር ዔሊያስ መናገር ጀመረ ‹‹ፀጋ በቴክኒካል ተርሙ ሄሚፕሌጂያ ተብሎ የሚጠራ በሽታ ተጠቂ ነች፡፡በሌላ አነጋገር ሴሬብራል ፓልሲ ታማሚ ነች ማለት ነው፡፡ በሰውነቷ አንድ ጎን በግራ እጇ እና በግራ እግሯ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮባታል..አጥንቶቾ በጣም ደካማ ስለሆኑ እንደልብ ለመንቀሳቀስ ትቸገራለች…በተወሰነ መልኩ የመስማትና ቃላቶችን አቀላጥፎ የማውራት ችግርም አለባት።የእሷን ጤና ሁኔታ ለማሻሻል በሚደረገው ሂደት ውስጥ የሚሳተፉትን - ፊዚዬ ቴራፒስት ጨምሮ፣ ብዙ ባለሞያዎች አሉ.. እና እያንዳንዱን መቼ መቼ ማየት እንዳለባት አስረዳት፡፡
‹‹በተጨማሪም የጆሮ ኢንፌክሽንን እየተዋጋች ስለነበረ አንቲባዮቲክ ትወስዳለች።››ዔሊ የራሔልን እይታ በመሸሽ እስክሪብቶውን አንሥቶ መሞነጫጨር ጀመረ።
ራሄል ትዕግስት በማጣት‹‹ዶክተር ሌላ ልትነግረኝ የሚገባ ነገር እንዳለ ይሰማኛል››አለችው.
‹‹ትሁት ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት በሽታ እየተሰቃየች ነው ። ስለዚህ ስሜቷን በጥንቃቄ መከታተል እና የሚያበሳጮትን ነገሮች ማስወገድ ያስፈልግሻል ማለት ነው ።ያው እንድትናደድ ከፈቀድሽላት የሚጥል በሽታ ስላለባት ነገሮች ይባባሳሉ… እንደ አለመታደል ሆኖ ይሄንን ጉዳይ በመድኃኒቷን ማስተካከል አልቻልንም።››
‹‹ትሁት ማለት?››ግራ በመጋባት ጠየቀችው
‹‹ይቅርታ..ፀጋ ወደእናንተ ቤት ከመምጣቷ በፊት ወላጅ እናቷ ትሁት ብላ ነበር ስም ያወጣችላት….ከዛ ነው አባትሽ ፀጋ ያለት፡፡እና እኔ ትሁት የሚለውን ስም ለረጅም ጊዜ ስለተጠቀምኩበት በቀላሉ ከአእምሮዬ ላወጣው አልቻልኩም…..››
‹‹አይ ችግር ለውም..ትሁትም ደስ የሚል ስም ነው››
‹‹አዎ…እና እንዳልኩሽ ፀጋ ማለት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋት ልጅ ነች፣፣በተለይ መናደድ የለባትም….ምክንያቱም ከንዴቷ በኋላ የሚከሰተው የሚጥል በሽታ ሌሎች ብዙ የጤና ችግሯቾን ነው የሚያናጋባት››
በራሔል ፊት ላይ የፍርሃት ብልጭታ ሲያይ ተገረመ።
‹‹የሚጥል በሽታ ሊነሳባት መሆኑን እንዴት አውቃለሁ እና ምን ያህል መጥፎ ነው?››
‹‹ትለይወለሽ…እጆቿ ይንቀጥቀጣሉ… የዐይን ሽፋኖቿን ይርገበገባሉ እነዚህን እና የመሳሰሉት ምልክቶችን ታሳያለች፡፡የዛን ጊዜ አጓጉል ወድቃ እራሷን እንዳትጎዳ ጥንቃቄ መውሰድ ይገባሻል፡፡ ማንኛውም አሳሳቢ የጤና ችግር ሲያጋጥማት በአፋጣኝ ወደሆስፒታል ልትወስጂያት የግድ ነው፡፡ በመደበኝነት በሳምንት ሶስት ቀን ሆስፒታል የህክምና ክትትል አለት፡፡በመሀል አስፈላጊ ሲሆን ለእኔ በማንኛውም ሰዓት ልትደውይልኝ ትችያለሽ ፣ ወዲያውኑ ልመጣ እችላለሁ።..›› ዔሊያስ መጀመሪያ ያሰበው ለፀጋ ነው።‹ራሔል በዚህች ልጅ ላይ ያለውን ችግር በሙሉ ማወቅ አለባት› ሲል በውስጡ አሰበ፡፡
