አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)


...“በጣም ጎበዝ ያቤዝ፡፡ ስለ አለብህ የጤና ችግር ለማውቅ መፈለግ በጣም ጉብዝና ነው፡፡ በተጨማሪም ብዙ ጥቅም አለው፡፡ ባይፖላር ዲስኦርደር ማለት፣ ሰዎች ሁለት የስሜት ዋልታዎች መፈራረቅን ተከትሎ፣ተደጋጋሚ የሚመጣ የባህሪ መለዋወጥ ሲያጋጥማቸው ነው።
መለዋወጦቹም፧ በስሜት ከፍታዎች እና በስሜት ዝቅታዎች መካከል የሚከሰት ነው:: በመሆኑም ይህ ችግር ያለበት ሰው፣ ባለበት የስሜት ከፍታ ወይም ዝቅታ መሰረት አሰተሳሰቡ፣ ውሳኔ አሰጣጡ፣ በነገሮች ላይ የሚኖረው ፍላጎት፣ ድርጊቶችን ለማድረግ የሚኖረው ሀይልና ጉልበት፣ በአጠቃላይ የህይወት አመለካከቱና አረዳዱ በሰዐቱ እንዳለው
የስሜት ሁኔታ የተለያየ ነው፡፡ በተጨማሪም፣ የዚህ ችግር ተጠቂ የሆኑ
ሰዎች ውስጣዊ ለውጦች ሊኖራቸው፣ አካባቢያቸው የተለወጠ ስለሚመስላቸው የሚሰጡት ምላሽ የተሳሳተ ሊሆን ይችላል፡፡

የዚህ ችግር ተጠቂዎች የስሜት ከፍታ ሲኖራቸው ማኒያ ወይም ሃይፖማኒያ ይባላል፡፡ ማኒያ ከሃይፖማኒያ ተመሳሳይ ምልክት ቢኖረውም፣ ማኒያ በህመም ደረጃው ከበድ ያለ በሽታ ነው፡፡ ይህ
የባህሪዎች መለዋወጥ፣ ችግሩ ያለባቸውን ሰዎች በስራ፣ በትምህርት፣
በማህበራዊ እንቅስቃሴያቸው እና ግንኙነቶቻቸው ላይ ችግሮች
ማወቅ እንዲከሰቱ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ የስሜት ከፍታ ላይ ሲሆኑ፤ በፊት
ብዙም ትኩረት ማይሰጡትን ጉዳይ የማየት፣ የመስማትና የማወቅ ፍላጎት መጨመርን ያሳያሉ፤ ከነበራቸው ማህበራዊ መግባባት የጨመረ
የመቀራረብና የመግባባት ባህሪ ያሳያሉ፣ የማይጨበጡ፣ ወይም

ቶሎቶሎ ሚቀያየሩ አዳዲስ ሀሳቦችንና ንድፎችን በማምጣት ያወራሉ፤አንድ ቦታና አንድ ሃሳብ ላይ በጥልቀት ማስብ ስለሚያስጨንቃቸው ቶሎ ከሃሳብ ወደ ሃሳብ ይቀያይራሉ፣ በጥቃቅን ነገሮች አክርረው ይጨቃጨቃሉ፣ ነገሮቹ ከነርሱ ህይወት ጋር ጠቃሚ ግንኙነት ባይኖራቸውም፣ ስለሚሰሟቸው ነገር ከፍተኛ የማወቅ ፍፈላጎት ያሳያሉ፤ ለነገሮች ከተገቢው በላይ ይናደዳሉ፣ ይበሳጨሉ፣ ከብሰጭት ስሜት መውጣት ይቸገራሉ፣ የተጋነነ በራስ የመተማመን ስሜት ይኖራቸዋል፤ የሚያመጧቸውን ሀሳቦች ፍፁም አድርገው ያስባሉ፡፡
ትችትና አስተያየት መቀበል ይከብዳቸዋል እንደሚተገብሯቸው እርግጠኛ መሆን፡፡ የእንቅልፍ ፍላጎት መቀነስ፤ በፊት ከሚተኙበት ሰዓት ዘግይቶ መተኛትና ባልተለመደ ንቁ መሆን፤ ያልተለመደ
ወሬኛነት፤ ከማይግባቧቸውና ከማያቋቸው ሰዎች ጋር ጭምር
ያልተለመደ የማውራት ፍላጎት፤ ነገሮችን አብዝቶ ማቅለል፤ ደካማ ውሳኔ መስጠት ያስከትላል፡፡ የመሳስሉትን ምልክቶች የሚያሳዩ ሰዎች ሃይፖማኒያ ይባላል፡፡”

“ስለዚህ ዶክ፣ አንድ ሰው የተዘረዘሩት ምልክቶች በሙሉ ሊኖርበት ነው ይሄ ችግሩ አለበት ሚባለው?”

