አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።

“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?

"አራት ዓመት!”

"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "

“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።

“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”

“ሒድ'ደረቅ ! ”

ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !

"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።

የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።

“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”

ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””

“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ

“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።

“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።

«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።

“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።

“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!

እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !

“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።

ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::

ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።

ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”

ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።

“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «

“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች

“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”

ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "

እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...

“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡

በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..

"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
👍21
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

..... የረር ጎታ ሲቃረቡ ነበር ሲቲና ከእንቅልፏ የተነሳችው፡፡

“ለምን አትተኛም ነበር? ቀንኮ ይደክምሃል» አለችው:: እንቅልፍ
ያሳቀጣቸውን ጉንጮቿን እያሻሸች::

“ተመችቶሽ ተኛሽ? ” አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመሰግናለህ፡፡ የሚመች ትከሻ አላህ፡፡” አለች እየሳቀች፡፡ ጎንበስ ብላ ከሻንጣዋ ውስጥ ሎሚ አወጣችና አንድ ለእሱ አንድ ለራሷ ወሰደች::
“ሎማ ያነቃቃል፤ ታውቃለሁ? " አለች የያዘችውን ሎሚ እየመጠጠች፡፡

ድሬዳዋ ለገሃሬ ደርሰው ከባቡሩ ሲወርዱ ናትናኤል ተደነጋገረው:: የባቡር ጣቢያው በሰው ተጨናንቋል፡፡ አንድ እርምጃ ለመራመድ ሁለት ሦስት ሰዎች መገፍተር አለባቸው:: ሰው የት ወደየት እንደሚሄድ መለየት ያስቸግራል፡፡ ብቻ ባለበት ይተራመሳል፧ ይገፋፋል ፧ ይታሻሽል። ከኋላው ተቀምጣ የነበረችው ሴት አብሯት ከተቀመጠው ተሳፋሪ ጋር እያወራች ስትወርድ ዞሮ ተመሰክታት:: አብሯትት ካለው ሰው ጋር ታውራ እንጂ
አይኖቿ ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ እርግጠኛ ነው... ከዚህ ቀደም አያቷታል፡፡

“የት ነው የምታርፈው አለችው
ሲቲና ቀደማ ከባበሩ እየወረደች::

“እ… አልወሰንኩም።” አላት ከጀርባው ተቀምጣ የነበረችውን ሴት ማንነት ለማስታወስ እየጣረ:: እርግጠኛ ነው.. መልኳን ያውቀዋል ግን ራቀበት፡፡
“ማለቴ ዘመድ ጋ ነው... ወይስ ሆቴል?” አለችው ሲቲና::ድንገት ብልጭ ሲልለት ድጋሚ ፊቱን ወደ ሴትየዋ አዙሮ ተመለከታት፡፡ የአብርሃም ሠራተኛ! ዞሮ ተመስከታት:: ሳያውቀው ዓይን ለዓይን ተጋጩ፡፡ ቀድማው ፊቷን መለሰች:: ሴትየዋ ቀድሞ ካላያቸው ሁለት ሰዎች ጋር ስታወራ ተመለከተ፡፡

“እ..ምን አልሺኝ? አይ…. ሆቴል ነው የማርፈው ለጊዜው፡፡” አለ ፊቱን ወደ ስቲና መልሶ፡፡

“ከፈለግህ እኔጋ ማረፍ ትችላለህ፡ባዶ ቤት ነው ያለሁት፡፡”
“እ... አለ አሁንም ፊቱን መልሶ የአብርሃምን ሠራተኛ ባየበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ ዓይኑን የምትሸሽ መሰለው፡፡ አብረዋት የነበሩት ሦስት ሰዎች በአጠገቧ የሉም፡፡ ሴትየዋ ብቻዋን ጥግ ይዛ ቆማለች፡፡

«ማለቴ ለሁለት ለሦስት ቀን ችግር የለም ማለቴ ነው፡» ከጎኑ ከጎኑ እየሄደች አንገቷን አቀርቅራ ተናገረችው ሲቲና፡፡

ከሰው ግፊያ ወጣ ብለው ወደዳር ላይ የያዟቸውን ሻንጣዎች ከመሬት ላይ አሳርፎ ቀና ሲል ባሻገር ተመለከታት፡፡ ሴትየዋ አሁንም ታየዋለች:: ምናልባት የት እንያምታውቀኝ ጠፍቷት ይሆናል።" ብሎ አሰበ፡፡

“አስቸግርሽ እንደሆነ…” አለ ፊቱን ወደ ሲቲና መልሶ፡፡
“በፍጹም፡፡” አለች ፊቷ በሃፍረት እየቀላ፡፡
“እ... ” ናትናኤል አመነታ፡፡ ሆቴል አለመያዙ ከዓይን የሚያድነው ብቻ ሳይሆን ገንዘብም የሚቆጥብለት ነው፡፡ ግን ይቺን ልጅ ተከትሎ ከቤቷ ሄዶ ምን እንደሚከተል ለማወቅ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ መቼም ምሳና እራት ሊያባላት ወይ ለነፍሷ ብላ እንዳላስጠጋችው ግልጽ ነው፡፡ ግን ቢሆንስ እንዴት ድንገት ልታቀርበው ፈለገች? “ምን መሰለሽ…” አለ ግብዣዋን
እምቢ የሚልበት ዘዴ ጠፍቶት ኣቧራ ያበላሸውን ነጭ ጀለቢያውን
እያራገፈ፡፡

“አስቸግራታለሁ ብለህ አስበህ ከሆነ ምንም ችግር የለም፡፡ ባዶ ቤት ነው ከፍቼ የምገባው:: ወላሂ አልኩህ፡፡”

“እስቲ እየሄድን እናውራ፡፡” አለ ናትናኤል - የሰው ትፍግፍግ ማለትና የአየሩ ሙቀት ትንፋሽ ቢያሳጥረው።

ጎንበስ ብሎ ሻንጣውን ሲያነሳ ከጎኑ ቆማ የነበረችው ሲቲና ገፍትራ ከመሬት ደባለቀችው፡፡ መሬት ላይ ሁለቴ ተንኮበሉ ቀና ሲል ነበር ነገሩ ጭንቅላቱን የመታው ከጀርባወ ቆመው የነበሩ አንድ አዛውንት በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ወደ ሠሬት ሲያዘቅጡ አያኖቹን አፍጥጦ
ተመለከታቸው!” እሪ አለች ከጎናቸው የነበረች ወጣት ሴት፡፡ ከወደቀበት
ለመነሳት ሲጣደፍ ሲቲና ሸብረክ ብላ ከተከናነበችው ድሪያ ስር ሽጉጥ
መዥረጥ ስታደርግ አያት:: ተቀደመች:: የያዘችው ሽጉጥ እጇ ወስጥ ተፈናጥሮ ሲወረወር እሷ ደረቷን አፍና ወደ ኋላዋ ወደቀች.. ዙሪያውን ረብሻ ሆነ... ጩኸት... ሩጫ.. ኡኡታ... ቶክስ እሪታ ዙሪያወን አደባለቀው..ናትናኤል ከአንገቷ ቀና አደረጋት...

«ሩ...ጥ! ተክትለውሃል... ሩጥ!» አለችው በግራ እጇ በደም የተዘፈቀውን ደረቷን አፍና እንደያዘች ሲር ሲር ከሚለው ትንፋሿ እየቆነጠበች ‹‹ ሩጥ!»

ቀና ሲል አየው:: የጨበጠውን ሽጉጥ ከትከሻው በላይ ይዞ ከፊቱ የሚጋረጡትን ሰዎች አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየገፋ እየገፈታተረ ወደ እሱ እየቀረበ ሲመጣ በሚተራመሰው ሕዝብ መሃል በሩቁ አየሁ
ከአብርሃም ሠራተኛ ጋር የነበረውን አንድ ሰውዬ! እንደ ጥንቸል ተፈናጥሮ ከሚደነባበረው ከሚራበሸው ሕዝብ መሃል እየተሹለከለከ በትርምሱ ውስጥ
ሰመጠ... የአብርሃም ሠራተኛ! የፈጣሪ ያለህ! የአብርሃም ሠራተኛ! ከራሱ ጋር እያነበነበ ሮጠ፡፡ ከጀርባው የተኩስ እሩምታ አጀበው::

ወዴት እንደሚሮጥ.. የት እንደሚደርስ ግድ አልነበረውም:: ብቻ ሮጠ፡፡ እራቅ እንዳለ በሩቁ እንዳይለዩት ጭንቅላቱ ላይ የጠመጠመውን ሽርጡን አውልቆ በእጁ ያዘው:: ትንሽ ከራቀ በኋላ ደግሞ ወደ ጥግ ዞር አለና ጀለቢያውን አውልቆ ወርውሮ ከወገቡ በታች ሽርጡን አጥልቆ ከላይ ነጭ ሸሚዙን እንዳደረገ ከራሱ ጋር እያጉተመተመ ሮጠ፡፡ የአብርሃም
ሠሪተኛ! እንዴት ሊከተሉት ቻሉ? ወደ ድሬዳዋ መምጣቱንስ እንደት አወቁ? ሲቲና ባትገፈትረው'ኮ ወደፊቱ ሲወድቅ ባይስቱት'ኮ.. ' በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ያዘቀጡት ሽማግሌ ታዩት:: የፈጣሪ ያለህ! ገለውት ነበር'ኮ የአብርሃም ሠራተኛ! ወያኔ አብርሃም! ለካ ሳያውቀው!

ሲቲና ማነች? ሩጥ…ተከትለውሃል ሩጥ የምስራችን የገደለቻት ሴት ምንድን ነበር ያለችው? ሩጥ!' ሲቲና ማነች? የፈጣሪ ያለህ! ሁሉ ነገር ተወሳሰበበት:: ማሰቡን አቁሞ ሩጫውን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ያለበት ቦታ የት እንደሆነ ለመረዳት አልቻለም፡፡ በስተግራው መደዳ የተሰሩ ቤቶች ማስታወቂያዎቻቸውን በየቢሮዎቻቸው ላይ እንዳንጠለጠሉ ተደርድረዋል:: ፈቶግራፍ ቤት..የልብስ ሰፊ...ስዓት ማደሻ..በስተቀኙ ደግሞ በረንዳው ላይ የሳጠራ ወንበሮች የተደረደሩበት በሐረግ የተሸፈነ በረንዳ ያለው ቤት ይታያል ድሪዳዋ፡፡

ወደ ቡና ቤቱ፡ ተጠጋና አካባቢያን ለማጥናት ሞክረ፡፡ የፊተኛው ክፍል ሰፊ ቢሆንም ጨለምለም ያለ ነው፡፡ ፈጠን አለና ወደ ውስጥ ገባ፡፡በትናንሽ ጠረጴዛዎች ዙሪያ የተኮለኮሉ ትናንሽ የብረት ወንበሮች ፈንጠር ፈንጠር ብለው ክብ ክብ ሰርተዋል፡፡ በጋዝ የተወለወለው የሲሚንቶ ወለል ቢያብለጨልጭም ሽታው ይከብዳል:: ቁርስ የሚያቂርጉ የቡና ቤቱ ደንበኞች በየወንበሮቻቸው ተቀምጠሁ ያዘዙትን ይስተናግዳሉ፡፡

ባዶ ወረጴዛ ፈለገና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡

“ምን ልታዘዝም ! በስተቀኝ የተንዘላዘለ ፀጉሯን ጣቷ ላይ እየጠመጠመች እየፈታች ጠየቀችው::

ሻይ አላት ቶሎ ለመገላገል፡፡ ፊቷን መልሳ ሄደች፡፡ ናትናኤል ከራሱ ጋር ምክክር ቀጠለ።

ጊዜ የለውም:: መፍጠን አለበት:: አለበለዚያ ያገኙታል በማያውቀው ከተማ ውስጥ ተደብቆ መቆየት ዘበት ነው ግን እንዴት ተከተሉት? ከርብቃ ቤት አምልጦ ሲሮጥ ተከትለውት ነበር ማለት ነው?
መሆን አለበት፡፡ የአብርሃምስ የቤት ሰራተኛ እዚህ ምን አመጣት? ወይኔ!
አብርሃምን ትከታተለው ነበር ማለት ነው! አሁን ደግሞ

የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዘውን ሻይ አምጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት::

እባክሽ የእኔ እመቤት የስልክ ቁጥር ማውጫ ደብተር ይኖራችኋል? “ አላት

“ይቅርታ የለንም ለምን ማዞሪያ አይጠይቁም
👍1
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

ድርጅት የእገታ ማስለቀቂያውን የገንዘብ ክፍያ ከታጋች ቤተሰብ ተቀብለው እና ድርሻቸውን ቆርጠው ለአጋቾች እንደሚሰጡ ነው፡፡ ይሄ ደግሞ አንደኛው የቢዝነስ አካሄድ ነው፡፡ ሌላኛው ነገር ደግሞ ራሳቸው የወሮበላ ቡድኖቹ አብረዋቸው የሚሰሩ ሰዎቻቸውን ወደ አሜሪካ ከገቡ በኋላ በአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች ላይ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው ጥበቃ ከሚደረግላቸው ሰዎች መዝገብ ውስጥ እንዲገቡ ታስደርግላቸዋለች፡፡ ይሄ ደግሞ የሚያሳየው እሷን የሚያግዝ የመንግስት አካል ከውስጥ እንዳላት ነው።

“ከፖሊሶች ውስጥ ማለት ነው?” ብላ ኒኪ ጠየቀች፡፡ ዊሊያምስም ትንሽ ፈገግ አለና “አትገረሚ፡፡ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ ከባድ ልብስ ሲሰቀልበት እንደሚረግብ አሮጌ የልብስ መስቀያ ሆኗል፡፡ ሌላው ደግሞ የጠፉ ልጆችን በህገወጥ መንገድ ከሚያዘዋውሩ ሰዎች እጅ ውስጥ እንደሚገቡ ነው፤ እነዚህ በአየር
መንገዱ የተጠለፉ ህፃናት እና ወጣት ሴቶችም ለሩሲያ የወሲብ ንግድ
አስማሪ የወርበሎች ቡድን ይሸጣሉ የሚል መረጃ አለኝ፡፡ ይህንንም
ላረጋግጥልሽ አልችልም ግን ያው ውስጥ ለውስጥ የሚወራ ነገር ነው፡፡” ኒኪም አይኗን ገርጥጣ “እና ቻርሎቴ ክላንሲ...?” ዊሊያምም ራሱን በአሉታ
ነቅንቆ “አይመስለኝም፤ የወሲብ ንግድ የሚሰሩ ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ
በየሀገሩ የሚያዘዋውሩ ቢዝነሶች አነስተኛ ገቢ ነው ያላቸው፡፡ ቤተሰቦቻቸው
አጥብቀው የማይፈልጓቸውን ህፃናት ወንዶችና ሴቶችን ነው በዚህ ሥራ ላይ
የሚያሰማሩት፡፡ ስለዚህ አንዲት የ18 ዓመት ዕድሜ ሴትን በዚህ ቢዝነስ
ውስጥ ማሰራታቸው ይጎዳቸዋል እንጂ አይጠቅማቸውም፡፡ ብቻ በአንድም
ሆነ በሌላ መልኩ ይህ የቫላንቲና ቡድን ድርጅት ከፊት ለፊቱ የጠፉ ሰዎችን
የሚያፈላልግ መስሎ ከጀርባ ግን የሚፈልጉትን ሥራ ይሰራሉ። በቫላንቲና
ባደን የበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥም ሌሎች የበጎ አድራጎት ድርጅቶች
ከሚያገኙት (ከሚያስጭኑት) ገንዘብ እጅግ በጣም የላቀ ገንዘብን ያስገባል።”
አላት፡፡

ኒኪ በዝምታ ውስጥ ሆና ዊሊያምስ በወሬ ሰማሁ ያላትን ጓደኛዋ ግሬንቸን እና ገና በወጣትነቷ እህቷን ያጣችውን ቫላንቲና ባደንን ከዚህ ቡድን ጋር ማጣመር አቃታት፡፡ እርግጥ ነው ሁሉም በዙሪያዋ የሚገኙ ሰዎች በመንፈስና በምግባር ጥንካሬ እየለሰለሱ መሆናቸውን እያየች ቢሆንም ዊሊያምን ተሳስተሃል ለማለት ተቸገረች፡፡

“በማንኛውም መልኩ” ብሎ ዊልያምስ በመሀከላቸው ያለውን ዝምታ ሰበረ እና “ሚስ ባደን እዚህ ነገር ተግባር ላይ እንድትገኝ የሚያደርገው የምትገኘው ዋነኛው ስው ሉዊስ ሮድሪጌዝ ነው፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ደግሞ ትኩረቱን ከኮኬይን ላይ አንስቶ ክሮክ ላይ አድርጓል። በዚህም
የኤል.ኤን የዕፅ ገበያን ከሩሲያኖቹ ለመንጠቅ አጥብቀው እየሰሩ ይገኛሉ።
እዚህ ከተማ ውስጥ በጣም ብዙ ሰዎች አሉት። በቃ እነርሱ ልክ እንደ ወረርሽኝ ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛሉ።” አላት፡፡

ዊልያምስ እነርሱ እንደ ወረርሽኝ ሁሉም ቦታ ላይ ይገኛሉ ብሎ የተናገረውን ነገር ስትሰማ ካርተርን አስታወሰች፡፡ ምክንያቱም ቀን ላይ ካርተር ይገድሉኛል ብሎ ስለሚፈራቸው ሜክሲካውያን ሲነግራት የገለፀላት በዚሁ መንገድ ነበር። ስለዚህ የካርተርን ሀሳብ ማመን ይኖርብኝ ይሆን?”

“ሌላ ግንኙነት። ሌላ የጭለማ ውስጥ የሸረሪት ድር”

ከዚህ የጥልፍልፎሽ ሀሳብ ውስጥ በጠራ አዕምሮ ማሰብ ፈልጋም “እሺ ሉዊስ ያደንዥ ዕፅ ቢዝነስ ውስጥ አለበት እንበል። ግን አኔ ስለዚህ ነገር
ታውቃለች?” ብላ ዊልያምስን ጠየቀችው፡፡

“ሉዊስ የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ እንደሚሰራ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ይህቺ ሚስቱ ይሄን ሁሉ ገንዘብ ከየት እንደሚያመጣው ትወቅ አትወቅ ግን እርግጠኛ አይደለሁም። አንቺ ስለእሷ ከነገርሺኝ ነገር በመነሳት ግን እሷ ይህንን ነገር የምታውቅ አይመስለኝም:: ምክንያቱም ሮድሪጌዝ ሁለት ስብእና ያለው ሰው ነው፡፡ ቢዝነሱን ከግላዊ ኑሮው ለይቶ ማስኬድ ይችላል።”

ይህንንማ ለአኔ መንገር አለብኝ ብላ አሰበች በውስጧ፡፡ ኒኪ የእሷ ባል
ማን እንደሆነ የማወቅ መብት አላት። እያንዳንዷ ሚስት ይህ መብት ሊኖራት ይገባል። እየተዋሸች መኖር የለባትም። ብላ አሰበች፡፡

“እሺ ይህንን የእሱን ሥራ ፖሊሶች ያውቁታል ብለኸኛል? እዚህ
የኤል.ኤ. ፖሊስ እና የኤፍ.ቢ.አይ ሰዎችም ስለ ጉዳዩ ያውቃሉ?”

“በደንብ ነዋ” ብሎ ዊሊያምስ ፈገግ አለ እና ባይገርምሽ የኤሌ.ኤ.ፒ.ዲ የፀረ አደንዛዥ ዕፅ የምርመራ ቡድን ስለ ዴላ ሮዛ እና ስለ ሮድሪጌዝ ክምር ዶሴዎች ሁሉ ሳይኖራቸው ይቀራል ብለሽ ነው?”

“ይሄ ንፁህ የተባለው ክሮክ ከየት እንደሚመጣ በደንብ ያውቁታል።
ምናልባትም ሩሲያውያን ይህንን ሥራ ከሚሰሩት ሜክሲካውያን እንዲሰሩት
ፈልገውም ይሆናል ዝም የሚሉት፡፡ አልያም ደግሞ አንድ ትልቅ የፖሊስ
አለቃ ከእያንዳንዱ የአደንዛዥ ዕፁ ሽያጭ ላይ የሚቆረጥለት ነገር አለ ማለት
ነው።”
ኒክም የሰማችውን ነገር ለጥቂት ሰኮንዶች ያህል ስታመነዥክ ቆየች እና
“አንተ የምትለው ፖሊሶቹ እዚህ ድርድር ውስጥ አሉበት ነው? ማለቴ ልክ
የጠፉ ሰዎችን አፈላላጊ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ እንደሚያደርገው ማለት
ነው?”

“አዎን እንደዚያ ነው ብዬ አምናለሁ” አላት እና ዊሊያምስ በመቀጠልም ፖሊሶቹ እናም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች እዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ሽያጭ ላይ ይኖሩበታል፡፡ ሮድሪጌዝ ደግሞ ልክ ሜክሲኮ ውስጥ ሲያደርግ የነበረውን
ነገር እዚህም በማድረግ ላይ ይገኛል። ወንዶችን ማፍራት፣ በእጅ መሄድን
ያውቅበታል። በዚያ ላይ ደግሞ በአደንዛዥ ዕፅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ለድሆችም የልገሳ እጁን በስፋት በመዘርጋት ላይ ይገኛል።”

ሃሳቡን እየተናገረ እያለ ኒኪ በትኩረት ስትከታተለው ስላየ ከተጣላችኝም
ይለይለት አለና “የሜክሲኮ አደንዛዥ ዕፅ አምራቾች ከትሬይ እና ከሊዛ ፍላንገን ግድያዎች በስተጀርባ እንደሚገኝ አልጠራጠርም፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ
ምናልባትም በባለቤትሽም ግድያ ላይ እጃቸው ሊኖርበት ስለሚችል ለዚህም
ራስሽን አዘጋጂ” አላት፡፡

ኒኪ ይህን ስትሰማ አይኗ በራ። ምናልባት የባለቤትሽ ግድያ ውስጥ የሊዊስ እጃቸው ሊኖርበት ይችላል ማለቱን አልወደደችለትም፡፡ ምክንያቱም
ከባሏ እና ከውሽማው ግድያ ጋር በተያያዘ የእሷ ታካሚ የሆነችው ከአኔ
ባለቤት ሉዊስ ሮድሪጌዝ ጋር እንዲገናኝ አትፈልግም፡፡ ይህ እንዴት ሊሆን
ይችላል? ብላ አሰበች፡፡

“ለማንኛውም ማጠቃለያ ይህንን ይመስላል” ብሎ ባወራት ነገር የረካው
ዊሊያምስ ወደ ኋላ ወንበሩ ላይ እየተለጠጠ “በሚቀጥለው ምን ላይ አተኩሬ ሥራዬን እንድሠራ ትፈልጊያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡ ኒኪ ዝም ብላ ስታየው
ዊሊያምስ ነገሩን ማብራራት ጀመረ “በዚህ ሳምንት ትኩረቴን ትሬድ ላይ
አድርጌ ነው ምርመራዬን ላካሂድ የፈለግኩት።” አላት እና ዊሊያምስ
በመቀጠልም ከነገ ጀምሮ ሊና ፍላንገን ላይ ትኩረቴን ለማድረግ አስቤያለሁ፡፡ ማለትም ስለ በፊቱ የአደንዛዥ ዕፅ አጠቃቀሟ ምናልባትም ከሆነ ትልቅ የዕፅ አዘዋዋሪ ጋር ስላላት ግንኙነት ወይም ደግሞ ከዊሊ ቡድን ጋር ስላላት ግንኙነት ምናልባትም ደግሞ እኔ ካሰብኩት በላይ የዊሊ እና ቫለንቲና ቡድን እዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ ውስጥ ሊኖሩበት ይችሉ ይሆናል፡፡ አሊያም ደግሞ ፖሊሶች የአንቺ የቀድሞ ታካሚ ከሆነው ብራንዶን ግሮልሽ ላይ አትኩሮታቸውን አድርገው በመንቀሳቀስ ላይ እንዳሉ
በማወቅ ላይ አትኩሮቴን ማድረግ እፈልጋለሁ። ደግሞም መርማሪ ፖሊስ
ጆንሰን ይሄ ዘረኛ እጁ እዚህ ነገር ውስጥ በሙስና
👍3
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት

#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል

....ጋሻዬነህ ከእናቴ ጋር ውሉ አደረ፡፡ የየወዲያነሽ የእናትነት አንጀት በናፍቆት ተላወሰ፡፡ ሮብ ጧት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን «ምነው ዝም አልክ ጌታነህ? ረሳኸው እንዴ? ከጋሼ ጉልላት ጋር ምን ምን ነበር የተባባላችሁት?
ሂድና አምጣው እንጂ» አለችኝ፡፡

“ምናልባት ዛሬ የውብነሽ ታመጣው ይሆናል» አልኩና እንደገና ደግሞ
«ምናለባት ጋሻዬነህን ለእነርሱ ብንሰጣቸውና እኔና አንቺ ደግሞ….ሌላ» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ደረቷን ሁለት ጊዜ በጥፊ ደቃችና «ህ! እንዴት ያለህው ዓለመኛ ነህ! ምነው ምን በወጣኝ! ዕድሜ ላንተ እያልኩ ዐይን ዐይኑን እንዳላይ ነው!» ብላ ከነጥርጣሬዋ ዝም አለች።

ሐሳብን ማሻሻልና ፈጽሞም መለወጥ አንድ ዐይነት ዕድገት በሆኑ የሐሳቧ መለወጥና ተቃውሞዋ ደስ አለኝ፡፡ ለጥያቄዋ መልስ ሳልሰጥ ወደ ሥራ ሄድኩ፡፡
የውብነሽ ቀንም ሆነ ማታ ብቅ ሳትል ቀረች፡፡ የሮብ ጀንበር ጠልቃ የሐሙሷ ተወለደች፡፡ አዲሱ የፍርሃት ሸክም ከየወዲያነሽ ይልቅ እኔን ከበደኝ፡፡ ከማታ
ትምህርት መልስ ሻይ እየጠጣን ስናወራ አንዱን ተረስቶ የቀረ የጋሻዬነህን የሒሳብ ደብተር እያገላበጠች «እሷ መች ሥራ አጣችና ነው ይዛው ትመጣለች
የምትለው? እኔ እኮ ነገሩ የገባኝ የመማሪያ ደብተሩን ይዛ ስትሒድ ነው» ብላ ወደ ራሷ ደብተሮች መለስ አለች፡፡

«እኔን ያሠጋኝ ሌላው አይደለም.....አባባ ይመለሳል ከተባለበት ቀን ቀደም ብሎ ቢመለስና ይኸ ልጅ የማን ነው ልጅ? ብሎ ቢጠየቅ ምን ይላሉ?
እናቴ ገና እንማከራለን ነው ያለችኝ እንጂ ሌላ የተነጋገርነው ነገር የለም ከማለቴ፣ የማን ልጅ እንዲባልልህ ትፈልጋለህ? የጌታነህ ልጅ ነው ብለው
ይነግሩልሃላ» ብላ ኩታ አጣፍቶ የመልበስ ያህል ጉዳዩን አቃልላ መለሰችልኝ።

«እንዴት አንቺ? እኔ እኮ ገና ብዙ ግብግብና ትግል ይጠብቀኛል።
የሙሉ ድሌ ቀኔ ገና ነው:: ምኑ ተያዘና!ምኑ ተነካና! እንዴት አድርጌ እንደምገጥመውና ድል እንደማደርገው ዕቅድና ብልሃቴ አልተጠናቀቀም፡፡ወደፊት የሚቀረኝ የትግል ጉራንጉር ያለፉትን የመከራና የትግል ገድሎች ሁሉ ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ ቀሪው ትግል በዕድልና በአጋጣሚ የማምንበት ነገር
የለም፡፡ የሚጠብቀኝ ውጣ ውረድ ሁሉ በበቂ ምክንያትና በተግባር የሚመራ ነው። «የዘልማድ ዝላይና ባወጣ ያውጣኝ በቃው! በቂ ምክንያት ጥሩ የተግባር
ዋስትና» ብዬ በመጀመር ለወደፊት ከሚያጋጠሙኝ አንደንድ ችግሮች መኻል አንዳንዶቹን በከፊል አዋየኋት፡፡

ዓርብ ከጧቱ ሁለት ሰዓት ላይ የውብነሽ ጋሻዬነህን ይዛ መጣች።
የሚያምር አዲስ ልብስ ለብሶ
ከፈገግታው ጋር ሲታይ የመስከረም ዝናብ ያጠባት
የለጋ ዘንባባ ተክል መስሏል። የወዲያነሽ ግልገሏን አስከትላ ጢሻ ውስጥ እንደምትገባ ሰስ ልጅዋን አስከትላ ወደ ጓዳ ገባች። እኔና የውብነሽ ወጣ ብለን ሰበሰቡ ላይ እንደቆምን «አባባ የነገ ሳምንት ከሰዓት በኋላ ይገባል፡፡ ባለቢትህን እንዴት አድርገን እሱ ፊት እንደምናቀርባት፡ አንተም ምንና ምን እያልክ መናገርና ማስረዳት እንዳለብህ አንድ ባንድ አውጥተን አውርደን ጨርሰናል» ብላ ስለ እኛ ሕይወት እኔና ባለቤቴ ያልተካፈልንበትን የአፈጻጸም ዕቅድ አረዳችኝ፡፡
የችግሬን ዐይነትና ዓላማዬን የማውቀው እኔ ሆኜ ሳለሁ መወከልና ማስፈጸም
የማይገባቸው እኅቴና እናቴ አፈ ቀላጤ ሆነን እንገኝ ሲሉ በመስማቴ ተናደድኩ፡፡
አልተዋጠልኝም፡፡

የአባቴ ግብዝነትና ቁጣዉ፣ ግትርነቱንና የመጣ ይምጣ ባይነቱ፣ እንደ ጨካኝ አገረ ገዢ ፊት ለፊት ቆሞ እንደ እሳት ፈጀኝ፡፡ «ማታ ከትምህርት ቤት
መልስ ከየወዲያነሽ ጋር እንድትመጡ፣ ነገሩን አብራራልሃለሁ። አሁን ግን
ቸኩያለሁ ደኀና ዋል» ብላኝ ቶሉ ብለህ ና እንደ ተባለ መልእክተኛ ጥላኝ ሄደች። አእምሮዬ በሐሳብ ተወቃ፡፡ ሁለመናዬ ብው ብሎ ጋመ፡፡ አዳዲስ ጭንቀቶች በውስጤ ተራወጡ፡፡ የሐሳቤ አድማስ ለመጥበብም ሆነ ለመስፋት ባለመቻሉ መረጋጊያ አጣሁ፡፡

ጎርፍ እንደ ገረሰሰው ዛፍ ግድግዳውን ተደግፌ ቆምኩ፡፡ የወዲያነሽ ከወደ ውስጥ መጥታ «ከምን ጊዜው ሄደች? ያንተ ነገር እኮ...አናደድካት እንዴ?» ብላ
በሥጋት አዘል ሁኔታ ጠየቀችኝ፡፡ «ቸኩላ ነበር፡ ታናድደኛለች እንጂ ምን አናድዳታለሁ፡፡ የማይጠቅሙሽ እጠቅምሻለሁ፣ የሚያጠፉሽ አለማሻለሁ፣
የሚገድሉሽ አድንሻለሁ ሲሉሽ አትናደጂም? አሁን የነገረችኝን ማታ ስትነግረኝ ትሰሚያታለሽ፡፡ አሁን ወደ ሥራሽ ሂጂ» ብያት ዝም አልኩ፡፡ የእርሷ ከአጠገቤ
ገለል ማለት የሚረዳኝ ስለ መሰላት ተመልሳ ገባች፡፡ በአካባቢዬ የሚገኙት ነገሮች
ሁሉ ለችግሮች ማቃለያ የሚሆን ብልሃት ያቀርቡልኝ ይመስል ትክ ብዬ አየኋቸው:: ሆኖም ከበድን መልስ የለምና አፍጥጨ ቀረሁ። ሳላስበው ከቤት ወጣ ብዬ ቆምኩ፡፡ የማለዳዋ ፀሐይ ደጋናማ ጉዞዋን ጀምራለች፡፡ ደመና የማይታይበትን ሰማይ ትኩር ብሎ ላየው ኣስፈሪነቱ አይጣል! ዘልዓለም የሚሉት ይህን ርቀትና
ጥልቀት ይሆን? አንጋጥጬ ስመለከት ሐሳብ አሽቆልቁሎ አየኝ፡፡ አካባቢዬን ፈራሁት፡፡ ጥቂት ርምጃ ተራምጄ ግቢው መኻል ተገተርኩ፡፡ ከመሬት ውስጥ
መልስ ይፈልቅልኝ ይመስል ደቃቁን አፈርና ኮረት ባይኔ ሰለልኩት። ቀዝቃዛና ለስላሳ ትንሽ እጅ የቀኝ እጄን ከበስተኋላዬ ስትነካው ከፍዘቴ ነቃሁ። ጋሻዬነህን እጁን ስቤ ወደፊት አዞርኩት፡፡ ከፍ ብለው የሚበርሩ አዕዋፋትን እንደሚከታተል
ወፍ ጠባቂ ዐይኖቼን አሻቅቦ ከፈለገ በኋላ ና ቶሎ! አሁኑኑ ና ቶሎ ብላሃለች እማማዬ» ብሎ መልሴን ለመስማት ኣፉን እንደ ከፈተ ዝም አለ፡፡ ከቁመቱ ጋር ለማስተካከል ጉልበቴን አጥፈ ቁጢጥ አልኩና፣ እኔን ነው እማማዬህን ነው የምትወደው ጋሻዬነህ?» አልኩት።ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ የደብር ጉልላት የሚመስሉት ዐይኖቹ በሰፊው ተከፈቱ። «አንተንም እማማዬንም እወዳችኋለሁ...ያንን ቀይ ሽጉጥ እገዛልሃለሁ አላልከኝም ነበር፡ መቼ ትገዛልኛለህ?» ብሎ ዐይን ዐይኔን ሲያይ ዐይኖቹ በዐይኖቼ ውስጥ ሠረጉ፡፡ ትልቋ እማማስ እዚያ ትልቁ ቤት ውስጥ ያየሃቸው
የእኔ እናት አያትህ ጥሩ ናቸው? በል እስኪ ንገረኝ፡ ያንን ሽጉጥ እንድገዛልህ?»አልኩት። ከንፈሩን ትንሽ ሾል ካደረገ በኋላ «እሳቸው ደግሞ በጣም ደስ ሊሉኝ፡
ጥሩ ናቸው፡፡ ያንተ እማማ ናቸው እንዴ? እወዳቸዋለሁ» ካለ በኋላ ትልቅ በመሆኔ ከእናት ያልተወለድኩ ይመስል አወጣጧ የምታምር ሞንሟና ሣቅ ሣቀ።

«እስኪ ትወደኝ እንደሆነ ሳመኝ?» አልኩት፡፡ ጉንጩን ተራ በተራ ሳመ። «ኧረ እባካችሁ ኑ ግቡ! እባትና ልጅ ምን ትማከራላችሁ? እኔ እንዳልሰማችሁ ነው?» የሚል ድምፅ ከወደ ቤት ተሰማ፡፡ የወዲያነሽ ፍቅራዊ ትእዛዝ ስለሆነብኝ ጋሻዬነህን ይዤ ገባሁ፡፡ ቁርስ ይዛ ከተፍ አለች፡፡ የጀመረችውን ሥራ ለመዉረስ
መለስ ስትል «በይ አንሺና ይዘሽው ሂጂ!» ብዩ የካንገት በላይ ቁጣን በሚገልጽ
ስሜት ተናገርኩ፡፡ ደንገጥ ብላ ተመለሰችና «ምነው? ምን አጠፋሁ? የት ልሄድ
ነው? እደርሳለሁ ብዬ ነው ! » በማለት በፍርሃት ሳይሆን በፍቅራዊ ስሜት ትኩር
👍6
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


...የተቃራኒ ፆታ ሱስ እስከሚያንጠራራው ድረስ ተጨነቀ ጭኖቹ በጭኖቿ መካከል ነበሩ አልቻለም፡፡ ከንፈሮቿን እየሳመ ቀስ ብሎ የሆነ ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት፡በዚህ ጊዜ አማረች በጣም ተበሳጨች፡፡

ሂድ! ባለጌ! ወንዶች ስትባሉ ይሄው ናችሁ። ፍቅር ሲሏችሁ ዘላችሁ የምትሰፍሩት እዚያ ላይ ነው፡፡ ፍቅር ማለት እሱ ብቻ ነው የሚመስላችሁ፡፡ እኔኮ አንተን ለብዙ ነገር ነበር የምመኝህ፡፡ እንደዚህ አይነት ሰው አትመስለኝም ነበር፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ልጃገረድ መሆኔን ማወቅ አለብህ!ባንተ ዘንድ ረከስኩ እንጂ ውድ ነበርኩ፡፡ ሽርሙጣ አይደለሁም፡፡ ገባህ?!" ጮኽችበት። ደነገጠ።

“እንደሱ አይደለም የኔ ቆንጆ። በሌላ መልክ አይቼሽ አይደለም፡፡ በጣም ስለምወድሽ ነው በጣም አማረች.." ቃላት አጥረውት ተጨነቀ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ስውነቱ በስሜት ግሏል። ነዷል። "እኔኮ እኔኮ . እወድሻለሁ.... እስከ መጨረሻው የኔ እንድትሆኚ እፈልጋለሁ" አፉ ሲወተውት
ጣቶቹ ባልተፈቀደላቸው ድንበር ዘለው ገብተው አሰሳ ማካሄዳቸውን አላቋረጡም ነበር፡፡ ድርጊቱ አማረችን የበለጠ አናደዳት።

"ልቀቀኝ! ልቀቀኝ!" መንጭቃው ተነሳች። "እኔው ነኝ ወረዳዋ! አንተ
ምን አደረክ? በለሊቱ በርህን አንኳኩቼ የገባሁት እኔ! ጥፋተኛዋ እኔ!" ፀጉሯን እየነሰነሰች….ያንን ውብ ዳሌዋን እያውረገረገች ከአልጋው ላይ ወረደች፡፡ በድንጋጤ ዐይኖቹ ፈጠጡ። የሚናገረው ጠፍቶበት በፈፀመው የብልግና ድርጊት ራሱን ወቀሰ፡፡ በስሜት ግፊት ተሸንፎ ከፍላጎትዋ ውጭ በፈፀመው ድርጊት ተፀፀተ።

ቆይ!!. . ቆይ! . ቆይ! " እጆቹን ዘርግቶ ተከትሏት ብድግ አለ።
“ሂድ!" በሩን አላትማ ወጣች።
“አማ.አማረች..አንዴ .ምን…. መሆንሽ ነው?ቆይ እስቲ..." ሲወራጭ የአልጋው ብረት ቅዝቃዜ እንደ ኤሌክትሪክ ነዘረውና ብንን አለ። ጭንቀቱ..
ቅዠቱ.. ላብ በላብ አድርጎት ነበር፡፡
“በስመአብ ወልድ!“ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ ከለሊቱ ስምንት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ ቀስ ብሎ ያየውን ህልም ይመረምር ጀመር፡፡ ያንን የማይጨበጥ ጉም የማይዳሰስ ተስፋ መጨረሻው ባያምርም እቅፍ አድርጎ
በላይዋ ላይ እየተንፈላሰለ እንጆሪ ከንፈሮቿን የቀሰመበት ዓለም እንደ
ሰቀቀን ሆኖ አለፈ። ዐይኖቹን ጭፍን ክድን ጭፍን ክድን አደረጋቸው። መብራቱን አበራና ሁለቱንም ትራሶች ደራርቦ ከወገቡ በላይ ራቁቱን ሆነ፡ ዐይኖቹን ፊት ለፊቱ አማረችን በጋረደበት ግድግድ ላይ በንዴት ተክሎ በሀሳብ እሷ ክፍል ገባ፡፡ እንደ ንዴቱና እንደ ብሽቀቱ ቢሆን ኖሮ
ከዐይኖቹ የሚወረወሩት ጨረሮች ያንን የግንብ ግድግዳ የጤፍ መንፊያ ወንፊት ባደረጉት ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ እንቅልፍ በዐይኑ ሳይዞር ቀሪውን ጊዜ በመቀመጥና በመገላበጥ አሳለፈው፡፡ ጠዋት ቁርሳቸውን እዚያው በሉና በፕሮግራማቸው መሰረት ወደ ላንጋኖ ጉዞ ጀመሩ፡፡ ዛሬ አማረች
የዋና ተለማማጅና የህይወት አድን ሰራተኛ ፈላጊ ሆና ለመቅረብ አቅዳለች። ለዘዴዋ፡፡ ላንጋኖ ደርስው ለዋና ተዘጋጁ፡፡ አማረች ልብሷን አወላልቃ በውስጥ ሱሪ ብቻ ወደ ሃይቁ መጣች፡፡ ጌትነት ያንን ውብ ተክለ ቁመናዋን የሚያጓጓ ራቁት ገላዋን በውስጥ ሱሪ ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ
አየው። ልቡ ወደ ሰማይ ወጥታ እንደ እምቧይ ፈረጠች፡፡ ወደር የሌለው አፍ የሚያስከፍት ቅርፅ.. ስምንት ቁጥር ቁጭቁጭ.ያሉ ጡቶቿ ዐይኖቻቸውን አፍጠው ምራቃቸውን በሚውጡ ተመልካቾቿ ድርጊት ተቆጥተው እንደ ነብር ያበጡ ይመስላሉ። ጌትነት ዘወር ዘወር ብሎ ሲመለከት የበርካታ ዋናተኞች አፎች ተከፍተው መቅረታቸውን አስተዋለ። ቅንአት ቢጤ ቆነጠጠው...

"እውን የኔ ትሆኝ ይሆን ?"አለ በልቡ። ይሄንን ልቡ የተመኘውን ምኞት ዐይኑ እንዳያሳብቅበት ፈራና ለመሸፋፈን ጥረት አደረገ፡፡ ተወት ያደረጋት ለመምሰል ማዶ ማዶውን ማየት አበዛ... አማረች ደግሞ የጌትነትን አንጀት ለመብላት ስትል አንድ አላስፈላጊ ድርጊት ፈፀመች። ጡት ማስ
ያዣዋን በመጠኑ ዝቅ አደረገች። ማግኔት!!

"ጌትሽ ይሄኛው ጥልቅ ነው እኔ እዚህ አልዋኝም፡፡ እሰምጣለሁ። እዚ ቅርቡ ጋ ሄደን እንዋኝ?” ሰው ወደሌለበት አካባቢ በአገጭዋ እያሳየችው አካባቢውን ጠቆመችው። ወደዚያ እሷ ወዳለችው የሃይቁ ዳርቻ ተያይዘው ሄዱ፡፡ አማረች አዲስ ዋና ተማሪ ሆና ቁጭ አለች፡፡ ወይ አበሳው?!
ያንን መጠጋት የፈራውን እፍኝ የማይሞላ ወገቧን ይዞ ከፍ ዝቅ ወደ..ፊት ወደ ኋላ... እያደረገ ያለማምዳት ጀመር። በሷ እንቅስቃሴ አቅጣጫ
እየተመራች የሱም ልብ ከቦታዋ ለቃ እየተንከራተተች ነበር፡፡
ጌትነት የትናንትናው ህልም ዓለም ክፍል ሁለት እንዳይሆን ዐይኖቹን
ተጠራጠረ፡፡ ሲፈራው የኖረ ውብ ገላዋን በኒያ አለንጋ መሳይ ጣቶቹ
እያሻሽ አንዳንዴም ልቡ ሲከዳው ጣቶቹ ደግሞ ሳይታዘዙ ወደ ጡቶቿ እያዘገሙ ከዚያም ድንግጥ ብሎ ሲመልሳቸው ደግሞም ላያስበው በስሜት
ሌላ ሃሳብ ውስጥ ይገባና ወደ ዳሌዋ አድርሶ ሲመልሳቸው.. በአማረች ፈተና እንደያዘችው ቁም ስቅሉን ሲያይ ዋለ፡፡ እሷ አውቃ ስትፈራገጥ እሱም ጎበዝ አሰልጣኝ ለመሆን ሲታገል ሲተሻሹ ሲደባበሱ..ብዙ ቆዩ።
ሰው እንደ ጨው የሚሟሟ ቢሆን ኖሮ ሟሙተው ሟሙተው በጠፉ
ነበር፡፡ የሱ ጣቶች በገላዋ ላይ በሚርመሰመሱበት ጊዜ አማረች በከፍተኛ የፍቅር ስሜት ውስጥ ነበረች። ከውጭ ቀዝቃዛው ውሃ ባያቀዘቅዛት ኖሮ ውስጧ በስሜት እየጋለ እየነደደ ሄዶ እንደ ስም ቀልጣ በፈሰሰች ነበር፡፡

የሁለት ዓመት የትምህርት ቤት ጓደኛዋ ከአንገቷ ቀና አድርጎ ዐይን
ዐይኖቿን በፍቅር እያየ አበባ ከንፈሮችዋን ለመቅሰም ያልታደለ ንብ ሆኖ አንገቱን እያቀረቀረ እሷ በጉጉት ስትጠብቀው እያሳፈራት ሁለት አመታት እንደ ዋዛ አለፉ፡፡ እሱ እንደዚያ ማድረግ ቢችል ኖሮ ከወዲሁ ስሜቷን ቢረዳላት ኖሮ ያንን ያክል የሚባክን ጊዜ ባልተፈጠረ ነበር፡፡ ገና
ከጅምሩ ፍላጎትዋን አውቆ በአንደኛና በሁለተኛው ወር ላይ በአፉ ባያወጣው እንኳ ሚስጥሩን በዐይኖቹ ቢገልፅላት ኖሮ ተቀላጥፋ ምላሹን በደስታ በገለፀችለት ነበር፡፡ እሱ ግን ያንን ማድረግ ባለመቻሉ ግንኙነታቸው በጥናት ላይ ብቻ ተወሰነና ጊዜው ተላለፈና በእህትነት በወንድምት
በሚል ፈሊጥ ምኞታቸውን ከመገላለፅ ተቆጠቡ።

በልባቸው እየተፈላለጉ ከአሁን በኋላ ምን ይለኝ? ምን ትለኝ? በመባባል ተፈራርተው በመካከላቸው አፏን ከፍታ የምታዛጋውን ፍቅር ሁለት
ዓመት ሙሉ በሱስ እንድትሰቃይ አደረጓት። በይሉኝታ ገመድ በመታሰር ምን ይለኛል ምን ትለኛለች በሚል ፍራቻ ግልፅነት ሲጠፋ ትርፉ ውስጥ ውስጡን መሰቃየት ነውና አማረችና ጌትነት የዚህ የፍቅር ጋግርት የይሉኝታ ሰለባዎች ሆኑና የሱን ልወቀው ከሷ ይምጣ እየተባባሉ የመፈላለግ ደረጃቸው ገሃድ ሳይወጣ ሁለት ዓመታት ተቆጠሩ።

በማህበረሰቡ ዘንድ ሴት ልጅ ስትለመን፣ ደጅ ስታስጠና፣ ስትሽኮረመም ትወደዳለች የሚል አመለካከት በስፋት የሚንፀባረቅ በመሆኑ ፍቅሯን አስቀድማ ለመግለፅ ትቸገራለች። አማረችንም አፏን ያፈነው ይሄው
ነበር፡፡ በአንዳንድ ሁኔታዎቹ የተረታላት መሆኑን ብታውቅም አስጠናኝ ብዬ በግድ የቀረብኩት ልጅ ቀድሜ ወደድኩህ ብለውና "አልፈልግሽም ዞር በይ" ቢለኝስ? በሚል ፍራቻ ዝምታን መርጣ ቆየች። እሺ እንደ ሃሳብሽ ቢላት እንኳ ወደ ፊት አንድ ቀን “እሷ ራሷ ወደድኩህ አበድኩልህ ብላ ተለማምጣኝ ነው" ብሎ ሊያወራ ነው። ከዚህ ሁሉ እንደተከባበርን ቢቀርስ? ከዚህ ሁሉ ነገሩ ከሱ ገፍቶ እስከሚመጣ ድረስ በትዕግስት ብጠብቅስ? በማለት ሁለት ዓመት ሙሉ ታገሰች። ከጌትነት በኩል ገሀድ የሚወጣ
👍4
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

....ሸዋዬ በህዳር ወር የመጨረሻ ሳምንት ላይ ቆማ የመጀመርያው መንፈቅ ትምህርት አልቆ ለአጭር ጊዜ እረፍት ትምህርት ቤት የሚዘጋበትን የጥር ወር መጨረሻ በናፍቆት ትጠባበቃለች። ከብረ መንግስት የምትደርስበት ቀን ሳይቀር ተወስኗል።እቅዷ ከሔዋን
ወይም ከወላጆቿ ተቃውሞ ቢገጥመው ማሳመኛ ይሆናል የምታስበውን እያዘጋጀች ነው። ዘዴና ብልሀት በልቧ ይውጠነጠናል።

ለሆዳም በሬ ጭድ ያዝለታል እንዲሉ ወንድሟ አስራት ተስፋዬ ባላሰበችው ቀንና ሰአት ከቤቷ ከች ብሎ ያደረሳት ብሥራት ግን ሰጋትና ፍርሃቷን ሁሉ ከልቧ ውስጥ እንደ እድፍ አጠበው። ሔዋን የልብ ህመምተኛ ሆናለች በሰው ላይ ክፉ ደግ አለና መተሽ እያት ከማለት ውጭ ስለ ሔዋን ሁኔታ ምንም አይነት ፍንጭ ለሸዋዬ እንዳይሰጥ በተለይ በእናቱ አደራ የተባለው አስራት የልጅ ነገር ሆኖበት አንዳንድ ነገሮችን ማፈንዳቱ አልቀረም ሔዋን ዛፍ ስር ተቀምጣ መዋል ማዘውተሯን በሀሳብ እየተዋጠች ቤተሰቧን ማሳሰቧንና በተለይ በህመሟ ምክንያት አገር ብትቀይር የተሻለ መሆኑ መታመኑን ሁሉ አልደበቃትም።

የሔዋን አገር መቀየር አስፈላጊነት የታመነበት ስለመሆኑ መስማቷ ሸዋዬን ከምንም ነገር በላይ አስፈነጠዛት። ሔዋን አገር መቀየር ካለባት ቀላሉ ከክብረ መንግስት ወደ ዲላ ነው ይህ ደግሞ በቤተሰቦቿ ዘንድ ተፈጥሮ ይሆናል ብላ ከምታስበው ቅሬታ ነፃ የምትሆንበት አጋጣሚን ይፈጥራልና ወቅትና ጊዜ ያለ ሽማግሌ ሲያስታርቃት በመቅረቡ አምላኳን አመሰገነች፡፡ ወደ ክብረ መንግስት ልትሄድ በልቧ ይዛው የነበረውን የጊዜ ቀጠሮ አሳጠረችው፡፡ ወንድሟ አስራት
ከቤቷ በደረሰ በአራተኛው ቀን እንዲሆን አደረገችው:: በመሀል ያሉት ሁለት ቀኖችም የዝግጅት ጊዜ ሆነ::
ብሥራቱን ያካፈለቻችው በድሉና ማንደፍሮ በእነዚህ ሁለት ቀናት
አልተለዮትም፡፡ ወደ ክበር መንግስት አካሄዷን ሊያሳምሩ ሽርጉድ አሉ። አብረዋት
እየዋሉ አብረዋት አመሹ። በየገበያው ቦታ አብረዋት ዞሩ። አዘጋጇት፤ አዘገጃጇት ጠዋት ወደ ክበረ መንግስት ልትሄድ ሻንጣዋ የያዘውን ይዞ ማታውኑ ተቆለፈ
የማግስቷ ጀምበር ክብረ መንግስት የምታደርስ የልቧ መብራት ሆነች::

ልክ በዚያ ዕለት ምሽት ላይ ክብረ መንግስት ሌላ ዝግጅት በመደረግ ላይ ነው። የሄዋን አባትና እናት ሔዋን ወደ ዲላ መሄድ ያለ መሄድ ፍላጎቷን ለመጠየቅ ሊያነጋግሯት በተመካከሩበት መሠረት ውይይቱ ተጀመረ፡፡
«እሙዬ !» ሲሉ ጠሯት ለስለስ ባለ አነጋገር።
«አቤት እማ» አለቻቸው ሔዋን ከአጠገባቸው መደብ ላይ ገደም ብላ ሳለች። አባቷ ደግሞ ከባላቤታቸው ፊት ለፊት ምድጃኑ እጠገብ ተቀምጠው እሳት ይሞቃሉ።
«እንደው ይቺ ልብሽ ያስቸገረችሽ ይኸን አገር ጠልታብሽ ይሆን? እማስበው ባጣ ይህን ነገር በእሊናዬ አውጠነጥነው ጀመር ልጄ? አሏት ጉልበታቸውን በሁለት
እጆቻቸው ደገፍ በማድረግ ዓይን ዓይኗን እየተመለከቱ፡፡
«አዩ! እማ ቢቸግርሽ!»
«ቸገረኝ ልጄ! በጣም ችግረኝ፡፡»
«የት ልሂድ ታዲያ እማ»
«እውነትሽ ነው:: መሄጃማ ይቸግራል የኔ ልጅ፡፡» ካሉ በኋላ የሔዋን እናት ወደ አቶ ተስፋዩ ዞር በማለት «እንደው ወደ ዲላ ትሂድ ይሆን አቶ ተስፋዬ» ሲሉ ጠየቋቸው።
«ተሆነማ ወደዚያው ነው ኋላማ መይት ትሄደዋለች? ከዚያ ሌላ አገር አታውቅ አሉ አቶ ተስፋዬ አንገታቸውን ወደ እሳቱ ደፋ አድርገው፡፡
«ከማን ጋር ልኖር?»ስትል ሔዋን ጠየቀቻቸው፡፡
«በኔ ልብማ ከነዚያ ከነታፈሡ ጋር ትንሽ ተጨዋውተሽ ትመለሽ እንደሆን ብዬ ነዋ!»አሉ እናቷ ለስለስ ባለ አነጋገር።
«እህቷስ አለች አይደል! »አሉ አቶ ተስፋዬ ወደ እሳቱ እንዳቀረቀሩ።
«እንደገና ከእታ አበባ ጋር?» አለች ሔዋን ደንገጥ ብላ።
«እሷን ለሰበብ ተዚያ በኋላ ደግሞ ከእነዚያ ልጆች ጋር አንዳንድ ጊዜ
መጫወቱ ትንሽ ያፍታታሽና ልብሽም እየተወችሽ ትሄድ እንደሆነ ብዬ እኮ ነው፡፡»
አሉ እናቷ የሔዋንን ቁጣ ለመመለስ ረጋ ብለው።
«ተይ እማ! እንዲህማ አይሆንም::»
«ቀለብሽን ተሆነ እኔ እችላለሁ ሔዋኔ ከቶ የአንቺ ጤና ይመለስ እንጂ፣ደሞ ላንቺ ያልሆነ አዱኒያ ምን ሊያደርግልኝ! ላም ተሆነች ላም! በሬ ተሆነም በሬ ይሸጣል :: አይዞሽ!» አሉ የሔዋን አባት በቆራጥነት።
«እናንተ የማታወቁት ልላም ችግር አለ:: አለች ሔዋን፡፡
«ብትነግሪን አይፈታም?» አሏት እናቷ፡፡ ግን ትዝ ያላቸው ነገር አለ፤ ያኔ ታፈሡ በማትፈልገው ሰው ልታስደፍራት ያለቻቸው ነገር። ፈታ ብላ ብታወባና ሁኔታውን በግልጽ ቢረዱት ፈለጉ፡፡
«እኔና እት-አባበ አብረን መኖር አንችልም፡፡» አለች ሔዋን ነገሩን ደፈንፈን አድርጋ።
«ኧረ ተይ ሔዋኔ፣ በእትማማቾች መካከል ቂም ተያይዞ አይኖርም!» አሉ አባቷ አሻግረው መልከት እያሏት፡፡
«ከበድኳችሁ እንዴ አባዬ?»
«ለአንቺ ብለን ነው እንጂ እሙዬ ደሞ አንቺ ምን ትከብጅናለሽ የኔ ልጅ?»
አሏት እናቷ በማሳዘን ዓይነት አነጋገር፡፡
«እንግዲያው እዚሁ ብሆን ይሻለኛል፡፡» አለችና ሔዋን በረጅሙ ተነፈስች።

የሔዎን እናትና አባት ግራ ተጋቡ። ልጃቸው ወደ ዲላ ለመሄድ ፈቃደኛ አለመሆኗ ገባቸው። ከዚያ በኋላ ምንም ሳይነጋገሩ ጊዜው መሸ፡፡ እንደ ተዳፈጡ ተኙ፡፡ ሌሊቱ በሀሳብ ነግቶ ቀኑም በትካዜ አለቀ።

የደስታ ፈረስ ጋልባ ሶምሶማ ስትጋልብ የዋለችው ሸዋዬ ከቤተሰቦቿ ቤት የደረሰችው ከአመሻሹ አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ ነው፡፡ በዚያ ሠዓት አባቷ
ከብቶቻቸውን ይዘው ከመስክ እየተመለሱ ነው። እናቷ ደግሞ ምናልባት ሔዋን ሸዋዬ ስትመጣ ሀሳቧን የቀየረች እንደሆነ ብለው ለወደፊቱ ግንኙነት እንዲያመች
የዘመድ ስልክ ቁጥር ሊያመጡ ወደ ከተማ ሄደው እየተመለሱ ገና በመንገድ ላይ ናቸው:: ሽዋዬና አባቷ በር ላይ ተገናኝተው በመሳሳም ናፍቆታቸውን አውጥተው እየተነጋገሩ ወደ ቤት ሲገቡ ሔዋን በጎሮ በር በኩል ወደ ቤት ስትገባ ዓይን ለዓይን ግጥምጥም አሉ።

"እማሃይዬ! አለች ሔዋን ሸዋዬን ስታይ ደንግጣ። የትናንት ማታው ወሬ መሰረቱ ምን እንደነበር ልቧ ጠረጠረ።
«እህትሽ መጣች ሔዋኔ!» አሉ አባቷ ቀድመው::
«ጠፋሁባት ይሆን?» በማለት ሽዋዬም ሳቅ እያለች ወደ ቤት ገባችና በሔዋን ላይ ጥምጥም ብላ ሳመቻት::
«አንቺ! አለቻት አጠገቧ ቆማ ከእግር እስከ ራሷ እየተመለከተቻት፡፡
«አቤት» አለች ሔዋን ወደ መሬት እንዳቀረቀረች::
«በቃ አንዲህ ሆነሽ ቀረሽ?»
ሔዋን ሽዋዩ ምን እያለች እንደሆነ አልገባትም፡፡ ጠቁራባት ይሁን
ከስታባት ብቻ ያየችባትን አካላዊ ለውጥ ገና ትነግራት እንደሆነ እንጂ ለጊዜው አለየላትም።
ሸዋዬ እንደ መናደድ ዓይነት እጆቿን ጨብ ጨብ ጨብ እያረገች ዋይ-ዋይ-ዋይ-ዋይ…አለች ደጋግማ:: በአባታቸው ግብዣ
ሁሉም በመደብ ላይ ተቀመጡ።

«ሔዋኔ ክብረ መንግስት እንዳላደገችበት ሁሉ ዛሬ ዛሬ አልስማማት ብሏል የሸዋ!» አሉ የሔዋን አባት የሸዋዬ ቁጭት መነሻው የሔዋን መጎሳቆል መስሏቸው።
«ለመሆኑ ያምሻል?» ስትል ሸዋዬ ሔዋንን ጠየቀቻት፡፡
«እል አልፎ ልቢን ያመኛል::
👍51
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....ለዓመታት በርካታ የመንፈስ ድል ስትቀዳጅ ቆይታ ልጇ ከሞተ በኋላ፣ ይኸው ድል ወደ ሽንፈት የተቀየረ በመሰላት ሰዐት እሱን በማግኘቷ ልቧ ተነሳስቶ ኸንግዲህ ሞት እንጂ ሌላ አይለየንም አለች።
አስተናጋጅ ወይን ጠጅ አምጥቶ ቀድቶላቸው ወጣ።

“ጠጣ እስቲ!” አለችው፣ ፈገግ ብላ።

የትካዜው ድባብ ተገፈፈ።

“ለመሆኑ ሥዕል እንዴት ዠመርህ?”