‹‹ፀጋን ከተወለደች ቀን ጀምሮ እየተንከባከባት ነበር…እናትዬው ተስፋ ቆርጣበት በሆስፒታል አልጋ ላይ ማሽን እንደተሰካካባት ጥላት ስትሰወርም አንደኛ እናትዬውን ከልጅነት ጀምሮ የሚያውቃት ጓደኛው ስለሆነች ሲሆን ሁለተኛም ከራሱ ህይወት ጋር አያይዞ ሲንከባከባትና እንደወላጅ ስለሚጨነቅላት ነው፡፡በመጨረሻም ከስድስት ወር የሆስፒታል ቆይታዋ በኃላ የራሄልን ወላጆችን በግሉ ፈልጎ በማግኘት በጉዲፈቻ እንዲወስዷት በማድረግ ሂደት ላይ የአንበሳውን ድርሻ የእሱ ነው፡፡ከዛም በኃላ በቃ በኃላፊነት የሚያሳድጓት እና የሚንከባከቧት ወላጆች አግኝታለች ብሎ አልተዋትም፤ በቆሚነት የእሷ ሀኪም በመሆን እነ አቶ ቸርነት ቤት ድረስ እየተመላለሰ ሁኔታዋን ይከታተላል፤ ታማለች ብለው ሲደውሉለት ያለምንም ማቅማማት ሞተሩን ተረክ አድርጎ በሮ ይሄድና ያያታል…እናም ይህቺ ልጅ ለእሱ እንደአንድ ታካሚው ብቻ አይደለችም…የህይወቱ አካል ነች….ስቃዮ ያመዋል…ለቅሶዋ ይሰማዋል….ፈገግታዋ ያስቀዋል….ለዛ ነው ራሄልን በትክክል እናቷ በምትንከባከባት መጠን ትንከባከባታለች ብሎ ሊያምን ያልቻለው፡፡
‹‹ራሄል ምን መሰለሽ ፀጋን እንዲህ ስታያት በአካላዊ እይታ ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለች ሊመስልሽ ይችላል, ግን ውስብስብ በሆነ የህክምና ሂደት ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰውነቷ እየሰጠ ያለው መልስ በጣም ደካማ ነው. ለሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት በጤና እሷን ማቆየት ከቻልን ትልቅ ድል ነው…በህክምናው ሂደት ከባድ ችግር እያጋጠመን ነው ››
ራሔል በፍጥነት ማስታወሻ እየወሰደች ሲሆን በእጇ ላይ ትንሽ መንቀጥቀጥ አየ፡፡‹‹ስለ ምን ዓይነት የሕክምና ችግሮች ነው የምታወራው?››
‹‹በአእምሯዋ ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ጀምሮል እና ተጨማሪ ኢንፌክሽኖች እና ሌሎች ችግሮችም እየተከሰቱባት ነው፡፡››
እሺ፣ ምናልባት ትንሽ አክብዶባት ሊሆን ይችላል ግን ማወቅ አለባት። የበለጠ መረጃ ባላት ቁጥር እሷ ማድረግ የምትችለው የተሻሉ ውሳኔዎች ትወስናለች፣ ።
‹‹ወላጆቼ ግን ፀጋ ያለባትን ይሄን ሁሉ የጤና ችግር ያውቃሉ?››
‹‹አዎ..እንደውም ለአንቺ በጥቅሉ ነው የነገርኩሽ እንሱ ግን እሷን ለማሳደግ ከመወሰናቸው በፊት እያንዳንዱን በዝርዝር አስረድቻቸዋለው…..ግን ለምን ጠየቅሺኝ?››