“ኖኖ! እንደዛ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ከላይ ከዘረዘርኳቸው ውስጥ፣ ሶስቱን ወይም ከዚያ በላይ ምልክቶች ካሳየና በሃኪም
ከተረጋገጠ ሃይፖማኒያ አለበት ልንል እንችላለን፡፡” በውስጤ አሰላሰልኩ፡፡ እነዚህ ስሜቶች ሶስቱ ሳይሆን ሁሉም ግዜ ጠብቀው፣እብደቴ ሲነሳ በደስታ ማስተናግዳቸው ሲሜቶች ናቸው፡፡

“ዶክ ከእነዚህ ስሜቶች አብዛኞቹ በተደጋጋ እኔን ሲስሙኝ ኖረዋል። ታዲያ ሃይፖማንያ ሳይሆን ለምን ባይፖላር አለብህ አልከኝ?”

ትክክል ነህ ያቤዝ፡፡ አንተ እነዚህ ስሜቶች ሲሰሙህ እንደከረሙ ነግረኸኛል፡፡ ነገር ግን፣ ሃይፖማንያ ሚባሉት እነዚህን
ስሜቶች ብቻ ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ አንተ ግን፣ እነዚህ ስሜቶች ብቻ አይደሉም ሲሰሙህ የነበረው፡፡ ሌላም ስሜቶች ነበሩህ፡፡”

“ሌላ ስሜትም ስትለኝ፣ ሌላ ምን አይነት ስሜት?"

“አንተ የሃይፖኒያ ስሜቶች ብቻ ሳይሆን የነበረህ፣ ግዜን ጠብቆ ሚፈራረቅ የስሜት ዝቅታ ወይም የዲፕረሽን ምልክቶችም ነበሩህ፡፡”

“የስሜት ዝቅታ /የዲፕረሽን/ ምልክቶችስ ምን ምን ናቸው?"

“የዲፕረሽን ምልክቶች የምንላቸው፤ ከፍተኛ ብስጭት፣ማህበራዊ መነጠል፣ ብቸኝነት ማብዛት፤ ከፍተኛ ምክንያት የለሽ የድካም ስሜት፧ የጡንቻ መዛል፤ ቁርጥማት፣ የጀርባ ህመም፤ የመረበሽ
ስሜት ፣ በስራ፣ በትምህርትና ቤተሰባዊ ሃላፊነቶች ከተገቢው በላይ መጨነቅ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፍላጎት መቀነስ፣ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የመዝናናት የፍላጎት ማጣት፣ እንዲሁም፣ የጥፋተኝነት ስሜቶች፣ ዋጋቢስ እና ተገቢ ያልሆነ ራስን መቅጣት፣ በራስ የመተማመን ስሜት መቀነስ፣ ደካማ እና የቀነሰ ትኩረት፣ አፍራሽ እና መጥፎ ሃሳቦችን በተደጋጋሚ ማሰብ፣ ራስን የማጥፋት አስተሳሰብ እና ራስን የመጉዳት ወይም ራስን የመግደል ሙከራዎች እና የመሳሰሉት ምልክቶች ካሉበት፤ የዲፕረሽን ችግር አለበት ይባላል”

እነዚህ የበሽታ ምልክቶች ከሆኑማ
ታምሜያለሁ፣ሲፈራረቁብኝ ኖረዋል፡፡ ነገር ግን፣ ብዙ ሰው እንደዛ ሚሰማው
ይመስለኛል፡፡ ሃኒ በአምሮዬ ውልብ አለች፡፡ ትበሳጭ ነበር፤ ትናደድ ነበር፤ ብቻዋን መደበቅ ፈልጋ ስትመጣ ነው የተገናኘነው፣ እራሷን አጥፍታለች። እና ሃኒም እንደኔ የዲፕረሽን ታማሚ ነበረች ማለት ነው?፣ እራሷን ለማጥፋት ያደረሳት ይህ ህመም አልባ በሽታ ነበር ማለት ነው?

“እና ዲፕረሽን አሁን ከጠቀስካቸው ምልክት ሶስቱን ማሳየት ማለት ነው?”

“አይደለም፡፡ ዲፕረሽን እንደ ሃይፖ ማንያ በሶስት ምልክት ብቻ አይደለም፡፡ ከእነዚህ ምልክቶች መካከል አምስቱን ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑት አንድ ስው ደጋግሞ ሲኖረውና የእለት ተለት ህይወቱን እንዳይመራ ተፅእኖ ሊኖራቸው ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህን በሽታዎች
ሃኪም ሳያማክሩ ምልክት በመቁጠር ብቻ እንዲህ ነኝ እንዲያ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ግን ምልክቶቹ ከተደጋገሙና ከቆዩ ሃኪም ማማከር አስፈላጊ ነው፡፡”

“እነዚህም ምልክቶች እኮ በደንብ እንደነበሩኝ ነግሬሃለው ዶክተር፡፡ ታድያ ለምን ዲፕረሽንም አለብህ አላልከኝም? ህይወቴን እዚህ ያደረሱት እኮ አሁን የጠቀስካቸው ምልክቶች ሲስሙኝ ነው። ያማል፣ያላምጣል፣ ያመነዥካል፣ ሞት እንደ ጣፋጭ መድሃኒት ይናፍቃ፡ ዶክ፣
ስለዚህ እኔ ያለብኝ ችግር እንደውም ዲፕረሽን ነው፡፡”

