አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....“አትነሳ መጣሁ ቡና ይዤልህ::” ተነስታ ወጣች ርብቃ፡፡

ናትናኤል ሃሳቡ እየተሰባስበለት ሲመጣ የሆነው ሁሉ ድጋሚ እየመጣ ፊቱ ላይ ይመላለስ ጀመር፡፡ 'ወይኔ! ወደኔ አብርሃም! ግን ለምን? ለምን? ለምን ገደሉት? ምን አደረጋቸውና ገደሉት? እርሱ ነበር የእባቡን ጭራ የረገጠ፡፡ አብርሃም ለምን ተነደፈ? እሱ እንዴት ዳነ? እሱን እንዴት ተወት? ለምን ተውት?' በሃኪም ቤቱ ደረቅ አልጋ ላይ በጀርባው ተንጋሉ ያየው ጓደኛው በዓይነ
ህሊናው አፈጠጠበት፡፡ ትክ ብለው ሽቅብ
የተመለከቱት የአብርሃም ዓይኖች መጥተው ድቅን አሉበት፡፡ 'ናትናኤል
አላልኩሀም? በእሳት እየተጫወትን ነው አላልኩህም? የምመክርህ ነገር
ቢኖር ይህን ነገር ማነፍነፍሀን ትተህ በሠላም ስራህን እንድትሰራ ነው።
እንደ እሳት እራት መጥፊያሀን ስታሳድድ ዝም ማለት አልችልም! ናቲ
ራሴን ለአደጋ ማጋለጥ አልፈልግም… አባት መሆኛዬ ደርሷል.. ልጄ አባት
ይፈልጋል... ናቲ ለጥቅምት ሚዜዬ እንድትሆን ብጠይቅህስ . ካልቨርትን
አግኝ… ካልቨርትን ካልቨርትን…ካልቨርትን

አይኖቹን እየሞላ ከሳይ ከላዩ እየዋለላ የሚዥጎደጎደው እንባው አላቆምልህ አለው፡፡ ሌላ አስጠሊታ ድምፅ ጆሮው ላይ አንቃጨለበት አንተ ነህ የገደልከው! አንተ ነህ ጎዳዩ!አንተ ነህ!አንተ!..
የአብርሃም እጮኛ ሁኔታ ታወሰው፡፡ እንደ እብድ በግራና ከቀኝ ክንድና ክንዷን ይዘዋት ያ ውብ ፊቷ ተንጨባሮ እንደ ህልም ታየው።

ጎንበስ ብላ ስትንሰቀሰቅ ፊቱ ላይ መጣችበት፡፡ ዓይኖቹን ጨመቃቸው፡፡
'... አንተ ነህ! አንተ! አንተ ናትናኤል ከቆመበት አልተንቀሳቀሰም፡፡ በሆስፒታሉ መተላለፊያ ፍዝዝ ብሎ እንደቆመ ቆየ፡፡ ከሆስፒታሉ የወጣው ዘግይቶ ነበር፡፡ ድንገት እራሱን በረጅሙ መተላለፊያ ብቻውን ቆሞ አገኘው። ከኋላው በር ሲከፈት ተሰማው:: ፊቱን መለሰ ሁለት ነርሶች ከፊትና ከኋላ ሆነው በተሽከርካሪ
አልጋ ላይ የተንጋለለውን የጓደኛውን በድን እየጎተቱ ወጡ፡፡ ከጫፍ እስከ ጫፍ ነጭ ስስ ጨርቅ አልብሰውታል፡፡ በመተላለፊያው እየገፉ ይዘውት
ሄዱ፡፡ በቆመበት ለመጨረሻ ጊዜ አብርሃምን ተሰናበተው፡፡ ናቲ ለጥቅምት
ሚዜዬ እንድትሆን ብጠይቅህስ?

አጥወለወለው፡፡ ቶሎ ብሎ ነጩን የሆስፒታል ግድግዳ ደገፍ አለና ቆመ፡፡ በቀስታ እየተራመደ ከሆስፒታሉ ህንፃ ወጣ፡፡ ከአጥሩ በር ሲደርስ የሆስፒታሉ በእኛ ላአንድ አፍታ ፊቱን ከተመለከተ በኋላ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ በሩን ከፈተለት፡፡ ከአጥር ግቢው ወጣ፡፡ መንገዱን ሊሻገር ሲል ድጋሚ የሚያየው ሁሉ ብዥ አለበት:: ቶሉ ብሎ መንገድ ጥግ ይዛ የቆመች ነጭ ሲትሮይን ላይ ደገፍ ኣለ፡፡ መኪናውን የት ነበር ያቆማት? እሩቅ ትሆን? እ.አይደለችም፡፡ 'ካልቨርትን አግኝ.… ካልቨርትን

ከዚያ በኋላ የሆነው ጭጋግ ሆኖ ነው የሚታየው፡፡ ብቻ ርብቃ ደግፋ መኪናው ውስጥ ስታስገባው እንደ ህልም ትዝ ይለዋል፡፡
“ቀና ብለህ ብትቀመጥ አደጃልህም? ”

ትራሱን ከጀርባው አስገባችለት፡፡ አልጋው ላይ ተቀምጣ እፍ እፍ እያለች ማንኪያውን ወደ ኣፉ እስጠጋችለት፡፡ በደመነፍስ አፉን ከፈተ ሾርባ፡፡ አፉ ውስጥ ቀፈፈው፡፡ ወይኔ አብርሃም! “በቃኝ:: አላት ማንኪያ የያዘውን እጇን በእጁ እየገፋ፡፡

ናቲ ምን መሆን ነው?…ራስህን ተቆጣጠረው እንጂ? ”
“በቃኝ አልኩሽ በቃኝ፡፡”
“እሺ በኋላ ራትህን ትበላለህ ፤ ይሄን ጠጣ አሁን፡፡”
ቀመሰው:: ወተት:: አፉ ላይ ተንቀዋለለበት፡፡ , “ ቢሆንም ሊያስቸግራት አልፈለገም፡፡ መልሶ ፉት አለው::

“በቃ ናትዬ:: ጨክን ማለት ነው ያለብህ፡፡ ናትናኤል አንተ ተጽናንተሀ ቤተሰቦቹን ማዕናናት ነው ያለብህ፡፡” አለች ርብቃ ትራሱን ከጀርባ እያስተካከለችለት፡፡
ቤተሰቦቹ
…አንተ ነህ ገዳዩ !… አንተ ነህ! አንተ!... አንተ!… "
ወተት የያዘውን ብርጭቆ አቀበላትና በሁለት እጆቹ ጆሮዎቹን ጥርቅም አድርጎ ያዛቸው::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የበሩ ደወል ሲጮህ ከተኛበት በርግጎ ተነሳ፡፡ ከአልጋው ላይ የተበታተኑትን እርቃናቸውን ያሉ የሴቶች ፎቶግራፎች የያዘ መጽሄቶችን ሰብሰብ አድርጎ ቁምሳጥኑን ከፈተና ወደ ውስጥ ወረወራቸው፡፡ የጠዋት ልብሱንና ጫማውን አጠለቀና ነጥብ 22 ብሬታ ሽጉጡን ከራስጌ አንስቶ ከመኝታ ቤቱ ወጣ፡፡ የበሩ ደወል ድጋሚ ሲያንባርቅ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ከሀያ፡፡

ሽጉጡን በጠዋት ልብሱ የግራ ኪስ ውስጥ እንደከተተ የበሩን ሰንሰለት ሳይነቅል በሩን በቀጭኑ ከፍቶ ተመለከተ፡፡

“አሃሮን!” በሩን ዘጋና ሰንሰለቱን ነቅሎ - ቁልፉን ከፍቶ በሩን በረገደው:: “ምን ሆነሃል?” አለ አመድ የመሰለውን የአሃሮንን ፊት ሲመለከት መንገድ ለቅቆ እያስገባው፡፡

“አሁንም ተቀደምን፡፡” አለ አሃሮን በብስጭት ፋረልን አልፎ ሄዶ በአንደኛው የሳሎን ሶፋ ላይ ዘፍ እያለ።

“ምንድነው ነገሩ?” ፋረል በሩን ቆልፎ ባለበት ፊቱን መልሶ አሃሮን ላይ አፈጠጠ፡፡
ገደሉት”
'“ማንን?”
“አብርሃምን"
ፋረል በዝምታ ከአሃሮን ፊት ለፊት ተቀመጠና በግራ ኪሱ የያዛትን
ብሬታ አውጥቶ መሃል ጠረጴዛ ላይ ወርወር አደረጋት፡፡
“ጥፋቱ የኛ ነው፣፣ ሰውየው ስለ ካልቨርት የሚያውቀው ነገር እንዳለ ጠርጥሬአለሁ እንዳልኩህ ብንመለምለው ኖሮ…”

“እንዳትመለምለው የገፋፋሁህ በበቂ ምክንያት ነው:: አለ አሃሮን እራሱን በመከላከል ዓይነት፡፡ «ለዛውም ሰውየውን እንዲህ በቀላል ልትመለምለው የምትችል አይመስለኝም፡፡»

“እሱ ችግር አይፈጥርም ነበር፡፡ : ወኪል አመላመል ስማር አስተማሪዎቼ በንቁ አይኖች እንድከታተል የነገሩኝን እያንዳንዱን ነጥብ የሚያሟላ ሰው ነበር፡፡ አንደኛ ከፍተኛ የባንክ ዕዳ አለበት” እለ ፋረል ጣቶቹን ሁሉ ጨብጦ የአውራ ጣቱን ቀስሮ “ሁለተኛ አለ ኣመልካች ጣቱን አወጣና “ለአለቆቹ ከፍተኛ ጥላቻ እንዳለው እዚያው ካለ ወኪሌ
ተረድቻለሁ፡፡ ብቻ ያ ሁሉ ዋጋ የለውም አሁን” አለ ድንገት እጁን አወናጭፎ፡፡”

“አሁን ዋናው ጥያቄ ለምን ገደሉት የሚለው ይመስለኛል፡፡" አሃሮን
በረጅሙ ተነፈሰ፡፡

“ለዚህ ምንም ጥርጥር የለኝም:: ሰውየው : አንድ የደረሰበት ምስጢር አለ፡፡ ወይ ሁላችን የምንፈልገውን ካልቨርት ይዞት የተሰወረውን ምሥጢር ያውቃል፡፡ አለበለዚያም የካልቨርትን አድራሻ ደርሶበታል።”

“ጥሩ” አለ አሃሮን ፋረልን ወደሚፈልገው መስመር እየመራ፡፡ “ግን እስካሁን ለምን ሳያስወግዱት ቆዩ ትላንት ማታ ምን አዲስ ነጥብ ተገኘ?”

“ያንን ለመናገር ይከብዳል” አላ ፋረል፡፡ በብስጭት ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ መጠጥ መደርደሪያው እየሄደ፡፡ በጠዋት ለመጠጣትና ላለመጠጣት ጭንቅላቱ እርስ በርሱ ሲጋጭበት ለአንድ አፍታ ቆም አለና ፊቱን ወደ አሃሮን መለሰ፡ «አሃሮን አዝናለሁ.…ግን አሁን ያሰኘኝ ቁጭ ብል ማልቀስ ነው:: አንዴ ብትወጣልኝ ያንን ነበር የማደርገው፡፡ ሰዎቹ ጤነኛ አይመስለኝም:: እያንዳንዱን ፍንጭ ያለርህራሄ የሚገድሉ ከሆነ…“

“ብስጭቱን ለጊዜው እናቆየውና ወደ ፍሬነገሩ እንመለስ፡፡ ትላንት ምን አዲስ ነገር ስላገኙ ይመስልሃል ኣብርሃምን የገደሉት?“ አለ አሃሮን ረጋ ባለ መንፈስ፡፡

“ሮበርት… እኔ ግን ቀን ከትገናኘው ሰው ጋር በተያያዘ ምክንያት ይመስለኛል ለሞት የበቃው፡፡ ምናልባት አብርሃም ለውጭ ጉዳይ ሰው የሰጠው መረጃ ይኖራል፡፡ አለበለዚያም እሱ ራሱ ከሰውየው ያገኘው ወደ ወጥመድ የከተተው ምስጢር አለ፡፡ ያም ሆነ ይህ የሁለቱ መገናኘት ለጊዜው ልንገልፀው ያልቻልነው ሚዛን አናግቷል፡፡”

“እሺ ልክ ነህ እንበል፡፡”
👍5
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....የሎስ አንጀለስ ፖሊስ ዲፓርትመንት መርማሪ ፖሊሶች በሊዛ እና ትሬይ ግድያ ላይ የተገኘውን የዲ.ኤን.ኤ ውጤት ከሰሙ በኋላ ሁሉም አትኩሮታቸው የእነዚህ ግድያ ምርመራዎች ላይ ሆኗል። ምክንያቱም ገዳዬ ወሬ ዞምቢ ነው'
የሚለው ወሬ በመሰራጨቱ የምርመራውን መጨረሻ ለማወቅ ጓጉተዋል።

“ይሄውላችሁ ያለምንም መረጃ ዶክተሯ ላይ ኃጢአቱን መደፍደፋችሁ ትክክል ያልሆነበትን ምክንያት አንድ በአንድ ላስቀምጥላችሁ።

ሀ፦ ኒኪ ሮበርትስ ሁለቱንም ግድያዎችን ለመፈፀም የሚያስችላት አንድም ተጨባጭ ምክንያት የላትም፡፡

ለ፦ የእሷ ቁመት አምስት ጫማ ከሶስት ኢንቺ ሲሆን ክብደቷም ከመቶ ፓውንድ ያነሰ ነው። ትሬይ ሬሞንድ ደግሞ 6 ጫማ ከሁለት ኢንች ሲሆን ክብደቱም 186 ፓውንድ ነው። ሰውነቱም በፈረጠሙ ጡንቻዎች የተገነባ ነው። እና ይህቺ ሴት ናት እሱን በጉልበት ጥላው በጩቤ ወጋግታ የምትገድለው ብላችሁ ነው የምትሞግቱኝ?”

“ምናልባት በወቅቱ የሚያግዛት ሰው አብሯት ነበር::” ብሎ ጆንሰን በመቀጠልም “ምናልባትም ግድያውን ሊያግዛት የሚችል አንድ ሰው
ቀጥራም ሊሆን ይችላል።”

“ያ! ምናልባትም አንጀሊና ጆሊ በድንገት መጥታ እራት ልትጋብዝህም ይሆናል እኮ” ብላ ሀና ባይኔስ ተረበችው እና ቢራዋን እየጨለጠች “ሰው ቀጥራ የሚለው ሀሳብህ በፅንሰ ሀሳብ ደረጃ ሊያስኬድ ቢችልም በተግባር ግን
የሚሆን አይደለም።” ብላ ስትናገር ፖሊሶቹ በሙሉ ከት ብለው ሳቁበት።
“ሉው ትክክል ነው፡፡ ጆንሰን ይህቺን ሴት ማስረጃ ሳይኖርህ ወንጀለኛ ናት ብለህ ማሰብህ ትክክል አይደለም፡፡” ብላም አና ተናገረችው። ጆንስንም ፍንጥር ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ እና አና ላይ ጣቱን ቀስሮ

“አሁን ላይ ማስረጃ የለኝም፡፡ በቅርቡ ግን ይኖረኛል፡፡ እሷ ነጭ ውሸት ነው እየዋሸች ያለችው፡፡ ስለዚህ ሁላችሁም ገደል መግባት ትችላላችሁ።
ብሎ ከባሩ እየተመናጨቀ ወጣ፡፡

“በእየሱስ ሥም ይሄ ሰውዬ ምን ሆኗል?” ብላ ጉድማንን ጠየቀችው።

“ከእናንተ ጋር የቆየ ወዳጅነት አላችሁ አይደል። እናንተ ለምን ስለእሱ የምታውቁት ነገር ካላችሁ አትነግሩኝም? ሚክ ዶ/ር ሮበርትስን ይሄን ያህል
ለምን አምርሮ እንደሚጠላት ግልፅ ሊሆንልኝ አልቻለም።” አለው ጉድማን፡፡
“ምናልባት እንደዚህ ቢሆንስ?” አላቸው ፓድሬ ሳንቼዝ፡፡

ሳንቼዝ እንደባልደረባው ባይኔስ ለፍላፊ ሳይሆን ብዙ የማያወራ ሰው ነው። ብዙውን ጊዜ አስተያየት መስጠት አይወድም፡፡ አንድ አስተያየት
ሲሰጥም የሚሰጠው አስተያየት ጠብ አይልም፡፡

“ይህቺ ዶክተር ሮበርትስ በየጊዜው የባለሙያ ምስክርነትን እድትሰጥ
ፍርድ ቤቶች ውስጥ ትጠራ ነበር” አላቸው፡፡

“የሳይካትሪክ ምዘናን ትሰጥ ነበር ማለት ነው?” ብሎ ጉድማን ጠየቀ፡፡
“አዎን በተለይ ከአደንዛዥ እፅ ጋር በተያያዘ ሙያዊ ምስክርነትን ትሰጥ
ነበር። እሷ እና ባለቤቷ በአደንዛዥ ዕፅ ለተጎዱ ሰዎች የስነ ልቦና ህክምናን
የሚሰጡ ነበሩ።” አላቸው፡፡

“ሚክ የቀድሞ የአደንዛዥ ዕፅ መርማሪ ነበር ማለት ነው' ብሎ ጉድማን አሰበ “እና በጆንሰን ላይ የተቃዋሚ የባለ ሙያ ምስክር ሆና ቀርባለች ማለት ነው?” ብሎ ሳንቼዝ ጠየቃቸው።

“እኔ ይህን አላውቅም። ለምን ራሱን ጆንሰንን አትጠይቁም? ብቻ ሴትየዋ ለፖሊስ ሀይል ጥሩ አመለካከት እንደሌላት እርግጠኛ ሆኜ ልናገር
እችላለሁ፡፡ እሱ ደግሞ ያው ምን ያህል ቂም ቋጥሮ እንደሚቆይ ታውቃለህ?” ብሎ መለሰለት፡፡

የሳንቼዝን መልስ ከሰማ በኋላ ጉድማን ሃያ ዶላር ባንኮኒው ላይ አስቀምጦ እየሮጠ ወደ ውጭ ወጣ። ሳንቼዝ ከነገረው ነገር ተነስቶም አንድ
ሀሳብ ስለመጣለት ነበር ወደ ውጭ መውጣቱ።

“ሚክ!” ብሎ ጮሆ ተጣራ፡፡
ጆንሰንም ጥሪውን ሰምቶ ዞር አለ። በስልክ የጠራውን የሁበር መኪና
እየጠበቀ ነበር ጉድማን ያገኘው፡፡
ጉድማን ጆንሰን አጠገብ እንደደረስ በቀጥታ ወደ አሰበው ጉዳይ በመግባት “ዶክተር ሮበርትስ በግድያው ውስጥ አለችበት እንበል” አለው

“አለችበት ብቻ? እርግጠኛ ነኝ እንዲያውም።” አለው ጆንሰን በስካር
ምላሱ እየተሳሰረበት፡፡

“ግን አንተ ባልከው መንገድ ሳይሆን እሷ ራሷ ላይ ግድያው ሊፈፀምባት
ታስቦ ቢሆንስ?” አለው ጉድማን፡፡
ጆንሰንም አይኑን እያጉረጠረጠ “ይህንን ነገር ተነጋግረንበት የጨረስን
መሰለኝ በድጋሚ እንድናወራበት አልፈልግም” አለው፡፡

“ሊዛ ፍላንገን የዶክተር ሮበርትስን ረዥም የዝናብ ጃኬት ለብሳ ነበር ያን ምሽት የዶክተሯ ክሊኒክ ቢሮ ከሚገኝበት ህንፃ የወጣችው።”

“እሷ እንደነገረችን ከሆነ ነዋ” ብሎ ጆንሰን እየተንተባተበ መለሰለት እና
በማስከተልም “ይሄውልህ ስለ ጃኬቱ ስትነግረን እኔም ልክ እንደ አንተ
በወቅቱ ተደስቼ ነበር፡፡ ግን ጃኬቱን ልናገኘው አልቻልንም። ስለዚህ ስለ
ጃኬቱ ያለን መረጃ የዚያች ዶክተር ቃል ብቻ ነው።” አለው፡፡

“ግን እሷ እንደዚያ ባለ ነገር ላይ ለምን ትዋሰናለች? እስቲ አስብ” ብሎ
ጉድማን ሞገተው። ጆንሰን ጉድማን የጠየቀው ጥያቄ ትክክል ቢሆንም በውስጡ አጉረመረመ። ጉድማንም ባልደረባው ጆንሰንን ለማሳመን “ጭለማ ነበርበዚያ ላይ ያን ምሽት እየዘነበ ነበር። ከዶክተር ሮበርትስ ቢሮ ስትወጣም
የዶክተሯን የዝናብ ጃኬት ለብሳ ነበር፡፡ የሁለቱም ቁመት እኩል ነው። የፀጉር ስታይላቸውም አንድ አይነት ነው። ስለዚህ ገዳዩ ከኋላ በኩል የቀረባት ከሆነ...”
“እሺ እሺ ገባኝ” አለው ጆንሰን፡፡

“ይሄ ሊሆን አይችልም ትላለህ?” ብሎ ጉድማን ጆንሰንን ይበልጥ ለማሳመን ድምፁን ጠንከር አድርጎ ጠየቀው::
“ልክ ብልሃል ሊሆን ይችላል። ግን ትሬይ ሬይሞንድስ? ከላይ ሊዛ ላይ ያነሳኸው አመክንዮ እሱ ላይ አይሰራም አይደል? የእሱ ቁመት 6 ጫማ ከሁለት ኢንች ነው፡፡ መልኩ ደግሞ ልክ አንተ እንዳደረግከው ባርኔጣ ጥቁር ነው::” አለው፡፡

“ምናልባት ትሬይ የተገደለው ለኒኪ የቅርብ ሰው ስለሆነ ይሆናል” አለ
እና ጉድማን በመቀጠልም “ዶክተር ኒኪ በአደንዛዥ ዕፅ ዙሪያ ላይ በሚካሄዱ
ችሎቶች ላይ የባለሙያ ምስክርነት ትሰጥ አልነበር? ምናልባት
የመሰከረችባቸው ሰዎች እሷን እና ባለቤቷን በጠላትነት እንዲያይዋት
ሊያደርጋቸው ያስችላቸዋል፡፡”
ይህንን የሰማው ጆንሰንም አይኑን አጥብቦ ጉድማንን እየተመለከተው
“እ የባለሙያ ምስክርነትን በየፍርድ ቤቱ ችሎቶች ላይ ትሰጥ እንደነበር ማን ነው የነገረህ?” ብሎ ጉድማንን ጠየቀው፡፡

“እንዴ እንደዚህ አይነት ነገሮችንማ ካላወቅኩኝ ምኑን መርማሪ ሆንኩት?” ብሎ መረጃውን ከሳንቼዝ እንዳገኘ ሳይነግረው ቀረ እና በመቀጠልም
“ምናልባትም በእሷ የምስክርነት ቃል የተፈረደበት የአደንዛዥ ዕፅ አቅራቢ የዶክተር ኒኪን ጃኬት ለብሳ የነበረችውን ሊዛን ዶክተሯ ናት ብሎ ስላስበ በስህተት ገደላት፡፡ ምናልባትም ደግሞ ትሬይ ገዳዩ ማን እንደሆነ ደርሶበት ሊሆን ስለሚችልም ይሆናል እሱም ቢሆን የተገደለው”

ጆንሰንም የማሽሟጠጥ ሳቁን ለቀቀው እና “እና ትሬይ መርማሪ ነው በለኛ?”

“ተው አትድረቅ ሚክ ሀሳቤ ትክክል አይመስልህም?”

ጆንሰንም ዶክተር ኒኪን እንደ አጥቂ እንጂ እንደ ተጠቂ ማየት እንዲጀምር የሚያስገድደውን ሀሳብ ስለቀረበለት ባይወጣለትም ለመረታት ቻለ።

“በዚህ ጉዳይ ላይ ሁላችንም ምንም ነገር አለመደባበቅ እንችላለን?” ብሎ
ጠየቀው፡፡

“እሺ” ግን ግልፅነታችን በሁለታችንም በኩል መሆን አለበት” አለው ጆንሰን፡፡

“ማለት?”

“ማለትም ዶክተር ሮበትስ ከግድያው በስተጀርባ እንዳልሆነች የሚያሳይ
ምንም አይነት ማስረጃ
#የወድያነሽ


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል

....«እኔ በበኩሌ ብዙ ጊዜ ነግሬሃለሁ። እናትህም ብትሆን ዘወትር እንደ ለመነችህ ነው:: የተማረ ሰው ጥቅምና ጉዳቱን ለይቶ ማወት ያቅተዋል ብዬ አላስብም፡፡ ርግጥ ነው፡ ዐዋቂም ቢሆን መካሪና ነጋሪ ያስፈልገዋል። ግን ሁልጊዜ የሚመከርና የሚነገር ጤነኛ ሰው አይደለም፡፡ በከንቱ ከምታማስነን ይልቅ ዐይንህን የጣልክባትና የወደድካት የጨዋ ልጅ ካለች ንገረኝ። አለበለዚያም እኔ
የምመርጥልህንና ደኅና ሰው ቤት ገብቼ የማመጣልህን ተቀበል፡፡ እኔማ ካነገርኩህ
ይኸው ሁለት ዓመት ዐለፈ፡፡ ምነው የወንድሞችህንና የእኀቶችህን ልብ ቢሰጥ ብሎ መልሴን ለመስማት ትክ ብሎ አየኝ፡፡

«አየህ አባዬ በማለት በተለመደች አጠሪሬ ንግግሬን ጀመርኩ።
“ማንኛውም ሰው የሚያገባው ራሱን ለማስደሰትና ኑሮውን ለመመሥረት እንጂ
ሌላውን ደስ ለማሰኘት አይደለም፡፡ አንተ የምትመርጥልኝን አልቀበልም ለማለት
ሳይሆን ላንተ የምትስማማህና ደስ የምትልህ ለእኔ ደስ አትለኝም ይሆናል።
"ማንኛውም ሰው እለማወት ወይ ድንቁርና ከተገቢዉ በላይ ብዙ እንዲያደንቅና በጠባብ አስተሳሰብ እንዲሠራ በስውርና በግልጽ ሊያስገድዱት ይችላሉ፡፡ እኔ በመጠኑም ቢሆን ከጠባብ አስተሳሰብ ተላቅቄአለሁ። በአጭሩ እንድታውቅልኝና እንድትገነዘብልኝ የምፈልገው ግን ለመግባባት የሚችል ሕሊና እንጂ ከቀን ወደ ቀን የሚለወጥ ሰብአዊ ውበት ብቻውን ጋብቻን ጽኑና ተፈላጊ መሠረት ሊሰጠው አይችልም» ብዬ ረዘም ባለው አነጋገሬ የምን ይለኝ ጅራፍ እየለመጠጠኝ
በመናገር አይኖቼን ወደ ወለሉ ተክዩ ዝም እልኩ፡፡

«ኤድያ! ኤድያ! ደርሶ መንዘባነን ደስ አይለኝ! የዘንድሮ ወጣቶች ሐሳብና መልስ በየቤቱ ይኸው ሆኗል፡፡ ቁም ነገር የሚሠራ ሰው ብዘ አያወራም፡፡ ጋብቻ የጎበዝና የደፋር ሙያ እንጂ ለሰነፍና ለፈሪ የሚታደግ የጠበል ፃዲቅ
ድርሻ አይደለም፡፡ አስተዋይ ልቦና ያለው እንዳቅሙ ይዘላል፡፡ ያለ መቸኮልህስ
ይሁን በጄ! የአቦ ዕለት ሲሉህ የመድኃኔ ዓለም ዕለት ማለት ግን በዛ፡፡ ዛሬን
እንደ ዛሬ ኑረህ ነገን እንደ ነገ መኖርና ነገን መስለህ መገኘት ቁርጥ ዓላማህና
ፍላጎትህ መሆን አለበት፡፡ ዝምታህ እምቢታ መሆኑን ዐውቃለሁ» ብሎ ከጉዳዩ ጋር የተያያዘውንና ያልተያያዘውን ሁሉ ተናግሮ ቆጣ አለ፡፡ ከጊዜያዊ ቁጣው
በኋላ ዝምታ እንዳይጀምር በማሰብ “ምናልባት በሰው ልጅ እኩልነት የምታምን ከሆነ ለምን የትልቅ ሰው ልጅ፡ አጥንተ ጥሩ፣ ባለክብር፣ ባለ ዝና እያልክ
ታማርጣለህ? » ብዬ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅንጣት ድፍረት የተቀላቀለባትን ጥያቄ
ሆዴ በፍርሃት እየተናጠ አቀረብኩኝ።

«አድሮ ጥጃ አለ ያገሬ ሰው ብዙ ጊዜ ነግሬሃለሁ፡ ለምን ነጋ ጠባ
ትጠይቀኛለህ? በማለት ንግግሩን ሲጀምር በቁጣ ትክ ብሎ
የማይሆነውንና የማይገባውን ሁሉ አትመኝ"ሐለሙ ሕልመ ወአልቦ ዘረከቡ"
ተብሏል፡፡ ማንም ሰው ቢሆን የኑሮ ደረጃውን መጠበቅና መመልከት አለበት።
እኔ እባትህ ከትልልቅና ካዋቂ ሰዎች ጋር የምውል ነኝ። አንተም እንደ እኔ
መሆን ይገባሃል።

ዝናና ክብር ቀላል ነገር አይምሰልህ፡፡ ከሜዳ ላይ አይታፈስም። የዘመኑ
ሰዎች ለጤና ያድርግላችሁ እንጂ “አለ "አብልሑ ልሳኖሙ ከመ አርዌ ምድር»
እንዳለው ሆናችኋል። የምታመጣት ልጅ ከጨዋ ቤተሰብ የተወለደች፣ ዘርና
ትውልዷ የታወቀና የጠራ መሆን አለበት። ወይራ ከወይራ ነው፡ ስንዴ ከጓያ
አይቀየጥም፡፡ «ከመልኮስኮስ መመንኮስ» ሲባል አልሰማህም እንዴ? «የማንንም ስድ አደግና ቅሬ ከየትም ለቅመህ ዝናና ክብሬን ብታጠፋት አደባባይ አውጥተሀ የገደልከኝ ያህል እቆጥረዋለሁ፡፡ የደሃ ቀርቀቦ ቢንከባለል ከደሃ ደጅ” ምኞትህ ሁሉ ልክስክስ አይሁን» ብሎ ቁጭቱን ለመግለጽ ያህል ራሱን ነቀነቀ።

ያቺ በስንትና ስንት ጊዜ ውስጥ የምታጋጥመኝ ጭቅጭቅ አይሏት
ውይይት አብዛኛውን ጊዜ ፍፃሜዋ አያምርም። የእኔና የእርሱ ሐሳብ በተቃራኒ አቅጣጫ ስለሚጓዝ ከመከራከርና ከመጨነቅ ይልቅ ሰምቼ መለየትን እመርጣለሁ።

«ማንንና እንዴት ለማግባት እንደምፈልግ ለመግለጽ እስከምችል ድረስ
የመዘጋጃ ጊዜ ቢሰጠኝና ከራሴ ጋር ብመክር ጥሩ ነው:: እኔ ግን ከአንዳንድ
ሁኔታዎች በስተቀር ማንኛውም ሰው በተፈጥሮ ዐይን ሲታይና ሲመዘን እኩል
ነው” በሚለው አምናለሁ» ብዬ እምነቴን ገለጽኩ፡፡ ለመነሣት ሲመቻች ጋብቻን
እንደ አንድ ትልቅ ጦርነት የምትፈራው መስለህ ታይተኸኛል። ጋብቻ ማለት
ሌላ ነገር አይምሰልህ፡ ከአንዲት ከምትወዳት ሴት ጋር ለመኖር የምታደርገው የኑሮ ውል ነው፡፡ ከሆነችህ አብረሃት መኖር፡ እንዲያ ሆነም ምን ውጣ ወረድ አለው፡ ደህና ዋይ ብሉ ማሰናበት ነው:: ከዛሬ ጀምሮ ግን አግባ አታግባ እያልኩ አልነታረክም፡፡ አስቦና የሚሻውን ወስኖ ለማደር ከቻለ አቅመ አዳም ከደረሰ ሰው ጋር ስለ ራሱ ጉዳይ መከራከር ከንቱ ድካም ነው::

«አንተማ በልብህ ግን እንደኔ ማለትህ አይቀርም፣ ንገሩኝ ባይ!»

“ከትንሽ ጅረት ውስጥ የምትንሳፈፍ ቅጠል ከትልቁ ኩሬ ውስጥ ስትገባ
ቁጫጭ አህላ ትታያለች፡፡ ዐወቅሁ ብለህ ሙተሃል፡፡ የሰው ልጅ ክፉ ጠላቱ ደግሞ
በውስጡ የታጎረው ሽካራ ሐሳቡ ነው:: ካንጀቴ ነው:: ራስን ለማረምና ለማሻሻልም እኮ ከሌሎች ሰዎች ስሕተት መማርና መረዳት ካስተዋይነታቸውም መልካም መልካሙን መቅሰም ማለፊያ ዘዴ ነው» ብሎ ፈንጠር ብላ በጸጥታ ነጠላ ወደምትቋጨው እናቴ አሻግሮ አየ። ምንም እንኳ ላቀረበው ሐሳብ ተነጻጻሪና የተሻለ መልስ ቢኖረኝም
እያደር የሚንር ቁጣውን በመፍራት ደጓን ዝምታ ቀጠልኩ።

የተጨማደደውን ግንባሩን እየጠራረገ ከተነሣ በኋላ ሐሳቤን በጠቅላላ
የሚቃወም መሆኑን ለማስረዳት ወለሉን በቀኝ እግሩ ጠፍ ጠፍ እደረገው፡፡
«የሚታየው እኮ እንዴትና የት ማደግህ ብቻ አይደለም፡ ከማን መወለድህም ጭምር እንጂ። መልካም አዝመራ የሚገኘው እንደ ገበሬውና እንደ
መሬቱ ብቻ ሳይሆን እንደ ዘሩም ነው» ብሎ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤቱ ሔደ::

ወደ ውስጥ ሰምጣ የነበረችው ለስላሳ መቀመጫ ትንሽ በትንሽ በመሙላት ቅርጿ ተስተካከለ።

«እስኪ አሁን በኪዳነ ምሕረትና በእሑድ ምድር ባትጨቃጨቁ ምን ቸገረሀ ልጄ? ነጋ ጠባ ይነግርሃል፤ እርሱ አይደክመው፣ አንተ አይሰለችህ! መጥኔ እቴ! ወዴት አባቴ ልግባላችሁ ይሆን? በዚያ ላይ ደግሞ ስንተዜ ልንገርህ? ሲሆን
ሲሆን አንተና እኔ ምንና ምን? አንተ በትምርትህም ቢሆን አታጣውም፡ አሁን
በዚህ በአንተ ምልልስ የተነሣ ያ ሰበበኛ የደም ብዛቱ ቢነሣ አበሳው ለኛው ነው፡፡
እሞት አገር አድርሶ እንደሚመልሰው ታውቃለህ፡፡ ከሐኪሙ ቤት የሚያመጣውን አንድ ቁና ኪነን ታያለህ፡፡ እሱ በጦም በጸሉት እያለ ባይዘው ኖሮ ይኸነዩ ጥሪኝ አፈር ሆኖ ነበር። እሱ እንደሁ እሱ ነው: አንተ ግን ሲያመር ሲያመር ከፊቱ ገለል በልለት» በማለት ራቅ ብላ የተቀመጠችው እናቴ ምሬቷን ገለጸች፡፡

አሁንም እንደገና ከእናቴ ጋር የነገር ገበና ለመጫወት ባለመፈለጌ ሰምቼ
ዝም አልኩ። ዐልፎ በልፎ ከሚሰማው ከእናቴ የጉሮሮ ማስሊያ እህህታ በስተቀር
ቤቱ በዝምታ ታመቀ። በሐሳብ ዐውሎ ነፋስ ከወዲያ ወዲህ በመንገዋለል ላይ
እንዳለሁ ጉልላት ከቸች አለ።

እጆቹን ወደ ኋሳ አጥፍቶ እርስ እርሳቸው ካያያዘ በኋላ አንድ እግሩን ትንሽ ቀደም በማድረግ ጎንበስ ብሎ ለእናቴ ሰላምታ አቀረበ፡፡ እናቴ ስለ ጉልላት ስትናገር «እኔ ከሌላው ከሌላዉ ሁሉ የሚያስደስተኝ ትትናውን እጅ አነሳሡ ነው» ትላለች። ከጎኔ ተቀመጠ። ከእናቴ ጋር ልብ ለልብ ተገናኝቼ እንደማላወራ ስለሚያውቅ የጋሪ ወሬ ለመክፈት አልፈለገም፡፡
👍1
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

....ሽመልስ በማግስቱ ለአብዱላሂ ስልክ ደወለለት አብዱላሂ ስልኩን አነሳና ጌትነት ያለመኖሩን በድጋሚ አረጋገጠለት። ሽመልስ ተጨነቀ።
“ምን አጋጥሞት ይሆን?" በሚል ሃሳብ ተዋጠ፡፡ ፈተናው የሚሰጠው ከአንድ ቀን በኋላ ነው። ባስመዘገበው ስልክ ተደውሎለት ባይገኝ ደግሞ

ለነአቶ አባይነህ ደስታቸው ነው፡፡ በጣም ተበሳጨ፡፡ ከምሳ ስዓት በኋላ ግን ጌትነት ስለ ሥራው ብቻ ሳይሆን ስለህልውናው ጭምር ጓዙን ጠቅልሎ የሱን ጊዜያዊ ርዳታ ሊጠይቅ ከተፍ አለ።

"እንግዳ ይፈልግሀል ይግባ?"አለች የሽመልስ ፀሐፊ ከውስጥ ስልክ፡፡
"አስገቢው" አላት። እንግዳው ወደ ውስጥ ሲዘልቅ ሽመልስ ዐይኑን ማመን አቃተው፡፡
“ኮንግራጁሌሽን!” አለና ጮኸ፡፡
ጌትነት ያልጠበቀው ዱብ ዕዳ ሆነበት። የሽመልስን ሁኔታ ሲያይ ከደስታው የተነሳ የሆነ ስሜት ስውነቱን ውርር አደረገው፡፡ ሽመልስ አይዞህ ከጎንህ ነኝ እንዳለው አድርጎት ይሆን? እንደመርበትበት እያደረገው የተዘረጋለትን እጅ በደመነፍስ ጨበጠ፡፡
"አረፍ በል እስቲ!"አለና ወንበር ጋበዘው። ጌትነት ከእንግዳ መቀመጫ ወንበሩ ላይ ሄዶ ተቀመጠና በሁለመናው አሰፍስፎ ሽመልስን በጉጉት ይጠባበቀው ጀመር፡፡ ሌሊቱን በሙሉ እንቅልፍ ሳይወስደው ስላደረ ፊቱ ላይ የመጎሳቆል ምልክት ይታይበታል፡፡

"ለመሆኑ የት ጠፍተህ ከረምክ? በተደጋጋሚ ስልክ ደውዬ ሳጣህ ተስፋ
ወደ መቁረጡ ተቃርቤ ነበር። ትግላችን መስመር እየያዘ የመጣ ይመስለኛል። አንተና ፀሀይ በድጋሚ ፈተና እንድትወስዱ መወሰኑን እና ለፈተናው እንድትዘጋጅ ልነግርህ ነበር የፈለኩህ፡ ከየባለስልጣኑና ከአንዳንድ ሰራተኞች ጋር የተናነቅኩት ለዚህ ነበር። የመጨረሻው ውጤት የሰመረ እንደሚሆን ደግሞ ምንም ጥርጥር የለኝም" ሳቅ አለ።
ጌትነት ከመቀመጫው ዘሎ አቅፎ ሊስመው ከጀለ፡፡ ተንበርክኮ እግሩ
ላይ ሊወድቅ ተመኘ፡፡ ፊቱ በደስታ እንደማሽላ ፈካ፡፡ ፍንድቅድቁ ወጣ፡፡ የእድል ገመዱ ስለለች እንጂ አለመበጠሷን አወቀ፡፡ እንደገና አዲስ
የተስፋ ብርሃን፣ አዲስ የህይወት ምዕራፍ እየሞተ ከሄደው ተስፋው ውስጥ ብቅ ሊል ሲያንስራራ ታወቀው:: ለሱ ለአንድ ምስኪን ተቆርቋሪ ሆኖ በሥራ ህይወቱ ውስጥ ሊጠቅሙትም ሆነ ሊጎዱት ከሚችሉ በርካታ የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ጋር ተናንቆ ለዚህ ስላበቃው ሽመልስን የሚያመስግንበት ቋንቋ አጠረው። ሽመልስ ከዚህ ወሳኝ ምዕራፍ
ላይ አድርሶታል፡፡ ፈረስ ያደርሳልንጂ ጦር ይዞ አይዋጋም፡፡ ከዚህ በኋላ የሱ ብርታት ብቻ ነው የሚያስፈልገው፡፡ ይህንን የምስራች ከሰማ በኋላ ከአብዱላሂ ቤት መውጣቱንና ለጊዜው ጎኑን የሚያሳርፍበት ቦታ እንኳ እንደሌለው በፍርሃት ተውጦ ገለፀለት።

"አይዞህ ጌትነት አቅሜ በሚፈቅደው ሁሉ ልረዳህ ዝግጁ ነኝ ስለማደሪያህ ብዙም አትጨነቅ " በማለት ሞራል ሰጠው፡፡
"የናት አባቴ አምላክ" አለና በልቡ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ ማምሻውን ተያይዘው ወደ ሽመልስ መኖሪያ ቤት ሄዱ።
ቤቷ ሶስት ክፍሎች ያሏት በንፅህና የተያዘች ናት፡፡ ሽመልስ ሶስት ጉልቻ
ሊመሰርት ቅድመ ሁኔታችን በማጠናቀቅ ላይ ያለ ሰው ነው፡፡ ከአስረኛ ክፍል ጀምሮ በጓደኝነት አብራው የቆየችው ኤልሳቤጥን ለማግባት የቤት ዕቃዎችን በሟሟላት ላይ ሲሆን ለጊዜው የሚኖረው በሠራተኛ ነው።
ጌትነት ነፃ ሆኖ ሰውነቱን ታጥቦ የታጠበ ልብስ ቀይሮ ጥሩ በልቶ ጥሩ ጠጥቶ ለፈተናው ሲዘጋጅ አደረ። እኩለ ለሊት ሲሆን የጠዋቱ ተፈታኝ ፈጣሪው በጣለለት ሲሳይ በሽመልስ ላይ ሀሳቡን ጣል አድርጎ በተስፋ የሰላም እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡

“ታዲያስ ጌትነት? አዳር ተመቸህ?" ሽመልስ ቀድሞት ተነስቶ ነበር፡፡

“እግዚአብሔር ይመስገን ጋሼ ሽመልስ፡፡ ነጋ እንዴ? የሶስት ቀን የእንቅልፍ ዕዳዬን ሳወራርድ ነው ያደርኩት። መንጋቱን እንኳ አላወቅኩም ነበር" ከአልጋው ውስጥ ለመውጣት ታገለ።
“እባክህ ይሄንን ጋሼ የምትለኝን ነገር ተወኝ። ሽመልስ እያልክ ጥራኝ።
እንደሱ ስትጠራኝ ነው ደስ የሚለኝ"
"ይሻላል ጋሼ ሽመልስ? መዳፈር አይሆንም? እንዴት ብዬ በአንድ ጊዜ?"

"ተውንጂ! አሁንምኮ ጋሼ እያልክ ነው!"
“እሺ…አንተኮ ወንድሜም ጓደኛዬም አባቴም ነህ። ለኔ ይሄንን ያክል የሚጨነቁልኝ አባቴና እናቴ ብቻ ነበሩ"
“ጌትነት አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ፡፡ እኔ የምታገለው፣ የምጨነቀው ላንተ ብቻ ሳይሆን ፀፀት ሰላሜን እንዳይነሳኝ ለራሴ ጭምር ነው።
በአንተ ላይ የደረሰው በደል በኔም ላይ በተመሳሳይ መልኩ ደርሶብኝ ነበረ፡፡ በነገሩ ይበልጥ እንድገፋበት ያደረገኝ አንዱ ምክንያት ያንን በራሴ ላይ ደርሶብኝ የነበረውን በደል የምዋጋበት አጋጣሚ ሆኖ ስላገኘሁት ነው። ከዩኒቨርሲቲ ተመርቄ ሥራ እንደጀመርኩ በሃላፊነት ላይ
የተቀመጡ ሰዎች ወጣት በመሆኔ ብቻ ለሥራ መደቡ ሊከፈል የሚገባው ደመወዝ እንዳይከፈለኝ ተጽዕኖ አድርገውብኝ ነበር። ሥራውን እንድሠራ ነገር ግን ደመወዙን እንዳላገኝ ሆን ብለው በፈጠሩት ተንኮል ሊጎዱኝ ሞከሩ፡፡ ምን ታደርገዋለህ? በብቃት ሳይሆን በዘመድ የተሾሙ በአድልዎና በጉቦ የነበዙ ከንቱዎች ከዚህ የተሻለ እንዲሰሩ
ቅም፡፡ ተምረህ ሲያዩ ደማቸው ይፈላል። ነገ ቦታዬን ይቀማኛል በሚል ስንኩል ፍርሀት ትንሽ ቀና ስትል በኩርኩም ይገጩሀል።ያሸማቅቁሀል፡፡ ደመወዝ የሚወስነው በሥራ ክብደትና በተሰጠህ ሀላፊነት እንጂ በሥጋህ ወይንም በዕድሜህ ክብደት አይደለም፡፡ አንዳንዶቹ ይሄንን አይገነዘቡትም። ወፍራምና ረጅም ከሆንክ ጥሩ ደመወዝ እንድታገኝ ወጣትና
አጭር ከሆንክ ደግሞ ዝቅተኛ ክፍያ እንዲከፈልህ እስከማድረግ የዘቀጠ
በክብደትና በቁመት ላይ የተመሰረተ የደመወዝ አከፋፈል ሥርአትን
ለመዘርጋት የሚጥሩ ከንቱዎች ናቸው፡፡ እኔም ከዩኒቨርስቲ ተመርቄ ስቀጠር የዚህ የጫጨና የቀጨጨ የድንክ አስተሳሰባቸው ሰለባ ሆኜ ነበር። ወጣት በመሆኔ ብቻ ተመሳሳይ ስራ እየሰራሁ ዝቅተኛ ደመወዝ እንዳገኝ ወስነውብኝ በብዙ ውጣ ውረድና በብዙ ክርክር ነበር መርታት የቻልኩት። ያንተም ጉዳይ ከዚህ የተለየ አይደለም። ወፍራም ጭንቅላት እያለህ እንጀራህን ወፍራም ዘመድ ላለው ሰው አሳልፈው እየሰጡት ነው።ይሄንን ሁኔታ በቸልታ ባልፈው ደግሞ ትናንትና የደረሰብኝን በደል መርሳት፣ እኔነቴን መካድ ነው የሚሆነው፡፡ ስለዚህ ጥረቴ ላንተነትህ በሰጠሁት ግምት ብቻ ሳይሆን ለእኔነቴ ጭምር የከፈልኩት ዋጋ
በመሆኑ እንደ ውለታ አትቁጠረው፡፡ ጌትነት አንተም ይህንን ችግርና
ፈተና አልፈህ በድል ስትወጣ የዚህ ሁሉ ችግር ድምር ውጤት ሰው መሆንህን መርሳት የለብህም፡፡ ችግር የሰው ልጅ እንደ እርሳስ የሚቀረፅበት ትምህርት ቤት ነውና ከዚህ ችግር ልትማርበት ይገባል። የህይወትን ጣፋጭነት የበለጠ የምታጣጥመው ከፈተናዋ ውስጥ በድል አድራጊነት ስትወጣ ነውና ለቀሪው ህይወትህ ጥሩ ትምህርት ይሆንሀል። ስለ ሌሎች እንድታስብ ስለ እውነት እንድትከራከር ስንቅ ይሆንሃልና የኔን
ጥረት ብዙም አትጨነቅበት" አለው።

ጌትነት የሽመልስን ምክር አዳምጦ ቁም ነገሩን በልቡ ኣስቀረና አብረው ቁርስ ሊበሉ ተያይዘው ወጡ፡፡ ቁርሳቸውን አብረው ከበሉ በኋላ ሽመልስ
“መልካም ዕድል!" ብሎት ወደ መስሪያ ቤት ሲሄድ ጌትነት ደግሞ በስድስት ሰዓት ለሚሰጠው ፈተና ሲዘጋጅ አረፈደ።

የሰራተኞቹ ሹክሹክታ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ግማሹ ሽመልስን ያደንቃል፡፡ያመስግነዋል፡፡ገሚሱ"ምቀኛ!እርኩስ!”እያለ ይረግመዋል። አቶ
አባይነህም ይደነፋሉ፡፡ “እከካም የድሃ ልጅ ሁላ ትናንትና እከኩን አራግፈንለት ጥብቆ ሲቀይር ጊዜ ማንነቱን ረሳው ቁርስን በልቶ ምሳውን
👍6
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....አስቻለው የተሳፈረበት አንደኛ በራሪ አውቶብስ ከዲላ መውጫ ኬላ ጀምሮ በጩኮ፤ በአፖስቶ በአቢላ እና በአዋሳ ጥቁር ውሃ ፍተሻ ጣቢያዎች ላይ ፍዳውን
ጨርሶ ከሻሽመኔው ኬላ ላይ ከእረፋዱ አራት ሠዓት አካባቢ ደረሰ። የማይቀረው ዕዳ ሊከፈል ተጓዥ ሁሉ ከመኪና ላይ ወረደ:: ከአስቻለሁ አጠገብ በስተግራ በኩል የመስኮት ጥግ ይዘው ተቀምጠው የነበሩት ወይዘሮ ግን አልወረዱም፡፡

ፈታሾች ከመኪናው ዙሪያ እንደ ልማዳቸው ሲጎማለሉ በርካታ ደቂቃዎችን ከአሳለፉ በኋላ ሁለት ፈታሾች ከመኪናው ፊትና ኋላ በር በኩል ገብተው ለመበርበር
ተዘጋጁ ቀድሞ በፊት በር በኩል የነበረው ፈታሽ የመኪናውን በር መወጣጫ ረግጦ ጠልጠል ሲል እኒያ ሴትዮ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው አገኛቸው፡፡

ምንድነው?» ሲል ዓይኑን ፈጠጥ አድርጎ ጠየቃቸው። ፈታሹ አጠር
ጠየም ያለ ነው፡፡ የፊቱ ወዝ ያብረቀርቃል፡፡ ፊቱ ጠፍጠፍ ያለና አፍንጫው ደፍጠጥ ያለው ጎረምሳ ቢጤ ነው፡፡ የመለዮውን እጅጌ ሰቅስቆት የእጁ ጡንቻ ፍርጥም ብሎ ይታያል። ሰንሰስት የሚያህል የወርቅ ሐብል ደረቱ ላይ ተጋድሞ ይንቀለቀላል፡፡

የኔ ልጅ መውጣት መውረዱ ስልችት ብሎኛል ና እዚሁ ፈትሽ ጎሽ!» አሉት ሴትዮዋ በልመና ዓይነት ፈገግ ብለው ፈታሹን እየተመለከቱት፡፡
«ባክሽ ውረጅ! ምን ትቀልዳለች!" አለና ፈታሹ ቆጣ ብሎ በዓይኑም
ገርመም አደረጋቸው።
ሴትዮዋ ፈገግታቸው ድንገት እልም ብሎ ጠፋና ፊታቸው ኮስተርተር፣ ዓይናቸውም ፍጥጥ አለ። ተናደዱ: በተቀመጡበት ወንበር ላይ እንደ መቅበጥበጥ
እያሉ «እንቺ አትበለኝ አንተ ኧረ ይሄ ደፋር!» አሉት፡፡

«ኣ?» አለ ፈታሹ ወደ ወስጥ ገባ እያለ:: እንደገና «ምን አልሽ አንቺ?» ብሎ ቁልቁል ይመለከታቸው ጀመር፡፡አንቺ አትበለኝ አልኩህ!» አሉና ደሞ ምን ያፈጥብኛል?" ብለው
እሳቸውም አፈጠጡበት::

«ቆይ ምንድነሽ አንቺ?» አላቸው ድፍረታቸው ያልተለመደ ሆኖበት።
ሰው! አውሬ እመስላለሁ?» ፈታሹ ለአፍታ ያህል ፍጥጥ ብሎ ተመለከታቸውና ወደ ውጭ እየተመለከተ
«በቃ ይሄ መኪና ተገትሮ ይውላታል እንጂ ይቺ አሮጊት ሳትወርድ አይፈተሽም።»
ብሎ ከመኪናው ላይ ወረደ:: እንዳትገባ!» ሲል በኋላ በኩል ሊገባ የነበረውንም ፈታሽ ከለከለው።

ተሳፋሪው ሁኔታውን ይከታተል ነበርና ግራ የመጋባት ስሜት አደረበት፡፡ሊጉላሉ ነው:: ግማሹ ፈታሹን ይለምን ጀመር፡፡ ሌላው ደግሞ ከመኪና ሌይ እንዲወርዱ ሴትዮዋን፡፡ ሴትዮዋ ግን ፍንክች አልል አሉ። ይልቁንም በሚለምናቸው ተሳፋሪ ላይ ወረዱበት። «መድሐኒዓለም ይለመነኝ ንቅንቅ አልልም!» አሉና አዳሜ አትጨቅጭቀኝ ወዲያ ሄደህ የምትለምነውን ለምን መቼም አንዴ ወኔህን
ተሰልበህ! ልበ ሙት ሁላ ደሞ እኔንም ይዘኸኝ ሙታ!» አሉ ትንፋሻቸው በርክቶ አፍንጫቸው ነፋ ሞሽሽ፣ ነፋ ሞሽሽ እያለ::
በሁለቱም አቅጣጫ ልመና ያልተሳካለት ተሳፋሪ ያለው አማራጭ አንድ ብቻ ነበር፣ ወደ ኬላው ሃሳፊ በመሄድ የተፈጠረውን ሁኔታ ማስታወቅ። በእርግጥም በርካታ ተሳፋሪ ወደ ሃላፊው ቢሮ ተከታትሎ ሄደና አቤቱታውን ማቅረብ ጀመረ፡፡
በዚህ መሀል ግን ብዙ ጊዜ ባከነ፡፡
ከበርካታ ደቂቃዎች በኋላ የኪላው ሃሳፊ ሳይሆን የማይቀር አንድ ፖሊስ የመቶ አለቅነት መለያ ምልክቱን ደርድሮ ከቢሮ ወጣና በለመነው ተሳፋሪ ታጅቦ
ወደ መኪናው አመራ። ቀጠን ያለ ረጅም ነው፡፡ ፈካ ያስ ጠይም ሆኖ ገተር ባለው አፍንጫው ላይ ጥቁር መነጽር አድርጓል። ልክ ከመኪናው የፊት በር አጠገብ
ሲደርስ የተጣላቸውን ፈታሽ ጨምሮ ተሰፋሪው ሀሉ የሚፈጠረውን ሁኔታ ለማየት ዙሪያውን አሰፈሰፈ:: አስቻለውም" ከህዝቡ ፊት ሆኖ ከፈታሾቹ አጠገብ ቆሟል የኬላው ሀላፊ ወደ ውስጥ ሴትየዋን እያየ «ምንድን ነው ችግሩ? » ሲል ጠየቃቸው
«እናቱ እያላችሁ ችግር መች ይጠፋል? ችግር ለመፍጠር አይደል! በየቦታው የተኮለኮላችሁት» አሉ ሴትየዋ ዓይናቸውን አፍጥጠው ቆነጥነጥ እያሉ
«መኪናው አይፈተሽ ነው የሚሉት?»
«እኔ አልወጣኝም፡፡ ስትልጉ መነቃትሩት።» አሉና ሁለመናቸውን አንዘራቸው በል! ስንት አንበሳ የመሳሰለ ጀግና ወልጄ ወልጀ ለወግ ማረግ
ያደረስኩ ሴትዬ አንድ ጓጉንቸር በመሰለ አሽከርህ ልዋረድ!» አሉና ቀሚሳቸውን ቀልጠፍ እያረጉ! ይህ ቅሌታም! አያውቅም እንጂ እኔ አቦነሽ ሃይሌ ስንት ኮረኔል የሚያከብረኝ ሴት ነኝ፡፡ ይህ ባለጌ ባለጌ ያሳደገው! አሉ በማከታተል።
«አሁንም አታርፊ አንቺ አሮጊት!» አላችው ያ መጀመሪያ የተጣላቸው
ፈታሽ በመቶ አለቃው ትክክሻ ላይ አንገቱን ሰገግ አድርጎ ወደ ውስጥ እያየ።ወደ ውስጥ እያየ

ሴትዮዋ እሁንም እየተቅበጠበጡ «አንተ እንደኔ አታረጅ፣ አንት የተረገምክ ዕድሜ እኮ የንጥህና ምልክት ነው። አዳሜን እያስለቀስክ ዛሬ ደረትህ ቢያብጥ
ዘላለም የምትኖር መሰለህ ዛሬ ሰው ቢያቅተው ነገ አንድዬ ይደፋሃል። ምናምንቴ
የምናምንቴ ልጅ! አሉት ወይዘሮ አቦነሽ ሀይሌ። ምናልባት አፍ እላፊ የተናገሩ መስሏቸው ለማካካስ ሳይሆን አይቅርም ከተቀመጡበት ድንገት ብድግ አሉና ግማሽ ጭናቸው እስከሚታይ ድረስ ቀሚሳቸውን እያራገፉ «ቡና ቋጥራለች ብላችሁ
ተሆነ ያው! አቦነሽ ሃይሌ ነጣ!» ብለው ቁጭ እያሉ «ከእንግዲህ ወዲያ አዳሜ ዓይንህን ብታፈጥ የምፈራህ እንዳይመስልህ» አሉ፡፡ እንዳነጋገራቸው የኬላውንም ሀላፊ ነካ እያረጉ ይመስላል።

መቶ አለቃው ቀጥሎ ምን ማድረግ እንዳለበት በማሰብ ላይ ሳለ በሴትዮዋ ቆራጥነትና አነጋገር ልቡ ሲነካ የቆየው አስቻለው ጣልቃ ገባ። «እኔ እምልህ መቶ
አለቃ» አለው አጀቹን በደረቱ ላይ አቆላልፎ የኬላውን ሃላፊ ዓይን ዓይኑን እያየ::
«አንተ እምትለኝ» አለው መቶ አለቃው በንቀት ዓይን እያየው::
«የምትፈልጉት ቡና አለማለፉን ወይስ የተሳፋሪውን ከመኪና ላይ
መውረድና መውጣት?» ሲል ኮስተር ብሎ ጠየቀው::
«አንተ ምንድን ነህ?» አለው ያ መጀመሪያ ከሴትዮዋ ጋር የተጣላ ፈታሽ ጣልቃ ገብቶ። ዓይኑንም አፈጠጠበት።
አስቻለው ውስጡ ተቆጣ፡ ቀድሞም ቢሆን መቶ አለቃው በንቀት ዓይን ሲያየው በስጨት ብሎ ነበርና እሁን ደግሞ የባሰ በመናደድ «ምንድነህ?» ሲል
የፈታሹን ጥያቄ ራሱ ደገመው፡፡
«አዎ ምንድነህ?»
አስቻለው ድንገት ሳያስበው አንድ ነገር በአዕምሮው ብልጭ አለበት። በሆዱ የመጣው ይምጣ እያለ «ካኪ አለመልበሴን አይተህ ከሆነ ተሳስተሃል! እኔ ግን
ሙሉ የፖርቲ አባል ነኝ!» ብሎ በመታወቂያ እንደመፈለግ ዓይነት እጆቹን ከአንድ ኪሱ ወደ ሌላው ያራውጣቸው ጀመር፡፡
ቆይ ጓድ!» አለ መቶ አለቃው ፈጠን ብሎ፡፡ የአስቻለውን ሁለት እጆች በሁለት እጆቹ ያዛቸው።
ደሞ ምንድህ ይለኛል እንዴ ይሄl?» በማለት አስቻለው በፈታሹ ላይ ዓይኑን አፈጠጠ፡፡ ያ ፈታሽ በሀፍረትና በፍርሀት ፊቱ ልውጥውጥ አለ።
«የኛ ችግር እኮ - » ብሉ መቶ አለቃው ንግግር ሲጀምር አስቻለው ቶሎ ብሎ አቋረጠው::
“እ! የእናንተ ችግር?»
«አንዱን አስወርደን ሌላውን ስንተው ሕዝቡ አድሎ አደረጋችሁ እያለ» ብሎ ሳይጨርስ አሁንም አስቻለው አቋረጠው፡፡ ፈጠን ፈጠን ባለ አነጋገር፡፡
1
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...ጃን ተከል ከወትሮው የበለጠ ሰው ተሰብስቦበታል። ወሬው ሁሉ ስለ ቅዳሜው ግብርና ስለ ምንትዋብ ውበት ነው። ቅዳሜ ዕለት ኣብርሃ ቤተመንግሥት በር ላይ የድኃ ተራ እስኪደርስ ጠብቆ ግብር ተካፍሎ ነበርና በአኮፋዳው
ከየዓይነቱ ምግብ ጠቅጥቆ መጥቶ ጥላዬን እንዲበላ
ሲጋብዘው አልበላም ብሎታል።
አብርሃ ምንትዋብን ባያያትም፣
ስለግብሩ ትልቅነት ሲያወራ አልበቃው በማለቱ ጥላዬ ደከመኝ ልተኛ ብሎት ተለያይተዋል።

ጥላዬ፣ ዋርካው ጠርዝ ላይ ቆሞ፣ “ምንትዋብ ብለው ስም አወጡላት እያሉ ወሬውን ሲቀባበሉ ሰማ። አብርሃን ሲያየው ካንዱ ወደ ሌላው እየሄደ ወሬ ይጨልፋል። ምነው እንደሱ የማላውቃት ባረገኝ። ወደ
ቅጥር ውጭ እኔ ዛፉ ስር ቁሜ አንቺ ነጠላ ተከናንበሽ ገና ኸደጀሰላሙ የልቤን ሳላወጋሽ። የቅርብ ሩቅ ሁኜ ስላንቺ ሰማለሁ። ኸዛ ኸበተክሲያን ወለቴ ምንትዋብ አሉሽ ለኔ ሁሌም ወለቴ ነሽ፡፡ አንድ ቀን ስንኳ ብቅ ስትይ ልቤ ሚተረከከውን ምን ግዝየም አልረሳው። አንድ ቀን ያነን ድንቅ ፊትሽን እሥል ይሆናል። እስተዛው የወፍታው ኻንቺ ጋር ይሁን ብሎ የፍቅራቸውን ምዕራፍ መዝጋት እንዳለበት ለልቡ አስገነዘበ።

አብርሃ የቃረመውን ወሬ ሊነግረው ሲመጣ፣ ጥላዬ መስማት አልፈለገም። “ኸዛው እንኸድና ለሥላሤ ምስጋናዬን ላቅርብ” አለው፣ ወሬውን ሳይጀምር።

“ምናለ፣ እንኸዳ” አለው፣ ግራ የተጋባው አብርሃ።አብርሃ ወደቤቱ ሲሄድ ጥላዬ ቤተክርስቲያኑ ደጅ ላይ ተደፍቶ ምስጋናውን አቀረበ። የተሰበረ ልቡን ሥላሤ እንዲጠግኑለትም ጸሎት
አድርጎ ከዐይኑ ያመለጠውን እንባ ሰው ሳያየው በጋቢው ጠራርጎ ተነሣ።ከመጣ ጊዜ ጀምሮ ሲቀመጥበት የነበረው ዋንዛ ዛፍ ሥር ተቀምጦአካባቢውን ሲቃኝ፣ የቆሎ ተማሪው ግማሹ የለቀመውን ዕንጨት በእቅፉ
ይዞ ወደቤቱ ይሄዳል፣ ሌላው ውሃ ቀድቶ መመለሱ ነው። በየአጥሩ ጥግ መነኮሳትና አረጋውያን ተቀምጠው ዳዊት ይደግማሉ፣ የቁም ጸሐፊው ብራና ላይ ይጽፋል፣ አንዱ ብራና ሲደጉስ ሌላው ቅዱሳት መጻሕፍትን
ያስጌጣል።

ጥላዬ፣ ለሥራቸው በሚሰጡት ትኩረት ተገረመ። እሱም እንደነሱ
ተቀምጦ ሥራውን የሚሠራበትን ቀን ናፈቀ። አለቃ ሔኖክ ትምህርት
እስኪያስጀምሩት ቸኮለ። እዚያው ግቢውን ሲቃኝ ቆይቶ፣ ከሰዐት
በኋላ፣ ወደ እሳቸው ቤት አመራ።
እሳቸው ስላልነበሩ ደጅ ተቀመጠ። ወርቄ በር ላይ ቆማ የሆነ
ያልሆነውን ስትጠይቀውና ሲመልስ ቆይተው፣ ወደ ውስጥ እንደገባች አለቃ ሔኖክ ቅጥር ግቢው ገቡ።

“አምሽተህ ነው?” ብለውት ወደ ውስጥ ገቡ።ቆየት ብለው ወጥተው ወደ ጓሮ እንዲመጣ በእጃቸው አመለከቱት ኩታውን እያስተካከለ ተከተላቸው። ጎጆውጋ ሲደርሱ፣ “ይህቻት
እንግዲህ ማደሪያህ” አሉት።
"እመቤቴ ትስጥልኝ” አላቸው፣ ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ።

አንገቱን ወደ ውስጥ መዘዝ አድርጎ ተመለከተ። ከአንድ አነስተኛ ቁርበት በስተቀር ጎጆዋ ውስጥ ሌላ ምንም ነገር የለም። የአቧራዋ ሽታ ይሰነፍጣል ።

“እዝች ሁነህ ሥራህን ትሠራለህ። የትምርት ግዝየ ሲደርስ እኔ አለሁ።ምግብ ወርቄ ትሰጥኻለች። አንተ ዛዲያ እንጨት ትለቅምላታለህ፣ ውሃ
ትቀዳላታለህ፣ ልብስም ታጥባለህ” አሉት።

“እረ ምን ገዶኝ!”

አለቃ ወደ ቤት ሲመለሱ፣ ቁርበቱ ላይ ጋደም እንዳለ መላ አካላቱ
በሐሳብ ደክሞ ነበርና እንቅልፍ ወሰደው። ምሽት ላይ፣ ወርቄ እራቱን ይዛለት መጣች። ራቱን በልቶ ተኛ።በነጋታው አለቃ ሔኖክ በወርቄ አስጠርተውት ሲገባ እሳቸው መደብ ላይ ተቀምጠዋል። ሰላምታ ሰጥቷቸው በእሳቸው ትይዩ ተቀመጠ።
ወርቄ ቁርስ አቅርባላቸው ከበሉ በኋላ፣ አለቃ ሔኖክ፣ አነስተኛ ብራናና የቀለም ቀንድ ይዘው አብሯቸው ደጅ እንዲወጣ ነገሩት።

“ብራናና ቀለም እኔ ሰጥኻለሁ። ወደፊት ብራና ሆነ ቀለም ራስህ
ታዘጋጃለህ። ቀለም አቀማመም አሳይሀለሁ። ንድፍም አሳይህና በዚያ መሠረት ኸርኩሳኑ መኻል ምትፈልገውን ሠርተህ ታመጣልኛለኸ አሉት።

እጅ ነሥቶ ትኩረቱን እጃቸው ላይ ያለው ብራና ላይ አደረገ።
ቀስ ብለው ንድፍ እንዴት እንደሚሠራና ቀለም እንዴት እንደሚቀባ አሳዩት።
“ለነገሩ ንድፍ አይቸግርህም። በአክርማ ስትሠራ ቆይተህ የለ?”
አሉት፣ እየሳቁ።
ዐይኑን ከብራናውና ንድፉን ከሚሠሩበት የቀርከሀ ስንጥር ላይ
ሳያነሳ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ።

ትምህርቱን ጨርሰው እሳቸው ወደ ውስጥ ሲገቡ፣ እሱ ወደ ቤቱ
ሄደ። ጋቢውን ቁርበቱ ላይ ወርውሮ ደጅ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ፣ለመጀመሪያ ጊዜ ሲመኝ የኖረው ብራና እጁ በመግባቱ ሊስመው ቃጣው።

ሕይወቱ ዐዲስ ምዕራፍ የያዘ መሰለው።ሥዕሉን በምን እንደሚጀምር አወጣ አወረደ... እባብ? ሳጥናኤል? ቁራ? በመጨረሻም ስለምን ሳጥናኤኔልን አልሰራም አለ፣ ለራሱ።አለቃ ሔኖክ ባሳዩት መሠረት ንድፍ ሞከረ፤ ተንጋደደበት። ብራናውን
ያበላሽ ስለመሰለው ደነገጠ። ሆኖም መሣሉን ቀጠለ። አለቅጥ ረጀም፣ግራና ቀኝ አስፈሪ ቀንዶች ያለው፣ ጆሮዎቹ በጣም ትልልቅና ጭራ ያለው ፍጡር ሣለ። ቤቱ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ፣ ብራናውን ደጋግሞ እየተመለከተ ስቆ እንደማያውቀው ሳቀ። በነጋታው ፈራ ተባ እያለ አለቃ ሔኖክጋ ሲሄድ ወርቄ፣ “ኣፍህን እንድትሽር ልጠራህ ስል መጣህ” አለችው።

“ለመብልማ እስትትጠራ አትጠብቅ። ቤትህ እኮ ነው” አሉት፣ አለቃ ሔኖክ።

ቁርስ አድርገው ከጨረሱ በኋላ፣ “እስቲ ምን ሠራህ?” አሉት።

ብራናውን ብድግ ብሎ ሲያቀብላቸው፣ ቀረብ፣ ራቅ አድርገው ተመለከቱትና ሳቁ። “ሳጥናኤል... ማለፊያ ነው። ንድፉም መልካም ነው። ተሰጥኦ እንዳለህ ያስታውቃል” አሉት።

“ንድፉ ተንጋደደብኝ እንጂ።”

ርኩሳንን ከሀዲያንን፣ አጋንንትንና ክፉዎችን ስትሥል ንድፉ ቢንጋደድ ምንም አዶለም። ባሕሪያቸው ነው፤ መንጋደድ ይስማማቸዋል። ላንተ ግን ዋናው እጅ ማፍታታትህ ነው። ወደፊት ቅዱሳንን፣ መላዕክትንና ሌሎችን ስትሥል ግን ንድፍ ማንሻሽፍ
አይፈቀድም። በል በርታ” ብለው ብራናውን መልሰው ሰጡት።

እጅ ነሥቶ ወጣ።

በሚቀጥሉት ቀናት፣ እሳቸው በነገሩት መሠረት ጥቁር ቀለም ከተለያዩ ዕጽዋት ቀምሞ ሥዕል መሣሉን ተያያዘው። እንደሱ ቢሆን፣ ርኩሳንን ብቻ ሳይሆን የፈለገውን ቢሰራ በመረጠ። ብዙውን ጊዜ የምንትዋብ
መልክ ፊቱ ላይ ድቅን ይላል። እንደበፊቱ እንስሳውን ቤቶቹን ሁሉ
መሣል ይፈልጋል። አንዳንዴ የፈለገውን የሚሥልበት የቤታቸው ጓሮ ይናፍቀዋል።

ሥዕል በማይሥልበት፣ ለወርቄ ውሃ በማይቀዳበት፣ ዕንጨት
በማይለቅምበትና የአለቃ ሔኖክን ልብስ በማያጥብበት ጊዜ፣ ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል እየሄደ ወሬ ይሰማል። ጃን ተከል ብቅ ማለት እሱስ ሆኖበታል። ቤተመንግሥት ግብር ሲጣል፣ አብርሃ ምግብ ብቻ ሳይሆን
ስለ ምንትዋብ ወሬ ይዞለት ይመጣል ።

በትምህርቱ እየጎበዘ ሲመጣ፣ አለቃ ሔኖክ በሥራው ቢደሰቱም፣
“መልካም ነው፣ በርታ” ከማለት በስተቀር ብዙ ስለማያብራሩ ጥቂት ቅር ይሰኛል፣ ቢያሞጋግሱት ይመርጣል። የሠራውን ሲመለከቱ፣ ፊታቸው
ላይ የሚንፀባረቀውን አድናቆት ለምን በቃላት እንደማይገልጹለት
ይገርመዋል።

አንድ ቀን አስደሰቱት። ግቢው ውስጥ ተቀምጠዋል። እንዴትና
የት እንደዋለ ከጠየቁት በኋላ፣ “ጥላዬ፣ ሥዕል ኸዠመርህ ወራት
አልፈውሀል። እጅህም ጥሩ ተፍታቷል። እንደነገርሁህ ጥቂት ቆይተህ ቄሶችን፣ መሪጌታዎችን፣ ሊቀጠበብቶችን ቤተክስቲያን አካባቢ ያሉ ሰዎችን መሣል ትዝምራለህ” አሉት።

ደስ ተሰኘ።
👍15😱1
#ትኩሳት


#ክፍል_አስራ_አራት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር


...አንድ ማታ ኒኮልን ከተማ ሬስቶራንት እራት ጋበዝኳትና ብዙ
ወይን እያጠጣኋት ስለልብ ወለድ መፃህፍትና ስለ ፊልሞች ጨዋታ
እስጀመርኳት። መጀመሪያ ስለምንወዳቸው ደራስያን፣ ስላየናቸው ፊልሞች፣ ስለምናውቃቸው ሰዎች እና በልብ ወለድ መፃህፍት ውስጥ ካገኘናቸው ሰዎች ጋር በምን እንደሚመሳሰሉ ማለት
ስለራሳችን ሳይሆን ስለ ሌላ ነገር ስናወራ፣ ወይን ስንጠጣ፣ ብዙ ጊዜ አሳለፍን። እየለመደችኝ ሄደች። ወይኑም እየሰራ ሄደ። አይናፋርነቷ እየረገፈ፣ እንደ ልቧ ለማውራት እየቻለች ሄደች፡፡ እኔም ፈረንሳይኛ እሷ ስትናገረው በጣም የሚጥም መሆኑን እያስተዋልኩ ሄድኩ።

ቀስ ብዩ ወሬውን ወደ ባህራም ወሰድኩት:: እንዴት ጎበዝ ሆኖ
እንደሚታየኝና፣ ምን ያህል እንደማደንቀው ከነገርኳት በኋላ፣
ባህራም ላንቺ እንዴት ሆኖ ነው የሚታይሽ? አልኳት። ደራሲ
መሆን እንደምፈልግና ስለሰዎች ማወቅ እንዳለብኝ፣ ይልቁንም
ሴቶች ወንዶችን እንዴት እንደሚያዩዋቸው ማጥናት እንደሚገባኝ ስለዚህ፣ እሷ ስለራሷ ብትነግረኝ ለኔ ትልቅ ዋጋ እንዳለው፣ በሰፊው ዘረዘርኩላት። ተቀበለችኝና ስትናገር፣ በቃላትዋ እየተንሳፈፍኩ የድምፅዋ ዜማ እየተመቸኝ አዳመጥኳት
ደራሲ ሳትሆንም ስለራሴ ብነግርህ ግድ የለኝም አለችኝ።
ባሀራም ስላንተ ብዙ ጥሩ ጥሩ ነገር ስለነገረኝ ነው መሰለኝ፣ በጣም የማውቅህ መስሎ ይሰማኛል። ደሞ እወድሀለሁ:: በጣም ተወዳጅ ልጅ ነህ። ብዙ ሴቶች ይህን ነግረውህ የለ? ተናገር፡ (ትስቃለች።እሷ የተናገረችው በንፁህ ልብ ነበር። እኔ ግን ምኞቴ ተቀሰቀሰ፡፡
እግሮቼን አጣመርኩ። የሉልሰገድንና የሷን ታሪክ ባላውቅ ኖሮ አሁን ምኞቴ ይቀሰቀስብኝ ነበር? እንጃ፡፡ ኒኮል ቀጠለችልኝ

«በአስራ ስድስት አመቴ ማርሴል ከሚባል ልጅ ፍቅር ያዘኝ
ማርሴልም ወደደኝ። ቤቶቻችን ሁለቱም ሀብታም ቡርዥም
በመሆናቸው ይከባበሩና ይዋደዱ ስለነበረ፣ በመዋደዳችን እጅግ
ተደሰቱ። እስክንጋባ ቸኮሉ፡፡ ግን
ሁለታችንም የዩኒቨርሲቲ
ትምህርታችንን እስክንጨርስ ላንጋባ ቆረጥን። ቤቶቻችንን ለማስደ ሰት ስንል ተጫጨን፡፡ በዚህ መካከል ማርሴል አየር ሀይል ገባ

«አንቷን ደ ሴንት ኤግዙፔሪን ታውቀው የለ? በኤሮፕላን
ስለመብረር፣ ስለአደጋው፣ ስለክብሩ፣ ስለጀግንነቱ የደረሳቸውን መፃህፍት፣ ማርሴል ደጋግሞ ያነባቸው ነበር፡፡ ከልቡ ሴንት ኤግዙፔሪኝ ያደንቀው ነበር፤ ያመልከው ነበር፡፡ ለዚህ ይመስለኛል አየር ሀይል የገባው፡፡ እኔ ተው አትግባ፤ እንደ ሴንት ኤግዙፔሪ በኤሮፕላን አደጋ ትሞታለህ፣ አልኩት። መሞት የት ይቀራል? አለኝ። የሰው ልጅ ተግባሩ ከሞት ለማምለጥ መጣጣር ሳይሆን፡ ሞት
እስኪመጣ ድረስ ክብር ያለው፣ ኩራት ያለው ኑሮን መኖር ነው፣
አለኝ። አለቀስኩ። እምባዬን ጠረገልኝ። አሮፕላን ነጂ ሆነ
ይህ ሁሉ ሲሆን በግብረ ስጋ ሊገናኘኝ ይሞክር ነበር፡፡ በብዙ
ይለምነኝ ነበር፡፡ ሳንጋባ አይሆንም ብዬ እምቢ አልኩት አንድ ቀን የኤሮፕላን እደጋ ደረሰበት። ሁለት ወር ሙሉ ሀኪም ቤት ተኛ። ከዚያ ወደ ቤቱ መጣ። የአየር ሀይል ኑሮ፣ የሴንት ኤግዙፔሪ አይነት ኑሮ፣ ክብር፣ አደጋና ጉብዝና የሞላበት ኑሮ፣ የጀግኖች አይነት ኑሮ በቃው:: ከአየር ሀይል አሰናበቱት።ምክንያቱም ወገቡ ተሰብሮ እግሮቹ ሽባ ሆኑ። በተሽከርካሪ ወምበር ቁጭ ብሎ፣ እኔ ወይም እናቱ እየገፋነው ነበር አየር ለመቀበል እንኳ የሚወጣው
«ካንጀቴ አዘንኩለት፡ በሀይል ወደድኩት እሱ ግን አሁንም ሽባ ሆኖ የሴንት ኤግዘፔሪን መፃህፍት
ያነብ ነበር። ስለአደጋ፣ ስለጀግንነት፣ ስለክብር ስለሞት ያነብ ነበር።አንድ ቀን ሽጉጡን ጠጥቶ ሞተ ሀዘን ጀመረኝ። ግን ሀዘን ይለመዳል። ወጣት ከሆንክማ ትንሽ ቆይቶም ይረሳል። በተለይ ያጠቃኝ ፀፀት ነበር። ፀፀት አይለመድም፣
አይረሳም፣ የማይጠግብ የማይተኛ ውስጣዊ ትል ነው፡ እድሜ ልክህን ይበላሀል። የቆጨኝ ማርሴል በግብረ ስጋ ሊገናኘኝ ሲፈልግ እምቢ ማለቴ ነው:: እወደው ነበር፡ ስጋዬን ለሱ መስጠት እንዴት አቃተኝ? በሀይል ይቆጨኝ ይሞረሙረኝ ጀመር

ነብስ አባቴ ጋ ሄድኩና ሁሉን ተናዘዝኩ፡፡ የሠራሽው ልክ
ነበር አሉኝ። እኔግን ፍፁም ስህተት እንደነበረ የበለጠ እየተገነዘብኩ ሄድኩ፡፡ ራሴን መቅጣት ጀመርኩ፡፡ ከጠየቀኝ ሁሉ መተኛት
ጀመርኩ። ደሞ ብዙዎች ይጠይቁኝ ጀመር። ርካሽ ሴት ሆንኩ

«ግን አሁንም ፀፀቱ አልተወኝም»

በካሎሪያዬን እንዳለፍኩ ለዩኒቨርሲቲ ትምህርት ወደ ኤክስ
መጣሁ፡፡ ቤቶቼም ማርሴልን ለመርሳት ካለአቨር ከተማ መራቅ
እንዳለብኝ ስላወቁ ሂጂ አሉኝ። ኤክስ መጥቼ በርካሽነቴ ላይ
ጠጪነት ጨመርኩበት። የፈለገኝ እንግዲህ እስክሰክር ድረስ ማጠጣት አለበት። ብዙ ሰአት ካንዱ ጋር ስጠጣ አመሻለሁ። ጧት ወደ አምስት ሰአት ላይ ስነቃ አልጋው ውስጥ ነኝ፡፡ ሲደሰትብኝ እንዳደረ ይታወቀኛል፣ ግን ምን ምን እንደሰራን እንደ ህልም'ንጂ እንደ ውን ሆኖ አይታየኝም

ካንዲት የኔ ብጤ ርካሽ ጋር ገጠምኩ፣ አብረን መጠጥና
ወንድ ስናሳድድ እናመሽ ጀመር

እንዲህ ስል አመቱ አለፈ፡ ፈተና ወደቅኩ፡ ክፍል ደገምኩ፣
ሁለተኛው አመት ተጀመረ፣ ያንኑ ኑሮዩን ቀጠልኩ

አንድ ረቡእ ጧት እንደ ልማዴ አንዱ እማላውቀው መኝታ
ቤት ነቃሁ። ሰውየው ቁርስ ያቀርባል፡፡ ልዩ ሰው ሆኖ ታየኝ።
ሳይነካኝ አድሯል፡፡ ከመስከሩ የተነሳ ሊነካኝ ባይችል ነው እንዳልል፣ ትላንት ማታ ፓርቲው ጋ ልሰክር ትንሽ ሲቀረኝ ጠጣ እንጂ»
ስለው ሁለታችንም ከሰከርንማ ማን ማንን ይደግፋል?» ሲለኝ
አስታወሰው
“አልጋ ውስጥ እንዳለሁ ቁርስ ከበላን በኋሳ፣ ሰውየው በተሰባበረ
ፈረንሳይኛ
“ እንቁላል ከተሰበረ ወድያ ምንም
እንደማይሆን ታውቂ የለ?» አለኝ፡፡ ምን እንደሚል ሳይገባኝ «አዎን”
አልኩት። ወጣትነትም አንዴ ከተሰበረ ሊጠገን አይችልም» አለኝ

«ምን ማለትህ ነው?» አልኩት

«ያንቺ ወጣትነት ገና አልተሰበረም:: ግን ሊሰበር ትንሽ ነው የቀረው። እንደዚህ አይነት ኑሮ ከቀጠልሽ ከትንሽ ጊዜ በኋላ
ይሰበራል»

ተናደድኩ «ምን አገባህ?» አልኩት
«ምን አገባህ አትበይኝ፡ ፈረንሳይ መሰልኩሽ እንዴ? እናንተ
ፈረንሳዮች ፈሪ ናችሁ፡፡ ግብዝ ናችሁ። ተግባራችሁን መፈፀም
አስቸጋሪ የሆነባችሁ እንደሆነ፣ እኔ ምን አገባኝ? Ca me regarde pas. ብላችሁ ትተዉታላችሁ፡፡ እኔ ግን እንደሱ አይደለሁም፡፡»

«እና በኔ ህይወት አንተ ምን አገባህ?»

«አንቺ አልጋዬ ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ? በኔ ህይወት ውስጥ
ገባሽ ማለት አይደለም?» አለኝ። መልስ ስላጣሁ ዝም አልኩ
መጥቶ አልጋው ላይ አጠገቤ ቁጭ እለና፣ አይን አይኔን እያየኝ
«አሁን እስቲ ለሁለት ደቂቃ ፈረንሳይ መሆኑን ተይና ሰው
ሁኚ፡፡ ለሁለት ደቂቃ ብቻ፣ እሺ? አለዚያ ለመናገር አልችልም»
አለኝ፡፡ አንድ አይነት ደግ ፈገግታ አሳየኝ፡፡ ረስቼው የነበረ
አይናፋርነቴ ድንገት ተመልሶ ሽፍን አደረገኝ፡፡ ወደታች ሳይ ፊቴን
በእጆቹ ይዞ ቀና አደረገኝና ግምባሬን ሳመኝ

«አገሬ ኣንቺን የሚያካክሉ ታናናሽ እህቶች አሉኝ፡፡ አንቺ
የምታረጊውን ሲያረጉ ባያቸው ዝም አልላቸውም። ስለዚህ አንቺንም ዝም አልልሽም። ይገባሻል?»
👍28👏2
#ምንዱባን


#ክፍል_አስራ_አራት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

....«ጌታዬ ይቀመጡ» አለው የጠባቂዎች ኃላፊ:: ሰውዬው እንዲሄድለት ግድግዳውን ተደግፎ ቆመ፤ አላበው፧ መተንፈስ አቃተው፤ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡ እንደገና ቁጭ አለ፡፡ የተቀመጠበት ቦታ ትንሽ ዞር ያለ ስለነበር ለሰው በግልፅ አይታይም
ቁጭ እንዳለ አሳቡን የመለወጥ ዝንባሌ ታየበት:: “እስቲ አሁን ማን
አስገድዶኝ ነው የመጣሁት» ሲል አሰበ:: ነገር ግን እንዴት እንደሆነ
ሳያውቀው ቶሎ ብድግ ብሎ በመራመድ ችሎቱ ውስጥ ዳኞች ከነበሩበት አካባቢ ተጠጋ::

አካባቢውን በሚገባ ቃኘው:: ዳኞች ከፊት ለፊት ከፍ ካለው ሥፍራ ተቀምጠዋል:: ጠበቆች አፍጥጠዋል:: ጠባቂ ወታደሮች በየጥጉ ተበታትነው ቆመዋል:: የዳኞች ጠረጴዛ በደማቅ ጨርቅ ተሸፍኖአል:: የበሮች እጄታ
አካባቢ በእድፍ ጠቁሯዋል:: «
ስው ሰራሽ ሕግ እውነትን ያወጣል» በሚል እምነት ከዚያ የነበረ ሁሉ በጥሞና ያዳምጣል:: የሰው ብዛት ከመጠን በላይ
ስለነበር እርሱን ማንም ልብ አላለውም:: ሰው ሁሉ ይመለከት የነበረው ከወንጀለኞች መቆሚያ ላይ በሁለት ጠባቂዎች ታጅቦ ቆሞ የነበረውን ሰው
ነው::

በሁለት ጠባቂዎች ታጅበው የቆሙት ተከሳሹ ሻምፕማቲዩ ነበሩ፡፡መሴይ ማንደላይን አተኩሮ ተመለከታቸው:: በመልክ መመሳሰላቸውን ተገነዘበ፡፡ በእድሜ ግን ከእርሱ በጣም ያረጁ ይመስላል::

እየቀረበ ሲሄድ የመሐል ዳኛውና አቃቤ ሕጉ በጉልህ ስላዩትና
ስለለዩት በአንገት ሰላም አሉት:: ዳኞቹን፣ ሕግ አስከባሪውና እዚያ የነበሩ ጠበቆችና ጠባቂዎች ከሃያ ሰባት ዓመት በፊት ያያቸው መሆኑን አስታወሰ፡፡
አሁንም ከስንት ዓመት በኋላ ከእነዚህ ሰዎች እጅ ሊወድቅ በመሆኑና ውሳኔያቸው ስለአስፈራው ዓይኑን ጨፈነ፡፡ ከፊት ለፊቱ የቆሙት ተከሳሽ
«ዣን ቫልዣ ናቸው ተብለው ነው የተከሰሱት» የሚል አሳብ ስለተሰረጸበትና ሕሊናው እንደ መሳት ስላለ ቶሎ ብሎ ተቀመጠ፡፡ እንደተቀመጠ ዣቬርን በዓይኑ ፈለገው ፤ አላገኘውም፡፡ ሕግ አስከባሪው መንገድ ላይ ስለተቀመጠ ምስክሮችን ሊያያቸው አልቻለም:: ክፍሉም ቢሆን በመጠኑ ጨለምለም
ያለ እንጂ ቦግ ብሉ የበራ ብርሃን አልነበረውም::

ክርክሩ የፈጀው ወደ ሦስት ሰዓት ገደማ ሲሆን ተከሳሹ ኣንደበተ
ርቱዕ ስልነበሩ የተከሰሱበትን ይካዱ እንጂ በሚገባ አላስረዱም:: እንዲያውም
ብዙውን ጊዜ ጣራ ጣራውን ነበር የሚያዩት:: ሲያዩዋቸው ቂላቂልና
ጅላጅል ቢጤ ይመስላሉ፡፡ ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው በእኚህ ሰው ዝምታ የተነሣ ሰው ሁሉ የጠበቀው ከባድ ቅጣት ነው።

ሕግ አስከባሪው የሚከተለውን ተናገረ::

«ተከሳሹ በቅድሚያ ክስ የቀረበባቸው በፍራፍሬ ስርቆት ወንጀል ነበር፡፡ ክሱ ሲመሠረት የቀረበው ማስረጃ 'የሠረቁት ፍሬ ከእነቅጠሉ በእጃቸው ላይ ተገኝቷል' የሚል ነበር፡፡ ሆኖም ይህ ብቻ እንደ ማስረጃ
ተቆጥሮ ለመስረቃቸው ማረጋገጫ ሊሆን አይችልም:: ተከሳሹ ከየት እንዳገኙት ሲጠየቁ ከመሬት ነው ያነሳሁት' ብለዋል፡፡ እርግጥም የፍራፍሬውን
ዛፍ ሌባ ቀጥፎ መንገድ ሊጥለው ይችላል፡፡ ስለዚህ ፍሬዎችን የያዘ
ቅርንጫፍ በመስበር የሰረቁት ሻምፕማትዩ ናቸው ለማለት ያስቸግራል።
ይህም በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ሊከሰሱ አይችሉም፡፡ ነገር ግን ከእስር ቤት ያመለጠ ወንጀለኛ ለመሆናቸው በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡ ምንም እንኳን
ዣን ቫልዣ ለመሆናቸው ምስክሮች ቢያረጋግጡም ተከሳሹ እስከመጨረሻው ክደዋል፡፡ ክህደቱን ትተው የፍርድ ቤቱን አስተያየት ቢጠይቁ የሚሻላቸው
ለመሆኑ ቢገለጽላቸውም አሻፈረኝ ብለዋል፡፡ በተከሳሹ አመለካከት ስለካዱ ከቅጣት የሚያመልጡ መስሎአቸው ይሆናል፡፡ በዚህ በኩል ተሳስተዋል፡፡ሆኖም ይህ ከእውቀት ማነስ እንጂ ሆን ብሎ የተደረገ ሊሆን አይችልም፡፡
ተከሳሹ በእርግጥ ንቃት ይጉድላቸዋል፡፡ ይህም የሆነው ምናልባት ለረጅም ጊዜ እስር ቤት ቆይተው በመሰቃየታቸው ከዚያም በኋላ ብዙ ስለተንከራተቱ
ሊሆን ይችላል፡፡ ወይም ደግሞ በሌላም፣ በሌላም ምክንያት ሊሆን ይችላል።ሆነም ቀረም የእርሳቸው አነጋገር አለማወቅ ወይም ችሎታ ማነስ ከሚሰጠው
ብያኔ ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር አይገባም:: ነገር ግን ተከሳሹ ዣን ቫልዣ እንደሆነና የቅጣት ዘመናቸውን ሳይጨርሱ አምልጠው ለመጥፋታቸው
ጥርጥር የለውም:: ስለዚህ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በወንጀለኛ
መቅጫ አንቀጽ መሠረት ተገቢውን ቅጣት ይቀበላሉ፡፡»

ሕግ አስከባሪው ዳኞች ስለሰጡት አስተያየትና ስለፈጸሙት ጥልቅ
ምርምር በቅድሚያ ምስጋናውን አቅርቦአል፡፡ ተከሳሹን ግን የዳኞቹን ትንተና መሠረት በማድረግ በጣም ነቅፎዋቸዋል፡፡ ተከሳሽ ዣን ቫልዣ እንደሆነ
ስለመረጋገጡ ሲያስረዳ «ዝም ማለታቸው ነገሩን አምነው እንደተቀበሉ ያሳያል» አለ፡፡

«ቀደም ሲል ግን ክደው ነበር:: ለመሆኑ ዣን ቫልዣ ማነው? ዣን ቫልዣ የተተፋ፣ አገር የጠላውና ሌላም ሌላም ሰው ነው፡፡»
ሕግ አስከባሪው ይህን ሲናገር ከዚያ የነበረ ሰው ሰውነት ሁሉ
ስቅጥጥ አለ፡፡ «ሻምፕማንቲዩ ማለት ዣን ቫልዣ ነው» ተብሎ ክስ
ሲመሠረት «ዦርናል ደ. ለ ፕሪፊትየር የተባለ ጋዜጣ ዣን ቫልዣ ማን እንደሆነ ሲያስረዳ «ዣን ቫልዣ ማለት ወሮበላ፣ ለማኝ፣ ቀጣፊ፣ መተዳዳሪያ
የሌለው አውደልዳይ፣ ሕይወቱን ወንጀል በመሥራት የሚመራ እንዲሁም ሌላም ሌላም ቅጽል ሊሰጠው የሚገባ ነው» ብሎ እንደጻፈ ተናገረ፡፡

«ይህ ሰው ፍራፍሬ ሠርቆ ቢያዝም አድራጐቱን ክዷል፡፡ እንዲሁም ከእስር ቤት ለማምለጡም ከሕግ ፊት ክዷል፡፡ የሚገርመው የገዛ ስሙን
እንኳን የካደ ሰው ነው:: ምን ያልካደው ነገር አለ! ሕልውናውን ጨምሮ ነው የካደው ለማለት ይቻላል፡፡ ነገር ግን እርሱ ሽንጡን ገትሮ ቢክድም አራት ምስክሮች መስክረውበታል: የተከበሩትና ውሽት የማያውቁት የፖሊስ
አዛዥ ዣቬር እንኳን በእርሱ ላይ መስክረዋል፡፡ እስር ቤት ውስጥ ከተከሳሹ ጋር አብረው ታስረው ከነበሩት ሰዎች መካከል ሦስት እስረኞችም መስክረውበታል፡፡ እነዚህ ምስክሮች ከመሰከሩበት በኋላ እንኳን ወንጀሉን አምኖ ይቅርታ አልጠየቀም:: ስለዚህ ማኅበራዊ ኑሮን ሊያፋልስ ታጥቆ
የተነሣ ወንጀለኛ ስለሆነ ቅጣቱ ሊቀልለት አይገባም፡፡»

ሕግ አስከባሪው ይህን ማብራሪያ ሲሰጥ ካህኑ ተከሳሽ አፋቸውን
ከፍተው በመገረምና በመደነቅ አዳመጠ፡፡ ሕግ አስከባሪው አንደበተ ርቱዕ በመሆኑ ቢያደንቁትም በማያውቁት ነገር እንደዚያ ስለወረደባቸው ከልብ
ረገሙት:: ግራ ቀኙን ከቃኙ በኋላ ተከሳሹ ራሳቸውን ነቀነቁ፡፡
ሕግ አስከባሪው ትችቱን በመቀጠል «ማንም ሰው ወንጀል ሊሠራ ወይም ውሸት ሊናገር ይችላል፡፡ ግን ከሕግ ሊያመልጥ አይችልም፡፡ ይህ ሰው ግን ወንጀል ከመፈጸም አልፎ ከሕግ ለማምለጥ ሞክሮአል፡፡ ይህም
ከባድ ወንጀል በመሆኑ በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ አሳብ ኣቀርባለሁ::»

«ስለተሰጠው አስተያየት የምትሰጠው መልስ አለ?» ሲሉ ዳኛው ተከሳሹን ጠየቁዋቸው:: ቆባቸውን ያፍተለትሉ የነበሩት ተከሳሽ ምንም ነገር እንዳልሰማ ዝም አሉ::

ዳኛው ጥያቄውን ደገመላቸው::
አሁን ግን ጥያቄውን ስለሰሙ ዳኛው ምን ማለት እንደፈለጉ ገባቸው::ከእንቅልፍ እንደነቃ ሰው ከወዲያ ወዲህ ተመለከቱ፡፡ ዳኞቹን፣ ሕግ አስከባሪውን፣ ጠበቆቹንና ተመልካቹን ሕዝብ አፍጥጠው ካዩ በኋላ ከፊት
ለፊት የነበረውን መከለያ ብረት አጥብቀው ይዘው በድንገት በከፍተኛ ድምፅ መናገር ጀመሩ፡፡ ቃላት ተሽቀዳድመው «እኔ ልቅደም፧ የለም እኔ ልቅደም» ያልዋቸው ይመስል እየተቻኮሉ በጣም በፍጥነት ተናገሩ፡፡
👍194
#ገረገራ


#ክፍል_አስራ_አራት


#በታደለ_አያሌው


....“ሃያ ስምጉት ሳምንት: ደህና። መቼም ዉሃ እስከሚበቃ ጠጥተሻል አይደለም?” አለችኝ፣ ኮስተር ብላ በአንዴ ከጓደኛነት ወደ ሐኪምምነት እየተሻገረች።.


"አዎ፤ ሽንቴን ለመቋጠር ስቁነጠነጥ አታዪኝም?”

“ደምሽንስ እየተከታተልሽዉ ነዉ፤ ጥሩ ነዉ?”

“እዉነቱን ለመናገ Check አድርጌዉ አላዉቅም ወሰድ መለስ ሲያደርገኝ ሰንብቼ ወደ ቀልቤ የተመለስሁት ገና ዛሬ ነዉ
አልገርምሽም? ቅድም ስንገባ ራሱ ምድር ቤት መለካት እችል ነበር።

ደርሼ ልምጣ እንዴ አሁንም?”

“አይ አይ፤ ኧረ እዚሁ እናየዋለ”
እጅጌዬን ሰበሰብሁና ጠረጴዛዉ ጠርዝ ላይ አስደግፌ ዘረጋሁላት። የደም
ግፊት መለኪያዉን አምጥታ አሰረችልኝ፡

“oK. Nice, right? 128/74 ይላል። ጥሩ ነዉ ያለሽዉ። ሌላ የተለየ
ያጋጠመሽ ነገር የለም አይደል?”

ለመናገር ዳድቼ፣ እንደ መሳቀቅ ብዬ ቀረሁባት።

“ምንድነዉ እሱ፤ አለ እንዴ? "

“አልፎ እልፎ፣ ቀለል ያለ ደም ይፈሰኛል” በዚያ ላይ ቀደም ብሎ ይሰማኝ
የነበረዉ የፅንሱ እቅስቃሴ፣ አሁን እየተሰማኝ አይደለም”

"ምን'? ታዲያ መምጣት አልነበረብሽም? የተለየ ነገር ከገጠመሽ እንድትመጪ ተስማምተን አልነበረ?”

ልክ መሆኗን ስላወቅሁ፣ ምላሽ የሚሆን አላገኘሁላትም። ዝም ብዬ
አቀርቅሬ መሬት መሬቱን አየሁ፡

“እሺ መቼ ነዉ የጀመረሽ?”

“ምኑ?”

“ደም መፍሰሱ”

“እ፤ ደም መፍሰሱ እኳን ትናንት ነዉ የጀመረኝ ገና የእሷ እንቅስቃሴ ግን
ከተሰማኝ ሰንብቷል: አንድ ሳምት አያልፍም ብለሽ ነዉ?”

አስከትላ ማንኛዉም ለእርግዝና ክትትል የመጣ ታካሚ የሚጠየቀዉን ሁሉ ጠየቀችኝ: መቼስ ከሐኪም እና ከንስሐ አባት የሚደበቅ የለም ይባል የለ? ስለ ምግብ፣ ስሜት፣ የአካል እንቅስቃሴ፣ መንፈሳዊ ብርታት እና ስለመሳሰሉት ሁኔታዎቼ ሁሉ እንደ አጠያየቋ በግልጽነት እዉነት ዉነቱን ብቻ መለስሁላት የሁሉም መልስ ግን ያዉ ነዉ በአጭሩ፣
የትኛዎቹም ላይ ግድ የለሽ እንደ ነበርሁ አመንሁላት፡ አሁን እንደ ጓደኛም እንደ ሐኪምም ብትቆጣኝ እንደሚያምርባት ስለማዉቅ ራሴን ለዚያ አመቻችቻለሁ

“ዉብዬ፣ እኔ አንቺን እንዲህ አድርጊ ወይ አታድርጊ አልልሽም" ራስሽ
ታዉቂዋለሽ” ብላ ወደ በሩ እንደ መራመድ ካለች በኋላ፣ በሩን በኃይል ቦርቀቅ አድርጋ ከፍታ አፈጠጠችብኝ

ተከትያት ልነሳ በእጄ እሸቴ ጭን ላይ ስመረኮዝ፣ ስልኩን ሰረቅ አድርጎ አሳየኝ አሁኑኑ የሚል መልእክት ከባልቻ ተልኮለት ኖሮ፣ ምን ይሻላል የሚል ፊቱን አስነበበኝ። ቃል ሳናወጣ አዉርተን፣ አሁኑኑ ወደ ሲራክ ፯ መሄድ እንዳለበት ተማከርን ተግባባን፡

ብድግ አለ

“ወዴት ነዉ እሸቴ? እዚህ እኮ ልትጠብቀን ትችላለህ” አለችዉ፣ በቢሮ መቆየቱ አሳቅቶት የተነሳ መስሏት።

“አይ አይ፤ መሄድ አለብኝ: አጉል አድርጌ የተዉኩት ሥራ ነበረብኝ
አሁኑኑ መሄድ አለብኝ”

“እንዴ! ዉቤን ለብቻዋ ጥለሃት?”

“ምን ታደርጊዋለሽ፤ የእኀጀራ ጉዳይ…”
“ይኼን ያህል? የት ነዉ ግን የምትሠራዉ?”

“እ” ተንተባተበ፡፡ እንዲያዉም እንዲያ ነሽ አሉ ተረተኞች? እንኳን እሱ
እኔም ከእሷ ያልጠበቅሁት ጥያቄ ስለነበር፣ ክዉ ብያለሁ።

“የየየየየየ መንግሥት መሥሪያ ቤት ነዉ የምሠራዉ” አለ ለፊቷ መመለሻ፣ ወዳፉ እንደ መጣለት፡ ጎበዝ አልሁት በምልክት

“ተዉ እንጂ፣ የት?”

“..እ..…ንንንን..ግድ
የኢትዮጵያ ንግድ ባክ”

“አሪፍ! ባንከሮችማ መናፈሻችሁ ሳይቀር የብር ጫካ ነዉ አላሉም?''

“ሳቅንላት፡ ተሳሳቅን፡ አጋጣሚዋን በመጠቀም፣ እሸቴ በሳቅ እያታለለ
ሹልክ ብሎ ወጣ፡ በቅጡ እንኳን አልተሰናበታትም

"አንቺስ ዉቤ?

“እ..ኔ ምን?” አልኋት፣ የእሸቴን መንተባተብ እኔም እየደገምሁት
የት እንደምትሠሪ መቼ ነገርሽኝ''
“አይ እኔ እንኳ ን ለጊዜዉ ሥራ የለኝም። ምናልባት አንቺ በሆስፒታላችሁ
ታስቀጥሪኝ እደሆነ እንጂ፣ የቤት እመቤት ነኝ”

"አግኝተነሽ ነዉ? በይ ነይ ተነሺ ይልቅ አልትራሳዉድ ክፍል ደርሰን እንምጣ” አለችኝ፣ እንድነሳ በግማሽ ዓይኗ እየደገፈችኝ።

"ውቤ! ሰዓቱን ግን ልብ ብለሽዋል? ባለሙያዉ አልትራሳዉንድ ክፍሉን
ጠርቅሞት ይኼድልሽና በብላሽ መመለስሽ ነዉ: አጅሬዉ ጠዋት ሲገባ
ማርፈዱን እንጂ፣ ከመዉጫ ሰዓቱ እንኳን ደቂቃ ማሳለፉንም አያዉቅበት። ቶሎ በይ፣ እንድረስበት”

እኔ ሆኜባት ነዉ እንጂ፣ አብራ የመዉጣት የመዉረድ ግዴታዋ ሆኖ አይደለም ለየክፍሉ የየራሱ ባለሙያ ስላለዉ፣ ሂጅ ዉጤቱን አሰርተሽ አምጪ ማለት ትችላለች እኔ ግን እኔ ሆንሁባት
እንዳለችዉም፣ ስንደርስ ባለሙያዉ ሊወጣ በር በሩን እያየ ነበር ልክ
ሲያየን ብልጭ አለበት፡ በተለይ እሷን ከፍ ዝቅ አድርጎ ጮኸባት፡ ባለፈዉ በእኔ ጉዳይ ተዋክባ እሷ እሱን በዚሁ ድምፀት ስታናግረዉ ሰማኋት ያን ያህል አልደነገጥሁም፡ ብድሩን ነዉ የመለሰባት፡

“ምን ነካሽ ዶክተር? መዉጫ ሰዓቴን ጠብቀሽ መምጣት ምን የሚሉት
ነገር ፍለጋ ነዉ? ''

“ግድየለም፣ ያን ያህል ጊዜ አልፈጅብህም” አለችዉ፣ ልክ ትርፍ ዉለታ እንደምትጠይቀዉ ሁሉ በመለማመጥ

""ቤቴ የት ሀገር እንደሆነ እያወቅሽ?”

“ነገርኩህ እኮ፤ከመዉጫ ሰዓትህ አንዲት ደቂቃ አላሳልፍብህም ካሳለፍሁብህ ደግሞ ታቋርጠኛለህ። ቶሎ በል ይልቅ አብራዉ አጠፋፍተኸዋል መሰል ደግሞ”

እኔም ጊዜ ለመቆጠብ፣ እስከምታዘዝ ድረስ ሳልጠብቅ ቀልጠፍ ብዬ
አልጋዉ ላይ ለምርመራ ተመቻችቼ የእንግላል ሆንሁላቸዉ
እየተነጫነጨም ቢሆን የፈጀዉን ጊዜ ፈጅቶ፣ ሁሉንም ነገር ዝግጁ አደረገዉ
ከዶክተር ሸዊት የወደድሁላት ጥሩ ጸባይ፣ ያለ ሙያዋ ጥልቅ አትልም ዛሬም ሆነ ባለፈዉ እንዳስተዋልኋት ከሆነ፣ ጣልቃ መግባት ቢያስፈልጋት እንኳን፣ ቢያንስ ቢያንስ ፈቃድ ትጠይቃለች፡ ዛሬም
እንዲህ ባለቀ ሰዓት ዉስጥ ሆና፣ ባለሙያዉን ጠበቀችዉ፡ ለነገሩ
ሙያዉም ያንን አይፈቅድም፡፡ በተለይ አልትራሳዉንድ በባሕሪዉ፣ ለማዳ እጅ ይፈልጋል ዉጤቱን ትክክልም ስሕተትም የሚያመጣዉ ከመሣሪያዉ ዘመናዊነት ይልቅ የባለሙያዉ (የራዲዮሎጂስቱ) ልምድ ያለው እጅ መሆኑ ነው ይባላል።

“እያየሽዉ ነዉ ዶክተ?” አለ ራዲዮሎጂስቱ፣ መከሰቻዉ ላይ ዓይኑን
ሰክቶ ልክ ያልሆነ ነገር እንዳየ አዉቂያለሁ

“እ፤ እስኪ እስኪ” አለች እሷም፣ ትንፋሿ እየተቆራረጠ፡ ባለሙያዉን
ገፈተረችዉና ራሷ ገባችበት፡ “NO! አይደረግም!” ብላ ጮኸች።
ወዲያዉ ደግሞ በፊቴ መደንገጧ ይበልጥ አስደነገጣት፡ ጀርባዋን ሰጥታኝ
ያልደነገጠች ለመምሰል ብትሞክርም፣ እንደገና ከድንጋጤዋ ለመመለስ
ብትሞክርም፣ የትኛዉም አልሆነላትም

“በቃ፣ ጨርሻለሁ። መዘጋጋት ትችላለህ” አለችዉ ግራ ቀኝ ስትንቆራራጠጥ ቆይታ፣ ከአልጋዉ ላይ ደግፋ እያስነሳችኝ፡፡
“ኧረ ችግር የለም፣ የማግዝሽ ነገር ካለ እንዲያዉም ያን ያህል የሚ ያስቸኩል ጉዳይ የለኝም” አላት፣ እንደዚያ እሳት ለብሶ የነበረዉ ሰዉዬ በአንድ ጊዜ ዉሃ እየሆነ በሐዘኔታ አየኝ፡

“ዉብዬ” አለችኝ፣ የተከሰተዉን እንድመለከተዉ በአገጯ እየጠቆመችኝ
ግብኔን ወደ ጠቆመችኝ መከሰቻ አዞርሁላት። “ያዉ፣ ባለፈዉ እንደ ጠበቅነዉ፤ እንደፈራነዉ ሳይሆን አልቀረም በእርግጥ ያን ጊዜ ምልክቶቹን ባየን ጊዜ፣መልሶ ይቀንሳል የሚል ጭላንጭ ተስፋ ነበረኝ በበኩሌ።ሆኖም ፅንሱን እንደምታይዉ
ባልተመጣጠነ የጭንቅላት የፈሳሽ መጠን የተነሳ፣ ጭንቅላቱ ከመጠን በላይ አድጓል። ይኼ እንዳለ ሆኖ፣ መጀመሪያም ምልክቱን ያየነዉ የጀርባዋ አጥት ክፍተት ደግሞ እየሰፋ መጥቷል”
ትንሽ ተያየን፡፡ ከእሷም በሆዴ ካለችዋም ጋር አጭር ቆይታ አደረግሁ
👍34
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አስራ_አራት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ

....ምናልባትም ቅዳሜ ወይም እሁድ መቼ እንደሆነ እየፀፀታት ይሆናል የቀን መቁጠሪያው በትክክል በቀይ የኤክስ ምልክቶች ተሞልቷል የታሰርንባቸው ቀናት፣ ሙቀቱ፣ ብቸኝነቱ፣ የልብ መሰቀሉ
የተጎዳንባቸው ቀናት ላይ በሙሉ ምልክት አድርገንባቸዋል.
ወንበር ላይ ተቀምጣ የሚያምሩ እግሮቿን አነባበረችና ራሷን ለማቀዝቀዝ ልታራግብበት መፅሄት አንሳች ደስ የሚል የፍቅር ፈገግታ ወደኔ አቅጣጫ እያሳየች “ስላስጠበቅኳችሁ ይቅርታ። ጠዋት መጥቼ ላያችሁ ነበር። ግን
አባቴ ሙሉ ትኩረቴን ፈልጎ ስለነበር ከሰዓት ልጎበኛችሁ እቅድ አወጣሁ:: ከዚያ የሄድኩበትን ጉዳይ አሳጥሬ ከእራት በፊት ከልጆቼ ጋር ጊዜ ለማሳለፍ
እንድችል ብዬ ስሮጥ መጣሁ” አለች: “ሀይቁ ላይ እየቀዘፍኩ ነበር።ወንድሞቼ የዘጠኝ አመት ልጅ ሳለሁ እንዴት እንደምቀዝፍ አስተምረውኝ ነበር ከዚያ አባታችሁ እዚህ ሊኖር ሲመጣ እንዴት መቅዘፍ እንዳለበት
አስተማርኩት ሀይቁ ላይ ብዙ ጊዜ እናሳልፍ ነበር፡ መቅዘፍ ልክ እንደ
መብረር ነው... አስደናቂ ደስታ ይሰጣል” የእሷ ደስታ የእኛን ደስታ እንደሰረቀ አስተውላ መናገሯን አቆመች።

“መቅዘፍ?” ጮህኩ። “ለምን ምድር ቤት ሄደሽ ለወንድ አያትየው ስለኛ አልነገርሽውም? እዚህ ውስጥ ቆልፈሽ የምታስቀምጪን እስከ መቼ ነው?
ለዘለዓለም?”

ሰማያዊ አይኖቿ ክፍሉ ውስጥ ተንከራተቱ ከወንበሩ ላይ ልትነሳ ከጀለች:ክሪስ ጣሪያው ስር ካለው ክፍል መፅሀፍቶች ተሸክሞ መጣ።

“ካቲ እናትሽ ላይ አትጩሂባት!” አለኝ፡ “ሰላም እማዬ፣ በጣም አምሮብሻል፡'የያዛቸውን መፃህፍት ጠረጴዛ ላይ አደረገና አቀፋት በእናቴ ብቻ ሳይሆን በወንድሜም እንደተጎዳሁ ተሰማኝ፡ ምንም ሳናደርግ በጋው ሊያልቅ ነው።
ሽርሽር ወይም ዋና ቦታ አልሄድንም ወይም ጫካ ውስጥ አልተንሽራሸርንም ጀልባ አላየንም ወይም የዋና ልብስ ለብሰን ጓሮ ያለው የመዋኛ ገንዳ ውስጥ
እንኳን አልተንቦራጨቅንም

“እማዬ!” ጮህኩ፡ በእግሮቼ ቆሜ ለነፃነታችን ለመታገል እየተዘጋጀሁ
“ለአባትሽ ስለኛ ለመንገር ጊዜው ደርሷል ብዬ አስባለሁ! እዚህ ክፍል ውስጥ መኖርና ጣሪያው ስር ያለው ቦታ ላይ መጫወት ሰልችቶኛል! መንትዮቹ |
ንፁህ አየርና የፀሀይ ብርሀን እንዲያገኙ እፈልጋለሁ። እኔም መውጣት እፈልጋለሁ ወንድ አያታችን አባታችንን በማግባትሽ ይቅር ካለሽ ለምን እኛን ሊቀበለን አይችልም? እኛን የስጋ ዘመዶቹ እንደሆንን የማይቆጥረንና
የሚያፍርብን ያን ያህል አስቀያሚ አስቸጋሪ ወይም ደደብ ነን እንዴ?"

ክሪስን ገፋ አድርጋ የተነሳችበት ወንበር ላይ አንገቷን አቀርቅራ ፊቷን በእጆቿ ቀብራ ተቀመጠች: በደመነፍስ ከዚህ በፊት ደብቃን የነበረን የሆነ እውነት ልታወጣው እንደሆነ ገመትኩ። ኮሪና ኬሪን ጠርቼ ጎንና ጎኔ አስቀመጥኳቸው:
ክንዶቼን እያንዳንዳቸው ላይ አደረግኩ፡ ክሪስ ከእናታችን ጎን ይሆናል ብዬ ሳስብ ወደኛ መጥቶ አልጋው ላይ ከኮሪ አጠገብ ተቀመጠ፡ እንደገና እንደ በፊቱ ከባድ ንፋስ ሊወስደን ያለ፣ በልብስ ማስጫ ገመድ ላይ የተቀመጥን ትናንሽ ወፎች መስለን ነበር።

"ካቲ፣ ክሪስቶፈር…” ስትል ጀመረች:: አሁንም አንገቷን እንዳቀረቀረች ነው:
“ለእናንተ ሙሉ በሙሉ እውነተኛ አልነበርኩም” አለች ልክ ይህን እንዳልገመትኩ ሁሉ፡-

“ዛሬ ለእራት ከእኛ ጋር አትቆይም?” ስል ጠየቅኳት በሆነ ምክንያት ሁሉንም እውነቶች አለማንሳት ፈልጌያለሁ።

“ስለጠየቅሽኝ አመሰግናለሁ መቆየት እፈልግ ነበር ግን ለዚህ ምሽት ሌሎች እቅዶች አሉኝ" ይህ የእኛ ቀን ነው እስኪጨልም ከሷ ጋር የምንሆንበት ጊዜ ትናንትና ከእኛ ጋር የቆየችው ለግማሽ ሰዓት ብቻ ነበር።

“ደብዳቤው” አጉረመረመችና አንገቷን ቀና አደረገች: “ግላድስተን እያለን እናቴ
የፃፈችው ደብዳቤ ላይ እዚህ እንድንኖር ጋብዞናል ግን ደብዳቤው መጨረሻ ላይ አባቴ አጭር ማስታወሻ ፅፎ እንደነበር አልነገርኳችሁም:"

“አዎ” እኔም ገፋፋኋት፡ “መንገር ያለብሽን ንገሪን እንቀበለዋለን” አልኳት።

እናታችን ራሷን የምትቆጣጠር ሴት ናት᎓ ነገር ግን መቆጣጠር የማትችለው አንድ ነገር አለ እሱም እጆቿን ነው: ሁልጊዜም እጆቿ ስሜቶቿን ይከዳሉ።እጆቿ ረፍት የለሽና ልክ እንደሚታጠብ ሰው ይንቀሳቀሳሉ።

“ሴት አያታችሁ ደብዳቤውን ፅፋ ፈረመችው፣ መጨረሻው ላይ ደግሞ አባቴ የራሱን ማስታወሻ ጨመረበት…" አመነታች: አይኖቿን ለአንድ ወይም ለሁለት ሰከንድ ጨፈነች: ከዚያ ከፈተቻቸውና እንደገና አየች። “ወንድ
አያታችሁ ሲፅፍ አባታችሁ በመሞቱ ደስ እንዳለውና ክፉ ሰዎች ሁልጊዜም የሚገባቸውን እንደሚያገኙ፣ ከእኔ ጋብቻ ብቸኛው መልካም ነገር የሰይጣን
ዘሮች አለመፈጠራቸው እንደሆነ ተናግሮ ነበር፡

በፊት ቢሆን “ምንድነው?” ብዬ እጠይቅ ነበር፡ አሁን ግን አውቃለሁ የሰይጣን ዘሮች ማለት ከሰይጣን የተፈለፈሉ ከሚለው ጋር አንድ ነው የሆነ ክፉ፣ የተበላሸ፣ መጥፎ ሆኖ የተወለደ።

ክንዶቼን መንትዮቹ ላይ እንዳደረግኩ አልጋው ላይ ተቀምጬ ወደ ክሪስ
ተመለስኩ፡ ክሪስ ቁርጥ አባታችንን ይመስላል: አባታችን ነጭ የቴኒስ ልብስ የሚለብስ፣ ረጅም፣ ኩሩ፣ ባለ ወርቃማ ፀጉርና ነሀስ የመሰለ ቆዳ ያለው ነበር:
ክፉ የሚባለው ደግሞ ጥቁር፣ ጠማማ፣ ያደፈጠና ትንሽ እንጂ ዋሽተው የማያውቁ ንፁህ ሰማይ የመሰሉ ሰማያዊ አይኖች ያሉትና የሚያምር ፈገግታ ያለው ረጅም ሰው አይደለም።

“እናቴ እናንተን ስለመደበቅ ያላትን እቅድ አባቴ ባላነበበው ደብዳቤ ላይ አሰፈረች" አለችና አጠቃለለች ፊቷ ቀልቶ ነበር።

“አባታችን የወንድሙን ልጅ በማግባቱ ምክንያት ብቻ ነው እንደ ክፉና ምግባረ ብልሹ የተቆጠረው?” ክሪስ ጠየቀ፡ “የሰራው ስህተት ያ ብቻ ነው?
“አዎ!” ብላ ጮኸች የምትወደው ልጇ ስለተረዳት ደስ ብሏታል። “አባታችሁ ህይወቱን ሙሉ አንድ ይቅር የማይባል ኃጢአት ሰርቷል እሱም ከእኔ ጋር በፍቅር መውደቁ ነው ህጉ በአጎትና በወንድም ልጅ መካከል ያለ ጋብቻን
ይከለክላል፤ ዝምድናቸው በግማሽ ቢሆንም እንኳን። እባካችሁ አትርገሙን
እንዴት እንደነበረ ነግሬያችኋለሁ ከሁላችንም አባታችሁ በጣም ምርጥ ነበር” ልታለቅስ ደረሰች በአይኖቿ እየለመነችን ነበር ቀጥሎ የሚመጣውን
አውቄያለሁ:

“ክፋት ምንድነው? ምግባረ ብልሹነት ምንድነው? ሁሉም ያለው በተመልካች አይን ውስጥ ነው:” በእሷ መንገድ እንድናየው በጥድፊያ ቀጠለች። “ወንድ
አያታችሁ መልአክ ላይ ሳይቀር ስህተት ያገኛል። እሱ በሁሉም የቤተሰቡ አባላት ላይ ፍፁምነት የሚጠብቅ አይነት ሰው ነው እሱ ግን ከፍፁምነት እጅግ የራቀ ነው: ነገር ግን ያንን ልትነግረው ብትሞክር በጥፊ ያጮልሀል
ክሪስቶፈር፣ የሆነ ጊዜ ስላንተ ልነግረው እችላለሁ ብዬ አስባለሁ። እንዴት ጎበዝ ተማሪ እንደሆንክና ሁልጊዜ ትልቅ ማርክ የምታገኝ እንደሆንክ ካቲን ሲያይና ትልቅ የዳንስ ተሰጥኦዋን ሲያውቅ… እነዚህ ሁለት ነገሮች
ብቻ ገና መንትዮቹን ሳያይ እንዲለዝብ ያደርጉታል። እንደማስበውና ተስፋ
እንደማደርገው በቀላሉ ይሸነፍልንና ጋብቻችን ትክክል እንዳልሆነ ማመኑ ስህተት እንደነበረ ይረዳል”
👍314