‹‹እኔ እንጃ…..በዚህ ሁሉ የጤና እክል ውስጥ ሆኖ ምን አልባትም የመሞቻ ቀኗን እየተጠባበቀች ያለች እና ክፉና ደጉን የማታውቅ ልጅ እንዴት ለማሳደግ እንደፈቀዱ ግራ ስለገባኝ ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ….እኔም ወላጆችሽን በጣም የማከብራቸውና ከልቤ ማደንቃቸው በዚህ ውሳኔያቸው ነው…እነሱ ያደረጉትን ማንም ሌላ ሰው ያደርገዋል ብዬ አላስብም..እነሱ ለእኔ የህይወት ዘመን ጀግናዎቼ ናቸው፡፡››አለና ካርዱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ሰጣት። ‹‹ይህ የሆስፒታሉ የድንገተኛ አደጋ ቁጥር፣የቤቴ ቁጥር እና የሞባይል ቁጥሬ ነው። በፈለግሺኝ ጊዜ ደዉይልኝ››ራሄል መረጃውን እንደያዘች ረጅም እና ዘገምተኛ ትንፋሽ ወደ ውስጣ ሳበች ከዛ ወደ ውጭ ተነፈሰች፡፡ ወረቀቱን እና ካርዱን በቦርሳዋ ውስጥ አስገባች።
‹‹ከመሄዴ በፊት ግን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅህ?››
‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ››አላት በጉጉት፡፡
‹‹ፀጋን ቤተሰቦቼ እንዲያሳድጓት በግል የጠየቅካቸውና ያሳመንካቸው አንተ ነህ….ለሌሎችም ታካሚዎችህ እንደዛ ታደርጋለህ?››ስትል ያለሳበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር የፀጋ እናት የልጅነት ጎደኛዬ ነች…አንድ ሰፈር ነው ያደግነው…ህይወት ባልሆነ መንገድ መርታ ያልሆነ ማጥ ውስጥ ጨመረቻት እንጂ እንዲህ እንደቀልድ ልጇን ጥላ የምትሰወር ልጅ አልነበረችም….እና ፀጋን ዝም ብዬ ችላ ብዬ ማደጎ ቤት ስትገባ ማየት አልቻልኩም…የምተማመንባቸው አሳዳጊዎች መፈለግ ጀምርኩ..መጀመሪያ የራሴ ወላጆች ነበር የመጡልኝ..ግን የጽጌረዳ ሰፈር እዛው ስለነበረ ትንሽ ልክ መስሎ አልተሰማኝም….ከዛ ምክንያት ነው ወላጆችሽን ያገኘሁት…እናም ደግሞ ሁሉንም ነገር በግልፅ ነግሬያቸዋለው….ምንም የማያውቁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አባቷስ?››
‹‹ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅ…አባቷ እንደሞተ ነው የነገረችኝ… ሌላ ጥያቄ ይኖርሻል?››
‹‹ አይ የለኝም..አመሰግናለው…. ››አለች… ቆመች… እጁን ለመጨበጥ ከጠረጴዛው አሻግራ እጇን ዘረጋች፡፡
❤75👍3🥰1
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
❤55
#እናትነት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//////
የእኔ ቅንዝርነት የልጅቷ ድህነት፤እናትነት እና ተስፋ ቢስነት
ስሟ ግን ማን ነበር?
ምን አይነት ችግር ላይ እንዳለሁ ልትገምቱ አትችሉም፡፡ ሀገር አማን ነው ብዬ በእንቅልፍ ዓለም ከተዋጥኩ በኋላ በእኩለ ለሊት ላይ ለመንገድ መብራት ማቆሚያ እደተተከለ የእንጨት ምሰሶ ቀጥ ይላል፡፡ ቀጥ ማለቱ ብቻ አይደለም እኮ የሚያበሳጨኝ ቀጥ በማለቱ ውስጥ ጥዝጣዜ ነገር አለው፡፡ የመነዝነዝ ዓይነት እና ለመግለፅ የሚያስቸግር ግራ አጋቢ ህመም ከእቅልፍ እስከማባበነን ድረስ የሚደርስ ኃይል ያለው ህመም ፡፡እስከአሁን ስለምን እንደማወራችሁ አልገባችሁም አይደል?