“አየህ ያቤዝ፣ ቅድም ለዛ ነበር ሃኪም ሳያማክሩ ምልክቶችን ቆጥሮ ይሄ ነው፣ ያ ነው ያለብኝ፣ ማለት አይቻልም ያልኩህ፡፡ አንተ የሃይፖማንያም የዲፕረሽንም ምልክቶች እየተቀያየሩብህ አሳይተሃል፡፡
አንድ ስው የሃይፖማንያ ምልክት ብቻ ካለው፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ ሃይፖማንያ አለበት ይባላል፤ የድባቴ ምልክቶች ብቻ ካሉበት፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ የድባቴ ችግር አለበት ይባላል፤ የሁለቱ በሽታዎች ምልክት እየተፈራረቁ ከተሰሙት ደግሞ፣ በሃኪም ከተረጋገጠ በኋላ የባይፖላር ችግር አለበት ይባላል፡፡”

አሁን ለቀናት ሳነብ አልገለጥልህ ያለኝ ተገለጠልኝ፡፡ አይኔ በራ፡፡ዶክተር እያወራ ነው፡፡ “ባይፖላር ዲስኦርደር የዕድሜ ልክ ሁኔታ ቢሆንም፣ሕክምና በመከታተል የስሜት መለዋወጥን እና ሌሎች
ምልክቶችን በመቆጣጠርና መሰናክሎችን በማስቀረት በህይወት ስኬታማ መሆን ይቻላል፡፡ ባይፖላር
ዲስኦርደር በስነ ልቦና ምክር (ሳይኮቴራፒ)እና በመድኃኒቶች ይታከማል፡፡

በግማሽ ልቤ ነው ማዳምጠው፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ተወሽቄያለሁ።ወደኋላ ተመልሼ በሃሳብ እየተብሰለሰልኩ ነው፡፡ ዶክተር እውነቱን ነው::ቅድም የጠቀሳቸው ስሜቶች ብዙ ግዜ ተፈራርቀውብኛል። ባይፖላር ዲስኦርደር፣ በጋና ክረምት የሚመሰሉ ስሜቶች መፈራረቅን ተከትሎ
የሚመጣ የባህሪ መለዋወጥ ነው፡፡ በጋ፣ ብርሀን ነው ፧ ተስፋ ነው ፤ በጋ ሙቀት ነው ፤ ሀይል ነው፤ መቦረቅ ነው፡፡ ክረምት ግን፣ ብርድ ነው ፤መሸሸግ፣ መኮራመት ነው፡፡ አዎ! የኔ
👍3😁1
#ሰመመን


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

አቤል ወላጆቹን ትቶ ወደ ትዕግሥት በሐሳቡ መጓዝ ስለጀመረ ዐይኑን ቦዘዝ እንዳደረገ ዝም አለ ።

ምነው ? ”አሉ ዮናታን ፥ አንዳች ስሜቴን የሚጎዳ ነገር የተናገሩ መስሎአቸው ተደናግጠው ። ሐሳባቸው ዘሎ
ያረፈው እናቱ ወይም አባቱ ሞተዋል ከሚል ግምት ላይ ነበር ። ይህን ደግሞ ከአሁን በፊት አልነገራቸውም ፡ ግራ ተጋቡ።

“ ምንም አይደለም ”አላቸው ከሐሳቡ ባነነና ። እርስዎ ለእኔ ያለዎት ክብርና ፍቅር እየታሰበኝ ነው ።ለእኔ መድከምዎ አንሶ ወላጆቼን ሊረዱልኝ ሲያስቡ ... ”

“ ይህ ውለታ ሆኖ ካሳሰበህ ተሳስተሃል ” አሉት ዮናታን “ይህ ማንኛውም ዜጋ ሊያደርገው የሚገባ ነገርም ነው ። ማስተማር ለእኔ ግዴታ ሳይሆን ፥ የመንፈስ ክብርና ኩራት የሚሰጠኝ መስክ ነው ። እናም ጥሩ ተማሪዬን ጥሩ
ቦታ ወይም የሙያ ዘርፍ ላይ ለማየት እንጂ የማስተማር ግዴታዩን ለመወጣት ብቻ አይደለም የማስተምረው ። መረዳዳት ያስፈልጋል ። ደግሞም አጥብቀን አናስበውም እንጂ
ከመረዳዳት ውጪ የሆነ እንቅስቃሴ ምን ታገኛለህ ? ሁሉም የግል ጎጆ ቢቀልስም፡ የሕይወት እንቅስቃሴው የጋራ ነው። ማኅ
በረሰብ ከሌለ ግለሰብ የሚባል ነገር የለም " ምኑን ከምን አርጎ ሊንቀሳቀስ ? ነገሩ ይህ ሆኖ ሳለ ከግል ኑሮአችን በመነሳት የምናደርገው፥ ማኅበራዊ ግንኙነት ከመረዳዳት እንጻር
አጉልተን አናየውም እንጂ ኑሮአችን በመረዳዳት የተሳሰረ ነው።

ዮናታን ከልባቸው እየተመሰጡ ንግግራቸው እየጎላና እየረቀቁ ሲሔድ ፥ የአቤልን እንባ አደረቀው ። አፉን ከፍቶ
ነበር የሚያዳምጣቸው ።

