አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በአሌክስ_አብርሃም

"ልጄን! ልጄን እያለች እናቴ ወደ እኔ
ስትሮጥ ይሰማኛል …ቀለል አለኝ !
።።።።
ለድፍን አንድ ሳምንት ከቤቴ ሳልወጣ አሳለፍኩ፤ ከእሁድ እስከ እሁድ፡፡ ምን እኔ ብቻ፣ ከዚያች ምሽት ጀምሮ እናቴ እንቅልፍ አልነበራትም፣ ለወትሮው ጧት ጧት ሳታዛንፍ የምትስመውን ቤተክርስቲያን ርግፍ አድርጋ ትታ፣ የእኔው ጠባቂ ሆና አብራኝ ታሰረች፡፡ እንኳን ከቤት ርቄ ልሄድ፣ ለሽንት እንኳን ከቤታችን ኋላ ወዳለው መፀዳጃ ቤት ደረስ ብዬ ለመመለስ አታምነኝም፡፡ ተከትላኝ ወጥታ በር ላይ ትቆማለች፡፡ ተጨንቃ ነበር፡፡
እውነት ነበራት ደግሞ፤ ድፍን ከተማው ሌላ ወሬ አልነበረውም፡፡ “የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛው የአቶ ዝናቡ ልጅ እቤታቸው ያስጠጓትን ምስኪን ሕፃን ልጅ ደፈረ…”

እግዚኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦ! ስምንተኛው ሺ!”

ጎረቤቱ ከላይ እስከታች በአንድ ጊዜ የነመሐሪን ቤተሰቦች ረጋሚ እና ዘላፊ ሆኖ ነበር፡፡
ይኼ ዘለፋ ታዲያ ባለፍ ገደም ወደኔም እንጥፍጣፊው መድረሱ አልቀረም፡፡ ያስገረመኝ የዚህ የጥላቻ ዘመቻ ዋና አራጋቢዎች ሰፈር ውስጥ ትምህርት እምቢ ያላቸው ልጆች መሆናቸው! እነሱም ብሎ ጎበዝ ተማሪም ይላሉ፡፡ መቼም መሐሪ ሲነሳ “እነሱ” ከተባለ
ያው አንዱ እኔው ነኝ፡፡ እስቲ አሁን ጉብዝናችን ላይ ምን ወስዶ አንጠላጠላቸው? በዚህ ሰበብ ጉብዝናችንን ካዱትም አልካዱትም ትምህርት ሚኒስተር መጽዋች ስለሆነ አይደለም አራት ነጥብ የሰጠን፡፡ ምን ያገናኘዋል? ሲያጨበጭቡልን እየተበሳጩ ነበር እንዴ ሰፈራችንን አስጠራችሁት ያሉት፣ ሰበብ አግኝተው እንደ ኦሪት መስዋዕት ከሰፈር አውጥተው ሊያቃጥሉን ነበር እንዴ? ግን ከተፈጠረው ነገር ይልቅ፣ የተበለጡትን መከረኛ ትምህርት እያነሱ፣ መሐሪንም እኔንም ሲያንቋሽሹ ነበር ውለው የሚያድሩት፡፡
አብሯቸው የኖረ የበታችነት እና የመብለጥ ስሜት፣ ሳሌም የምትባል መርፌ ስትወጋው እንደባሉን እየተነፈሰ ነበር ፡፡

አባባ እንደ ማንኛውም ቀን ፣ምንም እንዳልተፈጠረ፣ በነጠላ እራፊ የተጠመጠመ እግሩን በተደራረበ ትራስ ላይ አሳርፎ፣ (አስር ጊዜ ትራሱን አስተካክልልኝ እያለ)ስለእቁብ
ሲያወራ ይውላል፡፡ ይኼ ነገሩ ትንሽ ቢያሳዝነኝም፣ ከእናቴ ጭንቀት ይልቅ የእርሱ ግድ የለሽነት የተሻለ ያረጋጋኝ ስለነበር፣ ብዙውን ጊዜ የማሳልፈው ከአባባ ጋ በማውራት ነበር፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን የሆነ ነገር እንዲለኝ ፈልጌ ነበር፡፡ ቢያንስ አይዞህ እንዲለኝ፡፡
አይዞህ ብቻ፡፡ ምንም ቢያወራ ነገሬ ብዬ ከማልሰማው አባባ፣ አንድ ቃል ናፈቀኝ፡፡
አባትነት ልጅ በመውለድ ብቻ የሚመጣ ነገር እንዳልሆነ የገባኝ ያኔ ነው እየወደድኩት ውስጤ ያዝን ነበር፡፡ ነፍሱ ውስጥ እኔ የለሁም እላለሁ፡፡ ሩቅ
ሐገር ተፈጽሞ በዜና ቢሰማ እንኳን ስሜትን የሚረብሽ ነገር እዚህ አፍንጫው ሥር፣ ያውም ከወንድምም በሚቀርብ የልጁ ጓደኛ ተፈጽሞ ፣ ጎረቤቱ ሁሉ እየዛተና እየፎከረ - “ድሮውንም አንገት
ደፊ” በሚል ገደምዳሞሽ አሽሙር፣ በሌለሁበት እኔንም ጨምሮ እየቀጣኝ ምንም ስሜት ያልሰጠው አባት፣ እንዴት ዓይነት ተፈጥሮ ቢኖረው ነው!? እያልኩ እገረማለሁ፡፡

ለእኔ ብቻ ሳይሆን፣ የእናቴን ጭንቀት ትንሽ እንኳ ቢካፈላት፣ ሌት ተቀን ልጇን ሊነጥቋት እንደከበቧት አራስ ነብር፣ ቁጣና ስጋት ከቧት ስትንቆራጠጥ፡ ኮሽ ባለ ቁጥር ብርክ ሲይዛትና፣ በበር ሽንቁር ወደውጭ እያጨነቆረች ስትመለከት፣ እይዞሽ ቢላት ምናለበት፣ እያልኩ አስባለሁ፡፡ ተኚ እኔ አለሁ ለምን አይላትም? እልናገረውም ግን
አስባለሁ፡፡ ምንም ይሁን አባት፣ ፈርጣማ ክንድ ባይኖረው እንኳ፣ ተስፋና ማጽናናት
እንዴት ይነጥፍበታል፡፡ “እንድ ሰው የልጄን ስም ያነሳና፣ ውርድ ከራሴ፣ እሱ ምን
ያርጋችሁ? እዚህ እንደ እንሽላሊት በየጥጋጥጉ እየሄዳችሁ የምታሽሟጥጡት” ቢል ምን
ይሆናል አንድ ቤት የምንኖር ሳይሆን፣ ታክሲ ፌርማታ ላይ ድንገት ተገናኝተን፣ ታክሲ እስከሚመጣ የምንጠብቅ መንገደኞች የሆንን እስኪመስለኝ ምንም የምንጋራው ስሜት አልነበረም፡፡ ቸልተኛ ነበር፤ እሽ ይሁን፡ ቸልተኝነቱን ትንሽ ወደ ምክር ቢለውጠው እና አይደል፤ አትስማቸው '' ችላ ብሎ ማለፍ ነው" ቢል፡፡

ገና እቤት መዋል በጀመርኩ በሦስተኛው ቀን፡ እናቴን እንዲህ እላት፡፡ “በመንደሩ ያለው ሰው የዝናቡ ልጅ ብቻ ነው እንዴ?…ይውጣና ኮመንደሩ ልጆች ጋር ንፋስ ተቀብሎ ይምጣ፤ እንግዲህ አንዴ የሆነው ሁኗል፡ የፈሰሰ ውሃ እይታፈስ!”፡፡ እንዴ የሆነው ሁኗል ማለት ምን ማለት ነው? እንዳትደግመው እንጂ የሆነው ሆኗል ነበር የሚመስለው አነጋገሩ፡፡ ከዚያ በፊት ችላ ብየው፣ አልያም ሳላስተውለው ቆይቼ የገረመኝ ነገር ደግሞ፣አባቴ መሐሪን በስሙ ጠርቶትም ሆነ ጓደኛህ” ብሎ አያቅም፡፡ “የዝናቡ ልጅ” ነው የሚለው፡፡ ለነገሩ አባባ፣ መሐሪን ብቻ ሳይሆን፣ ሕፃንም ይሁን ወጣት በስም
አይጠራም፡፡ የእከሌ ልጅ ነው የሚለው፡፡ ሴቶችን ሳይቀር “ይች የእከሌ ሚስት” ነው የሚለው፡፡

ይኼው አሁንም “የዝናቡ ልጅ ብቻ ነው ወይ በመንደሩ ያለው? ይለኛል፡፡እና በመንደሩ ማን አለ? …ከመሐሪ ሌላ ማን አለ? …መሐሪ ከሰፈር ልጆች እንዱ አልነበረምኮ መሐሪ ጓደኛ ብቻ አልነበረምኮ ከመኖር ብዛት የራሳችንን ቋንቋ የፈጠርን፣ ሁለት ሰዎች ውስጥ የተቀመጠች አንዲት ውብ ነፍስ የተጋራን ፍጥረቶች ነበርን፡፡ ቃል ሳንተነፍስ
ልባችን ውስጥ ያለውን ሐሳብ በአንድ የዓይን ጥቅሻ የምንካፈል፡፡ ትንሽ ዓለሜ
የቆመችው፣ ሁለት ምሰሶዎች ላይ ነበር፡፡ አንዱ እኔ ራሴ፣ አንዱ መሐሪ! ግማሽ እኔ እስር ቤት ውስጥ ነኝ ሚዛኗን ስታ እየተንገዳገደች ያለች ሚጢጢ ዓለሜን፣ ወደፊት መራመዱ ቢቀር፣ ቀጥ ብላ እንድትቆም እየታገልኩ ነበር፡፡ ለድጋፍ እጁን የሚሰጥ ሰው እንጂ፣ ግዴለም በአንድ እግርህ ውጣና፣ ሌላ እግር ፈልግ የሚል ሰው አልነበረም ፍላጎቴ! “ከሰፈር ልጆች ጋር ነፋስ ተቀበል” ይለኛል፡፡ እንኳን አብሬው ነፋስ የምቀበለው የሰፈር ልጅ፣ በመንደሩ ውስጥ ነፋስ አለ ወይ?… መንደሩስ ራሱ አለወይ … እቤቴ ቁጭ
ያልኩት (ምን ቁጭ ያልኩት የተደበኩት) እንደ ሕፃን ልጅ የራሴን ዓይን ስጨፍን
ከዓለም ሁሉ የተደበቅሁ መስሎ እየተሰማኝ፣ ለአፍታም ቢሆን እፎይታ ስለሚሰማኝ ነበር፡፡ በሆነው ሁሉ ከማፈሬ ብዛት የሰው ዓይን ፈርቼ ነበር፡፡
መሐሪ ሁለት ቀን ፖሊስ ጣቢያ ቆይቶ በሦስተኛው ቀን ፍርድ ቤት ቀረበ ተባለ፡፡ የዚያኑ ቀን ከሰዓት በኋላ፣ ወደ ትልቁ ማረሚያ ቤት እንደተወሰደ ሰማሁ፡፡ ይኼን ሲነግሩኝ፣ ያ አሮጌ የብረት በር እየተንሳጠጠ ከኋለው ሲከረቸምበት ታየኝ፡፡ ውስጤ ሂድ ሂድ ይለኛል፡፡ከስንት ዓመታት በፊት ያየሁት ማረሚያ ቤት ሲታወሰኝ፣ዘገነነኝ፡፡ የማቅለሽለሽ
ስሜትም ተሰማኝ፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ ዝም ብሎ የማቅለሽለሽ ስሜት ቶሎ ቶሎ
ይሰማኛል፡፡ሳምንቱን ሙሉ እንደ ነፍሰጡር ምግብ ሲሸተኝ፣ ጧት ስነሳ ያቅለሸልሽኝ ነበር፡፡

ግንኮ እስከ ዛሬ ብዙ ነገር ይስተካከል ይሆናል” ብዬ እራሴን ለማጽናናት ሞከርኩ፡፡ለምሳሌ ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ዘመናዊ የመዋኛ ገንዳ ተሠርቶ ሊሆን ይችላል (መሐሪ ዋኝቶ አያውቅም እንጂ ዋና ይወዳል፡፡ ስናድግ እቤቱ የመዋኛ ገንዳ ሊያስገባ ሐሳብ ነበረው) ምናልባት ምሳቸው በባልዲ የተቀዳ ወጥ ሳይሆን፣ ነጫጭ ልብስ በለበሱ ጠረጴዛዎች ላይ፣ በቆንጆ አስተናጋጆች በሸክላ ሰሀን የሚቀርብ ብዙ ዓይነት ምግብ ሊሆን ይችላል፡፡ በቅመም ያበደ ሻይም ከምሳ በኋላ ይቀርብላቸው ይሆናል። (መሐሪ
ከምሳ በኋላ እንደዚያ ዓይነት ሻይ ይወዳል) ከዚህ ሁሉ
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_አራት


#በአሌክስ_አብርሃም

“ወረተኛ ሁሉ! ያሳደግሽውን ልጅ እንደ ድመት ልትበይ አሰፍስፈሻል ና ውርርርር ድመት ሁሉ እያለ ይጮኻል፡፡ ጮኸ ብሎ ይጣራል አብርሃም …አይዞህ! እናስፈታዋለን! ድመት ሁሉ! ውርርርርር …የነገ ዶክተር ….የነገ ኢንጅነር …የነገ ጠቅላይ ሚንስትር ልትበይ አሰፍስፈሻል! …ውርርርርርር …ልጆቻችን ናቸው! …ውርርር! ደፋሪም ተደፋሪም ልጆቻችን ናቸው! ለሁለቱም ማልቀስ ነበር የሚበጀን ሁልጊዜ ማታ ጋሽ አዳሙን እጠብቅ ነበር፡፡ የተመሰከረለት ሰካራም ቢሆንም ቅሉ፣ በእውነት፣ እንደ ደግ አባት
የጨለማ ንግግሩ ይናፍቀኝ ነበር፡፡

ቤት ውስጥ በተቀመጥኩ ልክ በሳምንቱ፣ እሁድ ቀን እዚያ ታች ሰፈር የሚኖሩ ሁልጊዜ ከእናቴ ጋር ቤተክርስቲያን የሚገናኙ ሴትዮ፣ አንድም እናቴን ቤተክርስቲያ ስላላገኟት ለመጠየቅ፣ እግረመንገዳቸውንም አባባን ተሻለህ ወይ ለማለት፣ ከቤተክርስቲያን ሲመለሱ
እቤታችን ጎራ አሉ፡፡ ገና እንደገቡ እኔን ሲያዩ አንተ አብርሃም እንዲያው ምን
ይሻላችኋል” ብለው አለፍ አሉና ተቀመጡ፡፡ ቡና ተፈልቶ ስለነበር (አቦል ረግጠውማ አይሄዱም) ተብለው ቁጭ አሉ፡፡ቡና እየጠጡ ያው የዚያን ሰሞኑን ወሬ ሲያወሩ ድንገት እናቱን ያየ ሰው ያች ቆንጆ ናት ወይ ያስብላል፣ ባንዴ አመዱን ነስንሶባታል አሉ፡፡ ጆሮዬ ቆመ፤ ስለመሐሪ እናት ስለማሚ ነበር የሚያውሩት፡፡

“ምን ታርግ፣ ይኼ መዓት እንኳን እሷን …" እናቴ ሳትጨርስ ተወችው፡፡

ትላንት ለልጁ ስንቅ ልታደርስ ወደ እስር ቤት ስትሄድ፣ እዚህ ኮረኮቹ ላይ ወደ
ፈረንጆቹ ቤት መገንጣያዋ ጋ፣ የተደበቁ ልጆች ድንጋይ ወርውረው መቷት አሉ፡፡

“ውይ ውይ ውይ የሚመታ ይምታቸው እቴ፣ ሰይጣኖች! እሷ ምናረገች፡፡ ሰው ቀና ብላ የማታይ ሴት፣ ምናረገች ይላሉ እሰቲ አሁን፣ ተጎዳች… ምኗን መቷት?” አለች እናቴ፡፡እንባ ተናንቋት ደረቷን እየደቃች ነበር፡፡