እንጠራራ እና ከእንቅልፌ ጋር እየታገልኩ ዓይኔን እያሻሸው በዳበሳ ወደ ሽንት ቤት ሄዳለው… ምን አልባት ሽንቴ ወጥሮኝ እንደሆነ ብዬ…ግን ብጨምቀው ባልበው ጠብ አይለኝም ፡፡
በንጭንጭ ወደ አልጋዬ እመለስና እያተገላበጥኩ እንቅልፍ እስኪያሸንፈኝ እሰቃያለው፡፡ከሰዓታት በኃላ እንደምንም እንቅልፍ ያሸንፈኛል፡፡ሊነጋጋ ሲል መለልሶ ይቀሰቅሰኛል፡፡የዚህኛውን ጊዜ እንኳን ፊት አልሰጠውም …ከነ ተረቱ ‹ የጥዋት ቁ› ይባል የለ …ሽንት እንዲወጠር እድርጎት ይሆን ትክክለኛ አምሮት ይሁን መለየት አይቻልም…ሀሰተኛ መሲ ነገር ነው፡፡
ይሄ ነገር እየተደጋገመ ሲያስቸግረኝ ህልሜን ሁሉ የከተማዋ ቆነጃጅቶች እና በአካልም በምናብም የማውቃቸው ሴቶች ሲሞሉት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ወሰንኩ…፡፡ በእኔ ምክር ሳይሆን በተፈጥሮ ህግ የሚመራውን ቅንዝሬን የሆነ ዘዴ ፈጥሬ ማቀዝቀዝ አለብኝ..ስለዚህ ግዢ ልወጣ ወሰንኩ፡፡
ሰፈሩን ባልነግራችሁም …ለግዢ ምቹ ናቸው ሲባሉ ከሰማዋቸው የከተማዋ ጉድ ሰፈሮች መካከል ወደ አንዱ ነው የሄድኩት…ቺቺኒያ አይተንሀል አላችሁኝ…..?ምን አልባት እኔን የመሰለ ሰው አይታችሁ ይሆናል እንጂ እኔ ወደ እዛ ሰፈር ዝር አላልኩም…ደግሞስ እናንተ ራሳችሁ እዛ ሰፈር ምን ስትሰሩ ነበር? ለማንኛውም ያልኳችሁ ቦታ ሄድኩ …ቀድሜ አልጋ ተከራየው….
ከዛ ወደ ቡና ቤቶቹ ወይም ወደ ጭፈራ ቤቶቹ አልነበረም ጎራ ያልኩት፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ወደ ጎዳናው ነው የወጣሁት…፡፡ከቤት ውስጥ ግዢ የውጩን ለምን እንደመረጥኩ አልገባኝም…. ብቻ ስሜቴ ወደ እዛ ነው የገፋኝ ፡፡ዞሬ ለመምረጥ… መርጬ ለማነጋገር እና ለመስማማት..ተስማምቶም ይዞ ለመሄድ ..አንድ ሰዓት ገደማ ፈጀብኝ፡፡
ልጅቷ የተከራየሁት ቤርጎ ገብታ አልጋው ጠርዝ ላይ እንደተቀመጠች ፊቷን ለማንበብ ሞከርኩ..፡፡ፊቷ ሜካፕ የነከካው ቢሆንም በስርዓቱ አልተዳረሰም… የሆነ መዝረክረክ ይታይበታል፡፡ከቀይ ዳማ መልክ ወደ ግራጫ የተቀየረ የፊት ቀለም ይታየኛል..፡፡የዓይኖቾ ቅንድቦች ቀና ማለት ደክሟቸው መሰለኝ ተደፍተዋል፡፡ጉንጮቾ ወደ ውስጥ ስርጉድ ብለው በረሀ ላይ ውሃ እንዲወጣባቸው የተቆፈሩ ጉድጓዶች ነው የሚመስሉት ...፡፡ከንፈሮቾ ቁርፍድፍድ ብለው የመሰነጣጠቅ ምልክት ይታይባቸዋል፡፡ግን በተቀባችው ቀይ ሊፒስቲክ ልትሸፍነው ሞክራለች፡፡ውጭ ከመብራቱ ፖል አቅራቢያ ከሚገኝ ግንብ አጥር ጋር ተጣብቃ ግማሽ ብርሀን እና ግማሽ ጨለማ ከቧት ሳነጋግራት ይሄ ሁሉ አሁን የዘረዘርኩላችሁን የመልኳ ሁኔታ አልተገለፀልኝ ነበር.፡፡አቋሟን እና የፊቷን ቅርጽ በከፊል ነበር የገመገምኩት….፡፡ገምግሜም አስፓልቱ ላይ ከተኰለኰሉት መሀከል እሷን የመረጥኳት…መርጬም ያነጋገርኳት …አነጋሬም የተሰመመማነው… ተስማምተን ወደ ተከራየውት ቤርጎ ይዤት የገባሁት፡፡
አሁን ..ከገባችና በመጠኑም ፈንጠር ብላ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ ሳስተውላት ግን አሁን ከላይ እንደዘረዘርኩላችሁ የተለየች ሆና ነው ያገኘኋት፡፡ ገና ያልበሰለች የ16 ዓመት አካባቢ ጨቅላ ወጣት ነች ፡፡ቢሆንም ውስጧ የ60 ዓመት …የጎበጠች እና የጨረጨሰች አሮጊት በእሷነቷ ውስጥ ተደብቃ ትታያለች፡፡ ወጣትነቷ በፍጥነት ወደ መጠውለግ ሲንደረደር ይታያል፡፡