“እሺ እንግዲህ 'እንዳሉት 'አሁን ያለኝ ምርጫ ትምህርቴን ማቋረጥ ነው ። እናም አቋርጠዋለሁ ” አለ የሜዝት
በሚመስል ጉልህ ድምፅ "

«« አዎ ! ቆራጥነት ያስፈልጋል አሉ ዮናታን
“ቆራጥ ካልሆንክና ውሳኔ መውሰድ ካልቻልክ ሕይወትህ የተመሰቃቀለ ይሆንብሃል ። አብዛኛውን ጊዜ ሕይወት የባለ ቤቷን ቆራጥነት ትፈታተናለች የቆራጥነትና ወሳኝነት ትርጉም የሚገባህ ውጤቱን ካየህ በሁዋላ ነው ። አይዞህ
በአንተም ሆነ በወላጆችህ ላይ የሚደርስ ጊዜያዊ ችግር ቢኖር በጋራ እንወጣዋለን አንተም ነገ ትልቅ ሰው እንደምትሆን
አትጠራጠር ። ”

በፊት ያንዣብብ የነበረው የጭንቀት ደመና ከአቤል ፊት ሳይ እየጠፋ መሔዱን ሲመለከቱ ዮናታን ደስታ ተሰማቸው
ጥረታቸው ዋጋ እንዳገኘ እድርገው ገመቱ።

“ እሺ ፤ ለማቋረጥ የሚያስፈልጉኝን ነገሮች ላሟላ ”ብሎ አቤል ከተቀመጠበት ተነሣ ።

“ ግሩም ! ” አሉ ዮናታን ሐሳቡን በመደግፍ ለማቋረጡ ተግባር የምረዳህ ነገር ካለ ብቅ ብለህ አማክረኝ ፡

አቤል እጅ ነሥቶ ሲወጣ በቆራጥነት ስሜት ግንባሩን አኮማትሮ ነበር ። በሐሳቡ የታየው ነገር ይህን “ የሥቃይ
ግቢ ” በአስቸኳይ ለቅቆ መውጣት ብቻ ነበር ። አንድ የሆነ ተቃራኒ ስሜት ጭንቅላቱን ቢከብደውም እስኪወጣ ድረስ ቀውል አልተከሠተለትም ።

ዮናታን ከደስታቸው ብዛት የሚይዙ የሚለቁትን አትተው ፊታቸው የተቀመጡትን ወረቀቶች ያለ ምንም ዓላማ ወዲያ ወዲህ ያገላብጡ ጀመር ፡ አቤል ሐሳባቸውን መቀበሉን የመጀመሪያው ደረጃ አድርገው ወሰዱት የዕቅዳቸው መጀመሪያ እንደ ተሳካ አድርገው በመገመት በጥረታቸው ረኩ ።

“ እሺ እንግዲህ ፡ ትምህርቱን አቋረጠ ። ከዚያ በኋላስ ምን መደረግ አለበት?” በማለት ዮናታን ፥ አቤልን ከተጠመደበት የዐይን ፍቅር ሕመም ለማዳን የሚቀጥለው ደረጃ ምን መሆን እንዳለበት ማሰብ ጀመሩ ። ይህን ሐሳብ በማውጣትና በማውረድ ላይ እንዳሉ በሩ ተከፈተ ።

ቀና ሲሉ አቤል ነው ፊቱ ከስሏል ዐይኖቹ ቀልተዋል በሆነ ስሜት ከራሱ ጋር የተጣላ ይመስላል ከኋላ እንደ ተባረረ ሰው እየቻኮለ ነበር በሩን የከፈተው።

ይቅርታ ያድርጉልኝ ለምን እንደ ዋሸሆዎት አላውቅም። ምናልባት ፈርቼዎት ይሆናል ትምህርቴን ማቋረጥ የለብኝም ብሞክርም አልችልም አላቸው ወደ ውስጥ ሳይገባ በሩ ላይ ቆሞ።

ዮናታን ግር አላቸው ምን ሰይጣን ነው በአንዴ ሐሳቡን ያስቀለበሰው ለጊዜው
የሚመልሱትም ሆነ የሚጠይቁት ነገር እልነበራቸውም።

አቤል ሐሳቡን የቀየረው በሩን ወጥቶ ገና ጥቂት እንኳን ሳይራመድ ነው ። ክፍል ውስጥ ሆኖ ከዮናታን ጋር ሲስማማ ከውስጡ ሲጫጫነውና ሲከብደው የነበረው ተቃራኒ ስሜት ገና ከመውጣ እውነት አሁን ትምህርትህን አቋርጠክ ይህን ትእግስት ያለችበትን ግቢ ልትለቅ ነው? እውነት ከትእግስት ጋር ሳትተያይ ውለህ ማደር የምትችል ይመስልሃል?
የዐይን ፍቅረኛህን ትተህ የት ልትደርስ? እያለ እንደ ጥላ ተከተለው ። አቋርጣለሁ እያለ ቀድሞ ሲፎክር የነበረው ሁሉ ባዶ ጩህት ሆኖ አገኘው ትእግሥትን ጥሎ
ወዴት ?

