#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ከአዲስ አበባ ፍልውሃ በታች ከማህተማ ጋንዲ መንገድ መስመር ከብሔራዊ ስታዲዬም ብዙም ሳይርቅ ከግዮን
ከኢትዮጵያ ከሒልተን
ሆቴል... ለሚመጡ እንግዶች አመች የሆነው የ“ጎጆ” ምግብ ቤት ግቢው በመኪና ተጣቧል።
ቢኤም ደብሊው መኪና በዘበኛው መሪነት ቦታዋን ይዛ እንደቆመች ሁለቱ እንግሊዛውያን ወደ ምግብ ቤቱ አመሩ። እሷ ቀደም እሱ ደግሞ ከኋላዋ ተከትሏት ሲገባ እንደ ቀልድ ቁመናዋን አስተዋለ: ፀጉሯ አጠር ከማለቱ ሌላ ስትሄድ የሚደንሰው ዳሌዋ አለ
'' የለም' »አስኝቶ የሚያወራርደው ወገቧ
ያው ነው።ስትጠመጠም እንደ ላስቲክ እየተሳሳበ በሰራ አካላቱ የሚስለከለከው አካሏ ለውጥ የለውም። ልክ እንደ ዛሬ ሁለት ዓመት ከስድስት ወሩ ነው ጥቁር ቲሽርት እንደ ወትሮው ሁሉ ጂንስ ሱሪ ለባብሳለች።ወገቧና አንገቷ ልብሷ አልደረሰበትም:
የሴት እምብርት ሲያይ ጎሮሮውን እንዳነቁት ሁሉ አይኑ የሚፈጠው ስቲቭ አጎጠጎጤ ጡቷን ደረቱ ላይ አስደግፋ ለጠጥ ብላ
ሽቅብ ተስባ ስትስመው እንደ ህፃን ልጅ በእቅፉ አልሞላ ስትለው እቅፉን ጠበቅ አድርጎ እንደ ቄጤማ አካሉ ላይ የለጠፉት ትዝ
አለው።
ገባ ብለው ክፍት ቦታ ሲያማትሩ አስተናጋጁ በስተግራ በኩል ግድግዳው ጥግ ባዶ ቦታ አሳያቸው።
የሲሊን ዲዮን ዜማ በለሆስታ ይሰማል ካርለት ድምፀ መረዋ ካናዳዊት አቀንቃኝ ስሊን ዲዮን ኒወርክ “ብራንድ ዌይ
ዳንሰሮች ጋር አይኖቿዋን እያስለመለመች, እግሮችዋን መሬት
ለመሬት እየሳበች ወለሉ ላይ እየተኛች...በለበሰችው ጃፖኒ እርቃን የሆነውን ትከሻዋን እየላሰች ስትዘፍን ስላየቻት ይበልጥ ወዳታለች::
እና! ገና "ከመግባታቸው በፊት የምትወደውን ዜማ ስትሰማ የደስታ ስሜት ተሰምቷታል።
አስተናጋጁ የምግብ ዝርዝር ይዞላቸው መጣ: ሁለቱም
ዝርዝሩን ተቀበሉና በፀጥታ አንብበው ካዘዙ በኋላ ጨዋታቸውን ሊጀምሩ ሲሉ
“የሚጠጣስ?” አይኖቹን ግራና ቀኝ እያዟዟረ ጠየቀ
አስተናጋጁ።
“ማርቲኒ” አለችው ካርለት
“ነጭ ወይንስ ቀይ ማርቲኒ” የሾለ ፊቱን ወደ ፊት አስግጎ ጠየቃት።
ነጭ ይሁንልኝ አለችው። አስተናጋጁ ለጨዋታ
መጣደፋቸውን ተረድቶ ይቅርታ በሚጠይቅ አስተያየት ስቲቭን
እያየ አገጩን ሽቅብ ሰበቀ።
“ብሳክ ሌብል” አለው።
ካርለት ቦርሳዋን ወንበሩ ላይ አንጠልጥላ ፈገግ እያለች።
“እሺ ስቲቭ! ስትለው ስቲቭም ወንበሩ ላይ ጠረዼዛው እያስጠጋ ፈገግ ብሎ አንገቱን ወዘወዘ ደህና ነኝ ለማለት።
“…ኢንግላንድ መልም ጊዜ አሳለፍሽ?
“ከናቴ ከጓደኞቺ ጋር በመገናኘቴ ደስ ብሎኛል። ብዙዎቹ ጓደኞቼ ግን ደስተኞች አይደሉም:: ሁሉም ያለሙትን ህይወት
መኖር የቻሉ አልመሰለኝም። ከጎይቲና ከከሎ ጋር ያሳለፍኩት ጊዜም ባመዛኙ እንግዳ ለሆነባቸው ስልጣኔ እያንዳንዷ እንደ ህፃን
ልጅ ማስረዳቱ አድካሚ ቢሆንም ወድጄዋለሁ:
“ጥናቴን በተመለከተ ማንቸስተር ያቀረብሁት ዝግጅት ለአማሪዬና ስብሰባ ተሳታፊዎቼ ጥሩ ስሜት የፈጠረ በመሆኑ ደስ ብሉኛል። ከዚህ ተጨማሪ ከማንቸስተር ዩንቨርስቲ አዳራሽ ስንወጣ ብዛት ያላቸው የ" ጋርዲያን የሄራልድ ትሪቡን…
ጋዜጠኞች ለኔ ለጎይቲና ለከሎ ያቀረቡልን ጥያቄ የሰጠነው መልስ በቤቱ ውስጥ የነበረው የመግባባትና የማድነቅ እንድምታ ስቃይን እሚያስረሳ ነበር። “በተለይም ሴቶችን አስገድዶ መድፈርና
የወሲብ ብዝበዛ በሐመር ምድር የተወገዘና የማይፈፀም ፀያፍ ጉዳይ
መሆኑን ላስረዳቸውና ጎይቲ “ሴትን ያለፍቃዷ ማን ያስቸግራታል ደሞ." ያለችው ስሜታዊ አባባል ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ውስጥ
ዋናው ነበር።
“በተረፈ ለአንድ ሳምንት ስፔን ለአንድ ሳምንት ደግሞ
ደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ሄጄ ነበር: እንደ ማይክል ጃክሰን በዚች ፕላኔት ካለው ወፈ ሰማያት ህዝብ መሀከል የማደንቀው ሁለት ሰው ነው:: ማንዴላንና ማር ትሬዛን ብዬ ባልደመድምም በደረጃ ከማይክል አስተያየት የማላርቀውን ማንዴላንና የሱን አመራር
በቅርብ ለማየት እድል ለማግኘቴ የተደሰተሁ ሲሆን በጆሀንስበርግ ሰሜን ማዕክል ብራምፎንቴን በሚገኘው ዊትስ ዩንቨርስቲ የአባቴ ስራዎች በመታሰቢያነት ሲቀርቡ ንግግር ማድረግ መቻሌሞ ጥሩ አባት ሞቶም የደስታ ምንጭ እንደሚሆን ለማመን ችያለሁ።
የነፃነት ረጅም ጉዞ በሚል
ርዕስ በ1994 ዓ.ም
በማክዶናልድ አሳታሚ ኩባንያ በኔልስን ማንዴላ የታተመው የ ባለ 617 ገጽ መጽሐፍም በመርፌ ቀዳዳ የሚታይን ብርሃን ተከትሎ
ከፀሐይ አካል መድረስ መቻሉን የተማርኩበት ነበረ።
“የፍቅር ህይወቴን በተመለከተ ግን እግሮቼ ሁለት መሰላል ላይ ናቸው:: ባል የማግቢያዬ ልጅ የመውለጃዬ ጊዜ እያለፈ
መሆኑን ሳስብ አንጀቴ በሃዘን መኮራመቱ ባይቀርም የሰለጠነው
ዓለም ለፍቅር ቀረቤታ ያለው አነስተኛ ግምት የመመዘኛ ዝባንዝንኬው በተፈጥሮው ዓለም ደግሞ ህይወቱን ላልኖረው ሰው
ያለው አስቸጋሪነትና የፍቅር አለመጣጣም... ለጊዜው መምረጥ ከሚያስቸግር ሁኔታ ላይ እንደጣለኝ ነው የምረዳው።
“እዚህ ላይ ግን ልገልፅልህ የምወደው እንደማንኛውም
ሰው መጭው ህይወቴ ምን መምሰል እንዳለበት ሳስብ ብዥ ብዥ እያለ የሚታየኝ ህልም አስጨናቂና አሳሳቢ ቢሆንም ከምንም በላይ
የምፈልገው በአባቴ የሰው ልጅ ሕይወት ምርምር ጎዳና መጓዝንና ለሙያዬ መሉ መስዋዕትን መክፈል ስለሆነ መፅናኛዬ ሚዛኍን
የደፋ ነው፡፡ ስለዚህ ደስተኛነቴ አሁንም ከቁጥጥሬ አልወጣም ብላ
ፈገግ አለች::
ስቲቭ ሃሣቧን ያዝኩት ሲል ወዲያ ስታላጋው ወዲህ
ስታጋጨወ ቆይታ እንደ ጥሩ ተውኔት ጨዋታውን ባላሰበው መንገድ ደመደመችበት።
ለጥቂት ጊዜ ሁለቱም በየግል ሃሣባቸው ተውጠው እንደቆዩ ፈጣኗ ካርለት ከነበረችበት የሃሣብ ግልቢያ ድንገት ልጓሟን ስባ የስቲቭን ቀኝ እጅ በቀኝ እጅዋ ቀስ ብላ ጫን አድርጋ
ሳታስደነግጠው ሳታሽብረው ሃሣቡን ሳታምታታበት ትክ ብላ
መረጋጋቱን ካስተዋለች በኋላ፡-
“ስቲቭ! አንተስ ከተለያዬን በኋላ ጥሩ ጊዜ አሳሰፍክ?"
አለችው።
ዘናና ፈገግ ብሎ “በስራዪ ብዙም ውጥረት አልነበረኝም የዲፕሎማት ትልቁ ሥራ ግንኙነት መፍጠር፤ የአገሪቱን
ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አዝማሚያ መከታተል፤ ተስፋን መመገብ ገደብ አልባ የሆነ ቃል ኪዳን መግባት በመሆኑ በፈቀደልኝ የጉዞ ፍጥነት እያሽከረከርኩ ስራዬን ለመወጣት ሞክሬያለሁ፡ የኢትዮጵያ ኑሮ ግን ከብዶኛል" አላት
እንዴት? የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ!" አለችው ውስጡን
ጠልቃ ለመመልከት አይኖቹን እየፈለገች።
ካርለት የሰዎችን አይን በማየት ስለ ሁኔታዎች ምንነት ለማወቅ እንደሚቻል በስነ ልቦናዊ ትምህርቷ ታውቃለች። አንድ ሰው ያስጨነቀው ነገር ትዝታውን• ፍቅሩን ጥላቻውን... ሲገልፅ
የአይኖቹ ኳሶች የት እንደሚሆኑ ወዴት እንደሚዞሩ ከስነ አዕምሮ
ባለሙያዋ እናቷ ተምራለች። ሌላው ቀርቶ እውነትና ውሸት አባባልን የአይንን እንቅስቃሴ አይታ በከፊል መግለጽ ትችላለች።
ከዚህ በተጨማሪም የአንድ ሰው አመለካከቱ በመስማት ወይንም በማየት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ከአገላለፁ በመረዳት አይኑና ሃሣቡ ከሚሰጣት ግንዛቤ ግንኙነቷን ለመመዘንና ለመለካት
አትቸገርም። ለዚህም ካርለት ስቲቭ ሲያወራት አይኖቹን ትፈልግ ነበር: ኋላ ግን አይኑን በአይኗ ያዘችው እንቅስቃሴዋንም
አስተከለችና፡-
"...የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ? አለችው ደግማ ስቲቭ
በአፍንጫው ጫን አድርጎ ተነፈሰና፡-
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ከአዲስ አበባ ፍልውሃ በታች ከማህተማ ጋንዲ መንገድ መስመር ከብሔራዊ ስታዲዬም ብዙም ሳይርቅ ከግዮን
ከኢትዮጵያ ከሒልተን
ሆቴል... ለሚመጡ እንግዶች አመች የሆነው የ“ጎጆ” ምግብ ቤት ግቢው በመኪና ተጣቧል።
ቢኤም ደብሊው መኪና በዘበኛው መሪነት ቦታዋን ይዛ እንደቆመች ሁለቱ እንግሊዛውያን ወደ ምግብ ቤቱ አመሩ። እሷ ቀደም እሱ ደግሞ ከኋላዋ ተከትሏት ሲገባ እንደ ቀልድ ቁመናዋን አስተዋለ: ፀጉሯ አጠር ከማለቱ ሌላ ስትሄድ የሚደንሰው ዳሌዋ አለ
'' የለም' »አስኝቶ የሚያወራርደው ወገቧ
ያው ነው።ስትጠመጠም እንደ ላስቲክ እየተሳሳበ በሰራ አካላቱ የሚስለከለከው አካሏ ለውጥ የለውም። ልክ እንደ ዛሬ ሁለት ዓመት ከስድስት ወሩ ነው ጥቁር ቲሽርት እንደ ወትሮው ሁሉ ጂንስ ሱሪ ለባብሳለች።ወገቧና አንገቷ ልብሷ አልደረሰበትም:
የሴት እምብርት ሲያይ ጎሮሮውን እንዳነቁት ሁሉ አይኑ የሚፈጠው ስቲቭ አጎጠጎጤ ጡቷን ደረቱ ላይ አስደግፋ ለጠጥ ብላ
ሽቅብ ተስባ ስትስመው እንደ ህፃን ልጅ በእቅፉ አልሞላ ስትለው እቅፉን ጠበቅ አድርጎ እንደ ቄጤማ አካሉ ላይ የለጠፉት ትዝ
አለው።
ገባ ብለው ክፍት ቦታ ሲያማትሩ አስተናጋጁ በስተግራ በኩል ግድግዳው ጥግ ባዶ ቦታ አሳያቸው።
የሲሊን ዲዮን ዜማ በለሆስታ ይሰማል ካርለት ድምፀ መረዋ ካናዳዊት አቀንቃኝ ስሊን ዲዮን ኒወርክ “ብራንድ ዌይ
ዳንሰሮች ጋር አይኖቿዋን እያስለመለመች, እግሮችዋን መሬት
ለመሬት እየሳበች ወለሉ ላይ እየተኛች...በለበሰችው ጃፖኒ እርቃን የሆነውን ትከሻዋን እየላሰች ስትዘፍን ስላየቻት ይበልጥ ወዳታለች::
እና! ገና "ከመግባታቸው በፊት የምትወደውን ዜማ ስትሰማ የደስታ ስሜት ተሰምቷታል።
አስተናጋጁ የምግብ ዝርዝር ይዞላቸው መጣ: ሁለቱም
ዝርዝሩን ተቀበሉና በፀጥታ አንብበው ካዘዙ በኋላ ጨዋታቸውን ሊጀምሩ ሲሉ
“የሚጠጣስ?” አይኖቹን ግራና ቀኝ እያዟዟረ ጠየቀ
አስተናጋጁ።
“ማርቲኒ” አለችው ካርለት
“ነጭ ወይንስ ቀይ ማርቲኒ” የሾለ ፊቱን ወደ ፊት አስግጎ ጠየቃት።
ነጭ ይሁንልኝ አለችው። አስተናጋጁ ለጨዋታ
መጣደፋቸውን ተረድቶ ይቅርታ በሚጠይቅ አስተያየት ስቲቭን
እያየ አገጩን ሽቅብ ሰበቀ።
“ብሳክ ሌብል” አለው።
ካርለት ቦርሳዋን ወንበሩ ላይ አንጠልጥላ ፈገግ እያለች።
“እሺ ስቲቭ! ስትለው ስቲቭም ወንበሩ ላይ ጠረዼዛው እያስጠጋ ፈገግ ብሎ አንገቱን ወዘወዘ ደህና ነኝ ለማለት።
“…ኢንግላንድ መልም ጊዜ አሳለፍሽ?
“ከናቴ ከጓደኞቺ ጋር በመገናኘቴ ደስ ብሎኛል። ብዙዎቹ ጓደኞቼ ግን ደስተኞች አይደሉም:: ሁሉም ያለሙትን ህይወት
መኖር የቻሉ አልመሰለኝም። ከጎይቲና ከከሎ ጋር ያሳለፍኩት ጊዜም ባመዛኙ እንግዳ ለሆነባቸው ስልጣኔ እያንዳንዷ እንደ ህፃን
ልጅ ማስረዳቱ አድካሚ ቢሆንም ወድጄዋለሁ:
“ጥናቴን በተመለከተ ማንቸስተር ያቀረብሁት ዝግጅት ለአማሪዬና ስብሰባ ተሳታፊዎቼ ጥሩ ስሜት የፈጠረ በመሆኑ ደስ ብሉኛል። ከዚህ ተጨማሪ ከማንቸስተር ዩንቨርስቲ አዳራሽ ስንወጣ ብዛት ያላቸው የ" ጋርዲያን የሄራልድ ትሪቡን…
ጋዜጠኞች ለኔ ለጎይቲና ለከሎ ያቀረቡልን ጥያቄ የሰጠነው መልስ በቤቱ ውስጥ የነበረው የመግባባትና የማድነቅ እንድምታ ስቃይን እሚያስረሳ ነበር። “በተለይም ሴቶችን አስገድዶ መድፈርና
የወሲብ ብዝበዛ በሐመር ምድር የተወገዘና የማይፈፀም ፀያፍ ጉዳይ
መሆኑን ላስረዳቸውና ጎይቲ “ሴትን ያለፍቃዷ ማን ያስቸግራታል ደሞ." ያለችው ስሜታዊ አባባል ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ውስጥ
ዋናው ነበር።
“በተረፈ ለአንድ ሳምንት ስፔን ለአንድ ሳምንት ደግሞ
ደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ሄጄ ነበር: እንደ ማይክል ጃክሰን በዚች ፕላኔት ካለው ወፈ ሰማያት ህዝብ መሀከል የማደንቀው ሁለት ሰው ነው:: ማንዴላንና ማር ትሬዛን ብዬ ባልደመድምም በደረጃ ከማይክል አስተያየት የማላርቀውን ማንዴላንና የሱን አመራር
በቅርብ ለማየት እድል ለማግኘቴ የተደሰተሁ ሲሆን በጆሀንስበርግ ሰሜን ማዕክል ብራምፎንቴን በሚገኘው ዊትስ ዩንቨርስቲ የአባቴ ስራዎች በመታሰቢያነት ሲቀርቡ ንግግር ማድረግ መቻሌሞ ጥሩ አባት ሞቶም የደስታ ምንጭ እንደሚሆን ለማመን ችያለሁ።
የነፃነት ረጅም ጉዞ በሚል
ርዕስ በ1994 ዓ.ም
በማክዶናልድ አሳታሚ ኩባንያ በኔልስን ማንዴላ የታተመው የ ባለ 617 ገጽ መጽሐፍም በመርፌ ቀዳዳ የሚታይን ብርሃን ተከትሎ
ከፀሐይ አካል መድረስ መቻሉን የተማርኩበት ነበረ።
“የፍቅር ህይወቴን በተመለከተ ግን እግሮቼ ሁለት መሰላል ላይ ናቸው:: ባል የማግቢያዬ ልጅ የመውለጃዬ ጊዜ እያለፈ
መሆኑን ሳስብ አንጀቴ በሃዘን መኮራመቱ ባይቀርም የሰለጠነው
ዓለም ለፍቅር ቀረቤታ ያለው አነስተኛ ግምት የመመዘኛ ዝባንዝንኬው በተፈጥሮው ዓለም ደግሞ ህይወቱን ላልኖረው ሰው
ያለው አስቸጋሪነትና የፍቅር አለመጣጣም... ለጊዜው መምረጥ ከሚያስቸግር ሁኔታ ላይ እንደጣለኝ ነው የምረዳው።
“እዚህ ላይ ግን ልገልፅልህ የምወደው እንደማንኛውም
ሰው መጭው ህይወቴ ምን መምሰል እንዳለበት ሳስብ ብዥ ብዥ እያለ የሚታየኝ ህልም አስጨናቂና አሳሳቢ ቢሆንም ከምንም በላይ
የምፈልገው በአባቴ የሰው ልጅ ሕይወት ምርምር ጎዳና መጓዝንና ለሙያዬ መሉ መስዋዕትን መክፈል ስለሆነ መፅናኛዬ ሚዛኍን
የደፋ ነው፡፡ ስለዚህ ደስተኛነቴ አሁንም ከቁጥጥሬ አልወጣም ብላ
ፈገግ አለች::
ስቲቭ ሃሣቧን ያዝኩት ሲል ወዲያ ስታላጋው ወዲህ
ስታጋጨወ ቆይታ እንደ ጥሩ ተውኔት ጨዋታውን ባላሰበው መንገድ ደመደመችበት።
ለጥቂት ጊዜ ሁለቱም በየግል ሃሣባቸው ተውጠው እንደቆዩ ፈጣኗ ካርለት ከነበረችበት የሃሣብ ግልቢያ ድንገት ልጓሟን ስባ የስቲቭን ቀኝ እጅ በቀኝ እጅዋ ቀስ ብላ ጫን አድርጋ
ሳታስደነግጠው ሳታሽብረው ሃሣቡን ሳታምታታበት ትክ ብላ
መረጋጋቱን ካስተዋለች በኋላ፡-
“ስቲቭ! አንተስ ከተለያዬን በኋላ ጥሩ ጊዜ አሳሰፍክ?"
አለችው።
ዘናና ፈገግ ብሎ “በስራዪ ብዙም ውጥረት አልነበረኝም የዲፕሎማት ትልቁ ሥራ ግንኙነት መፍጠር፤ የአገሪቱን
ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አዝማሚያ መከታተል፤ ተስፋን መመገብ ገደብ አልባ የሆነ ቃል ኪዳን መግባት በመሆኑ በፈቀደልኝ የጉዞ ፍጥነት እያሽከረከርኩ ስራዬን ለመወጣት ሞክሬያለሁ፡ የኢትዮጵያ ኑሮ ግን ከብዶኛል" አላት
እንዴት? የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ!" አለችው ውስጡን
ጠልቃ ለመመልከት አይኖቹን እየፈለገች።
ካርለት የሰዎችን አይን በማየት ስለ ሁኔታዎች ምንነት ለማወቅ እንደሚቻል በስነ ልቦናዊ ትምህርቷ ታውቃለች። አንድ ሰው ያስጨነቀው ነገር ትዝታውን• ፍቅሩን ጥላቻውን... ሲገልፅ
የአይኖቹ ኳሶች የት እንደሚሆኑ ወዴት እንደሚዞሩ ከስነ አዕምሮ
ባለሙያዋ እናቷ ተምራለች። ሌላው ቀርቶ እውነትና ውሸት አባባልን የአይንን እንቅስቃሴ አይታ በከፊል መግለጽ ትችላለች።
ከዚህ በተጨማሪም የአንድ ሰው አመለካከቱ በመስማት ወይንም በማየት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ከአገላለፁ በመረዳት አይኑና ሃሣቡ ከሚሰጣት ግንዛቤ ግንኙነቷን ለመመዘንና ለመለካት
አትቸገርም። ለዚህም ካርለት ስቲቭ ሲያወራት አይኖቹን ትፈልግ ነበር: ኋላ ግን አይኑን በአይኗ ያዘችው እንቅስቃሴዋንም
አስተከለችና፡-
"...የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ? አለችው ደግማ ስቲቭ
በአፍንጫው ጫን አድርጎ ተነፈሰና፡-
👍22
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
...በሙዚቃው ደነስኩ.. ውልቅልቅ እስክል ውስኪውን አንጠፍጥፌ ጠጣሁ"..አዎ አውቃኛለች... ፈፅሞ አልረሳችኝም...ከሁሉም ያስደሰተኝ ደግሞ ‹‹ቀናህ!!!›› የምትለዋ ቃል ነች...ምክንያቱም ቅናት እነጠቃለሁ ብሎ ከመፍራት ጋር ወይም ከመሠሠት ጋር ተያይዞ የሚመጣ ስሜት ነው።ፍርሀትም ስስትም ምንጫቸው ፍቅር ነው...እርግጠኝነት ከጎደለው ፍቅር።እና ታፈቅረኛለህ እያለችኝ ነው?ግን እንዳዛ ስላሰበች ለምንድነው እንደዚህ የፈነጠዝኩት? የእውነት እያፈቀርኳት ይሆን እንዴ ? እንዴ ከነጠላ ስሞ ሌላ ስለእሷ ምንም የማላውቃትን ሴት እንዴት ላፈቅራት እችላለሁ? ግን እኮ ፍቅር የኋላ ታሪክን አጥንቶ የወደፊት መድረሻን ገምቶ አሁን የቋሙበትን ድልዳል በሚዛን መዝኖ የሚገባበት የምክንያትና ውጤት ቁርኝት ማሳያ አይደለም..?ፍቅር ጨርቁን እንደጣለ ዕብድ ነገረ ስራው ቅፅበታዊና ተአምራዊ ነው።ስለዚህ ሳላቃትም በፍቅሯ ብወድቅ የሚደንቅ አይደለም!ግን ዕድሜዋ ጉዳይስ? ቢያንስ 10 አመት ትበልጠኛለች? እርግጥ በዕድሜ ሰላሳም ሀምሳም የምትበልጠውን እንስት ማፍቀር የተለመደ ነው?ቢሆንም ግን ቢገለበጥ ነበር የሚያምረው ..እኔ 10 አመት ብበልጣት።
ወየጉድ አሁንኮ ነገረ ስራዬን ላየ የመጀመሪያ የፍቅር አይነጥላዬን ገና እየገለጥኩ ያለው ጀማሪ አፍቃሪ ነው የምመስለው ፤ግን እኔ ቢያንስ አምስት አጫጭር ጣፍጭ ለወግ የሚበቁ እና አንድ ረጅም የተወሳሰበ ልቤንም ቅስሜንም አብሮ እንቅሽቅሽ አድርጎ የሠበረ.. በአለንጋ ተደጋግሞ በመገረፍ የተነሳ ትላልቅ ተጠላላፊ ሰንበር እንደተጋደመበት ጀርባ የእኔም ልብ በዛ ፍቅር ምክንያት ዙሪያ ጥምጥም የዞረበት ጠባሳ የተጋደመበት ሆኗል...
"ያ ፍቅር ህይወትን አስተምሮኛል ?ያ ፍቅር ደስታን አሳይቶኛል...?ያ ፍቅር ዘመዶቼን አሳጥቶ የከተማ ስደተኛና ምፅተኛ አድርጎኛል...ያ ፍቅር በራስ መታመኔን እንቅሽቅሽ አድርጎ የህይወት መስመሬን ከላይ ወደታች ገለባብጦታል…ያ ፍቅር ዛሬ ቢቋረጥም ግን ትዝታ ብቻ ሆኖ የቀረ እንደይመስላችሁ፡፡ ዛሬም ጣጣው እያደነኝ ነው...፡፡
እስከህይወቴ ፍፃሜ እንደተጣባኝ የሚዘልቅ ይመስለኛል። ...ይሄው ስድስት አመት ሞላኝ ባዶ ሆኜ መኖር ከጀመርኩ ...እና አሁን የማፍቀር ስሜት ሲሰማኝ የተገረምኩት ለዛ ነው።እውነት እርቃን ገላዋን ስላሳየችኝ ...ተዳፍኖ የኖረው የወሲብ ስሜቴ ስለተወጣጠረ ነው የተምታታብኝ። ግን አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ ስንት ጊዜ በፍቅር ፍላፃ ይወጋል..?ማወራው በወንድና ሴት መካከለል ስላለ ፆታዊ ፍቅር ነው።አንዳንድ ፍቅር አንዴ ብቻ ነው..ሌላው ጊዜያዊ ስሜት ነው ይላል፤ ብዙሀኑም ያንን ተቀብሎ ያስተጋባል።መሬት ላይ ያለው እውነታስ ምንድነው የሚያሳየው?መልሱ በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ እናገኘዎለን ...የእውነት ፍቅር አንዴ ነው ብለን የምናምን ከሆነ ወይ የህይወት ጅማሮ ላይ የምንገኝ ቲኔጀሮች ነን...ወይ ደግሞ ባጋጣሚ በልጅነታችን ከአንድ ሰው ጋር የመሰረትነው ፍቅር እስከ እርጅናችን ዘልቆልን ማጣጣም የቻልን እድለኞች ስለሆን ይሆናል።
እንጂማ በእውነታው ፍቅር ደጋግሞ ሊጎበኘን ይችላል..ለአመታት አብሮን ሊዘልቅ አልያም ለአንድ ቀን ብቻ ብልጭ ብሎ ድርግም ሊል ይችላል። አንዳንድ ፍቅር ከቃላት ልውውጥ እና ከአይን መሠራረቅ ላያልፍ ይችላል፤ሌላው እስከስሜት መጋራትና በወሲብ እስከመደራት ድረስ ከዘለቀ በኃላ ሊቋረጥ ይችላል..እስከጋብቻ ዘልቆ ልጅ ከተወለደ በኃላም ሊሰናከል ይችላል።ታዲያ ይሄኛው ፍቅር ነበረ ይሄኛው ደግሞ ዝምብሎ ግንኙነት ነው ብለን ፍርድ የምንሰጥበት ምን አይነት ተቀባይነት ያለው የህግ አንቀፅ አለ?።
ደግሞ ተፍቅሮ የተጣመረ ሁሉ ሲለያይ የግድ ፍቅሩ ስላለቀ ነው ብለን መደምደም አንችልም... አንዳንዴ በተጣማሪዎች መካከል ፍቅሩ ሞልቶ ተርፎ ግን በሌሎች አብሮ ለመኖር ምቾት በሚነሱ ምክንያቶች የተነሳም ሳይወድ በግዳቸው ፍቅራቸውን በልባቸው ቀብረው ጉዞቸውን በተለያየ ጎዳና ሊቀጥሉ የሚገደዱባቸው አያሌ አጋጣሚዎች አሉ። ምክንያቱም ለሁለት ጥንዶች አብሮ ለመኖር ፍቅር የአንበሳውን ድርሻ ይያዝ እንጂ ግን ደግሞ ብቸኛው አስፈላጊ ነገር አይደለም።
ወይ ጉድ ..በዚህች እንግዳ ሴት የተነሳ የፍቅር ኤክሰፐርት መሆን ዳዳኝ እኮ….ጠርሙሶ ውስጥ ያለችውን መጠጥ እያወዛወዝኩ ከሆቴል ወጣሁና በእኩለ ለሊት ወደቤቴ ገባሁ፡፡በፀጥታ አልጋዬ ላይ ተዘረርኩ….፡፡ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰደኝ፡፡
ጥዋት
..ከእንቅልፌ ባንኜ አይኖቼን ብገልጥም ቀልጠፍ ብዬ ከአልጋዬ መውረድ አልቻልኩም። ብነሳም ምን አልባት ምሳዬን ሰርቼ ከመብላት ውጭ ሌላ የምሄድበት ቦታ የለም ።ምሳ ደግሞ አላሰኘኝም፡፡ ምን አልባት ቁርሴን ከጋሽ ሙሉአለም የተሠጠኝን ቋንጣ ፈርፍር በደንብ ስለበላሁ ይሆናል። ተንጠራራሁና ከኮመዲኖዬ ላይ rich Dad poor Dad የሚለውን መፅሀፍ አነሳሁና ማንበብ ጀመርኩ .. አንድንም አባት የሌለው ሰው ሁለት አባቶች ያሉት ሰው የፃፈውን መፅሀፍ ለማንበብ መቋመጡ የሚገርም ነው። ብቻ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ ሁለት ገፅ ሳላነብ ስልኬ ጠራ አነሳሁና አየሁት..፡፡
የማላውቀው ቁጥር ነው ፡፡ላንሳው ልተወው ተወዛገብኩ።በስተመጨረሻ አነሳሁት
‹‹ሄሎ»
"ሄ...ሎ"ጥፍጥ ያለ የህፃን ድምፅ...ደነገጥኩ፡፡
‹‹ሄሎ..ሄሎ ..ማን ልበል?"
«ተአምል...ነኝ»
"ተአምር"የተኛሁበት የእንጨት አልጋ ከስር እርብራብ ተቀንጥሶ ይዞኝ ወደታች እየሰመጠ መሠለኝ...፡፡ስልክ ባልያዘው ቀኝ እጄ ፍራሹን ጨምድጄ ያዝኩ....፡፡እለተ መፅአት የፊታችን እሁድ መሆኑን ተረጋገጠ የሚል አዎጅን አስከትሎ የነጋሪት ጉሰማ ብሰማ ራሱ እንዲህ ሰማይ ምድሩ አይዞርብኝ፡፡
ልጅቷ ኩልትፍትፍ ባለ ድምፅ ንግግሯን ቀጠለች
"አዎ ተአምል...ል..ጅህ"
ይሄ መቼስ ተአምር ነው....፡፡ ተአምር አሁን ስምንት አመቷ ነው።በአካል ከተያየን 6 አመት አልፎናል።ማለቴ ቀጥታ በአካል ያየዋት አቅፌ የሳምኮት :ለጥቂት ቀናትም ቢሆን ስታለቅስ ያባበልኮት የዛሬ ስድስት አመት ገና ክፉና ደጉን በቅጡ መለየት ባልቻለችበት ጊዜ ነው። ለዛውም እንደአባትና እንደልጅ እኮ አይደለም እንደ እህቴ ልጅ...እንደአጎቷ ሆኜ..፡፡ለምን እንደዛ ሆነ የእውነትም አጎቷ ስለሆንኩ፤ እንደዛም ስለመሰለኝ...፡፡ከዛ ወላጆቾ የውጭ ፕሮሰስ ጀምረው ስለነበር ተአምር ዲ.ኤን. ኤ ምርመራ ማድረግ ግዴታ ሆነ …ተመረመረች...ውጤቱ ለቤተሠብ በሀይለኛ መብረቅ የመመታት ያህል ድብ እዳና አስደንጋጭ ነበር... ልጅቱ የእህቴ ባል አይደለችም?