እንጃ ምኗን እንዳገኟት ምን እንደገፋኝ እንጃ ከተቀመጥኩበት ጥግ ተነስቼ በእናቴና በሴትዮዋ መሀል የተዘረጋውን ረከቦት ዘልዬ ወደነመሐሪ ቤት ከነፍኩ፡፡ የቆምኩት የግቢያቸው በር ላይ ስደርስ ነበር፡፡ በሩን ሳንኳካ ፊት ለፊት መንገዱን ተሻግሮ ያለ ግቢ በር ገርበብ ብሎ ተከፈተና፣ መዓዛ የምትባለው የጎረቤት ልጅ ብቅ ብላ አይታኝ፣ መገዱን ተሻግሮ እስኪሰማኝ ኤጭ!” ብላ በሩን ወርውራ ዘጋችው! መዓዛ እኔን አይታ
ኤጭ አለች፡ህ! …እኔና መሐሪን ባየች ቁጥር፣ ቀሚሷን እንደ ሰላም ባንዲራ
እያውለበለበች በዓይኗ ከሁለት አንዳችሁ ተኙኝ እያለች ስትማጸን የኖረች ከንቱ ናት!
ከንቱ ብቻ አልነበረችም፣ ደደብም ጭምር ነበረች፡፡ እኔ የሠራሁላት የቤት ሥራና
አሳይሜት ብቻ ቢቆጠር፣ ከሷ የበለጠ የሷን ትምህርት ተማርኩላት ያስብል ነበር፡፡ደደብ ብቻም አልነበረችም፡፡ ዓይናውጣ። ነገርም ነበረች፡፡ መሐሪን የቤት ሥራ ሥራልኝ ብላ እቤታቸው ሄዳ ልትስመው ሞክራ፡ ገፈታትሮ አስወጥቷት፡ እየሮጠ እኔ ጋ መጥቶ ነግሮኝነበር፡፡አሯሯጡ ራሱ ነፍሱን የሚያድ እንጅ ከንፈር የተቃጣባትን አይመስልም ነበር
ሁሉም የተናቀውን ያህል ሰበብ ፈልጎ ሊንቅ ሲያደባ የኖረ ነበር እንዴ? ውስጤ ተቆጣ ይኼ ሕዝብ ወንጀል አይጸየፍም እንዲያውም የጠላቸውን እና ቀን
የሚጠብቅላቸውን ሰዎች ማጥቂያ በረከት አድርጎ ነው የሚመለከተው።

“ማነው?” አለች ማሚ፡፡ ለዘመናት ሲጸልይ ቆይቶ፣ ፈጣሪ ከሰማይ ድምፁን እንዳሰማው አማኝ፡ ድምጿ ተአምር ነበር የሆነብኝ፡፡

"እኔ ነኝ ማሚ"

በሩን በፍጥነት ከፍታ፣ ሁለት እጆቿን እንደ ከንፍ እንደዘረጋች ተንደርድራ አቀፈችኝና፡
ደረቷ ላይ ለጥፋኝ ማልቀስ ጀመረች ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ፡፡ ከማጥበቋ ብዛት የተነሳ ደረቷ ላይ ያለችው የወርቅ ሐብል ማጫወቻ ጉንጨን የበሳችው እስኪመስለኝ እየወጋችኝ ነበር፡፡ የማደርገው ነገር ግራ ገብቶኝ፣ ደረቷ ላይ ተለጥፌ ዝም አልኩ፡፡ ወጥ ወጥ
ትሽታለች:: ትንሽ አቅፋኝ እንደቆየች፣

“የኔ ነገር፣ ና ግባ ና አለችና መልሼ እንዳልሄድ የፈራች ይመስል በአንድ እጇ
እንባዋን እየጠረገች፣ በሌላኛው እጇ እጄን ይዛ እየጎተተች ወደ ውስጥ መራችኝ፡፡
“ግቢው፣ ቤቱ አዲስ ሆነብኝ፡፡ብዙ ዓመት ቆይቼ የመጣሁ ያህል አዲስ ሆነብኝ፡፡ ዛፎቹን እንደ ሰው እያቀፍኩ ብስማቸው ብዬ ተመኘሁ፡፡ በረንዳ ላይ የተቀመጠውን የጋሽ ዝናቡን ተወዛዋዥ ወንበር፣ እንደ ሰው ስላም ልለው ዳዳኝ፡፡ ከዚህ ግቢ ለአንድ ሳምንት የቀረሁበትን ጊዜ አላስታውስም፡፡ ጭር ብሏል፡፡

የመጠየቂያው ስዓት እንዳይረፍድብኝ ብዬ ወጥ እየሠራሁ ስሯሯጥ ቤቱንም
እላዘጋጀሁት እለች፡፡ እስረኛ መጠየቂያው ስዓት ማለት አልፈለገችም፡፡ ሳሎን ባለው
ሶፋ ላይ፣ በርከት ያሉ የመሐሪ ልብሶች እዚያና እዚህ ተዝረክርከዋል፡፡ የተወሰኑት
በሥርዓት ታጥፈው በአንድ ጎን ተቀምጠዋል፡፡ ቅያሬ ልብስ ልትወስድ አዘጋጅታቸው ነበር፡፡

ድንጋይ እንደወረወሩብሽ ሰምቼ ነው የመጣሁት አልኩ፡፡ ድንገት ነው ያመለጠኝ፡፡

“ዝምብለው ነው ባክህ ልጆች

ጎዱሽ …

አረ ጠጠር ነው፡፡ እግሬን ጫር አድርጎኝ አለፈ፡፡ ታውቀው የለ፣ የዚህ ሰፈር ውሪዎች ጨዋታቸው ለዛ ቢስ ነው፡፡ እናተም ያው ነበራችሁ፡፡ በየቀኑ ስሞታ ነበር ብላ ለመሳቅ ሞከረች ፡፡ ዓይኔን ወደ እግሯ ላከሁት ነጭ ካልሲ አድርጋለች፡፡ ማሚ በጭራሽ ካልሲ አድርጋ አይቻት አላውቅም! ወደ ማድቤት አብሪያት ሄድኩና፣ ግድግዳውን ተደግፌ
ቆምኩ፡፡ የኤሌክትሪክ ምድጃ ላይ ሁለት ብረት ድስት ጥዳ ወጥ እየሠራች ነበር፡፡
አንዱ ድንች በሥጋ የመሐሪ ቁጥር አንድ ምግብ (ሚስቴ አሪፍ ድንች በሥጋ መሥራት ከቻለች ለምን እንፋታለን ብሎኝ ነበር ..ድሮ ስለ ሚስት ይሁን ስለ ፍች ስናወራ )

ከማሚ ጋር ሳንነጋገር ዘለግ ያሉ
ደቂቃዎች ቆየን፡፡ ወዲያ ወዲህ ስትል በዝምታ እመለከታታለሁ፡፡ማንኪያ ታነሳለች፣ ታስቀምጣለች፣ ማማሰያ ታነሳለች እንዲሁ ወጡን ነካክታ ትመልሰዋለች፡፡ ጸጉሯ በሻሽ ጥፍንግ ብሎ ስለታሰረ ነው መሰል፣ ግንባሯ ወጣ
ብሏል፡፡ውስጤ እንደገና እቀፋት እቀፋት ይለኛል፡፡ፊቷን ኮስተር አድርጋ እንዳቀረቀረች በፍጥነት ነበር ወዲያ ወዲህ የምትለው፡፡ አውቃለሁ ማሚ እንዲህ የምትሆነው፣ እንባ
እየተናነቃት ላለማልቀስ ነው፡፡

ድንገት ከሩቅ በመጣ በሚመስል ድምፅ
“እየተዘጋጀህ ነው?” አለች፡፡

“ለምኑ? አልኩ፡፡

“ዩኒቨርስቲ መሄጃችሁ እየደረሰኮ ነው…ልብውልቅ”

ዝም ተባብለን ቆየንና፣ “መሐሪም እዚያ እተረገመ እስር ቤት የሚቆይ አይመስለኝም፤
አብራችሁ ዩንቨርስቲ መሄዳችሁ አይቀርም፡፡ አላደርስ አለኝ እንጂ ዳቦ ቆሎም በሶም አዘጋጅላችኋለሁ፡፡ ግዴለም ትንሽ ቀን አለ” ብላ ወገቧ ላይ ያሰረችውን ሽርጥ ወደ ላይ ስባ እንባዋን ጠረገች፡፡ ምን እንደምል ጨንቆኝ ዝም ብየ እንደቆምኩ፣ ድንገት የግቢው
በር ተንኳኳ፡፡

አንተ እዚሁ ቆይ" ብላኝ ሄደች፡፡ ተከተልኳት፡፡ እናቴ ነበረች፤ ነጠላዋን እንኳን በወጉ ሳትለብስ አንጠልጥላ ስትከንፍ የደረሰችው። ገና ስታየኝ፣ እጇን ልቧ ላይ አድሮ እንባዋን ዘረገፈችው፡፡
“ምንም ኤልሆነልኝም ዘንድሮ፣ በስንቱ ተጨንቄ ልሙት እኔ፣ ምን አደረኩ ምን
በደልኩ እያለች ማልቀስ ስትጀምር፣ ማሚ አቅፋ አጽናናቻት፡፡ ድንገት ዋናው ጉዳይ
ትዝ ያላቸው ይመስል፣ እኔን ትተውኝ ተቃቅፈው ይኼን ለቅሶ እስኪወጣላቸው
አስነኩት፡፡ መሐሪ ከታሰረ በኋላ የተገናኙት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ አልቅሰው ሲወጣላቸው እንግዲህ እግዜር አመጣው፣ ተይው፣ ተይው” ተባብለው ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡

እናቴ በለቅሶ ድምፅ ዘንድሮ መቼም እንዳትታዘቢኝ” ከማለቷ
👍2
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_አምስት


#በአሌክስ_አብርሃም

“…ባልወልዳትም እናት ነኝ ብዬ በነጋታው ሳሌምን ልጠይቅ ሆስፒታል ብሄድ፣ ጥድቄ እንደውሻ አከላፍታ መለሰችኝ፡፡ ያች ምስኪን ናት ወይ ትያለሽ፡፡ ሰው ጉድ እስኪል፣ ምን ቀርቶሽ መጣሽ ብላ ኡኡ አለች፡፡ ውሻ አረገችኝ …ውሻ፡፡ ቀና ብዬ የሰው ዓይን ማየት እስከፈራ አቀርቅሬ ወጣሁ፡፡ ይሁን እናት ናት፣ አላዘንኩም፡፡ በኋላ ስሰማ ሳሌምንም ጥድቄንም ፈረንጆቹ እዚያው ግቢ ወስደው አስጠጓቸው አሉ” እንባዋን ጠራረገችና ቀጠለች፡፡

ዝናቡም ይኼው ሳምንቱን ሙሉ ቃል ሳይተነፍስ፣ ከቤትም ሳይወጣ ጧት እዚች
በረንዳ ላይ እንደተቀመጠ ማታ ገብቶ ይተኛል፡፡ ላናግረውም ብል አይተነፍስም፡፡
መሐሪም በሄድኩ ቁጥር አባባ ደህና ነው ወይ ካጠገቡ አትለዬ እንዳለኝ ነው፡፡
እንደሸማኔ መወርወሪያ ከዚያ ከዚህ ስል እውላለሁ… እንደ እብድ ብቻዬን ማውራት
ሁኗል ሥራዬ …የምያዝ ምጨብጠውን አጥቻለሁ”

ዛሬ ጋሽ ዝናቡ የት ሂዶ ነው ታዲያ?”

“ካለወትሮው ጧት ተነስቶ፣ እስቲ ነጠላ ስጭኝ ቤተከርስቲያን ልሂድ አለኝ

እሰይ እንኳን ሄደ፡፡ እሱ መድኃኒያለም ይስማው አለች እናቴ፡፡ እኔ ግን ገረመኝ፡፡
ጋሼን ሳውቀው ጀምሮ ቤተክርስቲያን ረግጦ የሚያውቀው፣ ሰው ሲሞት ለቀብር ብቻ ነበር፡፡ ማሚ ልብሱንም ምግቡንም በሁለት ፌስታሎች ቆጣጥራ አብረን ወጣን፡፡

አብሬሽ ልሂድ ማሚ” አልኳት፡፡ እናቴ ይሉኝታ ይዟት ዓይኗን ማሳረፊያ አጥታ
ስታንከራትት፣ ማሚ የእናቴ ነገር ገብቷት ይሁን አልያም እውነቷን እንጃ፣ ሌላ ቀን! ዛሬ ቤተሰብ ብቻ ነው …አንድ ሰው ብቻ ነው የሚያስገቡት” ብላ ወደ እናቴ ገፋ አደረገችኝና እየተጣደፈች ሄደች፡፡ ገብቶኛል፣ እንባዋ መጥቷል፡፡ እሷ ወደግራ እኛ ወደቀኝ ስንለያይ ዞር ብዬ ከኋላ ተመለከትኳት፡፡ ያች በተረከዘ ረጅም ጫማና ባጭር ቀሚስ መንሳፈፍ በሚመስል መውረግረግ መንገዱ ላይ የምትነግሥ ሴት፣ አላፊ አግዳሚው ጎንበስ ቀና እያለ ወገቡ እስኪቀነጠስ ለሰላምታ የሚያሸረግድላት ሴት፣ ነጠላዋን ተከናንባና ባለማስሪያ ሸራ ጫማ አድርጋ ከኋላዋ የሚያሳድዳት አንዳች ነገር እንዳለ ሁሉ፣ ከሶምሶማ ባልተናነሰ ርምጃ ትገሰግሳለች፡፡ ብቻዋን፡፡ አንድ ልጇን፣ ጓደኛዋን፣ ሁሉ ነገሯን
ወደታሰረበት ማረሚያ ቤት፡፡

እንዴት ነው አሁን መሐሪን የሚያርሙት? ሁለተኛ ሴት እንዳትደፍር ሊሉት ነው?…ሁለተኛ ይችን ምስኪን እናትህን ትተህ የትም እንዳትሄድ ሊሉት ነው ? ጓደኛህ
ሁሉም ነገር የተደበላለቀበት በአንተ ምክንያት ነው፤ ከአሁን በኋላ ሴት ከመድፈርህ በፊት አማክረው ሊሉት ነው ምን ብለው ነው የሚያርሙት ?ምናለ እግዚአብሔር እኔን ለአንድ ጊዜ እግዚሐርነቱን በከፊል ሊያውሰኝ እና፣ ነገሮችን በአንድ ሳምንት
ወደ ኋላ ብመልሳቸው .እግዚሐርነቴን እውር ላብራበት፣ አልያም ሽባ ልተርትርበት አልልም፣ የሞተም በሰላም ይረፍ፣ እሱን አስነስቼ አላንዘፋዝፍም፡፡ አንዲት ነገር ብቻ ትንሽ ተአምር … ሮሐ ያመጣችውን ውስኪ በተአምር ወደ ውሃ፣ ቢራውንም ወደ አምቦ ውሃ ለመቀየር፡፡ ገድልም ይጻፍልኝ አልል፡፡ እንደው በምስጢር ይችን ተአምር ለማድረግ ብቻ!
።።።።
መሐሪን ሳልጠይቀው ሠላሳ ቀናት ነጎዱ፡፡ ድፍን አንድ ወር፡፡ ሰውን ፈርቼ አልነበረም፡፡ሰው ስለመሐሪ እስኪበቃው አውርቶ ወጥቶለት፣ ችላ ወደማለቱ ነበር፡፡ መሐሪን ራሱን ማየት ፈራሁ፡፡ ፊቱን ማየት ፈራሁ፡፡ የመሐሪን ፊት ማየት ፈራሁ፡፡ በቃ አንድ ቀን በጨመረ ቁጥር ፍርሃቴ በዚያው ልክ እያደገ ዓይኑን ማየት ፈራሁ፡፡ መሐሪን አለመጠየቄ ከቤተሰቦቹም አራቀኝ፡፡ ለምን አልጠየቅኸውም ቢሉኝ ምን እላለሁ? የሚል ፍርሃት፡፡ እናቴ እንኳን ከእኔ ተሽላ “አሁን ተረጋግቷል ሂደን ጠይቀነው እንመለስ” ስትለኝ፣ “አንች
ሂጂ ብያት ቀረሁ፡፡ ደርሳ እክትመለስ በጉጉት ስጠብቃት ቆየሁና፣ ከመጣች በኋላ ስለ መሐሪ ልታወራኝ እስረኛው ብዛቱ ብላ ስትጀምር፣ ትቻት ወደ ውጭ ወጣሁ፡፡
የሆነ ዝግንን የሚል ስሜት ሰውነቴን ወረረኝ፡፡ ማንም ሕመሙን ሊረዳው አይችልም፡፡ እንቁላል እራሱ ላይ
አስቀምጦ በቀጭን ገመድ ላይ እንደሚራመድ ሰው ነበር፣ ትላንቴ
ወድቆ እንዳይንኮታኮት የምታገለው፡፡ በቃ የመሐሪ ነገር “ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን” ሆነ፡፡በዚህ ዝምታ ውስጥ እያለሁ ነበር የተመደብንበት ዩኒቨርስቲ ዝርዝር በጋዜጣ የወጣው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመደብኩ፡፡ ውስጤ የዓመታት ምኞቱ እንደተሳካለት ሰው አልፈነደቀም፡፡ እናቴ ምናለች?