ለዮናታን ቃል መግባታ አሳዝነው ። እንዴት እንደሚያስተባብላቸወ በማሸበ ቆሞ ተጨነቀ። ሆኖም ዮናታን ያቋርጣል በሚል ተስፋ ልባቸውን ሞልተው እንዳይቀመጡ ቶሎ ተመልሶ ማስተባበል
ነበረበት እራሱን እየረገመ ነው የተመለሰው ምነው? ተስማምተን አልሔድክም እንዴ? ምን ነካህ? ” አሉት ዮናታን በተደናገጠ ስሜት።

አዎ በሃሳቦዎ ተስማምቼ ነበር የወጣሁት ነገር ግን አርቄ ሳስባት ፈተና ተፈትኜ ዕድሌን መሞከር አለብኝ ?” አላቸውና መልስ ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ ሔደ።

«ስማኝ እንጂ አቤል ! ቆይ እስቲ ?” አሉት ዮናታን ከተቀመጡበት ተነስተው ሊከተሉት እየሞከሩ ዝም ብሏቸው ካጠገባቸው መጭ አለ።

ዮናታን በብስጭት ፈዘው ቀሩ ለሰም ሰው እኔ ምን አስጨነቀኝ ? ” የሚል ተፈታታኝ ሐሳብ መጣባቸው
ተስፋ የመቁረረጥ ስሜት ተስማቸው አኳኋኑ አናደዳቸው ግን ሁኔታን ባስታወሱ ጊዜ ልባቸው ሊጨክን አልቻለም ። እድራጎቱ አንድም የልጅነት አሊያም የፍቅር ቡሶት ነው ደመደሙ።

ቢሮእቸውን ቆልፈው ቀጥታ ወደ አቶ ቢልልኝ ቢሮ አመሩ አረማመዳቸው የሩጫ ያህል ነበር ። በመንገዳቸው
ላይ ሦስት ያህል የሚያውቋቸው ሰዎች ሰላምታ ሳይሰጡ ማለፋቸው አልታወቃቸውም።

ከከባቢልልኝ ቢሮ እንደ ደረሱ ሰላምታ እንኳን ሳይለዋወጡ አረእስተ ጉዳያቸውን አነሱ።

«ቢልልኝ የዚያን ልጅ ጉዳይ ሁላችሁም ቸል ማለታችሁ ነው ?

አቶ ቢልልኝ ! የዮናታን አርእስቱ ስለ አቤል ጉዳይ መሆኑ ለመገመት ጊዜ አልወሰደባቸውም።

የአቤልን ነገር ነው ?...ችላ ማለት አይደለም ኮ እኔ በበኩሌ የዐቅሜን እየመበከርኩ ነው። ሆኖም የልጁ ሁንታ
አስቸኳይ መፍትሔ የሚገኝለት አልሆነም።

"እንዴት ? ” አሉ ዮናታን ፡ ለመቀመጥ ወንበሩን እየሳቡ።

እስቸኳይ መፍትሔ ለማግኘት ልጁ ምቹ አይደለም ቢልልኝ ወደ ጉዳዩ ጠልቀው ሲገቡ ፊታቸው እየተለዋወጠ አዎ አቤል ግልጽ አይደለም ። አንዳንዱ ሰው ሰላፈቀራት ሴት ላገኘው ሰው ሁሉ በየደቂቃው ካላወራ አይሆንለትም ፤ ሌላ አርዕስት የለውም ። ሁሌ ሰው ለሰ
ፍቅር መፍትሔ የሚፈልግለት ይመስለዋል አንዳንዴ ደግሞ ለማንም ሳያዋይ ፍቅሩን ራሱ ዋጥ አርጎ ውስጥ ውስጡን
መቃጠል ይመርጣል ። ሌላ ሰው ለሱ ፍቅር ጤናማ አመለካከት ያለው አይመስለውም የአቤል በደረጃ ከመለየቱ በቀር ይሄኛውን ይመስላል ሁሉም አይነት ግን አስተዳደግና አካባቢን የተመረኮዘ መሠረት ይኖረዋል።

"ታዲያ አሁን የአቤል ነገር እንዴት ይሻላል ?” አሉ ዮናታን ፥ በተጨነቀና በተቻኮለ ስሜት ።

“ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ መፍትሔ ያገኛል ” አሉ ቢልልኝ፡ “ ጊዜ ! ጊዜ ይወስዳል ። የሥነ ልቡና ጥናት
ሥራ ዘዴና ትዕግሥት ይጠይቃል አቤል ፥ ሌላው ቀርቶ የግል የሕይወት ታሪኩን ለመናገር ፈቃደኛ አልሆነም
ስለዚህ ሥራችን
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

.....ሻምበል ብሩክ ይመስላታል፡፡
የሆነ ደስ የሚል መናፈሻ ውስጥ እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ሲንሸራሸሩ ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ኣንድ ጥላው ቀዝቀዝ ያለ፣ ንፁህ አየር ወደሚነፍስበት የወይን ዛፍ ሥር
ይመጡና ከሥሩ ካለው ለምለም ሣር ላይ ጋደም ይላሉ::