‹‹እንዴት ሆኗ...?"የህግ ሚስቱ እኮ ነች…፡፡››
"በተክሊል ነው እኮ የተጋብት"ብዙ ብዙ ተባለ... እኔ የምገባበት ጠፋኝ..ጠጋ አልኩና
በወቅቱ"ምስር ይሄ ነገር እንዴት እንደዚህ ሆነ ?››ብዬ ጠየቅኳት።
"አንተም እንደሌላው እንዴት ሆነ ብለህ ትጠይቀኛለህ?"
‹‹ምን ማለት ነው ?እንዴት አልጠይቅሽም?"
‹‹ያደረከውን ታውቃለህ ብዬ ነዋ ?››
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
...በሙዚቃው ደነስኩ.. ውልቅልቅ እስክል ውስኪውን አንጠፍጥፌ ጠጣሁ"..አዎ አውቃኛለች... ፈፅሞ አልረሳችኝም...ከሁሉም ያስደሰተኝ ደግሞ ‹‹ቀናህ!!!›› የምትለዋ ቃል ነች...ምክንያቱም ቅናት እነጠቃለሁ ብሎ ከመፍራት ጋር ወይም ከመሠሠት ጋር ተያይዞ የሚመጣ ስሜት ነው።ፍርሀትም ስስትም ምንጫቸው ፍቅር ነው...እርግጠኝነት ከጎደለው ፍቅር።እና ታፈቅረኛለህ እያለችኝ ነው?ግን እንዳዛ ስላሰበች ለምንድነው እንደዚህ የፈነጠዝኩት? የእውነት እያፈቀርኳት ይሆን እንዴ ? እንዴ ከነጠላ ስሞ ሌላ ስለእሷ ምንም የማላውቃትን ሴት እንዴት ላፈቅራት እችላለሁ? ግን እኮ ፍቅር የኋላ ታሪክን አጥንቶ የወደፊት መድረሻን ገምቶ አሁን የቋሙበትን ድልዳል በሚዛን መዝኖ የሚገባበት የምክንያትና ውጤት ቁርኝት ማሳያ አይደለም..?ፍቅር ጨርቁን እንደጣለ ዕብድ ነገረ ስራው ቅፅበታዊና ተአምራዊ ነው።ስለዚህ ሳላቃትም በፍቅሯ ብወድቅ የሚደንቅ አይደለም!ግን ዕድሜዋ ጉዳይስ? ቢያንስ 10 አመት ትበልጠኛለች? እርግጥ በዕድሜ ሰላሳም ሀምሳም የምትበልጠውን እንስት ማፍቀር የተለመደ ነው?ቢሆንም ግን ቢገለበጥ ነበር የሚያምረው ..እኔ 10 አመት ብበልጣት።
ወየጉድ አሁንኮ ነገረ ስራዬን ላየ የመጀመሪያ የፍቅር አይነጥላዬን ገና እየገለጥኩ ያለው ጀማሪ አፍቃሪ ነው የምመስለው ፤ግን እኔ ቢያንስ አምስት አጫጭር ጣፍጭ ለወግ የሚበቁ እና አንድ ረጅም የተወሳሰበ ልቤንም ቅስሜንም አብሮ እንቅሽቅሽ አድርጎ የሠበረ.. በአለንጋ ተደጋግሞ በመገረፍ የተነሳ ትላልቅ ተጠላላፊ ሰንበር እንደተጋደመበት ጀርባ የእኔም ልብ በዛ ፍቅር ምክንያት ዙሪያ ጥምጥም የዞረበት ጠባሳ የተጋደመበት ሆኗል...
"ያ ፍቅር ህይወትን አስተምሮኛል ?ያ ፍቅር ደስታን አሳይቶኛል...?ያ ፍቅር ዘመዶቼን አሳጥቶ የከተማ ስደተኛና ምፅተኛ አድርጎኛል...ያ ፍቅር በራስ መታመኔን እንቅሽቅሽ አድርጎ የህይወት መስመሬን ከላይ ወደታች ገለባብጦታል…ያ ፍቅር ዛሬ ቢቋረጥም ግን ትዝታ ብቻ ሆኖ የቀረ እንደይመስላችሁ፡፡ ዛሬም ጣጣው እያደነኝ ነው...፡፡
እስከህይወቴ ፍፃሜ እንደተጣባኝ የሚዘልቅ ይመስለኛል። ...ይሄው ስድስት አመት ሞላኝ ባዶ ሆኜ መኖር ከጀመርኩ ...እና አሁን የማፍቀር ስሜት ሲሰማኝ የተገረምኩት ለዛ ነው።እውነት እርቃን ገላዋን ስላሳየችኝ ...ተዳፍኖ የኖረው የወሲብ ስሜቴ ስለተወጣጠረ ነው የተምታታብኝ። ግን አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ ስንት ጊዜ በፍቅር ፍላፃ ይወጋል..?ማወራው በወንድና ሴት መካከለል ስላለ ፆታዊ ፍቅር ነው።አንዳንድ ፍቅር አንዴ ብቻ ነው..ሌላው ጊዜያዊ ስሜት ነው ይላል፤ ብዙሀኑም ያንን ተቀብሎ ያስተጋባል።መሬት ላይ ያለው እውነታስ ምንድነው የሚያሳየው?መልሱ በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ እናገኘዎለን ...የእውነት ፍቅር አንዴ ነው ብለን የምናምን ከሆነ ወይ የህይወት ጅማሮ ላይ የምንገኝ ቲኔጀሮች ነን...ወይ ደግሞ ባጋጣሚ በልጅነታችን ከአንድ ሰው ጋር የመሰረትነው ፍቅር እስከ እርጅናችን ዘልቆልን ማጣጣም የቻልን እድለኞች ስለሆን ይሆናል።
እንጂማ በእውነታው ፍቅር ደጋግሞ ሊጎበኘን ይችላል..ለአመታት አብሮን ሊዘልቅ አልያም ለአንድ ቀን ብቻ ብልጭ ብሎ ድርግም ሊል ይችላል። አንዳንድ ፍቅር ከቃላት ልውውጥ እና ከአይን መሠራረቅ ላያልፍ ይችላል፤ሌላው እስከስሜት መጋራትና በወሲብ እስከመደራት ድረስ ከዘለቀ በኃላ ሊቋረጥ ይችላል..እስከጋብቻ ዘልቆ ልጅ ከተወለደ በኃላም ሊሰናከል ይችላል።ታዲያ ይሄኛው ፍቅር ነበረ ይሄኛው ደግሞ ዝምብሎ ግንኙነት ነው ብለን ፍርድ የምንሰጥበት ምን አይነት ተቀባይነት ያለው የህግ አንቀፅ አለ?።
ደግሞ ተፍቅሮ የተጣመረ ሁሉ ሲለያይ የግድ ፍቅሩ ስላለቀ ነው ብለን መደምደም አንችልም... አንዳንዴ በተጣማሪዎች መካከል ፍቅሩ ሞልቶ ተርፎ ግን በሌሎች አብሮ ለመኖር ምቾት በሚነሱ ምክንያቶች የተነሳም ሳይወድ በግዳቸው ፍቅራቸውን በልባቸው ቀብረው ጉዞቸውን በተለያየ ጎዳና ሊቀጥሉ የሚገደዱባቸው አያሌ አጋጣሚዎች አሉ። ምክንያቱም ለሁለት ጥንዶች አብሮ ለመኖር ፍቅር የአንበሳውን ድርሻ ይያዝ እንጂ ግን ደግሞ ብቸኛው አስፈላጊ ነገር አይደለም።
ወይ ጉድ ..በዚህች እንግዳ ሴት የተነሳ የፍቅር ኤክሰፐርት መሆን ዳዳኝ እኮ….ጠርሙሶ ውስጥ ያለችውን መጠጥ እያወዛወዝኩ ከሆቴል ወጣሁና በእኩለ ለሊት ወደቤቴ ገባሁ፡፡በፀጥታ አልጋዬ ላይ ተዘረርኩ….፡፡ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰደኝ፡፡
ጥዋት
..ከእንቅልፌ ባንኜ አይኖቼን ብገልጥም ቀልጠፍ ብዬ ከአልጋዬ መውረድ አልቻልኩም። ብነሳም ምን አልባት ምሳዬን ሰርቼ ከመብላት ውጭ ሌላ የምሄድበት ቦታ የለም ።ምሳ ደግሞ አላሰኘኝም፡፡ ምን አልባት ቁርሴን ከጋሽ ሙሉአለም የተሠጠኝን ቋንጣ ፈርፍር በደንብ ስለበላሁ ይሆናል። ተንጠራራሁና ከኮመዲኖዬ ላይ rich Dad poor Dad የሚለውን መፅሀፍ አነሳሁና ማንበብ ጀመርኩ .. አንድንም አባት የሌለው ሰው ሁለት አባቶች ያሉት ሰው የፃፈውን መፅሀፍ ለማንበብ መቋመጡ የሚገርም ነው። ብቻ ማንበብ ጀመርኩ፡፡ ሁለት ገፅ ሳላነብ ስልኬ ጠራ አነሳሁና አየሁት..፡፡
የማላውቀው ቁጥር ነው ፡፡ላንሳው ልተወው ተወዛገብኩ።በስተመጨረሻ አነሳሁት
‹‹ሄሎ»
"ሄ...ሎ"ጥፍጥ ያለ የህፃን ድምፅ...ደነገጥኩ፡፡
‹‹ሄሎ..ሄሎ ..ማን ልበል?"
«ተአምል...ነኝ»
"ተአምር"የተኛሁበት የእንጨት አልጋ ከስር እርብራብ ተቀንጥሶ ይዞኝ ወደታች እየሰመጠ መሠለኝ...፡፡ስልክ ባልያዘው ቀኝ እጄ ፍራሹን ጨምድጄ ያዝኩ....፡፡እለተ መፅአት የፊታችን እሁድ መሆኑን ተረጋገጠ የሚል አዎጅን አስከትሎ የነጋሪት ጉሰማ ብሰማ ራሱ እንዲህ ሰማይ ምድሩ አይዞርብኝ፡፡
ልጅቷ ኩልትፍትፍ ባለ ድምፅ ንግግሯን ቀጠለች
"አዎ ተአምል...ል..ጅህ"
ይሄ መቼስ ተአምር ነው....፡፡ ተአምር አሁን ስምንት አመቷ ነው።በአካል ከተያየን 6 አመት አልፎናል።ማለቴ ቀጥታ በአካል ያየዋት አቅፌ የሳምኮት :ለጥቂት ቀናትም ቢሆን ስታለቅስ ያባበልኮት የዛሬ ስድስት አመት ገና ክፉና ደጉን በቅጡ መለየት ባልቻለችበት ጊዜ ነው። ለዛውም እንደአባትና እንደልጅ እኮ አይደለም እንደ እህቴ ልጅ...እንደአጎቷ ሆኜ..፡፡ለምን እንደዛ ሆነ የእውነትም አጎቷ ስለሆንኩ፤ እንደዛም ስለመሰለኝ...፡፡ከዛ ወላጆቾ የውጭ ፕሮሰስ ጀምረው ስለነበር ተአምር ዲ.ኤን. ኤ ምርመራ ማድረግ ግዴታ ሆነ …ተመረመረች...ውጤቱ ለቤተሠብ በሀይለኛ መብረቅ የመመታት ያህል ድብ እዳና አስደንጋጭ ነበር... ልጅቱ የእህቴ ባል አይደለችም?
‹‹እንዴት ሆኗ...?"የህግ ሚስቱ እኮ ነች…፡፡››
"በተክሊል ነው እኮ የተጋብት"ብዙ ብዙ ተባለ... እኔ የምገባበት ጠፋኝ..ጠጋ አልኩና
በወቅቱ"ምስር ይሄ ነገር እንዴት እንደዚህ ሆነ ?››ብዬ ጠየቅኳት።
"አንተም እንደሌላው እንዴት ሆነ ብለህ ትጠይቀኛለህ?"
‹‹ምን ማለት ነው ?እንዴት አልጠይቅሽም?"
‹‹ያደረከውን ታውቃለህ ብዬ ነዋ ?››
👍56😁2😱1
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ብዙ ፍላጎቶች አሏት..ለዛውም ያልተገሩ ፍላጎቶች ።አንደኛውን ለማሟላት በቀኝ ትጓዛለች ..ሌላው ደግሞ ወደግራ ያስፈነጥራታል...እንዲሁ የፍላጎቶቾን ጭራ ተከትላ ከግራ ቀኝ ስትላጋ ትከርምና በስተመጨረሻ እራሷ ከራሷ ትጠፋለች‹‹...የት ነው ያለሁት?ምን እየሠራሁ ነው? ምንድነበር የምፈልገው?››የአንድንም መልስ መመለስ አትችልም.... ፍፅም ድንዛዜ ውስጥ ትገባለች።ነፍሷ በማጥ ተይዛ እዛው ጭቃ ውስጥ መውጣት አቅቷት የምትንቧጫረቅ ይመስላታል..‹‹.ጭቃ ውስጥ ገብቼ እንደዚህ እየዳከርኩ ያለሁት እኔ ነኝ ሌላ ሰው?›› ግራ ይገባታል...እራሷው ከእራሷ ትጠፋለች።አንድ ሰው እራሱ ጠፊ እራሱ ደግሞ ፈላጊ ሲሆን የሚፈጠረው ነገር?
ለሊቱ በመከራ ነው የነጋላት..ምን አልባትም በህይወቷ ካጋጠሟት እጅግ አታካችና ደባሪ ለሊቶች ውስጥ አንዱ ነው….አስራአንድ ሰዓት ከሆነ በኃላ ክፍሏ ውስጥ መቆየት አልቻለችም ፡፡ መኝታዋን ለቃ ወረደችና ቁምሳጥኗን ከፋፍታ ፊት ለፊት ያገኘቻውን ልብስ ያለምንም ማሰብ ለባበሰችና ስልኳንና የቃልን ላፕቶፕ በቦርሳዋ ከተተች፡፡ ከክፍሏ ይዛ ወጣች…በሩን ስትዘጋና ስትከፍት እናቷን እንዳትቀሰቅስና እሄዳለሁ አትሂጂም የሚል አተካራ ውስጥ ላለመግባት ብላ በጥንቃቄና በፀጥታ ወደታች ወረደች ፡፡ የሳሎኑን በራፍ ከፍታ ወጣች... ግቢው ውስጥ የለሊቱን መንጋት የሚያበስሩ ባለ ብዙ ቀለም ማራኪ ወፎች ከአንዱ ዛፍ ወደሌላው ዛፍ እየተሸጋገሩ ሲዘምሩ ከሚሰማው ተፈጥሮዊ ዝማሬ በስተቀር ሙሉ አካባቢው ፀጥ ያለ ነው፡፡ወደ ዘበኛው ቤት ሄደችና በስሱ አንኳኳች‹‹…..ማነው….?››የሚል ሻካራ ድምጽ ከውስጥ ተሰማ፡፡
‹‹ድምፅህን ቀንስ እኔ ነኝ?››
‹‹እትዬ ልዩ ምነው?››የ50 አመቱ ጎልማሳ እሷን የ23 አመቷን ልጅ እትዬ እያለ ሲጠራት ሁሌ እንዳስፈገጋት ነው…ብዙ ጊዜ ልዩ ብቻ ብሎ እንዲጠራት ነግራውም አስፈራርታውም ነበር..እሺ ይላል እንጂ በተአምር ተሳስቶ ልዩን ከእትዬ ነጠሎ ጠርቷት አያውቅም.. አሁንማ እሷም ለመደችው …
‹‹ድምፅ ቀንስ እኮ አልኩህ…ፈልጌህ ነው?››
‹‹እሺ እሺ..›› እየተደናበረ ወጣ፡፡››
‹‹ምነው…? ፈለግሺኝ….?››
‹‹መኪና ይዤ ልወጣ ነው፡፡››
‹‹ከማ ጋር?››
‹‹ከአንተ ጋር ››
‹‹ምን አልሺኝ እትዬ?››
‹‹ብቻዬን ነዋ…እዚህ አካባቢ በዚህን ሰዓት አብሮኝ ሊሄድ የሚችል ሰው ይታይሀል?..አሁን ክፈትልኝ…እስከዛ ሞተር ላሙቅ ››እለችውና መኪኖች ወደሚቆሙበት ስፍራ ሄደች…
ሶስት ሚኪኖች በተርታ ተጠጋግተው ቆመዋል፡፡ዝም ብላ የእናቷን ሰማያዊ ኮሮላ መኪና ውስጥ ገባች፡፡ያው በእነሱ ቤት ልምድ መኪኖች ግቢ ውስጥ ከገቡ በኃላ ቁልፋቸው አይነቀልም..ምን አልባት ኢመርጀንሲ ተፈጥሮ ቢፈለጉ ገና ቁልፉን ከቤት ወይም ከሹፌሮች ጋር ከመፈለግ መንዳት የሚችል ሰው ወዲያው ገባ ብሎ ይነዳቸዋል..ይህ ህግ የወጣው በእሷ ምክንያት ነው..፡፡ያው በተለያ ሰበብ ሁሌ አደጋ ስለማያጣት…ሹፌር ፍለጋና ቁልፍ ፍለጋ ህይወቷንም ጭምር ሊያሳጣት የደረሰ አጋጣሚ ተከስቶ ስለነበር ይሄ ውሳኔ ተወሰነ..እና ይሄው ዛሬ ለራሷ ረዳት…፡፡
ላፕቶፑን ያለበትን ቦርሳዋን ከጎኗ አስቀመጠችና ቁልፉን አሽከርክራ ሞተሩን አስነሳችው.‹‹.መቼስ እማዬ የመኪናውን የሞተር ድምፅ ሰምታ በመንቃት መጥታ እንደማትቀውጠው ተስፋ አደርጋለሁ፡፡››አለች
ዘበኛው በራፉን በልቅጦ ከፈተና እየተጎተተ ወደእሷ መጣ….. በአሳዛኝ ሁኔታ እየተቅለሰለሰ‹‹እትዬ ልዩ ግን አትዬ እንዴት እንደሚቆጡኝ እየታየኝ ሆዴ ተሸብሮብኛል…. ሊያባርሩኝ ሁሉ ይችላሉ፡፡›› አላት፡፡
ኪሷ ገባችና ድፍን ሁለት መቶ ብር በማውጣት በእጁ አስጨበጠችው… ‹‹ከሰደበችህ በዚህ ቻለው…ከባረረችህ ግን ደውልልኝ እኔ አስቆማታለሁ…›› አለችው፡፡
በደስታ ተፍለቅልቆ‹‹እሺ የእኔ ደግ..ይሁን እችለዋለሁ…በይ ሂጂ›››አለታ
መኪናውን አስነሳችና ግቢውን ለቃ ወጣች….መንገዱ ነፃና ምንም አደናቃፊ ስለሌለበት 25 ደቂቃ ነው የፈጀባት፡፡በራፉ ላይ ደርሳ የመኪናዋን አፍንጫ የግቢ በራፋቸው ላይ አስደግፋ አቆመች ..ሰአቷን ስታይ ሰውነቷ ቀዘቀዘ.. ‹‹በዚህ ሰዓት ለምን መጣሁ? ምንድነው የማደርገው..?›› ግራ ገባት…፡፡
‹‹በዚህ ለሊት እንደመርዶ ነጋሪ የሰው በራፍ አላንኳኳም፡፡የራሱ ቤት እንኳን ቢሆን የራሱ ጉዳይ….የኪራይ ቤት ለዛውም አሮጊት…..ምን አለ የዛን ቀን ስልክ ቁጥሩን ተቀብዬው ቢሆን.. አሁን ደውልለትና ቀጥታ መጥቶ ይከፍትልኝ ነበር….ከዛ ይሄንን ላፕቶፕ አፍንጫው ላይ ወርውሬለት የመኪናዬን መሪ ወደኃላ አዙሬ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ይሄን ሰፈር እለቅ ነበር…ከህይወቴ እስከመጨረሻ አሽቀንጥሬ እወረውረውና ከእነመፈጠሩም እረሳው ነበር፡፡››ስትል አብሰለሰለች፡፡
የመኪናዋ መሪ ላይ ተደፍታ እነዚህንና መሰል ሀሳቦች እያሰበች ሳለ ባልገመተችው ሁኔታ የግቢው ትንሿ በራፍ ከውስጥ መንጓጓት ጀመረች…..ነቃ አለችና, ከተደፋችበት ተነሳች፡፡ በራፉ ተከፍቶ ነጭ በነጭ የለበሰች አንድ ሰትዬ ወጡ …አሮጊቷ የቃል አከራይ ናቸው፡፡አለባበሳቸውን ብቻ አይቶ ወደቤተክርስቲያን ሊሄዱ እንደሆነ መናገር ይቻላል…ከወጡ በኃላ ባልተለመደ ሁኔታ መኪና በራፋቸውን ታኮ መቆም እንዳስገረማቸውም እንዳስደነገጣቸውም ከሁኔታቸው መገመት ይቻላል፡፡…ልዩ ያንን ስለተረዳች ፈጠን ብላ ገቢናውን ከፈተችና በመውረድ ወደ እሳቸው ተጠጋች፡፡
‹‹ደህና አደሩ ማዘር …የቃል ጓደኛ ነኝ፡፡››
‹‹እ…የበቀደሞ ልጅ ነሽ;››
‹‹ቆቅ አሮጊት ናቸው››ስትል አሰበች… እንዲህ በፍጥነት ያውቁኛል ብላ አልገመተችም ነበር፡፡
‹‹አዎ..አውቀውኛል››
‹‹ታዲያ ሰላምም አይደለሽ…?ገና ለሊት ነው እኮ፡፡››
‹‹‹አዎ ከቃል ጋር 12.30 የሆነ ቦታ ለመሄድ ተቀጣጥረን ነበር …ሳላስበው ትንሽ ቀደም ብዬ መጣሁና ማንኳኳት ደበረኝ፡፡››
‹‹እና አትደውይለትም ነበር?››
‹‹ሞክሬ ነበር..ዘግቶታል መስለኝ አይሰራም››ውሸት መቼስ የተካነችበት ነው..ከልጅነቷ ጀምሮ በብቃት የምትሰራቸው ሶስት ነገሮች ሌብነትና ቅጥፈት እና ወሬ(የሰው ሚስጥር)ማነፍነፍ ናቸው…፡፡
‹‹ግቢያ ….በራፍን ልክፈትልሽና ሚኪናዋን ታስገቢያት?››
የበቀደምለታው ግልምጫ ከዛሬው መሽቆጥቀጥ ጋር አመዛዝና ፈገግ አለች፡፡በቀደም የዱርዬ ገፀ ባህሪ ተላብሳ ነው ፊታቸው የተጋረጠችው ዛሬ ደግሞ የሞጃ ልጅ .ስለዚህ አይፈረድባቸውም፡፡
‹‹…ግዴለም ማዘር እርሶ ይሂዱ እኔ ከፍቼ አስገባዋለሁ››አለቻቸው፡፡
‹‹እሺ ልጄ.ደህና ዋይ ..››.ብለው በራፍን ለቀውላት ወደፊት መራመድ ሲጀምሩ የእሳቸውን ቀልብ ምትማርክበት የሆነች ሸር ነገር ብልጭ አለችላት…ኪሷ ገባችና ድፍን ሁለት መቶ ብር አወጣች፡፡
‹‹ማዘር.. ››
‹‹አቤት ልጄ›› ባሉበት ቆሙና ፊታቸው ወደ እሷ አዞሩ..ሮጣ ሄደችና ተጠጋቻቸው.
.‹‹‹ይቅርታ ይቺን ሙዳይ ምፅዋት ውስጥ ያስገቡልኝና..ያሰበችው ይሳካላት ብለው ይፀሉልኝ፡፡››
ፊታቸው ሲፈካ በግልፅ ይታያታል…‹‹ልጄ ይሳካልሽ…. ተባረኪ… ወይ አንቺም እንደቃልዬ ነሽ መሰለኝ..ለመሆኑ ስምሽ ማነው?››ሲሉ ጠየቋት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ብዙ ፍላጎቶች አሏት..ለዛውም ያልተገሩ ፍላጎቶች ።አንደኛውን ለማሟላት በቀኝ ትጓዛለች ..ሌላው ደግሞ ወደግራ ያስፈነጥራታል...እንዲሁ የፍላጎቶቾን ጭራ ተከትላ ከግራ ቀኝ ስትላጋ ትከርምና በስተመጨረሻ እራሷ ከራሷ ትጠፋለች‹‹...የት ነው ያለሁት?ምን እየሠራሁ ነው? ምንድነበር የምፈልገው?››የአንድንም መልስ መመለስ አትችልም.... ፍፅም ድንዛዜ ውስጥ ትገባለች።ነፍሷ በማጥ ተይዛ እዛው ጭቃ ውስጥ መውጣት አቅቷት የምትንቧጫረቅ ይመስላታል..‹‹.ጭቃ ውስጥ ገብቼ እንደዚህ እየዳከርኩ ያለሁት እኔ ነኝ ሌላ ሰው?›› ግራ ይገባታል...እራሷው ከእራሷ ትጠፋለች።አንድ ሰው እራሱ ጠፊ እራሱ ደግሞ ፈላጊ ሲሆን የሚፈጠረው ነገር?
ለሊቱ በመከራ ነው የነጋላት..ምን አልባትም በህይወቷ ካጋጠሟት እጅግ አታካችና ደባሪ ለሊቶች ውስጥ አንዱ ነው….አስራአንድ ሰዓት ከሆነ በኃላ ክፍሏ ውስጥ መቆየት አልቻለችም ፡፡ መኝታዋን ለቃ ወረደችና ቁምሳጥኗን ከፋፍታ ፊት ለፊት ያገኘቻውን ልብስ ያለምንም ማሰብ ለባበሰችና ስልኳንና የቃልን ላፕቶፕ በቦርሳዋ ከተተች፡፡ ከክፍሏ ይዛ ወጣች…በሩን ስትዘጋና ስትከፍት እናቷን እንዳትቀሰቅስና እሄዳለሁ አትሂጂም የሚል አተካራ ውስጥ ላለመግባት ብላ በጥንቃቄና በፀጥታ ወደታች ወረደች ፡፡ የሳሎኑን በራፍ ከፍታ ወጣች... ግቢው ውስጥ የለሊቱን መንጋት የሚያበስሩ ባለ ብዙ ቀለም ማራኪ ወፎች ከአንዱ ዛፍ ወደሌላው ዛፍ እየተሸጋገሩ ሲዘምሩ ከሚሰማው ተፈጥሮዊ ዝማሬ በስተቀር ሙሉ አካባቢው ፀጥ ያለ ነው፡፡ወደ ዘበኛው ቤት ሄደችና በስሱ አንኳኳች‹‹…..ማነው….?››የሚል ሻካራ ድምጽ ከውስጥ ተሰማ፡፡
‹‹ድምፅህን ቀንስ እኔ ነኝ?››
‹‹እትዬ ልዩ ምነው?››የ50 አመቱ ጎልማሳ እሷን የ23 አመቷን ልጅ እትዬ እያለ ሲጠራት ሁሌ እንዳስፈገጋት ነው…ብዙ ጊዜ ልዩ ብቻ ብሎ እንዲጠራት ነግራውም አስፈራርታውም ነበር..እሺ ይላል እንጂ በተአምር ተሳስቶ ልዩን ከእትዬ ነጠሎ ጠርቷት አያውቅም.. አሁንማ እሷም ለመደችው …
‹‹ድምፅ ቀንስ እኮ አልኩህ…ፈልጌህ ነው?››
‹‹እሺ እሺ..›› እየተደናበረ ወጣ፡፡››
‹‹ምነው…? ፈለግሺኝ….?››
‹‹መኪና ይዤ ልወጣ ነው፡፡››
‹‹ከማ ጋር?››
‹‹ከአንተ ጋር ››
‹‹ምን አልሺኝ እትዬ?››
‹‹ብቻዬን ነዋ…እዚህ አካባቢ በዚህን ሰዓት አብሮኝ ሊሄድ የሚችል ሰው ይታይሀል?..አሁን ክፈትልኝ…እስከዛ ሞተር ላሙቅ ››እለችውና መኪኖች ወደሚቆሙበት ስፍራ ሄደች…
ሶስት ሚኪኖች በተርታ ተጠጋግተው ቆመዋል፡፡ዝም ብላ የእናቷን ሰማያዊ ኮሮላ መኪና ውስጥ ገባች፡፡ያው በእነሱ ቤት ልምድ መኪኖች ግቢ ውስጥ ከገቡ በኃላ ቁልፋቸው አይነቀልም..ምን አልባት ኢመርጀንሲ ተፈጥሮ ቢፈለጉ ገና ቁልፉን ከቤት ወይም ከሹፌሮች ጋር ከመፈለግ መንዳት የሚችል ሰው ወዲያው ገባ ብሎ ይነዳቸዋል..ይህ ህግ የወጣው በእሷ ምክንያት ነው..፡፡ያው በተለያ ሰበብ ሁሌ አደጋ ስለማያጣት…ሹፌር ፍለጋና ቁልፍ ፍለጋ ህይወቷንም ጭምር ሊያሳጣት የደረሰ አጋጣሚ ተከስቶ ስለነበር ይሄ ውሳኔ ተወሰነ..እና ይሄው ዛሬ ለራሷ ረዳት…፡፡
ላፕቶፑን ያለበትን ቦርሳዋን ከጎኗ አስቀመጠችና ቁልፉን አሽከርክራ ሞተሩን አስነሳችው.‹‹.መቼስ እማዬ የመኪናውን የሞተር ድምፅ ሰምታ በመንቃት መጥታ እንደማትቀውጠው ተስፋ አደርጋለሁ፡፡››አለች
ዘበኛው በራፉን በልቅጦ ከፈተና እየተጎተተ ወደእሷ መጣ….. በአሳዛኝ ሁኔታ እየተቅለሰለሰ‹‹እትዬ ልዩ ግን አትዬ እንዴት እንደሚቆጡኝ እየታየኝ ሆዴ ተሸብሮብኛል…. ሊያባርሩኝ ሁሉ ይችላሉ፡፡›› አላት፡፡
ኪሷ ገባችና ድፍን ሁለት መቶ ብር በማውጣት በእጁ አስጨበጠችው… ‹‹ከሰደበችህ በዚህ ቻለው…ከባረረችህ ግን ደውልልኝ እኔ አስቆማታለሁ…›› አለችው፡፡
በደስታ ተፍለቅልቆ‹‹እሺ የእኔ ደግ..ይሁን እችለዋለሁ…በይ ሂጂ›››አለታ
መኪናውን አስነሳችና ግቢውን ለቃ ወጣች….መንገዱ ነፃና ምንም አደናቃፊ ስለሌለበት 25 ደቂቃ ነው የፈጀባት፡፡በራፉ ላይ ደርሳ የመኪናዋን አፍንጫ የግቢ በራፋቸው ላይ አስደግፋ አቆመች ..ሰአቷን ስታይ ሰውነቷ ቀዘቀዘ.. ‹‹በዚህ ሰዓት ለምን መጣሁ? ምንድነው የማደርገው..?›› ግራ ገባት…፡፡
‹‹በዚህ ለሊት እንደመርዶ ነጋሪ የሰው በራፍ አላንኳኳም፡፡የራሱ ቤት እንኳን ቢሆን የራሱ ጉዳይ….የኪራይ ቤት ለዛውም አሮጊት…..ምን አለ የዛን ቀን ስልክ ቁጥሩን ተቀብዬው ቢሆን.. አሁን ደውልለትና ቀጥታ መጥቶ ይከፍትልኝ ነበር….ከዛ ይሄንን ላፕቶፕ አፍንጫው ላይ ወርውሬለት የመኪናዬን መሪ ወደኃላ አዙሬ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ይሄን ሰፈር እለቅ ነበር…ከህይወቴ እስከመጨረሻ አሽቀንጥሬ እወረውረውና ከእነመፈጠሩም እረሳው ነበር፡፡››ስትል አብሰለሰለች፡፡
የመኪናዋ መሪ ላይ ተደፍታ እነዚህንና መሰል ሀሳቦች እያሰበች ሳለ ባልገመተችው ሁኔታ የግቢው ትንሿ በራፍ ከውስጥ መንጓጓት ጀመረች…..ነቃ አለችና, ከተደፋችበት ተነሳች፡፡ በራፉ ተከፍቶ ነጭ በነጭ የለበሰች አንድ ሰትዬ ወጡ …አሮጊቷ የቃል አከራይ ናቸው፡፡አለባበሳቸውን ብቻ አይቶ ወደቤተክርስቲያን ሊሄዱ እንደሆነ መናገር ይቻላል…ከወጡ በኃላ ባልተለመደ ሁኔታ መኪና በራፋቸውን ታኮ መቆም እንዳስገረማቸውም እንዳስደነገጣቸውም ከሁኔታቸው መገመት ይቻላል፡፡…ልዩ ያንን ስለተረዳች ፈጠን ብላ ገቢናውን ከፈተችና በመውረድ ወደ እሳቸው ተጠጋች፡፡
‹‹ደህና አደሩ ማዘር …የቃል ጓደኛ ነኝ፡፡››
‹‹እ…የበቀደሞ ልጅ ነሽ;››
‹‹ቆቅ አሮጊት ናቸው››ስትል አሰበች… እንዲህ በፍጥነት ያውቁኛል ብላ አልገመተችም ነበር፡፡
‹‹አዎ..አውቀውኛል››
‹‹ታዲያ ሰላምም አይደለሽ…?ገና ለሊት ነው እኮ፡፡››
‹‹‹አዎ ከቃል ጋር 12.30 የሆነ ቦታ ለመሄድ ተቀጣጥረን ነበር …ሳላስበው ትንሽ ቀደም ብዬ መጣሁና ማንኳኳት ደበረኝ፡፡››
‹‹እና አትደውይለትም ነበር?››
‹‹ሞክሬ ነበር..ዘግቶታል መስለኝ አይሰራም››ውሸት መቼስ የተካነችበት ነው..ከልጅነቷ ጀምሮ በብቃት የምትሰራቸው ሶስት ነገሮች ሌብነትና ቅጥፈት እና ወሬ(የሰው ሚስጥር)ማነፍነፍ ናቸው…፡፡
‹‹ግቢያ ….በራፍን ልክፈትልሽና ሚኪናዋን ታስገቢያት?››
የበቀደምለታው ግልምጫ ከዛሬው መሽቆጥቀጥ ጋር አመዛዝና ፈገግ አለች፡፡በቀደም የዱርዬ ገፀ ባህሪ ተላብሳ ነው ፊታቸው የተጋረጠችው ዛሬ ደግሞ የሞጃ ልጅ .ስለዚህ አይፈረድባቸውም፡፡
‹‹…ግዴለም ማዘር እርሶ ይሂዱ እኔ ከፍቼ አስገባዋለሁ››አለቻቸው፡፡
‹‹እሺ ልጄ.ደህና ዋይ ..››.ብለው በራፍን ለቀውላት ወደፊት መራመድ ሲጀምሩ የእሳቸውን ቀልብ ምትማርክበት የሆነች ሸር ነገር ብልጭ አለችላት…ኪሷ ገባችና ድፍን ሁለት መቶ ብር አወጣች፡፡
‹‹ማዘር.. ››
‹‹አቤት ልጄ›› ባሉበት ቆሙና ፊታቸው ወደ እሷ አዞሩ..ሮጣ ሄደችና ተጠጋቻቸው.
.‹‹‹ይቅርታ ይቺን ሙዳይ ምፅዋት ውስጥ ያስገቡልኝና..ያሰበችው ይሳካላት ብለው ይፀሉልኝ፡፡››
ፊታቸው ሲፈካ በግልፅ ይታያታል…‹‹ልጄ ይሳካልሽ…. ተባረኪ… ወይ አንቺም እንደቃልዬ ነሽ መሰለኝ..ለመሆኑ ስምሽ ማነው?››ሲሉ ጠየቋት፡፡
👍91😁8❤5👎2🔥1👏1🤔1
#ህያብ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
"ህያብ ያለፈ ታሪክሽ ምንም ይሁን ምን አንቺን ከማፍቀር ሊያቆመኝ አይችልም። የኔ ቆንጆ የፍቅር ጓደኛዬ ትሆኛለሽ?"
"ዮኒ.." ተርበተበትኩ... ቢኒን ዞር ብዬ ሳየው ፈገግ ብሎ እያዬን ነው። ፈገግታው ውስጥ ሁሉም ነገር ሰላም ነው የሚል መልዕክት ያነበብኩ መሰለኝ••• አበባውን ተቀበልኩ
ከዮኒ ጋር ህልም የሚመስሉ ሁለት ሳምንታትን አሳለፍን። ሁሉም ነገር በጣም ደስ የሚል ነበር እያንዳንዷን ቀን ደስ በሚል ሁኔታ አሳለፍናት።
ጎንደርን ለቆ ወደ አዲስ አበባ የሚሄድበት ቀን ደረሰ እኔና ቢን ቀድመን ለመሰናበት አገኘነው።
ካፌ ተገናኝተን ሞቅ ያለ ወሬ እያወራን በመሀል ቢኒ
"ይህን ሁሉ ጊዜ አስለፍተሀት አንድ ወርም ሳይቆይ ልትሄድ ነው?" አለው።
"በልፋት እንኳን ከኔ የበለጠ የለፋች አይመስለኝም ሀሀሀሀ ስቀልድ ነው። ይሄን የመሰለ ፍቅር ትቼ መሄዴ ሳያስከፋኝ ቀርቶ መሰለህ በእርግጥ መጀመሪያ ወድጄና ፈቅጄ እንደውም በጣም ፈልጌው ነበር ዝውውር የጠየኩት" ያልሰማሁት አዲስ ነገር ሆነብኝ
"አንተ ጠይቀህ ነው እንዴ የተዘዋወርከው" ግርም ብሎኝ ጠየኩት
"አዎ ለዚህ ዝውውር እስከ ጥግ ለፍቻለሁ አሁን ግን አልፈልገውም ነበር ግን ምንም ማድረግ አልችልም" እዝን ብሎ አንገቱን ደፋ
"ለምን ነበር ዝውውሩን የጠየከው" ቢኒ ጣልቃ ገባ
"በሷ ምክንያት ነዋ" እጄን በእጁ እያጠላለፈ "ያን ሁሉ ነገር ሰማሁ ምንም ብሰማ እንኳን ላንቺ ያለኝ ፍቅር ሊቀንስ አልቻለም ጭራሽ የማላውቀው ስበት ወዳንቺ ይገፋኛል። መቋቋም አቃተኝ ስራዬ ላይ ሳይቀር ተፅዕኖ ፈጠረብኝ እናም መሸሽን መረጥኩ እና ዝውውር ጠየኩ"
"የዚህ አመት ትምህርት ሲያልቅ እመጣ አይደል ከእናቴ ውጪ የሚቀበለኝ ሰው አለ ማለት ነው" መሄዱ ሀዘን እንዳይለቅብኝ መልካም መልካም ነገሮችን ለማውራትና ለማሰብ ሞከርኩ
"እስከዛው አደራ የምለው ላንተ ነው ቢኒያም.... ናፍቆት ናፍቆት እያለች ትምህርት ላይ እንዳትዘናጋ ደግሞ በስልክም እናወራለን" ቢኒ በአንገት ንቅናቄ እሽታውን ገለፀ።
ፍቅሬን ሞቅ ባለ ስንብት ወደ አዲስ አበባ ሸኘነው።
እኔ ልሁን እሱ ይሁን ማን እንደተቀየረ ባይገባኝም ከቢኒ ጋር እንደድሯችን ልንሆን አልቻልንም ሳገኘው ሳወራው የሆነ ክፍተት እንዳለ ይሰማኛል። መጥፎ ስሜቶች አብረውኝ እንዲቆዩ አልፋግም እሱን ለማውራት ወሰንኩ
"ቢን ግን የተፈጠረ ችግር አለ ማለቴ ምንም እንደድሮው ልንሆን አልቻልንም እኮ ያጠፋሁት ጥፋት አለ እንዴ"
"ኖ ህያብ ምንም አላጠፋሽም እኔ ነኝ በራሴ ችግር ምክንያት ነው አንቺም ለይ ተፅዕኖ እንደፈጠረ አላወኩም.... "
"እና ችግሩን ንገራታ መፍትሄው እኮ በሷ እጅ ነው" የቢኒ ጓደኛ ሀብታሙ ከየት መጣ ሳይባል አጠገባችን ተገኝቷል
"እየውልሽ ህያብ ቢኒ ባንቺ ምክንያት ሀገ..." ንግግሩን ሳይጨርስ የቢኒ እጅ አፉ ላይ አረፈ እና እንቅ አድርጎ ያዘው ትንሽ ከታገሉ በኋላ ለቀቀው
"ባለፈው እንደነገርኩህ ነው ወይ ንገራት ካለዛ እኔ እነግራታለሁ"
" ቢኒ ምንድነው ማወቅ ያለብኝ ነገር አለ" ቢኒ ግራ ገብቶት አንዴ እሱን አንዴ እኔን ያያል።
"አቦ ዝም ብለህ እኮ ነው የምታካብደው" ሀብታሙ በንዴት እየተወናጨፈ ትቶን ሄደ
"ቢን ንገረኝ ምንድነው ከኔ የምትደብቀው ነገር አለ እንዴ"
"አይ ህያብ ለመደበቅ አይደለም እነግርሻለሁ ምን መሰለሽ ግን.... እ...እ....እ ማለቴ እኔ ካንቺ..... ማለቴ ....አንቺን.... "
እኔ ቢኒያም ነኝ ልተርክላቹ
ከመጀመሪያ ጀምሮ ምን እንደተፈጠረ ልንገራችሁ። ህያብን አፈቅራታለሁ አጠገቤ እያለች የማንም ሳትሆን በየቀኑ አብሪያት ስሆን ስንተቃቀፍ ስናወራ አብረን ስንበላና ስንጠጣ ጭንቅላቴ የሚያስበው ጓደኛዬ እንደሆነች ቢሆንም ይህ ልቤ ግን ሁሉን ነገር ፍቅር ብሎ ይወስደው ነበር። ሁሉም ነገር የገባኝ ህያብን በሌላ ሰው እቅፍ ውስጥ ሳያት ነው። መቋቋም አቃተኝ
ከዮኒ ጋር ካወራን በኋላ እሷ ያለምንም ጥርጥር የሱ እንደምትሆን አመንኩ በዛው ልክ ደግሞ ህያብን ላጣት እንደሆነ እና መቼም የኔ እንደማትሆን ተረዳሁ.... አለ አይደል በቃ ሳስብ የኖርኩት የዮኒ ብልግና የሆነ ቀን አንገሽግሿት እሱን መፈለጓን ለማቆም የምትወስን..... ከዛ የኔ የምትሆንበት ሰፊ እድል.....
በነዛ ሁሉ ጊዜያቶች ለራሴ ስነግረው የነበረው ህያብ መቼም ቢሆን ከዛ ባለጌ ዮኒ ጋር ልትሆን እንደማትችል እና የኔ እና የኔ ብቻ እንደምትሆን ነበር። ሁኔታዎች ግን ባላሰብኩት መንገድ ድብልቅልቃቸው ወጣ ህያብን በሌላ ሰው እቅፍ ውስጥ ላያት ሆነ።
ለዶርም ጓደኞቼ ህያብም ሆነ ማንም ቢጠይቃቸው ቤተሰብ ጋ እንደሄድኩ እንዲነግሩ አስጠንቅቄ ከሀብታሙ ጋር አዲስ አበባ አክስቱ ቤት ሄድን። ሀብታሙ ከስር ከመሰረቱ ለሷ ያለኝን ፍቅር ያውቃል እንድቀርባትም ያደፋፈረኝ እሱ ነበር ለዛም ነው ብቻዬን ልሂድ ስለው አይሆንም ብሎኝ አክስቱ ጋር በነፃነት መሆን እንደምንችል አሳምኖኝ አብሮኝ የመጣው
ለቀናት ጠጣሁ ሰከርኩ በእብደት አለም ውስጥ ዋዠኩ። መርጋጋት የሚባለው ነገር ከኔ በእጥፍ እራቀ። ሁኔታዬ ያሳሰበው ሀብትሽ ከቀናት በኋላ መጠጥ ከሚባል ቦታ እንዳልደርስ በግድ ከለከለኝ
ወደምጠጣበት ቦታ ለመሄድ ወንበር ላይ ቁጭ ብዬ ጫማዬን እያሰርኩ ፊት ለፊቴ መጥቶ ቆመና "ምን እየሆንክ ነው በዚህ ሁኔታህ ህያብን የምታገኛት ይመስልሀል። ቢኒያም እንደዚህ እየሆነ መሆኑን የምታውቅ መሰለህ.... እሷማ የምታውቀው ቢኒ እንደታላቅ ወንድም የምታየው ጓደኛዋ እንደሆነ ነው። ንገረኝ እስኪ በማን ላይ ነው የተናደድከው ህያብ ላይ ነው?"
"አይደለም" አልኩት አንገቴን እንደደፋሁ
"በፍቅር ነው?"
"አይደለም እሷን በማፍቀሬማ ደስተኛ ነኝ"
"በራስህ ነው?"
"አዎ ምክንያቱም እስከዛሬ ያመንኩበት ሁሉ ገደል ገባ"
"ይህ እንዳይሆን ማድረግ የምትችለው ነገር ነበር?"
"አላውቅም ምን ላደርግ እችላለሁ መጀመሪያ ነግሪያት ቢሆን የምትወደው ጓደኛዋ ለመሆን አልችልም ነበር። መሀል ላይ ደግሞ ያመንኩት የሱ ነገር ስልችቷት እኔን እንደምታይ ነበር። አሁን ደግሞ ረፍዷል እና በራሴ የትኛውን ነገር አላደረክም ብዬ ልናደድበት?"
"ጥያቄዬን በጥያቄ ሳይሆን በቀጥታ መልስልኝ በራስህ ነው የተናደድከው?"
"አይደለም" አልኩት
"በዮኒ ነው?"
"አይደለም"?
" እና በማን ነው"?
"አላውቅም" አልኩት እውነት ግን በማን ነው የተናደድኩት
"እሺ ለምንድነው እንደዚ እየሆንክ ያለኸው"
"ትቀልዳለህ እንዴ ህያብ የኔ ስለማትሆን ነዋ! በናትህ አሁን መጠጣት ነው የምፈልገው" አልኩት ወሬውን ጨርሶ ዞር እንዲልልኝ በማሰብ
"እንደዚህ መሆንህ ህያብን ያንተ እንድትሆን ያደርጋታል?"
"አያደርጋትም" ከፊት ለፊቴ ዞር አለና ከኮመዲኖ ላይ ቁልፍ እነሳ ከዛ ቀጥታ ወደበሩ አመራ እና ቁልፉን እያሳየኝ
"ስለዚህ በማን እንደተናደድክ አታውቅም ግን ምስኪኑን ጨጓራህን በመጠጥ እያነደድከው ነው ቢያንስ ለጨጓራህ በጠዋት እየተነሳሁ እስከማታ በመጠጥ የማነድህ በዚህ ሰው ተናድጄ ነው ብለህ አንድ ምክንያት ንገረው። ህያብ ደግሞ ከእጅህ ወጥታለች ስለዚህ ሁኔታዎችን አምነህ ተቀበል ወይም ያንተ የምትሆን ከሆነ ያንን ጊዜ ጠብቅ.... ወደራስህ ተመልሰህ ጠብቀኝ ምግብ ይዤ እመጣለሁ" በሩን ቆልፎብኝ ሄደ
ያለሁበት አንድ ክፍል ቤት ሌላ መውጫ የለውም ከተቀመጥኩበት ተነሳሁና አልጋ ላይ ወጥቼ ጥቅልል ብዬ ተኛሁ።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
"ህያብ ያለፈ ታሪክሽ ምንም ይሁን ምን አንቺን ከማፍቀር ሊያቆመኝ አይችልም። የኔ ቆንጆ የፍቅር ጓደኛዬ ትሆኛለሽ?"
"ዮኒ.." ተርበተበትኩ... ቢኒን ዞር ብዬ ሳየው ፈገግ ብሎ እያዬን ነው። ፈገግታው ውስጥ ሁሉም ነገር ሰላም ነው የሚል መልዕክት ያነበብኩ መሰለኝ••• አበባውን ተቀበልኩ
ከዮኒ ጋር ህልም የሚመስሉ ሁለት ሳምንታትን አሳለፍን። ሁሉም ነገር በጣም ደስ የሚል ነበር እያንዳንዷን ቀን ደስ በሚል ሁኔታ አሳለፍናት።
ጎንደርን ለቆ ወደ አዲስ አበባ የሚሄድበት ቀን ደረሰ እኔና ቢን ቀድመን ለመሰናበት አገኘነው።
ካፌ ተገናኝተን ሞቅ ያለ ወሬ እያወራን በመሀል ቢኒ
"ይህን ሁሉ ጊዜ አስለፍተሀት አንድ ወርም ሳይቆይ ልትሄድ ነው?" አለው።
"በልፋት እንኳን ከኔ የበለጠ የለፋች አይመስለኝም ሀሀሀሀ ስቀልድ ነው። ይሄን የመሰለ ፍቅር ትቼ መሄዴ ሳያስከፋኝ ቀርቶ መሰለህ በእርግጥ መጀመሪያ ወድጄና ፈቅጄ እንደውም በጣም ፈልጌው ነበር ዝውውር የጠየኩት" ያልሰማሁት አዲስ ነገር ሆነብኝ
"አንተ ጠይቀህ ነው እንዴ የተዘዋወርከው" ግርም ብሎኝ ጠየኩት
"አዎ ለዚህ ዝውውር እስከ ጥግ ለፍቻለሁ አሁን ግን አልፈልገውም ነበር ግን ምንም ማድረግ አልችልም" እዝን ብሎ አንገቱን ደፋ
"ለምን ነበር ዝውውሩን የጠየከው" ቢኒ ጣልቃ ገባ
"በሷ ምክንያት ነዋ" እጄን በእጁ እያጠላለፈ "ያን ሁሉ ነገር ሰማሁ ምንም ብሰማ እንኳን ላንቺ ያለኝ ፍቅር ሊቀንስ አልቻለም ጭራሽ የማላውቀው ስበት ወዳንቺ ይገፋኛል። መቋቋም አቃተኝ ስራዬ ላይ ሳይቀር ተፅዕኖ ፈጠረብኝ እናም መሸሽን መረጥኩ እና ዝውውር ጠየኩ"
"የዚህ አመት ትምህርት ሲያልቅ እመጣ አይደል ከእናቴ ውጪ የሚቀበለኝ ሰው አለ ማለት ነው" መሄዱ ሀዘን እንዳይለቅብኝ መልካም መልካም ነገሮችን ለማውራትና ለማሰብ ሞከርኩ
"እስከዛው አደራ የምለው ላንተ ነው ቢኒያም.... ናፍቆት ናፍቆት እያለች ትምህርት ላይ እንዳትዘናጋ ደግሞ በስልክም እናወራለን" ቢኒ በአንገት ንቅናቄ እሽታውን ገለፀ።
ፍቅሬን ሞቅ ባለ ስንብት ወደ አዲስ አበባ ሸኘነው።
እኔ ልሁን እሱ ይሁን ማን እንደተቀየረ ባይገባኝም ከቢኒ ጋር እንደድሯችን ልንሆን አልቻልንም ሳገኘው ሳወራው የሆነ ክፍተት እንዳለ ይሰማኛል። መጥፎ ስሜቶች አብረውኝ እንዲቆዩ አልፋግም እሱን ለማውራት ወሰንኩ
"ቢን ግን የተፈጠረ ችግር አለ ማለቴ ምንም እንደድሮው ልንሆን አልቻልንም እኮ ያጠፋሁት ጥፋት አለ እንዴ"
"ኖ ህያብ ምንም አላጠፋሽም እኔ ነኝ በራሴ ችግር ምክንያት ነው አንቺም ለይ ተፅዕኖ እንደፈጠረ አላወኩም.... "
"እና ችግሩን ንገራታ መፍትሄው እኮ በሷ እጅ ነው" የቢኒ ጓደኛ ሀብታሙ ከየት መጣ ሳይባል አጠገባችን ተገኝቷል
"እየውልሽ ህያብ ቢኒ ባንቺ ምክንያት ሀገ..." ንግግሩን ሳይጨርስ የቢኒ እጅ አፉ ላይ አረፈ እና እንቅ አድርጎ ያዘው ትንሽ ከታገሉ በኋላ ለቀቀው
"ባለፈው እንደነገርኩህ ነው ወይ ንገራት ካለዛ እኔ እነግራታለሁ"
" ቢኒ ምንድነው ማወቅ ያለብኝ ነገር አለ" ቢኒ ግራ ገብቶት አንዴ እሱን አንዴ እኔን ያያል።
"አቦ ዝም ብለህ እኮ ነው የምታካብደው" ሀብታሙ በንዴት እየተወናጨፈ ትቶን ሄደ
"ቢን ንገረኝ ምንድነው ከኔ የምትደብቀው ነገር አለ እንዴ"
"አይ ህያብ ለመደበቅ አይደለም እነግርሻለሁ ምን መሰለሽ ግን.... እ...እ....እ ማለቴ እኔ ካንቺ..... ማለቴ ....አንቺን.... "
እኔ ቢኒያም ነኝ ልተርክላቹ
ከመጀመሪያ ጀምሮ ምን እንደተፈጠረ ልንገራችሁ። ህያብን አፈቅራታለሁ አጠገቤ እያለች የማንም ሳትሆን በየቀኑ አብሪያት ስሆን ስንተቃቀፍ ስናወራ አብረን ስንበላና ስንጠጣ ጭንቅላቴ የሚያስበው ጓደኛዬ እንደሆነች ቢሆንም ይህ ልቤ ግን ሁሉን ነገር ፍቅር ብሎ ይወስደው ነበር። ሁሉም ነገር የገባኝ ህያብን በሌላ ሰው እቅፍ ውስጥ ሳያት ነው። መቋቋም አቃተኝ
ከዮኒ ጋር ካወራን በኋላ እሷ ያለምንም ጥርጥር የሱ እንደምትሆን አመንኩ በዛው ልክ ደግሞ ህያብን ላጣት እንደሆነ እና መቼም የኔ እንደማትሆን ተረዳሁ.... አለ አይደል በቃ ሳስብ የኖርኩት የዮኒ ብልግና የሆነ ቀን አንገሽግሿት እሱን መፈለጓን ለማቆም የምትወስን..... ከዛ የኔ የምትሆንበት ሰፊ እድል.....
በነዛ ሁሉ ጊዜያቶች ለራሴ ስነግረው የነበረው ህያብ መቼም ቢሆን ከዛ ባለጌ ዮኒ ጋር ልትሆን እንደማትችል እና የኔ እና የኔ ብቻ እንደምትሆን ነበር። ሁኔታዎች ግን ባላሰብኩት መንገድ ድብልቅልቃቸው ወጣ ህያብን በሌላ ሰው እቅፍ ውስጥ ላያት ሆነ።
ለዶርም ጓደኞቼ ህያብም ሆነ ማንም ቢጠይቃቸው ቤተሰብ ጋ እንደሄድኩ እንዲነግሩ አስጠንቅቄ ከሀብታሙ ጋር አዲስ አበባ አክስቱ ቤት ሄድን። ሀብታሙ ከስር ከመሰረቱ ለሷ ያለኝን ፍቅር ያውቃል እንድቀርባትም ያደፋፈረኝ እሱ ነበር ለዛም ነው ብቻዬን ልሂድ ስለው አይሆንም ብሎኝ አክስቱ ጋር በነፃነት መሆን እንደምንችል አሳምኖኝ አብሮኝ የመጣው
ለቀናት ጠጣሁ ሰከርኩ በእብደት አለም ውስጥ ዋዠኩ። መርጋጋት የሚባለው ነገር ከኔ በእጥፍ እራቀ። ሁኔታዬ ያሳሰበው ሀብትሽ ከቀናት በኋላ መጠጥ ከሚባል ቦታ እንዳልደርስ በግድ ከለከለኝ
ወደምጠጣበት ቦታ ለመሄድ ወንበር ላይ ቁጭ ብዬ ጫማዬን እያሰርኩ ፊት ለፊቴ መጥቶ ቆመና "ምን እየሆንክ ነው በዚህ ሁኔታህ ህያብን የምታገኛት ይመስልሀል። ቢኒያም እንደዚህ እየሆነ መሆኑን የምታውቅ መሰለህ.... እሷማ የምታውቀው ቢኒ እንደታላቅ ወንድም የምታየው ጓደኛዋ እንደሆነ ነው። ንገረኝ እስኪ በማን ላይ ነው የተናደድከው ህያብ ላይ ነው?"
"አይደለም" አልኩት አንገቴን እንደደፋሁ
"በፍቅር ነው?"
"አይደለም እሷን በማፍቀሬማ ደስተኛ ነኝ"
"በራስህ ነው?"
"አዎ ምክንያቱም እስከዛሬ ያመንኩበት ሁሉ ገደል ገባ"
"ይህ እንዳይሆን ማድረግ የምትችለው ነገር ነበር?"
"አላውቅም ምን ላደርግ እችላለሁ መጀመሪያ ነግሪያት ቢሆን የምትወደው ጓደኛዋ ለመሆን አልችልም ነበር። መሀል ላይ ደግሞ ያመንኩት የሱ ነገር ስልችቷት እኔን እንደምታይ ነበር። አሁን ደግሞ ረፍዷል እና በራሴ የትኛውን ነገር አላደረክም ብዬ ልናደድበት?"
"ጥያቄዬን በጥያቄ ሳይሆን በቀጥታ መልስልኝ በራስህ ነው የተናደድከው?"
"አይደለም" አልኩት
"በዮኒ ነው?"
"አይደለም"?
" እና በማን ነው"?
"አላውቅም" አልኩት እውነት ግን በማን ነው የተናደድኩት
"እሺ ለምንድነው እንደዚ እየሆንክ ያለኸው"
"ትቀልዳለህ እንዴ ህያብ የኔ ስለማትሆን ነዋ! በናትህ አሁን መጠጣት ነው የምፈልገው" አልኩት ወሬውን ጨርሶ ዞር እንዲልልኝ በማሰብ
"እንደዚህ መሆንህ ህያብን ያንተ እንድትሆን ያደርጋታል?"
"አያደርጋትም" ከፊት ለፊቴ ዞር አለና ከኮመዲኖ ላይ ቁልፍ እነሳ ከዛ ቀጥታ ወደበሩ አመራ እና ቁልፉን እያሳየኝ
"ስለዚህ በማን እንደተናደድክ አታውቅም ግን ምስኪኑን ጨጓራህን በመጠጥ እያነደድከው ነው ቢያንስ ለጨጓራህ በጠዋት እየተነሳሁ እስከማታ በመጠጥ የማነድህ በዚህ ሰው ተናድጄ ነው ብለህ አንድ ምክንያት ንገረው። ህያብ ደግሞ ከእጅህ ወጥታለች ስለዚህ ሁኔታዎችን አምነህ ተቀበል ወይም ያንተ የምትሆን ከሆነ ያንን ጊዜ ጠብቅ.... ወደራስህ ተመልሰህ ጠብቀኝ ምግብ ይዤ እመጣለሁ" በሩን ቆልፎብኝ ሄደ
ያለሁበት አንድ ክፍል ቤት ሌላ መውጫ የለውም ከተቀመጥኩበት ተነሳሁና አልጋ ላይ ወጥቼ ጥቅልል ብዬ ተኛሁ።
👍96❤11👏4🔥2🤩1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹ፀባይ ይኑርሻ..››እያለ ወደእሷ ተጠጋና የሆኑ አንድ ሶስት ቁልፎችን ጫን ጫን ሲያደርጋቸው የለበሰችው ልበስ በመፈታታት ወለሉ ላይ ዝርግፍ ብሎ ወደቀ…እርቃኗን ቀረች፡፡
‹‹እንዴ..!!!››በድንጋጤ በርግጋ የእጇን መዳፎች በማነባር ቶሎ ብላ ብልቷ ላይ ከደነችው--ለካ መለመላዋን ነው ይዟት የመጣው…..ዘግይቶ ነው ይሄን የተረዳችው፡፡
‹‹ልቀቂው ….በጣም እኮ ነው የምታምሪው››
‹‹ሂድ እዛ…ሌላ ቀለል ያለ ሚለበስ ነገር የለህም..?››
‹‹የለኝም…››
ቶሎ ብላ አልጋ ላይ ወጣቸና አንሶላ የመሰለውን ጨርቅ ይሁን ልስልስ በረት ያለየችውን ልብስ ገልጣ ገባች
‹‹እኔም አብሬሽ ልተኛ…?››
በመለማመጥ ጠየቃት…
‹‹ከውስጥ ሳትገባ..ከላይ ከሆነ ተኛ››
እሱ ‹‹እሺ ››ብሎ የሜትር ያህል ርቀት በማሀላቸው ትቶ እንዳለችው ከላይ ተኛ
‹‹ምን እያደረግኩ ነው..?እስቲ አንድ ሴት ለዛውም ልጃገረድ ነኝ ብላ በአካባቢዋ ባሉ ወጣቶች ላይ ጉራዋን የምትነዛ እንዴት ለመጀመሪያ ቀን የመጣችበት ለዛውም በጥልቀት እኳን የማታውቀው የወንድ ቤት ውስጥ ዘላ ከመግባቷ አልጋ ላይ ትወጣለች…ይሄ ቅብጠት ነው ጅልነት….?ወይኔ ይሄ ግራ አጋቢ ፍጡር ምን አስነክቶኛል….?››ስትል አጉረመረመች፡፡
ደግሞ እሺ አልጋ ላይ መውጣቷ ሳያንስ እሱም ከጎኗ እንዲተኛ መፍቀዷ የዋህነትቷ ውጤት እንደሆነ እና ቆይቶ የሚያፀፅት ስህተት እንደሚያሰራ እንዲሁ ታወቃት….?
‹‹በጣም ቆንጆ እኮ ነህ….?ቆንጆ ና የምትገርም ፍጡር ››ይህን የተናገረችው እሷ እሯሷ መሆኗን ማመን አልቻለችም… ‹‹በቃ ለይቶልኛል…››አለች በውስጧ፡፡
‹‹አፍቅረሺኛል ማለት ነው.?›› እሱ ደግሞ ጭራሽ የዲፕሎማሲ ቃና በሌለው ጥሬ ንግግሩ ፀፀቷን አናረው፡፡
‹‹ኸረ በፍጽም… ባፈቅርህስ ምን ታደርግልኛለህ..?ሰው አይደለህ አላገባህ…››የገዛ ልቧ ግን ሰው ሆነ ሌላ ፍጡር ዋናው ማፈቀርሽ ነው እያላት ነው…
‹‹ሰው ባልሆንስ ከተመቸውሽ ብታገቢኝ ምን አለበት.?››
‹‹ምንም የለበትም …ግን ያው ባገባህስ ምን ዋጋ አለው ብዬ ነው.?››
‹‹እንዴት.? ››
‹‹እንትንህ እኮ ባቄላ ነው የምታህለው..ለእኔ ተፈጥሮ የሚስማማ ሆኖ አይደለም የተፈጠረው……እና ምንም ማድረግ አልችልም››
‹‹እንዴ ግን እንደዚህ እየተናገርኩ ያለሁት እኔው ነኝ…››ስትል የራሷን ባህሪ ባለማመን ጠየቀች..ለነገሩ እውነቷን ነው በጊዜው ተደብቆ የሚያዳምጣት ሰው ቢኖር እኮ በቃ የአራት አምስት አመት አሪፍ ልምድ ያለት ባልቴት ነው የምትመስለው…በአዲሱ የባህሪ ለውጧ እራሷን ከፉኛ ታዘበች፡፡
‹‹እና ታዲያ ወደውስጥ እንዳልገባ ለምን ከለከልሺኝ.?››
‹‹ዝም ብዬ ነዋ››
‹‹ዝም ብለሽ ከሆነማ ልግባ ..››ከእሷ አንደበት የሚወጣውን መልስ ሳይጠብቅ ተስፈንጥሮ ከውስጥ ገባ…ግን ሰውነቱ ከሰውነቷ ለማስጠጋት አልደፈረም ….ድርጊቱን ችላ አለችና…
‹‹ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ.?››ስትል የሁለቱንም ትኩረት ወደሌላ አቅጣጫ ዘወረችው፡፡
‹‹ጠይቂኝ››
‹‹እዚህ ማለት ከራስህ ወገን ሚስት አላገባህም.?››
‹‹እኛ ጋር ማግባት የሚባል ነገር የለም..ቃሉም አይታወቅም….››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹እና ታዲያ እንዴት ነው የምትኖሩት . .?እንዴትስ ነው የምትዋለድት.?››
‹‹የምንኖረው ያው ሁለታችንም እራሳችንን ችለን ነው..ሴቷም ሆነች ወንድ ራሳቸውን ችለው ነው የሚኖሩት…ግንኙነትም ለመፈፀም በሁለቱ ፃታዎች መሀከል በእለቱ ያለ ስሜት ብቻ ነው ወሳኙ…
ለመውለድ ግን እዚህ እንደእናንተ በአጋጣሚ ወይም ሁሉም እንደፈለገው አይደለም የሚወልደው….
‹‹እና እንዴት ነው.?››ጠየቀችው ገርሟት
‹‹በአመት ስንት አዲስ ልጅ መወለድ አለበት.? የሚለውን የሚወስኑት የማህበረሰቡ የበላይ ጠባቂዎቹ ናቸው፡፡በተወሰነው ቁጥር መሰረት መውለድ የሚፈልጉ ሴቶች ይወዳደራሉ…..ከዛ እድሉ ቀንቶቸው የተመረጡት ሴቶች ከተመረጡ ወንዶች ጋር ግንኙነት በመፈፀም አርግዘው ይወልዳሉ..