‹‹ተጫወቺ እንጂ …ምነው ከእኔ ጋር ማደሩ ደስ አላለሽም እንዴ? ››አልኳት፡፡
ፊቷን እንዳጨማደደች አላስፈላጊ ጥያቄ እንደጠየቀ ሰው በግርምት እያየችኝ
‹‹መደሰት እና አለመደሰት እዚህ ጋር ምን አመጣው›ስትል መለሰችልኝ፡፡
‹‹አልገባኝም››
‹‹እንዴት አይገባህም..እኔ ገንዘብህን ነው የምፈልገው፡፡ ከፍለኸኛል….ከከፈልከኝ ደግሞ ደስ አለኝም አላለኝም አብሬህ ማደር ግዴታዬ ነው››አለችኝ እና ልብሶቾን ማወላለቅ ጀመረች፡፡
እኔም አወላለቅኩና ተከተልኳት..ተያይዘን አንድ አንሶላና ፍራሽ ከስር..አንድ አንሶላና ብርድ ልብስ ከላይ አድርገን ከመሀከል ገባን…፡፡
‹‹እዛ ባዶ ቤት ብቻውን በነበረበት ሰዓት ዘራፍ እያለ እረፍት ይነሳኝ የነበረው አጅሬን‹‹ አሁን እስቲ ጉዱህን እየዋለው….ሜዳውም ፈረሱንም ያው አመቻችቼለታለው… ›› አልኩት.፡፡
ግን ለእኔም ሆነ ለአጅሬው እንደአሰብነውና እደጓጓነው የሆነልን አይመስለኝም ….የሆነ ደስ የማይል ስሜት እየተሰማኝ ነው…እሱም አንዴ ቀጥ ከዛ መልሶ እንደመልፈስፈስ እያለ ፈራ ተባ ውስጥ ገብቷል፡፡ወደ እሷ ፊቴን አዞርኩና እጄን ትከሻዋ ላይ ጣል አደረግኩ..ስጠጋት ከሰውነቷ የሚረጨው ጠረን ተምዘግዝጎ ወደ አፍንጫዬ ሲገባ ደስ የማይል ስሜት ነው የተሰማኝ..እርግጥ ከለበሰችው ልብስ አልፎ ሰውነቷ ላይ የቀረ የሽቶ ሽታ አለ ..፡፡ግን ከሽቶው ተደባልቆ ና ተዋህዶ የሚበተን ሌላ ጠረን አለ..ምንነቱን ልለየው ያልቻልኩት ትንሽ የሚረብሽ ጠረን….፡፡
እንደዛም ሆኖ በደንብ ተጠጋኋት ..ሰውነቴን ከሰውነቷ አጣበቅኩ…እዳብሳት እና አሻሻት ጀመርኩ፡፡..ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጋለ እየሞቀ ቢመጣም ከእሷ ወደ እኔ እየተላለፈ ያለ ምንም አይነት ሙቀት ሊሰማኝ አልቻለም…. አሁንም በረዶ እንደሆነችና ሰውነቷ ከፍሪጅ እደወጣ ስጋ እንደደረ ነው፡፡ማሻሸቴ ቀጥሎ ጡቶቾ ጋር ደረሰ ....ጨመቅ ለቀቅ.. ጨመቅ ለቀቅ ሳደርግ አስደንጋጭ ፈሳሽ ከጡቶቾ ፊን ብሎ ደረቴ ላይ ተረጨ..ደነገጥኩ ፡፡
በደነገጥኩበት ፍጥነት አሷም ይበልጥ በመበሳጨት ጮኸችብኝ፡፡
‹‹በናትህ ዝም ብለህ ማሻሻቱን ጥለህ ..ማድረግ አትችልም ?››
‹‹ምድነው ከጡትሽ የወጣው?››
‹‹ምን እንዲወጣ ትፈልጋለህ… ነዳጅ…››.በማሾፍ መለሰችልኝ፡፡
‹‹እሱማ ወተት ነው…ግን እንዴት...?እንዲህ ይሆናል እንዴ?››
‹‹እመጫት ስለሆንኩ እና ስለማጠባ ነው››ግዴለሽ እና ስሜት አልባ በሆነ ስሜት መለሰችልኝ፡፡
‹‹ማ….? አንቺ?››
‹‹አዎ …የሁለት ወር አራስ ልጅ ቤት ጥዬ ነው የመጣሁት››
በድንጋጤ ከመኝታዬ ተስፈንጥሬ በመነሳት ቁጭ አልኩ
‹‹ አቤት ጭካኔ ..የሁለት ወር አራስ ቤት አስተኝቶ ለሽርሙጥና መሰማራት ሀጥያት ብቻ ስይሆን ወንጀልም ነው..ምን አይነጠቷ አውሬ ነሽ በእግዚያብሄር…!!!!››አልኳት፡፡
ተንፈቅፍቃ የሹፈት ሳቅ ሳቀችብኝ‹‹ሀጥያት አልክ ..?ማነው እኔን ወንጀለኛ እና ሀጥያተኛ ነሽ ብሎ ሊፈርድብኝ የሞራል ብቃት ያለው..?ያሳደገኝ ማበረሰብ…? ሚያስተዳድረኝ መንግስት …?ቄሱ..?ፓስተሩ…? አንተ ..
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//////
የእኔ ቅንዝርነት የልጅቷ ድህነት፤እናትነት እና ተስፋ ቢስነት
ስሟ ግን ማን ነበር?
ምን አይነት ችግር ላይ እንዳለሁ ልትገምቱ አትችሉም፡፡ ሀገር አማን ነው ብዬ በእንቅልፍ ዓለም ከተዋጥኩ በኋላ በእኩለ ለሊት ላይ ለመንገድ መብራት ማቆሚያ እደተተከለ የእንጨት ምሰሶ ቀጥ ይላል፡፡ ቀጥ ማለቱ ብቻ አይደለም እኮ የሚያበሳጨኝ ቀጥ በማለቱ ውስጥ ጥዝጣዜ ነገር አለው፡፡ የመነዝነዝ ዓይነት እና ለመግለፅ የሚያስቸግር ግራ አጋቢ ህመም ከእቅልፍ እስከማባበነን ድረስ የሚደርስ ኃይል ያለው ህመም ፡፡እስከአሁን ስለምን እንደማወራችሁ አልገባችሁም አይደል?
እንጠራራ እና ከእንቅልፌ ጋር እየታገልኩ ዓይኔን እያሻሸው በዳበሳ ወደ ሽንት ቤት ሄዳለው… ምን አልባት ሽንቴ ወጥሮኝ እንደሆነ ብዬ…ግን ብጨምቀው ባልበው ጠብ አይለኝም ፡፡
በንጭንጭ ወደ አልጋዬ እመለስና እያተገላበጥኩ እንቅልፍ እስኪያሸንፈኝ እሰቃያለው፡፡ከሰዓታት በኃላ እንደምንም እንቅልፍ ያሸንፈኛል፡፡ሊነጋጋ ሲል መለልሶ ይቀሰቅሰኛል፡፡የዚህኛውን ጊዜ እንኳን ፊት አልሰጠውም …ከነ ተረቱ ‹ የጥዋት ቁ› ይባል የለ …ሽንት እንዲወጠር እድርጎት ይሆን ትክክለኛ አምሮት ይሁን መለየት አይቻልም…ሀሰተኛ መሲ ነገር ነው፡፡
ይሄ ነገር እየተደጋገመ ሲያስቸግረኝ ህልሜን ሁሉ የከተማዋ ቆነጃጅቶች እና በአካልም በምናብም የማውቃቸው ሴቶች ሲሞሉት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ወሰንኩ…፡፡ በእኔ ምክር ሳይሆን በተፈጥሮ ህግ የሚመራውን ቅንዝሬን የሆነ ዘዴ ፈጥሬ ማቀዝቀዝ አለብኝ..ስለዚህ ግዢ ልወጣ ወሰንኩ፡፡
ሰፈሩን ባልነግራችሁም …ለግዢ ምቹ ናቸው ሲባሉ ከሰማዋቸው የከተማዋ ጉድ ሰፈሮች መካከል ወደ አንዱ ነው የሄድኩት…ቺቺኒያ አይተንሀል አላችሁኝ…..?ምን አልባት እኔን የመሰለ ሰው አይታችሁ ይሆናል እንጂ እኔ ወደ እዛ ሰፈር ዝር አላልኩም…ደግሞስ እናንተ ራሳችሁ እዛ ሰፈር ምን ስትሰሩ ነበር? ለማንኛውም ያልኳችሁ ቦታ ሄድኩ …ቀድሜ አልጋ ተከራየው….
ከዛ ወደ ቡና ቤቶቹ ወይም ወደ ጭፈራ ቤቶቹ አልነበረም ጎራ ያልኩት፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ወደ ጎዳናው ነው የወጣሁት…፡፡ከቤት ውስጥ ግዢ የውጩን ለምን እንደመረጥኩ አልገባኝም…. ብቻ ስሜቴ ወደ እዛ ነው የገፋኝ ፡፡ዞሬ ለመምረጥ… መርጬ ለማነጋገር እና ለመስማማት..ተስማምቶም ይዞ ለመሄድ ..አንድ ሰዓት ገደማ ፈጀብኝ፡፡
ልጅቷ የተከራየሁት ቤርጎ ገብታ አልጋው ጠርዝ ላይ እንደተቀመጠች ፊቷን ለማንበብ ሞከርኩ..፡፡ፊቷ ሜካፕ የነከካው ቢሆንም በስርዓቱ አልተዳረሰም… የሆነ መዝረክረክ ይታይበታል፡፡ከቀይ ዳማ መልክ ወደ ግራጫ የተቀየረ የፊት ቀለም ይታየኛል..፡፡የዓይኖቾ ቅንድቦች ቀና ማለት ደክሟቸው መሰለኝ ተደፍተዋል፡፡ጉንጮቾ ወደ ውስጥ ስርጉድ ብለው በረሀ ላይ ውሃ እንዲወጣባቸው የተቆፈሩ ጉድጓዶች ነው የሚመስሉት ...፡፡ከንፈሮቾ ቁርፍድፍድ ብለው የመሰነጣጠቅ ምልክት ይታይባቸዋል፡፡ግን በተቀባችው ቀይ ሊፒስቲክ ልትሸፍነው ሞክራለች፡፡ውጭ ከመብራቱ ፖል አቅራቢያ ከሚገኝ ግንብ አጥር ጋር ተጣብቃ ግማሽ ብርሀን እና ግማሽ ጨለማ ከቧት ሳነጋግራት ይሄ ሁሉ አሁን የዘረዘርኩላችሁን የመልኳ ሁኔታ አልተገለፀልኝ ነበር.፡፡አቋሟን እና የፊቷን ቅርጽ በከፊል ነበር የገመገምኩት….፡፡ገምግሜም አስፓልቱ ላይ ከተኰለኰሉት መሀከል እሷን የመረጥኳት…መርጬም ያነጋገርኳት …አነጋሬም የተሰመመማነው… ተስማምተን ወደ ተከራየውት ቤርጎ ይዤት የገባሁት፡፡
አሁን ..ከገባችና በመጠኑም ፈንጠር ብላ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ ሳስተውላት ግን አሁን ከላይ እንደዘረዘርኩላችሁ የተለየች ሆና ነው ያገኘኋት፡፡ ገና ያልበሰለች የ16 ዓመት አካባቢ ጨቅላ ወጣት ነች ፡፡ቢሆንም ውስጧ የ60 ዓመት …የጎበጠች እና የጨረጨሰች አሮጊት በእሷነቷ ውስጥ ተደብቃ ትታያለች፡፡ ወጣትነቷ በፍጥነት ወደ መጠውለግ ሲንደረደር ይታያል፡፡
‹‹ተጫወቺ እንጂ …ምነው ከእኔ ጋር ማደሩ ደስ አላለሽም እንዴ? ››አልኳት፡፡
ፊቷን እንዳጨማደደች አላስፈላጊ ጥያቄ እንደጠየቀ ሰው በግርምት እያየችኝ
‹‹መደሰት እና አለመደሰት እዚህ ጋር ምን አመጣው›ስትል መለሰችልኝ፡፡
‹‹አልገባኝም››
‹‹እንዴት አይገባህም..እኔ ገንዘብህን ነው የምፈልገው፡፡ ከፍለኸኛል….ከከፈልከኝ ደግሞ ደስ አለኝም አላለኝም አብሬህ ማደር ግዴታዬ ነው››አለችኝ እና ልብሶቾን ማወላለቅ ጀመረች፡፡
እኔም አወላለቅኩና ተከተልኳት..ተያይዘን አንድ አንሶላና ፍራሽ ከስር..አንድ አንሶላና ብርድ ልብስ ከላይ አድርገን ከመሀከል ገባን…፡፡
‹‹እዛ ባዶ ቤት ብቻውን በነበረበት ሰዓት ዘራፍ እያለ እረፍት ይነሳኝ የነበረው አጅሬን‹‹ አሁን እስቲ ጉዱህን እየዋለው….ሜዳውም ፈረሱንም ያው አመቻችቼለታለው… ›› አልኩት.፡፡
ግን ለእኔም ሆነ ለአጅሬው እንደአሰብነውና እደጓጓነው የሆነልን አይመስለኝም ….የሆነ ደስ የማይል ስሜት እየተሰማኝ ነው…እሱም አንዴ ቀጥ ከዛ መልሶ እንደመልፈስፈስ እያለ ፈራ ተባ ውስጥ ገብቷል፡፡ወደ እሷ ፊቴን አዞርኩና እጄን ትከሻዋ ላይ ጣል አደረግኩ..ስጠጋት ከሰውነቷ የሚረጨው ጠረን ተምዘግዝጎ ወደ አፍንጫዬ ሲገባ ደስ የማይል ስሜት ነው የተሰማኝ..እርግጥ ከለበሰችው ልብስ አልፎ ሰውነቷ ላይ የቀረ የሽቶ ሽታ አለ ..፡፡ግን ከሽቶው ተደባልቆ ና ተዋህዶ የሚበተን ሌላ ጠረን አለ..ምንነቱን ልለየው ያልቻልኩት ትንሽ የሚረብሽ ጠረን….፡፡
እንደዛም ሆኖ በደንብ ተጠጋኋት ..ሰውነቴን ከሰውነቷ አጣበቅኩ…እዳብሳት እና አሻሻት ጀመርኩ፡፡..ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጋለ እየሞቀ ቢመጣም ከእሷ ወደ እኔ እየተላለፈ ያለ ምንም አይነት ሙቀት ሊሰማኝ አልቻለም…. አሁንም በረዶ እንደሆነችና ሰውነቷ ከፍሪጅ እደወጣ ስጋ እንደደረ ነው፡፡ማሻሸቴ ቀጥሎ ጡቶቾ ጋር ደረሰ ....ጨመቅ ለቀቅ.. ጨመቅ ለቀቅ ሳደርግ አስደንጋጭ ፈሳሽ ከጡቶቾ ፊን ብሎ ደረቴ ላይ ተረጨ..ደነገጥኩ ፡፡
በደነገጥኩበት ፍጥነት አሷም ይበልጥ በመበሳጨት ጮኸችብኝ፡፡
‹‹በናትህ ዝም ብለህ ማሻሻቱን ጥለህ ..ማድረግ አትችልም ?››
‹‹ምድነው ከጡትሽ የወጣው?››
‹‹ምን እንዲወጣ ትፈልጋለህ… ነዳጅ…››.በማሾፍ መለሰችልኝ፡፡
‹‹እሱማ ወተት ነው…ግን እንዴት...?እንዲህ ይሆናል እንዴ?››
‹‹እመጫት ስለሆንኩ እና ስለማጠባ ነው››ግዴለሽ እና ስሜት አልባ በሆነ ስሜት መለሰችልኝ፡፡
‹‹ማ….? አንቺ?››
‹‹አዎ …የሁለት ወር አራስ ልጅ ቤት ጥዬ ነው የመጣሁት››
በድንጋጤ ከመኝታዬ ተስፈንጥሬ በመነሳት ቁጭ አልኩ
‹‹ አቤት ጭካኔ ..የሁለት ወር አራስ ቤት አስተኝቶ ለሽርሙጥና መሰማራት ሀጥያት ብቻ ስይሆን ወንጀልም ነው..ምን አይነጠቷ አውሬ ነሽ በእግዚያብሄር…!!!!››አልኳት፡፡
ተንፈቅፍቃ የሹፈት ሳቅ ሳቀችብኝ‹‹ሀጥያት አልክ ..?ማነው እኔን ወንጀለኛ እና ሀጥያተኛ ነሽ ብሎ ሊፈርድብኝ የሞራል ብቃት ያለው..?ያሳደገኝ ማበረሰብ…? ሚያስተዳድረኝ መንግስት …?ቄሱ..?ፓስተሩ…? አንተ ..
❤45😢3🥰1