በዚህ ጊዜ እሷ እሱን ትራስ አድርጋ፣ ፀጥ ያለውን ኣካባቢ እየቃኙ የተፈጥሮ ውበትን ሲያደንቁ፤ የሁለቱም ዐይኖች ከፊት
ለፊታቸው በሚያዩዋት የጽጌዳ ቅርንጫፍ ላይ ባለችው እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ተማርኮ፤ ጽጌረዳዋን ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላ፤ ስለዚያች ጽጌረዳ ለመናገር በአንድ ጊዜ “ እንዴ ” ብለው ይጀምራሉ፡፡

"ምን ልትል ነበር?” ትለዋለች እየሣቀች::
“አንቺስ ምን ልትይ ነበር?” ይላታል እሱም እየሳቀ::

“እንዴት ታምራለች ልል ነበር” ስትለው..
“እኔም እንደሱ ልል ነበር:: ከማማሯም በላይ ደግሞ ልክ የሁለታችንን ፍቅር ትመስላለች ልልሽ ነበር” ይልና ቁልቁል ወርዶ ከንፈሯን ይስማታል፡፡

“ማማሯስ እሺ የሁለታችንን ፍቅር እንዴት ነው የምትመስለው?” ትለዋለች:: ስለፍቅራቸው የበለጠ እንዲያወራላት
ጓጉታ::

“ያልፈነዳ እንቡጥ ጽጌረዳ በአበባነት ደረጃ ላይ ካለው ፍቅራችን ጋር ይመሳሰላል” ይላታል፡፡

“አበባው ፍሬ የሚሆነው መቼ ነው ብሩኬ?” አይን፤ ዐይኑን ሽቅብ እያየች ትጠይቀዋለች::
ወፎች የሚዘምሩ ይመስላታል፡፡ ንፋሱ ሽውው ይላል፡፡ዛፎች ይደንሣሉ፡፡ሰማዩ የጠራ ነው፡፡ሌላ ዓለም፡: ልዩ ዓለም.....
“የሠርጋችን ዕለት በዚያ በጫጉላ ቤት ውስጥ አሀዱ ብለን ትዳርን ስንቀድሰው፡፡ አይመስልሽም ትሁቲና? ቆይ እንዲያውም ይህችን ጽጌረዳ ስለፍቅራችን ገፀበረከት ላቅርብልሽ” ይልና ብድግ ብሎ ያቺን የምታምር እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ቀጥፎ ያመጣና
ይሰጣታል::

“በሠርጋችን ዕለት? .... በጫጉላ ቤት? .... አሀዱ ብለን?... ስንቀድሰው?
ምን ዐይነት ጣጣ ነው? የሆነውን ሁሉ
ብነግረውስ? የጫጉላ ቤቱ ዕቅዳችን መፍረሱን፣ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንፅህናዬን መድፈሩን፤ ብገልጽለትስ?
አያምነኝ ይሆን?
በቃሽኝ አታላይ ነሽ ይለኝ ይሆን? ልንገረው? እያለቀስኩ ልግለጽለት
ወይንስ ልተወው? ወይኔ አምላኬ ምን ጣጣ ውስጥ ከተትከኝ? ወይኔ
ብሩኬ በዚህ ምክንያት እንለያይ ይሆን?...” በስጋት ተዋጠች፡፡
ይህንን ፍርሃቷን በልቧ አምቃ በጭንቀት እንደተዋጠች፤
ሻምበል ብሩክ ቀጥፎ የሰጣትን ጽጌረዳ እንባ በጋረዳቸው ዐይኖቿ ትኩር ብላ መመልከቷን ቀጠለች::
ያቺ የምታምር ጽጌረዳ፣ ያንን የመሰለ ማራኪ ውበት የተላበሰች ለምለም እንቡጥ አባባ፣ ቀስ በቀስ እየጠወለገች፣
እየጠወለገች፣እየደረቀች ሄደችና፣ በእጇ ላይ እንዳለች እርር ብላ ተንኮሻኩሻ ደቀቀች::
በዚህ ጊዜ ትህትና በድንጋጤ ተወራጭታ ከገባችበት አስደንጋጭ የህልም ዓለም ስትወጣ፤ ሰውነቷ ሁሉ በላብ ተዘፍቆ
መንቀጥቀጥ ጀመረች::
ቀስ ብላ ያየችውን ህልም ስትመረምር ፍርሃት ነገሰባትና፤ ሆድ ብሷት “በቃ ልክ ነው:: ህልሜ ትክክል ነው:: ብሩኬን አጣሁት ማለት ነው፡፡ ወይኔ ወይኔ” እያለች ስቅስቅ ብላ ዐይኖቿ
እስከሚያብጡ ድረስ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ ልጃገረድ ያለመህኗን ሲያውቅ፤ ውሸታም ባለጌ አድርጐ እንደሚገምታት፤ በቃሽኝ እንደሚላት፤ ጠርጥራ ልቧ በሀዘን ተሰበረ::
በዚህ መጥፎ ስሜት ውስጥ ገብታ በሃሣብ ስትዋዥቅ ከቆየች በኋላ፤ ሻምበል ብሩክን የራሷ አድርጋ ለማስቀረት የሚያስችላትን ዘዴ ማውጠንጠን ጀመረች፡፡ በመጨረሻም የሆነ ሃሣብ መጣላት::
“ማን ያውቃል? ዛሬም እንደበፊቱ ሁሉ ልጃገረድ የመሆኔ ምልክቱ ሙሉ ለሙሉ ላይጠፋ ይችላልና የማያስታውቅ ከሆነ ለምን አንድ ሙከራ አላደርግም?” ስትል አሰበች። በመጨረሻም ከሻምበል
ብሩክ ጋር ከመገናኘቷ በፊት ራሷን በዶክተር ልትፈትሽ ወሰነች::
አንዴ ላይታፈስ የፈሰሰ ውሃ፤ በድጋሚ የሚገኝ መስሏት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ቀጠሮ ያዘች::
ከመቸኮሏ የተነሳ አርብ ዕለት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር በያዘችው ቀጠሮ መሠረት
ወደ ቤት እንደደረሱ ተያይዘው ወደ ቤት እንደደረሱ ሠራተኛዋን አገላብጣ ሣመቻት::
ምነው ፍቅርሽ በዛ?” አለቻት ሠራተኛዋ በልቧ፡፡ ትህትና ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ካሳለፈችው ጊዜ ሁሉ ለየት ያለው የዛሬው ነው:: ለዛሬው ግንኙነታቸው የራሷ ምክንያት ስለአላት፤ የሚሆነውን ቶሎ ለማወቅ፤ ቶሎ ወደ አልጋ ለመሄድ
ቸኮለች፡፡
ቢሆንም ግን ይህንን መቸኮሏን
ዶክተር እንዲያውቅባት አላደረገችም::
እንደተለመደው ሁሉ ዶክተር እራሱን ሊፈትሽ፤ እሷም የልጃገረድነት ሚስጥሯን ልትፈትሽ፤ ተፈላልገውና፤ ተግባብተው፤
ተያይዘው፤ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ::
ዶክተር በዚያ ረገድ በራሱ ላይ እምነት እያጣ ስለሄደ በውስጡ የነበረው ጉጉት ቀዝቅዟል፡፡ ሆኖም እንደተለመደው የማይጠገብ ውብ የልጅነት ገላዋ የሚያመነጨውን ሙቀት ለመቋደስ ያህል ብቻ መፍጨርጨሩን ቀጠለ፡፡
......
እሷ ደግሞ በሥጋት እንደተዋጠች ከአሁን አሁን
“ምን ዐይነት ሁኔታ ይፈጠር ይሆን? ልጃገረድ በመሆንና ባለመሆን መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስል ይሆን? በማለት ቁርጧን ለማወቅ ልቧ ትር፤
ትር፤ እያለች የሚያደርገውን
እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በንቃት ትከታተላለች፡፡