የተወለደውን ማሳደጉ የሁሉም ኃላፊነት ነው ..በእናት እና ልጅ መካከል ያለው ቁርኝት እንደእናንተ አይደልም …እናት ትወልዳለች ከዛ ታስረክባለች..መውለድ ማለት ለማህበረሰቡ የተለየ አስዋፅኦ ማበርከት ማለት ነው እንጂ እናትም ሆነች አባት በሚወለደው አዲስ ልጅ ላይ የተለየ ኃላፊነትም ሆነ የተለየ መብት የላቸውም…››
‹‹ይገርማል…..ግን ደስ አይልም ..ልክ እንደ ማሽን ነው የምታስቡት ››
‹‹ብለሽ ነው ?ታዲያ እንደእናንተ የሰው ልጆች በስሜት መሞላትና በሆነ ባልሆነው መሳቀቅና ማልቀስ ይሻላል?
‹‹ቆይ ግን ይሄ ቦታ የት ነው ሚገኘው ?ምድር ላይ ነው?››አዲስ ርዕስ ከፈተች፡፡
አይ ከምድር በጣም ቅርብ የሆነ በመጠን ግን ከመሬት በጣም የሚያንስ ራሱን የቻለ ፕላኔት ነው፡፡
‹‹ስሙ ምን ይባላል?››
‹‹እኛ ኬድሮን እንለዋለን…የዕውቀት ምድር ማለት ነው ››
‹‹በእኛ በሰው ልጆችስ ስያሜው ምንድን ነው?››
‹‹አይ በሰው ልጆች አይታወቅም…››
‹‹እንዴት አይታወቅም ?ከምድር በጣም ቅርብ ነው አላልክም?››
‹‹ነው፡፡ ግን እራሳችንን ከጥቃትና ከውድመት ለመታደግ ባለን ለዘመናት በዳበረ እውቀትና ጥበብ አማካይነት ለእይታ እንዲሰወር አድርገነዋል..ለክ ቅድም ስትመጪ ከተማው ሙሉ በሙሉ ከእይታሽ ተሰውሮ እንደነበረ ሁሉ የእኛ ፕላኔት ምድር ላይም ሆነ ማርስ ላይ ሆነሽ እስከአሁን በተፈጠሩት በማንኛውም መሰሪያ ሊታይ የማይችል የተሰወረ እንዲሆን አድርገናል፡፡የሰው ልጅ ምደር ብቸኛዋ ህይወት የምታኖር ፕላኔት እንደሆነች ነው የሚያውቀው...ግን ደግሞ እኛ የምድር አፍንጫ ስር በማርስና በመሬት መካከል ተሰንቅረን ለአመታት በስኬት እየኖርን ነው፡፡ደግሞም አስፈላጊ ሲሆን ምድር ገብተን ብዙ ቡዙ ተልኮዎችን ፈፅመን ኮሽ ሳይል እንመለሳለን፡፡››
‹‹ወደፊትስ…?.››
‹‹ወደፊት እንግዲህ አናውቅም…በቴክኖለሎጂ ፍጥነት የሰው ልጅ መቼም ከእኛ የተሻለ መራቀቅ ላይ ይደርሳሉ ብዬ አላስብም››
‹‹ግን የእኛ ምድር ትለያለች አይደል?››ስትል ጠየቀችው፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹ፀባይ ይኑርሻ..››እያለ ወደእሷ ተጠጋና የሆኑ አንድ ሶስት ቁልፎችን ጫን ጫን ሲያደርጋቸው የለበሰችው ልበስ በመፈታታት ወለሉ ላይ ዝርግፍ ብሎ ወደቀ…እርቃኗን ቀረች፡፡
‹‹እንዴ..!!!››በድንጋጤ በርግጋ የእጇን መዳፎች በማነባር ቶሎ ብላ ብልቷ ላይ ከደነችው--ለካ መለመላዋን ነው ይዟት የመጣው…..ዘግይቶ ነው ይሄን የተረዳችው፡፡
‹‹ልቀቂው ….በጣም እኮ ነው የምታምሪው››
‹‹ሂድ እዛ…ሌላ ቀለል ያለ ሚለበስ ነገር የለህም..?››
‹‹የለኝም…››
ቶሎ ብላ አልጋ ላይ ወጣቸና አንሶላ የመሰለውን ጨርቅ ይሁን ልስልስ በረት ያለየችውን ልብስ ገልጣ ገባች
‹‹እኔም አብሬሽ ልተኛ…?››
በመለማመጥ ጠየቃት…
‹‹ከውስጥ ሳትገባ..ከላይ ከሆነ ተኛ››
እሱ ‹‹እሺ ››ብሎ የሜትር ያህል ርቀት በማሀላቸው ትቶ እንዳለችው ከላይ ተኛ
‹‹ምን እያደረግኩ ነው..?እስቲ አንድ ሴት ለዛውም ልጃገረድ ነኝ ብላ በአካባቢዋ ባሉ ወጣቶች ላይ ጉራዋን የምትነዛ እንዴት ለመጀመሪያ ቀን የመጣችበት ለዛውም በጥልቀት እኳን የማታውቀው የወንድ ቤት ውስጥ ዘላ ከመግባቷ አልጋ ላይ ትወጣለች…ይሄ ቅብጠት ነው ጅልነት….?ወይኔ ይሄ ግራ አጋቢ ፍጡር ምን አስነክቶኛል….?››ስትል አጉረመረመች፡፡
ደግሞ እሺ አልጋ ላይ መውጣቷ ሳያንስ እሱም ከጎኗ እንዲተኛ መፍቀዷ የዋህነትቷ ውጤት እንደሆነ እና ቆይቶ የሚያፀፅት ስህተት እንደሚያሰራ እንዲሁ ታወቃት….?
‹‹በጣም ቆንጆ እኮ ነህ….?ቆንጆ ና የምትገርም ፍጡር ››ይህን የተናገረችው እሷ እሯሷ መሆኗን ማመን አልቻለችም… ‹‹በቃ ለይቶልኛል…››አለች በውስጧ፡፡
‹‹አፍቅረሺኛል ማለት ነው.?›› እሱ ደግሞ ጭራሽ የዲፕሎማሲ ቃና በሌለው ጥሬ ንግግሩ ፀፀቷን አናረው፡፡
‹‹ኸረ በፍጽም… ባፈቅርህስ ምን ታደርግልኛለህ..?ሰው አይደለህ አላገባህ…››የገዛ ልቧ ግን ሰው ሆነ ሌላ ፍጡር ዋናው ማፈቀርሽ ነው እያላት ነው…
‹‹ሰው ባልሆንስ ከተመቸውሽ ብታገቢኝ ምን አለበት.?››
‹‹ምንም የለበትም …ግን ያው ባገባህስ ምን ዋጋ አለው ብዬ ነው.?››
‹‹እንዴት.? ››
‹‹እንትንህ እኮ ባቄላ ነው የምታህለው..ለእኔ ተፈጥሮ የሚስማማ ሆኖ አይደለም የተፈጠረው……እና ምንም ማድረግ አልችልም››
‹‹እንዴ ግን እንደዚህ እየተናገርኩ ያለሁት እኔው ነኝ…››ስትል የራሷን ባህሪ ባለማመን ጠየቀች..ለነገሩ እውነቷን ነው በጊዜው ተደብቆ የሚያዳምጣት ሰው ቢኖር እኮ በቃ የአራት አምስት አመት አሪፍ ልምድ ያለት ባልቴት ነው የምትመስለው…በአዲሱ የባህሪ ለውጧ እራሷን ከፉኛ ታዘበች፡፡
‹‹እና ታዲያ ወደውስጥ እንዳልገባ ለምን ከለከልሺኝ.?››
‹‹ዝም ብዬ ነዋ››
‹‹ዝም ብለሽ ከሆነማ ልግባ ..››ከእሷ አንደበት የሚወጣውን መልስ ሳይጠብቅ ተስፈንጥሮ ከውስጥ ገባ…ግን ሰውነቱ ከሰውነቷ ለማስጠጋት አልደፈረም ….ድርጊቱን ችላ አለችና…
‹‹ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ.?››ስትል የሁለቱንም ትኩረት ወደሌላ አቅጣጫ ዘወረችው፡፡
‹‹ጠይቂኝ››
‹‹እዚህ ማለት ከራስህ ወገን ሚስት አላገባህም.?››
‹‹እኛ ጋር ማግባት የሚባል ነገር የለም..ቃሉም አይታወቅም….››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹እና ታዲያ እንዴት ነው የምትኖሩት . .?እንዴትስ ነው የምትዋለድት.?››
‹‹የምንኖረው ያው ሁለታችንም እራሳችንን ችለን ነው..ሴቷም ሆነች ወንድ ራሳቸውን ችለው ነው የሚኖሩት…ግንኙነትም ለመፈፀም በሁለቱ ፃታዎች መሀከል በእለቱ ያለ ስሜት ብቻ ነው ወሳኙ…
ለመውለድ ግን እዚህ እንደእናንተ በአጋጣሚ ወይም ሁሉም እንደፈለገው አይደለም የሚወልደው….
‹‹እና እንዴት ነው.?››ጠየቀችው ገርሟት
‹‹በአመት ስንት አዲስ ልጅ መወለድ አለበት.? የሚለውን የሚወስኑት የማህበረሰቡ የበላይ ጠባቂዎቹ ናቸው፡፡በተወሰነው ቁጥር መሰረት መውለድ የሚፈልጉ ሴቶች ይወዳደራሉ…..ከዛ እድሉ ቀንቶቸው የተመረጡት ሴቶች ከተመረጡ ወንዶች ጋር ግንኙነት በመፈፀም አርግዘው ይወልዳሉ..
የተወለደውን ማሳደጉ የሁሉም ኃላፊነት ነው ..በእናት እና ልጅ መካከል ያለው ቁርኝት እንደእናንተ አይደልም …እናት ትወልዳለች ከዛ ታስረክባለች..መውለድ ማለት ለማህበረሰቡ የተለየ አስዋፅኦ ማበርከት ማለት ነው እንጂ እናትም ሆነች አባት በሚወለደው አዲስ ልጅ ላይ የተለየ ኃላፊነትም ሆነ የተለየ መብት የላቸውም…››
‹‹ይገርማል…..ግን ደስ አይልም ..ልክ እንደ ማሽን ነው የምታስቡት ››
‹‹ብለሽ ነው ?ታዲያ እንደእናንተ የሰው ልጆች በስሜት መሞላትና በሆነ ባልሆነው መሳቀቅና ማልቀስ ይሻላል?
‹‹ቆይ ግን ይሄ ቦታ የት ነው ሚገኘው ?ምድር ላይ ነው?››አዲስ ርዕስ ከፈተች፡፡
አይ ከምድር በጣም ቅርብ የሆነ በመጠን ግን ከመሬት በጣም የሚያንስ ራሱን የቻለ ፕላኔት ነው፡፡
‹‹ስሙ ምን ይባላል?››
‹‹እኛ ኬድሮን እንለዋለን…የዕውቀት ምድር ማለት ነው ››
‹‹በእኛ በሰው ልጆችስ ስያሜው ምንድን ነው?››
‹‹አይ በሰው ልጆች አይታወቅም…››
‹‹እንዴት አይታወቅም ?ከምድር በጣም ቅርብ ነው አላልክም?››
‹‹ነው፡፡ ግን እራሳችንን ከጥቃትና ከውድመት ለመታደግ ባለን ለዘመናት በዳበረ እውቀትና ጥበብ አማካይነት ለእይታ እንዲሰወር አድርገነዋል..ለክ ቅድም ስትመጪ ከተማው ሙሉ በሙሉ ከእይታሽ ተሰውሮ እንደነበረ ሁሉ የእኛ ፕላኔት ምድር ላይም ሆነ ማርስ ላይ ሆነሽ እስከአሁን በተፈጠሩት በማንኛውም መሰሪያ ሊታይ የማይችል የተሰወረ እንዲሆን አድርገናል፡፡የሰው ልጅ ምደር ብቸኛዋ ህይወት የምታኖር ፕላኔት እንደሆነች ነው የሚያውቀው...ግን ደግሞ እኛ የምድር አፍንጫ ስር በማርስና በመሬት መካከል ተሰንቅረን ለአመታት በስኬት እየኖርን ነው፡፡ደግሞም አስፈላጊ ሲሆን ምድር ገብተን ብዙ ቡዙ ተልኮዎችን ፈፅመን ኮሽ ሳይል እንመለሳለን፡፡››
‹‹ወደፊትስ…?.››
‹‹ወደፊት እንግዲህ አናውቅም…በቴክኖለሎጂ ፍጥነት የሰው ልጅ መቼም ከእኛ የተሻለ መራቀቅ ላይ ይደርሳሉ ብዬ አላስብም››
‹‹ግን የእኛ ምድር ትለያለች አይደል?››ስትል ጠየቀችው፡፡
✨ይቀጥላል✨
👍153😱15❤12😁9🤔4🥰1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
...በሱስ እና በወንጀል ወደ ተጨማለቀ የህይወት ማጥ መግባት ቁልቁለትን ተንደርድሮ የመውረድ ያህል ቀላልና አዝናኝ መሰል ነው ከአዙሪቱ መውጣት ግን ቀጥ ያለ ሰማይ ጠቀስ አቀበትን የመውጣት ያህል ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ ነው፡፡ ቢሆንም አሸናፊዎች በጥረታቸው ያሳኩታል፡፡
የዛሬው ቀን ለትንግርት ልዩ ነው፡፡ የክርስቲያኖችን ገና.. የሙስሊሞችን መውሊድ... የደርግን መስከረም 2፣ የወያኔን ግንቦት 2ዐ፣የኢትዮጵያውያንን እንቁጣጣሽ ዓይነት ነው፡፡ ሦስት ዓመት ከተንቦጫረቀችበ የሕይወት አዘቅት ወጥታ ሌላ አዲስ ምዕራፍ ለመጀመር የምትንደረደርበት የዳግም ውልደት ቀን፡፡ ይህንን የመሸጋገሪያ ቀን ደግሞ በልዩ ሁኔታ ልታከብረው ወስናለች፡፡ሳሪስ የሚገኘዉ ባለ ሦስት ክፍል ቤቷ በልዩ ሁኔታ አምሯል፡፡ ይሄንን ቤት ውጭ የሚገኙት ሁለት
ወንድሞቿና አንድ እህቷ አዋጥተው ነው የገዙላት፡፡ እናትና አባቷ ሳይቀሩ የሚኖሩት ካናዳ ነው፡፡ ከቤተሠቡ ውስጥ ብቸኛዋ አገር ቤት ኗሪ እሷ ነች፡፡ ብዙ ጊዜ ኢትዮጵያን ለቃ እነሱ ጋር እንድትመጣ ጨቅጭቀዋታል፤ ለምነዋታልም፡፡ ግን አልተሳካላቸውም፡፡ ይሄ ሁኔታ ደግሞ አሜሪካን እንደምድራዊ ገነት በሚያስብና በእውኑም በህልሙም ምድሪቷን ለመርገጥ በሚኳትን ሸፋታ ልብ ካለው ትውልድ መከከል ተፈጥራ አብራ እየኖረች የተለየ እምነት መያዟ ከእሷ በስተቀር ሰሚውን ሁሉ ያስገርማል ፡፡
‹‹ይህቺ መስኮት እንደሌለው ቤት በመከራ የምታፍን ነጻነት አልባ ሀገር ....››
‹‹ይህቺ ጥቂቶች ድራማ የሚሰሩባት..ብዙሀኑ በፍዘት የሚመለከቱባት ሀገር.... >>
‹‹ይህቺ በተረት የተሞላች...የምንቸገረኝ ሀገር.....>>
‹‹ይህቺ ማማት እንጂ ..አብሮ መስራት የማይሳካላቸው ጭንጋፍ ልጆች የሞሉባት ሀገር...>>
‹‹ይህቺ ባለውለታዎቾን የማታከብር... ባንዳዎችን የምትሾም የሽፍቶች ሀገር....››
‹‹ይህቺ ነበርኝ እንጂ አለኝን የማታውቅ ሀገር....>>
‹‹ይህቺ ዘረኞች የወረሯት...የጎጠኞች ሀገር...>>
‹‹ይህቺ ......>>በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ የቅርቧ ሰዎች ወደ ስደቱ ዓለም እንድትበር ለማበረታቻ የተሰነዘረላት ‹‹..ብትሄጂ ተገላገልሽ እንጂ ምንም አታጪም›› የሚለውን ሀሳብ ለማስረገጥ ከተነገሯት ንግግሮች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ያሉት ነገር ሁሉ ትክክል ቢሆንም ባይሆንም…ለእሷ ግን ከሀገር ለቆ ለመሰደድ ምክንያት አይሆናትም..… እሷ በቃ የሀገሯ ቋሚ ልጅ ነች፡፡ሀገሯ ለእሷ ተመቸቻትም ጐረበጠቻትም በቃ ሀገሯ ነች፤ልትከዳትም.. ልትሸሻትም አትሻም…. ‹‹ሀገሬ ብቻ እኮ አይደለችም ለእኔ ያልተመቸችኝ ..እኔስ ለሀገሬ መች ተመቸዋት?›› የሚል አባባል አላት፡፡በዚህ ምክንያት ዛሬም በውጣ ውረድ ህይወት እየተርገበገበችም ቢሆን ይሄው እዚሁ አለች፡፡ የሀገሯ እንብርት የሆነችው አዲስአበባ ላይ፡፡ የዛሬውን ልዩ ቀኗን ከወዳጆቿ ጋር ልታከብር እየተዘጋጀች፡፡
ሳሎኑ መሀከል ባለ ጠረጴዛ ላይ ሦስት ነጫጭ ሻማዎች ሳይለኮሱ ይታያሉ፣ደብዛዛ ሰማያዊ ቀለም የተቀባው የሳሎኑ ግድግዳ መስኮቱ ላይ ከተዘረጋው መጋረጃ ጋር ስምምነት ፈጥሯል፣ ሻማዎቹ የተቀመጡበትን ጠረጴዛ ስድስት በሚሆኑ በምርጥ ባለሙያ መሠራታቸው በሚያስታውቁ ደረቅ ወንበሮች ዙሪያውን ተከቧል፤በአንድ ጥግ ማዕዘን ላይ መካከለኛ መጠን ኖሮት ሠማያዊ ጨርቅ በለበሰ ጠረጴዛ ላይ የተለያዩ የወጥ ዓይነቶች የያዙ ሣህኖች.... የተቆረጠ እንጀራ ይዞ በነጭ ዳንቴል የተሸፈነ ትሪ.... ኩኪሶችና ብስኩቶች ሲገኙ፣ከአንድ ጥግ ደግሞ የተለያዩ መጠጦች የያዙ ጠርሙሶች ተደርድረዋል፡፡ለግብዣው የተጠሩት ሁሴን፣ ሰሎሞንና ሌሎች ሁለት የቡና ቤት ጓደኞቿ ናቸው፡፡ ድግሱ ግን አስር ያህል ሰዎችን ዘና ባለ ሁኔታ የማስተናገድ አቅም አለው፡፡
የሶኒ ምርት ከሆነው ቴፕ ሪከርደር በስሱ የተለቀቀው የአስቴር አወቀ ዘፈን ለቤቱ
ተጨማሪ ድባብ ለግሶታል፡፡ ግንባሯን ቀና አድርጋ የግድግዳ ሠዓቷን ተመለከተች፡፡ ስድስት ሠዓት ሊሞላ አስር ደቂቃ ነው የቀረው፡፡ የእንግዶቹ መምጫ ሰዓት ደርሷል፡፡
ሁለቱ ሴት ጓደኞቿ እቤቷን ቢያውቁትም ሠሎሞንና ሁሴን ግን ፍፁም አያውቁትም፡፡
ቤት እንዳላት እንኳን ያወቁት ከሦስት ቀን በፊት ስለ ዛሬው ቀን ዝግጅት ስትነግራቸው ነበር፡፡
ሁለቱም በአግራሞት ነበር ያፈጠጡባት፡፡እንደመሠሎቿ በምትሠራበት ቡና ቤት ውስጥ ምትኖር ነበር የሚመስላቸው፡፡ ሌላው ይቅር ለዓመታት አንሶላ የተጋፈፋት... ደጋግሞ ጠረን የተጋራት ሁሴን እንኳን ግምት አልነበረውም፡፡ ትንግርት በሌሎች ነገሮች ግልፅ የመሆኗን ያህል የግል ህይወቷን በተመለከተ ለማንም በጣም ድብቅ ነች፡፡
በተሠጣቸው ምልክት ታግዘው በመጀመያ
ቤት የደረሱት ሁሴንና ሠሎሞን ነበሩ፡፡
ሠሎሞን ጥቁር ሱፍ ከነጭ ሸሚዝና ቀይ መደብ ካለው ክራባት ጋር ለብሷል፡፡ አለባበሱ የቦርጩን መጠን አተልቆበታል፡፡ ሁሴን
እንደወትሮው ቀለል ያለ አለባበስ ነው የለበሰው፡፡ ሠማያዊ ጅንስ ሱሪ ነጣ ካለ ሹራብ ጋር ለብሶ ከታች ስኒከር ጫማ ተጫምቷል፡፡ሁለቱም ፊት ለፊታቸው
ለተገተረችው ትንግርት ሠላምታ መስጠት ዘንግተው የቤቱን ዙሪያ ገባ በአግራሞት ይቃኙ ጀመር፡፡የቤቱ ስፋትና ጥራት ብቻ ሳይሆን የትንግርት ከወትሮ የተለየ አለባበስ ጭምርም
ነበር ያፈዘዛቸው፡፡ እሷ የሆነ ገፀ ባህሪ ተላብሳ የምትተውንበት ቲያትር ቤት የገቡ ነው የመሠላቸው፡፡ ተረከዟ ድረስ የሚረዝም..
ባማረ ጥልፍ ያሸበረቀ የአገር ባህል ቀሚስ ለብሳ ነጭ አንገት ልብስ አንገቷ ላይ ጣል አድርጋለች፡፡
ድሮም የፈረስ ጭራ የሚመስለው ፀጉሯ ሹርባ ተሠርቶ ጀርባዋ ላይ ተነጥፏል፡፡
‹‹እውነትም ትንግርት ነሽ›› ሁሴን ነበር ተናጋሪው፡፡ በዝግታ እርምጃ ወደ እሷ ተጠግቶ ደረቱ ላይ ልጥፍ አድርጎ እያቀፋት፡፡
‹‹በዶላር ነበር እንዴ ስትሰሪ የከረምሽው?›› እጁን ለሠላምታ እየዘረጋላት ሠሎሞን እደዛ ያላት፡፡
‹‹አይ..በዩሮ ነው፡፡ ለማንኛውም ቁጭ በሉ፡፡›› በማለት ወደ ወንበሩ መርታ አስቀመጠቻቸው፡፡ በዛው ቅፅበት ሌሎች ተጋባዥ እንግዶቿም እጅ ለእጅ ተያይዘው ገቡ እና ተቀላቀሏቸው፡፡ ጨዋታው ደራ፣ ሳቁ ደመቀ፤ ሁሉም የምርጫቸውን እያነሱ ምሳቸውን ተመገቡ፡፡ ያሻቸውንም የመጠጥ ዓይነት እየመረጡ መጎንጨት ጀመሩ፡፡ ሻማዎቹ ተለኮሱ፡፡ እቤቱ
ደመቀ፡፡ ትንግርት በመሀከል ጨዋታቸውን
አቋረጠቻቸውና በተቀመጠችበት ሆና ንግግሯን ጀመረች፡፡ እንግዶቿም በፀጥታ ያዳምጧት ጀመር፡፡
‹‹ጥሪዬን አክብራችሁ እቤቴ ስለመጣችሁ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ ምክንያቱም ይህቺ ቀን ለእኔ ልዩ ነች፡፡ ልክ የዛሬ አምስት ዓመት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዲግሪ ስመረቅ የተሠማኝን ዓይነት የደስታ ስሜት ነው ዛሬም እየተሰማኝ ያለው›
‹‹በዲግሪ ስመረቅ ...?›› ሠሎሞን ነበር ፡፡
‹‹አዎ ምነው በሶስዮሎጂ ተመርቄያለሁ፡፡ ያንን ያህል እኮ ትልቅ ነገር አይደለም፡፡ እና ወደ ነገሬ ልመለስና ባለፉት ሦስት ዓመታት የቡና ቤት ሕይወቴ ሁለተኛ ዲግሪዬን ስማር እንደቆየሁና ዛሬ በእናንተ ፊት የምረቃ በዓሌን እያከበርኩ እንዳለሁ አርጋችሁ ቁጠሩት፡፡ እውቅና የሚሠጠኝ አካል ባይኖርምC ብዙ ተዓምር የሚያሠኙ የሕይወት ውጣ ውረዶችን አሳልፌያለሁ፡፡ መዓት ዓይነት ወንዶች
አጋጥመውኛል፡፡ ልምዱ የሌለው ጀማሪ….ያጎበደደ ሽማግሌ… አምስት አስር ልጆች ያሉት ባለትዳር... በስንፈተ ወሲብ የሚሰቃይ ጎልማሳ…ከወሲብ ጥማቱ በቀለሉ የማይረካ ጎረምሳ፣ደግ፣ንፉግ፣ተጫች፣ ዝጋታም፣ተደባዳቢ፣ኧረ ስንቱ…፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
...በሱስ እና በወንጀል ወደ ተጨማለቀ የህይወት ማጥ መግባት ቁልቁለትን ተንደርድሮ የመውረድ ያህል ቀላልና አዝናኝ መሰል ነው ከአዙሪቱ መውጣት ግን ቀጥ ያለ ሰማይ ጠቀስ አቀበትን የመውጣት ያህል ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ ነው፡፡ ቢሆንም አሸናፊዎች በጥረታቸው ያሳኩታል፡፡
የዛሬው ቀን ለትንግርት ልዩ ነው፡፡ የክርስቲያኖችን ገና.. የሙስሊሞችን መውሊድ... የደርግን መስከረም 2፣ የወያኔን ግንቦት 2ዐ፣የኢትዮጵያውያንን እንቁጣጣሽ ዓይነት ነው፡፡ ሦስት ዓመት ከተንቦጫረቀችበ የሕይወት አዘቅት ወጥታ ሌላ አዲስ ምዕራፍ ለመጀመር የምትንደረደርበት የዳግም ውልደት ቀን፡፡ ይህንን የመሸጋገሪያ ቀን ደግሞ በልዩ ሁኔታ ልታከብረው ወስናለች፡፡ሳሪስ የሚገኘዉ ባለ ሦስት ክፍል ቤቷ በልዩ ሁኔታ አምሯል፡፡ ይሄንን ቤት ውጭ የሚገኙት ሁለት
ወንድሞቿና አንድ እህቷ አዋጥተው ነው የገዙላት፡፡ እናትና አባቷ ሳይቀሩ የሚኖሩት ካናዳ ነው፡፡ ከቤተሠቡ ውስጥ ብቸኛዋ አገር ቤት ኗሪ እሷ ነች፡፡ ብዙ ጊዜ ኢትዮጵያን ለቃ እነሱ ጋር እንድትመጣ ጨቅጭቀዋታል፤ ለምነዋታልም፡፡ ግን አልተሳካላቸውም፡፡ ይሄ ሁኔታ ደግሞ አሜሪካን እንደምድራዊ ገነት በሚያስብና በእውኑም በህልሙም ምድሪቷን ለመርገጥ በሚኳትን ሸፋታ ልብ ካለው ትውልድ መከከል ተፈጥራ አብራ እየኖረች የተለየ እምነት መያዟ ከእሷ በስተቀር ሰሚውን ሁሉ ያስገርማል ፡፡
‹‹ይህቺ መስኮት እንደሌለው ቤት በመከራ የምታፍን ነጻነት አልባ ሀገር ....››
‹‹ይህቺ ጥቂቶች ድራማ የሚሰሩባት..ብዙሀኑ በፍዘት የሚመለከቱባት ሀገር.... >>
‹‹ይህቺ በተረት የተሞላች...የምንቸገረኝ ሀገር.....>>
‹‹ይህቺ ማማት እንጂ ..አብሮ መስራት የማይሳካላቸው ጭንጋፍ ልጆች የሞሉባት ሀገር...>>
‹‹ይህቺ ባለውለታዎቾን የማታከብር... ባንዳዎችን የምትሾም የሽፍቶች ሀገር....››
‹‹ይህቺ ነበርኝ እንጂ አለኝን የማታውቅ ሀገር....>>
‹‹ይህቺ ዘረኞች የወረሯት...የጎጠኞች ሀገር...>>
‹‹ይህቺ ......>>በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ የቅርቧ ሰዎች ወደ ስደቱ ዓለም እንድትበር ለማበረታቻ የተሰነዘረላት ‹‹..ብትሄጂ ተገላገልሽ እንጂ ምንም አታጪም›› የሚለውን ሀሳብ ለማስረገጥ ከተነገሯት ንግግሮች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ያሉት ነገር ሁሉ ትክክል ቢሆንም ባይሆንም…ለእሷ ግን ከሀገር ለቆ ለመሰደድ ምክንያት አይሆናትም..… እሷ በቃ የሀገሯ ቋሚ ልጅ ነች፡፡ሀገሯ ለእሷ ተመቸቻትም ጐረበጠቻትም በቃ ሀገሯ ነች፤ልትከዳትም.. ልትሸሻትም አትሻም…. ‹‹ሀገሬ ብቻ እኮ አይደለችም ለእኔ ያልተመቸችኝ ..እኔስ ለሀገሬ መች ተመቸዋት?›› የሚል አባባል አላት፡፡በዚህ ምክንያት ዛሬም በውጣ ውረድ ህይወት እየተርገበገበችም ቢሆን ይሄው እዚሁ አለች፡፡ የሀገሯ እንብርት የሆነችው አዲስአበባ ላይ፡፡ የዛሬውን ልዩ ቀኗን ከወዳጆቿ ጋር ልታከብር እየተዘጋጀች፡፡
ሳሎኑ መሀከል ባለ ጠረጴዛ ላይ ሦስት ነጫጭ ሻማዎች ሳይለኮሱ ይታያሉ፣ደብዛዛ ሰማያዊ ቀለም የተቀባው የሳሎኑ ግድግዳ መስኮቱ ላይ ከተዘረጋው መጋረጃ ጋር ስምምነት ፈጥሯል፣ ሻማዎቹ የተቀመጡበትን ጠረጴዛ ስድስት በሚሆኑ በምርጥ ባለሙያ መሠራታቸው በሚያስታውቁ ደረቅ ወንበሮች ዙሪያውን ተከቧል፤በአንድ ጥግ ማዕዘን ላይ መካከለኛ መጠን ኖሮት ሠማያዊ ጨርቅ በለበሰ ጠረጴዛ ላይ የተለያዩ የወጥ ዓይነቶች የያዙ ሣህኖች.... የተቆረጠ እንጀራ ይዞ በነጭ ዳንቴል የተሸፈነ ትሪ.... ኩኪሶችና ብስኩቶች ሲገኙ፣ከአንድ ጥግ ደግሞ የተለያዩ መጠጦች የያዙ ጠርሙሶች ተደርድረዋል፡፡ለግብዣው የተጠሩት ሁሴን፣ ሰሎሞንና ሌሎች ሁለት የቡና ቤት ጓደኞቿ ናቸው፡፡ ድግሱ ግን አስር ያህል ሰዎችን ዘና ባለ ሁኔታ የማስተናገድ አቅም አለው፡፡
የሶኒ ምርት ከሆነው ቴፕ ሪከርደር በስሱ የተለቀቀው የአስቴር አወቀ ዘፈን ለቤቱ
ተጨማሪ ድባብ ለግሶታል፡፡ ግንባሯን ቀና አድርጋ የግድግዳ ሠዓቷን ተመለከተች፡፡ ስድስት ሠዓት ሊሞላ አስር ደቂቃ ነው የቀረው፡፡ የእንግዶቹ መምጫ ሰዓት ደርሷል፡፡
ሁለቱ ሴት ጓደኞቿ እቤቷን ቢያውቁትም ሠሎሞንና ሁሴን ግን ፍፁም አያውቁትም፡፡
ቤት እንዳላት እንኳን ያወቁት ከሦስት ቀን በፊት ስለ ዛሬው ቀን ዝግጅት ስትነግራቸው ነበር፡፡
ሁለቱም በአግራሞት ነበር ያፈጠጡባት፡፡እንደመሠሎቿ በምትሠራበት ቡና ቤት ውስጥ ምትኖር ነበር የሚመስላቸው፡፡ ሌላው ይቅር ለዓመታት አንሶላ የተጋፈፋት... ደጋግሞ ጠረን የተጋራት ሁሴን እንኳን ግምት አልነበረውም፡፡ ትንግርት በሌሎች ነገሮች ግልፅ የመሆኗን ያህል የግል ህይወቷን በተመለከተ ለማንም በጣም ድብቅ ነች፡፡
በተሠጣቸው ምልክት ታግዘው በመጀመያ
ቤት የደረሱት ሁሴንና ሠሎሞን ነበሩ፡፡
ሠሎሞን ጥቁር ሱፍ ከነጭ ሸሚዝና ቀይ መደብ ካለው ክራባት ጋር ለብሷል፡፡ አለባበሱ የቦርጩን መጠን አተልቆበታል፡፡ ሁሴን
እንደወትሮው ቀለል ያለ አለባበስ ነው የለበሰው፡፡ ሠማያዊ ጅንስ ሱሪ ነጣ ካለ ሹራብ ጋር ለብሶ ከታች ስኒከር ጫማ ተጫምቷል፡፡ሁለቱም ፊት ለፊታቸው
ለተገተረችው ትንግርት ሠላምታ መስጠት ዘንግተው የቤቱን ዙሪያ ገባ በአግራሞት ይቃኙ ጀመር፡፡የቤቱ ስፋትና ጥራት ብቻ ሳይሆን የትንግርት ከወትሮ የተለየ አለባበስ ጭምርም
ነበር ያፈዘዛቸው፡፡ እሷ የሆነ ገፀ ባህሪ ተላብሳ የምትተውንበት ቲያትር ቤት የገቡ ነው የመሠላቸው፡፡ ተረከዟ ድረስ የሚረዝም..
ባማረ ጥልፍ ያሸበረቀ የአገር ባህል ቀሚስ ለብሳ ነጭ አንገት ልብስ አንገቷ ላይ ጣል አድርጋለች፡፡
ድሮም የፈረስ ጭራ የሚመስለው ፀጉሯ ሹርባ ተሠርቶ ጀርባዋ ላይ ተነጥፏል፡፡
‹‹እውነትም ትንግርት ነሽ›› ሁሴን ነበር ተናጋሪው፡፡ በዝግታ እርምጃ ወደ እሷ ተጠግቶ ደረቱ ላይ ልጥፍ አድርጎ እያቀፋት፡፡
‹‹በዶላር ነበር እንዴ ስትሰሪ የከረምሽው?›› እጁን ለሠላምታ እየዘረጋላት ሠሎሞን እደዛ ያላት፡፡
‹‹አይ..በዩሮ ነው፡፡ ለማንኛውም ቁጭ በሉ፡፡›› በማለት ወደ ወንበሩ መርታ አስቀመጠቻቸው፡፡ በዛው ቅፅበት ሌሎች ተጋባዥ እንግዶቿም እጅ ለእጅ ተያይዘው ገቡ እና ተቀላቀሏቸው፡፡ ጨዋታው ደራ፣ ሳቁ ደመቀ፤ ሁሉም የምርጫቸውን እያነሱ ምሳቸውን ተመገቡ፡፡ ያሻቸውንም የመጠጥ ዓይነት እየመረጡ መጎንጨት ጀመሩ፡፡ ሻማዎቹ ተለኮሱ፡፡ እቤቱ
ደመቀ፡፡ ትንግርት በመሀከል ጨዋታቸውን
አቋረጠቻቸውና በተቀመጠችበት ሆና ንግግሯን ጀመረች፡፡ እንግዶቿም በፀጥታ ያዳምጧት ጀመር፡፡
‹‹ጥሪዬን አክብራችሁ እቤቴ ስለመጣችሁ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ ምክንያቱም ይህቺ ቀን ለእኔ ልዩ ነች፡፡ ልክ የዛሬ አምስት ዓመት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዲግሪ ስመረቅ የተሠማኝን ዓይነት የደስታ ስሜት ነው ዛሬም እየተሰማኝ ያለው›
‹‹በዲግሪ ስመረቅ ...?›› ሠሎሞን ነበር ፡፡
‹‹አዎ ምነው በሶስዮሎጂ ተመርቄያለሁ፡፡ ያንን ያህል እኮ ትልቅ ነገር አይደለም፡፡ እና ወደ ነገሬ ልመለስና ባለፉት ሦስት ዓመታት የቡና ቤት ሕይወቴ ሁለተኛ ዲግሪዬን ስማር እንደቆየሁና ዛሬ በእናንተ ፊት የምረቃ በዓሌን እያከበርኩ እንዳለሁ አርጋችሁ ቁጠሩት፡፡ እውቅና የሚሠጠኝ አካል ባይኖርምC ብዙ ተዓምር የሚያሠኙ የሕይወት ውጣ ውረዶችን አሳልፌያለሁ፡፡ መዓት ዓይነት ወንዶች
አጋጥመውኛል፡፡ ልምዱ የሌለው ጀማሪ….ያጎበደደ ሽማግሌ… አምስት አስር ልጆች ያሉት ባለትዳር... በስንፈተ ወሲብ የሚሰቃይ ጎልማሳ…ከወሲብ ጥማቱ በቀለሉ የማይረካ ጎረምሳ፣ደግ፣ንፉግ፣ተጫች፣ ዝጋታም፣ተደባዳቢ፣ኧረ ስንቱ…፡፡
👍106❤10👎4🔥4😁3👏1🎉1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁንገመቹዋቤ
‹‹አሁን አልነግርህም...ግን ለወራት ያስብኩበት አንድ ነገር አለ፡፡››
‹‹እኮ ንገሪኛ?››
‹‹አይ መጀመሪያ ከእሷ ጋር ልነጋገር…ግን አንተ ምንም አታስብ እሷን በምንም ዘዴ ቢሆን በምንም አሳምናታለሁ..በእኔ ጣለው…ትሄዳለች፡፡››
‹‹አንቺስ?››
‹‹ጋሼ እኔ እዚሁ ነኝ…የግል ኮሌጆች ምዝገባቸው ለወራት የሚዘልቅ ነው…ጊዜ አለን…ለማንኛውም ብሩ አንተው ጋር ይቀመጥ..ልመዘገብ ስሄድ እወስደዋለሁ›› ብላ ነበር ብሩን መልሳለት የወጣች፡፡
ሳባ በደንብ ትዝ ይላታል..በዛን ቀን ማታ እራት ተበልቶ ቡና ተጠጥቶ እንዳለቀ የሚፈልገውን ነገር ለአባታቸው አቀራረቡና ተያይዘው ወደመኝታ ቤታቸው ሄዱ፡፡ክፍላቸውን ዘጋግተው አልጋቸው ላይ ወጡና ወሬ ጀመሩ፡፡
‹‹ሳቢ አርብ ነው ወይስ ሰኞ የምትሄጂው?››አለቻት ስንዱ
ሳባ ግራ በመጋባት‹‹የት ነው የምሄደው ?›ስትል መልሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹አዲስ አበባ ነዋ….ምዝገባው እኮ ከአርብ እስከ ማክሰኞ ነው፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ?የምን ምዝገባ ነው?ዕድሜ ልኩን ወጥ እየወጠወጠና ልብሶቼን እያጠበ፤ንፍጤን እየጠረገና ለሀጬን እያበሰ ያለእናት ያሳደገኝን አባቴን እግር አልባ ሆኖ አልጋ ላይ ቀርቶ እያየሁ፤ እኔ ገና ለገና ነገ ባለድግሪ ለመሆን ብዬ ጥዬው የምሄድ ይመስልሻል…?እንደውም ስለትምህርት ሲጠራ እንዴት እንደሚቀፈኝ ብታውቂ ››
‹‹እንዴት ?ለምንድነው ትምህርት ሊቀፍሽ ሚችለው?›
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?እንደአንቺ ማትሪክ ሳይመጣልኝ ቀርቶ ቢሆን ኖሮ አባቴ ልሸኝሽ ብሎ በዛን ጊዜ አዲስ አበባ ይሄድ ነበር?.ባይሄድ ደግሞ ለዛ አደጋ ይጋለጥና እንደዛ ኩሩና ሀገር የማይበቃው የነበረው አባቴ እንዲህ ተቆራምዶ ቤት ይቀር ነበር…?››
‹‹ምን ነካሽ…..ያ የእግዚያብሄር ፍቃድ ነው፡፡ ደግሞ አባታችን በህይወት ስለተረፈልንና ዛሬም በእጆቹ እየዳበሰን ስለሆነ... ዛሬም በአንደበቱ እየመከረንና እየገሰፀን ስለሆነ ማመስገን ነው ያለብን፡፡ዛሬም ስለነጋችን እየተጨነቀና
መንገድ እያሳየን በመሆኑ እድለኞች ነን፡፡ከእሱ ጋር በመኪና ውስጥ የነበሩት ሰዎች እኮ ግማሹ ወዲያው ነው የሞቱት፡፡››
‹እሱስ እውነትሽን ነው…ተመስገን ነው…አባቴን ባጣ ምን ይዉጠኝ.ነበር?ግን አትልፊ…እኔ የትም አልሄድም፡፡››
‹‹ቆይ ጋሽ በአምላክ.. ለእኔም አባቴ እንደሆነ ታምኛለሽ?››
‹‹ምን ማለትሽ ነው…በጣም እንጂi አንቺ እኮ እህትና ወንድም ስለሌለኝ በውስጤ የነበረውን ቁጭትና ሀዘን ያጠፋሺልኝ ምርጥ እህቴ ነሽ››
‹‹ይሄን በመስማቴ ተደስቼያለሁ..ታዲያ አሁን ዩኒቨርሲቲ ብትገቢ እኔ.አንቺ እዚህ ሆነሽ ከምትንከባከቢው በታች ትንከባከበዋለች ብለሽ ታስቢያለሽ?››
‹‹በፍፁም… እንደውም እሱን በመንከባከብ አንቺ ከእኔ የተሻልሽ ነሽ፡፡››
‹‹እና ታዲያ በእኔ እምነት ይኑርሻ፡፡››
‹‹ባንቺ እምነት ሳይኖረኝ ቀርቶ እኮ አይደለም፡፡አመታቱ ረጅም.መሆናቸው አሳስቦኝ ነው..አራት አመት…››
‹‹አራት አመት ምን አላት? አርባ አመትስ ቢሆን?››
‹‹ምን ነካሽ አንቺም እኮ የራስሽ ህይወት አለሽ…ችላ ብለሽ ልታልፊው የማትችይው የስራ ዕድል ሊያጋጥምሽ ይችላል..?ልታፈቅሪ ትችያለሽ…ባል ማግባትም ልትወስኚ ትችያለሽ…አንቺ ባትፈልጊ እንኳን ቤተሰቦችሽ ሊያስገድዱሽ ይችላሉ፡፡ያኔ እንዴት ሊሆን ነው…?ትምህርቴን ለሁለተኛ ጊዜ መልሼ ላቋርጥ ነው…?፡፡የማልወጣውን ነገር መነካካት አልፈልግም፡፡ግድ የለም ይቅርብኝ፡፡እዚሁ የተዘጋውን የአባቴን ሱቅ ከፍቼ እሱን እየሰራው ብንከባከበው ይሻላል፡፡››
‹‹አይ እንደዛ ማደርገው እኔ ነኝ፡፡አንቺ ወደ ትምህርትሽ ነው የምትሄጂው፡፡ ብታፈቅሪስ ላለሽው ቆየሁኮ አፍቅሬያለሁ፡፡››
‹‹ባክሽ ቀልዱን አቁሚ፡፡››
‹‹እየቀለድኩ እኮ አይደለም ..እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እንዴ አንቺ…?ከመቼ ጀምሮ...?ትራሷን ከፍ አደረገችና ከአንገቷ ቀና ብላ አፋጠጠችባት››
‹‹ቢያንስ ሶስት አመት…፡፡››
‹‹አንቺ ሶሰት አመት ሙሉ አፍቅረሽ ለእኔ ሳትነግሪኝ..?እኔ እኮ በህልሜ ያናገረኝን ወንድ ማንነት ሳይቀር ነው የምነግርሽ፡፡››
‹‹እንደምታስቢው ለመናገር ቀላል አልነበረም፡፡››
‹‹…እውነትሽን ነው ቀላል አልነበረም….?››ሳባ ተበሳጨች… ከዛ በላይ ማውራት አልፈለገችም፡፡ትራሷን ወደታች አወረደችና ብርድ ልብሱን ተከናንባ ተኛች፡
‹‹እንዴ ጥለሺኝ እየተኛሽ ነው…?ማን ነው ያፈቀርሺው ብለሽ አትጠይቂኝም?››
‹‹ምን ሊያደርግልኝ… ሶስት አመት ሙሉ የደበቅሺኝን ዛሬ ብሰማው ምን ይረባኛል… ?.እንደውም ከማያምነኝ ሰው ጋር መተኛት አልፈልግም፡፡›› ብላ ነበር መኝታዋን ለቃ በመውረድ ከላይ ያለውን አልጋ ልብስ ገፋ ስሊፐሯን ተጫምታ ከክፍሉ ለመውጣት ወደበራፍ መራመድ የጀመረች...ለመክፈት እጇን ወደ እጀታው ስትዘረጋ ከስንዱ አንደበት እጅግ አስደንጋጭ መንፈሰን የሚያርድና የሚያደነዝዝ ቃል ነበር የወጣው ፡፡
‹‹ያፈቀርኩት አባትሽን ነው፡፡››
በቆመችበት ደንዝዛ ለደቂቃዎች ቆመች...እንደምንም ፊቷን አዞረችና
‹‹አልሰማሁሽም››ነበር ያለቻት፡፡እውነታው ግን የተናገረችውን ሶስት ቃላት በትክክል ሰምታለች…ግን.አልገባትም.ወይም.ሊታመን የሚችል ዜና ሆኖ አላገኘችውም፡፡
‹‹አዎ ለዛ ነው ሶስት አመት መሉ ሳልነግርሽ በውስጤ አፍኜ የኖርኩት..አባትሽን ስላፈቀርኩ በራሴ አፍሬያለሁ፡፡››
‹‹ቀስ ብላ እግሮቿን እየጎተተች ወደውስጥ ተመለሰችና አልጋ ልብሱን እንደተከናነበች አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች፡፡በሰማችው ዜና ደስታ ይሰማት ወይስ ሀዘን ማወቅ አልቻለችም…..አባቷን እኩያዋ የሆነች ልጅ ለዛውም አብራት የምትኖር የገዛ ጓደኛዋ ስታፈቅረው ፡፡
‹‹እርግጠኛ ነሽ ግን?››
‹‹እስከ ዛሬ አመት ማለቴ ጋሼ አደጋ እስኪደርስበት ድረስ እርግጠኛ አልነበርኩም…እንዲሁ ውስጤ የተፈጠረ ቅዠት አድርጌ በማሰብ ራሴን በመገሰፅ ነገሮችን አዳፍኜ መቀጠልን ነበር የወሰንኩት፡፡ጋሼ የተጎዳ ጊዜ ግን በተለይ ዜናውን ፖሊሶች ደውለው ሲነግሩኝ የተሰማኝ ስሜት፤የፈራሁት ፍርሀት፤ላፈቀርሽውና ህይወትሽን ሳይቀር ልትሰጪው ፍቃደኛ ከሆንሺለት ሰው ውጭ ለሌላ ሰው የሚሰማሽ እንዳልሆነ ገባኝ..እውነትም አፍቅሬዋለሁ ብዬ ሙሉ በሙሉ የደመደምኩት የዛኔ ነው››
በወቅቱ ሳባ ምንም ልትላት አልቻለችም….
‹‹ምነው አላመንሺኝም አይደል..?አልፈርድብሽም እኔ ለራሴ የልቤን ጩኸት አምኖ ለመቀበል አመታት ከወሰደብኝ አንቺ እንዴት እንዲህ በፍጥነት ትረጂዋለሽ ብዬ አስባለሁ?፡፡››
‹‹አይደለም እኮ …ማለት አባዬ ለአንቺም እንደአባትሽ ነው፤ለእሱ ካለሽ ክብርና መውደድ የተነሳ ምን አልባት ተምታቶብሽ እንዳይሆን ብዬ ነው እኮ…?›
‹‹ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር እኮ..ግን አይደለም..ጋሼ አባቴ ሳይሆን ባሌ እንዲሆን ነው የምፈልገው፡፡›
‹‹አባዬ እኮ 42 አመቱ ነው ፤ከአንቺ በ22 ዓመት ይበልጣል፡፡››
‹‹አውቃለሁ… ግን ያ ግድ አይሰጠኝም..››
‹‹እሺ አሁን ያለበት ሁኔታስ…?››
‹‹እሱም ጉዳዬ አይደለም…እኔን የሚያስጨንቀኝ ብቸኛው ምክንያት አንቺ ስለነገሩ ምን ታስቢያለሸ ?የሚለው ነው…፡፡››
‹‹እኔ ደግሞ ምን?››
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
ደራሲ-ዘሪሁንገመቹዋቤ
‹‹አሁን አልነግርህም...ግን ለወራት ያስብኩበት አንድ ነገር አለ፡፡››
‹‹እኮ ንገሪኛ?››
‹‹አይ መጀመሪያ ከእሷ ጋር ልነጋገር…ግን አንተ ምንም አታስብ እሷን በምንም ዘዴ ቢሆን በምንም አሳምናታለሁ..በእኔ ጣለው…ትሄዳለች፡፡››
‹‹አንቺስ?››
‹‹ጋሼ እኔ እዚሁ ነኝ…የግል ኮሌጆች ምዝገባቸው ለወራት የሚዘልቅ ነው…ጊዜ አለን…ለማንኛውም ብሩ አንተው ጋር ይቀመጥ..ልመዘገብ ስሄድ እወስደዋለሁ›› ብላ ነበር ብሩን መልሳለት የወጣች፡፡
ሳባ በደንብ ትዝ ይላታል..በዛን ቀን ማታ እራት ተበልቶ ቡና ተጠጥቶ እንዳለቀ የሚፈልገውን ነገር ለአባታቸው አቀራረቡና ተያይዘው ወደመኝታ ቤታቸው ሄዱ፡፡ክፍላቸውን ዘጋግተው አልጋቸው ላይ ወጡና ወሬ ጀመሩ፡፡
‹‹ሳቢ አርብ ነው ወይስ ሰኞ የምትሄጂው?››አለቻት ስንዱ
ሳባ ግራ በመጋባት‹‹የት ነው የምሄደው ?›ስትል መልሳ ጠየቀቻት፡፡
‹‹አዲስ አበባ ነዋ….ምዝገባው እኮ ከአርብ እስከ ማክሰኞ ነው፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ?የምን ምዝገባ ነው?ዕድሜ ልኩን ወጥ እየወጠወጠና ልብሶቼን እያጠበ፤ንፍጤን እየጠረገና ለሀጬን እያበሰ ያለእናት ያሳደገኝን አባቴን እግር አልባ ሆኖ አልጋ ላይ ቀርቶ እያየሁ፤ እኔ ገና ለገና ነገ ባለድግሪ ለመሆን ብዬ ጥዬው የምሄድ ይመስልሻል…?እንደውም ስለትምህርት ሲጠራ እንዴት እንደሚቀፈኝ ብታውቂ ››
‹‹እንዴት ?ለምንድነው ትምህርት ሊቀፍሽ ሚችለው?›
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?እንደአንቺ ማትሪክ ሳይመጣልኝ ቀርቶ ቢሆን ኖሮ አባቴ ልሸኝሽ ብሎ በዛን ጊዜ አዲስ አበባ ይሄድ ነበር?.ባይሄድ ደግሞ ለዛ አደጋ ይጋለጥና እንደዛ ኩሩና ሀገር የማይበቃው የነበረው አባቴ እንዲህ ተቆራምዶ ቤት ይቀር ነበር…?››
‹‹ምን ነካሽ…..ያ የእግዚያብሄር ፍቃድ ነው፡፡ ደግሞ አባታችን በህይወት ስለተረፈልንና ዛሬም በእጆቹ እየዳበሰን ስለሆነ... ዛሬም በአንደበቱ እየመከረንና እየገሰፀን ስለሆነ ማመስገን ነው ያለብን፡፡ዛሬም ስለነጋችን እየተጨነቀና
መንገድ እያሳየን በመሆኑ እድለኞች ነን፡፡ከእሱ ጋር በመኪና ውስጥ የነበሩት ሰዎች እኮ ግማሹ ወዲያው ነው የሞቱት፡፡››
‹እሱስ እውነትሽን ነው…ተመስገን ነው…አባቴን ባጣ ምን ይዉጠኝ.ነበር?ግን አትልፊ…እኔ የትም አልሄድም፡፡››
‹‹ቆይ ጋሽ በአምላክ.. ለእኔም አባቴ እንደሆነ ታምኛለሽ?››
‹‹ምን ማለትሽ ነው…በጣም እንጂi አንቺ እኮ እህትና ወንድም ስለሌለኝ በውስጤ የነበረውን ቁጭትና ሀዘን ያጠፋሺልኝ ምርጥ እህቴ ነሽ››
‹‹ይሄን በመስማቴ ተደስቼያለሁ..ታዲያ አሁን ዩኒቨርሲቲ ብትገቢ እኔ.አንቺ እዚህ ሆነሽ ከምትንከባከቢው በታች ትንከባከበዋለች ብለሽ ታስቢያለሽ?››
‹‹በፍፁም… እንደውም እሱን በመንከባከብ አንቺ ከእኔ የተሻልሽ ነሽ፡፡››
‹‹እና ታዲያ በእኔ እምነት ይኑርሻ፡፡››
‹‹ባንቺ እምነት ሳይኖረኝ ቀርቶ እኮ አይደለም፡፡አመታቱ ረጅም.መሆናቸው አሳስቦኝ ነው..አራት አመት…››
‹‹አራት አመት ምን አላት? አርባ አመትስ ቢሆን?››
‹‹ምን ነካሽ አንቺም እኮ የራስሽ ህይወት አለሽ…ችላ ብለሽ ልታልፊው የማትችይው የስራ ዕድል ሊያጋጥምሽ ይችላል..?ልታፈቅሪ ትችያለሽ…ባል ማግባትም ልትወስኚ ትችያለሽ…አንቺ ባትፈልጊ እንኳን ቤተሰቦችሽ ሊያስገድዱሽ ይችላሉ፡፡ያኔ እንዴት ሊሆን ነው…?ትምህርቴን ለሁለተኛ ጊዜ መልሼ ላቋርጥ ነው…?፡፡የማልወጣውን ነገር መነካካት አልፈልግም፡፡ግድ የለም ይቅርብኝ፡፡እዚሁ የተዘጋውን የአባቴን ሱቅ ከፍቼ እሱን እየሰራው ብንከባከበው ይሻላል፡፡››
‹‹አይ እንደዛ ማደርገው እኔ ነኝ፡፡አንቺ ወደ ትምህርትሽ ነው የምትሄጂው፡፡ ብታፈቅሪስ ላለሽው ቆየሁኮ አፍቅሬያለሁ፡፡››
‹‹ባክሽ ቀልዱን አቁሚ፡፡››
‹‹እየቀለድኩ እኮ አይደለም ..እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እንዴ አንቺ…?ከመቼ ጀምሮ...?ትራሷን ከፍ አደረገችና ከአንገቷ ቀና ብላ አፋጠጠችባት››
‹‹ቢያንስ ሶስት አመት…፡፡››
‹‹አንቺ ሶሰት አመት ሙሉ አፍቅረሽ ለእኔ ሳትነግሪኝ..?እኔ እኮ በህልሜ ያናገረኝን ወንድ ማንነት ሳይቀር ነው የምነግርሽ፡፡››
‹‹እንደምታስቢው ለመናገር ቀላል አልነበረም፡፡››
‹‹…እውነትሽን ነው ቀላል አልነበረም….?››ሳባ ተበሳጨች… ከዛ በላይ ማውራት አልፈለገችም፡፡ትራሷን ወደታች አወረደችና ብርድ ልብሱን ተከናንባ ተኛች፡
‹‹እንዴ ጥለሺኝ እየተኛሽ ነው…?ማን ነው ያፈቀርሺው ብለሽ አትጠይቂኝም?››
‹‹ምን ሊያደርግልኝ… ሶስት አመት ሙሉ የደበቅሺኝን ዛሬ ብሰማው ምን ይረባኛል… ?.እንደውም ከማያምነኝ ሰው ጋር መተኛት አልፈልግም፡፡›› ብላ ነበር መኝታዋን ለቃ በመውረድ ከላይ ያለውን አልጋ ልብስ ገፋ ስሊፐሯን ተጫምታ ከክፍሉ ለመውጣት ወደበራፍ መራመድ የጀመረች...ለመክፈት እጇን ወደ እጀታው ስትዘረጋ ከስንዱ አንደበት እጅግ አስደንጋጭ መንፈሰን የሚያርድና የሚያደነዝዝ ቃል ነበር የወጣው ፡፡
‹‹ያፈቀርኩት አባትሽን ነው፡፡››
በቆመችበት ደንዝዛ ለደቂቃዎች ቆመች...እንደምንም ፊቷን አዞረችና
‹‹አልሰማሁሽም››ነበር ያለቻት፡፡እውነታው ግን የተናገረችውን ሶስት ቃላት በትክክል ሰምታለች…ግን.አልገባትም.ወይም.ሊታመን የሚችል ዜና ሆኖ አላገኘችውም፡፡
‹‹አዎ ለዛ ነው ሶስት አመት መሉ ሳልነግርሽ በውስጤ አፍኜ የኖርኩት..አባትሽን ስላፈቀርኩ በራሴ አፍሬያለሁ፡፡››
‹‹ቀስ ብላ እግሮቿን እየጎተተች ወደውስጥ ተመለሰችና አልጋ ልብሱን እንደተከናነበች አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች፡፡በሰማችው ዜና ደስታ ይሰማት ወይስ ሀዘን ማወቅ አልቻለችም…..አባቷን እኩያዋ የሆነች ልጅ ለዛውም አብራት የምትኖር የገዛ ጓደኛዋ ስታፈቅረው ፡፡
‹‹እርግጠኛ ነሽ ግን?››
‹‹እስከ ዛሬ አመት ማለቴ ጋሼ አደጋ እስኪደርስበት ድረስ እርግጠኛ አልነበርኩም…እንዲሁ ውስጤ የተፈጠረ ቅዠት አድርጌ በማሰብ ራሴን በመገሰፅ ነገሮችን አዳፍኜ መቀጠልን ነበር የወሰንኩት፡፡ጋሼ የተጎዳ ጊዜ ግን በተለይ ዜናውን ፖሊሶች ደውለው ሲነግሩኝ የተሰማኝ ስሜት፤የፈራሁት ፍርሀት፤ላፈቀርሽውና ህይወትሽን ሳይቀር ልትሰጪው ፍቃደኛ ከሆንሺለት ሰው ውጭ ለሌላ ሰው የሚሰማሽ እንዳልሆነ ገባኝ..እውነትም አፍቅሬዋለሁ ብዬ ሙሉ በሙሉ የደመደምኩት የዛኔ ነው››
በወቅቱ ሳባ ምንም ልትላት አልቻለችም….
‹‹ምነው አላመንሺኝም አይደል..?አልፈርድብሽም እኔ ለራሴ የልቤን ጩኸት አምኖ ለመቀበል አመታት ከወሰደብኝ አንቺ እንዴት እንዲህ በፍጥነት ትረጂዋለሽ ብዬ አስባለሁ?፡፡››
‹‹አይደለም እኮ …ማለት አባዬ ለአንቺም እንደአባትሽ ነው፤ለእሱ ካለሽ ክብርና መውደድ የተነሳ ምን አልባት ተምታቶብሽ እንዳይሆን ብዬ ነው እኮ…?›
‹‹ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር እኮ..ግን አይደለም..ጋሼ አባቴ ሳይሆን ባሌ እንዲሆን ነው የምፈልገው፡፡›
‹‹አባዬ እኮ 42 አመቱ ነው ፤ከአንቺ በ22 ዓመት ይበልጣል፡፡››
‹‹አውቃለሁ… ግን ያ ግድ አይሰጠኝም..››
‹‹እሺ አሁን ያለበት ሁኔታስ…?››
‹‹እሱም ጉዳዬ አይደለም…እኔን የሚያስጨንቀኝ ብቸኛው ምክንያት አንቺ ስለነገሩ ምን ታስቢያለሸ ?የሚለው ነው…፡፡››
‹‹እኔ ደግሞ ምን?››
👍75❤11👎4👏2
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ጥያቄዋ እሱን በጣም ነበረ ያሳቀቀው ፤ ወዲያው ነበር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ወደእሷ የተጠጋው፡፡ከዛ ከጎኗ ተቀመጠና ወደራሱ ስቦ አቀፋት..በዛ ልስልስና ጣፋጭ አንደበቱ‹‹እንደውም በጣም የምወድሽማ አሁን ነው፡፡በጣም እኮ ነው የምታሳዝኚኝ፡፡አንቺ ብቻ ነሽ እኮ ያለሺን፡፡እንዴት አንቺን ላለመወደድ እችላለሁ?ከአንቺ ውጭ እኮ ምንም ነገር የለኝም፡፡››ብሎ በመረረና በጠነከረ ንግግር ስለፍቅሩ ጥልቀት አስረዳት፡፡
በጣም ነበር ያሳዘናት‹‹አንተም እነአባቢን ተከትለህ ጥለኸኝ ሄደህ ቢሆን ኖሮ ምን እሆን ነበር….?››አለችው ፡፡ያንን ስትለው መላ ሰውነቷ በፍራቻ እየተንቀጠቀጠባት እንደነበረ ትዝ ይላታል፡፡ናኦል ከገቡበት ከጨላማ ውስጥ ከሚመዘዝ የትዝታ ጉዞ በከፊልም ቢሆን እንዲወጡ ፈለገና የጫወታቸውን ርዕስ ቀየረ፡፡‹‹በቃ አሁን ልደሽን እናክብር….››አላት
‹‹ልደቱ የእኔ ብቻ ነው እንዴ…?የሁለታችንም እኮ ነው፡፡››
‹‹ታውቂያለሽ እኔ ልደቴን ማክበር እንደማልወድ››
‹‹እንዳልክ እሺ… ግን መጀመሪያ የእኔን ሻማ እንለኩስና የእነአባቢን የሙት አመት መታሰቢያ እናክብር››ብላ መለሰችለት፡፡
እሱ ግን‹‹አይ ልደቱም ሀዘኑም የእኛው አይደል ..ሁለቱንም ሻማዎች አንድ ላይ እንለኩሳቸው››አላት
አልተከራከረችውም‹‹ ክብሪቱን የት አደረከው?››
ከኪሱ ውስጥ ፈልጎ አወጣና ሰጣት ..ጫረችና የመጀመሪያውን የራሷን ሻማ በመለኮስ አባቷ መቃብር ላይ በማንጠባጠብ እረሱን ችሎ እንዲቆም አደረገች፡፡ከዛ ሌለናውን ሻማ ከወንድሟ እጅ ተቀበለችና ለኩሳ ወደግራዋ ዞራ እናቷ መቃብር ላይ በተመሳሳይ መልኩ አስቀመጠች፡፡በመቀጠል የራሷን የተቀዳደደ የጃኬት ኪስ ፈተሸችና ሁለት ብስኩት አወጣች፡፡ወደ ወንድሟ በስስት እያየች‹‹ወንድሜ ለልደቴ ሻማ ስለለኮስክልኝ አመሰግናለው .. ለእንተም መልካም ልደት ይሁንልህ..ለእኔ ስትል አብረኸኝ ስለተወለድክ አመሰግናለው፡፡››አለችውና ከኪሷ ያወጣችውን ብስኩት እጁ ላይ አደረገች፡፡
ትዝ ይላታል በጣም ነበር ደስ ያለው፡፡ያንን ብስኩት መያዟን አያውቅም ነበር፡፡ሳንቲሙን ከየት አግኝታ? መቼ ገዝታ? እንዴት ከእሱ ደብቃ ይዛ እንደመጣች አያውቅም፡፡እሱም ግን ሊያስደምማት ለሳምንት ሲያስብበት ነበረ፡፡እጁን ወደኪሱ ሰደደና አንድ ቸኮሌትና አንድ ጦር ማስቲካ በማውጣት .‹‹እህቴ እንኳን ተወለድሽ..ደግሞ ልደቱን የሚያከብር ሰው ስጦታ ይቀበላል እንጂ ስጦታ አይሰጥም›› ብሎ እጆ ላይ አስቀመጠላት፡፡
ኑሀሚ ቸኮሌትና መስቲካውን በጣም እንደምትወደው ያውቃል፡፡ ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ እናትዬው የመስቲካ ሱሰኛ አባትዬው ደግሞ የቸኮሌት ሱሰኛ አድርገዋት ነበር፡፡ያኔ በሰላሙ ጊዜ በቀን ሁለቴ ወይም ሶስቴ ሰበብ እየፈጠረች ታለቅስ ነበር፡፡ለቅሶዋን ምታቆመው ደግሞ ወይ ቸኮሌት ወይም ደግሞ መስቲካ ሲሰጣት ብቻ ነበር፡፡ይሄም በደንብ ስለሚታወቅ ቀደም ተብሎ ይገዛና ተደብቆ ይቀመጥላታል፡፡ …..እና በወቅቱ የወንድሟ ስጦታ እናትና አባቷን በአንድ ላይ በጥልቀት እንድታስታውስ ነበር ያደረጋት፡፡ መልካቸው ብቻ ሳይሆን ጠረናቸውም ነበር ትዝ ያላት፡፡
‹‹ወንድሜ በጣም ነው ያስደሰትከኝ፡፡አንተ ስላለህልኝ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹እህቴ ስናድግ የቸኮሌት ፋብሪካ ይኖረኛል፡፡እና ያንን ፋብሪካ ላንቺ ስል ነው የምከፍተው፡፡ሁል ጊዜ የፈለግሽውን ያህል ቸኮሌት መብላት እንድትቺይ እፈልጋለሁ፡፡››ሲል ከጥልቅ ልቡ የመነጨውን ምኞቱን በፍቅር እና በስስት አይን አይኗን እያየ ነበር ቃል የገባላት፡፡ወደእዚህ አሁን ወዳለችበት ደቡብ አሜሪካ ከመምጣቷ በፊት ወንድሟ የዛን ጊዜ በልጅነታቸው ቃል የገባላትን ቸኮሌት ፋብሪካ ለመገንባት ማሽኑ የሚተከልበትን ዌርሀውስ ማስገንባት ጀምሮ ነበር፡፡ምን አልባት እስከአሁን አጠናቆትም ሊሆን ይችላል፡፡በጣም የሚያሳዝነውና መራሩ ሀቅ ግን ቸኮሌት ፋብሪካው ተተክሎ ማምረት ቢጀምር እንኳን እህቱን ማብላት አይችልም፡፡እህቱን በሰው ሀገር ምድር ላይ በሞት መነጠቋን ካወቀ ፋብሪካውን ያቃጥለዋል፡፡በዛ እርግጠኛ ነች፡፡
በወቅቱ በዛ የልጅነት ጊዜያቸው በወላጆቻቸው መቃብር ስር ስለቸኮሌት ፋብሪካው ቃል ሲገበላት‹‹ወንድሜ ቸኮሌት ፋብሪካ ለመክፈት እኮ ብዙ ብር ነው የሚያስፈልገው…ሀብታም መሆን አለብህ..ያ እንዴት ሊሆን ይችላል? ፡፡››ብላ ነበር የጠየቀችው፡፡
ወንድሟ እጆቹን ዘርግቶ ግራና ቀኝ ትከሻዋን በመያዝ ትኩር ብሎ አይኖቹን አይኖቾ ላይ ተክሎ‹‹አዎ ሀብታም መሆን አለብኝ፡፡እኔ ብቻ ሳልሆን አንቺም ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡ለእኛ ሀብታም መሆን የግድ ነው፡፡እኔ ላንቺ ስል ሀብታምና ብዙ ብር ያለው ሰው መሆን እፈልጋለሁ፡፡አንቺም ለእኔ ስትይ እንደዛው ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡››ነበር ያላት
‹‹እንዴት ግን..?ትምህርታችንን ከሶስተኛ ክፍል እንዳቋረጥን ነው፡፡ሳንማር እንዴት ነው ሀብታም ልንሆን የምንችለው?››
‹‹እንችላለን፡፡ማለቴ ሳይማሩ ሀብታም መሆን የሚቻል ይመስለኛል፡፡ያለበለዚያ ቡዙ የተማሩ ሆነው ምንም ብር የሌለቸውና አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች ደግሞ ሀብታሞች ሆነው አናገኝም ነበር፡፡አዎ እንዴት እንደሆነ ለጊዜው ባላውቅም ሳይማሩም ሀብታም መሆን እንደሚቻል እርግጠኛ ነኝ፡፡››አላት፡፡
አዎ..የወደፊት ህልማቸውን በተመለከተ ወንድሟ የሚያወራው ነገር በጣም መሳጭ እና አጓጊ ሆኖ ነበር ያገኘችው፡፡ቢሆንም ግን እንዴት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል በወቅቱ ምንም ፍንጭ አልታያትም፡፡ግን ደግሞ የወንድሟን ንግግር የሞኝ ቅዠት አድርጋም አልወሰደችውም፡፡ ወንድሟን አይደለም በዛን ጊዜ አሁንም ታምነዋለች፡፡ከፍቅር የመነጨ እምነት፡፡
እርግጥ እሷም ከእሱ ጋር ተቀራራቢ የሆነ ሀሳብ ሁሌ በውስጧ ታሰላስል ነበር፡፡ስታድግ የተወለዱበትንና ያደጉበትን የወላጆቾን ቤት መልሳ መግዛት የዘወትር ምኞቷ ነበር፡፡አዎ በወቅቱ እቤቱን የአባታቸው የልብ ጓደኛው በነበረ ሰው ባለቤትነት ተይዟል፡፡ ወላጆቻቸው ሞተው ወር እንኳን ሳይሞላው ነበር ከመሟቱ በፊት ለስራ ብሎ ብዙ ሚሊዬን ብር ተበድሮኛል ብሎ የተናገረው፡፡ብዙም ሳይቆይ የተናገረውን የሚያረጋግጥለት ሰንድ አቀረበ፡፡ከዛ በቀላሉ በፍርድ ቤት ከሶ ወላጆቻቸው ሞተው በተቀበሩ በሶስተኛው ወር እቤቱን ተረክበ፡፡ለእነሱ ቀርቦ የሚከራከርላቸውም ሆነ ወስዶ የሚያሳድጋቸው አንድም ዘመድ መቅረብ ስላልቻለ …ሰውዬው ጎዳና ጣላቸው የሚለውን የሰው አፍ ብቻ በመፍራት ወስዶ ለማደጎ ቤት አስረከባቸው፡፡ኑሀሚ በዛ ጮርቃ እድሜዋ ላይ ሆና እንኳን ያ ሁሉ የተወሳሰበ ቲያትር መሰል አሻጥር ፈፅሞ አይዋጥላትም ነበር፡፡ያንን ቤት በጣም ትወደዋለች፡፡ልጅነቷ ያለው እዛ ቤት ውስጥ ነው፡፡ሳቅና ደስታዋ እዛ ቤት የሆነ ቁምሳጥን ወይም የኮመዲኖ ኪስ ውስጥ የተቆመለፈበት ነበር የሚመስላት፡፡እና አንድ ቀን ተሳክቶላት ያንን ቤት ማስመለስና የራሳቸው ማድረግ ብትችል እናትና አባቷንም በከፊልም ቢሆን ከሞት አለም ማስመለስ እንደሆነ አድርጋ ነበር የምትቆጥረው ፡፡ዘወትር ትንሽ በከፋት ቁጥር የሚተኙበትን መኝታ ቤት ትዝ ይላታል፤እናቷ ምግብ የምታበስልበት ኪችን ሙሉ ስዕሉ በአእምሮዋ ይመላለስባት ነበር፡፡አባቷ በእረፍት ቀኑ ቢጃማ ለብሶ በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ሲያነብ …እሷ ድክ ድክ እያለች ከሳሎን መጥታ ታፋው ላይ በመቀመጥ ከኪሱ ስልኩን አውጥታ ጌም ስትጫወት….
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ጥያቄዋ እሱን በጣም ነበረ ያሳቀቀው ፤ ወዲያው ነበር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ወደእሷ የተጠጋው፡፡ከዛ ከጎኗ ተቀመጠና ወደራሱ ስቦ አቀፋት..በዛ ልስልስና ጣፋጭ አንደበቱ‹‹እንደውም በጣም የምወድሽማ አሁን ነው፡፡በጣም እኮ ነው የምታሳዝኚኝ፡፡አንቺ ብቻ ነሽ እኮ ያለሺን፡፡እንዴት አንቺን ላለመወደድ እችላለሁ?ከአንቺ ውጭ እኮ ምንም ነገር የለኝም፡፡››ብሎ በመረረና በጠነከረ ንግግር ስለፍቅሩ ጥልቀት አስረዳት፡፡
በጣም ነበር ያሳዘናት‹‹አንተም እነአባቢን ተከትለህ ጥለኸኝ ሄደህ ቢሆን ኖሮ ምን እሆን ነበር….?››አለችው ፡፡ያንን ስትለው መላ ሰውነቷ በፍራቻ እየተንቀጠቀጠባት እንደነበረ ትዝ ይላታል፡፡ናኦል ከገቡበት ከጨላማ ውስጥ ከሚመዘዝ የትዝታ ጉዞ በከፊልም ቢሆን እንዲወጡ ፈለገና የጫወታቸውን ርዕስ ቀየረ፡፡‹‹በቃ አሁን ልደሽን እናክብር….››አላት
‹‹ልደቱ የእኔ ብቻ ነው እንዴ…?የሁለታችንም እኮ ነው፡፡››
‹‹ታውቂያለሽ እኔ ልደቴን ማክበር እንደማልወድ››
‹‹እንዳልክ እሺ… ግን መጀመሪያ የእኔን ሻማ እንለኩስና የእነአባቢን የሙት አመት መታሰቢያ እናክብር››ብላ መለሰችለት፡፡
እሱ ግን‹‹አይ ልደቱም ሀዘኑም የእኛው አይደል ..ሁለቱንም ሻማዎች አንድ ላይ እንለኩሳቸው››አላት
አልተከራከረችውም‹‹ ክብሪቱን የት አደረከው?››
ከኪሱ ውስጥ ፈልጎ አወጣና ሰጣት ..ጫረችና የመጀመሪያውን የራሷን ሻማ በመለኮስ አባቷ መቃብር ላይ በማንጠባጠብ እረሱን ችሎ እንዲቆም አደረገች፡፡ከዛ ሌለናውን ሻማ ከወንድሟ እጅ ተቀበለችና ለኩሳ ወደግራዋ ዞራ እናቷ መቃብር ላይ በተመሳሳይ መልኩ አስቀመጠች፡፡በመቀጠል የራሷን የተቀዳደደ የጃኬት ኪስ ፈተሸችና ሁለት ብስኩት አወጣች፡፡ወደ ወንድሟ በስስት እያየች‹‹ወንድሜ ለልደቴ ሻማ ስለለኮስክልኝ አመሰግናለው .. ለእንተም መልካም ልደት ይሁንልህ..ለእኔ ስትል አብረኸኝ ስለተወለድክ አመሰግናለው፡፡››አለችውና ከኪሷ ያወጣችውን ብስኩት እጁ ላይ አደረገች፡፡
ትዝ ይላታል በጣም ነበር ደስ ያለው፡፡ያንን ብስኩት መያዟን አያውቅም ነበር፡፡ሳንቲሙን ከየት አግኝታ? መቼ ገዝታ? እንዴት ከእሱ ደብቃ ይዛ እንደመጣች አያውቅም፡፡እሱም ግን ሊያስደምማት ለሳምንት ሲያስብበት ነበረ፡፡እጁን ወደኪሱ ሰደደና አንድ ቸኮሌትና አንድ ጦር ማስቲካ በማውጣት .‹‹እህቴ እንኳን ተወለድሽ..ደግሞ ልደቱን የሚያከብር ሰው ስጦታ ይቀበላል እንጂ ስጦታ አይሰጥም›› ብሎ እጆ ላይ አስቀመጠላት፡፡
ኑሀሚ ቸኮሌትና መስቲካውን በጣም እንደምትወደው ያውቃል፡፡ ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ እናትዬው የመስቲካ ሱሰኛ አባትዬው ደግሞ የቸኮሌት ሱሰኛ አድርገዋት ነበር፡፡ያኔ በሰላሙ ጊዜ በቀን ሁለቴ ወይም ሶስቴ ሰበብ እየፈጠረች ታለቅስ ነበር፡፡ለቅሶዋን ምታቆመው ደግሞ ወይ ቸኮሌት ወይም ደግሞ መስቲካ ሲሰጣት ብቻ ነበር፡፡ይሄም በደንብ ስለሚታወቅ ቀደም ተብሎ ይገዛና ተደብቆ ይቀመጥላታል፡፡ …..እና በወቅቱ የወንድሟ ስጦታ እናትና አባቷን በአንድ ላይ በጥልቀት እንድታስታውስ ነበር ያደረጋት፡፡ መልካቸው ብቻ ሳይሆን ጠረናቸውም ነበር ትዝ ያላት፡፡
‹‹ወንድሜ በጣም ነው ያስደሰትከኝ፡፡አንተ ስላለህልኝ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹እህቴ ስናድግ የቸኮሌት ፋብሪካ ይኖረኛል፡፡እና ያንን ፋብሪካ ላንቺ ስል ነው የምከፍተው፡፡ሁል ጊዜ የፈለግሽውን ያህል ቸኮሌት መብላት እንድትቺይ እፈልጋለሁ፡፡››ሲል ከጥልቅ ልቡ የመነጨውን ምኞቱን በፍቅር እና በስስት አይን አይኗን እያየ ነበር ቃል የገባላት፡፡ወደእዚህ አሁን ወዳለችበት ደቡብ አሜሪካ ከመምጣቷ በፊት ወንድሟ የዛን ጊዜ በልጅነታቸው ቃል የገባላትን ቸኮሌት ፋብሪካ ለመገንባት ማሽኑ የሚተከልበትን ዌርሀውስ ማስገንባት ጀምሮ ነበር፡፡ምን አልባት እስከአሁን አጠናቆትም ሊሆን ይችላል፡፡በጣም የሚያሳዝነውና መራሩ ሀቅ ግን ቸኮሌት ፋብሪካው ተተክሎ ማምረት ቢጀምር እንኳን እህቱን ማብላት አይችልም፡፡እህቱን በሰው ሀገር ምድር ላይ በሞት መነጠቋን ካወቀ ፋብሪካውን ያቃጥለዋል፡፡በዛ እርግጠኛ ነች፡፡
በወቅቱ በዛ የልጅነት ጊዜያቸው በወላጆቻቸው መቃብር ስር ስለቸኮሌት ፋብሪካው ቃል ሲገበላት‹‹ወንድሜ ቸኮሌት ፋብሪካ ለመክፈት እኮ ብዙ ብር ነው የሚያስፈልገው…ሀብታም መሆን አለብህ..ያ እንዴት ሊሆን ይችላል? ፡፡››ብላ ነበር የጠየቀችው፡፡
ወንድሟ እጆቹን ዘርግቶ ግራና ቀኝ ትከሻዋን በመያዝ ትኩር ብሎ አይኖቹን አይኖቾ ላይ ተክሎ‹‹አዎ ሀብታም መሆን አለብኝ፡፡እኔ ብቻ ሳልሆን አንቺም ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡ለእኛ ሀብታም መሆን የግድ ነው፡፡እኔ ላንቺ ስል ሀብታምና ብዙ ብር ያለው ሰው መሆን እፈልጋለሁ፡፡አንቺም ለእኔ ስትይ እንደዛው ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡››ነበር ያላት
‹‹እንዴት ግን..?ትምህርታችንን ከሶስተኛ ክፍል እንዳቋረጥን ነው፡፡ሳንማር እንዴት ነው ሀብታም ልንሆን የምንችለው?››
‹‹እንችላለን፡፡ማለቴ ሳይማሩ ሀብታም መሆን የሚቻል ይመስለኛል፡፡ያለበለዚያ ቡዙ የተማሩ ሆነው ምንም ብር የሌለቸውና አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች ደግሞ ሀብታሞች ሆነው አናገኝም ነበር፡፡አዎ እንዴት እንደሆነ ለጊዜው ባላውቅም ሳይማሩም ሀብታም መሆን እንደሚቻል እርግጠኛ ነኝ፡፡››አላት፡፡
አዎ..የወደፊት ህልማቸውን በተመለከተ ወንድሟ የሚያወራው ነገር በጣም መሳጭ እና አጓጊ ሆኖ ነበር ያገኘችው፡፡ቢሆንም ግን እንዴት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል በወቅቱ ምንም ፍንጭ አልታያትም፡፡ግን ደግሞ የወንድሟን ንግግር የሞኝ ቅዠት አድርጋም አልወሰደችውም፡፡ ወንድሟን አይደለም በዛን ጊዜ አሁንም ታምነዋለች፡፡ከፍቅር የመነጨ እምነት፡፡
እርግጥ እሷም ከእሱ ጋር ተቀራራቢ የሆነ ሀሳብ ሁሌ በውስጧ ታሰላስል ነበር፡፡ስታድግ የተወለዱበትንና ያደጉበትን የወላጆቾን ቤት መልሳ መግዛት የዘወትር ምኞቷ ነበር፡፡አዎ በወቅቱ እቤቱን የአባታቸው የልብ ጓደኛው በነበረ ሰው ባለቤትነት ተይዟል፡፡ ወላጆቻቸው ሞተው ወር እንኳን ሳይሞላው ነበር ከመሟቱ በፊት ለስራ ብሎ ብዙ ሚሊዬን ብር ተበድሮኛል ብሎ የተናገረው፡፡ብዙም ሳይቆይ የተናገረውን የሚያረጋግጥለት ሰንድ አቀረበ፡፡ከዛ በቀላሉ በፍርድ ቤት ከሶ ወላጆቻቸው ሞተው በተቀበሩ በሶስተኛው ወር እቤቱን ተረክበ፡፡ለእነሱ ቀርቦ የሚከራከርላቸውም ሆነ ወስዶ የሚያሳድጋቸው አንድም ዘመድ መቅረብ ስላልቻለ …ሰውዬው ጎዳና ጣላቸው የሚለውን የሰው አፍ ብቻ በመፍራት ወስዶ ለማደጎ ቤት አስረከባቸው፡፡ኑሀሚ በዛ ጮርቃ እድሜዋ ላይ ሆና እንኳን ያ ሁሉ የተወሳሰበ ቲያትር መሰል አሻጥር ፈፅሞ አይዋጥላትም ነበር፡፡ያንን ቤት በጣም ትወደዋለች፡፡ልጅነቷ ያለው እዛ ቤት ውስጥ ነው፡፡ሳቅና ደስታዋ እዛ ቤት የሆነ ቁምሳጥን ወይም የኮመዲኖ ኪስ ውስጥ የተቆመለፈበት ነበር የሚመስላት፡፡እና አንድ ቀን ተሳክቶላት ያንን ቤት ማስመለስና የራሳቸው ማድረግ ብትችል እናትና አባቷንም በከፊልም ቢሆን ከሞት አለም ማስመለስ እንደሆነ አድርጋ ነበር የምትቆጥረው ፡፡ዘወትር ትንሽ በከፋት ቁጥር የሚተኙበትን መኝታ ቤት ትዝ ይላታል፤እናቷ ምግብ የምታበስልበት ኪችን ሙሉ ስዕሉ በአእምሮዋ ይመላለስባት ነበር፡፡አባቷ በእረፍት ቀኑ ቢጃማ ለብሶ በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ሲያነብ …እሷ ድክ ድክ እያለች ከሳሎን መጥታ ታፋው ላይ በመቀመጥ ከኪሱ ስልኩን አውጥታ ጌም ስትጫወት….
👍72❤9👎2👏2
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ስራው "የፍቅርና የጋብቻ አማካሪነት ነው።የተማረው ፍልስፍና ነው።ሁለተኛ ዲግሪውን ግን አሜሪካ ሄዶ በስነልቦና መስራት ችሏል፡፡በፍቅርና ጋብቻ አማካሪነት የሰራውም እዛው አሜሪካ ነው….ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ሶስት አመት ተቀጥሮ ሰርቶል፡፡አሜሪካዊያኑ በፍቅርና በጋብቻ ጉዳይ ችግር ሲያጋጥማቸው ባለሞያ ጋር መሄድና ድጋፍ ማግኘት ባህላቸው ነው፡፡በመጀመሪያ ወደትዳር ከመግባታቸው በፊት ማድረግ ስለሚገባቸው ስነልቦናዊ ቅድመ ዝግጅት ለማወቅ ባለሞያው ጋር ይሄዳሉ..ትዳር ውስጥ ገብተው ችግር ሲያጋጥማቸው…እርስ በርስ ያለው ተግባቦታቸው አመርቂ ካልሆነ…የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት የሚያጨቃጭቃቸው ከሆነ…የወሲብ አለመጣጣም በመሀከላቸው ካለ ብቻ ማንኛውንም ችግር በመሀከላቸው ከተፈጠረ ወደ ጋብቻ አማካሪ ሄዶ ሞያዊ ምክር መጠየቅና ከዛም የሚሰጣቸውን ምክርና ትዕዛዝ ለየብቻም ሆነ አንድላይ በመተግበር ችግሩን ለመቅረፍ የሚያደርጉት ጥረት ያስቀናል፤ሌላው ይቅር ጋብቻቸው እንደማይሰራ እርግጠኛ ከሆኑ እንኳን ጤናማና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዴት መለያየትና ጓደኛሞች ሆኖ መቀጠል እንደሚችሉ ምክር ለማግኘት ተያይዘው ወደ ጋብቻ አማካሪ ቢሮ ይሄዳሉ..ይህ ጉዳይ በጣም ነበር የሚያስገርመው፡፡በተለይ በመሀከላቸው ልጆች ካሉ ለየብቻ ሆነው እራሱ
የልጆቻቸውን ስነልቦና ጠብቀው እንዴት ተግባባተው ማሳደግ እንዳለባቸው ዝርዝር መመሪያ ከአማካሪዎች በመስማት ያንን ሳያዛንፉ በመተግበር የልጆቻቸውን ደስታ ሆነ የእነሱን ሰላም ይጠብቃሉ፡፡ያም ሆኖ ግን ምንም እንኳን በስራው በጣም ደስተኛና ጥሩ ገቢ የሚያገኝበት ቢሆንም ከአምስት አመት በኃላ ጠቅልሎ ወደሀገሩ ተመለሰ….ሲሄድ መቼም ላይመለስ ነበር…..ሀገር ቤት ባሉ ነገሮች ጠቅላላ ተስፋ ቆርጦ ነበር…ግን እንዲመለስ የሚያስገድደው ቁራጭ ምክንያት አገኘ……እና ተመለሰ፡፡
ሰለሞን ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሰ መጀመሪያ ተቀጥሮ ለመስራት ስራ ለማፈላለግ ሞክሮ ነበር….።አስቴር ግን የራሱን ስራ መጀመር እንዳለበት በተደጋጋሚ ጊዜ ግፊት ስታደርግበት እራሱን ከተበታተንበት ሰበሰበና እና መኝታ ቤቱ ውስጥ ገብቶ በላዩ ላይ ዘጋና ስብሰባ ተቀመጠ።አስቴር የልጅነት ጓደኛው እናም ደግሞ ፍቅሩ ነች…ወጣት ሲሆኑ ደግሞ እህቱ ሆነች…እስከአሁንም እህቱ ሆና ቀረች..እሱ በልቡ ተመልሳ ፍቅሩ እንድትሆን ነው የሚመኘው….አላማውም እቅዱም ያ ነው..እሷ ግን ያንንን መስመር ጠርቅማ ዘግታበት አባቱን አባቷ እናቱን እናቷ አድርጋ ለእሱ ደግሞ እህቱ ሆናለች፡፡
ከልጅነቱ ጀምሮ ነው የሚያውቃት፡፡ ገና ሰባት ወይ ስምንት አመቱ ላይ…የእናቷን ጠርዙ የነተበ የቀሚስ ጫፍ በትናንሽና ለስላሳ እጆቾ ጨምድዳ ይዛ ስርስሯ ኩስ ኩስ እያለች ስትመጣ ነበር የሚያውቃት…የዛን ጊዜውን የልጅነት መልኳን አሁንም በአእምሮው ሰሌዳ ላይ በጉልህ ተስሎ ይገኛል..በአጭሩ ተቆርጦ እርስ በርሱ ተጠቅልሎ የተንጨፈረረ ወርቃማ ፀጉር…ጎላ ጎላ ብላው በፍርሀት የሚንካባለሉ አይኖች…በእንባና በአቧራ ብራብሬ የሆነ አሳዛኝ ፊት….ልክ የግቢው አጥር ተከፍቶላቸው የፊትለፊቱን ትልቁን የሳሎን በራፍ አልፈው ወደጓሮ ሲዞሩ ከኃላ ተከትሎቸው ይሄዳል…እናትዬውን ተከትላ ማድቤት ስትገባ ተከትሏቸው ይገባል…
‹‹የእኔ ልጅ፣ እስኪ እኔ ስራዬን ልስራበት አንቺ ከሰሎሞን ጋር አብራችሁ ተጫወቱ››እያለች እናትዬው ታባብላታለች…እሷም የእናትዬውን ልመና ተቀብላ ከእሱ ጋር ለመጫወት ፍቃደኛ እንድትሆን በአይኖቹ ጭምር ይለማመጣታል….የተቋጠረ ግንባሯን ሳትፈታ በቀሰስተኛ እርምጃ ወደእሱ ትጠጋለች…በደስታ አጇን አፈፍ አድርጎ ይይዛትና እየጎተተ ወደትልቁ ቤት ይዞት ይሄዳል…ከታላቅ እህቱ ጋር በጋራ ወደሚኖርበት መኝታ ክፍላችው ይዞት ይገባል፣..ያሉትን መጫወቻዎች ሁሉ ከየመደርደሪያዎቹን ከየአልጋ ስሩ እየጎተተ ያወጣና ፊት ለፊቷ ወለሉ ላይ ይቆልላል፣ለእሱ የሰለቹትን መጫወቻዎች ለእሷ ብርቅ ነበሩ….እናትዬው እነሱ ቤት በተመላላሽነት በሳምንት ሶስት ቀን ትሰራለች፡፡እና እነዛን ሶስት ቀናት በናፍቆትና በፍቅር ነበር የሚወዳቸው… ሳምንቱን ሙሉ ለምን እንዳማይመጡ ይገርመው ነበር..ከዛ አባቱ እሱን አንደኛ ክፍል አስመዝግቦ ትምህርት ሲያስጀምረው ለእሷም እንደዛው ደብተርና ዩኒፎርም ገዝቶ እሱ የሚማርበት ትምህርት ቤት እናቷ እንድታስመዘግባት አደረገ…አንድ ትምህርት ቤት አንድ ክፍል መማር ጀመሩ…ይሄ ደግሞ የሚገናኙበትን የቀን ብዛትና አጋጣሚ አሰፋው…..ጓደኝነታቸው አብሮ ዕቃ ዕቃ ከመጫወት የተጀመረ ….ከዛ ኤለመንተሪ ጀምረው እስከ ሀይ እስኩል በተመሳሳይ ጊዜ በተመሳሳይ ክፍል ውስጥ ነው የተማሩት።
የተወሰኑ ክፍሎችን አንድ ክፍል ጥቂት ክፍሎችን ደግሞ አንድ መቀመጫ ላይም አብረው ተቀምጠው የመማር አጋጣሚዋች ነበሯቸው።ስለዚህ እሷ ልክ አብረውት እንደተወለድ ወንድሞቹ እና እህቱ እድሜ ልኩን ነው የሚያውቃት፡፡
ፍቅር የጀመሩት 8ተኛ ክፍል ሲማሩ ነው።በወቅቱ እሱ 8ተኛ ቢ ሲማር እሷ ደግሞ 8ተኛ ኤፍ ክፍል ነበረች።ግን ቢሆንም ብዙውን ጊዜ ወደት/ቤት ሲሄድና ወደሰፈር ሲመለሱ ተጠራርተውና ተጠባብቀው ነበር።እና አንድ ቀን ከትምህርት ቤት ሲወጡ እየጠበቀችው ነበር።አብረው ወደቤት መመለስ ቢጀምሩም ግን አንደበቷ እንደተቆለፈና እንደተበሳጨች ነበር...ምን እንደሆነች ቢጠይቃትም በቀላሉ ልትነግረው አልቻለችም..በኋላ በስንት ጭቅጭቅ ከቦርሳዋ አንድ ወረቀት አውጥታ ሰጠችው።ምንድነው? ብሎ በጉጉት ተቀብሎ አነበበው።
አስቴርዬ የእኔ ቆንጆ..የፍቅርሽ ፍላፃ ልቤ ላይ ነው የተሰካው….እስካሁን ሰንኮፉን
አልነቀልኩትም…ያልነቀልኩት ሲሰካብኝ ከነበረው ጊዜ በላይ ስነቅለው ያመኝ ይሁን በሚል ስጋት ነው…….ምን አልባት አንቺው በትንፋሽሽ አዘናግተሸ በልስልስ እጆችሽ ቀስ ብለሽ ብትነቅይልኝ መልካም ይሆን ይመስለኛል፡፡፡አንቺ እኮ ከአለም ሴቶች ጭምር ተወዳዳሪ
የሌለሽ ውብ ነሽ።እኔ አፍቃሪሽ በአንቺ ፍቅር መንገላታት ከጀመርኩ አመታት አልፈዋል።ግን እስከዛሬ ስቃዬን በውስጤ አፍኜ ህመሜን የቻልኩት ከጓደኛዬ ከሰለሞን ጋር ግንኙነት ያላችሁ ስለሚመስለኝ ነበር።ግን በቀደም ወኔዬን አሰባስቤ ስጠይቀው ጓደኛሞች ብቻ እንደሆናችሁ ነገረኝና ነፍሴን በሀሴት አስጨፈራት።እና ውዴ አንቺስ ምን ትያለሽ...
?መልስሽን በጉጉት እጠብቃለሁ... የአንቺው አፍቃሪ መስፍን ጋዲሳ›› ይል ነበር።
አነበበውና ግራ የመጋባትና የመደነጋገር ስሜት ተሠማው..በደብዳቤው ላይ እንደተጠቀሰው በቀደም በብዙ ጓደኞቻቸው መካከል ስለፍቅር አንስተው ሲያወሩ መስፍን እንደቀልድ ‹‹አስቴርና ሰለሞን ፍቅረኛሞች ናቸው›› አለ ወዲያው ሰለሞን ከአፉ ተቀበለና
‹‹እውነት አይደለም እኔና አስቴር ፍቅረኛሞች ሳንሆን ጓደኛሞች ነን ››ብሎ መልስ ሰጠ ።ነገሩ በዚህ ተደመደመ።ደብዳቤውን ባነበበበት ወቅት ግን መሠፍን ሆነ ብሎ ለገዛ የግል ጥቅሙ ጥያቄውን ጠይቆት እንደነበረና እሱንም ማኖ እንዳስነካው ገባውና በጅልነቱ ተበሳጨ።
ግን ደግሞ የአስቴር ወቅታዊ ኩርፊያ አልገባውም ነበር።‹‹መስፍን ደብዳቤ ለፃፈላት እኔን ለምን ልታኮርፈኝ ቻለች?››እራሱን ጠየቀ
"እና እኔ ምን አጠፋው..የምታኮርፊኝ?"ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ስራው "የፍቅርና የጋብቻ አማካሪነት ነው።የተማረው ፍልስፍና ነው።ሁለተኛ ዲግሪውን ግን አሜሪካ ሄዶ በስነልቦና መስራት ችሏል፡፡በፍቅርና ጋብቻ አማካሪነት የሰራውም እዛው አሜሪካ ነው….ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ሶስት አመት ተቀጥሮ ሰርቶል፡፡አሜሪካዊያኑ በፍቅርና በጋብቻ ጉዳይ ችግር ሲያጋጥማቸው ባለሞያ ጋር መሄድና ድጋፍ ማግኘት ባህላቸው ነው፡፡በመጀመሪያ ወደትዳር ከመግባታቸው በፊት ማድረግ ስለሚገባቸው ስነልቦናዊ ቅድመ ዝግጅት ለማወቅ ባለሞያው ጋር ይሄዳሉ..ትዳር ውስጥ ገብተው ችግር ሲያጋጥማቸው…እርስ በርስ ያለው ተግባቦታቸው አመርቂ ካልሆነ…የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት የሚያጨቃጭቃቸው ከሆነ…የወሲብ አለመጣጣም በመሀከላቸው ካለ ብቻ ማንኛውንም ችግር በመሀከላቸው ከተፈጠረ ወደ ጋብቻ አማካሪ ሄዶ ሞያዊ ምክር መጠየቅና ከዛም የሚሰጣቸውን ምክርና ትዕዛዝ ለየብቻም ሆነ አንድላይ በመተግበር ችግሩን ለመቅረፍ የሚያደርጉት ጥረት ያስቀናል፤ሌላው ይቅር ጋብቻቸው እንደማይሰራ እርግጠኛ ከሆኑ እንኳን ጤናማና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዴት መለያየትና ጓደኛሞች ሆኖ መቀጠል እንደሚችሉ ምክር ለማግኘት ተያይዘው ወደ ጋብቻ አማካሪ ቢሮ ይሄዳሉ..ይህ ጉዳይ በጣም ነበር የሚያስገርመው፡፡በተለይ በመሀከላቸው ልጆች ካሉ ለየብቻ ሆነው እራሱ
የልጆቻቸውን ስነልቦና ጠብቀው እንዴት ተግባባተው ማሳደግ እንዳለባቸው ዝርዝር መመሪያ ከአማካሪዎች በመስማት ያንን ሳያዛንፉ በመተግበር የልጆቻቸውን ደስታ ሆነ የእነሱን ሰላም ይጠብቃሉ፡፡ያም ሆኖ ግን ምንም እንኳን በስራው በጣም ደስተኛና ጥሩ ገቢ የሚያገኝበት ቢሆንም ከአምስት አመት በኃላ ጠቅልሎ ወደሀገሩ ተመለሰ….ሲሄድ መቼም ላይመለስ ነበር…..ሀገር ቤት ባሉ ነገሮች ጠቅላላ ተስፋ ቆርጦ ነበር…ግን እንዲመለስ የሚያስገድደው ቁራጭ ምክንያት አገኘ……እና ተመለሰ፡፡
ሰለሞን ወደ ሀገር ቤት እንደተመለሰ መጀመሪያ ተቀጥሮ ለመስራት ስራ ለማፈላለግ ሞክሮ ነበር….።አስቴር ግን የራሱን ስራ መጀመር እንዳለበት በተደጋጋሚ ጊዜ ግፊት ስታደርግበት እራሱን ከተበታተንበት ሰበሰበና እና መኝታ ቤቱ ውስጥ ገብቶ በላዩ ላይ ዘጋና ስብሰባ ተቀመጠ።አስቴር የልጅነት ጓደኛው እናም ደግሞ ፍቅሩ ነች…ወጣት ሲሆኑ ደግሞ እህቱ ሆነች…እስከአሁንም እህቱ ሆና ቀረች..እሱ በልቡ ተመልሳ ፍቅሩ እንድትሆን ነው የሚመኘው….አላማውም እቅዱም ያ ነው..እሷ ግን ያንንን መስመር ጠርቅማ ዘግታበት አባቱን አባቷ እናቱን እናቷ አድርጋ ለእሱ ደግሞ እህቱ ሆናለች፡፡
ከልጅነቱ ጀምሮ ነው የሚያውቃት፡፡ ገና ሰባት ወይ ስምንት አመቱ ላይ…የእናቷን ጠርዙ የነተበ የቀሚስ ጫፍ በትናንሽና ለስላሳ እጆቾ ጨምድዳ ይዛ ስርስሯ ኩስ ኩስ እያለች ስትመጣ ነበር የሚያውቃት…የዛን ጊዜውን የልጅነት መልኳን አሁንም በአእምሮው ሰሌዳ ላይ በጉልህ ተስሎ ይገኛል..በአጭሩ ተቆርጦ እርስ በርሱ ተጠቅልሎ የተንጨፈረረ ወርቃማ ፀጉር…ጎላ ጎላ ብላው በፍርሀት የሚንካባለሉ አይኖች…በእንባና በአቧራ ብራብሬ የሆነ አሳዛኝ ፊት….ልክ የግቢው አጥር ተከፍቶላቸው የፊትለፊቱን ትልቁን የሳሎን በራፍ አልፈው ወደጓሮ ሲዞሩ ከኃላ ተከትሎቸው ይሄዳል…እናትዬውን ተከትላ ማድቤት ስትገባ ተከትሏቸው ይገባል…
‹‹የእኔ ልጅ፣ እስኪ እኔ ስራዬን ልስራበት አንቺ ከሰሎሞን ጋር አብራችሁ ተጫወቱ››እያለች እናትዬው ታባብላታለች…እሷም የእናትዬውን ልመና ተቀብላ ከእሱ ጋር ለመጫወት ፍቃደኛ እንድትሆን በአይኖቹ ጭምር ይለማመጣታል….የተቋጠረ ግንባሯን ሳትፈታ በቀሰስተኛ እርምጃ ወደእሱ ትጠጋለች…በደስታ አጇን አፈፍ አድርጎ ይይዛትና እየጎተተ ወደትልቁ ቤት ይዞት ይሄዳል…ከታላቅ እህቱ ጋር በጋራ ወደሚኖርበት መኝታ ክፍላችው ይዞት ይገባል፣..ያሉትን መጫወቻዎች ሁሉ ከየመደርደሪያዎቹን ከየአልጋ ስሩ እየጎተተ ያወጣና ፊት ለፊቷ ወለሉ ላይ ይቆልላል፣ለእሱ የሰለቹትን መጫወቻዎች ለእሷ ብርቅ ነበሩ….እናትዬው እነሱ ቤት በተመላላሽነት በሳምንት ሶስት ቀን ትሰራለች፡፡እና እነዛን ሶስት ቀናት በናፍቆትና በፍቅር ነበር የሚወዳቸው… ሳምንቱን ሙሉ ለምን እንዳማይመጡ ይገርመው ነበር..ከዛ አባቱ እሱን አንደኛ ክፍል አስመዝግቦ ትምህርት ሲያስጀምረው ለእሷም እንደዛው ደብተርና ዩኒፎርም ገዝቶ እሱ የሚማርበት ትምህርት ቤት እናቷ እንድታስመዘግባት አደረገ…አንድ ትምህርት ቤት አንድ ክፍል መማር ጀመሩ…ይሄ ደግሞ የሚገናኙበትን የቀን ብዛትና አጋጣሚ አሰፋው…..ጓደኝነታቸው አብሮ ዕቃ ዕቃ ከመጫወት የተጀመረ ….ከዛ ኤለመንተሪ ጀምረው እስከ ሀይ እስኩል በተመሳሳይ ጊዜ በተመሳሳይ ክፍል ውስጥ ነው የተማሩት።
የተወሰኑ ክፍሎችን አንድ ክፍል ጥቂት ክፍሎችን ደግሞ አንድ መቀመጫ ላይም አብረው ተቀምጠው የመማር አጋጣሚዋች ነበሯቸው።ስለዚህ እሷ ልክ አብረውት እንደተወለድ ወንድሞቹ እና እህቱ እድሜ ልኩን ነው የሚያውቃት፡፡
ፍቅር የጀመሩት 8ተኛ ክፍል ሲማሩ ነው።በወቅቱ እሱ 8ተኛ ቢ ሲማር እሷ ደግሞ 8ተኛ ኤፍ ክፍል ነበረች።ግን ቢሆንም ብዙውን ጊዜ ወደት/ቤት ሲሄድና ወደሰፈር ሲመለሱ ተጠራርተውና ተጠባብቀው ነበር።እና አንድ ቀን ከትምህርት ቤት ሲወጡ እየጠበቀችው ነበር።አብረው ወደቤት መመለስ ቢጀምሩም ግን አንደበቷ እንደተቆለፈና እንደተበሳጨች ነበር...ምን እንደሆነች ቢጠይቃትም በቀላሉ ልትነግረው አልቻለችም..በኋላ በስንት ጭቅጭቅ ከቦርሳዋ አንድ ወረቀት አውጥታ ሰጠችው።ምንድነው? ብሎ በጉጉት ተቀብሎ አነበበው።
አስቴርዬ የእኔ ቆንጆ..የፍቅርሽ ፍላፃ ልቤ ላይ ነው የተሰካው….እስካሁን ሰንኮፉን
አልነቀልኩትም…ያልነቀልኩት ሲሰካብኝ ከነበረው ጊዜ በላይ ስነቅለው ያመኝ ይሁን በሚል ስጋት ነው…….ምን አልባት አንቺው በትንፋሽሽ አዘናግተሸ በልስልስ እጆችሽ ቀስ ብለሽ ብትነቅይልኝ መልካም ይሆን ይመስለኛል፡፡፡አንቺ እኮ ከአለም ሴቶች ጭምር ተወዳዳሪ
የሌለሽ ውብ ነሽ።እኔ አፍቃሪሽ በአንቺ ፍቅር መንገላታት ከጀመርኩ አመታት አልፈዋል።ግን እስከዛሬ ስቃዬን በውስጤ አፍኜ ህመሜን የቻልኩት ከጓደኛዬ ከሰለሞን ጋር ግንኙነት ያላችሁ ስለሚመስለኝ ነበር።ግን በቀደም ወኔዬን አሰባስቤ ስጠይቀው ጓደኛሞች ብቻ እንደሆናችሁ ነገረኝና ነፍሴን በሀሴት አስጨፈራት።እና ውዴ አንቺስ ምን ትያለሽ...
?መልስሽን በጉጉት እጠብቃለሁ... የአንቺው አፍቃሪ መስፍን ጋዲሳ›› ይል ነበር።
አነበበውና ግራ የመጋባትና የመደነጋገር ስሜት ተሠማው..በደብዳቤው ላይ እንደተጠቀሰው በቀደም በብዙ ጓደኞቻቸው መካከል ስለፍቅር አንስተው ሲያወሩ መስፍን እንደቀልድ ‹‹አስቴርና ሰለሞን ፍቅረኛሞች ናቸው›› አለ ወዲያው ሰለሞን ከአፉ ተቀበለና
‹‹እውነት አይደለም እኔና አስቴር ፍቅረኛሞች ሳንሆን ጓደኛሞች ነን ››ብሎ መልስ ሰጠ ።ነገሩ በዚህ ተደመደመ።ደብዳቤውን ባነበበበት ወቅት ግን መሠፍን ሆነ ብሎ ለገዛ የግል ጥቅሙ ጥያቄውን ጠይቆት እንደነበረና እሱንም ማኖ እንዳስነካው ገባውና በጅልነቱ ተበሳጨ።
ግን ደግሞ የአስቴር ወቅታዊ ኩርፊያ አልገባውም ነበር።‹‹መስፍን ደብዳቤ ለፃፈላት እኔን ለምን ልታኮርፈኝ ቻለች?››እራሱን ጠየቀ
"እና እኔ ምን አጠፋው..የምታኮርፊኝ?"ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
👍68❤13🔥2
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
👍56❤12
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
==================
ተው በአያትህ አትፍረድ…ማንኛውም በቃኝ መመልኮስ ፈልጋለው ብሎ እራሱን ከአለም ለመለየት የወሰነ ሰው ማድረግ ያለበት ልክ እሷቸው እንዳደረጉት ነው፡፡የምልኩስና ህይወትን ለመንፈሳዊ መንገድ ራስን አሳልፎ መስጠት ነው፡፡ከአለም ሆነ ከገዛ ዘመድ ምንም ነገር አለመጠበቅ ነው፡፡ከዛም አልፎ ለአለምም ሆነ ለገዛ ዘመድ ምንም አይነት ኃላፊነት አለመቀበል ማለት ነው፡፡አንድ ሰው ከመለኮሰ ልጄ ለምን ሳይጦረኝ ወንድሜ ለምን ሳይጠይቀኝ ብሎ የመጠየቅም ሆነ የመውቀስ መብት የለውም..በዛውም ልክ እናቴን መጦር ነበረብኝ..ወንድሜን መርዳት ይጠበቅብኛል..የልጅ ልጆቼን መንከባከብ የእኔ ኃላፊነት ነው ከሚለው ማህበራዊ ኃላፊነቶችም ራሱን ነፃ ማድረግ አለበት፡፡
ሙሉ ትኩረቱ መንፈሳዊ ብልፅግና እራስን ማጎልበት ላይ መሆን አለበት፡፡ለዘመዱም ሆነ ለመላ አለሙ እኩል ፀሎት ማድረግ ነው የሚጠበቅባቸው፡፡ስለክርስቶስ ፍቅር መትጋት ፤ዳቢሎስ ለመጥላትና ለመርገም ግን ጊዜ ከማባከን መቆጠብ ነው ከእነሱ የምጠበቀው…ምክንያቱም በአንድ ንፅህ ልብ ፍቅርና ጥላቻ እውነትና ሀሰት ክፋትና መልካምነት ተጎራብተው መኖር አይቻላቸውምና፡፡ሁለቱንም አቻችሎ እያኖረ ያለ ልብ የመንፈሳዊ ሰው ልብ ሊባል አይችልም፡፡እና በአያትህ ውሳኔና ድርጊት ቅንጣት ያህል ቅሬታ እንዳያድርብህ ..እንደውም በተቃራኒው በረከታቸው እንዲጠብቅህ ብቻ ነው መመኘት ያለብህ››
‹‹ትክክል ነሽ እቴቴ…ለማንኛውም አንቺን ደጋግሜ አመሰግናለሁ››
‹‹እኔም አመሰግናለው ልጄ….ይሄ ፀባይህ መቼም እንዳይቀየር .አሁን ምን ማድረግ እንዳለብህ የምትወስነው አንተ ነህ…እንደእኔ እንደእኔ ኮሌጅ ገብተህ የሙያ ትምህርት ለመማር በመወሰንህ በጣም ጥሩ ነው…ሞያ ያለው ሰው ወድቆ አይወድቅም…ቢያንስ የሆነ ተባራሪ ስራ ሰርቶ ወይም የሆነ ነገር ጠጋግኖ የእለት ጉርሱን ያገኛል..ቀስ እያልክ ደግሞ በሂደት የራስህን ድርጅት የማቋቋም እድልም ይኖርሀል….እና እኔ እናትህ ሁሌም በውሳኔህ አብሬህ ነኝ፡፡››
‹‹አቴቴ አታስቢ ከሰሎሜና ከአላዛር ጋር ተነጋግረን ወስነናል…የሆነ ሞያ እንማራለን ››
‹‹ጎሽ ልጄ እንደዛ ነው…ሰሎሜንም ስለምትንከባከባት አመሰግናለሁ››
‹‹እንዴ እቴቴ እህቴ አይደለችም እንዴ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…እንደውም ትልቁ ላመሰግንህ የሚገባው እሷን በተመለከተ ነው…እናንተ ላትሰሙ ትችላላችሁ ፡፡ከጎረመሰችና ለአቅመ አዳምና ሄዋን ከደረሳችሁ በኃላ የሰፈሩ ሰው በሰበብ አስባብ እያደረገ…‹‹ይሄ ጎረምሳ ልጇን አስረግዞ ጉድ ያደርጋታል….››ሲሉኝ፡፡‹‹እንዚህ ልጆች እንዳይሳሳቱና አጉል ችግር ውስጥ እንዳይከቱሽ›› እያሉ ሲመክሩኝ፡፡እኔ ግን ከልጄ ይልቅ በአንተ ላይ ሙሉ እምነት ነበረኝ…አለማየሁማ እኔ እናቱን እንዳፍርና አንገቴን አንቄ እራሴን እንዳጠፋ አያደርገኝም….የገዛ እህቱን የሆነ ነገር አድርጎ የሰፈርተኛውን ሟርት እውን በማድረግ እኔ እናቱን ወደመቃብር አይልከኝም››የሚል ፅኑ እምነት ነበረኝ፡፡እናም ቤተክርስቲያን ስሄድ ጌታ ሆይ ለሁለቱም ልጆቼ ልቦና ስጥልኝ ብዬ ከመፀለይ ውጭ በእናንተ ላይ ምንም አይነት ተፅእኖም ሆነ ክትትል አድርጌ አላውቅም ፤ወደፊትም ስለማምናችሁ ስጋት የለብኝም…እና ለዚህም አመሰግናለው፡፡
አለማየሁ አቴቴ ስለእሱና ስለሰሎሜ እያንዳንዱን ቃላት ከአንደበታቸው አውጥተው በተናገሩት ቁጥር ከልቡ የተወሰነ አካሉ እየተሸራረፈ ሲረግፍ ይታወቀው ነበር..በቃ የአላዛር የእንጀራ እናት ከቀናት በፊት የሰነጣጠቀችው ልቡን አሁን ሙሉ በሙሉ ተሰባበረ፡፡ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሁለቱም የፍቅር ክንፎቹ ተቆርጦ ሲወድቅበት ..መቋቋም ከሚችለው በላይ ፍፅም ተስፋ መቁረት ውስጥ ነው የገባው፡፡‹‹እቴቴ ..ይሄን ሁሉ ሰቀቀን ስላሳለፍሽ ቅርታ….አይዞሽ አታስቢ …እኔ ልጅሽ ነኝ ልጅሽም እንደሆንኩ እቀጥላለሁ፡፡››ሲል ነበር በደመነፍስ ቃል የገባላቸው፡፡
በዚህ ሁኔታ ነበር ሁለቱም ተመሰጋግነውና ተላቅሰው ከቤተክርሰቲያን የተመለሱት፡፡
ከዛ በኃላ ግን አለማየሁ ሁሉም ነገሩ ነው የተመሰቃቀለበት፡፡ማትሪክ ውጤት አይቶ ዩኒቨርሲቲ መግባት እንደማይችል ያወቀ ሰሞን እንኳን እንዲህ መላ ነገሩ አልተተረማመሰም፡፡ከአላዛር እንጀራ እናት በተለያየበት ቀንም የተወሰነ የሚመረኮዘው ተስፋ ነበርው…ከቴቴ ጋር ካወራ በኃላ ግን በቃል ታስሮል….ከሚወዱትና ከሚያከብሩት ሰው አንደበት የወጣ ቃል ደግሞ ከፖሊስ ካቴና የጠበቀ ቀፍድዶ የሚያስር ነው፡፡አሁን ለአስራዘጠኝ አመት ሲንከባከበውና ሲፋለምለት ከነበረው የፍቅር ሀዲድ ተገፍትሮ ወጥቷል…፡፡የሰሎሜን ፍቅር ከልቡ አውጥቶ በአንደበቱ ማወጅ አይችልም…፡፡እንደዛ ካደረገ እናቷን ማሳዘን አንገት ማስደፋት እንደሆነ ገብቷታል፡፡ከሁለት አንዱን መምረጥ ያለበት ጊዜ ላይ እንደሆነ አውቆል፡፡
ልክ የሀይስኩል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቀ. ለሰሎሜ ያለውን ፍቅር ለማፈንዳትና እሷን ከተቀናቃኞቹ ሁሴንና አላዛር ፈልቅቆ ራሱ ለማድረግ የአመታት እቅድ ነበረው…ያ ቀን እስኪደርስ በመመኘት ብዙ ቀን እንቅልፍ አጥቶል፡፡ በስንት ጣር ቀኑ ሲደርስ ግን እናቷ ያልጠበቀውን ዱብ እዳ ነገሩት፡፡እሱ እንደውም ይሰጋ የነበረው እንዲህ አይነት ነገር ተፈጥሮ ከሰሎሜ ፍቅር ይነጥለኛል ብሎ ሳይሆን ከአስካለ ጋር የነበረው የድብቅ ፍቅር ሰሎሜ ጆሮ ገብቶ እሷን ያሳጣኝ ይሆን ብሎ ነበር፡፡
ግን ይሄው ጨርሶ ባልጠበቀው መንገድ አሳዳጊ እናቱ እቴቴ እሱና ሰሎሜ በእህት እና ወንድም ስሌት እንዲቀጥሉ እንጂ ፍቅር የሚባል ነገር በመሀከላቸው እንዲበቅል ምንም ፍላጎት እንደሌላቸውና እንደውም እስከሞት ሚያደርስ ሀዘን ላይ እንደሚጥላቸው ግልፅ ባለ አማርኛ ነገርውታል፡፡
እሱ ብቻ ሳይሆን የገዛ ጓደኞቹ አላዛርና ሁሴንም እንደሚያፈቅሯትን በቅርብ በማንኛውም ጊዜ ፍቅራቸውን እንደሚናዘዙላት ያውቃል፡፡ለዚህ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ሶስቱም እሷን እንደሚያፈቅሮት ስለሚያውቁና እርስ በርስም ለዘመናት ሲነጋገሩና ሲወያዩ በመኖራቸው…‹‹.ስንጠይቃት ለየት ያለ ዝግጅት አዘጋጅተን..ሶስታችንም በአንድ ቃል..ሰሎሜ እኛ ሶስቱ ጓደኞችሽ አንቺን ከልጅነታችን ጀምሮ እናፈቅርሻለኝ… ሶስታችንም የእኛ እንድትሆኚ እንፈልጋለን፡፡አንቺ ከሶስታችንን ማንን ትመርጫለሽ…?በውሳኔሽ እንስማማለን፡፡አስበሽበት ከሶስታችን ማንኛችንን እንደምትመርጪ አሳውቂን ››ብለው ሰርፕራይዝ ሊያደርጓትና የመምረጡን እድል ለእሷ ሊሰጡ ገና ዘጠነኛ ክፍል እያሉ ነበር ቃል የተገባቡት፡፡
እና ከእቴቴ ጋር ከማውራቱ ከሳምንት በፊት በሁሴን ሽኝት ላይ ይሄንን ጉዳይ አንስተው ደግሞው ተነጋገርውበት ነበር፡፡ሁሴንም‹‹በቃ አንድ ሴሚስተር ተምሬ ከጨረስኩ በኃላ በሴሚስተር ዝግ ስመጣ እንደተባባልነው እናዳርጋለን›› ብሏቸዋል…እነሱም በሀሳቡ ተስማምተው ነበር፡፡ እስከዛ ማንም አፈቅርሻለው ብሎ እንዳይነግራት ተማምለው ከእንደገና ቃላቸውን አድሰው ነበር፡፡እና በዚህ ሁሉ ውይይትና ንግግር ሰሎሜ አሱን እንደምትመርጥ ከእነሱ በላይ ሰባና ሰማኒያ ፐርሰንት እድል እንዳለው ያምን ነበር..እንደዛ እንዲያስብ ያደረገው ደግሞ ከጓደኝነታቸውም በላይ እንደእህትና ወንድም አንድ ቤት በመኖራቸው..ቀን ብቻ ሳይሆን ምሽትም ለሊትም አንድ ቤት ውስጥ ስለሚሆኑ …ታፋው ላይ ያለውን ጠባሳ ስለምታውቅና ከጡቷ ዝቅ ብሎ ያለውን የማሪያም ስሞሽ ሰልሚያውቅ…ጭምር ነበር የእሷ ተመራጭ እሱ እንደሚሆን እርግጠኛ የሆነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
==================
ተው በአያትህ አትፍረድ…ማንኛውም በቃኝ መመልኮስ ፈልጋለው ብሎ እራሱን ከአለም ለመለየት የወሰነ ሰው ማድረግ ያለበት ልክ እሷቸው እንዳደረጉት ነው፡፡የምልኩስና ህይወትን ለመንፈሳዊ መንገድ ራስን አሳልፎ መስጠት ነው፡፡ከአለም ሆነ ከገዛ ዘመድ ምንም ነገር አለመጠበቅ ነው፡፡ከዛም አልፎ ለአለምም ሆነ ለገዛ ዘመድ ምንም አይነት ኃላፊነት አለመቀበል ማለት ነው፡፡አንድ ሰው ከመለኮሰ ልጄ ለምን ሳይጦረኝ ወንድሜ ለምን ሳይጠይቀኝ ብሎ የመጠየቅም ሆነ የመውቀስ መብት የለውም..በዛውም ልክ እናቴን መጦር ነበረብኝ..ወንድሜን መርዳት ይጠበቅብኛል..የልጅ ልጆቼን መንከባከብ የእኔ ኃላፊነት ነው ከሚለው ማህበራዊ ኃላፊነቶችም ራሱን ነፃ ማድረግ አለበት፡፡
ሙሉ ትኩረቱ መንፈሳዊ ብልፅግና እራስን ማጎልበት ላይ መሆን አለበት፡፡ለዘመዱም ሆነ ለመላ አለሙ እኩል ፀሎት ማድረግ ነው የሚጠበቅባቸው፡፡ስለክርስቶስ ፍቅር መትጋት ፤ዳቢሎስ ለመጥላትና ለመርገም ግን ጊዜ ከማባከን መቆጠብ ነው ከእነሱ የምጠበቀው…ምክንያቱም በአንድ ንፅህ ልብ ፍቅርና ጥላቻ እውነትና ሀሰት ክፋትና መልካምነት ተጎራብተው መኖር አይቻላቸውምና፡፡ሁለቱንም አቻችሎ እያኖረ ያለ ልብ የመንፈሳዊ ሰው ልብ ሊባል አይችልም፡፡እና በአያትህ ውሳኔና ድርጊት ቅንጣት ያህል ቅሬታ እንዳያድርብህ ..እንደውም በተቃራኒው በረከታቸው እንዲጠብቅህ ብቻ ነው መመኘት ያለብህ››
‹‹ትክክል ነሽ እቴቴ…ለማንኛውም አንቺን ደጋግሜ አመሰግናለሁ››
‹‹እኔም አመሰግናለው ልጄ….ይሄ ፀባይህ መቼም እንዳይቀየር .አሁን ምን ማድረግ እንዳለብህ የምትወስነው አንተ ነህ…እንደእኔ እንደእኔ ኮሌጅ ገብተህ የሙያ ትምህርት ለመማር በመወሰንህ በጣም ጥሩ ነው…ሞያ ያለው ሰው ወድቆ አይወድቅም…ቢያንስ የሆነ ተባራሪ ስራ ሰርቶ ወይም የሆነ ነገር ጠጋግኖ የእለት ጉርሱን ያገኛል..ቀስ እያልክ ደግሞ በሂደት የራስህን ድርጅት የማቋቋም እድልም ይኖርሀል….እና እኔ እናትህ ሁሌም በውሳኔህ አብሬህ ነኝ፡፡››
‹‹አቴቴ አታስቢ ከሰሎሜና ከአላዛር ጋር ተነጋግረን ወስነናል…የሆነ ሞያ እንማራለን ››
‹‹ጎሽ ልጄ እንደዛ ነው…ሰሎሜንም ስለምትንከባከባት አመሰግናለሁ››
‹‹እንዴ እቴቴ እህቴ አይደለችም እንዴ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…እንደውም ትልቁ ላመሰግንህ የሚገባው እሷን በተመለከተ ነው…እናንተ ላትሰሙ ትችላላችሁ ፡፡ከጎረመሰችና ለአቅመ አዳምና ሄዋን ከደረሳችሁ በኃላ የሰፈሩ ሰው በሰበብ አስባብ እያደረገ…‹‹ይሄ ጎረምሳ ልጇን አስረግዞ ጉድ ያደርጋታል….››ሲሉኝ፡፡‹‹እንዚህ ልጆች እንዳይሳሳቱና አጉል ችግር ውስጥ እንዳይከቱሽ›› እያሉ ሲመክሩኝ፡፡እኔ ግን ከልጄ ይልቅ በአንተ ላይ ሙሉ እምነት ነበረኝ…አለማየሁማ እኔ እናቱን እንዳፍርና አንገቴን አንቄ እራሴን እንዳጠፋ አያደርገኝም….የገዛ እህቱን የሆነ ነገር አድርጎ የሰፈርተኛውን ሟርት እውን በማድረግ እኔ እናቱን ወደመቃብር አይልከኝም››የሚል ፅኑ እምነት ነበረኝ፡፡እናም ቤተክርስቲያን ስሄድ ጌታ ሆይ ለሁለቱም ልጆቼ ልቦና ስጥልኝ ብዬ ከመፀለይ ውጭ በእናንተ ላይ ምንም አይነት ተፅእኖም ሆነ ክትትል አድርጌ አላውቅም ፤ወደፊትም ስለማምናችሁ ስጋት የለብኝም…እና ለዚህም አመሰግናለው፡፡
አለማየሁ አቴቴ ስለእሱና ስለሰሎሜ እያንዳንዱን ቃላት ከአንደበታቸው አውጥተው በተናገሩት ቁጥር ከልቡ የተወሰነ አካሉ እየተሸራረፈ ሲረግፍ ይታወቀው ነበር..በቃ የአላዛር የእንጀራ እናት ከቀናት በፊት የሰነጣጠቀችው ልቡን አሁን ሙሉ በሙሉ ተሰባበረ፡፡ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሁለቱም የፍቅር ክንፎቹ ተቆርጦ ሲወድቅበት ..መቋቋም ከሚችለው በላይ ፍፅም ተስፋ መቁረት ውስጥ ነው የገባው፡፡‹‹እቴቴ ..ይሄን ሁሉ ሰቀቀን ስላሳለፍሽ ቅርታ….አይዞሽ አታስቢ …እኔ ልጅሽ ነኝ ልጅሽም እንደሆንኩ እቀጥላለሁ፡፡››ሲል ነበር በደመነፍስ ቃል የገባላቸው፡፡
በዚህ ሁኔታ ነበር ሁለቱም ተመሰጋግነውና ተላቅሰው ከቤተክርሰቲያን የተመለሱት፡፡
ከዛ በኃላ ግን አለማየሁ ሁሉም ነገሩ ነው የተመሰቃቀለበት፡፡ማትሪክ ውጤት አይቶ ዩኒቨርሲቲ መግባት እንደማይችል ያወቀ ሰሞን እንኳን እንዲህ መላ ነገሩ አልተተረማመሰም፡፡ከአላዛር እንጀራ እናት በተለያየበት ቀንም የተወሰነ የሚመረኮዘው ተስፋ ነበርው…ከቴቴ ጋር ካወራ በኃላ ግን በቃል ታስሮል….ከሚወዱትና ከሚያከብሩት ሰው አንደበት የወጣ ቃል ደግሞ ከፖሊስ ካቴና የጠበቀ ቀፍድዶ የሚያስር ነው፡፡አሁን ለአስራዘጠኝ አመት ሲንከባከበውና ሲፋለምለት ከነበረው የፍቅር ሀዲድ ተገፍትሮ ወጥቷል…፡፡የሰሎሜን ፍቅር ከልቡ አውጥቶ በአንደበቱ ማወጅ አይችልም…፡፡እንደዛ ካደረገ እናቷን ማሳዘን አንገት ማስደፋት እንደሆነ ገብቷታል፡፡ከሁለት አንዱን መምረጥ ያለበት ጊዜ ላይ እንደሆነ አውቆል፡፡
ልክ የሀይስኩል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቀ. ለሰሎሜ ያለውን ፍቅር ለማፈንዳትና እሷን ከተቀናቃኞቹ ሁሴንና አላዛር ፈልቅቆ ራሱ ለማድረግ የአመታት እቅድ ነበረው…ያ ቀን እስኪደርስ በመመኘት ብዙ ቀን እንቅልፍ አጥቶል፡፡ በስንት ጣር ቀኑ ሲደርስ ግን እናቷ ያልጠበቀውን ዱብ እዳ ነገሩት፡፡እሱ እንደውም ይሰጋ የነበረው እንዲህ አይነት ነገር ተፈጥሮ ከሰሎሜ ፍቅር ይነጥለኛል ብሎ ሳይሆን ከአስካለ ጋር የነበረው የድብቅ ፍቅር ሰሎሜ ጆሮ ገብቶ እሷን ያሳጣኝ ይሆን ብሎ ነበር፡፡
ግን ይሄው ጨርሶ ባልጠበቀው መንገድ አሳዳጊ እናቱ እቴቴ እሱና ሰሎሜ በእህት እና ወንድም ስሌት እንዲቀጥሉ እንጂ ፍቅር የሚባል ነገር በመሀከላቸው እንዲበቅል ምንም ፍላጎት እንደሌላቸውና እንደውም እስከሞት ሚያደርስ ሀዘን ላይ እንደሚጥላቸው ግልፅ ባለ አማርኛ ነገርውታል፡፡
እሱ ብቻ ሳይሆን የገዛ ጓደኞቹ አላዛርና ሁሴንም እንደሚያፈቅሯትን በቅርብ በማንኛውም ጊዜ ፍቅራቸውን እንደሚናዘዙላት ያውቃል፡፡ለዚህ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ሶስቱም እሷን እንደሚያፈቅሮት ስለሚያውቁና እርስ በርስም ለዘመናት ሲነጋገሩና ሲወያዩ በመኖራቸው…‹‹.ስንጠይቃት ለየት ያለ ዝግጅት አዘጋጅተን..ሶስታችንም በአንድ ቃል..ሰሎሜ እኛ ሶስቱ ጓደኞችሽ አንቺን ከልጅነታችን ጀምሮ እናፈቅርሻለኝ… ሶስታችንም የእኛ እንድትሆኚ እንፈልጋለን፡፡አንቺ ከሶስታችንን ማንን ትመርጫለሽ…?በውሳኔሽ እንስማማለን፡፡አስበሽበት ከሶስታችን ማንኛችንን እንደምትመርጪ አሳውቂን ››ብለው ሰርፕራይዝ ሊያደርጓትና የመምረጡን እድል ለእሷ ሊሰጡ ገና ዘጠነኛ ክፍል እያሉ ነበር ቃል የተገባቡት፡፡
እና ከእቴቴ ጋር ከማውራቱ ከሳምንት በፊት በሁሴን ሽኝት ላይ ይሄንን ጉዳይ አንስተው ደግሞው ተነጋገርውበት ነበር፡፡ሁሴንም‹‹በቃ አንድ ሴሚስተር ተምሬ ከጨረስኩ በኃላ በሴሚስተር ዝግ ስመጣ እንደተባባልነው እናዳርጋለን›› ብሏቸዋል…እነሱም በሀሳቡ ተስማምተው ነበር፡፡ እስከዛ ማንም አፈቅርሻለው ብሎ እንዳይነግራት ተማምለው ከእንደገና ቃላቸውን አድሰው ነበር፡፡እና በዚህ ሁሉ ውይይትና ንግግር ሰሎሜ አሱን እንደምትመርጥ ከእነሱ በላይ ሰባና ሰማኒያ ፐርሰንት እድል እንዳለው ያምን ነበር..እንደዛ እንዲያስብ ያደረገው ደግሞ ከጓደኝነታቸውም በላይ እንደእህትና ወንድም አንድ ቤት በመኖራቸው..ቀን ብቻ ሳይሆን ምሽትም ለሊትም አንድ ቤት ውስጥ ስለሚሆኑ …ታፋው ላይ ያለውን ጠባሳ ስለምታውቅና ከጡቷ ዝቅ ብሎ ያለውን የማሪያም ስሞሽ ሰልሚያውቅ…ጭምር ነበር የእሷ ተመራጭ እሱ እንደሚሆን እርግጠኛ የሆነው፡፡
👍68❤11
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡
‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት
‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››
‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡
አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ
‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡
‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››
‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››
‹‹ድንግልናሽን?››
‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››
‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…
‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡
‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››
‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››
‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››
‹‹ማለት?››
‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡
‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››
‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡
‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡
‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››
‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››
‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››
‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››
‹‹ምን ያስፈራሀል?››
‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››
‹‹እንዴት …?››
‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››
‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››
‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››
‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››
‹‹ማለት?፡፡››
‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡
‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡
‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡
‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡
‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››
‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››
‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡
‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡
አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››
ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡
በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡ ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡
በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡
‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት
‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››
‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡
አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ
‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡
‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››
‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››
‹‹ድንግልናሽን?››
‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››
‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…
‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡
‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››
‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››
‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››
‹‹ማለት?››
‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡
‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››
‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡
‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡
‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››
‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››
‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››
‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››
‹‹ምን ያስፈራሀል?››
‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››
‹‹እንዴት …?››
‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››
‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››
‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››
‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››
‹‹ማለት?፡፡››
‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡
‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡
‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡
‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡
‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››
‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››
‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡
‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡
አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››
ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡
በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡ ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡
በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
👍54❤14👏2
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
ይህ ፋውንዴሽን አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰው በዚህ መንገድ ነበር, አሰበች እንደ ሮቤል ያሉ ሰዎች የወላጆቿ ሀብት የፋውንዴሽኑን የጀርባ አጥንት እንደሆነ ነው የሚያስቡት፣ ገንዘብ በቀላሉ ወደ ሣጥን ውስጥ እንደሚገባ ያስባሉ ። ፣ ከቅርብ ረዳቶቿ ከሆኑ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር፣ በዚህ ስራ ውስጥ ግንኙነቶች ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። ግንኙነቶች፣ መተማመን እና ከፍተኛ የስራ ስሜት ወሳኝ ነገሮች ናቸው። ገንዘቡ ወደፋውንዴሽኑ ከሚገባት ፍጥነት ሚወጣበት ፍጥነት ይበልጣል።ራሄል የፋውንዴሽኑን አስተዳደር ስትረከብ፣ የሂሳብ መዝገቡ አሁን ባለበት ሁኔታ ጤናማ አልነበረም።
ወላጆቿ ጥሩ ልብ ያላቸው የሰው ልጅን ያለልዩነት ለመርዳትና ለማገዝ ከልብ የሚጥሩ ቀና ሰዎች ቢሆኑም የተሳሳቱ ሰዎችን አምነው ስለነበር ለከፍተኛ ምዝበራ ተጋልጠው ነበር።እና ራሄል ስራዋን ከወላጇቾ ሙሉ በሙሉ ከተረከበች በኃላ አጠቃላይ የፋውንዴሽኑን ተቋማዊ አቅም ለማሻሻል ጥቂት አመታትን እና አንዳንድ ከባድ ውሳኔዎችን እንድትወስድ አስገድዷታል፣ከዛ ቀስ በቀስ ፋውንዴሽኑን አሁን ያለበት አቋም ላይ እንዲገኝ ማድረግ ችላለች፡፡ የተቋቋሙ ያገኘውን ገቢ በጥንቃቄ ለተከበሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንደሙዳይ…ሜቅዶኒያ ላሉ ገንዘብን ለታለመለት አላማ ብቻ ለሚያውሉ ተቋማት ያከፋፍላል፡፡ቀዳዳቸውን ይደፍናል ጉድለታቸውን ይሞላል፡፡
‹‹ሮቤል፣ ስለዚህ ጉዳይ አሁን ማውራት አልችልም። አሁንም ከሎዛ ጋር መገናኘት እና ከዚያም ፀጋን ከመዋለ ሕጻናት መውሰድ አለብኝ።ከዛ ቀጥታ ወ.ሮ ላምሮትን ሄጄ አገኛታለው….ደውልላት እና ከአንድ ሰዓት በኋላ እቤቷ እንደምገኝ ንገራት፡፡››አለችው፡፡ ወይዘሮ ላምሮት ብዙ ጊዜዋን እየወሰደች ነበር፣ ሴትየዋን ወደ ሎዛ ለማስተላለፍ አልደፈረችም ፡፡ለዚህ ነው ቀጥታ እራሷ ልታገኛት የወሰነችው፡፡
ቦርሳዋን ይዛ ከቢሯዋ ወጣች፡፡
ከአስራ አራት ደቂቃ በኋላ ወደ መዋዕለ ሕጻናት ማእከሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስትገባ ጎማ በጭቃ ውስጥ ገባ። ቦርሳዋን እና ቁልፏን ይዛ ከመኪናው ውስጥ ዘላ ወጣች፣ ጉልበቷን የበሩን ጠርዝ መታት..አቃሰተች እና ጎንበስ ብላ እያሻሸች መንገዷን ቀጠለች .. የሞባይል ስልኳ እየጠራ ቢሆንም ችላ ብላ የመዋዕለ ሕፃናት ማቆያውን የመስታወት በሮች ከፍታ ወደውስጥ ገባች ፡፡ለአባቷ የገባችው ቃል ኪዳን እና በኤሊያስ አይኖች ውስጥ ያነበበችው ጥርጣሬ ለፀጋ አስፈላጊውን ጊዜ መድቦ ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ቁርጠኛ እንድትሆን አድርጓታል። ከሁሉም በላይ ግን ፀጋ እህቷ ነበረች። እና ምንም አይነት አስቸጋሪ ቢሆንም በክፉ ቀን ቤተሰብ ለቤተሰብ መከታ መሆን እንዳለበት ታምናለች፡፡ ፀጋ ሰዓቱን በትኩረት በምትመለከተው የቀን ተንከባካቢ ሰራተኛ እቅፍ ውስጥ ሆና እየጠበቀቻት ነበር። አፏ እና ጠባብ አይኖቿ ስትመለከት ነገሮች ጥሩ እንዳልሄዱ ገመተች።
‹‹ሴት ልጃችሁን በፕሮግራማችን ስታስመዘግቡ ፖሊሲያችንን በግልፅ አሳውቀናችኋል።›› ሴትዬዋ በጠንካራ ንጭንጭ ተቀበለቻት፡፡
‹‹ይገባኛል... ›› አለች‹‹እና እህቴን በሰዓቱ ስላልወሰድኩ ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ››ስትል አከለችበት ፡፡
‹‹በጣም ዘግይተሻል››የሚለው ቃል አከለችበት ። ጎንበስ ብላ የፀጋን ዳይፐር ከቦርሳ አወጣች እና ከዚያም ወደ እህቷ ተጠጋች ።‹‹ቶሎ ልናገኝሽ ሞክረን ነበር።›› ወይዘሮ ባንቺ ወደ ፀጋ ተመለከተች እና ፊቷን አኮሰታተረች። ያን ጊዜ ነበር ራሄል የልጅቷን በእንባ የታጠበ ጉንጯች ያስተዋለች። ‹‹ፀጋ ጥሩ ቀን አላሳለፈችም። ነርሷ የሙቀት መጠንዋን ስትወስድ ከፍ ብሎ ነበር፣ በተቻለ ፍጥነት ሀኪም ቤት እንድትወስዷት ተናግራለች ።››
‹‹እንዴ አሁን?...ለማለት የፈለኩት ይህ ምን ያህል አጣዳፊ ነው? ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ልውሰዳት ወይስ ሁኔታዋን መከታተል አለብኝ?››ስትል ጠየቀች፡፡
ወይዘሮ ባንቺ ‹‹ወዲያውኑ ብትወስጂያት መልካም ይመስለኛል.. እህትሽ ካለባት የጤና ችግር አንፃር የበለጠ ንቁ መሆን ይገባታል።
‹‹ያንን አስቤ ነው ወደዚህ ያመጣኋት… በቃ ወስዳታለው›› የፀጋ የሰውነት ሙቀት በልብሷ አልፎ እየተሰማት ነው። ላለባት ቀጠሮ ሰዓቷን ለማየት አልደፈረችም። ሆስፒታሉ ከመዋዕለ ህጻናት ብዙም ባለመራቁ አመሰገነች፡፡
ከሃያ ደቂቃ በኋላ ወደ ሆስፒታሉ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ገባች እና በድንገተኛ ክፍል በሮች ቸኩላ ስታልፍ ትዝታዎቹ እየተጣደፉ መጡባት።በእቅፏ ወደተቀመመችው ፀጋ ተመለከተች እና አዲስ ፍርሃት መላ ሰውነቷን ተቆጣጠራት። ወደ መቀበያ ጠረጴዛው እየገሰገሰች ስትሄድ፣ ቀድሞውንስ ይሄን ጉዳይ እንዴት አድርጋት ልትወጣ እንዳሰበች ተገረመች። ላለፉት ስምንት አመታት በድንገት የሚደፈርስ ስሜት እና ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ድንገተኛ ብስጭትን ስትዋጋ ነው የኖረችው። አሁን የአንዲት ቀጫጫ ነርስን ማይረብ ጥያቄዎችን በትዕግስት እየመለሰች ነው።እንደጨረሰች በውስጧ እየበቀሉ ያሉ አሮጌ እና አዲስ ፍራቻዎችን እየታገለች፣ ለሆስፒታሎች ልዩ የሆኑትን የተለመዱ ሽታዎች እያሸተተች በተጨናነቀው የመጠበቂያ ክፍል ውስጥ ተመልሳ ተቀመጠች።
ከድንጋጤዋ የተነሳ መላ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ነው ፡፡ለፀጋ ስትል ትኩረቷን ለመሰብሰብ መሞከር አለባት።ፀጋ እጆቿ ይንቀጠቀጣሉ፣ ከሰውነቷ የሚወጣው ሙቀት በየደቂቃው እየጨመረ ነው። ነርሶቹ በስራ ተጠምደዋል፡፡ችሎታ ያለው እና ኃላፊነት የሚሰማው ዶ ር ለማግኘት ዙሪያውን አማተረች። አንዳቸውም ወደ ራሔል ዞር ብለው አላዩትም።ሰዎች ወንበሮች ላይ ተቀምጠው ይንቆራጥጣሉ፣ አንዳንዶቹ ጎንበስ ብለው ያቃስታሉ፣ ሌሎች ደግሞ ደንዝዘው እያንጓላጅጁ ነው፡፡
እያንዳንዳቸው በራሳቸው መከራና ሀዘን ተይዘዋል..ስለ ራሄል እና በእቅፏ ውስጥ እየተቃጠለች ስላለችው ህፃን ደንታ አልነበራቸውም።ከዚያም ፀጋ እየደነዘዘች ሄደች፡፡ ድንጋጤ የራሄልን ጉሮሮ አነቃት። አምላክ ማንኛውንም ነገር እንደሚያደርግ ብታምን ኖሮ አሁን በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ትጸልይ ነበር።እግዚአብሔር ግን ከዚህ በፊት ከልቧ በፀለየችበት ጊዜ ትኩረት አልሰጣትም ነበር እና አሁንም እሱ ላይ መንጠልጠል አልፈለገችም፡፡ ፀጋ ማቃሰቱን አቁማ እንደገና በመጠኑ ዘና ስትል እፎይታ ተሰማት። ራሄልን ቀና ብላ ተመለከተች፣ታናሽ እህቷ ለስላሳ ቡናማ አይኖቿን ራሄል ላይ አንከባለለችባት፡፡ ራሄል በምላሽ ልቧ ሲዘል ተሰማት። ከዚያም ራቅ ብላ ተመለከተች።
ፀጋ ለእሷ ግዴታዋ ነበርች ይህች ልጅ ቀስ በቀስ የፍቅር እሳት በልቧ ዙሪያ እንዲቀጣጠል እያደረገች ነው። እንደ ፀጋ ካለች ልጅ ጋር መጣበቅ ማለት ልቧን ለህመም እና ማጣት እምቅ ስቃይ መከፈት ማለት እንደሆነ ታውቃለች።እና ያንን በራሷ ላይ እንደገና ማድረግ ፈፅሞ አትፈልግም ነበር ፡፡ግን ደግሞ በምርጫዋ እያደረገችው ያለ ነገር አይደለም፡፡ከአሰልቺ ጥበቃ በኃላ ነርሷ መጥታ በመጋረጃ ወደተሸፈነው ክፍል ወሰዳቻቸው። ራሄል እህቷን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አስቀመጠቻት።ነርሷ የጥያቄዎችን ፣ የአለርጂዎችን ፣ የመድኃኒቶችን ዝርዝር ጠየቀቻት። ራሄል የምትችለውን ያህል መለሰች።እንደጨረሰች ነርሷ ጆሮዋ ውስጥ ቴርሞሜትር ጨመረች ..በዛ ቅፅበት አንድ ዶክተር ኮሪደሩን ሰንጥቆ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተመለከተች። ነጭ ጋወን አድረጎ ስቴቶስኮፕ አንገቱ ላይ አንጠልጥሏል ።ኤሊ ነበር።
❤55
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጁኒዬር አለምን ይዞ ወደ ወላጆቹ ቤት ሲደርስ ሳሎን ያለው አባቱ ብቻ ነው፡፡አቶ ፍሰሀ ከመቀመጫቸው ተነስተው እጇን እየጨበጡ"ጁኒየር ስላገኘሽ እና እንድትመጪም ስላሳመነሽ ደስ ብሎኛል" አላት፡፡
"እኔም እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።"
"ደህና….ተቀመጪ››
ተቀመጠች፡፡
"ምን ትጠጫለሽ?"ሲል ጁኒዬር ጠየቃት፡፡ "ነጭ ወይን ካለ ደስ ይለኛል…. እባክህ" አለች.
አቶ ፍሰሀ በጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ እያያት "ነጭ ወይን,? እንዳጋጣሚ ባለቤቴም የነጭ ወይን አፍቃሪ ስለሆነች ከእኛ ቤት ጠፍቶ አያውቅም… አሁን ትመጣና ትቀላለናለች
፡፡››አላት
ጁኒየር መጥሪያውን ሲጫን የቤቱ አገልጋይ ከውስጠኛው ክፍል እየሮጠች መጣች…ነጭ ወይን አምጥታ ለአለም እንድትቀዳላት አዘዛት፡፡ወይኑ መጣና ተቀዳላት..አቶ ፍሰሀና ልጃቸው ጁኒዬር ቢራ ያዙ፡፡
‹‹ጁኒዬር ወደቤት ይዞሽ እንዲመጣ ጠይቄው ነበር..እንዲህ በፍጥነት ይሳካለታል አላልኩም ነበር፡፡››
አለም ግራ ተገባች..እናም ወደ ጁኒዬር ዞር ብላ‹‹ወደእዚህ እንድመጣ ያንተ ፍላጎት መስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እሱማ የእኔም ፍላጎት ነው››አላት በእፍረት አንገቱን አቀርቅሮ፡፡ አለምም ወደ ፍሰሀ ዞራ "እሺ ለምን ነበር የፈለከኝ?"አለችው፡፡
በእሷ ቀጥተኛነት ለጊዜው ያልተደሰተ ይመስላል፣ ቢሆን እሱም በተመሳሳይ መንገድ መለሰላት
"ጠላቶች እንድንሆን… አንቺን በደንብ ማወቅ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"እኔም የመጣሁት ለዚህ ነው አቶ ፍሰሀ።"አለችው ፍርጥም ብላ፡፡
እሷን ትንሽ ጊዜ ወስዷ ሊያጠናት ሞከረ። "እንዴት ጠበቃ ለመሆን ፈለግሽ?"የተለመደ ግን ደግሞ ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"የእናቴን ግድያ ለመመርመር ወንጀለኛውን ለፍርድ ለማቅረብ እንድችል.››
መልሱ በድንገት ወደ ከንፈሮቿ የመጣ ነው፣ ይህም መልሷ እንሱን ብቻ ሳይሆን አለምን እራሷን አስገርሟታል። እሷ ከዚህ በፊት የእናቷን ገዳይ መፈለግ ዋና ግቧ እንደሆነ ተናግራ አታውቅም።በዚህ የእናቷ ግድያ ወንጀል ላይ እሷ ራሷም በአያቷ ዘንድ ይፋዊ ተጠርጣሪ ሆና መቅረቧ ነገሩን በቁርጠኝነት እንድትይዘው ገፊ ምክንያት ሆኗታል፡፡ በመጨረሻ ሞት አፋፍ ላይ የምትገኝ አያቷ ለእናቷ ሞት ዋና ተጠያቂ እሷ እንደሆንች በግልፅ ቃል ደጋግማ ነግራታለች።አያቷ የተናገረችው ስህተት እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሌላ ማስረጃ እስካላገኘች ድረስ ጥፋቱን እስከ ህይወቷ ድረስ ይዛ ለመኖር ትገደዳለች ። እና አሁን ከሻሸመኔ ከተማ ሃያሎቹ ጋር ተፋጣ የምትገኝት ዋና ምክንያት ራሷን ነፃ ለማውጣት ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ "ባል የለሽም? ልጆችስ?"ሲል ሌላ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"አይ የለኝም።
" "ለምን?"
"አባ" አለ ጁኒየር በአባቱ እፍረት ማጣት አፍሮ ‹‹አለም ልተዝናና እንጂ በጥያቅህ እንድታጨናንቃት ይዣት አልመጣሁም››
" ጁኒየር ምንም ችግር የለውም። ይህ የተለመደ ጥያቄ ነው።"አለች አለም፡፡
" እሺ እንደዛ ካልሽ መልስሽ ምንድነው?"አቶ ፍሰሀ ጠየቃት፡፡
"ጊዜ ወይም ዝንባሌ የለኝም."
"በዚህ በእኛ አካባቢም ተመሳሳይ ብዙ ጊዜ እና በቂ ዝንባሌ የለንም."
ጁኒየር በጠወለገ እይታ አባቱን ተመለከተው።የተነገረው አሽሙር እሱን የሚመለከት እንደሆነ ያውቃል"አባዬ የከሸፉብኝን ትዳሮቼን እየጠቀሰ ነው።››በማለት አብራራላት፡፡
"ጋብቻዎች? ስንት ነበሩ?"አለም በጉጉት ጠየቀች
"ሶስት" በማለት ተናዘዘ።
"እና አንዳቸውም እኔን አያት የማድረግ ፍላጎቱም ሆነ ብቃት አልነበራቸውም››አቶ ፍሰሀ ዋና ቅሬታውን ተናገረ፡፡
በዚህ መካከል ከፎቁ ወደታች የሚወርድ የጫማ ኳኳታ ሰሙና በተመሳሳይ ሦስቱም ዞሩ። አንዲት ሴት በተከፈተው በር ላይ ቆማ ነበር። አለም የአቶ ፍሰሀ ሚስት እና የጁኒዬር እናት መሆኗን አወቀች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ ድረስ ምን እንደምትመስል አእምሮአዊ ምስል ቀርጾ ነበር። ወይዘሮዋ ግን የአለምን አእምሮአዊ ምስል ተቃራኒ ነበረች።
ጁኒዬር እናቴ ጀማይካዊት ነች ስላላት..የሆነች ፈርጣም ..ጠቆር ያለች.. ከንፈረ ትልልቅ…የፀጉሯ ድሬድ መቀመጫዋን የሚነካ አይነት አድርጋ ነበር የሳለቻት…እሷ ግን ቅንጥስጥስ ያለች ቀጭን…ቀይ ቆንጆ ግን ደግሞ ስልችት ያለው ፊት ያየዘች…ሀበሻ መሳይ
ሴት ነች፡፡ጁኒዬር ያንን አፍዛዣ መሳይ ውበቱን እና ለስላሳ ባህሪውን ከማን እንደወረሰው አሁን በግልፅ ገባት ፡፡
"ሃኒ ይህቺ አለም ጎበና ነች" አለ አቶ ፍሰሀ ።
የጁኒዬር እናት ባለቤቷን ችላ ብላ ፈካ ያለ ፊቷ አብርቶ ቀጥ ያለ ቀጭን ከንፈሯ ወደቀኝ በመጠምዘዝ ‹‹አለም ወደቤታችን እንኳን በሰላም መጣሽ…ሳራ እባላለው..የጁኒዬር እናት ነኝ
››አለችና ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡
አለም ከሴትዬዋ ንግግር የፍሰሀ ባለቤት ከመሆኗ በላይ የጁኒዬር እናት በመሆኗ ኩራት እንደሚሰማት ነው የተረዳችው፡፡
"አመሰግናለሁ።"ስትል መለሰች፡፡
ጁኒየር ከተቀመጠበት ተነሳና አንድ ብርጭቆ ነጭ ወይን ቀዳና ለእናቱ አቀበላት.. ። በሚያብረቀርቅ ፈገግታ‹‹አመሰግናለው የእኔ ልጅ››በማለት ተቀበለችው፡፡
እሱም ጎንበስ ብሎ እናቱን የለሰለሰ ስርጉድ ጉንጯን ሳመ። "ራስ ምታትሽ እንዴት ነው?"
"ሙሉ በሙሉ አልተወኝም፣ ነገር ግን እንቅልፍ ረድቶኛል። ስለጠየቅከኝ አመሰግናለሁ።"
አለም የሴትዬዋን እጇች ስታይ ተገረመች …እጇ ነጭ ሲሆኑ … በአውሎ ንፋስ እንደተመታ አበባ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል።
ባሏን " መቼስ ስለከብቶችና ፈረሶች እያወራህ እያሰለቸሀት ነው አይደል?"አለችው፡፡
"በራሴ ቤት ውስጥ፣ ስለምንስ ባወራ አንቺን ምን ጨነቀሽ?" አቶ ፍሰሀ ቱግ አለ፡፡ ጁኒየር ንግግራቸውን ከዛ በላይ እንዳይጠነክርና አለም ፊት እንዳያሳፍሩን ፈጠን ብሎ ጣልቃ ገባ፡፡
"እማዬ ስለ እርባታ አይደለም እያወራን ያለነው ። አባዬ ከሚስቶቼ ወራሽ የሚሆን ልጅ ለመውለድ ባለመቻሌ እየወቀሰኝ ነበር።"ሲል አብራራላት፡፡
"ጊዜው ሲደርስ ከትክክለኛ ሴት ጋር ልጆች ትወልዳለህ››.አለችና ወደ አለም ዘወር ብላ ጠየቀች፡- “ወ.ሪት አለም በፍፁም አላገባሁም ስትይ ሰምቻለሁ ልበል ?” ብላ ጠየቀችው።
"ልክ ነው"
"እንግዳ ነገር ነው…ቢያንስ የወንድ ጓደኛ ሊኖርሽ ይገባ ነበር፡፡››
"አለም የወንድ ጓደኛ የለኝም አላለችም እኮ
››ጁኒየር አስተካከላት. "በቃ መራጭ ነች"ሲል አከለበት፡፡
"አዎ ከጋብቻ እና ቤተሰብ ከመመሥረት ይልቅ ሙያዬን መርጫለሁ።ለጊዜው፣ ለማንኛውም ነገር ጊዜ የለኝም። ግን እናቴ የሆነ ሙያ ባለቤት ለመሆን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ታውቃለች?"
"እሷን እስከማውቃት ድረስ እንደዛ አይነት ምኞት አልነበራትም" ሲል ጁኒየር መለሰ፣ አለም በፀፀት ስሜት "በጣም ቀድማ በልጅነቷ ነበር የወለደችኝ" አለች።
"ምናልባት ያለዕድሜ ጋብቻ ውስጥ መግባቷ እና ልጅ መውለዷ ወደ ሥራ እንዳትገባ አግዷት ይሆናል….ሰሎሜ የራሷን ምርጫ ነው ተግባራዊ ያደረገችው."ሲል መለሰላት፡፡
"የምታውቀውን ስለነገርከኝ አመሰግናለሁ.››
‹‹ አንድ ጊዜ እኔ እሷና ጀማል ለመዝናናት ወደወንዶ ገነት ሄደን ነበር፡፡በፍል ውሀ ስንታጠብና ስንዋኝ ከዋልን በኃላ በጣም ደክሞን ዛፍ ጥላ ስር ሳሩ ላይ ተዘርረን ሰማዩን አንጋጠን ስለ ምኞታችን ስናወራ እንደነበር ትዝ ይለኛል…ሁላችንም የዋና ልብስ ብቻ ነበር የለበስነው…እና እሷም በመሀላችን ተኝታ ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጁኒዬር አለምን ይዞ ወደ ወላጆቹ ቤት ሲደርስ ሳሎን ያለው አባቱ ብቻ ነው፡፡አቶ ፍሰሀ ከመቀመጫቸው ተነስተው እጇን እየጨበጡ"ጁኒየር ስላገኘሽ እና እንድትመጪም ስላሳመነሽ ደስ ብሎኛል" አላት፡፡
"እኔም እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።"
"ደህና….ተቀመጪ››
ተቀመጠች፡፡
"ምን ትጠጫለሽ?"ሲል ጁኒዬር ጠየቃት፡፡ "ነጭ ወይን ካለ ደስ ይለኛል…. እባክህ" አለች.
አቶ ፍሰሀ በጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ እያያት "ነጭ ወይን,? እንዳጋጣሚ ባለቤቴም የነጭ ወይን አፍቃሪ ስለሆነች ከእኛ ቤት ጠፍቶ አያውቅም… አሁን ትመጣና ትቀላለናለች
፡፡››አላት
ጁኒየር መጥሪያውን ሲጫን የቤቱ አገልጋይ ከውስጠኛው ክፍል እየሮጠች መጣች…ነጭ ወይን አምጥታ ለአለም እንድትቀዳላት አዘዛት፡፡ወይኑ መጣና ተቀዳላት..አቶ ፍሰሀና ልጃቸው ጁኒዬር ቢራ ያዙ፡፡
‹‹ጁኒዬር ወደቤት ይዞሽ እንዲመጣ ጠይቄው ነበር..እንዲህ በፍጥነት ይሳካለታል አላልኩም ነበር፡፡››
አለም ግራ ተገባች..እናም ወደ ጁኒዬር ዞር ብላ‹‹ወደእዚህ እንድመጣ ያንተ ፍላጎት መስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እሱማ የእኔም ፍላጎት ነው››አላት በእፍረት አንገቱን አቀርቅሮ፡፡ አለምም ወደ ፍሰሀ ዞራ "እሺ ለምን ነበር የፈለከኝ?"አለችው፡፡
በእሷ ቀጥተኛነት ለጊዜው ያልተደሰተ ይመስላል፣ ቢሆን እሱም በተመሳሳይ መንገድ መለሰላት
"ጠላቶች እንድንሆን… አንቺን በደንብ ማወቅ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"እኔም የመጣሁት ለዚህ ነው አቶ ፍሰሀ።"አለችው ፍርጥም ብላ፡፡
እሷን ትንሽ ጊዜ ወስዷ ሊያጠናት ሞከረ። "እንዴት ጠበቃ ለመሆን ፈለግሽ?"የተለመደ ግን ደግሞ ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"የእናቴን ግድያ ለመመርመር ወንጀለኛውን ለፍርድ ለማቅረብ እንድችል.››
መልሱ በድንገት ወደ ከንፈሮቿ የመጣ ነው፣ ይህም መልሷ እንሱን ብቻ ሳይሆን አለምን እራሷን አስገርሟታል። እሷ ከዚህ በፊት የእናቷን ገዳይ መፈለግ ዋና ግቧ እንደሆነ ተናግራ አታውቅም።በዚህ የእናቷ ግድያ ወንጀል ላይ እሷ ራሷም በአያቷ ዘንድ ይፋዊ ተጠርጣሪ ሆና መቅረቧ ነገሩን በቁርጠኝነት እንድትይዘው ገፊ ምክንያት ሆኗታል፡፡ በመጨረሻ ሞት አፋፍ ላይ የምትገኝ አያቷ ለእናቷ ሞት ዋና ተጠያቂ እሷ እንደሆንች በግልፅ ቃል ደጋግማ ነግራታለች።አያቷ የተናገረችው ስህተት እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሌላ ማስረጃ እስካላገኘች ድረስ ጥፋቱን እስከ ህይወቷ ድረስ ይዛ ለመኖር ትገደዳለች ። እና አሁን ከሻሸመኔ ከተማ ሃያሎቹ ጋር ተፋጣ የምትገኝት ዋና ምክንያት ራሷን ነፃ ለማውጣት ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ "ባል የለሽም? ልጆችስ?"ሲል ሌላ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"አይ የለኝም።
" "ለምን?"
"አባ" አለ ጁኒየር በአባቱ እፍረት ማጣት አፍሮ ‹‹አለም ልተዝናና እንጂ በጥያቅህ እንድታጨናንቃት ይዣት አልመጣሁም››
" ጁኒየር ምንም ችግር የለውም። ይህ የተለመደ ጥያቄ ነው።"አለች አለም፡፡
" እሺ እንደዛ ካልሽ መልስሽ ምንድነው?"አቶ ፍሰሀ ጠየቃት፡፡
"ጊዜ ወይም ዝንባሌ የለኝም."
"በዚህ በእኛ አካባቢም ተመሳሳይ ብዙ ጊዜ እና በቂ ዝንባሌ የለንም."
ጁኒየር በጠወለገ እይታ አባቱን ተመለከተው።የተነገረው አሽሙር እሱን የሚመለከት እንደሆነ ያውቃል"አባዬ የከሸፉብኝን ትዳሮቼን እየጠቀሰ ነው።››በማለት አብራራላት፡፡
"ጋብቻዎች? ስንት ነበሩ?"አለም በጉጉት ጠየቀች
"ሶስት" በማለት ተናዘዘ።
"እና አንዳቸውም እኔን አያት የማድረግ ፍላጎቱም ሆነ ብቃት አልነበራቸውም››አቶ ፍሰሀ ዋና ቅሬታውን ተናገረ፡፡
በዚህ መካከል ከፎቁ ወደታች የሚወርድ የጫማ ኳኳታ ሰሙና በተመሳሳይ ሦስቱም ዞሩ። አንዲት ሴት በተከፈተው በር ላይ ቆማ ነበር። አለም የአቶ ፍሰሀ ሚስት እና የጁኒዬር እናት መሆኗን አወቀች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ ድረስ ምን እንደምትመስል አእምሮአዊ ምስል ቀርጾ ነበር። ወይዘሮዋ ግን የአለምን አእምሮአዊ ምስል ተቃራኒ ነበረች።
ጁኒዬር እናቴ ጀማይካዊት ነች ስላላት..የሆነች ፈርጣም ..ጠቆር ያለች.. ከንፈረ ትልልቅ…የፀጉሯ ድሬድ መቀመጫዋን የሚነካ አይነት አድርጋ ነበር የሳለቻት…እሷ ግን ቅንጥስጥስ ያለች ቀጭን…ቀይ ቆንጆ ግን ደግሞ ስልችት ያለው ፊት ያየዘች…ሀበሻ መሳይ
ሴት ነች፡፡ጁኒዬር ያንን አፍዛዣ መሳይ ውበቱን እና ለስላሳ ባህሪውን ከማን እንደወረሰው አሁን በግልፅ ገባት ፡፡
"ሃኒ ይህቺ አለም ጎበና ነች" አለ አቶ ፍሰሀ ።
የጁኒዬር እናት ባለቤቷን ችላ ብላ ፈካ ያለ ፊቷ አብርቶ ቀጥ ያለ ቀጭን ከንፈሯ ወደቀኝ በመጠምዘዝ ‹‹አለም ወደቤታችን እንኳን በሰላም መጣሽ…ሳራ እባላለው..የጁኒዬር እናት ነኝ
››አለችና ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡
አለም ከሴትዬዋ ንግግር የፍሰሀ ባለቤት ከመሆኗ በላይ የጁኒዬር እናት በመሆኗ ኩራት እንደሚሰማት ነው የተረዳችው፡፡
"አመሰግናለሁ።"ስትል መለሰች፡፡
ጁኒየር ከተቀመጠበት ተነሳና አንድ ብርጭቆ ነጭ ወይን ቀዳና ለእናቱ አቀበላት.. ። በሚያብረቀርቅ ፈገግታ‹‹አመሰግናለው የእኔ ልጅ››በማለት ተቀበለችው፡፡
እሱም ጎንበስ ብሎ እናቱን የለሰለሰ ስርጉድ ጉንጯን ሳመ። "ራስ ምታትሽ እንዴት ነው?"
"ሙሉ በሙሉ አልተወኝም፣ ነገር ግን እንቅልፍ ረድቶኛል። ስለጠየቅከኝ አመሰግናለሁ።"
አለም የሴትዬዋን እጇች ስታይ ተገረመች …እጇ ነጭ ሲሆኑ … በአውሎ ንፋስ እንደተመታ አበባ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል።
ባሏን " መቼስ ስለከብቶችና ፈረሶች እያወራህ እያሰለቸሀት ነው አይደል?"አለችው፡፡
"በራሴ ቤት ውስጥ፣ ስለምንስ ባወራ አንቺን ምን ጨነቀሽ?" አቶ ፍሰሀ ቱግ አለ፡፡ ጁኒየር ንግግራቸውን ከዛ በላይ እንዳይጠነክርና አለም ፊት እንዳያሳፍሩን ፈጠን ብሎ ጣልቃ ገባ፡፡
"እማዬ ስለ እርባታ አይደለም እያወራን ያለነው ። አባዬ ከሚስቶቼ ወራሽ የሚሆን ልጅ ለመውለድ ባለመቻሌ እየወቀሰኝ ነበር።"ሲል አብራራላት፡፡
"ጊዜው ሲደርስ ከትክክለኛ ሴት ጋር ልጆች ትወልዳለህ››.አለችና ወደ አለም ዘወር ብላ ጠየቀች፡- “ወ.ሪት አለም በፍፁም አላገባሁም ስትይ ሰምቻለሁ ልበል ?” ብላ ጠየቀችው።
"ልክ ነው"
"እንግዳ ነገር ነው…ቢያንስ የወንድ ጓደኛ ሊኖርሽ ይገባ ነበር፡፡››
"አለም የወንድ ጓደኛ የለኝም አላለችም እኮ
››ጁኒየር አስተካከላት. "በቃ መራጭ ነች"ሲል አከለበት፡፡
"አዎ ከጋብቻ እና ቤተሰብ ከመመሥረት ይልቅ ሙያዬን መርጫለሁ።ለጊዜው፣ ለማንኛውም ነገር ጊዜ የለኝም። ግን እናቴ የሆነ ሙያ ባለቤት ለመሆን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ታውቃለች?"
"እሷን እስከማውቃት ድረስ እንደዛ አይነት ምኞት አልነበራትም" ሲል ጁኒየር መለሰ፣ አለም በፀፀት ስሜት "በጣም ቀድማ በልጅነቷ ነበር የወለደችኝ" አለች።
"ምናልባት ያለዕድሜ ጋብቻ ውስጥ መግባቷ እና ልጅ መውለዷ ወደ ሥራ እንዳትገባ አግዷት ይሆናል….ሰሎሜ የራሷን ምርጫ ነው ተግባራዊ ያደረገችው."ሲል መለሰላት፡፡
"የምታውቀውን ስለነገርከኝ አመሰግናለሁ.››
‹‹ አንድ ጊዜ እኔ እሷና ጀማል ለመዝናናት ወደወንዶ ገነት ሄደን ነበር፡፡በፍል ውሀ ስንታጠብና ስንዋኝ ከዋልን በኃላ በጣም ደክሞን ዛፍ ጥላ ስር ሳሩ ላይ ተዘርረን ሰማዩን አንጋጠን ስለ ምኞታችን ስናወራ እንደነበር ትዝ ይለኛል…ሁላችንም የዋና ልብስ ብቻ ነበር የለበስነው…እና እሷም በመሀላችን ተኝታ ነበር፡፡
❤44👍2