“ቋራ ሁኘ ነው የዠመርሁት” አለና ስለግድግዳው ታሪክ ነገራት።

ከት ብላ ሳቀች። “ሥዕል ትሥል እንደነበር ዛዲያ እንዴት
አላወቅሁም?”

“አባባ ለምሠራው ነገር ቁብ ሰጥተውት አያውቁም ነበር። ወዲያው ያጠፉት ነበረ። ቋራን ትቸ ጐንደር ዘልቄ እመኝ የነበረውን ሥዕል መማር ዠመርሁ። ኋላም ደብረ ወርቅ ማርያም ኸድሁ። መቸም በርስዎና በንጉሥ ኢያሱ ዘመን ሥዕል አደገ። ጐንደር ውስጥ የባሕር ማዶ ሰዎች ኸመጡ ወዲያ ሥዕል ለውጥ ኣምጥቶ ነበረ...” ብሎ ከጠጁ
ተጎነጨ።

“እንዴት?”

“የቀድሞዎቹን ሥዕሎች ያስተዋሉ እንደሆን መለኮታዊ ይዘት
ያላቸውና ታሪክ ተራኪ ነበሩ። ኋላ ግን መለኮታዊ ብቻ ሳይሆን ሥዕል ወደ ሰው ወረደ። ሥጋ ለባሾች... ነገሥታት ሚሣሉበት ዘመን ላይ መጣን። የቀለም አጠቃቀም ሁሉ ለውጥ አመጣ። መቸም የአጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመንም በትምርትም ሆነ በሥዕል ብዙ ለውጥ የመጣበት
ዘመን ነበር። ቁም ጸሐፊው፣ ደብተራው ቁጭ ማለት ያመጣበት ግዝየ ስለነበረ ቁጭ ሲባል ፉክክር፣ ክርክርና አሳብ ለአሳብ መለዋወጥ መጣ።እንዲያም ብሎ አንድምታ ትምርት ተዠመረ። ይኸ አሳብን መግለጽ ወደ ሥዕለም መጣ።”

“እንዴት ያለ ነገር ነገርኸኝ? ሁሉ ሚሆነው በግዝየው ነው መሰለኝ
ብላ ፈገግ አለች።
“አዎ ሁሉ ሚሆነው በግዝየና በቦታ ነው። አለግዝየውና አለቦታው ሚሆን ምን አለ?”

“ግዝየ ምንድነው?”

“ግዝየ እኛ ነን።”

“የግዝየ ነገር ይገርመኛል።”

“የሰው ነገር ይገርመኛል ማለትዎ ነው? ግዝየን ሆነ ቦታን ምንፈጥር
እኛ ሰዎች እኮ ነን። እዝጊሃር ምድርና ሰማይን ፈጠረ። እኛ ደሞ
ግዝየንና ቦታን ፈጠርን። ግዝየ ሆነ ቦታ አለኛ የሉም? ቦታም ግዝየም እኛ ነን። እኛ ጥሩ ስንሆን ግዝየም ጥሩ ይሆናል። እኛ ጥሩ ስንሆን የሰማዩም ደስ ይለዋል፣ ምድርም ለፍጥረታት ሁሉ ምቹ ቦታ
ትሆናለች።”

“አሳብህ ገባኝ። ግዝየ ሳይሆን እኛ ነን ምንገርመው ማለትህ ነው?
እንግዲያማ የሰው ነገር ይገርመኛል።”

“አየ እቴጌ ዝናዎን ሰምቻለሁ። ሊቃውንት ሆኑ ካህናት ያደንቅዎታል።እርስዎ የጠለቀ ዕውቀት... ትምርት ያለዎ... አንደበታምና ታሪክ
አስተካካይ... የሰው ባሕርይ ይግረምዎ?”

“አንተ የሥዕል ንጉሥ፣ የሰማዩንም የምድሩንም ብራና ላይ
ምታስቀምጥ እስቲ ንገረኝ። ሰው ማለት ምን ማለት ነው?”

“እቴጌ ሰው ማለት ምን ማለት እንደሆነ ኻወቅሁማ ፈጣሪን ሆንሁ።እኛ ሰዎች መሆን የነበረብን ሚዛኑ ከፍ አለና እኛ አነስን። መሆን ሚገባንን መሆን አልቻልንም። መቸም ጉድለት አለን ብንል ፈጣሪ ጉድለት ያለው ፈጠረ ማለት ይሆንብናል። ሙሉ ግን ማዶለን።”

“ዛዲያ የተሟላን መሆን ቢያቅተን፣ ኸሚዛኑ ብንጎድል፣ ለመሙላት
አንጥርምን?”

“ቢሆንልንማ እንዲያ ነበር።”

“እኔስ እንዲያው በተለየ አሁን ያለንበትን ሳስብ ክፋትና ደግነት
አብረውን የተወለዱ ናቸው ነው እምል።”

“ስለ ሰው ባሕርይ ተመራምረን ምንደርስበት አይመስለኝም::”
አለ ጥላዬ ከጠጁ አሁንም ጎንጨት ብሎ። እሷ የቀረበላትን ጠጅ አልነካችውም። “ይጠጡ እንጂ” እንዳይላት ድፍረት መሰለው።

“እኔ ለነገሩ ሰው ማለት ምን ማለት ነው ብየ የጠየቅሁት እንዳው
ያገራችን ነገር አሳስቦኝ ነው። ይረዳሉ ብለህ ያሰብኻቸው ሁሉ
አንተንም አገርንም ሲጎዱ ስታይ ይገርማል። ሰላም ጠፋ።”

“ርግጥ ነው ... ርግጥ ነው እቴጌ... ሁላችንን ሚያሳስበን ይኸው ነው” አለ፣ በሐሳብ ተውጦ ሳይመልስላት በመቅረቱ ደንገጥ ብሎ። “እቴጌ በእርስዎና በንጉሥ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ዘመን ደግ ግዝየ አለፈ።
እናንተ ደግ ጥሩ ነበራችሁና ግዝየውን ደግ... ጥሩ አረጋችሁ።
አዋቂው እንዳለው እኛ መልካም ስንሆን ግዝየውም መልካም ይሆናል። ከቶም ያገሩ ንጉሥ ወይም ገዥ ደግ ተኾነ ሕዝቡም ደግ ነው ሚኾን፤ገዥው ተከፋም ሕዝቡም አብሮ ይከፋል። “እስመ ከመ መኰንና ለአገር ከማሁ ይገብሩ እለ ውስቴታ ይላል፤ አገረ ገዥው የሚያደርገውን ነገር ሁሉ በአገሪቱ ያሉ ያደርጋሉ ሲል ነው። መቸም በሩቅም ቢሆን
ስለእርስዎ ደግነት ብዙ ሰምቻለሁ ሁሉ ያመሰግንዎታል። እርስዎ
ለምለም ልቡና ያለዎና ልበ ጽኑ በመሆንዎ አምላክ መንግሥትዎን
ሥሙር አርጎልዎ፣ አቅንቶልዎ ለዐርባ ዓመት ገደማ ሰላም የመላበት ዘመን ሰጡን። አጤ ኢያሱ ካደጉ በኋላ እርስዎም እሳቸውም ባሳያችሁት
ትጋት እፎይ ብለን ዐርፈን አለሥጋት ተማርን፤ ሠራን። አሁን ግን ይኸው ተኝተን ሳይሆን በቁማችን እንባንናለን።”

“የኛ ዘመን ... መቸም ዕድለኛ ሁነን...”

“ዕድለኛስ አይበሉ እቴጌ! ነገርዎን አቋረጥሁ እንጂ..”

“ኧረ ግዴለህም እህትህ ነኝ እንደ ሹመኛ አትሽቆጥቆጥብኝ
አለችው፣ በፈገግታና በሚያቀራርብ ቅላጼ።

“አይ ግዴለዎትም ቀስ እያልሁ እዘናለሁ፤ ክብረት ይስጥልኝ። ደሞስ መሽቆጥቆጥ ለካህናተ ደብተራ ወግ ማዶል” ብሎ ፈገግታውን እንደያዘ ነገሩን ቀጠለ። “ንጉሥ ኢያሱ ልዥ በነበሩ ግዝየ ያን ሁሉ ትጋትዎን አይተን... ሰምተን ማልነበር? እሳቸውም ካደጉ በኋላ ተባብራችሁ
አገራችንን ሰላም አረጋችሁ፤ ደከማችሁላት። የጥጋብ ዘመን ሰጣችሁን።ሰዉም ወደዳችሁ። የሰው መውደድ ብል አጤ በካፋስ እያሉ ቢሆን እርስዎ ተወዳጅ ነበሩ። ጠንካራም ይባሉ ነበር። ይኸ ዛዲያ እንደምን ስለ ዕድል ይቆጠራል? እኔማ ቢጠይቁኝ ዕድል ሚሄድበትን ያቃል እላለሁ። ያኔ በለጋነቴ እምብዛም አይገባኝም ነበር። አንዴ ዛዲያ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ሔኖክ ዕድል ከሰማይ አይወድቅም' ዕድል እንደ ሥዕል ነው። የሚገባውጋ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሆኖ
ማይጠብቀውጋ ኣይኸድም' ብለውኝ ያውቃሉ።”

“እኔም እሚታ ዮልያና ዕድል ኸሰማይ ይወድቃል?' ስትል
ሰምቻለሁ። አሳቡ አንድ ነው። እኔ ግን ዕድል ሚሰጠን እዝጊሃር ነው
እላለሁ።”

“ግና ማንችለውን አይሰጠንም። ማንችለውን ሰጥቶን ብንወድቅ...
ሳንችል ብንቀር ማን ሊጠየቅ ነው?”

“አየ ጥላዬ... ሰውን ትፈታተናለህ መሰል” አለችና ከት ብላ ሳቀች።

“እቴጌ... በመንበርዎ ትንሽ በቆዩ ኑሮ አሁን ኸመጣብን መቅሰፍት
እንድን ነበር” አለ፣ ጨዋታውን ለውጦ። “ድኻውም እኮ ቢሆን እርስዎን ተገን አርጎ ነበር የኖረ። ዛሬ ለሱ ሚያስብለት ማን አለው? ጉያዎ ደብቀው ያቆይዋትም አገር ይኸው አሁን መፈንጫ ሆነች። አሳቢ ጠፋ። አዋቂ ጠፋ። የዕውቀት ውጤቱ ሰላምና ቅንነት ነው፤ የዕውቀት ደግነቱ ማስተዋል ነው ብሎም ማልነበር ፈላስፋው? አሁን ሰላምም፣ ቅንነትም፣ ማስተዋልም የለ።”

ምንትዋብ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች። “አእምሮ ለነፍስ መዳኒቷ ነው፤ የልብ ሽልማት አእምሮ ነው' ይል የለ ፈላስፋው?”
👍14
#ምንዱባን


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ


ከፕሎሜ ጎዳና ላይ ያለ ቤት

ፕሎሜ ከተባለ ጎዳና ላይ ንብረትነቱ የመንግሥት ባለሥልጣን የሆነ ባለአንድ ፎቅ ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሁለት ክፍል ቤት ከፎቁ ላይ፣ ሁለት ክፍል
ደግሞ ከምድር ቤት ነበረው፡፡ በተጨማሪ እንደ ወጥ ቤት የሚያገለግል ተጨማሪ ክፍል ፎቁ ላይ ነበረው:: ከዋናው ጎዳና ጋር የተያያዘ ትልቅ የውጭ በር ሲኖረው በአበባ ያጌጠ ሰፊ ግቢ አለው:: ከበስተጓሮው እንደ
እቃና ማድቤቶች ሊጠቅሙ የሚችሉ ሌሎች ሦስት ክፍሎች ነበሩ:: በጓሮ በኩል ደግሞ የምሥጢር በር አለው::
ምስጢሩን ለሚያውቅ እንጂ ይህ
በር፣ በር መሆኑ በቀላሉ አይታይም:: ቤቱ ብዙ ጊዜ ሰው አይከራየውም::

በ1829 ዓ.ም አንድ በእድሜ በሰል ያለ ሰው መጥቶ ይህን ቤት
ይከራየዋል፡፡ ሰውዬው ብቻውን አልነበረም:: አንዲት ወጣት አብራው ነበረች፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ወጣትዋ ልጅ ደግሞ ኮዜት ናት፡፡ ቀደም ሲል ዣን ቫልዣ ይረዳት የነበረችው አሮጊት ደግሞ አብራቸው ናት:: ስምዋ ቱሴይ ይባላል:: ዣን ቫልዣ ቤቱን የተከራየው መሴይ ፎሽለማ በሚል ስም ነው::

ዣን ቫልዣ ለረጅም ጊዜ የኖረበትን ገዳም ለቅቆ ከወጣ በኋላ ምን
ተፈጸመ ቢባል ምንም የሆነ ነገር የለም:: እንደሚታወሰው ዣን ቫልዣ ገዳሙ ውስጥ ደስ ብሎት ነበር የሚኖረው:: በየቀኑ፡ ኮዜትን ያገኛታል።በተገናኙ ቁጥር ፍቅራቸው እየጠናና የአባትነት ስሜቱ እየዳበረ ይሄዳል፡፡
ልጅትዋን ፈጣሪ የሰጠው ፀጋ እንደሆነች ከማነ ባሻገር ይህችን ልጅ ከእርሱ ማንም ሊለያት እንደማይችል ገምቷል:: እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ከእርሱ የማትለይ ፍጡር ለመሆንዋ አልተጠራጠረም:: ይህም ደስታውን እጥፍ አደረገለት፡፡ ነገር ግን ልጅትዋን የግሉ ሀብት አድርጎ በመቀበልና የደስታው ምንጭ እንድትሆን በማድረጉ በመጠኑም ቢሆን የሕሊና ወቀሣ
ነበረበት::

ይህቺ ልጅ ገና እምቡጥ ናት:: ምንም ነገር አታውቅም:: ሕይወትዋን እንደፈቀደ የሚመራው ዣን ቫልዣ ነው:: ይህንንም ያደረገው ከክፉ ነገር
ላይ እንዳትወድቅ በማሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን ዓይነቱ አስተዳደግ የዓለምን ምንነት ለማወቅ እድል አልሰጣትም:: የራስዋን እድል ራስዋ ልትወስን አልቻለችም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሰውዬው ይህቺን ልጅ እንደ ቦይ ውሃ የመራት ከእርሱ እንዳትሄድ እንጂ ሙሉ በመሉ ለእርስዋ ብሎ አልነበረም፡፡
ይህ ነው የሕሊና ወቀሣ ያስከተለበት::
ከመነኩሴ ትምህርት ቤት ያስገባት እርሱ ነው:: መነኩሲት እንድትሆን የወሰነው እርሱ በመሆኑ ምናልባት ስታድግ በዚህ የተነሣ ልትጠላው ትችላለትች፡ ይህንና ይህን የመሳሰለ አሳቦች ናቸው ገዳሙን ለቅቆ እንዲወጣ
ያደረጉት:: ከዚህ ለመውጣት ከውሳኔ አሳብ ከደረሰ በኋላ አልቆየም::ግቢውን ለቅቆ ለመውጣት ጥሩ አጋጣሚ እየጠበቀ ሳለ ሽማግሌው ፎሽለማ መሞታቸው በዚሁ ሳቢያ ግቢውን ለቅቆ ወጣ፡፡

ከገዳሙ ሲወጣ ለገዳሙ አለቃ የነገራቸው ወንድሙ በመሞታቸውና እንደ እርሳቸውም መሞት የተነሣ መጠነኛ ሀብት ስለወረሰ ሌላ ቦታ ሄዶ መኖር የሚችል መሆኑን ነበር፡፡ ስለዚህ ልጁን ይዞ ያለ ብዙ ድካም ከሌላ
ቦታ ለመኖር የወሰነ መሆኑን ሲነግራቸው አልተቃወሙትም:: ልጅትዋን በማስተማር ገዳሙ ላበረከተው አስተዋጽኦ ለገዳሙ አምስት ሺህ ፍራንክ በስጦታ መልክ ሰጥቶ ነው የወጣው::

ከገዳሙ ሲወጣ የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅና ማንንም ሳያስቸግር
ያቺን ትንሽ ሳጥን እርሱ ራሱ በእጁ ይዞ ነው የወጣው:: የሳጥንዋን ቁልፍ ዘወትር ከእርሱ አይለያትም:: ስለሳጥንዋ ኮዜት ሁልጊዜም ትገረማለች፡፡አንድ ዓይነት የተለየ ጠረን አላት:: ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሳጥንዋን ከራሱ አይለያትም:: ሁልጊዜም የሚያስቀምጣት ከራሱ ክፍል ውስጥ ነው:: ከቦታ ወደ ቦታ በተዘዋወሩ ቀጥር እርስዋን ብቻ ነው አንጠልጥሉ የሚሄደው::
ኮዜት «ይህቺን ሣጥን ቀናሁባት» እያለች አንዳንዴ ብቻዋን ትስቃለች::

ከጊዜ በኋላ ዣን ቫልዣ ወደ ከተማ በወጣ ቁጥር እየተጨነቀ እንጂ
መዝናናትን ከተወ ሰንበት ብሉአል:: ፕሎሜ ጎዳና ላይ ካለው ቤት ውስጥ ከገባ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ከቤት አይወጣም:: ከዚያ ቤት ውስጥ እያለ ስሙ የሚታወቀው ኧልቲስ ፎሽለማ በሚል ስያሜ ነው::

እዚያው ቤት ውስጥ እያለ ሌሉች ሁለት አነስተኛ ቤቶች ከተለያዩ
ሰፈር ተከራይቶ በስሙ ይይዛል:: አልፎ አልፎ ወደ እነዚህ ቤቶች ተራ በተራ አንድ ጊዜ ከአንደኛው በሌላ ጊዜ ደግሞ ከሁለተኛው እየሄደ ወርም ሁለት ወርም ኮዜትን ይዞ ይቀመጣል:: አሮጊትዋን ግን ይዟት አይሄድም፡፡ይህንንም ያደረገው ከፖሊሶች ለመሰወር ነበር፡፡

ከቤት ውስጥ ሲሆኑ ቤቱን የምትመራው ኮዜት ናት ገዳም ውስጥ እያለች ስለቤት አያያዝ ትምህርት ቀስማለች:: ብዙውን ጊዜ ዣን ቫልዣ በጓሮ በኩል ከነበሩት ቤቶች ውስጥ ሲቀመጥ ኮዜት ከትልቁ ቤት ውስጥ
ፎቅ ላይ ነው የምትቀመጠው:: በየቀኑ ዣን ቫልዣ የኮዜትን እጅ እየያዘ ከዚያ ከተንጣለለውና ስአበባ ከአጌጠው ግቢያቸው ውስጥ ይንሸራሽራሉ፡፡
ወደ ከተማ የሚወጠበት ቀን
ውሰን ነው:: እሑድ እሑድ ግን
ወደ ውጭ ወጣ ብለው ይንሸራሸራሉ በዚህ ጊዜ የኮዜትን ቁንጅና ተመልካች እየበዛ መጣ በርግጥ እርሷም ሁሌ የምታስበው ነው ለሽርሽር በወጡ ቁጥር ወንዶች ሰብሰብ ብለው አንዱን አፍጥጣ ስታይ አንድ ሰው ‹‹በእርግጥም ቆንጆ ነሽ የሚላት መሰላት::ትንሽ ተሽኮረመመች:: ያን እለት ማታ ጥሩ እንቅልፍ አልተኛችም፡፡ ከተኛች በኋላ «እውነትም ቆንጆ ነኝ፤ የወንዶች ልብ አሁን እኔን ይመኛል?»
ስትል ብዙ አሰበች:: ገዳም ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የምታውቃቸውን ጓደኞችዋን በማስታወስ መልክዋን ከእነርሱ መልክ ጋር ማነፃፀር ጀመረች::
«እኔ እኮ ከእገሊት አላንስም፡፡ እገሊትም ብትሆን እስከዚህም የምትደነቅ ልጅ አይደለችም፡፡ ውይ እገሊት ግን በጣም ቆንጆ ናት:: እኔን ትበልጠኛለች ብቻ ምንዋ ነው ከእኔ የሚበልጠው?» እያለች ስለውበትዋ ታሰላስል
ጀመር::

አንድ ቀን ከግቢው ውስጥ እየተንሸራሸረች ሳለ አሮጊትዋ ቱሴይ
«ጌታዬ ይህቺ ልጅ እንዴት እየቆነጀች እንደሄደች ልብ ብለዋል?» ብላ ስትናገር ትሰማለች:: አባትዋ ምን መልስ እንደሰጠ ግን አልሰማችም::
የቱሴይ ንግግር ግን ስሜትዋን ነካው:: እየሮጠች ወደ ክፍልዋ ሄደች::
ከመስታወት ፊት ቆማ መልክዋን አየችው:: መስታወት በማየት መልክዋ ካስደነገጣት አንድ ሦስት ወር ያህል አልፎአል፡፡ የመጀመሪያው ቀን ሰው
ሳያያት ትንሽ አልቅሳለች:: የምታየው ራስዋን ሳይሆን የሌላ ሰው መስሎአት ነበር።

በጣም ቆንጆ ለመሆንዋ ለሁለተኛ ጊዜ አረጋገጠች:: መስታወቱና
ቱሴይ ያሉት ነገር ትክክል እንደሆነ አልተጠራጠረችም:: ቅርጽዋ፣ የቆዳዋ ቀለም፣ ፀጉርዋ፣ ዓይንዋ፣ ጥርስዋ፣ አፍንጫዋ ይህ ቀረሽ የምትባል ልጅ አልነበረችም:: ውበትዋ እንደጠዋት ፀሐይ ፊትዋ ላይ በራ፤ ተንጸባረቀ፣ ደመቀ፡፡ ወደ አበባው ቦታ ተመለሰች:፡ ወፎች ስለእርስዋ የሚዘምሩ መሰላት።
ራስዋንም እንደ ንግሥት ለመቁጠር ቃጣች::

ተመልሳ ስትመጣ ዣን ቫልዣ በአያት ጊዜ ልቡ ደነገጠ፡፡ የኮዚት
👍194
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ

ውድ አንባብያን #የጣሪያ_ስር_አበቦች የተሰኘው መፅሀፍ #በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ድርሰት ነው ስለዚህ እውነተኛ ታሪክ ደሞ የሚቀናነስ ነገር አይኖረውም ከባህላችን ምናምን አትበሉ እኛም በየቤታችን ስንት ጉድ አለ ያልወጣ ያልታተመ...መልካም ንባብ



...ይገባዋል እንዳልል እንኳን አእምሮው ውስጥ ያለውን ሙሉ በሙሉ አልተረዳሁትም። ያለውን ያደርጋል ብዬ ግን አስባለሁ ስሜት ግን ሰውን
የሚቆጣጠርበት መንገድ አለው ሁለታችንም ወለሉ ላይ ወደቅን ልታገለው ሞከርኩ። ታገልን፣ ተገለባበጥን፣
መንፈራገጥና መጨነቅ ያለበት የፀጥታ ትግል የእሱ ጥንካሬ ከእኔ ጋር።ፍልምያ አልነበረም።

እኔ ጠንካራ የዳንሰኛ እግሮች አሉኝ፡᎓ እሱ ትልቅ ክብደትና ቁመት አለው... በዛ ላይ ከእኔ የበለጠ የሆነ የጋለ ያበጠና ጠንካራ ነገር ለመጠቀም ማስተዋሉንና
ጤንነቱን የሰረቀው ቆራጥነት ነበረው
እወደዋለሁ ያንን ያህል የሚፈልገው ከሆነ እሱ የሚፈልገውን እኔም
እፈልገዋለሁ ትክክልም ይሁን ስህተት᎓ የሆነው ሆኖ ከዚህ ምሽት በፊት
ፍቅረኞችን የማያውቀው አሮጌ፣ ቆሻሻና የሚሸት ፍራሽ ላይ አረፍን፡ እዛ
ነው የወሰደኝ እና መርካት ያለበትን ያንን ያበጠ፣ ጠንካራ የወንድ የወሲብ
አካል በግድ ያስገባው: ጥብቅና የተቋቋመውን አካሌን ቀዶትና አድምቶት
ወደ ውስጥ ገባ።

አሁን በጭራሽ አናደርገውም ብለን የማልንበትን ነገር አደረግን።

አሁን ለዘለዓለም ተፈርዶብናል። ለዘለዓለም በእሳት ልንጠበስ ተረግመናል።በማያቋርጠው የገሀነም እሳት ውስጥ እርቃናችንን ተዘቅዝቀን እንሰቀላለን
ልክ አያትየው ከረጅም ጊዜ በፊት እንደተነበየችው ሆንን ኃጢአተኞች!

አሁን መልሶች ሁሉ አሉኝ፡

አሁን ልጅ ሊኖር ይችላል፡ ለእንደኛ አይነቶቹ የተዘጋጀውን ዘለአለማዊ
የገሀነም እሳት ሳይጠብቅ በህይወት ስለኃጢአታችን የሚያስከፍለን ልጅ
ይመጣል። ተራራቅንና እርስ በርስ ተያየን: ፊቶቻችን በድንጋጤ የደነዘዙና
የገረጡ ሆነዋል። ልብሶቻችንን ስናስተካክል መነጋገር እንኳን አልቻልንም

አዝናለሁ ማለት አያስፈልገውም ሁሉ ነገሩ ላይ ይታያል... የሚንቀጠቀጥበት
መንገድ፣ ልብሶቹን ለመቆለፍ ሲሞክር እጆቹ የሚንቀጠቀጡበት መንገድ
መደንገጡን ይናገራሉ፡

ቆይቶ ወደ ጣራው ላይ ወጣን።

ረጃጅም የደመና መስመሮች የድፍኗን ጨረቃ ፊት እያቋረጡ ነው እሷም
ትደበቅና እንደገና ትወጣለች:: ጣራው ላይ ሆነን ለፍቅረኞች በተዘጋጀው ምሽት ተቃቅፈን ተላቀስን ሊያደርገው ፈልጎ አልነበረም፡ እኔም ልፈቅድለት ፈልጌ አልነበረም ከእኔ ጋር ተመሳሳይ ደም ካለው ሰው ጋር አንድ ጊዜ ባደረግነው ነገር ልጅ የመምጣቱ ፍርሀት ወደ ጉሮሮዬ መጥቶ ምላሴ ላይ ቀረ: ከገሀነም ወይም ከእግዚአብሔር ቁጣ በላይ የሆነው ከባዱ ፍርሀቴ ጭራቅ የሚመስል፣ ቅርፁ የተበላሸና ደደብ ልጅ መውለድ አስፈርቶኛል። ግን
እንዴት ስለዚህ ጉዳይ ለክሪስ መናገር እችላለሁ? በበቂ ሁኔታ እየተሰቃየ
ነው: ሆኖም ግን መንገር አለብኝ ምክንያቱም የእሱ ሀሳቦች ከእኔ በተሻለ
በእውቀት ላይ የተመሰረቱ ናቸው።

“በአንድ ጊዜ መፀነስ አይኖርም:: ምንም ነገር ቢፈጠር ሌላ ጊዜ እንደማይሆን
እምልልሻለሁ፡ ይህ ነገር ከመፈጠሩ በፊት ራሴን አኮላሻለሁ! አለኝ፡ ከዚያ
ወደ እሱ ሳበኝና የጎን አጥንቶቼ የሚሰበሩ እስኪመስለኝ ድረስ አጥብቆ አቀፈኝ። “አትጥይኝ ካቲ… እባክሽ እንዳትጠይኝ፡ ልደፍርሽ ፈልጌ አልነበረም
በእግዚአብሔር እምልልሻለሁ። ብዙ ጊዜ ተፈትኜ አውቃለሁ ግን ብዙ ጊዜ ክፍሉን እለቃለሁ ወይም ወደ መታጠቢያ ቤት እገባለሁ አለዚያም ጣራው
ስር ወዳለው ክፍል እወጣለሁ ወይም እስክረጋጋ ድረስ አፍንጫዬን መፅሀፍ ውስጥ እቀብራለሁ እና ማለፍ ችዬ ነበር:”

በቻልኩት መጠን ጥብቅ አድርጌ አቀፍኩት። “አልጠላህም ክሪስ” ስል አንሾካሾኩ ጭንቅላቴን ደረቱ ላይ አድርጌያለሁ: “አልደፈርከኝም፤ የምሬን ብፈልግ ኖሮ ላስቆምህ እችል ነበር ማድረግ ያለብኝ ጉልበቴን ጥንክር አድርጌ ወደላይ ማድረግ ብቻ ነበር፡ የኔም ጥፋት ነው” አዎ የኔም ጥፋት ነው። የእናቴን
መልከመልካም ወጣት ባል ከመሳም የተሻለ ነገር ማወቅ ነበረብኝ፡ የወንድ
ጥንካሬ አካላዊ ፍላጎቶች ባሉትና ሁልጊዜ በሁሉም ነገርና በሁሉም ሰው
ተስፋ በቆረጠ ሰው ዙሪያ ወንድሜም ቢሆን እንኳን ሰውነትን የሚያሳይ ልብስ
መልበስ አልነበረብኝም: በፍላጎቶቹ እየተጫወትኩ፣ ሴትነቴን እየሞከርኩ፣
የራሴን የሚቃጠል የመርካት ፍላጎት እያየሁ ብቻ ነበር።

ይህ የተለየ አይነት ምሽት ነው፤ ልክ ዕድል ከረጅም ጊዜ በፊት ይህንን ቀን
ያቀደው ይመስላል እና ይህ ምሽት ትክክልም ይሁን ስህተት እጣ ፈንታችን
ነው:

ንፋሱና ቅጠሎቹ ዜማ አልባ ሙዚቃ ያሰማሉ: ሙዚቃው ያው ነው: ሰው የመሰለ አፍቃሪ የሆነ ፍጥረት እንዴት በዚህ ቆንጆ ምሽት አስቀያሚ ሊሆን
ይችላል?

ምናልባት ጣሪያው ላይ ብዙ ቆይተናል፡

የመስከረም መግቢያ በመሆኑ ጣሪያው ቀዝቃዛ፣ ጠንካራና ሻካራ ሆኗል።
ቅጠሎቹ መርገፍ ጀምረዋል ጣራው ስር ያለው ክፍል ልክ እንደ ገሀነም ያቃጥላል ጣራው ላይ ግን በጣም በጣም ይቀዘቅዛል
እኔና ክሪስ ለደህንነትና ለሙቀት ተቃቅፈን ተቀምጠናል። በጣም መጥፎ ወጣቶችና ኃጢአተኞች:: ያለማቋረጥ በመጠጋጋት በጣም ተወጥረው በቀጠኑ
ታሪኮች የራሳችንን ክብር አሽቀንጥረን ጥለነዋል፡ በአንድ ወቅት በራሳችን
ስሜታዊ ተፈጥሮ አብዝተን የተፈተንን ቢሆንም... በዚያ ወቅት እንኳን እሱ እኔም ስሜታዊ መሆኔን አላውቅም ነበር፡ ልቤን የሚሰውርና ሽንጤን
እንድሰብቅ የሚያደርገኝ ቆንጆ ሙዚቃ ብቻ ይመስለኝ ነበር፡ በጣም ተጨባጭ የሆነ ሌላ ነገር እንዳለ አላውቅም ነበር።

ልክ አንድ ልብ እንደምንጋራ ሁሉ በሰራነው ስራ ራስን የመቅጣት አሳዛኝ ቅኝት
እየደለቅን ነበር ቀዝቃዛው ነፋስ የረገፈ ቅጠል ወደ ጣራው አምጥቶ ድንገት
ፀጉሬ ውስጥ እንዲያዝ አደረገው:: ክሪስ ሊያነሳው ሲሞክር ደርቆና ተሰባብሮ
ወደቀ ህይወቱ ቅጠሉ በንፋስ መብረር እንዴት እንደሆነ በሚያውቀው
ሚስጥር ላይ የተመሰረተ ይመስል ክሪስ ቅጠሉን አተኩሮ እየተመለከተ
ነበር: እጆችም ክንፎችም የሉትም... ግን ሞቶም መብረር ይችላል።

“ካቲ” በሚደነቃቀፍ ደረቅ ድምፅ ጠራኝ፡ “አሁን ልክ ሶስት መቶ ዘጠና ስድስት
ዶላር ከአርባ አምስት ሳንቲም አለን በቅርቡ በረዶ መጣል ይጀምራል።
በልካችን የሆነ የክረምት ኮት ወይም ጫማዎች የሉንም፧ መንትዮቹ ደግሞ
ደካማ ስለሆኑ በቀላሉ ብርድ ሊያሳምማቸውና ከዚያ ወደ ኒሞኒያ ሊለወጥባቸው
ይችላል ሌሊት ነቅቼ ስለእነሱ እጨነቃለሁ እና አንቺንም አልጋሽ ላይ
ሆነሽ ኬሪን አተኩረሽ ስትመለከቻት አይሻለሁ፡ አንቺም ተጨንቀሽ መሆን
አለበት። አሁን ከእናታችን ክፍል ውስጥ እንደበፊቱ ገንዘብ የማግኘታችንን
ነገር እጠራጠራለሁ። ሠራተኞች ገንዘብ እየሰረቋቸው እንደሆነ ጠርጥረዋል።አሁን ምናልባት እናታችን አንቺ ልትሆኚ እንደምትችይ ትጠራጠር ይሆናል አላውቅም... እንደማይሆን ተስፋ አለኝ።

“እነሱ ምንም ቢያስቡ በሚቀጥለው ለመስረቅ ስሄድ ጌጣጌጧን ለመስረቅ
እገደዳለሁ። ትልቅ ነገር እወስድና ከዚያ እናመልጣለን ልክ ርቀን እንደሄድን በቂ ገንዘብ ስለሚኖረን መንትዮቹን ወደ ዶክተር እንወስዳቸዋለን፡” አለ፡

“ጌጣጌጦቹን ውሰድ።” እንዲወስድ ብዙ ጊዜ ለምኜው ነበር። በመጨረሻ
ሊያደርገው ነው እናታችን ልታገኘው የታገለችለትን ብዙ ገንዘብ የሚያወጣ
ጌጥ ታጣለች በዚያ ሂደት ውስጥ እኛንም ታጣለች: ግን ግድ ይኖራት
ይሆን?
👍402👏2