ቀስ በቀስ አካሉ ከአካሏ ጋር እየተሟሟቀ ፤እየተዋሀደ፣ እየተግባባ፤ መጣና የሷ ገላ እሾህ አመኬላውን አስወግዶ ሊያስተናግደው ዝግጁ መሆኑን ሳያውቅ፣ በሀይል ሲታገላት፤ባልጠበቀው መንገድ ተቀብሎ ያስተናግደው ጀመር፡፡
ትህትና ያንን ሁኔታ ስትመለከት ቅስሟ ስብር ብሎ፤ በሃሣብ ጭልጥ ብላ ሄዳ ሌላ ዓለም ውስጥ ገባች፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ ደግሞ በዚያ ባጋጠመው አዲስ ሁኔታ ተደንቆ ጉድ ነው!” አለና ለጊዜው ከገባበት ስሜታዊ ረመጥ ወጥቶ እፎይታ ለማግኘት ያህል ጉልበቱን
እንደድሮው እንደአፍላ የጉርምስና ዘመኑ አድርጐ መጫወቱን ቀጠለ፡፡
በቀላሉ ሊበርድ አልቻለም፡፡ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስዶ ተጫወተ፡፡
ይህቺ ሰው ጨው አላት መሰለኝ” እያለ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እየተደነቀ ነበር፡፡
ነበር፡፡
እሱ እንደዚያ በደስታ ሲቃ ተውጦ ሲቦርቅ ፣እሷ ግን በድን አካሏን ከሥሩ አጋድማ ዐይኖቿ በከፈቱት ቧንቧዎች እየታጠበች
ዶክተር የልቡ ሲደርስ ቀስ በቀስ ከዚያ ከሚናጥበት የስሜት ማዕበል ወጥቶ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ ያስበው ጀመር፡፡
በዚህ ጊዜ የሆነ የቅናት ስሜት ተለኮሰበትና ገላው በንዴት እየተቃጠለ ይጨስ ጀመር፡፡በወሲብ በኩል እርካታን ቢያገኝም፣ ልቡ በዚያው ልክ የምሬት
ደም ሲረጭ ተሰማው::
የልቡ ከደረሰ በኋላ ንጽህናዋን የወሰደው እሱ ባለመሆኑ፤የሆነ የቅናትና የዝቅተኝነት ስሜት አእምሮውን ሰርስሮት ገባ፡፡
መጀመሪያ ካገኛት ቀን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያደረገው ድካሙ ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ሲያስታውሰው፤ ያንን ውብ ገላዋን ለሌላ ሰው አሳልፋ መስጠቷን ሲያሰላስለው፣ በንዴት እያረረ፣ ጨጓራው ተቀቅሎ እንደገነተረ ሥጋ ሲገነትር ተሰማው:: የተናቀ የተተፋ መሰለው፡፡
የዚያን ጊዜ የልቡን በልቡ አድርጐ.....
“ትህትና እንደዚህ የማደርገው እኮ ስለምጠብቅሽ ነው” ያላት ቀን
“ይገባኛል ዶክተር” ነበር ያለችው:: ግን ዋሸችው:: እሱ ሲጠብቃት እሷ ከዳችው።

እሱ ተንከባክቦ ያቆየውን ውድ ነገር ለሌላ አስረክባቸው መጣች:: ዶክተር ሁሉም ነገር እንደሰንሰለት ተያይዞ በሃሣቡ
መጣበት:: ደካማነቱ የራሱ ሆኖ ሳለ ራሷን አሳልፋ የሰጠችውን ልጅ ሞራሏን
ሊነካው ፈለገ፡፡የሱ ሞራል ተነክቷል፤ ቅስሙ ተሰብሯልና፤ አጥንት በሌለው ምላሱ አጥንት የሚሰብር ንግግር ሊናገራት ፈልጎ ... ጠጋ አላትና
👍2
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

......ብዙም ሳይቆይ አንድ ቀጭን አጭር ሰው መንገዱን ተሻግሮ ወደ ቢጫዋ ቁርስ ቤት ሲጣደፍ ተመለከተ፡፡ኮቱን ትከሻው ላይ እንጠልጥሎታል፡፡ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት ካለው የላይቤርያ ኤምባሲ እስከ ቁርስ ቤቷ ለመድረስ ብዙ ባያስኬድም ወደፊት ደፋ
ደፋ የሚለው ሰው ረዥም መንገድ የተጓዘ ይመስላል፡፡ ሰውየው ከቁርስ ቤቷ እንደደረስ ወደውስጥ ከመግባቱ በፊት ቆም ብሎ ዙሪያውን ተገላምጦ
ተመለከተ፡፡ ወዲያው ዘው ብሎ ወደ ውስጥ ገባ፡፡

ሰውየው ወደ ውስጥ ሲገባ ናትናኤል ፈጠን ብሎ ከጥግ ወዳለ
የህዝብ ስልክ አመራና አንብቦ በጭንቅላቱ የያዘውን የቢጫዋን ቁርስ ቤት ቁጥር ደወለ፡፡

“አ.ቤት::” አለ የሴት ወይዘሮ ድምፅ፡፡
ያ ክምር ጡታቸው መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት ናትናኤል፡፡

“እንደምን ዋሉ...ደህና ኖት?” ሴትየዋ መልስ ከመስጠታቸው በፊት አጣደፋቸው “ገብረየሱስ ነኝ..እንደምን ኖት?!” አለ እንደሚያውቃቸው ተዝናንቶ፡፡ “እባኮት ስዩም ጋር ቀጠሮ ነበረን እርሶ ቤት
ያገናኙኝ…ስዩም ይበሉልኝ…እቤትዎ ውስጥ ነው ያለው…ደህና ኖት ግን
እርስዎ..በሉ ስዩምን ያገናኙኝ..” በላይ ቀላይ አጣደፋቸው፡፡

“የማን ስዩምን? አሉ ሴትየዋ ፋታ ሲያገኙ፡፡

“እንዴ!.. ረሱን እንዴ? እቤትዎ በልተን ጠጥተን? አይ የርሶ ነገር! ይብሉ ስዩም ይበሉልኝ፡፡ አይ የርሶ ነገር! ደንበኞቾንም ይረሱ ጀመር?” አጣደፋቸው፡፡

“ኧረ ንሽቴ! የምን መርሳት አመጣህብኝ::!” አሉ ሴትየዋ ድፍረት
አሰባስበው:: “ደሞ እናንተን ደንበኞቼን ልርሳ? ሄ! ሄ! ሄ! ገና ሳላረጅ ምነው
ባክህ! ደህና ነህ ግን አንተ ጠፋህሳ?”
ሴትየዋ ሲጣሩ “ስዩም የሚባል! ስልክ?” ሲሉ በስልኩ ውስጥ ተሰማው፡፡ ነፍሱ መለስ አለችለት:: ስልኩን ጆሮው ላይ እንዳይጠራቅምበት ሰግቶ ነበር፡፡

“ሀሎ… ” አለው ያው ነፍናፋ ድምፅ፡፡
“ስዩም? ” ናትናኤል ቆፍጠን ባለ ድምፅ ጠየቀ፡፡
“ነኝ.የት…?”

“ዝም ብለህ አዳምጠኝ::ቁርስ ቤቷ ውስጥ ይጠብቀኛል ብለህ አስበህ
ከሆነ ሞኝ ነህ፡፡ መልዕክቱን ብቻ እሰጥሀለሁ፡፡ ትስማማለህ?” አለ ናትናኤል ጥድፊያ በተቀላቀለው ድምፅ፡፡

“አዎ አዎ፡: ቀጥል፡፡”

“ጥሩ…. እንