አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....ታክሲው ውስጥ የሚጮኸው ሙዚቃ ጭንቅላቱን በጠበጠው፡፡ማታ እንቅልፍ አልወስድህ ብሎት ሲጨነቅ ነበር ያደረው::

“ምንድነው የሆንከው? ለምን አትነግረኝም?” አለች ዘውዲቱ
ከሆቴል ገዝታ ካመጣችው ምግብ እያጎረሰችው፡፡ “ምስኪን አሁንስ ሚስትህ
ናፈቀችሁ መሰለኝ::

ያጎረሰችውን እያላመጠ ዝም አላት:: ወሬ አላሰኘውም:: ምግቡም እንዳያስከፋት ብሎ ነው እንጅ ቢቀርበት በወደደ፡፡
እራት በልተው ተጣጥበው መብራቱን አጥፍተው አልጋ ላይ ከወጡ በኋላ ናትናኤል በጀርባው እንደተንጋለለ አያኖቹን ጣሪያው ላይ ተክሎ ቀረ፡፡

ምን ሆና ይሆን? እንዴት ሁለት ቀን ሙሉ ስራ ሳትገባ ትቀራለች በጤናዋ ባትሆን ነው እንጅ:: ደግሞ ምህረት እቤቷ: ደወዬ
የሚያነሳ አጣሁ ማለቷ ምን ማለቷ ነው? ቤቷን ዘግታ የት ትሄዳለች? ምናልባት አሟት ወላጆቿጋ ሄዳ ይሆን እንዴ? የወላጆቿን ቤት ደግሞ አያውቀውም ! ጉለሌ እንደሆኑ ነግራዋለች፡፡ ግን በደፈናው ጉለሌ ተብሎ አይኬድ፡፡ ቤቷ ሄዶ ይሞክር ይሆን?

ሌሊቱን ሲጨነቅ አደረ፡፡ አሁን ደግሞ ታክሲው ውስጥ ያለው ሙዚቃ አይሉት ጩኽት

“ሲጋራ ፋብሪካ ነው ያሉኝ?” አለው ባለታክሲው፡፡

“እ? አዎ የኔ ልጅ፡፡ ከዚህ ይበቃኛል፡፡” ናትናኤል የታክሲውን በር ከፍቶ ወረደ፡፡

“አባ ገንዘበስ?!” ባለታክሲው የመኪናውን ጥሩንባ ተጭኖ ጮኹ፡፡

“ይቅርታ! ይቅርታ!” አለ ናትናኤል ከሄደበት ተመልሶ ከጋቢው ስር
ከደረት ኪሱ ገንብ እያወጣ “ይቅርታ የኔ ልጅ፡፡ ሃሳብ ገብቶኝ ተዘንግቶኝ
ነው::” ገንዘቡን ለባለታክሲው አቀበለው

ዘውዲቱ የገዛችላት ላስቲክ ቦት ጫማ መንገደኛ ቢያስመስለውም እላይ ከፈፉ እግሩን ከርክሮት ክፉኛ አቁስሎታል። በተራመደ ቁጥር የጫማው ክፈፍ ቁስሉን ሲነካበትና ሲፈትግበት ይለበልበዋል፡፡
ከመንገዱ ባሻገር የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ህንፃ ብቻውን ተገትሯል ... ሥራ ፈት፡፡ ናትናኤል ይህንን ፎቅ ሲመለከት ምንም ትርጉም አይሰጠውም በፎቁ ቅርፅ ውስጥ መልዕክት ካለ አንድ የሚል መሆን አለበት ቀጥ ያለ ፎቅ እንድ፡፡

ናትናኤል አይኖቹን ከፎቁ ላይ ነቅሎ ሃሳቡን አሰባሰሰ፡፡ ለጥያቄው መፍትሄ የሚያገኝለት ካልቨርትን ቢያገኝ ብቻ እንደሆነ ከተረዳ ቆይቷል፡፡
ካልቨርትን : እግኝቶ የአውሬውን ማንነት ይፋ እስካላወጣ ድረስ የተደበቀውንና የተሸሸገውን ምሥጢር እስካላዝረከረከው ድረስ አንድ ቀን ከአንዱ ጥግ ነው የሚደፉት፡፡አብርሃምን እንደደፉት፡፡

ይህ ከመሆኑ በፊት ካልቨርትን ማግኘት አለበት፡፡ ግን ካልቨርትን ለማግኘት ከየት ሀ ብሎ እንደሚጀምር እንቆቅልሽ ሆነበት::

መረጃ የውስኪ ጠርሙስ ሾፌር ቤላ
መጠጥ ቤት…ሴት ሞሳድ ኤም አይ
ስድስት…ካዛንቺስ ወዳጁ ቤት… የሴት ልብስ ለብሶ ተሰወረ::

ቁልፉ የግድ እዚህ ውስጥ መሆን አለበት መፍትሄው እዚህ ውስጥ ከሌለ ካልቨርትን ሊያገኘው አይችልም:: ምክንያቱም እሱ የሚያውቀው ይህን ብቻ ነው አብርሃም የነገረውን፡፡

ያለጥርጥር ካልቨርት እንዲሰወር የካዛንቺሷ ወዳጁ ረድታዋለች፡፡ በመጨረሻ የታየው ከእሷ ቤት ሲወጣ ነው፡፡ ምናልባት የት እንደሚገኝም
ታውቅ ይሆናል፡፡ በተቻለው መንገድ ሴትየዋን ማግኘት አለበት:: ካልቨርትን
ለረዳው እንደሚፈልግ ሊያሳምናት ይገባል፡፡ ትጠረጥረው ይሆናል፡፡ ግን
ሊያሳምናት ከቻለና ካልቨርት ያለበትን ቦታ ከነገረችው ድብብቆሹ አበቃ ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜ ያለጥርጥር አውሬውን መረቡ ውስጥ ይከተዋል፡፡

ካልቨርት የሚያውቀው ነገር እንደሌለስ? ማወቅ አለበት ምንም የማያውቅ ከሆነ ለምን ተሸሽገ? ያውቃል፡፡ ለሕይወቱ የሚያሰጋው ምሥጢር ይዟል፡፡ ያንን ምስጢር ማግኘት አለበት፡፡ ካልቨርትን ለማግኘት ደግሞ መጀመሪያ የካዛንቺሷን ሴት አግኝቶ ማሳመን፤ ማግባባት ማሽነፍ፡፡፡ እሷ ብቻ ነች ዕድሉ፡፡

ግን አውሬው ለምን ሴትየዋን አቆያት? ያለጥርጥር ወደ ካልቨርት
የምትመሪ መንገድ ነች:: ይህንን ደግሞ አውሬው ሳያውቀው የሚቀር አያደለም:: ታዲያ ለምን አሰነበታት? ለምን አስገድዶም በሆን የካልቨርትን
እድራሻ አላወጣጣትም? ወያም ለማንኛውም ወገን ምሥጢሩን የካልቨርትን አድራሻ እንዳትጠቁም ለምን እንደ አብርሃም አሳስወገዳትም?

ምናልባት ሴትየዋ ራሷ ወጥመድ እንደሆነችስ? የካልቨርትን አድራሻ የሚያነፈንፍ፡ አይጥ ወደ ካዛንቺስ እንዲመጣና ከወጥመድ እንዲገባ
የተንጠለጠለች የሥጋ ቁራጭ እንደሆነችስ? ካዛንቺስ ከመድረሱ እንገቱን ቆርጠው ቢጥሉትስ?'፡ ናትናኤል ሰጋ:ዠ ኣብርሃም ያለው ትዝ አለው

“… ሁለቱን የክትትል ሰዎች ባሰማራን በሶስተኛው ቀን አንደኛው ሰዋችን በስለት ታርዶ እዛው ካዛንቺስ ቱቦ ውስጥ ተጥሎ ተገኘ.…”

ህ! “እዛው ካዛንቺስ” ወጥመድ

ያለጥርጥር ካዛንቺስ ወጥመድ ተጠምዶለታል፡፡ ቢሆንም ምርጫ
የለውም፡፡ ወደ ካልቨርት ሊቀርብ የሚችለው የካዛንቺሏን ሴት ሲያገኝ ብቻ
ነው:: የግድ ካዛንቺስ መሄድ አለበት፡፡
'ካዛንቺስ፡፡ ካዛንቺስ ምኑጋ? ካዛንቺስ ስንት አውራ መንገዶች አሉ?… ካዛንቺስ ስንት መጠጥ ቤቶች አሉ? የትኛዋ ነች የካልቨርት ወዳጅ? “የፈጣሪ ያለህ!' የካዛንቺስ ስፋቱና የቀሚስ ለባሹ ብዛት ታየው::

ሌላ ጥያቄ! እንዴት ሊያገኛት ይችላል? ማን ሊመራው ይችላል? አብርሃም ምንድነው ያለው.…?
የቅብብሎሹን ሠንሠለት መስበር ነው
ካልቨርት የሰረቀውን መረጃ…በውስኪ ጠርሙሶች…በሾፌርነት ለማያገለግል ኢትዮጵያዊ ያቀብላል..ሹፌሩ ቤላ መጠጥ ቤት ላላት.…”

ሹፌሩ ሹፌሩ ሌላ መጠጥ ቤት ያላትን ሴት ያውቃታል ማለት ነው፡፡ የካዛንቺሷንስ? ሊያውቃት ይችላል? ምናልባት ካልቨርት የሚቀርበው ከሆነ ሊያውቃት ያችላል፡፡ ያለው ምርጫ ሾፌሩ ነው:: ሾፌሩን አአግኝቶ የካዛንቺሷን ሴት እድራሻ እንዲሰጠው መጠየቅ::

ሾፌሩ የኛ ሰወ ነው በእሱ በኩል ነው
መረጃውን የምናገኘው...” ነበር ያለው
አብርሃም::
ሌላ ወጥመድ፡፡ ሾፌሩም አደገኛ ነው፡፡ ካዛንቺስ ያለችውን የካልቨርትን ወዳጅ ሆቴል ኣሳየኝ።” ሲለው መቼም መጠራጠሩ አይቀርም፡፡
“እሺ ና” ብሎ ገመድ አንገቱ ቢያስገባለትስ? መሬት ለመሬት እያንሻተተና እየጎተተ ቢያስይዘውስ? እርግጥ ያለው ምርጫ ወደ ካዛንቺሷ እመቤት የሚደርሰው ብቸኛ መንገድ የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ብቻ ነው:: ለይቶ የሚያውቀው አድራሻ የእርሱን ብቻ ነዋ! ቢሆንም ሰውየውን በአካል
መገናኘት የለበትም፡፡አንድ ዘዴ መፍጠር አለበት፡፡ ናትናኤል ለበርካታ ቀናቶች ሲያወጣ ሲያወርድ መልስ ሲሻለት የቆየው ጥያቄ ይህ ነበር፡፡መልሱን
አግኝቷል። አቅዶ ወጥኖ ጨርሷል፡፡ ትከሻው ላይ አላርፍልህ ያለውን ጋቢ
እያስተካከለ ከመንገድ ወዳለ ትንሽ ቁርስ ቤት ገባ፡፡

“የኔ ልጅ እባክሽ ስልክ ታስደውይኝ…እከፍላለሁ::ችግር አጋጥሞኝ ነው ልጅ ታማብኝ፡፡” አላቸው እናቱ የሚሆኑትን የቁርስ ቤቷን ባለቤት ጠጋ ብሎ። ያቀደውን ደረጃ በደረጃ ይፈጽም ጀመር፡፡

ሴትየዋ ስልክ ማስደወሉን ባይወዱትም ከቄስ ጋር! ከእግዚኣብሄር ሰው ጋር ክፉ መነጋገሩን አልፈለጉትም፡፡ ከባልኮኒው ስር አንድ ሰማያዊ ስልክ አውጥተው ቄሱ ፊት ቆለሉትና “ያው” ብለው ፊታቸውን አዙረው ሄዱ፡፡ · ደረታቸው ላይ የተቆለለው የጡት ተራራ የዘውዲቱን ጋራ
ያስንቃል፡፡

ናትናኤል ሴትየዋ ዞር እንዳሉለት የስልኩን መነጋገሪያ አንስቶ በመጀመሪያ ወደ ማዞሪያ ደውሎ የላይቤርያ ኤምባሲን የስልክ ቁጥር ከጠየቀና ካገኘ በኋላ ወደ ኤምባሲው ደወለ። በላይቤርያው ኤምባሲ ውስጥ ከአንድ በላይ ሾፌር ሊኖር ይችላል የትኛውን አቅርቡልኝ ሊል ነው? ብቻ ማናቸውም ቢሆኑ የካልቨርት
👍32🥰1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

......ብዙም ሳይቆይ አንድ ቀጭን አጭር ሰው መንገዱን ተሻግሮ ወደ ቢጫዋ ቁርስ ቤት ሲጣደፍ ተመለከተ፡፡ኮቱን ትከሻው ላይ እንጠልጥሎታል፡፡ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት ካለው የላይቤርያ ኤምባሲ እስከ ቁርስ ቤቷ ለመድረስ ብዙ ባያስኬድም ወደፊት ደፋ
ደፋ የሚለው ሰው ረዥም መንገድ የተጓዘ ይመስላል፡፡ ሰውየው ከቁርስ ቤቷ እንደደረስ ወደውስጥ ከመግባቱ በፊት ቆም ብሎ ዙሪያውን ተገላምጦ
ተመለከተ፡፡ ወዲያው ዘው ብሎ ወደ ውስጥ ገባ፡፡

ሰውየው ወደ ውስጥ ሲገባ ናትናኤል ፈጠን ብሎ ከጥግ ወዳለ
የህዝብ ስልክ አመራና አንብቦ በጭንቅላቱ የያዘውን የቢጫዋን ቁርስ ቤት ቁጥር ደወለ፡፡

“አ.ቤት::” አለ የሴት ወይዘሮ ድምፅ፡፡
ያ ክምር ጡታቸው መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት ናትናኤል፡፡

“እንደምን ዋሉ...ደህና ኖት?” ሴትየዋ መልስ ከመስጠታቸው በፊት አጣደፋቸው “ገብረየሱስ ነኝ..እንደምን ኖት?!” አለ እንደሚያውቃቸው ተዝናንቶ፡፡ “እባኮት ስዩም ጋር ቀጠሮ ነበረን እርሶ ቤት
ያገናኙኝ…ስዩም ይበሉልኝ…እቤትዎ ውስጥ ነው ያለው…ደህና ኖት ግን
እርስዎ..በሉ ስዩምን ያገናኙኝ..” በላይ ቀላይ አጣደፋቸው፡፡

“የማን ስዩምን? አሉ ሴትየዋ ፋታ ሲያገኙ፡፡

“እንዴ!.. ረሱን እንዴ? እቤትዎ በልተን ጠጥተን? አይ የርሶ ነገር! ይብሉ ስዩም ይበሉልኝ፡፡ አይ የርሶ ነገር! ደንበኞቾንም ይረሱ ጀመር?” አጣደፋቸው፡፡

“ኧረ ንሽቴ! የምን መርሳት አመጣህብኝ::!” አሉ ሴትየዋ ድፍረት
አሰባስበው:: “ደሞ እናንተን ደንበኞቼን ልርሳ? ሄ! ሄ! ሄ! ገና ሳላረጅ ምነው
ባክህ! ደህና ነህ ግን አንተ ጠፋህሳ?”
ሴትየዋ ሲጣሩ “ስዩም የሚባል! ስልክ?” ሲሉ በስልኩ ውስጥ ተሰማው፡፡ ነፍሱ መለስ አለችለት:: ስልኩን ጆሮው ላይ እንዳይጠራቅምበት ሰግቶ ነበር፡፡

“ሀሎ… ” አለው ያው ነፍናፋ ድምፅ፡፡
“ስዩም? ” ናትናኤል ቆፍጠን ባለ ድምፅ ጠየቀ፡፡
“ነኝ.የት…?”

“ዝም ብለህ አዳምጠኝ::ቁርስ ቤቷ ውስጥ ይጠብቀኛል ብለህ አስበህ
ከሆነ ሞኝ ነህ፡፡ መልዕክቱን ብቻ እሰጥሀለሁ፡፡ ትስማማለህ?” አለ ናትናኤል ጥድፊያ በተቀላቀለው ድምፅ፡፡

“አዎ አዎ፡: ቀጥል፡፡”

“ጥሩ…. እንዳልኩህ ካልቨርት ለአንተ የማደርስለትን መልዕክትና፡ በርከት ያለ ገንዘብ ሰጥቶኛል፡፡ መልእክቱን ከመስጠቴ በፊት ግን አንተነትህን ማረጋገጥ አለብኝ፡፡”

“ነኝ..ነኝ ግድ የለም:: ስዩም ነኝ፡፡”

“ዝም ብለህ አዳምጠኝ! ለምጠይቅህ ጥያቄ ብቻ ኣጫጭር መልስ ነው የምፈልገው፡፡” አለ ናትናኤል ሰውየውን ይበልጥ ለማደናገር ቱግ ብሎ:: “ካልቨርት በየትኛው ጣቱ ላይ ነው ቀለበት የሚያደርገው?” ያዘጋጃትን ማስመሰያ ጥያቄ አስቀደሙ:: በአውራጣቱ፡ ላያ ቢለውም ግድ አልነበ
ረውም፡፡ ነገር ግን ወደ ዋናዎቹ ጥያቄዎች ከመግባቱ በፊት የሰውየውን
ጭንቅላት ማሟሸት አለበት፡፡
“ቀለበት አያደርግም ካልቨርት::” አለ ሰውየው በሚያስደንቅ ፍጥነት::

“ጥሩ፡፡ አሁንም ፈጣን መልስ እፈልጋለሁ:: ተጠንቀቅ ብትሳሳት
ወይ ብትጠራጠር፡፡ ብትዘገይ ስልኩን ዘግቼ ነው የምሄደው:: የምፈልገው
ትክክለኛውን ስዩም ነው:: የያዝኩትን በርካታ ገንዘብ ላልሆነ ሰው ማስታቀፍ፣
አልፈልግም:: አድምጥ:: የካዛንቺሷ ሴት ስም ማነው?” ናትናኤል በጭንቀት
ትንፋሹን ያዘ፡፡

“የምሥራች ይልማ!” አለ ሰውየው ሌላ ሰው እንዳይቀድመው የፈራ ይመስል በጥድፊያ፡፡
“የስልክ ቁጥሯስ?” አከታትሉ ጠየቀው፡፡
“ትዝ አይለኝም::?”
“እንግዳው ስዩም አያደለህም፡፡ደህና ዋል።”
“ቆይ! ቆይ አለ ነፍናፋው ድምፅ በጭንቀት ተወጥሮ፡፡ቆይ
ስልኩን እንዳትዘጋው። ”
ማስታወሻዬን ልይ… ቆይ አንዴ. እ…ኤ… አዎ ...ይኸው..”

ናትናኤል ስልኩን በጆርውና በትከሻው መሃል ይዞ ሰውየው የነገረውን የስልክ ቁጥር በወረቀት ላይ ይጽፍ ጀመር፡፡ ድንገት ላይ ከሜክሲኮ አደባባይ አቅጣጫ ኣንድ ነጭ ፎርድ መኪና በከፍተኛ ፍጥነት መጥታ ከቢጫዋ ቁርስ ቤት በር ላይ ቆመች:: ወዲያው ከውስጥ የነበሩ ሁለት ሰዎች በሮቻቸውን እየከፈቱ፡ ወረዱ። ሁለቱም የመኪናዋን በሮች
ለመቆለፍ አንኳን ሳይሞክሩ. እየተጣደፉ ወደ ቁርስ ቤቷ አመሩ። ጥቋቁር ኮትና ሱሪ ለብስው የኮታቸውን ቁልፎች ቆልፈዋቸዋል። ናትናኤል ፈሊጡ ገባው:: ቶሎ ዘዴ መቀየስ እንዳለበት ተረዳ፡፡

“ጥሩ፡፡” አለ ድምፁን ሳይቀይር ረጋ ባለ መንፈስ፡፡ “ስዩም ያለሁት ናዝሬት ነው:: ነገ ከጠዋቱ ልክ በአራት ሰዓት ናዝሬት ከቴሌመኒኬሽን ሕንፃ ፊት ለፊት 'ግሪር ሆቴል' የሚል ቤት አለ እዛ እጠብቅሃለሁ:: ነጭ ኮትና ጥቁር መነጸር አደርጋለሁ፡፡ ፒፓ አጨሳለሁ፡፡ ኣደራ ያወራነውን በምሥጢር ያዘው ናትናኤል ስልኩን ዘግቶ እራቅ ብሎ ይጠባበቅ ጀመር፡፡

ወንዲያው ከቢጫዋ ቁርስ ቤት የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ሁለቱን
ስዎች አስከትሎ ብቅ አለ፡፡ ሦስቱ" ተከታትለው ወደ መኪናዋ ገቡ፡፡
መኪናዋ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ ከኋላ የተቀመጠው የላይቤርያው ኤምባሲ
ሾፌር እጆቹን እያወናጨፈ ሲያወራ ሁለቱ ሰዎች ፊታቸውን ወደኋላ መልሰው ሲያዳምጡት ቆዩ፡፡

ከጥቂት ደቂቃዎች ሰኋላ ስዩም ከመኪናዋ ዕርዶ ለብቻው መንገዱን ተሻግሮ ወደ መሥሪያ ቤቱ አቅጣጫ ሲያመራ ነጯ ፎርድ ተጠምዝዛ ሽቅብ በሜክስኮ አደባባይ አቅጣጫ ተፈተለከች፡፡
ፈገግ አለ ናትናኤል፡፡ “ነገ ናዝሬት እንገናኝ” አለ ከራሱ ጋር፡፡ ወዲያው ኪሱ ከቷት የነበረችውን ወረቀት አወጥቶ አነበባት፡፡ ካዛንቺስ የምሥራች ይልማ
የፈለገውን ይኸን ነበር፡፡ስሟንና የስልክ ቁጥሯን፡፡የፈለገውን ሁሉ አግኝቷል።

የላይቤርያው ሾፌር ያለጥርጥር ለበላይ አለቆቹ አስታውቋል፤ ለአብርሃም አለቆች:: ቢሆንም ለጊዜው አትኩሮታቸው ናዝሬት ከተማ ውስጥ ስለሚሆን እዛው ነው የሚሄዱት፡፡ የአውሬውም ጆሮ በአካባቢው ካለ የእውሬውም አይን ናዝሬት ላይ ነው የሚያፈጥ:: ሁሉም ናዝሬት ነው የሚንጋጉት፡፡ አሁን ነው ጊዜው:: አሁን ነው መነቃነቅ ያለባት፡፡

ሃሎ። “ የህዝብ ስልኩ ውስጥ ሳንቲም ጨምሮ ደወለ፡፡
ሃ..ሎው” ሙልቅቅ ያለ የሴት ድምፅ ጆሮው ውስጥ ዥረር አለበት፡፡

“እ... የምሥራች ይልማ ሆቴል ነው. እባኮት…”
“አዎ ነው፡፡ ማንን ላቅርብሎት?” ሙልቅቅቅ አለችበት፡፡

“እንደምንዋልሽ የኔ እመቤት፡፡ እ...ከባህር ዳር ነበር የመጣሁት፡፡
ባልንጀራዬ መስተንግዷችሁን አድንቆ እናንተጋ እንዳርፍ የስልክ ቁጥራችሁን
ሰጥቶኝ ነበር፡፡ እ... ለባለቤቲቱም ደብዳቤ ይዤ ነበር፡፡ ግን ቤታችሁን
ላገኘው አልቻልኩም፡፡ ባክሽ..
“እይውሎት…. " አቋረጠችው:: “ሞቢል ነዳጅ ማደያው አለ አይደል ካዛንቺስ?” የልጅቷ ድምፅ ሲወርድ እንደ ተልባ ነው፡፡
“ያውቁታል...? በቃ በሱጋ ቀጥታ ሲሄዱ እንደዚህ በስተቀኝ ወደ ላይ ወደግራ የሚታጠፍ መንገድ አለ.. አ..ዎ! እሱን ትተው በስተቀኝ ትንሽ እንደሄዱ በትልቁ
'የምሥራች ሆቴል' የሚል ማስታወቂያ አለ፡፡ አጥሩ ሮዝ ቀለም የተቀባ..”
እቅጣጫውን ከነምልክቱ ጥርት አድርጋ ነገረችው::

ናትናኤል ወዲያውነ ታክሲ ተሳፍሮ ወደ ካዛንቺስ በረረ፡፡ እዚያ ሲደርስ ምን እንደሚያደርግ ግን ለራሱም ግልፅ አልሆነለትም:: በሁለት ታክሲ አሳብሮ የምሥራች ሆቴልን ደጃፍ አለፍ እንዳለ የታክሲውን ሂሣብ ከፍሎ ወረደና ጋቢውን ትከሻው ላይ ቆልሎ ዘውዲቱ የገባችለትን አዲሱን ምርኩዙን እያስቀደመ እሱ እየተክተለ መንገድ ባሻገር ያለውን ሆቴል
እያጠና አለፈ፡፡ እራቅ ብሎ ከሄደ በኋላ ከአንድ የአውቶቡስ ፌርማታ ከለላ
አድርጎ ተቀምጦ
👍2
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

...“ናትናኤል የቆርቆሮውን የአጥር በር ገፋ አድርጎ ሲገባ ያጋጠመው ሰፊ ግቢ ነበር፡፡ በግራና በቀኝ አያሌ መኪኖች ተደርድረዋል፡፡ የሆቴሉ ህንፃ ውስጥ ገብተው መስተናገድ ያልፈለጉ ደንበኞች ያማራቸውን እዚያው ከየመኪናዎቻቸው ውስጥ አዘው ይጋበዛሉ፡፡ ፍጥነቱን ሳይቀንስ ወደፊት በሆቴሉ ዋና በር እቅጣጫ ገሰገሰ፡፡

ግቢው በጨለማ ቢዋጥም ከፊት ለፊት የሆቴሉ አዳራሽ ብርሃን እውጭ በረንዳው ላይ የምሽቱን እየር እየተነፊሱ የሚጋበዙ እንግዶችን ያሳያል፡፡

በዋናው በር መግባት አደገኛ ነው፡፡ ያለጥርጥር እሱን የሚጠብቅ ድንገት የሚወነጨፍ ወጥመድ ሊኖር ይችላል፡፡

ወደቀኝ እጥፍ ብሎ በሆቴል ቤቱ በስተቀኝ ወደጓሮ ዞረ፡፡

ጭስ፡፡ እዚያና እዚህ ተፍ ተፍ የሚሉ የወጥ ቤት ሴቶች፡፡ማናቸውም ቀና ብለው አላዩትም:: በጨለማው ውስጥ ዘና ብሎ ከኋለኛው በር ደጃፍ ወጣ ብላ ወደቆመች ሴት ጠጋ አለ፡፡

“ታዲያስ!” አላት እንደቤተኛ ተዝናንቶ::
“አለን!” አለች በጨለማው ውስጥ ፊቱን ለማየት እየሞከረች፡፡
“የምሥራችን ምን ነካት ዛሬ?” አለ ጎንበስ ብሎ የእግር ሹራብን ሳብ ሳብ እያደረገ ፊቱን እንዳታየው:: ጨለማው ፊቱን እንደሚከልልለት ቢረዳም መንፈሱ አልረጋጋልህ አለው፡፡

“እንዴት ምን ሆኑ?” አለች ሴትየዋ የእመቤቷ ስም ሲነሳ፡፡
“አላየኋትም፡፡” አለ ፊቱን ወደ ማዕድ ማዘጋጃው ቤት መልሶ፡፡
“ኧረ አሉ፡፡ ከዋናወ ቤት ናቸው ኮ፡፡”
“ከዋናው አዳራሽ?” አለ ለጥቂት ሴኮንዶች ፊቱን መለስ አድርጎ
አይቷት ወዲያው ዞር ብሎ እየተንጠራራ፡፡ ሴትየዋ የምታወቀው ሰው የዘነጋችው ደንበኛ ይሆናል ብላ እንድትጠራጠር አለቅጥ እየተዝናናባት፡፡
“ዋናው አዳራሽማ ገብቼ ነበር፡፡ የለችም፡፡ ክፍል ጨርሳችኋል እንዴ?” አላት
አከታትሎ፡፡

“አልጨረስንም፡፡ ልያዝሎት? ” አለችው::
“አዎ፡፡” ከኪሱ ገንዘብ አውጥቶ ሰጣት፡፡
ሴትየዋ ወደ ውስጥ ስትገባ እያፏጨ እየተንጎራደደ ጠበቃት፡፡
ከወዲያ ወዲሀ የሚሯሯጠትን ብቅ ጥልቅ እያሉ እንግዶቻቸውን የሚያስተናግዱትን ሴቶች እየተመለከተ ቆየ::
“አዛሉ! ሁለት ጥብስ አንድ ክትፎ ሶስት ፍርፍር ቶሎ በይ!” አለች አንድ ሴት ከጀርባው ካለ መስኮት ብቅ ብላ፡፡ “ዓለም! ዓለምነሽ! ለሦስት ቁጥር ሰዎች አምቦ ውሃ ወሰጂላቸው እንጂ!” ወደ ውስጥ የገባችው ሴት መልሳ በዛው መስኮት ብቅ ብላ ተጣራች፡፡

“መጣሁ መጣሁ! እዚህም'ኮ ስራ ነው:: ጭቅጭቅ?” ዓለምነሽ እያልጎመጎመች ከማዕድ ቤቱ ወጥታ የአምቦ ውሃ ጨብጣ ወደ ዋናው ቤት ሮጠች፡፡

“ይኽው ሰባት ቁጥርን ያዝኩሎት፡፡” አለችው ቁልፉንና መልስ ገንዘብ የያዘችበትን እጇን ወደፊት ዘርግታ፡፡
ቁልፉን ብቻ ተቀብሎ “ተይው” አላት መልሱን ልትሰጠው ስትከጅል፡፡
“እግዜር ይስጥልኝ፡፡" አለች በጨለማው ውስጥ ፈገግታ ደርባ፡፡
“ምስር ከአዲስ ደንበኞች ጋር ነች መሰለኝ? እኛን ረሳችንሳ፡፡” አለ
የተከራየውን ክፍል ቁልፍ፡ ሌባ ጣቱ ላይ እያሽከረከረ፡፡
“አይ..ከነጋሼ ኪዳኔ ጋር ናቸው...ጓዳ፡፡”
“ኪዳኔ የኛ?” አላት በጭፍን፡፡
“አዎ፡፡” አለችው:: ቤተኛ ነው ብላ እንደደመደመች ግልጽ ሆነለት::
“አይ እነሱስ .. ከሆነ ችግር የለም፡፡ አንድ ሰው ይፈልግሻል በያት፡ክፍሌ ውስጥ ነኝ፡፡” ለመመለስ ጊዜ ሳይሰጣት ፊቱን መልሶ መደዳ ወደተሰሩት የመኝታ ቤቶች አመራ…4..5.6..7 ቁልፉን ከቶ በሩን ከፈተና ወደ ውስጥ ገባ፡፡ በሩን ከዘጋው በኋላ መብራቱን አበራው፡፡

የክፍሉን አብዛኛ ቦታ የያዘው ቀይ ጨርቅ የለበሰ አንድ ሰፊ አልጋ በሁለት ኮመዲኖዎችና ቁምሳጥን ታጅቦ መሃል ላይ ተንጋሏል፡፡ አነስተኛ የፊት መታጠቢያ ሳህን ከነፊት መስታወቱ በስተቀኝ ይታያል፡፡ ከክፍሉ ጀርባ ከአልጋው ራስጌ አንድ የተዘጋ የእንጨት መስኮት አላ:: ናትናኤል ክፍሉን ካጠና በኋላ ወደፊት ራመድ እልና በኮርኒሱ መሃል
የተንጠለጠለችውን አምፖል አላላት፡፡ ጨለማ፡፡

አልጋው ላይ ተቀምጦ መጠባበቅ ያዝ፡፡ ልቡ እየተነሳ ሲፈርጥ ደረቱን ሲነርተው እራሱን ኣሳፈረው፡፡ለሳምንታት አንድ በአንድ ሲያስኬደው የቆየው ዕቅድ ቀላል ሆኖ እንዳልታየው ሁሉ ሰዓቱ ሲደርስ በላብ ይዘፈቅ ጀመር፡፡ …ምንድነው የሚላት? ካልቨርት ያላትን ነው መድገም ያለበት፡፡የካልቨርት ቢጤ ምስኪን ተባራሪ ነው መሆን ያለበት፡፡ ያኔ ነው ካልቨርትን
ባየችበት አይኗ ልታየው የምትችለው፡፡ ባታምነውስ? ብትጮኽስ? ኡ! ኡ!
ብትልስ? ወይ አባብላ የተስማማች መስላ ብታስያዘውስ?. አንዱ ክፍሉ
ውስጥ ከገባች በኋሳ መውጣት የለባትም፡፡ መጀመሪያ መውጣት ያለበት እሱ ነው፡፡ ግን ብትጮህ ምን ያደርጋታል? አፏን አፍኖ ይዞ ማስፈራራት?
አጥፍቷል፡፡ ጩቤ ቢይዝ ጥሩ ነበር፡፡ ቀደም ብሎ ያላሰበው ያልጠረጠረው
ሁኔታ ሲከሰትላት ደንገጥ አለ፡፡ ለጥቂት ደቂቃዎች አሰላሰለና ድንገት አፈፍ
ብሎ ተነስቶ በሩን ከፍቶ ወደ ማዕድ ቤት ሮጥ ብሎ ሄደ፡፡

“እዛሉ! ዓለምነሽ! ማናችሁ... ምነው ዛሬ ችላ አላችሁን?” ጭንቅላቱን በማዕድ ቤቱ ጠባብ መስኮት ገባ እድርጎ ታጣራ፡፡ ከውስጥ የክፍሉ ብርሃን ሴቶቹን ቁልጭ አድርጎ ቢያሳየውም ከውጭ የቆመው
የእርሱ ፊት ግን በጨለማው ውስጥ እንደተዋጠ ነበር፡፡

“አቤት...ምንድነው?” አለች ኣዛለች ትሁን ዓለምነሽ ያልለያት ሴት በግራዋ መጥበሻ በቀኟ ሳህን እንደያዘች ፊቷን ወደ እርሱ መልሳ፡፡

“ስንቴ ነው የምንልክባችሁ? ቢላ ቢላ! ቢላ! በይ አሁን አንድ ስጪኝ!” አለ እጁን ዘርግቶ እያራገበ::

ዞር ብላ ከጠረጴዛው ላይ የተቀመጠ የገበታ ቢላ አንስታ አቀበለችው ቢላውን ከተቀበላት በኋላ ፊቱን መልሶ እየተጣደፈ ወደ ተከራየው ክፍል ሲመለስ ከጀርባው ድምጽ ተሰማው፡፡ የክፍሉን በር ከፍቶ እንደያዘ ዞር ብሎ ተመለከተ፡፡

“ማን ነው? ብለዋል እትዬ…ማን ልበላቸው ስሞትን?” አለች የላካት
ልጅ ስሙን ባለማስታወሷ እያፈረች፡፡
“ይሻላል? ህ ህ! ሀ! ሀ!” ልጅቷ ላይ አንቧረቀባት፡፡ “ብላ ብላ ደግሞ ማነው ትለኝ ጀመር? እንደምትያት መታወቂያ ወረቀቴን ብልክ አይሻልም ወይ? ብሏል በያት” ጊዜ ሳይሰጣት ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ “ማነሽ…ደሞ
ሻማና ክብሪት ይሽልኝ ተመለሽ፡ አምፖላችሁ ተቃጥሏል፡፡ እንደው ነው'ኮ
እዚህ የምንመጣ፡፡ የናንተ አስተናጋጅነት ድሮ ቀረ::” በሩን ዘጋው፡፡

አለቅጥ መዝናናቱ ልጅቷን ግራ እንደማያጋባትና እመቤቷ በቅርብ
የሚያውቁት ሰው ነው ብላ እንድታስብ እንደሚያደርጋት ገብቶታል፡፡ ክፍሉ
ውስጥ ከገባ በኋላ ቢላ የጨበጠ ቀኝ እጁን ኪሱ ውስጥ ከትቶ አልጋው ላይ
ተቀመጠና ጨሰማው ላይ ኣፈጠጠ፡፡
ቢላውን የጨበጠበት እጁ በላብ ሲጠመቅ አውጥቶ ሱሪው ላይ
ሞዥቀው፡፡ መፍራት የለበትም ቀፍፁም! አሳዳጆቹ ፍርሀት የሚገባቸው ፤
ርህራሄ የሚውጣቸው አይደሉም። አንገቱን አርደው ቱቦ ውስጥ ሊጥሉት
የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ፍርሀት አይበጀውም:: ፍርሀት አያዋጣውም፡፡

ምንድነው የሚላት? ሊያስፈራራት አይገባም፡፡ እሰም እንደ ካልቨርት ተባራሪ መሆኑን ነው ሊያሳምናት የሚገባው፡፡ ያን ጊዜ ነው የምታምነው! ካልቨርትን ባየችበት እይኗ የምታየው:: እንቢ ካለች ግን በራሷ ቢላዋ ያባብላታል፡፡

ያለበት ክፍል በር ወደ ውስጥ ተከፈተ፡፡
“እንዴ! ምነው ጨለማ ውስጥ ?!” ለሴት ጎርነን ያለ ድምፅ፡፡

“አምፖልሽ ተቃጥሏል ምስርዬ፡፡ ሻማ በያት ልጅቷን፡፡” አለ ናትናኤል በጭለማ ውስጥ እንደተቀመጠ ተዝናንቶ፡፡ ልቡ ትቼህ ልብረር ልብረር አለው፡፡

“ማነህ?” አለ ያው ጎርነን ያለ የሴት ድምፅ ጥርጣሬ የገባው በሚመስል ቃና

“እስቲ ሻማው ይምጣና
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

...ከሩቅ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ በርሜሎች ሲመለከት ክንዷን ይዞ ወደዚያው ጎተታት፡፡አካባቢውን ባለበሰው የቆሻሻ ክምር ላይ ተሻግረሁ ከበርሜሎቹ ጀርባ ዞረው ሸብረክ ሸብረክ አሉ፡፡በስተግሪ ራቅ ብሎ መደዳውን ከተኮለኮሉት የመሸታ ቤቶች የሚወጣው ደብዛዛ ብርሃን አካባቢውን በድቅድቁ ጨለማ ከመዋጥ አድኖታል ወዲያ ማዶ አንድ የጭነት መኪና ቆሟል፡፡ በስተቀኝ የውሾች ጥል በጨለማ ውስጥ አስተጋባ፡፡ድምፃቸውን አጥፍተው ተጠባበቁ፡፡

ናትናኤል ቀና ሲል በጨለማው ውስጥ አንድ ነገር ውልብ ሲል ተመለከተ፡፡ ዓይኖቹን በሰፊው ከፍቶ በጨለማው ላይ አፈጠጠ፡፡ ድምፅ ተሰማው... እየቀረበች ስትመጣ ሲለያት በእፎይታ ትንፋሽን ለቀቀ።ሰካራም ሴት ነበረች:: እንደመንገዳገድ ትልና ወደፊት ትራመዳለች፡፡ ትንሽ ታንጎራጉርና ደግሞ ወደፊት ተራመዳለች፡፡ ብዙም ሳይቆይ ከሰካራሟ ጀርባ የሌሎች ሰዎች ሩጫ ተሰማ፡፡ ናትናኤል ከበርሜሎቹ ጀርባ ሳይወጣ ጭንቅላቱን ብቻ አቅንቶ ተመለከተ::

ሦስት ሰዎች እየተሯሯጡ በኮረኮንቹ መንገድ መጡ፡፡ በኮረኮንቾ
መንገድ ላይ እየተወለካከፉ ሲሮጡ ናትናኤል አዳኞቹ እንደሆኑ ገባው::
ሰካራሟ ሴትጋ እንደደረሱ ከሦስቱ አንደኛው የያዘውን ባትሪ መለስ አድርጎ
ፊቷ ላይ ቦግ እደረገባት፡፡
“ትዝታ እ.. እባላለሁ፡፡” አለች ሰካራሟ ኣይኖቿን ባትሪው ብርሃን በክንዷ ከልላ “ሀ! ሀ! ሀ! ከፈለግህ ደሞ እቤት እንሂድና::ባትሪውን ያበራባት ሰው ትቷት ከጓደኞቹ ጋር ወደፊት ቀጠለ።
ሦስቱ ሰዎች ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያዎቹ ሲደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ቆም አሉና ተነጋገሩ፡፡ ወዲያው ሁለቱ በስተቀኝ ታጥፈው በጨለማው ውስጥ ሲሰወሩ ባትሪ የያዘው ሰው በበርሜሎቹ ኣቅጣጫ አመራ፡፡
ናትናኤል አብራው የተደበቀችውን የካልቨርትን ወዳጅ ጠረጠራት፡፡
ብትጮህስ? ብትጣራና ብታሲዘውስ? እዚሁ ቆሻሻ መጣያ በርሜል : ስር
ደፍተውት ሊሄዱ አይደል? ፈጠን ብሎ ቀኝ እጁን በትከሻዋ አሳልፎ አፏን
አፈናትና በግራ እጁ የያዘውን የቢላ ጫፍ አንገቷ ስር ሽጎጠው፡፡

“ትንፍሽ እንዳትይ… ፊቱን ከማዞሩ በፊት ይሄ ቢላ ማጅራትሽ ነው የሚደርሰው፡፡” አላት ዓይኖቹን በበርሜሎቹ አቅጣጫ ቀሮጠው ሰው ላይ ተክሎ፡፡

ሳትነቃነቅ አይኖቿን ብቻ ኣቅንታ በጭንቀት ተመለከተችው::እንገቷ ስር የተሸጎጠው የቢላ : ስሎት ለስላሳ ቆዳዋን እንደ ምላጭ ሲሰነጥቀው ተሰማት::
ሰውየው ወደ በርሜሎቹ እየተጠጋ በመጣ ቁጥር በደመነፍስ ያወቀና የተረዳ ይመስል ፍጥነቱን ቀንሶ የባትሪውን ብርሃን እንደ ነብር ጅራት ከወዲያ ወዲህ እያላጋ ዙሪያውን እየፈትሽ በዝግታ ይራመድ ጀመር፡፡ እየቀረባቸው ሲመጣ ናትናኤል በበርሜሎቹ አናት ላይ ተመለከተው።በግራው ባትሪውን እንደጨበጠ በስተቀኝ የኮት ኪሱ ውስጥ የጨመረውን እጁን ሲመለከት ስውየው መሣሪያ እንደያዘ ናትናኤል ተረዳ፡፡ በየምሥራች አፍ ላይ የጫነውን የቀኝ እጁን ጠበቅ አደረገና በግራው የያዘውን ቢላ ከአንገቷ ስር አውጥቶ ይዞ ተዘጋጀ፡፡ ተጠባበቀ፡፡ ከበርሜሎቹ ዙሪያ
የፈሰሰው ቆሻሻ ላይ ሲረግጥ የአዳኙ ኮቴ ኮሽታ ተሰማው። ሲጠጋውና
ሲቀርበው ሲደርስበት ተወርውሮ ቢላውን ሊሰካበት ተዘጋጀ፡፡ ሰውየው
ድንገት ቆም አለ፡፡ ያመነታ መስለ ባትሪውን ዞር አድርጎ በበርሜሎቹ ላይ
እበራ፡፡ የባትሪውን ብርሃን በዙሪያው አወናጨፈው፡፡ ወዲያው ፊቱን መልሶ
በኮረኮንቹ መንገድ ወደፊት ቀጠለ፡፡

ሰውየው ከራቀ ወዲያ ነበር ናትናኤል ለመተንፈስ የደፈረው።የምሥራችን አፍ ለቀቀና ቀና አደረጋት፡፡

“አይዞሽ አትፍሪ፤ ልጎዳሽ አልፈልግም:: እመኚኝ፡፡ ከዚህ በላይ ምን ማረጋገጫ ነው የምትፈልጊው?” አለ ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ እየነቀነቀ፡፡ “በይ ተነሺ… ሳንቻኮል በእርጋታ እየተራመድን ወደ ዋናው መንገድ እንውጣለን፡፡ ለመሮጥ ወይ ለመጮህ ብትሞክሪ ግን ምርጫ አይኖረኝም::”

“አልሮጥም::” አለች ፊቷን መልሳ በፍርሃት እየተመለከተችው::

ናትናኤል የምሥራችን ክንድ እንደያዘ ቁጢጥ ካለበት ብድግ ሲል እንቅስቃሴ ታየው፡፡ ተመልሶ ሸብረክ አለና እንዳጎነበሰ አሻግሮ ተመለከተ፡፡
እየተንገዳገደች ቆም ራመድ እንደገና ቆም እያለች በኮረኮንቹ መንገድ
ተመልሳ ትመጣለች ሰካራሟ፡፡

“ተነሽ…” አለ ናትናኤል የምሥራችን ክንድ እየጎተተ፡፡ “ሰካሪሟ ከተደበቁበት የቆሻሻ ማጠራቀሚያ በርሜሎች ስር ወጥተው ፈጠን ብለው በዋናው መንገድ አቅጣጫ አመሩ፡፡

“ታዲያስ!” አለቻቸው ከፊት ለፊታቸው እየተወለካከፈች፣ እየተንገዳገደች የምትመጣው ሰካራም::“እስቲ ወንድም ብር ግፋ፡፡” አለችው ናትናኤልን ስትመለከት እጇን ወደፊት ዘርግታ፡፡

“ዞር በይ!” አላ ናትናኤል አልፏት ለመሄድ እየሞከረ:: ድንገት በዘረጋችው መዳፏ ውስጥ የጨበጠችውን ሲመለከት ግን መላ አካላቱን ደነዘዘው፡፡ : የምሥራች ከፊቷ የተደቀነውን ስታይ እንዳትጮህ የፈራች ይመስል የገባ አፏን በገዛ መዳፏ ግጥም አድርጋ ዘጋችው፡፡

“የማይሆን ነገር አትሞክር፡፡” ኣለች ሰካራሟ የያዘችውን ሽጉጥ ወደ
ሆዱ ገፋ አድርጋ፡፡ “ተነቃነቅ..ዘረግፍሃለሁ፡፡” ድንገት ፊቷን ወደ የምሥራች መለሰችው፡፡ “አንድ ዕድል እሰጥሻለሁ፤ ካልቨርት የት ነው?”
የሽጉጧን አፈሙዝ መለስ አድርጋ የምሥራች ላይ ደቀነችው፡ “ንገሪኝ ጊዜ
አትውሰጂ!”

“እኔ ኣላውቅም፡፡”
በእጁ የጨበጠው የምሥራች ክንድ ሲንቀጠቀጥ ተሰማው:: “ተኩሼ ሳልቀረድድሽ ንገሪኝ:: ካልቨርት የት ነው?' ሴትየዋ አፏን ሳትከፍት በጥርሶቿ መሃል ተናገረች፡፡

“አላውቅምኮ፡፡” የምሥራች ድምፅ እንደ ወፍ ትንፋሽ ሳሳ፡፡ፍርሃት ያንቀጠቅጣት ጀመር፡፡

ሴትየዋ አላመነቻም፡፡ ወደኋላ ጥቂት እርምጃዎች አፈገፈገች፡፡ ናትናኤል ያልጠበቀው ድምፅ ቡፍ አለ፡፡ የምሥራች እጁ ላይ ተልፈሰፈሰችበት... ለቀቃት። ዝልፍልፍ ብላ በስተቀኙ ተዘረጋች፡፡ ከፊት
ለፊቱ ሽጉጧን ደግናበት ከቆመችው ሴት ጋር ተፋጠጠ፡፡ ትንፋሹን ይዞ ጠበቃት፡፡ አእምሮው እርስበርሱ ተጣላበት፡፡ ሊፈነዳ ያሰበ ይመስል ማጅራቱ ሲወጠር ተሰማው:: ዘሎ ይነቃት? ወይስ መጨረሻውን በቆመበት ይቀበል?
ድንገት ፈገግ ያለች መሰለው.. ፈገግ አለች ሴትየዋ፡፡ ከኋላው የሩጫ ድምፅ
ተሰማው፡፡ ከፊት ለፊቱ ቆማ የነበረችው ሴት በፍጥነት የሽጉጧን አፈሙ
ወደ መሬት መለሰችና ከትከሻው ላይ አሻግራ በጨለማው ላይ አፈጠጠች

“ሩጥ!” አለችው በሹክሹክታ ወደጎን ትታው የሩጫው ድምፅ ወደመጣበት እየተራመደች፡፡ “ተዋትና ሩጥ፤” አለችው ድጋሚ ፊቷን መልሳ፡፡ የምሥራችን እየጎተተ ወደ ጥግ ሲሸሸግ ስታየው፡፡ “እሷን ተውና ሩጥ!”

ናትናኤል ሳይመልስላት የምሥራችን ብብቶቿ ውስጥ ገብቶ እየጎተታት ወደ ጥግ ሽሽግ አለ፡፡ መሬቱ ላይ ተንበርክኮ የምሥራችን ጭንቅላት ቀና አደረገና ትንፋሿን አዳመጠ፡፡ አለች፡፡ የምሥራች... የምሥራች...” ድምፁን ቀንሶ ተጣራ፡፡
እያኖቿን በትግል ፡ ገልጣ ተመለከተችው.. እየሞተች ነው...
እየቀዘቀዘች ነው… እያበቃች ነው... ሊያድናት እንደማይችል ተረዳ፡፡
“የምስራች ንገሪኝ ካልቨርት የት ነው ንገሪኝ! ሁላችንን ሳይጨርሱን በፊት ንገሪኝ?”
“ካልቨርት ዮ....ሴፍ” ከጉሮሮዋ የሚወጣው ድምፅ ሻከረበት፡፡
“አዎ ዮሴፍ ዮሴፍ፡ ካልቨርት የት ነው ያለው?”
ከወዲያ የሚሰማው የሩጫ ድምፅ እየቀረበው መጣ አንድ ሴት
ስታንጎራጉር ይሰማል.. በጨለማው ውስጥ..
ዮ....ሴፍ...” የምሥራች ድምፅ በጭንቀት እየተበጣጠሰ ተንጠባጠበ፡፡
“አዎ.... አዎ የት ነው?”

የሩጫው ድምፅ ቀረበ፡፡ ናትናኤል ጭንቅላቱን መልሶ ከጀርባው ተመለከተ፡፡ ሰካራሟ መሀል
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_አንድ



#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....በጥፊ ጆሮ ግንዷን እናጋው፡፡
ለጥቂት ደቂቃዎች ያለችበት ጠፋት፤ዘሪያዋ ጨለማ ለበሰ፡፡ እዛው
አፓርትመንት ክፍሏ ውስጥ እጆቿንና እግርቿን ከአልጋዋ ጋር በአንሶላ
ጨርቅ ጥፍር አድርገው አስረው እንዳትጮህ አፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሰው ለጉመው አጋድመዋታል፡፡

“ንገሪኝ!” አለ ድጋሚ ሊያጣፋት እየተንጠራራ “የት ነው ያለው?
ትነግሪኛለሽ አትነግሪኝም?”
ጭንቅላቷን በጭንቀት አርገፈገፈችው:: ከተለጎመው አፏ ጀርባ ጉሮሮዋ . “የት እንዳለ አላውቅም:: እውነቴን ነው!” አለች:: ድምፅ ግን አላወጣችም፡፡

ውልብ አለባት ድጋሚ፡፡ ጆሮዋ ላይ ሌላ ጥፊ ደወለ፡፡
“ንገሪኝ!”

ዱላው እየጨመረ በመጣ ቁጥር እልኋና ቁጣዋ እንዴት ተደፈርኩ ባያነቷ እንደጨው እየሟመ ለማይታክተው እንባዋ እስረከበዋታል፡፡ ፀጉሯ
ሲጨመደድ ተሰማት::

“ንገሪኝ! የት ነው ያለው?”
ድጋሚ በጥፊ አይኖቿን ከደናቸው፡፡
“ንገሪኝ!”

ተከትሎ ምን እንደተናገረ አልሰማችውም:: ጆሮዋ ላይ የሚደውለውን ስቃይ ተከትሎ ዙሪያዋ ፅልመት ተከናነበ፡፡ አይኖቿን ድጋሚ ስትገልጣቸው ሰውነቷን ክፉኛ ቀዘቀዛት፡፡ለሶስተኛ ጊዜ ውሃ አፍስሰውባታል፡፡
አልጋዋ በየደቂቃው ህሊናዋን በሳተች ቁጥር በሚቸለስባት ቀዝቃዛ ውሃ
ረስርሳል:: የለበሰችው ስስ ቀሚስ እላይዋ ላይ ተጣብቋል፡፡

ዓይኖቿን ግርብብ አድርጋ ተመሰከተቻቸው፡፡ ሶስቱም በአልጋዋ
ዙሪያ ቆመው ቁልቁል ይመለከቷታል፡፡ ሁለቱን አታቃቸውም፡፡ ሶስተኛው
ግን ያው የህዋሷ መሪ ማርቆስ ነበር፡፡ በጠባሳ የተገመሰ ፊቱን ቁልቁል
አንዘርቦ ይመለከታታል፡፡ ደጉን የተወያየችው የገዛ ጓደኛዋ አልመስልሽ
አላት፡፡ አይኖቿን ጭምቅ አድርጋ ጨፈነቻቸው፡፡ በተንጋለለችበት እንባዋ
የገዛ አይኖቿን እንደጨው እየለበለበ ፈሰሰ፡፡

“ከሃዲ!” አለ ሰስተግራዋ የቆመ ሌሊቱን ሲጠፈጥፋት ያደረው ሰው ድንገት ፊቱን መልሶ የመኝታ ክፍሏን በር ከፍቶ እየወጣ፡፡

በክፍሉ ውስጥ የቀሩት ሁለት ሰዎች ለጥቂት ደቂቃዎች ያለ እንቅስቃሴ ቁልቁል ሲመለከቷት ቆዩ፡፡ ወዲያው ማርቆስ ጠጋ ብሎ አፏ የተለጎመበትን ጨርቅ መፍታት ጀመረ፡፡ ሽቅብ ፊቱን ስትመለከተው ከዓመት በላይ የምታውቀው አብራው የቀለደችና የሳቀች ያው የድሮው የህዋሷ መሪ ማርቆስ መሆኑን ማመን አቃታት፡፡

“ምን ማድረግህ ነው?” አለ ከበስተግርጌ የቆመው ጺማም ሰውዬ ማርቆስ አፏ የተለጎመበትን ጨርቅ ሲፈታላት ሲያይ እየተቁነጠነጠ።

ማርቆስ ለሰውየው መልስ ሳይሰጠው አፏን ሞልቶ ተርፎ የነበረውን ቡትቶ ጨርቅ ጎትቶ አወጣላት፡፡ ተበርግዶ የቆየ መንጋጋዋ የራሷ መንጋጋ እንዳልሆነ ሁሉ አልገጥምልሽ አላት፡፡ ደርቆ የቆየ ጉርሮዋ የገዛ ምራቋን አልውጥልሽ አላት፡፡ እንባዋ ብቻ ጉንጮቿን እየተለተለ መውረዱን
ቀጠለ፡፡

“ርብቃ …ለምን ለእኛም ለራስሽም አስቸጋሪ ትሆኛለሽ?” ማርቆስ
ቁልቁል እየተመላከተ ተማፀናት፡፡ “ርብቃ ልለምንሽ የት እንዳለ ንገሪንና
ይህ ሁሉ ያብቃ፡፡” ተለማመጣት፡፡

ለምን አይገባቸውም?! ናትናኤል የት እንደለ ኣላውቅም ስትላቸው ለምን አያምኗትም?! እንዴት አድርጋ ነው እውነቱን እውነት ነው የምትላቸው?

“የት እንዳለ አላውቅም፡፡” ልትል ፈለገችና ጉሮዋ አልታዘዝሽ አላት፡፡ በጀርባዋ በተንጋለለችበት ጭንቅላቷን ነቀነቀች፡፡
“ርብቃ ጊዜ በወሰድሽ ቁጥር ሁኔታው ለራስሽ እየከፋ ነው የሚሄደው፡፡ የምትጋፈጫቸው ሰዎች ትዕግሥታቸው ያለቀና ቁጣቸው ወደ ዕልህ የተቀየረ ራሳቸውን መቆጣጠር የማይችሉ ናቸው:: ርብቃ እነዚህ ሰዎች ሊያደርጉት የሚገፋፉትን ደግሞ ማንም አይወደውም፡፡ አንቺ ሴት ነሽ፡፡ እነዚህን ሰዎች የሚቋቋም የመንፈስ ጠንካራነት የለሽም:: በቀላሉ እንደቀርከሃ ሊሰባብሩሽ ይችላሉ፡፡ በቀላሉ! እባክሽን ንገሪኝ፡፡፡ ናትናኤል የት ነው?” የሌሊት ሁኔታዋን መቋቋም አቅቶት ሲቁነጠነጥ ያደረው
ማርቆስ የባሰ ከመምጣቱ በፊት ሊያሳምናት ታገለ፡፡

አ....አላውቅም፡፡” አለችው እንባዋን እያስተናገደች::
“ጥሩ፡፡ መስሪያ ቤትሽ ደውሉ ሲያጣሽና ስራ ከገባሽ ውሰሽ ማደርሽን ሲረዳ እንዴት እዚህ አልደወለም?”
“ፈርቶ ይሆናል... እኔ ምን አውቃለሁ፡፡” እውነተኛነቷን ይገልፅላት ይመስል ድምጿን አለሰለሰችው::

“ምን? ማንን ነው የሚፈራው?”
“እናንተን፡፡” አለች በለቅሶ መሃል፡፡

“አየሽ ይህ ማለት አንቺ ከእኛ ጋር ግንኙነት እንዳለሽ አውቋል ወይም በፊትም ያውቅ ነበር ማለት ነው፡፡ ይህን ሊያውቅ የሚችለው ደግሞ አንቺ....”

አልነገርኩትም!” አለች አቅጣጫውን ስትረዳ አቋርጣው፡፡ “እኔ አልነገርኩትም፡፡እኔ በእርሱ ላይ መረጃ ስስበስብ መቆየቴንም ጭራሽ አያውቅም፡፡ ግን እዚህ ሲመጣ ልታገኙት እንደምትችሉ ጠርጥሮ ይሆናል፡፡”
ለምን ድጋሚ መሥሪያ ቤትሽ ስልክ አልደወለም? ባለፈው ጊዜ ሲደውል ጓደኛሽ ቢሮ ከገባሽ ዉስሽ ማደርሽን እንድትነግረው አድርገናል፡፡እዚህ መደወል ወይ መምጣት ነበረበት፡፡ አልመጣም፧ አልደወለም:: መሥሪያ
ቤትሽም መልሶ አልደወለም:: ለምን?”

“አላውቅም::” እለች በማስተዛዘን፡፡

“ውሽት አውቋል… ሁሉንም ተረድቶታል:: ለዚህ ነው ሊገናኝሽ ያልሞከረ፡፡ ባያውቅ ኖር..”

“ውሸቴን አይደለም!” አቋረጠችው “እመኑኝ ናትናኤል ምንም የሚያውቀው ነገር የለም ናት…”

“ያውቃል! ያውቃል! ምንም የማያውቅ ሰው በጭካኔ የሁለት ሰው ነፍስ አጥፍቶ አይሰወርም፡፡ ትሰሚኛለሽ? የፈጸመው ወንጀል ምንም የማያውቅ ሰው የሚፈጽመው አይደለም!” ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ ነቅነቃት፡፡

“ናትናኤል ሰው ፡ አይገድልም...ውሸት
ነው፡፡” ለራሷ ፡ ነበር የተናገረችው፡፡

“ርብቃ…. ሰዎቻችን ያውቁታል፡፡ ለይተው ስላወቁትም ነው የተከታሉት፡፡ ይገባሻል? የካልቨርትን አድራሻ ከሴትየዋ ማግኘት ስላልቻለ ምናልባትም አድራሻውን አስገድዶ ካውጣጣት በኋላ ነው ደረቷን በጥይት የበሳው፤ ገድሏት የሄደው፡፡
አስታውሽ እሷን ብቻ አይደለም ያጠፋው!
የኛንም ሰው ነው:: ርብቃ… እባብ ነው ሰውዬሽ፡፡ ሁላችንንም አታሎናል፡፡
ምንም የማያውቅ የዋህ መስሎ አታሎናል፡፡ አንቺንም አታሎሻል፡፡ አብረን
ልናቆመው ይገባናል፡፡ ንገሪኝ፤ የት ነው የተሸሸገው?”

“አላውቀውም አልኩህ፡፡”
ገፁ በንዴት ተኮማተረ፡፡

“ርብቃ” አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታት፡፡ “በአንድ ወቅት ከጎናችን መቆምሽን አንዘነጋውም፤ ያ የሩቅ ትዝታ አይደለም፤ ግን ደግሞ መረባችን በከዳተኞች ምላጭ ሲበጣጠስና ውጥናችን በባንዳዎች ራስ ወዳድነት እርቃኑን ወጥቶ እያንዳንዳችን ለስደትና ለሞት ስንዳረግ በዝምታ መመልከት አንችልም፡፡ ይህ እንዳይሆን ደግሞ የምንጠላውንም ነገር ቢሆን ለማድረግ እንገደዳለን፡፡ ርብቃ ትሰሚኛለሽ? መንፈስሽ መኮሳሽት ካለበት እናኮላሽዋለን፤ሰውነትሽ መዋረድ ካለበት እናዋርደዋለን! ህሊናሽ መጨቅየት ካለበት እናጨቅየዋለን… የማታ ማታ የጠየቅንሽን ሁሉ ታወጪዋለሽ፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት አስተውይ፡፡ ናትናኤል አታሎሻል! የስጋ ፍላጎትሽን ተጠቅሞ
ምስጢራችንን ከቀዳ በኋላ አጋልጦሽ ተሰውሯል፡፡ የት ነው ያለው?
ናትናኤል የት ነው?”

“አላውቅም'ኮ” እንባዋ ገና ድሮ በቀደደው ቦይ ያንቆረቆር ጀመር፡፡

የመኝታ ቤቷ በር ተከፍቶ ሦስት ሰዎች ተከታትለው ገቡ፡፡ ሁለቱን አይታቸው አታወቅም አንደኛው ግን ከትላንት ጀምሮ ሲቀጠቅጣት የቆየ ነው ከፊት ቀደም ያለው ሰው በእድሜ ጠና ያለ ይመስላል፡፡ ወደፊት ራመድ ብሎ ወደ አልጋዋ ግርጌ ከተጠጋ በኋላ በክፍሉ ውስጥ ለተሰበሰቡት ሰዎች እንዲፈቷት ምልክት ሰጣቸውና ከማርቆስ ጋር በሹክሹክታ ይነጋገር ጀመር
1👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


.....ናትናኤል ጊዜ ሳያጠፋ ታክሲ ተሣፍሮ ወደ ለገሃር ሄደ፡፡ ደጋግሞ ደውሎ ነበር ስልኩ የተነሳለት፡፡ቀደም ብሎ የመሥሪያ ቤቷ ጓደኛዋ ምህረትጋ ደወሎ ርብቃን አቅርቢልኝ ሲላት: እሁንም ወደ ስራ
ገበታዋ አለመመሰሏን ስትነግረው አለቅጥ ተጨነቀ፤ከራሱ ጋር ክርክር
ገጠመ፡፡ እንደታመመችና ቤቷ ደውሎ ከቻለም ሄዶ ቢያያት እንደሚሻል
ምህረት ስትነግረው መንፈሱ ሸፈተበት፡፡ ልቡ ላይ እንደጦር የተሸነቀረበት
ግን ሌላ ነበር

“በጣም አሟታል እንዴ?” አላት ምህረትን ቅንድቦቹን አጠጋግቶ፡፡ “ምንድነው በሽታዋ ማለቴ…”
“እንዴት ነው ነገሩ..ኣላወቅህም ማለት ነው? ወይስ…ናትናኤል ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች፡፡”
ድንገት እንደመሽ ሁሉ ጭልምልም አለበት ፤ ጭንቅላቱ እንደ ድንጋይ ከበደው፤ ማጅራቱን ጨምድዶ ያዘው፡፡ አንድ ቃል ብቻ ይደጋግም ጀመር “ፈጣሪዬ! . ፈጣሪዬ! ፈጣሪዬ! ስልኩን ከዘጋ በኋላ በቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡ እንደህፃን ልጅ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ፈለገ፡፡ “ርብቃ ... ርብቃ!” ራሱን መቆጣጠር ተሳነው “ገደል ይግባ!” ሁሉ ነገር ገደል ይግባ!” የሚንቀጠቀጥ እጁን ኪሱ ከቶ ከአንድ ቡና ቤት ገብቶ ተቀመጠ፡፡ ለሰዓታት ከራሱ ጋር ተወራጨ፡፡ በመጨረሻ ከቡና ቤቱ ወጥቶ የህዝብ ስልክ ይፈልግ ጀመር፡፡

ስልኩ ቢጠራም የሚያነሳው ሰው አልነበረም፡፡ በሚንቀጠቀጥ ቀኝ
እጁ የስልኩን እጀታ ጨምድዶ ይዞ ተጠባበቀ:: ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች ስልኩ
ይጠራል፤ የማያነሳ የለም፡፡ ቀጥታ እቤቷ ድረስ ብሄድስ? አሰበ፡፡ መሄድ የለብኝም:: እሷንም ቢሆን ለባሱ አደጋ ማጋለጥ ነው የሚሆነው፡፡ ደጋግሞ ደውሎ ነበር ስልኩ የተነሳለት

“ሀሎ” አለ ስልኩ እንደተነሳ ቀድሞ፡፡ ድምፅ ተጠባበቀ፡፡ ግን ምንም
አልነበረም:: መልሶ “ሃሎ አለ የሚንቀጠቀጥ ድምፁን ማረጋጋት
እየታገለ፡፡

“ናቲ..ናናቲ” ድምጿን ከመቅጽፅት ለየው፡፡ ቢሆንም በጣም የደከመ ድምጽ ነበር፡፡
“ርብቃ! ደህና ነሽ…?”
“ናቲ...ናቲ አቃጠሉኝ..ና…” .
“ናትናኤል ነኝ ርብቃ… ጮክ በይ አይሰማኝም፡: ርብቃ መሥሪያ
ቤትሽ ደውዬ ነበር፡፡ ርብቃ… እ?… አይሰማም፡፡” ድምጿ እየደከመበት ሄደ፡፡
ሌላ ሰው ስልኩን እንደተቀበላት ተረዳ፡፡
“ሀሎ፡፡” አለ ለስለስ ያለ የወንድ ድምፅ፡፡
“ሃሎ.… እባኮት ርብቃን ነበር፡፡”
“ማን ልበል? ” .
“ሀሎ..እባኮት ርብቃን ያቅርቡልኝ::” ናትናኤል ረጋ ብሎ ጠየቀ፡፡
“ይቅርታ፡፡ትንሽ አሟታል፡፡ በስልክ መቅረብ አትችልም::
የምነግርልዎት መልዕክት ካለ.….”
"እሷኑ ለማነጋገር ስለምፈልግ ነበር፡፡” ናትናኤል ጠንከር አለ፡፡
“ይቅርታ… ስትነጋገር ስለሚደክማት ነው፡፡ መልዕክት ካሎት ልንገርሎት፡፡ ታናሽ ወንድሟ ነኝ ብስራት ነኝ፡፡”
ናትናኤል ለማስታወስ ሞከረ፡፡ ቤተሰቦቿን ብዙም አልቀረባቸውም፤ ቢሆንም ከብስራት ጋር ከአንድ ሁለት ሦስት ጊዜ ተገናኝተዋል፡፡ ብስራት ገና ሃያ ዓመት ያልሞላው ወጣት ወንድሟ ነው::

“እንደምንዋልክ ብስራት፡፡ ናትናኤል ነኝ፤
ታስታውሰኛለህ? የርብቃ..እ… ”

“እዎ እዎ አስታውስሃለሁ፡፡ እንደምንድነህ? ደህና ነህ? ምነው
ጠፋህ? ርብቃ በጣም አስባለች፡፡ ለምን ብቅ አትልም? ”

“እ..” ናትናኤል አመነታ፡፡ “ምን መሰለህ ብስራት መምጣት እንኳን አልችልም፡፡ ግን እሷ እንዴት ነች?”

“አሟታል…በጣም ነው የታመመችው ሐኪም ቤት እያመላለስናት ነው::”

“ምን አሉ ሐኪሞቹ? ማለቴ ምንድነው?” ናትናኤል በልቡ የሚንቀዋለለውን ለመጠየቅ ጭንቅ አለው::

“አላወቁላትም፡፡ ግን ምግብ አይበላላትም፤ ስትበላም አይረጋላትም፡፡
ሰውነቷ ላይ ግን ችግር የለባትም፡፡ 'ጭንቀት ነው' ነው የሚሉት ሐኪሞች፡፡
ምን እንደሚያስጨንቃት ግን ሊገባን ኣልቻለም፡፡ በጣም ደክማለች::
ናትናኤል መጥተህ ብታያት ጥሩ ነበር:: በእንቅልፍ ልቧ ሁሉ ስምህን
ትጠራላች፤ ከቀን ወደቀን እየባሰባት ነው፡፡” ናትናኤል በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ እጁን ግንባሩ ላይ ጫነ፡፡ ከራሱ ጋር ክርክር ገጠመ:: የፈለገው ይምጣ ሄዶ ያያታል፡፡ መቼም በቤቷ አካባቢ ሊያንዣብቡ ይችሉ ይሆናል፡፡ ግን ምርጫ የለውም:: ሹልክ ብሎ ገብቶ ሹልክ ብሎ ይወጣል ወሰነ::

“ብስራት መደወሌን ለማንም አትናገር ዛሬ ማታ መጥቼ አያታለሁ እሺ? ልክ ከምሽቱ አስራ ሁለት ተኩል ሲሆን ውጭ በሩጋ ጠብቀኝ” ናትናኤል ስልኩን ከዘጋ በኋላ በግራው ያንጠለጠለውን ትንሽ የሽራ
ሻንጣ ይዞ እዚያው ለገሃር ኣቅራቢያ ወዳለ አነስተኛ ቡና ቤት ተመልሶ ገባ፡፡
ጥግ ወዳለ ወንበር ሄዶ ሰውነቱን ለማርገብ፣ ለማረጋጋት በዝምታ
ተቀመጠ፡፡ በግራሶና ዘይት የተጨማለቀ ሰማያዊ ቱታ ለብሷል። ጭንቅላቱ
ላይ ያጠለቀው ዙሪያው እንደጠወለገ ቅጠል የተልፈሰፈሰው ባርኔጣ በግንባሩ
ላይ ኣዝምሞ ፊቱን ሸፍኖታል፡፡ ከደረት ኪሱ ሲጋራ አውጥቶ ከሚንቀጠቀጥ እጁ ጋር እየታገለ ከለኮሳት በኋላ ክብሪቱን እያጠፋ ሲጋራዋን ምጥጥ አደረጋት፡: “ርብቃ... ርብቃ.… ምነው አጠገብሽ መሆን ብችል!”

“ምን ልታዘዝ::” አለችው ሰማያዊ ሽርጥ ወገቧ ላይ ሸብ ያደረጎች አስተናጋጅ የለበሰውን ቆሻሻ ቱታ ስታይ ድምጿን ቆጥብን አድርጋ::

“ቡና፡፡” አላት ቀና ብሎ አያቷት የዋጠውን የሲጋራ ጭስ ቀረጁሙ እየለቀቀ፡፡

“ሂሣብ በቅድሚያ ነው የሚከፈለው፡፡” አለች ሁለት እጆቿን በጎንና ጎን የሽርጥ ክሶች ውስጥ እየወሸቀች፡፡

ከቀኝ ኪሱ ውስጥ ሣንቲሞች አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ በተን እደረገላት፡፡ ሃሳቡ ግን ሌላ ቦታ ነበር፡፡ ርብቃ ለምን ደበቀችው? «ወይስ ወሯ ገና ነው ማለት ነው ሊሆን አይችልም:: ደብቃው ነው፡፡ ግን ለምን.… ለምን?

የሚወደው ገጿ መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች የምህረት ድምፅ እቃጨለበት፤ አሟታል ምግብ አይበላላትም ብትበላም አይረጋላትም “ጭንቀት ነው" ነው የሚሉት ሐኪሞቹ….
የብስራት ድምፅ ደወለበት...

“አምላከኔ ምን ዓይነት ጉድ ወስጥ ነው የከተትከኝ ኣለ እምላከ ከፊት ለፊቱ ባለ ወንበር ላይ የተቀመጠ ይመስል ፊት ለፊት አፍጥጦ፡፡

ምንድነው ሊያደርግ የሚችለው? ቀጥ ብሎ ፖሊስጋ ሄዶ እጁን መስጠት፡፡ ቢገሉትስ? ይግደሉት፡፡ ከዚህ በላይ ስቃይ መሸከም አይችልም ግን ለፖሊሶችስ ምን ሆንኩ ብሎ እጁን ይሰጣል? ሁሉን ነዋ!.. የሆነውን
ሁሉ ዘርዝሮ ማውጣት ነዋ! ግን ማን ያዳምጠዋል? ማን ያምነዋል? ፍጹም!
ፖሊስ ወጥመድ ነው! እጁን መስጠት ማለት ሞቱን ማፋጠን ማለት ነው፡፡
ለማን ይበጃል መሞቱ? ለርብቃ? ስልጁ? የአብርሃም መሞት ማንን ጠቀመ?
መረጋጋት ነው ያለበት፡፡ ካሁን ወዲያ ወደኋላ ማለት አይችልም፤ መረጋጋት
ነው ያለበት፡፡

ከቁጥጥር ውጭ በሚንቀጠቀጥ ቀኝ እጁ የያዛትን ያለቀች ሲጋራ ለመጨረሻ ጊዜ መጠጣትና ከፊት ለፊቱ ጠረጴዛ ላደ በተቀመጠው የሲጋራ መተርኮሻ ውስጥ ደፈጠጣት፡፡ መረጋጋት…. መረጋጋት ነው ያለበት...

የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዛትን ቡና አምጥታ እፊቱ ደነቀረችለት::
አንስቶ ፉት ኣላው፡፡ ስኳር አልነበረውም:: ክፉኛ መረረው፡፡ ቢሆንም ስኳር
አልጠየቃትም፡፡ ድጋሚ ፉት ኣለው፡፡ ትኩስ ቡና በጉሮሮው አልፎ በሆዱ
ሲተራመስ ስንዝር በስንዝር ተከታትለው:: ሆዱ ጩርርርር ሲል ተሰማው:: ትላንት ምሳ የበላ ነው፡፡ ቢሆንም ምግብ አላሰኘውም:: ከቡናው ድጋሚ ፉት አለለት፡፡ ሰውነቱን ማዝናናት አለበት፤ ማረጋጋት አለበት፡፡በተቀመጠበት ወንበር ላይ በደኋላ ጋለል ብሎ ዓያኖቹን ጨፈናቸው፡፡ ቀኝ እጁ ከደረት ኪሱ ገብቶ ሲጋራና ክብሪት ይዞ ተመለሰ፡፡ ርብቃ ለምን ደበቀችው? በቃ በቃ... ስለርብቃ
👍2
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....ናትናኤል ለጥያቄው መልስ ሲያገኝ ይበልጥ ተበሳጨ፡፡ ለዚህ ቀላል ጥያቄ፣ ለዚህ ቀላል መልስ ይህን ያህል ከተቸገረ እንግዲያው ማስተዋል ቀንሷል ማለት ነው ከሚገባው በላይ ተወናብዷል ማለት ነው፡፡ ፈርቷል ማለት ነው፡፡

እራሱን ገሰጸወ፡፡

ረጋ ማለት አለበት፡፡ አለበለዚያ በማይረባ ስህተት እራሱን አጋልጦ ይሰጣል፡፡

ስሟን እስካወቀ፤ የስልክ ቁጥሯን እስካወቀ፤ የአባቷንና የአያቷን ስም ከማንኛውም የስልክ ደብተር ላይ በቀላሉ ያገኘዋል፡፡

ሌሊቱን በሙሉ በሃሳብ ሲታመስ ሳያሸልበው ፀሐይ ሥፍራዋን
ተረከበች::

ናትናኤል ከአልጋው ተነስቶ ማታ አለቅልቆና በእርጥብ መሃረቡ
ጠራርጎ ከግርጌ ካለ ወንበር ላይ ያሰጣቸውን ሸሚዙንና ኮቱን አንስቶ
ለባበሰና ወደ መታጠቢያ ቤት ገባ፡፡ በተቻለው መጠን ረጋ ብሎ ተጣጥቦ
ያለፈውን ሌሊት አሻራ ሙልጭ አድርጎ ካፀዳ በኋላ ወደ ሆቴሉ አዳራሽ ብቅ
አለ፡፡

ጥግ ላይ ተቀምጦ ሁለት ስኒ ቡና ጠጣና ፈጠን ብሎ ከሆቴሉ ወጣ፡፡ ሌላቱን ያለእንቅልፍ ቢያሳልፈውም የድካም ስሜት አልተሰማውም፡፡ምናልባት ድንጋጤው ይሆናል፧ ምናልባት ፍርሃት፣ ምናልባት ሥጋት፡፡

ደሙ በሰውነቱ ውስጥ ሲሽቀዳደምና ሲራወጥ ለራሱ ይሰማዋል፡፡ መፍጠኝና
መሮጥ አለበት!

ታክሲ ተሳፈረና ወደ መርካቶ ሸሸ፡፡

መርካቶ ባህር ነው ውቅያኖስ፤ መርካቶ ጫካ ነው ደን፡፡መርካቶ ቤቱ ነው የዘውድዬ፡፡


መሀል መርካቶ ከታክሲ እንደወረደ ወደ አንድ ቡና ቤት ገባ፡፡ገንዘብ ተቀባይዋን ተጠግቶ ሠላምታ ከሰጣት በኋሳ የስልክ ማውጫ ጠየቃት፡፡

“ጩኒ ቁልፍ፡፡” አለች ረጅም ወንበር ላይ የተቀመጠችው ወጣት ሴት ወደኋላ ዞራ፡፡
“ በእድሜ የሚመጣጠናት ወንድ ልጅ በቀጭን ሰንሰለት ውስጥ የተሰገሰጉ አስር የሚሆን ቁልፎች አቀበላት፡፡ ከቁልፎቹ ውስጥ አንዷን መርጣ አወጣችና አጠገቧ ያለ መሳቢያ ስባ የስልኩን ደብተር አውጥታ
አቀበለችው::

"እግዜር ይስጥልኝ” አላት ማውጫውን ተቀብሏት እየከፈተው፡፡

'የምሥራች ይልማ መጀመሪያ የምሥራችን ስም ፈለገ፡፡ በርካታ የምሥራች ይልማዎች የተደረደሩትን ገፅ እንዳገኘ የስልክ ቁጥሯን ፈለገው:: ቁጥሩን እንዳገኘ ወደኋላ ተመልሶ በትይዩ የተፃፈውን የምሥራችን ስም እስከ አያቷ ስም አነበበው የምሥራች ይልማ ገዛኽኝ::
“እቶ ይልማ ገዛኸኝ ድጋሚ የስልክ ማውጫውን እያገለባበጠ
ይፈልግ ጀመር አቶ ያልማ ገዛኸኝ... ይ.… ይ. ይ.. ያልማ አዳሙ... ይልማ መብራቱ
ይልማ ገብረማርያም…ያልማ ገዛኽኝ
የስልክ ቁጥሩን በወረቀት ላይ ገለበጠና የቡና ቤቱን ገንዘብ ተቀባይ አመስግኖ ወጣ፡፡ እዚያው አካባቢ የሕዝብ ስልክ ፈልጎ ኣቶ ይልማ ገዛኸኝ መኖሪያ ቤት ደወለ፡፡“

ከቤት” አለው ቀጠን ያለ የሴት ድምፅ፡፡
“እባኮት አቶ ይልማን ነበር”
“ሥራ ናቸው” አለች ሴትየዋ በተሰላቸ ድምዕ::
“እባኮት ችግር ገጥሞኝ ነው የሥራ ቦታቸውን ስልክ ቢሰጡኝ፡፡

“የሱቁን ነው?”
“አዎ ላገኛቸው የምችልበትን ቦታ፡፡”

ነገረችው:: ቀልጠፍ ብሎ ቁጥሩን ጻፍ ጻፍ አደረገና አመስግኗት ስልኩን ዘጋ:: ወዲያው የሰጠችውን ቁጥር ደወለ፡፡

ሃሎ” አለ ውፍረት የደፈነወ፣ ስጋ የዘጋው፣ እርስ በእርስ የሚተሻሽ ድምፅ::

“እባኮት አቶ ያልማ ይኖራሉ?”
“ነኝ:: ማን ልበል?”
“እንደምን ዋላ፡፡ የምሥራች ነበረች የላከችኝ..." ናትናኤል የሰውየውን ስሜት ለማጥናት ለአንድ አፍታ ዝም አለ፡፡

“ማን አሉኝ?” አለ ሰውየው መልሰው፡፡
“የምሥራች… የምሥራች ይልማ፡፡”
“ከየት ነው? ማንን ነው የሚፈልጉት?” ሰውየው ግራ የተጋቡ መሰሉ፡፡
“የምሥራች... የምሥራች የእርሶ ልጅ::”
“የማን ልጅ? ” ሰውየው ያበልጥ ተደነጋገራቸው፡፡
““ካዛንቺስ ሆቴል ያላት የእርሶ ልጅ::የምሥራች ይልማ ባለሆቴሏ...

“የምን ሆቴል ነው የሚሉኝ?”
ይቐርታ ጠይቋቸው ስልኩን ዘጋ፡፡

ሌላ ይልማ ገዛኽኝ በአዲስ አበባ ስልክ ማውጫ ደብተር ውስጥ የተመዘገበ የለም፡፡ ያለው አማራጭ ወደ ድሬዳዋ መንጎድ ብቻ ነው፡፡ድሬዳዋን አያውቃትም:: እዚያም ሄዶ መቸገሩ የማይቀር ነው፡፡ ግን የተሻለ
ምርጫ የለም::

መፍጠን አለበት፡፡ ምንም ጠባብ ቢሆን በተከፈተለት በር ሁሉ መሮጥ አለበት፡፡

ወደ ካልቨርት መጠጋት አለበት::
ዝግጅቱን ለማጠናቀቅ ወደ ባቡር ጣቢያ ሄዶ በማግስቱ ምሽት ላይ ወደ ድሬዳዋ በሚሄድ ባቡር ላይ የሁለተኛ ማዕረግ ትኬት ከቆረጠ በኋላ አውቶቡስ ተራ ወደ ዘውዲቱ ቤት ወደ ጎሬው በረረ፡፡

ምሳውን ከዘውዲቱ ጋር ከበላ በኋላ አሰዓት ወደ ገበያ ወጣ፡፡መርካቶ የዘመን መለወጫ በዓልን መስከረም አንድን ለመቀበል በሚዘገጃጅ ገብያተኛ ተጣባለች፡፡

ወደ ድሬዳዋ ሲሄድ ሊለብስ ያሰበውን ጀለቢያና ሽርጥ ነጠላ ጫማ እንዲሁም አንድ አነስተኛ የሸራ ሻንጣ ገዛ፡፡ አዲስ አበባ እስካለ ድረስ ደግሞ አጥልቆት የሚዘዋወረውን ወራጅ የጋራዥ ቱታና ፊቱን ጥሩ እድርጋ የምትሸፍንለት አንድ የተልፈሰፈሰች ባርኔጣ ጨመረ፡፡መንገድ ላይ ከኣንድ ጋራዥ ገባ ብሎ ለዘበኛወ ሁለት ብር ሰጠና በትንሽ ቆርቆሮ የተቃጠለ ዘያት ይዞ ወደ ጎሬው ሲመለስ ከእንድ ሱቅ ጎብቶ አንድ ጥሩ ሽቶና የሴት
ነጠላ ጫማ ሾመተ:: ከዘውዲቱ ቤት ሲደርስ ባይመሽም ቀኑ ገፍቶ ነበር።
ልብሱን አወላልቆ ዘወዲቱ እልጋ ወስጥ ገብቶ ጥቅልል አለ፡፡ የዘውዲቱን ቤት ተከራይቶ ከገባ ጀምር ለመጀመሪያ ጊዜ ዘውዲቱ፡ አብሯት የሚያድር ደንበኛ አጥታ እንድትመጣ ተመኘ፡፡

ያን ሌሊት በውዲቱ ቀንቷት ደንበኛ አገኘች አልተመለሰችም፡፡አልጋዊ ላይ ብቻዉን ሲገላበጥ ሲያቃዠው አደረ፡፡አንዱን ቅዠት ሳያገባድድ ሌላ ቅዠት እያቋረጠው ያባረረው ውሻ ሳያዘው ጭልጥ ካለ ገደል እየገባ ከገደሉ ወለል ደርሶ አናቱ እንደ እንቁላል ሳይፈርጥ አየር ላይ ጭልፊቶች
ገላውን እየገመጡ አይኖቹን እየጓጎጡት ሲወራጭ አደረ፡፡

ጠዋት በሩ ሲከፈት በርግጎ ሲነሳ ጭንቅላቱን በፋስ ሲወቅረው ተሰማው እራስ ምታት ነፍስ ዘርቶ፡፡

“እንደምን አደርክ?” አለችው ዘውዲቱ ወደ ውስጥ ገብታ በሩን እየዘጋች፡፡ እስካሁን አልተነሳህም? ሁለት ሰዓት አልፏልኮ::” የያዘችውን የላስቲክ ከረጢት ወንበር ላይ ጣል ኣድርጋ ኣልጋው ጫፍ ላይ ቁጭ አለችና ኩንታል ስትሸከም እንዳደረች “
ኡፍ.....ፍ፡!” አለች፡፡ “እንዴ ለምን እራትህን ሳትበላ አደርክ?” አለች ሳይከፈት ያደረውን የምግብ ሳህን ከራስጌ ስታይ ዞራ እየተመለከተችው::

“አላየሁትም ነበር፡፡” አላት ናትናኤል እራቁት ደረቱን እያከከ ዞር ከራስጌ የተቀመጠውን ሳህን እየተመለከተ::

“እና ጾምን አደርክ ማለት ነው? ደግሞ ከትላንት ወዲያ የት ነበር ያደርከው?” ጥያቄ አከታተለችበት፡፡

ሳይመልስላት ከአልጋው ተነስቶ ከወገቡ በላይ ለመለቃለቅ በሩን ከፍቶ ወጣ፡፡ ሰወነቱን ተለቃልቆ ሲመለስ ዘውዲቱ ከራስጌ ያደረውን ሳህን ከፍታ በግራ እጇ ይዛ እየተንጎራደደች በላይ በላዩ ስትጎርስ አገኛት::

“ቡዳ የሆነ ሰውዬ ራቴን ሳያበላኝ ቤቱ ወስዶ እንደቅሪላ ሲያለፋኝ አደረ::” አለች እየሳቀች፡፡ “ላጉርስህ? ”
ራሱን ነቀነቀ፡፡ ናትናኤል ምግብ አላሰኘውም፡፡
“ምን ሆነሃል? ቤት ደህና አይደሉም እንዴ? ”
“ደህና ናቸው እነሱስ...” የጀመረውን አንጠልጥሎ ተወው፡፡
“ታዲያ ምን ሆነሃል? "
“ሰውየው ተያዘ::”

የቱ ሰውዬ?” መንጎራደዷን አቁማ በተቀመጠበት ቁልቁል ተመለከተችው፡፡

“አለቃዬ። የመሥሪያ ቤታችንን ገንዘህ ያጠፋው፡፡”

“አትለኝም!” የያዘችውን የምግብ ሳህን ከራስጌ አስቀምጣ በወጥ የተጨማለቀ እጇን አንከርፋ ኣልጋው ላይ ከጎኑ
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....እንደ ድንጋይ ከተጫናት ሰመመን ውስጥ ቀስ በቀስ እየወጣች ስትመጣ… እላይዋ ላይ ተጭኖ የያዛት ድቅድቅ ጨለማ እንደ ጭስ እየሳሳ እየበነነ ለቋት ሲጠፋ በመጀመሪያ የተቀበላት በእግሮቿ መሃል የሚነዝራት የደነዘዘ ስቃይ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ እየጠራ ሲመጣም አይኖቿን ለመክፈት አልደፈረችም፡፡ ሌላ ዱላ፣ ሌላ ስቃይ ሌላ የጋለ ሽቦ የሚችል
አካል አልነበራትም። በክፍሉ ውስጥ ብቻዋን ትሁን አትሁን እርግጠኛ
አልነበረችም፡፡ አይኖቿን ለመክፈት ግን አልደፈረችም፡፡

እጆቿ ግራና ቀኝ ተወጥረው ከታሰሩሰት ተፈተው በድን እንደሆኑ ሁሉ በግራና በቀኝ ተዘርረዋል፡፡ በተኛችበት ልብስ ደርበውላታል፡፡ እግሮቿ ግን አሁንም ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ተወጥረው እንደታሰሩ ናቸው፡፡ ቁስሏን ለማዳመጥ ሞከረች፡፡ በጭኖቿ መሃል የሚሰማትን ስቃይ ለማዳመጥ ዝም አለች የተዳፈነ... የደነዘ… የደበዘዘ ስቃይ፡፡ ግራ ክንዷ ላይ ህመም ተሰማት:: ለመነቃነቅ ግን አልደፈረችም፡፡ በአይነ ህሊናዋ ሁኔታውን
ለመቅረፅ ሞከረች። መቼ ነበር በጋለ ሽቦ ጭኖቿ መሃል ሰውነቷን ያቃጠሏት? ዛሬ? ትላንት? ዛሬ ምንድነው? ቀን ነው ሌሊት? ሰዓታትና ቀናት ትርጉም ካጡባት ቆይተዋል፡፡

ድምፅ የሰማች መስላት። ዓይኖቿን እንደከደነች ጆሮዎቿን ኣስልታ ተጠባበቀች፡፡ የበር ድምፅ ተሰማት… የሚከፈት የበር የሚያሰማው ድምፅ..

“አልተነሳችም፡፡” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ፡፡

“ኮለኔል” አለ አንድ ድምፅ በሹክሹክታ “ዙርያውን አጥረነዋል።በርም ላይ አንድ ሰው አቁመን እየተጠባበቅን ነው::”

“መጣሁ” ሲል ተሰማት ማርቆስ፡፡

ሁለት የእግር ኮቴዎች በግራና በቀኟ ተስሟት…በስተቀኝ ኣንድ መዳፍ ግንባሯ ላይ አረፈ::

“ከነቃች የመርፌ ማደንዘዣውን ስጣትስቃይ ሊኖርባት ይችላል።” የማርቆስ ድምፅ ነበር።

“ካስቸገረችኝስ ልምታት?” አለ በስተግራዋ የቆመ ሌላ ሰው፡፡

“ረጋ ብለህ አባብለህ ውጋት። ለምን ትመታታለህ? ደግሞ አታስቸግርህም.. ከተወራጨችብህ ግን ግሉኮሱን ንቀልላት፡፡” አለ እጁን ግንባሯ ላይ የጫነው ማርቆስ በጣቶቹ ፀጉሯን ወደኋላ እያበጠረ፡፡ “ጠዋት እቀየርልሃለሁ፡፡”

ኮቴ ተሰማት፡፡ ተከታትለው ሲወጡ ሰማች። በሩ ሲዘጋ በክፍሉ ውስጥ ፀጥታ ሲነግስ ስትፈራ ስትቸር አይኖቿን ገለጠቻቸው::መኝታ ክፍሏ ውስጥ ብቻዋን አስተኝተዋታል፡፡ በቢጫው የብርድ ልብሷ ከአንገቷ እስከ
እግሯ ጫፍ ድረስ ሸፍነዋታል፡፡ በተንጋለለችበት ዙሪያዋን ተመለከተች፡፡
ግራ ክንዷ ላይ የሚሰማት ህመም ከራስጌዋ ከተንጠለጠለው የግሉኮስ
ከረጢት ጋር የተያያዘው መርፌ ክንዷን ጠልቆ የገባበት ላይ መሆኑን ተረዳች። የክፍሉ መጋረጃ ተዘግቷል፡፡ በጥግና ጥግ የታየው ሰማይ ጨልሟል... መሽቷል፡፡ ሰመነቃነቅ ስትሞክር ግራና ቀኝ የታሰሩት እግሮቿ መሃል የተዳፈነው ስቃይ እንደ ጦር ወጋት፡፡ ከስሱ የብርድ ልብስ በታች ያለው እራቁት ሰውነቷ ተንሰፈሰፈ፡፡

ድምፅ ተሰማት የመኝታ ቤቷ በር ተከፈተ፡፡ ቶሎ ዓይኖቿን ጨፈነቻቸው፡፡ : እንደነቃች ማወቅ የለባቸውም፡፡ ዝም ብላ መተኛት ነው ያለባት፡፡ መረበሽ የለባትም! አለበለዚያ ይመቷታል፡፡ ዝም ብላ መተኛት። በሩ ሲዘጋ ተሰማት: የእግር ኮቴ እየቀረባት መጣ. አንድ በላብ የረጠበ እጅ
እራቁት ትከሻዋ ላይ ሲያርፍ ተሰማት… ትንፋሼ እላይ እታች የሚል ትንፋሽ እላይዋ ላይ የነበረው ስስ የብርድልብስ ፡ ተገፈፈ፡ መረበሽ የለባትም… መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም... አለበለዚያ ድጋሚ
ያስቃይዋታል. , ትከሻዋ ላይ ያረፈው በላብ የራሰ መዳፍ ወደታች ወደ
ደረቷ ተንሸራተት…. እልተንቀሳቀሰችም ጡቶቿ ሲዳስሱ ተሰማት እላይ እታች የሚል ትንፋሽ… ፍርሃት ወረራ ግራ ክንዷ ላይ የተሰካውን መርፌ አስሮ የያዘው ፕላስተር ተላጠ.. ክንዷ ላይ የተሰካው መርፌ ተነቀለ መንቃቷን ማወቅ የለባቸውም… አለበለዚያ ይመቷታል... እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ቀረባት፡፡ ብርድ ልብሷ ወደታች ተጎተተ ፍርሃቷ
እየጨመረ መጣ እላይ እታች የሚለው ትንፋሽ ወደ አንገቷ ስር ሲጠጋ ተሰማት.. ብርድ ልብሱ ከላይዋ ላይ ተንሸራቶ ወደ መሬት ወደቀ፡፡ ራሷን መቆጣጠር አቃታት… አይኖቿን ገለጠቻቸው፡፡

ጺማሙ ሰውዬ ነበር፡፡ እላይዋ ላይ እንዳንገርበበ ድንገት አይኖቿን ስትገልጥ ደንገጥ አለ፡፡ ወዲያው ፈገግ አለላት... የሸሚዙን ቁልፎች መፍታት ጀመረ… ፈገግ አለላት ድጋሚ… ሸሚዙን ከላዩ ላይ ወርውሮ ተጠጋት… እጆቹን ጡቶቿ ላይ ጫናቅው ድንገት ተወራጨች፡፡ ሙቅ
እርጥብ እጆቹን ከላይዋ ላይ ገፍትራ ተሸማቀቀች ፈገግ አለላት፡፡ አልጋዋ
ላይ የተንጋለለውን እራቁት ገላዋን ከላይ እስከታች በተራሱ ኣይኖቹ ዳሰሰው፡፡ ምራቁን ሲውጥ ትልቅ ማንቁርቱ እላይ እታች ሲመላለስ በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡ ድንገት ዘሉ አፏን በመዳፉ ኣፈናት… ታገለችው…
እጆቿን እያፈራረቀች እንደብረት የደደሩ ሁለት ክንዶቹን ደበደበቻቸው
ቧጠጠቻቸው... ያለብዙ ችግር እፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሶ ለጎማት

ትንፍስ ትንፍስ እያለ ቁልቁል ተመለከታት፡፡ አይኖቹ የሚያርፉበት
ቦታ ያጠ ይመስላል፡፡ መላ ሰውነቷ ላይ ተንቀዠቀዡ።

ሱሪውን ማውለቅ ጀመሬ በተንጋለለችበት በምሬት… ጭንቅላቷን አወራጨችው… እንባዋ ደረሰላት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ቢሮው ትዕግስቱ አልቋል፡፡” አለ ከቴልአቪቭ የገባው ይሁዳ አሚ
የብርቱካን ጭማቂውን ተጎንጭቶ ብርጭቆውን ካስቀመጠ ሰኋላ ረጅም
ጺሙን እየዳሰሰ፡፡

የአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴልኝ የመዋኛ ስፍራ በስተቀኛቸው አድርገው ተቀምጠዋል፡፡ በርካታ እንግዶች በመዋኛ ልብሶቻቸው ወዲያ ወዲህ ይላሉ፡፡ የተቀሩት በደረትና በጀርባቸው እየተገላበጡ ጭል ጭል የምትለውን ለስላሳ የጳጉሜ ፀሐይ ይሻማሉ፡፡

ይሁዳ አሚ በሆቴሉ ውስጥ ከያዘው የመኝታ ክፍል ወጥቶ ከቀጠሮኣቸው ስፍራ የደረሰው ልክ በሰዓቱ ነበር። ከቀጠሮው ሰዓት ቀደም ብሎ የደረሰው አሃሮን የእንግዳውን ፀባይ ስለሚያውቅ የብርቱካን ጭማቂ አዝዞ ከፊት ለፊቱ አስቀምጦ ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሚ የሌሊት ልብሱን ሳይቀይር በላዩ ላይ ወፍራም የጠዋት ልብሱን ደርቦ ወገቡ ላይ ቀበቶውን ሽብ አድርጎ ከጥጥ የተሰራ ወፍራም የእግር ሹራብና የቤት ነጠላ ጫማዐእንዳደረገ ወደ መዋኛው ስፍራ የሚወስደውን ደረጃ በእርጋታ ወርዶ ወደዐአሃሮን አመራ፡፡

“እንኳን ደህና መጣህ፡፡” አለ አሃሮን ተነስቶ እንደቆመ የአሚን እጅ
ጠበቅ አድርጎ እየጨበጠ፡፡

“እንኳን ደህና ጠበቅኸኝ።” አለ አሚ ነጫጭ ውብ ጥርሶቹን ለአንድ አፍታ ብልጭ አድርጎ የጓደኛውን እጅ እየወዘወዘ፡፡

አሚ “ ኪዶን” በሚል ስያሜ በሚታወቀው የሞሳድ ገዳይና አፋኝ
ክፍል ውስጥ ለአስራ ሰባት ዓመታት የሰራና አትግደል እና አትዋሽ
ከሚሉት ከሙሴ ትዕዛዛት በስተቀር በተቅሩት በስምንቱ ትዕዛዛት ላይ ፌዝ
የማያውቅ ጥብቅ ሃይማኖተኛ አይሁዳዊ ነው። በሌሊት ልብሱ ላይ የደረበው
ወፍራም የጠዋት ልብስና ቡፍ ካለ ጥጥ መሳይ የቤት ጫማው ጋር ሲያዩት
ጺማሙ ሰው በቤት ውስጥ ተቀምጦ የሳጠራ ዘንቢሉችን ሲሰራ የሚውል
የዋህ በሬ ይመስላል፡፡

“የብርቱካን ጭማቂ፡፡” አለ አሚ ፈገግ ብሉ ከጎኑ የቆመውን የሆቴሉን አስተናጋጅ እየተመለከተ፡፡

የአልኮል መጠጥ ፍጹም የማይቀምስና የአሳማ ስጋ አፉ የማይገባ ጥብቅ ሃይማኖተኛ የሆነው አሚ በመስከረም 5 1972 በሙኒክ ሃያኛው ኦሎምፒክ ዝግጅት ላይ የብላክ ሴፕቴምበር ቡድን የእሥራኤል ስፖርተኞችን ሰፈር በመውረር አስራ አንድ ተጨዋቾችን ከገደለ በኋላ የጠቅላይ ሚኒስትር ጎልዳሜይርን የብቀላ ትዕዛዝ
👍2
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....አፓርትመንቷ ጋ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ እጥፍ ብሎ ከአንድ ትንሽ ሻይ ቤት ገባና በሩ አጠገብ ካለ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሻይ አዘዘ፡፡ ጥንቃቄ ያስፈልጋል እርጋታ፡፡ ባሻገር የሚታየው የአፓርትመንቱ ቅጥር ግቢ አለቅጥ ጭር ብሏል፡፡ የወትሮው ግርግር ወጪና ገቢ አይታይም፡፡ ከአፓርትመንቱ ስር መኪናዎች በስርኣት ተደርድረው ቆመዋል፡፡ ለወትሮው ሲሯሯጠ የሚታዩ ሲጫወቱ የሚገኙ የአፓርትመንቱ ነዋሪዎች ልጆች በግቢው አይታዩም፡፡በር ላይ ብቻ እኛው የድሮው ሽማግሌ ዘበኛ አፈርማ ካፖርታቸውን ደርበው ከዘበኛዋ ቤት ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለው ያንጎላጃሉ፡፡

ይህ ነው ብሎ ምክንያት ሳይሰጠውም ፍርሃት ገባው፡፡ ፀጥታ ተራ ነገር አይደለም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሙሉ ፀጥታ አደጋ ከመድረሱ በፊት የሚያንዣብብ ማዘናጊያና አደጋው ከደረሰ በኋላ ድንጋጤን ደርቦ የሚንጠለጠል ግግርት ነው፡፡ ጥፍሩን መቆረጣጠም ጀመረ። ጭንቅላቱ ግራና ቀኝ ቆሞ ይሟገት ጀመር፡፡

ሰዓቱን ተመለከተ አሥራ ሁለት ከሃያ፡፡

ዝም ብዬ ነውኮ ይልቅ ብሎ ገብቼ እይቻት ብወጣ ይሻላል...ግን በአካባቢው የአውሬው አይን ቢኖርስ ስገባ ቢያየኝስ?ወዲያው ቢከቡኝስ ታዲያ እስከመቼ እዚህ ተቀምጨ እቆያለሁ?! ስልክ ደውዩ
ወንድሟን «ውጣ» ብለውስ ከአፓርትመንቱ እራቅ እንዲል ነግሬው
ባነጋግረውስ ምን ዋጋ አለው? ገብቼ ካላየኋትማ ለምንስ መጣሁ? ብገባ
ይሻላል... አዎ አይቻት ቶሉ እወጣለሁ… በአካባቢው ካሉ ግን ያለጥርጥር
እንደ ጅግራ ነው ክንፌን ብለው የሚጥሉኝ…ምን ዘዴ መፍጠር ይሻላል?

ጭንቅላቱን አፋጨው፡፡ አካባቢው እየጨለመ መጣ፡፡ የመንገድ
መብራቶች ቦግ ቦግ ቢሉም ደቂቃዎች በሄዱ ቁጥር ይበልጥ የሚደምቀውን
ጨለማ መታገል ማሸነፍ መግፈፍ እያቃታቸው መጠ፡፡ ናትናኤል ያለበትን
ክፍል ቃኘው፡፡ ትንሿ የሻይ ቤት ንጽህና የሌላት ናት፡፡ . በውስጧ የተሰበሰቡትም ሰዎች እሱው?እንዳጠለቀው በህይት የተጨማለቀ የጋራዥ ቱታ ቆሻሻ ልብስ የለበሱ ቀዝቅተኛ ኑሮ የሚገፉ፤ የሚጎትቱ እንደሆነ “ ያስታውቃሉ፡፡ ሰዓቱን ድጋሚ ተመለከተ፡፡ አስራ ሁለት ተኩል፡፡
በተቀመጠበት እንዳለ አሻግሮ የአፓርትመቱን መግቢያ በር ቃኘው፡፡ በሩቅ በድንግዝግዝ አንድ ሰው ይታየዋል፡፡ የበሩን አንድ ወገን መቃን ተደግፎ ቆሟል ሰውየወ:: ናትናኤል አትካር ተመለከተው፤ ካፖርት ለብሶ
አንገተዬውን ቀልብሶ የቆመውን ሰው ግን ሊለየው አልቻለም፡፡

'ብስራት ይሆን? መሆን አለበት። አሰበ፡፡
ተነስቶ ወደ አፓርትመንቱ መሄድ ግን ፈራ፡፡ ድጋሚ ዞር አለና እሱ ከተቀመጠበት ስፍራ ፈንጠር ብሎ ሁለት ክንዶቹን ጠረጴዛ ላይ ተክሎ
ጉንጭጮቹን በሁለት መዳፎቹ ደግፎ የተቀመጠ ጎረምሳ ላይ አተኮረ፡፡ አንድ
ዘዴ መጣለት:: ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ ወጣቱ ተጠጋ፡፡

“ሰላም...ልቀመጥ?” አለ ከወጣቱ ጠረጴዛ ዙሪያ ከተደረደሩት ሦስት
ወንበሮች አንዱን ያዝ ኣድርጎ፡፡

ወጣቱ ጉንጮቹን ዘሁለት መዳፎቹ ውስጥ ሳያወጣ አይኑን ብቻ
አቅንቶ ተመለከተው::

“ተቀመጥ:: አለ ወጣቱ ግድ እንደሌለው ለማሳየት ትከሻውን ከፍ ዝቅ አድርጎ፡፡

“እንድ የምትሰራልኝ ስራ ነበር፡፡ በቂ ገንዘብ እከፍልሃለሁ፡፡” አለ ናትናኤል ከኪሱ ቦርሳወን አውጥቶ ሁለት የአስር ብር ኖቶች እየመዘዘ፡፡

ከፊት ለፊቱ የተቀመጠው ወጣት ቀያዮቹን ኖቶች ሲመለከት ጉንጮቹን ለቀቅ አደረገና ቀና አለ፡፡ የደረበው ረጅም አሮጌ ኮት አንገትዬው ነትቧል፤ ከውስጥ ሸሚዞ በሽቅጧል፡፡

“ትስማማለህ?”
“ምንድነው የምሰራልህ? የሚደበደብ ሰው ከሆነ እርሳው፡፡” አለ ወጣቱ አገጩ ላይ ችፍርግ ብሎ የበቀለውን የቆሽሽ ጺም እያከከ፡፡

“አይደለም፡፡” አለ ናትናኤል ወደፊት ጠጋ ብሎ “እየው ያ ፎቅ ይታይሃል? በሩ ላይ የቆመው ሰውዬ ይታይሃል?”
ወጣቱ በ'አዎንታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡

“…ቀጥ ብለህ ወደ ሰውየው ትሄድና አጠገቡ ልትደርስ ጥቂት
እርምጃዎች ሲቀርህ ናትናኤል ይፈልግሃል። ተከተለኝ በለውና ድንገት
ፊትህን መልሰህ እየሮጥክ ከግቢው ወጥተህ ትመጣለህ፡፡”

“እናስ.. ከዛ በኋላስ?”
“በቃ::”
“እንዴት በቃ? እለ ወጣቱ ፊቱ ጥርጣሬ ለብሶ:: “እዛች ደርሼ ስለተመለስኩ ነው ይህን የምትሰጠኝ?” ወጣቱ፡፡ ዓይኖቹን በሁለቱ፡ የአስር ብር ኖቶች ላይ አነጣጠራቸው፡፡

“አዎ::"
“ምንም ሳልሰራ?”
“አዎ፡፡”
“አትቀልድ፡፡ ነገር አለው፡፡” አለ ጎረምሳው ወደ አንድ ወገን እየሳቀ፡፡

“ምንም ነገር የለውም፡፡”

ወጣቱ ኣይኖቸን አጥብቦ ናትናኤልን ሊያጠናው ሞከረ::
“ለምን እራስህ አትሄድም?"
“ትፈልጋለህ አትፈልግም?” አለ ናትናኤል ሁለቱን የአስር ብር ኖቶች ወደፊት እየገፋ::

ወጣቱ፡ ከራሱ ጋር ክርክር የገጠመ መሰለ፡፡ ናትናኤል ድንገት ትቶት ሲነሳ ፈጠን ብሎ አብሮት ተነሳ፡፡

“እሺ አምጣ፡፡ ፀጥ ብዬ ገብቼ ናትናኤል ያጠራሃል ብዬው ፀጥ ብዬ መወጣት ነው… እይደል?”

“እየሮጥክ ነው የምትወጣው፤ ፀጥ ብለህ አያደለም:: ልክ ከሰውየው እንደምትሸሽ ዓይነት እየሮጥክ፡፡” ናትናኤል ቆፍጠን አለ ሃያ ብር
የያዘውን ቀኝ እጁን ወደኋላ ሰብስቦ፡፡

“እሺ ኣምጣ…. እሮጣለሁ፡፡” አለ ወጣቱ እጁን ወደ ብሩ ዘርግቶ፡፡
“ደርስህ ስትመለስ…. መሮጥሀን ካየሁ በኋላ፡፡” ናትናኤል ፈርጠም አላ::

“እሺ ግማሹን ስጠኝ::”
“ደርሰህ ስትመለስ መሉው ያንተ ነው፡፡”
ወጣቱ ከሻይ ቤቷ ወጥቶ ወደ አፓርትመንቱ ሲያመራ ናትናኤል
ተከትሎት ወጣና የመኪና መንገዱን ተሻግሮ ከለላ ይዞ የሚሆነውን
ይከታተል ጀመር፡፡

የሚጠባበቁት ሰዎች ካሉ ወደ አፓርትመንቱ ሲገባ ሊይዘት ወጥመድ ያጠመዱ ካሉ። ወጥመዳቸው በወጣቱ ላይ እንደሚወነጨፍ እርግጠኛ ነበር፡፡

ወጣቱ የአፓርትመንቱን የአጥር ግቢ በር አልፎ ሲገባ ሽማግሌው ዘበኛ ከእንቅልፋቸው አልነቁም:: ወጣቱ እጆቹን የኮት ከሶቹ ውስጥ ከትቶ በእርጋታ አፓርትመንቱ በር ላይ ወደቆመው ሰው አመራ፡፡ ሰውዬውጋ ለመድረስ በግምት አአስር እርምጃዎች ሲቀሩት ድንገት ቆም አለና ናትናኤል እንዳዘዘው መልዕክቱን ተንፍሶ ፊቱን መልሶ ሮጥ ከማለቱ፡ ግራና ቀኝ ቆመው የነበሩ መኪናዎች በሮች እየተበረገዱ አራት ሰዎች ዱብ ዱብ አሉ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን አፍጥጦ ቀረ፡፡ በሁኔታው የተደናገጠው ወጣት
ለማምለጥ ቢሞክርም ከአጥር ግቢው በር ከመድረሱ በፊት ይዘው እፍስፍጥ
አድርገው ከአንደኛዋ መኪና ውስጥ ከተቱት፡፡

ለደቂቃዎች ናትናኤል ካለበት ሳይንቀሳቀስ ተጠባበቀ፡፡ ወዲያው
የመኪናዋ በር ተከፈተና በሁለት በኩል የወጣቱን ክንዶች የልጨመደዱ ሁለት
ሰዎችና ሌሎች ተጨጨማሪ ሶስት ሰዎች ወደ አፓርትመንቱ፡ ግቢ በር ያጣደፉ ጀመር፡፡ ከአፓርትመንቱ፡ ግቢ ሲወጡ ናትናኤል ወደ ኋላ አፈገፈገና ጥሩ ከለላ ይዞ በሩቁ በአይኑ ያስተውላቸው ጀመር::

አምስቱ ሰዎች ወጣቱን ከበው ወደ ሻይ ቤቷ ተጣደፉ፡፡ ከሻይ ቤቷ ደጃፍ፡ እንደደረሱ ሀለቱ ልጁን አስቀድመን ከተል ብለው ሲገቡ ሁለቱ፡፡ በሻይ ቤቷ ጓሮ ዞሩ፡፡ የተቀረው አምስተኛው እፊት ለፊት ጀርባውን ግድግዳው ላያ ለጥፎ ቀኝ እጁን ከኮቱ፡ ስር ብብቱ ስር ከቶ ቆመ::

ናትናኤል ሰውየው ከኮቱ ስር የጨበጠው ምን እንደሆነ ሲረዳ አብርሃም ታወሰው፡፡ ሻይ ቤቷ ውስጥ የቡት ሰዎች ከውስጥ ሲያጡት ወጥተው አካበቢውን ሊያስሱ እንደሚችሉ ሲረዳ ፈጠን ብሎ ከተደበቀበት ወጣና ሽቅብ በሩጫ ተፈተለኩ ታክሲ ተራ ደርሶ ለገሃር ብሎ ታክሲው ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ሁሉ ሁለት ሦስቴ እየተገላመጠ ተመለከተ፡፡ ከጀርባው የተከተለው ሰው ግን አልነበረም፡፡ ወደኋላ መመለስ
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....በለሃጩ አጨማለቃት፡፡ራቁት ገላውን እራቁት ገላዋ ላይ እንደቁንቡርስ አንደባለለው፤ መላ ፊቷን በሚርገበገብ ከንፈሩና በምላሱ አልኮሰኮሰው፤ እጆቿንና እግሮቿን ከአልጋው ጠርዞች ጋር እንደተጠፈሩ አፍዋ በቡትቶ ታጭቆ እንደተጎስጎስ በተንጋለለችበት ጥያፌዋን፣ ምሬቷን ሰውነቷን እያወራጨች አሳየችው፡፡

ግድ አልነበረውም...

በከርዳዳ ጺም የተሸፈነ ፊቱን ከፊቷ ላይ አንስቶ እስረኛው ምርኮኛው በሆነው ከስሩ በተንጋለለላት ገላዋ ላይ አንቀዋለሰው፣ አይን አዋጅ ሆነበት:: ..በደመነፍስ ያዳብሳት ጀመር፡፡ በል..በል የሚለውን ግፊት፤

ሂድ..ሂድ የሚለውን ስካር ሩጥ..ሩጥ የሚለውን እብደት ጥድፊያ አምቆ
መቆየቱ ጣፋጭ የስቃይ ስሜት ፈጠረለት፡፡ ከረሜላውን ከአፉ ከትቶ
ኮረሻሽሞ ጎረዳድሞ ከመዋጡ በፊት፣ የጎረሰውን ከረሜላ እየመላለሰ በመዳፉ
ላያ እየተፋ በስስት በስቃይ ስሜት እያየ ቀስቃዩ በሰቀቀኑ እንደሚደሰት ህፃን
የጓጓለትን የተንቀዋለለለትን ገላዋን ከስሩ አጋድሞ ተሰቃየ ለራቁት ገላዋ
ሳሳለት፡፡

ፂማም ፊቱን ወደ ደረቷ አስጠግቶ በጡቶቿ መሃል ወደቀ፡፡ሳያጎረድማት መጠጣት፤ ሳይኮረሽማት ላሳት፤ መልሶ ከአፉ አውጥቶ ተመለከታት::አውሬ ሆነች፡፡ ጥላቻዋ እየጨመረ. ምሬታ እየኮረረ. እልኋ እየጋመ በመጣ ቁጥር የልቡ ምት እየጨመረና ትንፋሹ እየተፋጀ መጣ ሰውነቱ በላብ አሙለጨለጨ ፊቱን ከጡቶቿ መሃል አውጥቶ ቁልቁል
አዘገመ...

ወገቧን ሰብቃ ሰደበችው ፧ ሽንጧን እያላጋች ረገመችው፧ ጭኖቿን
እያማታች ተፋችው

ደስታው ወሰን አጣ…

ጎንበስ ብሎ የሚወራጭ . አካሏን በለሀጩ በራሱ ከንፈሮቹ ተረከበው:: እንደ እንፋሎት የሚጋረፍ፡ ትንፋሹ ለስላሳ ቆዳዋን ፈጃት ፡ ለበለባት:: ህሊናቸውን መሳት የጀመሩ ደዳራ ጣቶቹ የሴት አካልዋን በጭካኔ አፍረጠረጡት፡፡

በሩ ተበረገደ፡፡

በጉልበቶቿ መሃል እንደተንበረከከ በድንጋጤ ፊቱን ወደጀርባው መነጨቀው የተመለከተውን አልወደደውም፡፡ በር ላይ በድን ይመስል የተገተረው ሰው የሚያየውን ትርዒት ለመረዳት ጊዜ ፈጀበት:: የሚመለከተው እየተገለጸለት ሲሄድ በእልህ ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡

“ጠርጥሬሃለሁ! አንት ውሻ ጠርጥሬሃለሁ!” አለ ማርቆስ በሩን
ለቅቆ ወደ ክፍሉ ከመግባቱ በፊት ከኮቱ ስር ሽጉጡን ላጥ አድርጎ አቀባብሎ
እላይዋ ላይ በተከመረባት ሰው ላይ እየደገነ። “እንዳትነቃነቅ... ከዚያ አልጋ
ላይ ለመውረድ ሞክርና እንደ ውሻ እገድልሃለሁ!” አለ ማርቆስ ሽጉጠን
እንደደገነ ወደ ስልኩ እያመራ፡፡ “ትንሽ ተነቃነቅና ምክንያት ስጠኝ ግንድህን አጋድምሃለሁ!” በቀኝ የያዘውን ሬድዮ ወደ አፉ ኣስጠግቶ ተናገረ።
“ሃሎ… ቆንጆዎቹ ቡድን ለ... አስቸኳይ ነው... ዜሮ አራት” ለጥቂት ደቂቃዎች ዝም አለ፡፡ “ቁጥር አንድ ጋር አገናኝኝ፡፡” የሬዲዮ መገናኛውን በግራው እንደጨበጠ በቀኙ የያዘውን ሽጉጥ እላይዋ ላይ በተከመረው ሰው
ላይ ደግኖ ተጠባበቀ፡፡ “ሃሎ …ዜሮ አራት በፍጥነት እፈልግሃለሁ… እዚሁ
ድረስ… ሌላ ሰው አይደለም አንተ ራስህ ተገኝታህ መመልከት አለብህ።”
አነጋግሮ ሊያበቃ ስልኩን ዘግቶ ሽጉጡን ወደፊት ኣስቀድሞ ወደ አልጋው
ተጠጋ፡፡

“ጉድህን እናየዋለን” አለ ማርቆስ ጺማሙን ሰውዬ በጥላቻ
እየተመለከተ፡፡

“ይቅርታ አድርግልኝ ማርቆስ፡፡ ሌላው ይቅር ልብሴን ልልበስ፡፡” አለ ሰውየው በጭኖቿ መሃል እራቁቱን እንደተንበረከከ በልምምጥ ፊት ማርቆስን እየተመለከተው፡፡

“ከማነው ሃጢያታችንን የምንሸሽገው? ለዓመታት አንዳችን የአንዳችንን ሃጢያት እንዳናይ የገዛ ሃጢያታችን እንዳይታይ ፊታችንን ስንመላለስ ቆይተናል፡፡ ከአሁን ወዲያ ግን ገበናችን መገለጥ አለበት፡፡
ከኃጢያታችን እራቁታችንን መተያየት አለብን። : እውነት ተሽፋፍና ተጀቧቡና አትኖርም፡፡ እራቁቷን ነው የምታምር፡፡” በዕልህ ተንቀጠቀጠ፡፡
“እራቁቷን!”

“ማርቆስ ልብህ ይራራ… ሁላችን እንሳሳታለን… ማረኝ፡”

"ማነው አውሬ… ለተናካሽ እውሬ የሚራራ? ቀሚሷን ገልበው እርቃኗን አንጋለው ለሚያረክሷት፣ ጭኖቿን በርግደው ሴትነቷን አጋልጠው ለባእድ
ለሚሽጧት አፍሪካ ርህራሄ አይኖራትም፡፡ ምህረት ምንድነው? በየዋህነት ለቸረቸራችሁ፣ በልበ ገርነቷ ለሽረሞጣችሁ፣ በድንግልናዋ ላቃጠራችሁ ምህረት ምንድነው? አፍሪካ መቼ ነው ቀሚሷን ዝቅ የምታደርግ፣ ጭኖቿን የምትሰበስብ፣ እፍረቷን የምትሸፍን? እናንተ ስትጠረጉ ብቻ ነው! ምህረት አያሻም! ራቁታችንን መተያየት አለብን!”

የክፍሉ በር ከጀርባው ሲበረገድ የተንበረከከው ጺማም ሰው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የቢሮውን በር በርግዶ ሲገባ ብርጋድየር ጀኔራሉ ከጠረጴዛው ጀርባ እንደተቀመጠ አፍጥጦ ተመለከተው፡፡
“ያዝነው!” አለ ማርቆስ ትንፍስ ትንፍስ እያል፡፡
“ናትናኤልን?” አለ ጀኔራሉ የሰማውን ለማረጋገጥ፡፡
“አዎ፡፡” አለ ማርቆስ ጭንቅላቱን ነቅንቆ ፀጉሩን እየደባበሰ፡፡
“ብታምነኝም ባታምነኝም እራሴን እስከምጠላ ተስፋ ቆርጬ ነበር፡፡”

“እንዴት ያዝስከው? ማለቴ የት?” አለ ጀኔራሉ ማርቆስን ተቀመጥ ሳይለው በቆመበት እንዳፈጠጠበት፡፡

“ባቡር ላይ፡፡” አለ ማርቆስ ወደፊት ተራምዶ ወንበር ላይ እየተቀመጠ፡፡ “ዛሬ ማታ ወደ ድሬዳዋ ለመሄድ ባቡር ላይ ሲሳፈር እዛ የመደብኳቸው ሁለት ሠራተኞቼ አይተውት አብረውት ተሳፍረዋል፡፡”

“ወደ ድሬዳዋ ተሳፍራል ነው የምትለኝ? ያዝኩት ያልከኝ መስሎኝ ነበር'ኮ፡፡” አለ ጀኔሪሉ ፊቱን አኮሳትሮ “መከታተሉ ምንድነው ትርጉሙ ለምን ቀጥታ አላስወገድከውም? "

“አታስብ... ከአዲስ አበባ እስከ ድሬዳዋ ያሉትን ጣቢያዎች በሙሉ በሰዎቻችን ሸኛቸዋለሁ፡፡”

“ባበሩ ሳያነሳ ለምን አልያዝከውም
“ጀኔራል ሰውየው ትኬት ሲቆርጥ ሰዎቻችን አላዩትም፡፡ ምናልባት
በሌላ ሰው እስቆርጦም ሊሆን ይችላል:: ድንገት ባቡር ላይ ሲሳፈር ያዩ ሠራተኞቼ ምርጫ ስላልነበራቸt ስልክ ደውለው ሲያስታወቀኝ ባበር ጣቢያ ውስጥ አስወጋጅ ሃያል ስላልነበረ ተከትለውት እንዲሳፈሩ አዘዝኳቸው።

ታዲያ ምኑን ነው ያዝኩት የምትለኝ?”

“ከዚህ ወድያ ሊያመልጥ አይችልም:: በየትኛውም ጣበያ ቢወርድ
ከማንም ጋር ከመገናኘቱ በፊት እንዲያስወግዱት ትዕዛዝ አስተላልፌአለሁ::”አለ ማርቆስ በፍጹም እርጋታ:: “በየጣብያው የሚጠባበቁት ሰዎች አሉ።

“አንተ ራስህ ለምን ድሬዳዋ በረህ አትጠብቀውም? የምልህ ይህን
ሰው አደገኛ ነው ጀኔራሉ ተረበሸ… “አንተ ራስህ ቀድመህ ብትጠበቀው
እመርጣለሁ:::”
“አንድ ሄሊኮፕተር እዛጋጅቼ እየተጠባበቅሁ ነው… ቀጥታ ወደ
ድሬዳዋ እንዳልበር ምናልባት በመሃል ሊወርድ ስለሚችል ባቡሩ እያንዳንዱን
ጣቢያ ሲያልፍ፡-የጣቢያው ያሉ ሰዎች የሬድዮ መልዕክት እያስተላለፉልኝ
እየጠበቅሁ ነው::”

“የት ነው ያለው ኣሁን?” አላ ጀኔራሉ በጉጉት፡፡
“ባቡሩ ናዝሬትን ማለፉን :: እንዳረጋገጥኩ ነው ወዳንተ የመጣሁት:: አላ ማርቆስ፡፡

ማርቆስ!” አለ ጀኔራሉ ፊቱ በጭንቀት ተወሮ፡፡ “ይህ አካሄድህ አላማረኝም እንበልና ይህ ሰው በሁለት ጣቢያዎች መሃል ከባቡሩ ቢዘል ምን ልታደርግ ነው? ከቦታው ላይ ምን ያህል ዘግይተህ እንደምትደርስ አታውቅም?”

“አብረውት የተሳፈሩት ሰዎች የነፍስ ወከፍ መሳሪያ የታወቁ ናቸው፡፡”

“የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ይታጠቁ እንጂ ለዚህ ሥራ የሰለጠነና የተዘጋጁ አይመስሉኝም። ተራ የክትትል አባላት ናቸው… አይደለም?” አለ ጀኔራሉ ጠረጴዛውን ቡጢ ደልቆ፡፡

“እርግጥ የክትትል ሠራተኞች ናቸው ግን”

ማርቆስ! ማርቆስ! ምን እየሰራህ ነው?
👍3