እልልልልልልል … የትም ይሁን፤ ብቻ ከዚህ የተረገመ ሰፈር ሂድልኝ እንዲህ እያለች ታዲያ አቅፋኝ ታለቅሳለች፡፡

ዓይኔ ጋዜጣው ላይ ይንከራተታል፡፡ መሐሪ ጎንደር ዩኒቨርስቲ፣ አፄ ቴዎድሮስ
ከነሠራዊታቸው መጥተው እኔ መናገሻ ላይ የተመደበውን መሐሪን ፍቱ ብለው እስር ቤቱን ሰባብረው ነፃ ቢያስወጡት በቁሜ ቃዠሁ፡፡ (ያበድኩ እስኪመስለኝ) ሮሐ መቀሌ ተመደበች ሁሉም የመቀሌ ወንድ ዙሪያዋን ከብቦ ከበሮ እየደለቀ ምድራችን ላይ
ምናይነት ቆንጆ መጣችብ(ል)ን እያለ ሲጨፍር ታየኝ፡፡ አንድ ክፍሎም የሚባል የቀድሞ ታጋይ፣ የአሁን ባለስልጣን አግብታ አስራ አንድ ቆንጆ ልጆች ትወልዳለች፡፡ ብርክቲ፣ጸጋ፣ አብረኸት፣ ረዳኢ፣ ሐየሎም፣ወልደሰንበት፣ ገብረእግዚ፣ ጎይሌ፣ አጽብሃ ወላ መለስ
እና አርከበ ትላቸዋለች፡፡ ምንም አይለውጥም፣ የባለሥልጣን ሚስት ብትሆን ጊዜን ወደ ኋላ መመለስ አትችልም፡፡ እቃዣለሁ፡፡

ዝም ብዬ ተቀምጨ፣ የስንት ሺህ ተማሪ ስም ዝርዝር፣ አንድ በአንድ አንብቤ ጨረስኩ፡፡ ስጨርስ፣ ቆንጆ ልብ ወለድ እንዳነበበ ሰው እንደገና ከላይ ጀምሬ ማንበብ ጀመርኩና ድንገት፣ ከዚህ ሁሉ ሺህ ተማሪ እንዴት መሐሪ ተለይቶ እስር ቤት ገባ?” ብዬ አሰብኩ፡፡
ዓይኖቼን ከድኘ አንዱ ስም ላይ ጣቴን አሳርፌ ዓይኔን ስገልጥ፣ “ገረመው ታደሰ አለበል”ይላል፡፡ እሽ ገረመው ታደሰ አለበል ለምን አንዲት ሕፃን ኤልደፈረም? ምናልባት ገረመው የመሽኛ ዝግጅት አልተደረገልትም ይሆናል፣ ምናልባት ገረመው መጠጥ አልጠጣም ይሆናል፣ ወይም የዚያን ቀን የገረመው ጓደኛ፣ ከገረመው ጋር አድሮ ከዚህ መዓት
ታድጎት ይሆናል፡፡ ወይም ገረመው ገና ውጤት ተቀብሎ ወደ ቤት ሲሮጥ፣ መኪና
ገጭቶት ሞቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ለሞተ ሰው ምደባ አይመጣም ያለው ማነው? ይኼው ለታሰረስ ሰው እየመጣ አይደል እንዴ …?! እቃዣለሁ፡፡

እንዲህ እያልኩ ሳስብ ነበር፣ አንድ ሕፃን በራችንን አንኳኩቶ ሰው እንደሚፈልገኝ
የነገረኝ፡፡ ሮሐ ነበረች፡፡ መንገድ ዳር ላይ ቁማለች፡፡ መሐሪን ያየሁ ያህል ውስጤ በፍርሃት እየተሸማቀቀ ወደሷ ሄድኩ፡፡ ፈገግ ብላ አቀፈችኝ፡፡ እኔም አቀፍኳት “እንች… “አንተ” ስንባባል ቆይተን ስለ ምደባ ወሬ ጀመርን፡፡

እንኳን ደስ ያለሽ” አልኳት፡፡“እንኳን ደስ ያለህ አንተም ዝም ተባብለን ቆየንና አቀርቅራ መሬት መሬት እያየች…

አብርሽ …መሐሪን መጠየቅ ፈልጌ ነበር… እታካሂደኝም?” አለችኝ፡፡ ውስጤ በደስታ
ሲናወጥ ተሰማኝ፡፡ ለምንም አልነበረም፤ ለመሐሪ በዚህ ሰዓት ከማንም በላይ ሮሐ
ታስፈልገዋለች፡፡ እኔ ራሴ መሐሪን የማየት ድንገተኛ ፍላጎት ውስጤን ሞላው፡፡ በቀጣዩ ቀን ልንሄድ ተቀጣጥረን ተለያየን፡፡
ብዙ እስረኛ ጠያቂዎች እስረኞች፣ ፊት ለፊት እየተያዩ በመደዳ የተቀመጡበት ከእንጨት ርብራብ የተሠራ የማይመች አግዳሚ ላይ፣ እኔና ሮሐ ተቀምጠን ግርግሩን ስንመለከት፣
እሰረኞች ሮሐን ፍጥጥ ብለው ሲያዩዋት ጨነቀኝ፡፡ ዓይናቸውን አይነቅሉም ነበር::
ከጠያቂዎቻቸው ጋር እያዎሩ፣ ዐይናቸው ሮሐ ላይ ነው፡፡ ያኔ ስለ ጉዳዩ የሰሙና፣
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#በአሌክስ_አብርሃም

ድንገት ሮሐ ወደ ፊት ሰገግ ብላ ሹከሹክታ በሚመስል ድምፅ “ለምን መሐሪ …ለምን?” አለችው፡፡ ፊቷ ተቀያይሮ እንደ ቲማቲም ቀልቷል፡፡

“ለምን ምን አላት ምንም ሳይመስለው ፈገግ እንዳለ፡፡

ለምን ሳሌምን.....

ባኮሽ አታካብጅው ያጋጥማል!” አለ ትከሻውን ወደላይ በግዴለሽነት ጎፋ እድርስ፡፡
የመሐሪን ቆዳ ለብሶ የለየለት ወንጀለኛ ከፊታችን የተቀመጠ እስኪመስለኝ ድረስ፣ ፊቱ ላይ ትንሽ እንኳን ጸጸት አልነበረም፡፡ መሐሪ የዕድሜ ልክ ጓደኛዬ በአንድ ወር በምን ተአምር እንዲህ ዓይነት አስፈሪ ሰው እንደሆነ ሳወጣ ሳወርድ አልገባህ አለኝ፡፡ቢጨንቀኝ፣ ቀጥሎ ምን ይፈጠር ይሆን በሚል ግርምት፣ አንዴ ሮሐን አንዴ መሐሪን ማየት ጀመርኩ፡፡

“ምኑ ነው የሚያጋጥመው ሕፃን'ኮ ናት፣ እናተን አምና የተጠጋች ምስኪን ሕፃን
ትንሽዬ ልጅ…ትንሽ …" ሮሐ የምትለው ጠፍቶባት ፍጥጥ ብላ ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠና ዓይኗ እንባ ሞልቶ ስትመለከተው፣ ምንም በማይነበብበት ፊት ትክ ብሎ እያያት፣

ጠጥቸ ነበር፣ አንች ያመጣሽውን ውስኪ ጠጥቼ ነበር፡፡ በዚያ ላይ ትንሽ አሰሳጭተሸኝ ነበር፡፡ሁለታችሁም አበሳጭታችሁኝ ነበር” ብሎ ወደ እኔም ወደሷም ጠቆመና፣ “…በቃ የሆነው ሆነ…ይኼ አዲስ ነገር አይደለም፡፤ በኔ አልተጀመረም ብሎ ተራ በተራ አየን፡፡
ፈገግታው እስከዚያ ሰዓት ድረስ ሙሉ ለሙሉ አልከሰመም ነበር፡፡
እና ደፈርካት….” ብላ አንባረቀችበት፡፡ ድምፅዋ፣ እንኳን ድንገት የሰማውን፣ እኔም ጉዳዩን እየተከታተልኩ ያለሁትን የሚያስደነብር ነበር፡፡ በዙሪያችን የነበሩት ሁሉ ወደ እኛ ዙረው አዩን፡፡ መሐሪ አቀርቅሮ የእጁን መዳፍ እያገላበጠ ተመለከተና፣ ድንገት ተነስቶ
ቆመ፡፡

“ተቀመጥ አልጨረስንም? አለች ከመጀመሪያው በባሰ ጩኸት! ፖሊሶቹ ወደኛ እየመጡ ነበር፡፡
መሐሪ ልክ እንደሷ ጮሆ “ሁለተኛ እንዳትመጡ እዛው የራሳችሁን ሕይወት ኑሩ አለን፡፡ ግራ ተጋብቼ እንደተቀመጥኩ፣ ሮሐ ዘላ ተነስታ ቲሸርቱን ጨምድዳ አነቀችና፣ ባለ በሌለ ኃይሏ ቱ!” ብላ ምራቋን ፊቱ ላይ ተፋችበት፡፡ ከዚያ በኋላ እንደ እብድ መጮህ ጀመረች፡፡ ግራና ቀኝ የቆሙት ፖሊሶች አንቀው ወደኋላ ሲጎትቷት እካባቢው ድብልቅልቁ ወጣ፡፡
አንተ ደደብ! ምንም የማታውቅ ሕፃን ገድለህ፣ ደረትህን ትነፋለህ! መሃይም …ቱ! እዚህ ልትሸለም የመጣሀ መሰለህ? እስር ቤት የሚያኮራህ አንተ ማንዴላ ነህ? ለነፃነት ስትታገል ታስረህ ነው?…ወንጀለኛ ወንጀለኛ ሁነህ ነው! አንዲት ደሀ ቆሎ ሸጣ ያሳደገቻትን ሕፃን ደፍረህ! ዕድሜ ልክህን እዚህ ትበሰብሳለህ ቆሻሻ ኢዲየት! ልቀቁኝ ይኼን ውሻ ድንገት ጫማዋን ባልተያዘው እጁ አውልቃ ስትወረውር፣ መሐሪ ደረት ላይ አረፈ፡፡ ጥሩ ምት ነበር! ሌላ የሚወረወር ነገር ስትፈልግ፣ አንዱ ፖሊስ ሁለት እጇን አነባብሮ ጠፍንጎ ያዘና፣ እየገፈተረ ከእስረኛ መጠየቂያው ክልል ወደ ውጭ ወሰዳት፡፡ እየጮኸች ነበር
“ቆሻሻ ነህ! ራስሆን ነው የናከው! እብድ! ትንሽ ለቤተሰቦችህ አታዝንም? ውሻ

በተቀመጥኩበት እንደ ጨው አምድ ደርቄ ቀረሁ፡፡ መሐሪ የተወረወረበት ጫማ፣
ያረፈበት ቦታ ላይ ቲሸርቱን ተረጋግቶ አራገፈና፣ ጫማውን አንስቶ “ውሰድላት” ብሎ ሰጠኝ፡፡ ተቀበልኩት፡፡ በተረጋጋ እርምጃ ወደ ውስጥ ሲገባ፣ ከዓይኔ እስኪሰወር ተመለከትኩት፡፡ ዞር እንኳን አላለም፡፡ ፈጽሞ የማያውቀኝ ሰው ነበር የሚመስለው፡፡ በቃ የእድሜ ልክ ጓደኝነት ይኼው ነው …ጫማውን እንከርፍፌ እንደያዝኩ፣ እግሬን እየጎተትኩ ወደ ሮሐ ሄድኩ፡፡ አራት የሚሆኑ ፖሊሶች ከበዋት በየአፋቸው ይጮሁባታል፡፡ “አንች ያምሻል እንዴ? …የሕግ ታራሚ ልትደበድቢ ነው? ምኗ ጥጋበኛ
ናት! " ድንገት ቁጭ ብላ እራሷን ይዛ እዬዬዋን አስነካችው፡፡ ሌላኛው ፖሊስ ነገረ ሥራው አለቃ የሚመስል በእጁ መገናኛ ሬዲዮ የያዘ፣ ወደኔ በሬዲዮው አንቴና እየጠቆመ
“የጋሽ ግርማ ልጅ ናት አይደል” አለኝ፡፡ እራሴን በአዎንታ ነቀነቅሁ፡፡
“በል ይዘሃት ውጣ፡፡ ተነሽ አንች ውጭ !…” ብሎ ኮስተር አለ፡፡ ልይዛት ስሞከር እጇን መንጭቃ ተነሳችና፣ ጫማዋን አድርጋ ቀድማኝ መንገድ ጀመረች፡፡ ተከትያት ወጣሁ፡፡

ከዋናው በር እንደወጣን በጩኸት “አንድ ወር በሥርዓት እንኳን መተኛት አልቻልኩም በሽተኛ ነው የሆንኩት፣ ልክ አይደለሁም! ራሴን ስረግም ስጸጸት ነው የከረምኩት፡፡ ቢያንስ ትንሽ ጸጸት ፊቱ ላይ የማይ መስሎኝ ነበር፡፡ ራሴን ተጭኜ ይቅር ልለው፣ በዚህ ሰዓት ማንም ከጎኑ የለም ብዬ” ድንገት ወደ እስር ቤት የሚገቡ ስዎች አፍጥጠው እንደ
እብድ ሲመለከቷት ቆም ብላ፣
“ምን ሆናችሁ? ሰው አይታችሁ አታውቁም?” ብላ ስታምባርቅባቸው እንደ እብድ ሸሹን፡፡

"ሮሐ ተረጋጊ"

አታረጋጋኝ ..አልፈልግም፤ ማንም ተረጋጊ ምናምን እንዲለኝ አልፈልግም፡፡ ያሳለፍኩትን ራሴ ነኝ የማውቀው …”

“ይገባኛል…”

አይገባህም?

“ምንድነው የሚገባህ? ዳዲ፣ ሽጉጥ…ሽጉጥ ነው ያወጣብኝ! ለምን እሱን አፈቀርሽ ብሎ፡፡ እንደዛ ስላስፈራራኝ አቆምኩ? አላቆምኩም! ለምን? እወደው ነበራ! ምንድነው ችግሩ? ምንድነው እየሆነ ያለው? ምንም ሊገባኝ አልቻለም! …ምንም!! ታምነኛለህ? አፍ
አውጥቼ ሴክስ እናድርግ ብዬው አውቃለሁ፣ የፈራ መስሎኝ ልብሱን ላስወልቀው ታግዬዋለሁ፡፡ ሴት እንደዛ ታደርጋለች? አታደርግም! ሁሉን ነገሬን ለሱ መስጠት የመጨረሻ ደስታዬ ነበር፡፡ ምን ስለሆነ? ቆንጆ ስለሆነ…ምን ቆንጆ ነው? ጥሙጋ! ሃብታም ስለሆነ?…ምንም! በቃ ስላፈቀርኩት፡፡ ከመሳሳም አልፎ አያውቅም! እንደፈለክ አድርገኝ ብየዋለሁ …ከዚህ ወዲያ ምን ላድርግለት? ለምን ይቀናል? ለምን? እንደሚያፈቅረኝ ይነግረኛል፣ ቆንጆ እንደሆንኩ ይነግረኛል፡፡ አንችን ካላየሁ፣ ነፍሴ መንፈሴ ሲለኝ ነው የኖረው፡፡ የፈለገ ቢጠጣ በርሚል ሙሉ ቢጠጣ …ምን ሁኖ ነው አንዲት ሕፃን….በሽተኛ ነው! …በሽተኛ አስተዳደጉም ምኑም በሽተኛ በራሱ
የማይተማመን ስቱፒድ ያ እኔም በሽተኛ ነኝ በዚህ ዕድሜው መጸዳጃ ቤት ለመሄድ
እንኳን አባቱን የሚያስፈቅድ ልጅ፣ ጤነኛ አለመሆኑን እንዴት አላውቅም !በራሱ ቤት በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ የሚኖር በሽተኛ ቱ.. ጮሃ ጮሃ ሲወጣላት ትከሻዬ ላይ ተደፍታ ስቅስቅ ብላ አለቀሰችና፣ እኔ ምንም አላልኩትም የዛን ቀን ምሽት በእኔ
ምክንያት የሆነ እየመሰለኝ በጭንቀት ልሞት ነው. ያንን ውስኪ ማምጣቴ፣ በየቀኑ በየቀኑ ይጸጽተኛል” አለችና ማልቀስ ቀጠለች፡፡
“የዚያን ቀን ምሽት ነበርኩኮ እኔ ምስክር ነኝ …ሁሉም ነገር፣ የራሱ ችግር ነው፤ አንድም ነገር አላጠፋሽም፡፡ እመኝኝ፣ ላፅናናሽ እይደለም እንዲህ የምለው! ምንም ያጠፋሽው ነገር የለም፡፡ ራስሸን የምትወቅሽበት ምንም ምክንያት የለም! ውሸቱን ነው የቀባጠረው፤ የራሱ
ችግር ነው፣ የራሱ!” ከልቤ ነበር እንዲህ ያልኳት! ንግግሬ አጽናንቷት ይሁን፣ አልያም ለቅሶዋን ጨርሳ የዚያን ቀን እንባዋን ጠራርጋ ወደቤቷ ሄደች፡፡

ልቤ በመሐሪ ማዘኑን ትቶ “የራሱ ጉዳይ!” የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሶ ነበር፡፡
እግዚአብሔር የመሆን ፍላጎቴን ትቼ እንዲያውም ቀሪ ዘመኔን ሁሉ እንደ ሰይጣን በሰዎች ሁሉ ላይ ከፉ ለመሆን ተመኘሁ፡፡ ሰው የሚባል ፍጥረት ተለቃቅሞ ሲኦል ቢወረወር ሲያንሰው ነው፡፡ ሰበበኛ ሁሉ፡፡ መሐሪ ሳሌም ላይ ላደረገው ነገር ሁሉ እኔና ሮሐን መውቀሱ፣ ውስጤን ቢያቃጥለውም፣ በዚህ ጉዳይ በቃ አያገባኝም ብልም፣ ሳሌም ግን ትናፍቀኝ ነበር፡፡ የእውነት ትናፍቀኛለች፡፡ ሳቋ ይናፍቀኛል፣ ከእናቷ እቅፍ
ጀምሮ በዓይናችንና በነፍሳችን እቅፍ
👍4😁1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በአሌክስ_አብርሃም

አንዴ በሕይወት ውስጥ እያወቅናቸው ሰዎች ከናካቴው መስራት እና፣ከሕይወታችን ማስወጣት አንችልም። ሌላው ሁሉ ቢቀረሸ እንደ ሸረሪት ድር የቀጠነች ንፋስ የሚወዘውዛት የትዝታ ክር በመካከላችን ትኖራለች።

ጥሩም ይሁን መጥፎ ትዝታዬን በልቤ እንደተሸከምኩ ወደ ተመደብኩበት ዩኒቨርስቲ ተጓዝኩ፡፡ ያለፈ ታሪኬ ሁሉ በየአጋጣሚው እየመጣ ቢረብሸኝም የዩኒቨርስቲ ቆይታዬ ነገሮችን ወደኋላ እንድተዋቸውና በብዙ አዳዲስ ጓደኞች ተከብቤ አዲስ ሕይወት እንድጀምር አድርጎኝ ነበር፡፡ ሕይወቴ በማስታወስና በመርሳት መካከል የቆመች ነበረች፡፡
እጠናለሁ፡፡ብዙ ብዙ ነገር አጠናለሁ፤ ያጠናሁትን ላለመርሳት እታገላለሁ፡፡ በትምህርት ዓለም አለመርሳት ነበር ሰው የመሆን መሠረቱ፡፡ በተለይም በኔዋ አገር የትምህርት ዋጋው አዲስ ነገር ከመፍጠር በላይ፣ የሸመደዱትን አለመርሳት ነበር፡፡ በዚያው ልክ ያለፈ
ታሪኬን ለመርሳት እታገላለሁ፤ ሕይወት ውስጥ ወደፊት የመቀጠል መሠረቱ መርሳት ነበር፡፡ግን ደግሞ ልንረሳ ከምንሞከረው ትላንታችን ለይቶልን እንዳንርቅ፣የሚያስተሳስሩን ቀጫጭን ክሮች አይጠፉም፡፡ ሮሐ አንዷ ክር ነበረች፡፡ ሁለታችንም ዩኒቨርስቲ ከገባን
በኋላ፣ ቶሎ ቶሎ እንደዋወል ነበር፡፡በአምስት ዓመት የዩኒቨርስቲ ቆይታዬ ከመደዋወል በአካል እስከ መገናኘት እንደ ሮሐ የምቀርበው ሰው አልነበረም፡፡ በየጊዜው ስንደዋወል አብዛኛው ወሬያችን ስለየቀኑ ውሏችን ነበር፡፡ ብዙ እናወራለን፣ ሳቅ ለመፍጠር እንታገላለን፡፡

ዩኒቨርስቲ ተጋባሁ በወራት ውስጥ፣ መሐሪ የአስራ ስድስት ዓመት እስር እንደተፈረደበት ሰማሁ፡፡ ተውኩት፣ ረሳሁት፣ ያልኩት የመሐሪ ነገር አንጀቴን አንሰፍስፎት፣ የዚያን ቀን ምሽት ብቻዬን የሆነ ዛፍ ሥር ተቀምጨ አለቀስኩ፡፡ ያዘንኩት አንድ ወንጀል በሠራ ሰው
ላይ ስለተፈረደ ፍርድ አይደለም፣ እኔ እንደጓደኛ፣ ማሚና ጋሽ ዝናቡ ብዙ ዋጋ
ከፍሎ እንዳሳደገ ወላጅ፣ ሮሐ እንደፍቅረኛ፣ አገር እንደ አገር አንድ እንደላባ የሳሳ ንጹህ ነፍስ በአንድ ምሽት አጣን፡፡ ትልቅ ተስፋ፣ ያውም ተስፋውን እውን ከሚያደርግበት አቅም የነበረው ልጅ፣ አሥር ደቂቃ ባልሞላ ስሕተት ከገጸ ምድር ጠፋ፡፡ የመሐሪ ትንንሽ እጆች፣ ፍርሃቱ፣ ከልጆች ጋር ስንጣላ እንኳን፣ በፍርሃት እኔ ሥር መጥቶ ሽጉጥ የሚለው
ነገር፣ ሁሉም ነገር በየተራ እየታወሰኝ …አለቀስኩ:ማልቀስ ብቻ ሳይሆን፣ ብጮህ፣ኡኡ! ማለት አማረኝ፡፡

እዚያው እንደተቀመጥኩ ለሮሐ ደወልኩላት፡፡ በጋራ ለተነጠቅነው ፍቅር ቢያንስ ስሜት እንጋራለን ብዬ፡፡ቀድማኝ ሰምታ ነበር፡፡ ፍልቅልቅ ብላ ያንን ውሻ አስራ ስድስት ዓመት እከናነቡት ሲያንሰው ነው! አለችና በንግግሯ ተበሳጨሁ? ኤልተበሳጨሁም አዘንኩን
አላዘንኩም! ግን ፍቅር የሚባለው ነገር እንዴት ነው ትንሽ እንኳን ቅሪት ሳይተው
እንዲህ ጥርግርግ ብሎ የሚጠፋው? ብዬ ፍቅርን ተጠራጠርኩት፡፡ በዓለም ላይ የነበሩ የሰው ልጅ ሥልጣኔዎች ሁሉ ከምድር ላይ ለደመሰሱ፣ የሆነ ቅሪት ትተዋልኮ፣ ያንን ቅሪት ነው ቅርስ የምንለው፡፡ ስዎች ይህችን ዓለም ሲሰናበቱ፣ ቢያንስ ለሆነ ሰው ልብ
ውስጥ የሆነች ክር ይተዋሉ፣ ወንዞች ሲደርቁ፣ በደረቀ ምድር ላይ የሚተውት ዱካ አለ፡፡በዚያ መልካ ላ ነው ስዎች የሚሻገሩት፡፡ ምንም አሻራ የማይተው ጉዳይ፣ ሲጀመርም የሌላ ነገር ብቻ ነው፡፡ ወይስ የከሸፈ ፍቅር የሚተወው ዳና ጥላቻ ይሆን?

ለዕረፍት ወደ ቤተሰብ ስመለስ፣ ማሚንም ሆነ ጋሽ ዝናቡን ሂጄ አላየኋቸውም፡፡ እናቴ ሂድና ጠይቃቸው ብልግና ነው ብትለኝም፣ እሽ እያልኩ ሳልሄድ ቀረሁ፡፡ ወደ ዩኒቨርስቲ ከተመለስኩ በኋላ፣ አልፎ አልፎ ለማሚ የመደወል ሐሳብ ውል እያለብኝ፣
ስልኬን አንስቼ እንደስሜ ነፍሴ ላይ የታተመውንና መቼም የማልረሳውን የነመሐሪ ቁጥር ከደወልኩ በኋላ፣ ሲጠራ የዘጋሁበት ጊዜ ብዙ ነበር፡፡ ወደኋላዩ ከመዞር ይልቅ፣ ወደፊት ብቻ ለመራመድ ስታገል፣ ከፊቴ የሚያጋጥሙኝ ደማቅ የሕይወት ገጠመኞች ረድተውኝ፣
ትላቴን አደበዘዙት፡፡ ድብዛዜው ከመርሳት የማይተናነስ ነበር፡፡

የሦስተኛ ዓመት ተማሪ ሆኜ አንድ ቀን እቤት ስልክ ስደውል፣ እናቴ በብዙ መንጠራዘዝና የረዘመ ማለሳለስ (እንዲህ ስትሆን ይጨንቀኛል) አሳዛኝ ነገር ነገረችኝ፡፡

ምን ሁነሻል? አባባ ደህና አይደለም እንዴ?” አልኳት፡፡ ቀስ ብላ ጋሽ ዝናቡ ማረፉንና ቀብር ውለው መግባታቸው እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ መጀመሪያ ጋሽ ዝናቡ አረፈ ማለት፣ሞተ ማለት መሆኑን፣ ልክ ከሌላ ቋንቋ እንደሚተረጎም ለራሴ ተረጎምኩ እና እየፈራሁ
“ጋሽ ዝናሱ ሞተ” ብዬ ጠየቅኋት፡፡

“አዎ ትላንት ማታ አረፈ"

“ምን ሆነ? ታሞ ነበር እንዴ?

"አረ ድንገት ነው።"

በኋላ ቆይቼ ስሰማ፣ ጋሽ ዝናቡ የሞተው ራሱን አጥፍቶ ነበር፡፡ በተለይም መሐሪ
ከተፈረደበት በኋላ፣ አእምሮው ጤነኛ አልነበረም አሉኝ፡፡ብቻውን ያወራል፤ ሥራውንም በአግባቡ መሥራት ስላልቻለ ለጊዜው ጡረታ አስወጥተውት ነበር፡፡ በዳኝነት ተሠይሞ የሚቀርብለትን ፋይል ሁሉ፣ ትልልቅ ወንጀል የሥሩ ወንጀለኞችን ሳይቀር ነፃ ናችሁ እያለ መልቀቅ ጀምሮ ነበር፡፡ አንድም ቀን መሐሪን እስር ቤት ሂዶ አልጠየቅም፡፡
በመጨረሻም ያ ባለ ነጎድጓዳማ ድምፅ፣ጋሽ ዝናቡ ራሱን አጥፍቶ ይችን ዓለም በዝምታ ተሰናበታት፡፡ ውስጤ ተንገበገበ፡፡ ቢያንስ እየሄድኩም ሆነ እየደወልኩ ብጠይቀው፣ትንሽ
መጽናናት ይሆንለት እንደነበር ማን ያውቃል፡፡

"መሐሪ ሰማ ብዬ እናቴን ጠየቅኋት።

"እሱ ልጅማ ጤናም አይመስለኝ፣ አንዳች ነገር ለከፎታል”

እንዴት?”

“በፖሊስ ታጅቦ አባቱን እንዲቀብር የሰፈሩ ሰው ሁሉ ተሯሩጦ አስፈቅዶ፣ ና ውጣ
አባትህን ቅበር ቢሉት፣ ኤልሄድም አለ አሉ፡፡ በቃ አባቱን ላይቀብር ቀረ፡፡ እወደው
ነበር፡፡ በዚህ ነገር ትንሽ ቅር አለኝ፡፡ አይ ልክ አልሠራም

የዚያን ቀን ሁለት ሦስት ጊዜ ለማሚ ደውዬ ለቅሶ ለመድረስ አስቤ ተውኩት፡፡ ለእረፍት ወደ ቤተስብ ስመለስም፣ አልጠየኳትም፡፡ እሸሽ ነበር፡፡ አጥብቄ እሸሽ ነበር። መሐሪ እኔና ሮሐን እስር ቤት ከወቀሰን በኋላ ውስጤ፣ ትንሽ ይጨናነቅ ነበር፡፡ “የእውነት እኔና ሮሐ ሳሌም ላይ ያ ነገር ለመፈጠሩ ምክንያት ነበርን? እያልኩ አስባለሁ፡፡ ይኼን ነገር አንዳንዴ ለሮሐ ላነሳባት እፈልግና፣ ከአፌ ላይ እመልሰዋለሁ፡፡ ብቻዬን ራሴን ዕውቅስና
ሳጽናና ለዓመታት ኖሬያለሁ፡፡ ማጽናኛዬ ሁልጊዜም እንድ ዓይነት ነው፡፡መሐሪ ደደብ ነው የሚል፡፡ ራሱን ገደለ፣ አንዲት ሕፃን ገደለ፣ ይኼ አልበቃው ብሎ እንዴት እኔን ይወቅሳል?
።።
ሮሐ ከእኔ ቀድማ ነበር የተመረቀችው፡፡ በአካውንቲንግ፡፡ በዚያው በተመረቀችበት
ዓመት አዲስ አበባ መጣች፡፡ አዲስ አበባ በመምጣቷ፣ ከልቤ ተደስቼ ነበር፡፡ ውስጤ በደስታ ሲፍነከነክ በስልክ የገነባነው ጓደኝነት ግዝፈት ያኔ ገባኝ፡፡ ሥራ አልጀመረችም።ሀብታም ዘመዶቿ “ትምህርት ላይ ከርመሽ የምን ወደሥራ መሮጥ ነው” አሉኝ አለች።ያለው ማማሩ፡፡ በየቀኑ እንደዋወላለን (ለነገሩ እሷ ነች የምትደውልልኝ አንዳንዴ ድንገት ግቢ ትመጣለች፡፡ ጓደኞቼ ሁሉ አውቀዋት ነበር፡፡ “መልአክህ መጥታለች
ይሉኛል፡፡ እዚህ ግቢው በር ላይ
አቁመህ ቀክፍያ ብታስጎበኛትኮ፣ በሳምንት ውስጥ በቃ፣ ሚሊየነር ትሆናለህ” ይሉኛል፡፡

"በጣም ጥ፣ ያበደራችሁኝን ሁሉ በዚሁ ይጣጣ፣ አይታችኋታል” ብዬ በራሳቸው ቀልድ ሂሳብ ሠራሁ፡፡ ሮሐ ታዲያ ስትሰማ ስንት አበድረውህ ነው? አለችኝ እየሳቀች “ሦስት ብር

“በሦስት ብር፣ እንኳን እኔ፣ ድንቢጥ አይጎበኝም፣ ጥሩ ነጋዴ
👍1
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#በአሌክስ_አብርሃም

....አንድ ቅዳሜ ቀን ራት ስንበላ ድንገት “እስካሁን ጓደኛ አልያዝኩም” አለችኝ፡፡

አንች ምንድነሽ ታዲያ”

"ኖ... ሴት ጓደኛ"

“ይቅርታ፣ ወንድ መሆንሽን እላወኩም!”

ለዛ ቢስ …ገብቶሃል እስካሁን ፍቅረኛ ለምን አልያዝዘከም ኮስተር አለች፡፡

"እኔጃ ትከ ብላ አየችኝና፣

“መቼም እየደስከኝ አይደለም፣ አይደል?”

ለምን እደብቅሻለሁ? እኔጃ! በቃ ሙሉ ለሙሉ ትኩረቴ ትምህርት ላይ ነበር፡፡ ብዙም ርሌሽን ሽፕ ላይ ድፍረቱ አልነበረኝም፣ እፈራለሁ፣ በጣም እፈራለሁ፡፡ ወይም እኔጃ አልኳት፡፡ ዝም ብላ ቆየችና፣

እኔን አልጠየከኝም አራት ዓመት ሙሉ በስልክ ስናወራ ለዕረፍት ስንገናኝ አንድም ቀን ጓደኛ ልያዝ አልያዝ ጠይቀኸኝ አታውቅም፣ ምናገባኝ ነው፣ ወይስ አንዱ አንጠልጥሎ ወደዛ በወሰዳት ነው …ምንድነው?”ብላ አንገቷን ሰበር አድርጋ አየችኝ፡፡ ይኼን
አስተያየቷን ስወደው፡፡

አንዳንዴ ልጠይቅሽ አስብና …አለ አይደል

“ከመሐሪ ጋር የነበረንን ነገር የምታስታውሰኝ እየመሰለህ ወይም ምን አስቦ ነው ትለኛለች ብለህ ትፈራለህ?”

እንደዛ ነገር መሰለኝ

“ለማንኛውም ጓደኛ የለኝም … ወንዶችን መቅረብ አልቻልኩም

“ከመሓሪ ጋር በተያያዘ ነው? …”

አላውቅም! ከሆኑ ወንዶች ጋር እቀራረብና፣ ድንገት ዓይናቸውን ማየት ያስጠላኛል።በቃ ውስጤ ምንም የተረጋጋ አልነበረም፤ እረበሻለሁ፡፡ ለረዥም ጊዜ እንቅልፍ በማጣት ተቸግሬ ነበር፡፡ ሕከምና ሁሉ ወስጃለሁ"

ኧረ ባክሽ አልነገርሽኝም

"ለማንም አልተናገርኩም”

እንኳን ማንም መሆኔን ነገርሽኝ”

“ኖ..ብላ እጄን በሁለት እጆቿ አፈፍ አድርጋ ያዘችኝ! የእጆቿ ልስላሴና ሙቀት መቼም አይረሳኝም፡፡እጆቼን እንደያዘችኝ ትከ ብላ እያየችኝ “በእነዚህ አራት ዓመታት በሕይወትሽ ውስጥ የነበረ ብቸኛ ሰው ጥሪ ብባል አንተ ብቻ ነበርክ” ዝም ብዬ እየኋት፤ ለእንደዚህ ዓይነት ወሬዎች ባዕድ ነኝ፡፡ በውስጤ ግን ያለፉትን ዓመታት ተመልሼ ሳስብ፣ እኔም
ከእርሷ ሌላ ከልቤ የምቀርበው ሰው ማስታወስ አልቻልኩም፡፡

“እኔም ከአንች ውጭ የቀረብኩት ሰው አልነበረም ዝም ተባባልን፡፡ እጆቼን
እንደያዘቻቸው ነበር፡፡ በረዥሙ ተንፍሳ እጆቼን ለቀቀችና ቦርሳዋን አንስታ እንሂድ
አለችኝ፡፡

ከተለያየን በኋላ ስለ ሮሐ ሳስብ አመሸሁ፡፡ እንግዳ ነበር ስሜቱ፡፡ የተዘበራረቀ፡፡ እንደ
ማዕበል ውስጤን ያናወጠ ስሜት፡፡ አብሪያት የመሆን ፍላጎት ውስጤን ለጉድ
ይገፋዋል፡፡ ሁለት ሦስት ጊዜ ልደውልላት ስልኬን አንስቼ ተውኩት፡፡ የዚያን ቀን ሌሊት መሐሪን በሕልሜ አየሁት፡፡ ብዙ ጊዜ ሰሕልሜ አይቼው አውቃለሁ፡፡ ሁሉም ሕልሞቼ አብረን ካሳለፍናቸው ጊዜዎች ኣንዱ ላይ የሚያርፉ ነበሩ፡፡ የዚያን ጊዜው ግን የሚጨቅ
ዓይነት ሕልም ነበር፡፡ መሐሪ ጋር አብረን ታስረን ይመስለኛል፡፡አንነጋገርም፡፡
አንቀሳቀስም፡፡ ፊት ለፊት ተቀምጠን ዝም ብሎ ያየኛል፡፡ በቃ ማየት ብቻ!! ፊቱ ላይ ሳቅ የለ፣ ኩርፊያ የለ ዝም ያለ ፊት!
።።
ሮሐ ጋር ግንኙነታችን በየቀኑ ሆነ፡፡ የዘመዶቿ ቤት ቅርብ ነበር አራት ኪሎ አካባቢ፡፡ብዙ ጊዜ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት ያለች ባለ አንድ ፎቅ ካፌ ውስጥ ተቀምጣ ትጠብቀኛለች። እናወራለን፣ እንሳሳቃለን፡፡ እንዴት ፊት ለፊት ከመቀመጥ ጎን ለጎን ወደ መቀመጥ እንደተሸጋገርን ትዝ አይለኝም፡፡ እንዴት እጅ ለእጅ ተያይዞ መንገድ ላይ
መሄድ እንደጀመርን ትዝ አይለኝም፡፡ በሁለት እጆቿ ክንዴን ይዛ፣ ትከሻዬ ላይ እራሷን ጣል ማድረግ የጀመረችው መቼ እንደነበር አላስታውስም፡፡ራሳችንን ወደ ምንም አልገፋነውም፡፡ ከምንም አልከለከልንም፡፡ ልክ የሆነ ባሕር ላይ ያለች ጀልባ ውስጥ ነፍሳችንን እንደ ማስቀመጥ ነበር፡፡ ድንገት ማዕበል ተነስቶ ወደማናውቀው ቦታ
አሽቀንጥሮ ወሰደን፣ ዓይኖቻችንን ስንገልጥ፣ ያበደ ፍቅር ውስጥ ነበርን፡፡

ማዕበሉ የተነሳባትን ቅጽበት ግን አስታውሳለሁ፡፡ አንድ ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ቲያትር ልናይ ጎን ለጎን በተቀመጥንበት ጨለማ አዳራሽ ውስጥ ልክ ስማችን የተጠራ ይመስል፣
ሁለታችንም ድንገት ዙረን ተያየን፡፡ የማስታውሰው ዓይኖቼን ስጨፍንና የሮሐ
ከንፈሮች ከንፈሬ ላይ ሲያርፉ ነበር፡፡ ልክ ርችት እንደሚለኮሰው በዚያች ቅጽበት የሆነ ነገር በመሀላችን ተጫረ፡፡ ስማያትን በብዙ ብርሃንና ቀለማት ተጥለቀለቀ ደንግጨ ነበር፡፡ ስንወጣ አልተነጋገርንም ከንዴን ይዛኝ ቀዝምታ ሸኘኋት! ውስጤ ግን በጸጸት እየተጥለቀለቀ ነበር፡፡ ክሕደት ነው አልኩ ለራሴ፡፡ ብዙ ሚሊዮን ሴቶች ባሉባት ዓለም፣ ጊዜ የጣለውን የጓደኛየን ፍቅረኛ መንጠቅ ምን የሚሉት ከፋትና ስግብግብነት ነው? እያልኩ፣ በራሴ አፈርኩ፡፡ ምናልባትም ሳላውቀው ውስጤ ያደገ የበታችነት ስሜት ሳይሆን አይቀርም አልኩ፡፡ መሐሪን በዚህ የበለጥኩ መስሎኝ፡፡ ተብከነከንኩ፣ ግን
በዚያው ምሽት ሮሐ ደውላልኝ ገባህ ስትለኝና ምንም እንዳልተፈጠረ ስናወራ ሁሉም ነገር ከአእምሮዬ ጠፋ፡፡ ድምፅዋን ስሰማ እንቅዥቅዥ የሚያደርገኝ ነገር ነበር፡፡

ሮሐ ስታፈቅር ሁሉን ነገሯን የምትሰጥ ልጅ ነች፡፡ ሁሉ ነገሯን፡፡ ምናልባት ባይሳካስ ብላ የምታስቀረው ነገር የለም፡፡ ካፈቀረችው ሰው ውጭ ህይወት በምድር ላይ ስለመኖሩም ትዝ አይላትም፡፡ በሕይወቷ ውስጥ ምንም የተወሳሰበ ነገር የለም፡፡ የኑሮ ቀመሯ ግልጽ
ነው ካፈቀረች ታፈቅራለች፣ ከጠላች ትጠላለች በቃ ነፍሷ ወዶኝ ነበር፡፡ለምን
ይመስልሃል ጓደኛ ያልያዝኩት? ስለወደድኩህ ነው ስላፈቀርኩህ እወድሃለሁ የእውነት
እወድሃለሁ!" የተሰማትን ቃል በቃል ሳታፍር ትናገራለች፡፡“የዶርም ልጆች ሁሉ
ያውቃሉ፥ ካልተደዋወልን ስነጫነጭባቸው ነበር የምውለው፡፡”

ነፍሷ ያለፈውን ሁሉ ረስቶ እኔ ጋር ነበር .…መሐሪ የሚባል ሰው በምድር ላይ መኖሩን ሁሉ ስለማስታወሷም እንጃ፡፡ እኔ፣ ፍቅሬም ፍርሃትና ጸጸቴም በጥልቅ ዝምታ ውስጥ ነበሩ፡፡ ከልቤ ባፈቅራትም ጸጸት በየደቂቃው ውስጤ መጫሩ አልቀረም፡፡ ተገናኝተን በተለያየን ቁጥር፣ ያንገበግበኛል፡፡ አብረን ስንቀመጥ የሰው ሚስት ሰርቄ የተገናኘሁ ያህል፣ አካባቢዬ ምቾት አይሰጠኝም፡፡ በዚህ በኩል ኃይለኛ ጸጸት፣ በሌላ በኩል አቅሌን የሚስት ፍቅር እንደ ድፎ ዳቦ ከላይና ከታች የሚንቀለቀል እሳት ውስጥ ነበርኩ፡፡

ከአንድ ዓመት በላይ ሮሐ ጋር በፍቅር አበድን፡፡ ሲቆይ የኔውም ህሊና ዓይኖቹን ጨፈነ መሰለኝ፣ እኔ ብሽ ቁጭ አልኩ፡፡ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ጠበቡን፤ “…ከአምስት ኪሎ እስከ አራት ኪሎ ያሉት መንገዶች፣ ብዙ የተራመደባችሁ ማነው?” ቢባሉ አንዲት የሳበችውን አየር እንደ አኮረዲዮን ሙዚቃ እድርጋ ወደ ውጭ የምትተነፍስ ውብ ልጅና፣ ከዓመት እስከ ዓመት የማትቀየር ኦሞ ከለር ጅንስ ሱሪ የሚለብስ፣ እንደ ሌባ ዙሪያውን እየተገላመጠ የሚሄድ ልጅ” የሚሉ ይመስለኛል፡፡ መንገዱ ለምዶናል
መንገደኛው ለምዶናል፡፡ አምስት ኪሎ ታከሲ ተራው አጥሩ ሥር የሚቀመጥ የኔ ቢጤ፤ሮሐ በመጣች ቁጥር ምጽዋት አስለምዳው ኖሮ አንድ ቀን “ምነው አረፈድሽ” አላት፡፡ልክ ደመወዙን ይዛ እንዳረፈደችበት ዓይነት፡፡ እዚህ ድረስ መንገዱ የኛ ሆኖ ነበር፡፡

አዲስ አበባ የመቆየቷ ምክንያት እኔ ብቻ ነበርኩ፡፡ አትሠራም አትማርም፡፡ ዕድሜ
ለሀብታም ዘመዶቿ፣ ዘና ብላ እየኖረች፣ የመኖሯን ምክንያት ግን እኔን አድርጋ ነበር፡፡የአዲስ እበባ ሕዝብ ቁጥር ስንት ነው ብትባል አንድ” ብላ ወደ እኔ የምትጠቁም ነው የሚመስለኝ፡፡ ደስ ባላት ሰዓት፣ ድንገት ተነስታ ትመጣለች፡፡ ድንገት ስትመጣ፣ ነፍሴ በደስታ የሚያደርጋትን
👍2
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#በአሌክስ_አብርሃም

....ማሬ መሽኛኘት የለም… መሐንዲስ ሆንክ አይደል …እስቲ የዚህን ሆቴል ሕንጻ አሠራር እንገምግመው” ብላ እየሳቀች እዚያው ሆቴል አራተኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኝ ክፍል እጄን ይዛ ወሰደችኝ፡፡ ፈጽሞ ባላሰብኩት ቀን፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሮሐ ጋር አብረን ያደርነው እንደዚያ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ነበረች፡፡ ለእርሷም የመጀመሪያዋ፡፡ ጧት ፊቷን የሸፈናትን
ሉጫ ጸጉሯን እንደመጋረጃ ከፊቷ ላይ ወደኋላ እየሰበሰበች፣ ሐፍረት በቀላቀለበት ፈገግታ አየችኝና “ባለጌ ነህ እሽ” አለችኝ፡፡ ከዚያ ቀን በኋላ ብልግና ቀን ወጣለት፡፡የአዲስ አበባ አልቤርጎዎች እንደ አዲስ አበባ መንገዶች ሁሉ ዳናችን ታተመባቸው።በጠረናችን ነበራችን ተጻፈባቸው፡፡በፍቅር አብደን ነበር፡፡ስላለፈውም ስለ ወደፊቱም አላወራንም፡፡ማዕበሉ ወደፈለገበት እንዲወስደን ራሳችንን በፍቅር ጀልባ ላይ አስቀምጠን
ተውነው፡፡ በዚህ በኩል እንሂድ ብለን መንገድ ስላልመረጥን፣ የተሳሳተ መንገድ የሚባል ነገር በሕይወታችን አልነበረም፡፡ ምንም መዳረሻ ስላላለምን፣ የደረስንበት ሁሉ ልክ ነበር፡፡ ሮሐ ለፍቅር የተፈጠረች ልጅ ናት፡፡ ዝባዝንኬ ሳታበዛ በማፍቀር ብቻ፡፡የሕይወትን ደስታ ለምርኮ መውሰድ ተሰጥቷታል፡፡ ምርኮኛ ልሁን፣ አብሬያት ልሰለፍ ባይገባኝም፣ ብቸኛ ፍላጎቴ ሁልጊዜ የትም ቦታ አብሪያት መሆን ብቻ ነበር፡፡

ወደ ቤተሰብ ልመለስ ስዘጋጅ፣ ሮሐ አብረን እንሄዳለን ብላ መዘጋጀት ጀመረች፡፡ ከእንደገና የተዳፈነ ፍርሃቴ ሁሉ ተመለሰ፡፡ አንድ ላይ መሄዳችን ቢያንስ ለቤተሰቦቻትን ወሬው ጥሩ አይደለም፣ አንች ቆይተሸ ተመለሽ፣ ከሳምንት በኋላ መምጣት ትችያለሽ
አልኳት፡፡

ትክ ብላ እያየችኝ፣ “የራሱን መንገድ ተከትሎ የሄደ ሰው፣ ስእኔም ሆነ በአንተ ግንኙነት እንዲወስን አልፈልግም፡፡ ወላ ቤተሰብ፣ ወላ የአገሩ ሰው በሙሉ፡፡ ስለራሳችን ራሳችን ብቻ እንወስናለን

“ማለት የፈለኩት …"

“ማለት የፈለከውማ የጓደኛውን ገርል ፍሬንድ ቀማ ይሉኛል ነው፡፡ አይደል? ይበሉህ!አልቀማህም! ሲጀመር እኔ እንደ ኳስ የሚቀባበሉኝ መጫዎቻ አይደለሁም! ከልቤ ስላፈቀርኩህ የእውነት ስለወደድኩህ ነው አብሬህ የሆንኩት! መሐሪ የሚባል ጓደኛ ከአምስት ዓመት በፊት ነበረኝ፡፡ ለአንተም ጓደኛህ ነበር፡፡ አምናው ነፍሷን የሰጠችውን ሴት ቆሻሻ ላይ ሲወረውራት እክብረህ አነሳሃት ስላነሳሃት ሳይሆን፣ ከልቧ ስለወደደችህ
አብራህ ሆነች፣ በቃ! በራስህ ልትኮራ ነው የሚገባህ” የምትናገረው በቁጣ ስለነበር፣
የምላትን ነገር አጣሁ እናም ዝም ብዬ ስመለከታት

እሽ ሁሉም ነገር ይቅር፣ ተወልጀ ወዳደኩበት ከተማ መሄድ አልችልም እንዴ? ብላ ሳቀች፡፡

"አብሪያት ሳቅሁ"

“ግን በአጋጣሚ አውቶብስ ውስጥ ጎን ለጎን ካለ ወንበር ላይ አብሮኝ የተማረ ልጅ ጋር ተገናኘሁ፡፡ ይኼ መቼም አያስውግር አያሰቅል ወደኔ ጎትቸ አቀፍኳት፡፡ ጥብቅ አድርጌ አቀፍኳት፣ የእዉነት አፈቅራታለሁ፡፡ ምናባቴ እንደሚሻለኝ አላውቅም፡፡ ምን
እንደሚጠብቀን ደግሞ እርሷ አታውቅም

ቸኮ ነገር ነሽ”

በአንድ አውቶብስ ያውም የማውቃቸው የከተማችን ነጋዴዎች የታጨቁበት አውቶብስ በተደገፈችኝና በነካችኝ ቁጥር እየተሳቀቅሁ አብረን ተጓዝን፡፡ አዲስ አበባ ቆይቼ ስመለስ ሁልጊዜም ተወልጄ ያደኩባት ከተማ ትጠበኛለች፤ እታፈናለሁ፡፡ ሐሳቤ ከቤተሰቦቼ ጋር የተወሰነ ጊዜ ቆይቼ ወደ አዲስ አበባ ለመመለስና፣ሥራ ለመፈለግ ነበር ግን ያላሰብኩት ነገር ሆነ፡፡ በትውልድ ከተማዬ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ ሥራ አግኝቸ ጀመርኩ፡፡ ሥራዬ
መጀመሪያ አካባቢ አሰልቺ ነበር። የማንንም አጥርና ድንበር ስለካና ጓሮ ለጓሮ ስዞር እውላለሁ፡፡ ያውም ድንበሬ ተገፋ በሚል ነገረኛ እየተዘለፍኩና እየተዛተብኝ፡፡ የአገሬ ሰው ከአገሩ ድንበር የበለጠ፣ ለመኖሪያ ቤቱ ድንበር ልቡ ስስ መሆኑን ያወቅሁት ያኔ ነው፡፡ ለአገሩ የታፈሩ የተፈሩ የሚባሉ ሽማግሌ፣ የቡና ስኒ የማታስቀምጥ መሬት ከድንበሬ ሄደችብኝ ብለው፣ ሰው ካልገደልኩ ሲሉ አይቻለሁ፡፡ እንዲያውም እኔን ዝቅ
ያደረጉ መስሏቸው “ድንበሬን ማወቅ ከፈለከ ይኼን አባይ ሜትርህን ወዲያ ጣልና፣ አባትህን ሂድና ጠይቀው አጥሩን የሠራው እሱ ነው አሉኝ

ቤተሰቦቼ አብሪያቸው በመሆኔ በጣም ደስተኞች ስለነበሩ፣ እዚያው መቆየቴ ብዙም አላስከፋኝም፡፡ ከሮሐ ጋር መጀመሪያ አካባቢ ሰው አዬን አላዬን እያልን (እሷ እንኳን ግድ አልነበራትም ያው እኔው ነኝ አሳቻ ሰዓትና ቦታ፣ እየቆየን ግን ሰውም አውርቶ ሲወጣለት፣ በግልፅ መገናኘት ጀመርን፡፡ ያኔ ከሚተቸን ይልቅ “አይለያችሁ ባዩ ነበር የበዛው! መሐሪ ከነመፈጠሩም ተረስቶ ነበር፡፡ አንድ ሰው ብቻ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶኝ ነበር ጋሽ አዳሙ የሚባል የሰፈር ሰካራም፡፡ ስለ እኔና ስለ ሮሐ እንዴት እንደሰማ እንጃ፣ ጠምዶ ያዘኝ፡፡ ቀን ላይ ሳይሰክር አግኝቸው ስላም ስለው፣ ዘግቶኝ
አለፈ፡፡ በቃ አኮረፈ፡፡ ማታ ታዲያ በዚያ ሲያልፍ …ልክ በራችን ላይ ቁሞ፣

“ያምባሰል ማር ቆራጭ ይወጣል

በገመድ፣ አደራ ቢሰጡት ይበላል ወይ ዘመድ ብሎ ይጮሃል፡፡ ትንሽ ይሄድና፣ ጅብ እንኳን የጓደኛውን ሚሰት አይነካም፡፡ በርግጥ ጓደኛው ቆስሎ ካገኘው ይበለዋል” ይላል፡፡ ብስጭት እላለሁ ሁል ጊዜ ይችኑን ነው የሚደጋግመው ከእኔ ወጭ እናቴም ሆነች አባባ አይገባቸውም ተራ የሰካራም ልፍለፋ ነበር የሚመስላቸው ።በእርግጥ የእኔ
ቤተሰቦች ከሮሐ ጋር የነበረንን ነገር አያውቁም ነበር፡፡ ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዲሉ፣ አገር ምድሩ ሰምቶ ቤተሰቦቼ አልሰሙም፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ከሮሐ ጋር ለመጋባት ስንወሰን ነው የነገርኳቸው

ላገባ ነው !" አልኳቸው

እልልልልልልል፡ እሰይ እንዲያው ከዛሬ ነገ እነግርሃለሁ ስል እሰይ! " አለች እናቴ
በደስታ፡፡

የጥሩ ሰው ልጅ አገኘህ ?አለ አባባ፡፡

“ታውቋታላችሁ፣ የጋሽ ግርማ ልጅ”
ግርማ የቱ" አለች እናቴ ፊቷ ላይ ያለው ፈገግታ ልከ እንደ አምፑል ባንዴ ድርግም ብሎ ጠፍቶ፡፡

“ሮሐ"

"እኮ ሮሐ የመሐሪ"

"አንቺ ደግሞ የመቼውን ታሪክ ነው የምታወሪው …”

“የመቼስ ቢሆን እታደረግውም!” አለችና ዘላ ተነስታ ጆርዋን በሁለት እጇ ይዛ ወደ
ውስጥ ገባች፡፡እናቴ እንዲህ ስትሆን አይቻት አላውቅም! እንደ ኣንዳች ነገር ተቀያየረች፡፡ ተከትዬት ላሳምናት ብዙ ሞከርኩ፡፡ ወይ ፍንክች! እንዲያውም ሦስት ቀን ሙሉ ዘጋችኝ፡፡

አባባ ምኑም አልገባውም፣ አላስታወሳትም፡፡ ሮሐ በበኩሏ ለቤተሰቦቿ ስትነግራቸው አበዱ፡፡ ስንገናኝ ልክ እንደ አባቷ እየተንጎራደደች ያሉትን ሁሉ እየሳቀች ነገረችኝ “አንች
ለመሆኑ እዚያ ሰፈር የሚያልከሰክስሽ ምንድነው? ያስነኩሽ ነገር አለ? ሌላው ይቅር እንዴት ኅሊናሽ እሽ ይልሻል፣ ጓደኛውን? የዝናቡ ልጅ ከአባቱ ጋር ጠበኞች ነን፡፡
ቢሆንም ሞራል የሚባል ነገር አለ፡፡ እሱስ ምናይነት አንገት የሌለው ሰው፣ ነው ጓደኛው ታስሮ ምናይነት ዘመን ላይ ደረስን ባካችሁ? ሆሆሆሆሆሆሆሆ!”
በዚያ ብንል በዚህ የሁለታችንም ቤተሰቦች ባንገታችን ገመድ ቢገባ ይኼን ቅሌት አንፈቅድም አሉ፡፡ በተለይ እናቴ አታንሱብኝ አለች፡፡ ገና ነገሩን ሳነሳው ልክ እንደ ወባ ያንዘፈዝፉታል፡፡ ነውር የነውር ነውር መታሰቡስ አልውለደው እንጅ መሐሪ ልጄ ነው እስካሁን ልቤ አብሮት ታስሯል ልጀ ! ትላለች በቁጣ፡፡

አንድ ቀን ሮሐ እቤታችን መጣች፡፡ የቤተሰቦቼን ቤት በአንድ በኩል አስፈርሽ ሰፋ አስደርጌ ሰርቸላቸው ስለነበር፣ ልይላችሁ በሚል ሰበብ፣ ፍጥጥ ብላ መጣች፡፡ አሳዘነችኝ፡፡ እኔን ለማግባት እየተለማመጠች ነበር
👍4
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሀያ


#በአሌክስ_አብርሃም

“እጮኻለሁ ተይው አትጎትችው ይምጣ ይደብድበኝ የኔ የአዳሙ ጩኸት
እንዳይመስልሽ እንቅልፍ የነሳው! የራሱ ኅሊና ነው፣የራሱ ኅሊና አፍ ቢዘጋ ኅሊና ዝም እይልም የጅብ አገር ሕግ ባይምር፣ እንዴት ጓደኛ ጓደኛውን እይምርም? እንዴት ነው የሚኖረው እዚች ምድር ላይ? .…ድንበር መለካት ብቻ አደደለም መሐንዲስነት፣
ለራሳችን ስግብግብነትም ድንበር ማበጀት ነው:: ሁሉ ነገር ድንበር እለው፡፡ አቶ መሐንዲስ እኔም መሐንዲስ ነኝ፡፡ ሰው የሞራል ድንበሩን ሲያልፍ፣ እዚያ ነው
ድንበርህ እላለሁ፡፡ በሕግ አምላከ እላለሁ፡፡ በሕግ አምላክ ፍቅር በተዛነፈ መሠረት ላይ ሲቆም፣ ነገ ተንዶ ትውልድ ከመጫኑ በፊት በሕግ አምላክ እላለሁ ” እስኪበቃው ደንፍቶ በጨለማው ውስጥ ድምፁ እየቀነሰ …እየቀነሰ እየቀነስ ሄዶ ሰፈሩ ፀጥ ረጭ አለ፡፡ ዓይኖቼ በእንባ ተሞሉ፡፡
።።።
እናቴ በዚሀ ብላት በዚያ ብላት፣ የማግባቴን ነገር በጭራሽ አታንሳብኝ” አለች፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ጠቅልዩ አዲስ አበባ ገባሁ፡፡ አንድ የግል ሕንጻ ተቋራጭ ድርጅት ውስጥ ጥሩ ሥራ እግኝቼ ነበር፡፡ ሮሐ ከሦስት ወር በኋላ ተከተለችኝ፡፡ ጊዜ አላጠፋንም፤
ጓደኞቻችንን እማኝ አድርገን በፊርማ ተጋባን፡፡ ማታ ጓደኞቻችን ጋር ሰብሰብ ብለን ራት ተገባበዝን፡፡ ታዲያ እቤታችን ስንገባ ሮሐ ሞቅ ብሏት ነበር ልክ እንደ መፈክር እጁን ከፍ አድርጋ፡ የአብርሽ እናትና የኔ ቤተሰቦች ገደል ይግቡ!"ብላ ጮኸች፡፡ እናም አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስቅስቅ ብላ ማልቀስ ጀመረች፡፡ ትዳርን እንዲህ ጀመርን፡፡

ሕይወት ያላትን ሁሉ ሳትሰስት የሰጠችን ወጣት እና ደስተኛ ባለትዳሮች ሁነን ነበር!
በተጋባን በዓመታችን ልጅ ወለድን …. እንደናቱ በጣም ቆንጆ ልጅ … ልጃችንን ዝም ብዬ ሳየው፣ የእኔ ልጅ ሳይሆን የሮሐ ወንድም ይመስለኛል፡፡ በብዙ ጓደኞች ተከበብን በብዙ መልካም ሰዎች …የሕይወት ነፋስ ሁልጊዜም በዙሪያችን የሚነፍሰው ፍቅር እና ደስታ ተሸክሞ ነበር፡፡ ልክ እንደጥሩ ተረት “በደስታና በፍቅር ይኖሩ ጀመር የሚል ፍጻሜ የሚመስል ሕይወት፡፡

ሮሐ ጥሩ አፍቃሪ ብቻ ሳትሆን፣ ተወዳዳሪ የሌላት ሚስት፣ ወደር የሌላት እናትም
ነበረች፡፡ ለዚህም ይመስለኛል፣ ሁልጊዜ ፍቅረኞች የሆንን መስሎ የሚሰማኝ፡፡ ሁልጊዜ ፍቅረኛዬ ነው የምትመስይኝ ስላት፣ “ባንተ ቤት ሮማንቲክ' ሆነህ ሞተሃል ባክህ በሰርግ ስላልተጋባን ነው ትለኛለች፤ ሁልጊዜም ገና አዲስ የተዋወኳት ሴት መስላ እንድትታየኝ በሚያደርገኝ የአሽሙር ፈገግታዋ ታጅባ፡፡ እያዳፉ እዚያና እዚህ ሲያላጋን የነበረው የህይወት ማዕበል ሰፊ እና ውብ ባሕር ላይ በእርጋታ ያንሳፍፈን ጀመረ፡፡
ዓመታት ነጎዱ፡፡ አልፎ አልፎ፣ በጣም አልፎ አልፎ ከባሕር ውስጥ ዘለው ወጥተው መልሰው እንደሚገቡ ትናንሽ ዓሳዎች፣ የመሐሪ ነገር ለቅፅበት ትዝ ይለኝ ነበር፡፡ ከሮሐ ጋር ግን ፈጽሞ አንስተነው አናውቅም፡፡ አንዳንዴ በውስጧ ታስታውሰው ይሆን የሚል
ሐሳብ ውል ይልብኛል፤ እናም በስሱ፣ በጣም በስሉ፣ ልክ እንደነፋሻ አየር የቅናት ስሜት ዳስሶኝ ያልፋል፡፡

ልጅ ከወለድን በኋላ የሮሐ ቤተሰቦች ኩርፊያቸውን ትተው እየመጡ ይጠይቁን ነበር እኛም በየዓመቱ ልጃችንን ይዘን ፋሲካን ከቤተሰብ ጋር ማሳለፍ ጀመርን፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ እናቴ ልጄን ስትመለከት አለቀሰች ፡፡ እንግዲህ እናትነቷ ከዛ በላይ ለማኩረፍ አቅም አሳጥቷት ይሁን አልያም ዓይኔን አፍጥጬ ስሄድባት ውጣ የማትለኝ ነገር ሆኖባት፣ ኩርፌያችን በዛው እድሜው አጠረ፡፡ ሮሐ ታዲያ “ለማይረሳ ኩርፊያ ሰርጌን በሉት
ትላለች ፡፡
።።።
ተስፍሽ “ፔሌ' አብሮ አደግ የሰፈራችን ልጅ ነው፡፡ ጎበዝ እግር ኳስ ተጫዋች ስለነበር ነው ፔሌ ያልነው፡፡ ኳስ ከማሳደድ ይልቅ፣ ወንጀለኛ ማሳደድ ዕጣው ሆነና ከዩኒቨርስቲ ስመለስ፣ ፖሊስ ሆኖ አገኘሁት፡፡

ስቴዲየም ስንጠብቅህ በዩት በኩል ዙረህ ፖሊስ ጣቢያ ተገኘህ ?”አልኩት፣

ያው ነውኮ ሜዳው ይለያይ እንጂ እዚህም ያለው ሁለት ቡድን ነው፡፡ ፖሊስ አለ ወንጀለኛ አለ ሃሃሃሃሃ ብሎ ሳቀ፡፡ ማረሚያ ቤት ነው የሚሠራው፡፡ ከሮሐ ጋር በተጋባን በስድስተኛ ዓመታችን፣ ለፋሲካ በዓል ቤተሰብ ለመጠየቅ ሄድን፡፡ መምጣቴን እንደሰማ ተስፍሽ ሰላም ሊለኝ ወደ ቤት መጣ፡፡

በቀጣዩ ቀን ሻይ ቡና ካላልን ብሎኝ፣ ተያይዘን ወጣን፡፡ ተቀምጠን የልጅነታችንን ትዝታ ስናነሳና ስንጥል ቆይተን ስለመሐሪ ተነሳ፡፡ ውስጤ እየፈራ “መሐሪን ታገኘው ነበር?” አልኩት፡፡

“አዎ ያው ተረኛ ስሆን፣ አንዳንዴ ለሰላምታ ያህል እንተያያለን"

እንዴት ነው …” አልኩ፡፡ ለምን ራስህ ሂደህ አትጠይቀውም እንዳይለኝ እየፈራሁ፡፡

ታውቀው የለ ብዙ አያወራም፡፡ የሆነ ሆኖ ደህና ነው …መውጫው እየደረሰ መሰለኝ
አስራ ሁለት ይሁን አስራ ሦስት ዓመት ታሰረኮ ለማይረባ ነገር ….በስማም ጊዜው እንዴት ይከንፋል” አለና ተከዘ፡፡ ድንገት ምስጢር እንደሚያወራ ሰው ግራ ቀኙን አየት አድርጎ፣ ከአንገቱ ወደእኔ ሰገግ አለና …

አብርሽም አለኝ

"እ''

ለማንም ተናግሬ የማላውቀውን አንድ ነገር ልንገርህ ስለገረመኝ ነው። እስር ቤት
ለሦስት ዓመት አካባቢ ሰርቻለሁ በዚህ ሁሉ ዓመት መሐሪን የሚጠይቁት ሁለት ሰዎች ብቻ ነበሩ፡፡ አንድ እንኳን ሌላ ሰው መጥቶ አያውቅም፤ አንዷ ያው እትየ ሮሚ ነች (የመሐሪን እናት ማሚን ማለቱ ነው) አንዷ ማን እንደሆነች ገምት እስቲ

እኔጃ…ፍቅረኛ ምናምን ያዘ እንዴ …? አልኩ እንደማይሆን ባውቅም እንዲያው
ለመገመት ያህል፣

"ሳሌም !!” አለኝ !

“ምን?…ሳሌም !?” የምጠጣው ቡና ሸሚዜ ላይ እስኪረጭ ደነገጥኩ፡፡

ሳሌም የደፈራት ልጅ!”

“ባክህ አትቀልድ”

እናቴ ትሙት!”

እንዴ ምን ነካህ ተስፍሽ? የማይሆን ነገር

“ቢያንስ ለሁለት ዓመት አካባቢ እኔ ራሱ አላወኳትም ነበር! አንተ ራሱ ብታያት
አታውቃትም! ፈጽሞ አታውቃትም፡፡ ሁልጊዜ በየሳምንቱ ሐሙስ ከሰዓት አስር ተኩል ላይ ነው የምትመጣው፡፡ ያ ሰዓት ብዙም ጠያቂ አይበዛበትም ቆይ አንተ ታዲያ እንዴት አወካት ደግሞስ ፈረንጆቹ ውጭ አገር ወሰዷት አልተባለም
እንዴ?”
እኔም የሰማሁት እንደዛ ነበር አላውቅም! ብቻ ባጋጣሚ ነው ያወኩት፡፡ በነገራችን
ላይ የካቶሊክ መነኩሴ ሆናለች፣ እነዚህ ጥቁር ቀሚስ የሚለብሱት ..እዚህ ፈረንጆቹ ግቢ የሚኖሩት የሉም? ልክ እንደነሱ ነው የምትለብሰው፡፡ እዛው እኛ ሰፈር ፈረንጆቹ ግቢ ነውኮ የምትኖረው

እውነትህን ነው…?”

እናቴ ትሙት እያልኩህ”

"እና …”

አላመንከኝም ይገባኛል፣ ግን እሷ ነች ራሷ ማረሚያ ቤት በመጣች ቁጥር መጽሐፍና
የርቀት ትምህርት ሞጁል ነው ይዛ የምትመጣው ምግብ ምናምን ስታመጣ አይቻት አላውቅም! አንድ ቀን እንዲሁ ይች መነኩሴ ይኼን ሁሉ መጽሐፍ ለማነው የምታመጣው ብዬ በኋላኛው በር በኩል ወጣሁ በዚያ በኩል መጠየቂያው ቦታ ይታያል፡፡ እና ወደ እስረኞች መጠየቂያ ስመለከት ከመሐሪ ጋር ተቀምጠው ሲያወሩ አየኋት፡፡ ሥራዬ ብዬ ከዚያ በኋላ ነው መከታተል የጀመርኩት! ወሬ መውደድ ምናምን
ሳይሆን፣ አለ አይደል አብሮህ ያደገ የሰፈር ልጅ ከሆነች መነኩሴ ጋር ስታይ ዝም ብሎ የሚያጓጓ ነገር አለው፡፡ እና ስከታተላቸው በየሳምንቱ ሐሙስ ትጠይቀዋለች?” አለና ቡናውን ፉት አለ፡፡ዝም ብዬ አየሁት፡፡

እንግዲህ አለማመን ትችላለህ፡፡ ግን ልንገርህ፣ የሆነ ቀን ልክ እኔ ተረኛ ሁኜ ስትመጣ፣ መታወቂያዋን ተቀብየ አየሁት፡፡ ሳሌም ይላል፡፡ ሲስተር ሳሌም፡፡ እንግዲህ ግራህን ሲመቱህ ቀኝህን ስጥ የሚለው ትዛዝ ይኼው
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

እስከ ሐሙስ ከቆየህ፣ ለምን ራስህ አታያትም እውነቴን ነው ማረሚያ ቤት መሄጃ ጋ ካሉት ካፌዎች አንዱ በረንዳ ላይ ተቀምጠህ ስትገባ ማየት ትችላለህ”

እኔ ምን ትሰራልኛለች፤ ነገሩ ገርሞኝ ነው እንጂ”

"እሱማ እኔም በውስጤ ለብቻዬ ስገረም ነበር"

የዚያን ቀን እንዲቹ እንደፈጠጥኩ እንቅልፍ ሳይወስደኝ ሌሊቱን አጋመስኩት፡፡ ለሮሐ አልነገርኳትም፡፡ ልጃችንን ይዛ ቤተሰቦቿ ቤት ነበረች፡፡ እንኳን ለሷ ልነግራት ለራሴም በማመንና ባለማመን መሀል እየወላወልኩ ነበር፡፡ሳሌም እንዴት የደፈራትን መሐሪን ያውም በየሳምንቱ ለዓመታት እየሄደች ትጠይቀዋለች…? ያውም ያንን በደል ይቅር ብላ? እኔ የዓመታት ጓደኝነቴን በዚያች አጋጣሚ አሽቀንጥሬ ጥዬ ይኼው ዓይኑን ካየሁት አስራ
ሦስት ዓመቴ፡፡ ምን እሱን ብቻ እንደ እናት ያሳደገችኝን ማሚን እንኳን እንዴት ነሽ
ብያት አላውቅም፡፡ ወደ ወቀሳ በሚቀርብ ግርምት ስገረም አደርኩ፡፡ መጨረሻ ላይ
የራሷ ጉዳይ ነው … እኔ መነኩሴ አይደለሁም” ብዬ ራሴን አጽናናሁ፡፡
የሳሌምን ዕድሜ በውስጤ አሰላሁት ሃያ አምስት፣ ሲበዛ ሃያ ስድስት ቢሆናት ነው፡፡

ጧት ከእንቅልፌ ስነቃ፣ ድንገት ሳሌምን የማግኘት ሐሳብ ከውስጤ ገንፍሎ ወጣ፡፡በቀጣዩ ቀን ለሮሐ ጉዳዩን ሳልነግራት፣ እንዲሁ እስከ ቅዳሜ እንድንቆይ ነገርኳት፡፡ሐሙስ ነበር ወደ አዲስ አበባ ልንመለስ ያሰብነው፡፡

ችግር የለውም፣ ቤቢቾ ተመችቶታል፡፡ ዘና ብለህ የምትሠራውን ጨርስ” አለችኝ፡፡
ለምን? እንዴት? እንኳን አላለችኝም፡፡ እንዲህ ናት በቃ፡፡ የነፍሴ ምቾት ሮሐ፡፡ ጨረቃን አውርጄ ልከሰክሳት ነው ብላት፣ ቆይ መሰላል ልያዝልህ ከማለት አትመለስም፡፡

ሐሙስ ቀደም ብዬ ወጥቼ፣ ልክ ተስፍሽ ፔሌ እንደነገረኝ፣ በማረሚያ ቤቱ ዋና በር
በኩል ካሉት ካፍቴሪያዎች አንዱ በረንዳ ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ልቤ እንደጉድ ይመታ ነበር፡፡ምን አስፈራኝ…? ምንም ወንጀል አልሠራሁም እያልኩ ለራሴ! ከተቀመጥኩበት ቦታ ሦስት መቶ ሜትር ርቀት ላይ፣ ለአስራሦስት ዓመት ዓይኑን ያላየሁት መሐሪ የሚባል ልጅ አለ፡፡ እንደማግኔት ሞገድ ወደ ውስጥ ሳበኝ ይሰማኛል፡፡ ማን ያውቃል፣ በዚች
ቅጽበት ትከሻውን እየከበደው ይሆናል፡፡ ድንገት ሃሃሃሃ የሚል ሳቅ ሰምቼ ስዞር

ተስፍሽ "ፔሌ" አጠገቤ እንደጅብራ ተገትሯል፡፡ መላ ሰውነቴን እፍረት አጥለቅልቆ፣እፍረት የቀላቀለ ሳቅ አብሬው ሳቅሁ፡፡

እንደምትመጣ እርግጠኛ ነበርኩ” እለ።

"እንዴት አውቅህ ባክህ?”

ፖሊስ እይደለሁ?… ፊትህ ላይ አነበብኩት ወንበር ስቦ መንገዱ እንዲታየው አመቻችቶ እጠገቤ ተቀመጠና ሰዓቱን አየት አድርጎ በሹክሹከታ “አሁን ትመጣለች” ብሎኝ ፈገግ አለ፡፡

እንዲሁ ገርሞኝ ነው …አለ አይደል” አፍሬ ነበር፡፡

“ይገባኛል አብርሽ፣ ትንሽ ግራ የሚያጋባ ነገር ነው፤ እኔም እንዳንተው ነው የተሰማኝ፡፡እንዲያውም እንኳን መጣህ አብሮኝ የሚገረም ሰው አገኘሁ” ብሎ ትከሻዬን በወዳጅነት ቸብ አደረገኝ፡፡

ቡና አዘን እየጠጣን፣ እስረኛ ለመጠየቅ የሚገቡትን፣ ሰዎች ታሪክ ያወጋኝ ጀመር፡፡ “ይች ሴትዮ ባሏ የደርግ ባለሥልጣን ነበር ዕድሜ ልክ ፍርደኛ ነው… ያች በሷ ምክንያት በጩቤ ሰው የገደለ ቦይ ፍሬንዷን ነው የምትጠይቀው፣ ይኼ ባለባርኔጣው ሰውዬ " እያለ የጠያቂ ታሪክ ሲያሸመድደኝ ቆየንና፣ ድንገት በሹክሹክታ “መጣችልህ” አለኝ፡፡
ቢያንስ ከእኛ መቶ ሜትር እርቀት ላይ ረዥም ጥቁር ቀሚስ የለበሰች፣ ራስ ላይ
የሚጠለቅ ነጭ የጸጉር መሸፈኛ ሻሽ ያደረገች ረዘም ባለ ሰንሰለት አንገቷ ላይ የጣውላ መስቀል ያንጠለጠለች ወጣት መነኩሲት በፈጣን ርምጃ በእጄ ከበድ ያለ የጨርቅ ከረጢት አንጠልጥላ ስትመጣ አየሁ፡፡ እየቀረበች ስትመጣ ለአንዴ ነበር የለየኋት፡፡ ፊቷ ትንሽ ውፍረት ጨምሯል፡፡ ቀጥ ብሎ ወርዶ ጫፉ ወደላይ የሚቀሰር አፍንጫዋና ቀይ ፊቷ ግን ጩኾ ሳሌም ነኝ ይላል፡፡ ታጥፋ ወደ ማረሚያ ቤቱ የሚያስገባውን መንገድ ተከትላ ስትሄድ ከኋላዋ ፈዝዠ እያየኋት ነበር፡፡ ውስጤ ርብሽብሽ አለ፡፡ የዚያች ቀን ምሽት፣ እኔ እዚህ የተቀመጥኩት ሰውዬ ጓደኛዬ መሐሪን መጠጥ እንዳይጠጣ
ብከለክለው፣ ያችን ውስኪ ከሮሐ እጅ ሊቀበል ሲያቅማማ “ተው” ብለው፣ ይች ልጅ እንደዚህ ትሆን ነበር ወይ? ሰው መነኩሴም ይሁን ዓለማዊ፣ ምርጫው ከሆነ ችግር አይደለም፡፡ ሌሎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ገፍተው ለዚህ ሲያበቁት ግን ያሳዝናል፡፡ እዚህ ጥቁር ቀሚስ ሥር ያለ ቁስለኛ ልብ ላይ የእኔም ስም የተመዘገበበት የጥላቻ መዝገብ ይኖር እንደሆንስ ማን ያውቃል?፡፡ እነሱ አሳስተውኝ ነው፣ ይቅር በይኝ ብሏት ቢሆንስ?፡፡ እኛን ጭዳ አድርጎ በእኛ ስም እጁን ታጥቦ ቢሆን፡
እህ …ዋሸሁ ” አለኝ ተስፍሽ፡፡

"እሷ ነች አይደለችም?"

“ይገርማል! ራሷ ነች …”

ነገርኩህ …ምንስ ፎር ፖይንት አምጥተን ዩኒቨርስቲ ባንገባ፣ ይች ይችማ አታቅተንም እኔ የምልህ ተስፍሽ፣ ማናገር ብፈልግ ክልክል ይሆን እንዴ? ማለቴ በእምነታቸው ከወንድ ጋር አያወሩም..?

ኦ! ልታወራት ፈለክ …?

“ያው ታውቃለህ እህቴ ማለት ነበረች፡፡ እጃችን ላይ ነው ያደገችው:: ዩ ኖው ቁም
ነገር ባይሆንም እንዲሁ ባናግራት ደስ ይለኛል፡፡ ሰላም ብላት ምናምን፣ እኔጃ፣ ምን ይመስልሃል ችግር አለው?”

እኔጃ!

ስልኳን ማግኘት ግን እችላልሁ መዝገብ ላይ ስለሚመዘገብ ከፈለክ አመጣልሃለሁ

እባክህ ተቸገርልኝ "

ግን ሕጋዊ አይደለም ብሎ ሳቀ፡፡ ማታ እቤት መጣና ቁራጭ ወረቀት እያቀበለኝ
በሹክሹክታ “ሲስተር ሳሌም ማለት አትርሳ” ብሎኝ እየሳቀ ሄደ፡፡

በቀጣዩ ቀን ጧት ወደአራት ሰዓት አካባቢ ደወልኩ፡፡ ስልኩ ይጠራል አይነሳም፡፡
ሁለተ ሞከርኩ፡፡ አይነሳም፡፡ ወደምሳ ሰዓት አካባቢ መልሶ ተደወለልኝ፡፡ በረዥሙ ተንፍሽ አነሳሁና። ሔሎ አልኩ…
“ጤና ይስጥልኝ፣ በዚህ ስልክ ከሁለት ሰዓት በፊት ተደውሎልኝ፣ ሥራ ላይ ስለነበርኩ አላነሳሁም ይቅርታ፣ ማን ልበል?” አለችኝ ረጋ ባላ ጨዋ ድምፅ፡፡ ልቤ ተመንጥቃ ልትወጣ ደርሳ ነበር፡፡

“ አዎ! አዎ! ኢሲስተር ሳሌምን ፈልጌ ነበር” አልኩ እኔም ረጋ ብዬ፡፡

“ ሲስተር ሳሌም ነኝ… ማን ልበል እርስዎን” አንቱ ልበላት እንቺ ልበላት፣ ግራ ገባኝ…

“እኔ እኔ አብርሃም እባላለሁ፡፡ በጣም ቆየ እንጂ እንተዋወቃለን፡፡ እኔጃ እንዴት
መግለፅ እንዳለብኝ …ብቻ የመሐሪ ጓደኛ ነበርኩ፡፡ እንችም ልጅ ሁነሽ ታውቂኝ ነበር፡፡ እንጃ ታስታውሽኝ እንደሆን …” ኤፌ ተሳሰረብኝ፡፡

“አብርሃም ?እንዴት ነህ? እንዴ በሚገባ አስታውስሃለሁ እንጂ! የት ሄደ እያልኩ
ስጠይቅ ነበር? እንዴት ስልኬን አገኘኸው ኡፍፍፍ ቀለል አለኝ፡፡

“ታሪኩ ረዥም ነው …የምኖረው አዲስ አበባ ነው፡፡ አሁን ለሰዓል ከባለቤቴና ከልጄ ጋር መጥቸ ነው፡፡” አልኩ፡፡ ማግባትና መውለዴን የቀባጠርኩት እንድትረጋጋ ብዬ ነበር፡፡

“ እግዚእብሔር ይመሰገን …”ብላ ዝም አለች፡፡

“እንዲያው እንዴት መጠየቅ እንዳለብኝ አላውቅም፣ ግን ከቅዳሜ በፊት በአካል ባገኝሽና አይቸሽ ብመለስ ደስ ይለኝ ነበር፣ ይቻል ይሆን?”

በሚገባ ይቻላል… የምትመጣበትን ቀን ከነገርከኝ ጥበቃዎቹ ጋ የመግቢያ ካርድ
እተውልሃለሁ”

ኦ …ዛሬ ሰዓት ካለሽ፣ ከሰዓት መምጣት እችላለሁ?

አዎ ትችላለህ… እባከህ ና! ከስምንት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዐስር ሰዓት ባለው መምጣት ትችላለህ፣ ስትደርስ ስምህንና ከእኔ ጋር ቀጠሮ እንዳለህ ንገራቸው ውስጤ በደስታ፣በስጋት እና በማላውቀው ስሜት ተናወጠ፡፡ እንዲህ ይቀላል ብዬ አላሰብኩም
👍31
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#በአሌክስ_አብርሃም

ኧረ ለመሆኑ ምንድነው የምላት? “ምን ልታዘዝ? ብትለኝ ምን እላለሁ? በቃ እንዲሁ ላይሽ ነው የመጣሁት እላለኋ፡፡ በፍጥነት ሮሐ ጋ ደርሼ አብረን ምሳ በልተን ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ ያረፈችው ቤተሰቦቿ ጋር ነበር፡፡

የቀጠሮዬ ሰዓት ሲደርስ ለባብሼ ወጣሁ፡፡ እዚያው ሰፈራችን ያለው የፈረንጆች ግቢ” በዋናው በር ዙሬ በትንሽ የመስተዋት መስኮት በኩል ለተቀመጠው የጥበቃ ሠራተኛ ስሜንና ቀጠሮ እንዳለኝ ነገርኩት፡፡ የተወሰኑ ካርዶች ካገላበጠ በኋላ፣ ፈገግ ብሎ በሩን ከፈተልኝ፡፡ ግቢው እጅግ ሰፊና ውብ ነው፡፡ አትክልቶቹ ያስደምማሉ፡፡ ፀጥታው ሌላ
ሩቅ አገር እንጂ ተወልጄ ያደኩበት ሰፈር አልመስልህ አለኝ፡፡ ሰፈሬ ውስጥ የታጠረ
ገነት፡፡ ጥበቃው አንድ ልጅ እግር ሰራተኛ ጠርቶ “ወደ ሲስተር ሳሌም ቢሮ ውሰዳቸው አለው፡፡ ልጁ እየመራ ወደ አንድ የሚያምር የድሮ ሕንጻ ወሰደኝና፣ የሳሌምን በር ጠቆመኝ፡፡ በሩ ላይ በአማርኛና በእንግሊዝኛ “ሲስተር ሳሌም የሚል ወርቃማ ጽሑፍ ተለጥፎበታል፡፡ አንኳኩቼ ስገባ ሳሌምና አንዲት በዕድሜ የገፉ ፈረንጅ መነኩሴ በፈገግታ ተቀበሉኝ፡፡ እርስ በእርሳቸው በማላውቀው ቋንቋ አውሩና፣ ሴትዮዋ ሰላምታ ሰጥተውን እየሳቁ ወጡ፡፡

አብርሃም!” አለች እየሳቀች፡፡ እጂን መጨበጥ እችላለሁ ወይስ እምነታቸው ይከለክል ይሆን? ተንደርድሬ ማቀፍና እንደ ልጅነቷ ወደ ላይ ማንሳት እችላለሁ ወይስ ነው ነው? እያልኩ ግራ ስጋባ እጇን ለሰላምታ ዘረጋችልኝ፡፡

“ሳሌም ይቅርታ ሲስተር ሳ…

ችግር የለውም ሳሌም በለኝ፡፡ እንዴት ነህ? ሎንግ ታይም' ኡ” አለችኝ ትክ ብላ
አየችኝ፡፡ ምን እንደምናገር ግራ ገብቶኝ እኔም አየኋት፡፡ ከዕድሜዋ በላይ ትልቅ ሰው መስላለች፡፡ የደፋችው የራስ መሸፈኛም እንደሆነ እንደዚያ እንድትመስል ያደረጋት እንጃ፡፡ እንድቀመጥ ጋበዘችኝ፡፡

ምቹው የእንግዳ መቀበያ ወንበር ላይ አረፍ አልኩ፡፡ ቢሮው ትንሽ ቀዝቀዝ ያለ ነው:: ፊት ለፊቴ ተቀምጣ አንገቷን ሰበር እደረገችና

“ዩኒቨርስቲ መግባትህን ሰምቻለሁ ..ምን ተማርክ?” አለችኝ አወራሯ ረጋ ያለና እጅግ ትሕትና የተሞላበት ነበር፡፡

“ኢንጅነሪግ“

እግዚአብሔር ይመስገን አሁን እየሠራህ ያለኸው በዛው ዙሪያ ነው”

አዎ… አንድ የግል ድርጅት ውስጥ እየሠራሁ ነው፡፡ ይቅርታ እርሰዎ ነው የሚባለው አንች … ድፍረት እንዳይሆንብኝ አላወኩም” ፈገግ አለችና ችግር የለም፣ ዝም ብለህ አውራኝ…ለስላሳ፣ ውሃ አለ፤ ምን ትፈልጋለህ?”

“ውሃ ይሁንልኝ!” ጥግ ላይ ከቆመ ማቀዝቀዣ ለራሷም ለእኔም የታሸገ ውሃ አመጣች

ውሃዩን ተጎነጨሁና “ሁልጊዜ አስብሻለሁ
ወደ ውጭ አገር ሄዳለች የሚባል ነገር ሰምቼ ነበር.....

“እውነት ነው! አምስት ዓመት አካባቢ ጀርመን ነበርኩ” ምን እንደተማረች መጠየቅ ፈለግሁ፣ ግን ፈራሁ፡፡ እንደው ይኼ አስራ ሦስት ዓመት እንዴት አለፈ? እስቲ ንገሪኝ ማለት ፈለግሁ …ብቻ ብዙና የማያቋርጥ ነገር ልጠይቃት ፈልጌ ሁሉንም ነገር ተውኩትና፣ ለቅጽበት ዝም ተባብለን ቆየን፡፡ እንደምንም ራሴን እደፋፍሬ በቀጥታ እንዲህ እልኳት…
“ሳሌም! ምንም ነገር ተመልሼ ላስታውስሽ አልፈልግም ግን ሁልጊዜ እራሴን እንደወቀስኩና እንደተጸጸትኩ ነው፡፡ መቼም ስለኔና መሐሪ ታውቂያለሽ፣ ወንድሜ ማለት ነበር፤ የተፈጠረው ነገር ከተፈጠረ በኋላ፣ ለአሥራ ሦስት ዓመት ዓይኑን አላየሁትም፡፡ አፈርኩ፣ ዓይኑን ለማየት ተሳቀቅሁ! በየቀኑ ሳላስበው ውዬ አላውቅም፡፡ ግን በቃ፣ እንዴት ልበልሽ፣ የዛሬ አሥራ ሦስት ዓመት እንደታሰረ አካባቢ፣ እኔና ሮሐ ልናየው ሂደን የተፈጠረው ነገር ትንሽ የሚያሳፍር ነገር ነበር፣ መሐሪ እኔንም ሮሐንም ለሆነው ነገር ወቀሰን፡፡ የዚያን ቀን ምሽት ሮሐ መጠጥ ይዛ ነበር የመጣችው፣ እኔም
አትጠጣ አላልኩትም

“አውቃለሁ አብርሃም፣ አትጨነቅ፣ ሁሉም ነገር ይገባኛል”

“ታንኪው! ትንሽም ቢሆን ለተፈጠረው ነገር የእኔ ስህተት እለበት ብዬ ነው የማስበው፡፡የዚያን ምሽት እንዳይጠጣ ብከለከለው ኑሮ ወይም አብሬው ባድር ኖሮ ብቻ ብዙ ነገር ያሳቅቀኛል፡፡ ከዚያ በኋላም ብዙ ነገር እጠፋሁ፡፡ ቤተሰቦቹን ሄጄ ኤልጠየኳቸውም ጋሼ ሲያርፍ እንኳን ለቅሶ አልደረስኩም፡፡ በዚያ ላይ ስለ ሮሐ ልነግራት አስቤ አፌ ላይ አድርሼ ተውኩት፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ ንስሐ አባቱ ፊት እንደቀረበ ሰው መናዘዝ
ጀመርኩ፡፡ ዝም ብላ ስታዳምጠኝ ቆይታ፣

ራስህን አትውቀስ፣ ማንም ሰው የሚያደርገው ነገር ነው፡፡ ሕይወት መቼም ያለፈውን ለመቀየር ዕድል አትስጠንም፣ ወደፊት በተስፋ መጓዝ ብቻ ነው፡፡ መሐሪን በየሳምቱ ማረሚያ ቤት እየሄድኩ እጠይቀዋለሁ

ኧረ? እንዳላወቀ ሰው ለመሆን ሞከርኩ፤ ድራማው ተሳክቶልኝም እንደሆን እንጃ!

ዓዎ! በአንዳንድ ምክንያት ሰዎች እንደምጠይቀው እንዲያውቁ አልፈለኩም፡፡ ያው ይገባሃል መቼም፡፡ሁልጊዜ ስለ አንተ ያነሳልኛል፤መሐሪ ኤልተቀየመህም፤ እንደውም የእውነት ናፍቆሃል፣ ቢያይህ ደስ ይለዋል”

እውነት!?”

አንቺ በእምነትሽም ምክንያት ይሁን በተፈጥሮ፣ ነገሮችን የምትቋቋሚ ሆነሽ ይቅር አልሺው፣ ጋሽ ዝናቡ በተከበረበት አገር ተዋርዶ፣ እዝኖ፣ ራሱን ያጠፋው በማን ምክንያት ነው?..በመሐሪ ምክንያት ነው! ..አባቴ ማለት ነበር፣ አብሮ አሳድጎናል ድምጼ እየጨመረና እንባ እየተናነቀኝ ነበር፡፡

ሳሌም ዝም ብላ ስትመለከተኝ ቆዬች “መሐሪን ይቅር አላልኩትም፣ እንጃ ለዚያም የሚበቃ ልብ ያለኝ አይመስለኝም፡፡ መሐሪን የምጠይቀው፣ ከጎኑ የሆንኩት፣ ሌላው ይቅርና በራሴ ምርጫ እዚህ ለመሥራት መርጨ የተመለስኩትና በየቀኑ ከማስታውሰው
ሕመም ጋር እየታገልኩ የምኖረው ደግ ስለሆንኩ ይመስልሃል? ከአንተም ከሮሐም የተለየ መንፈሳዊ ከፍታ ላይ ስላለሁ ይመስልሃልን አይደለም! እውነታው መሐሪ ምንም ወንጀል የሌለበት ንጹህ ልጅ ስለሆነ …ካለ ሥራው ዕድሜ ልኩን በእስር ስለሟቀቀ ነው

“ተይ እንጂ! ምንም ወንጀል የለበትም?” አጉል ሃይማኖተኝነት መሰለኝ ተበሳጨሁ!

“አብርሃም! የዚያን ቀን ምሽት መሐሪ አልደፈረኝም” ፍጥጥ ብዬ እየኋት፡፡

የደፈረኝ ጋሽ ዝናቡ ነው

“ምን? …ምንድነው የምታወሪው ሳሌም”
“እውነቱን ማወቅ ከፈለክ ይኼው ነው! … መሐሪ የደረሰው በደም ተጨማልቄ ሰውዬው አፌን አፍኖ እንዳልናገር ሲዝትብኝ ነበር፡፡ አቅፎኝ በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ አብሮኝ ሲያለቅስ፣ እስከዛሬ ዓይኔ ላይ አለ፡፡ ወዴት ሊወስደኝ እንደነበር እንጃ ብቻ ይዞኝ ከዚያ
ክፍል ሲወጣ፣ ኮሪደሩ ላይ ከእናቴ ጋር ተገጣጠሙ፤ እናቴን ሳይ ጮህኩ ኡኡ አልኩ፡፡ ያን ለታ ማታ የለበስኩት ነጭ ቀሚስ ከፊትም ከኋላም በደም ተጨመላልቆ ነበር የሆነው ሆነ”

“እና…"

“እንድም ሰው መሐሪ ደፈረኝ አላልኩም፡፡ መሐሪ ራሱ ነበር ላገኘው ሰው ሁሉ
እንደደፈረኝ ሲያወራ የነበረው:: ለአንተና ሮሐ፡ ፍርድ ቤትም ጭምር አመነ፡፡ ማንም

ሰው አባቱን አልጠረጠረም፡፡ መሐሪ የዚያን ክፉ ሰውዬ ክብር ለመጠበቅ ሲል ከምንም በላይ እናቱ ተሳቅቃ እንዳትሞት፣ እንዳትሰማ፣ ራሱን መስዋዕት አደረገ፡፡ እኔም ተንፍሼ አላውቅም፡፡ ከእኔና ከመሐሪ ቀጥሎ አንተ መስማትህ ነው፡፡ ሰውዬው ሥራው አሳዶት ራሱን አጠፋ መሐሪም ውድ የወጣትነት ዘመኑን በእስር ቤት አሳለፈ፡፡ ከፍ ካልኩ በኋላ
የዚያን ወንጀለኛ ሰውዬ ድርጊት ለመደበቁ ለረዥም ጊዜ አዝኜበት ነበር፡፡ ግን ደግሞ
ማሚ፣ የእኔም እናት ናት፡፡ ውርደቷ ውርደቴ ነው፡፡ መሐሪ ዕድሜውን፣ እኔም የታፈነ በደሌን ለማሚ አዋጥተን ጐዳቷን ለመቀነስ ሞከርን፡፡
👍1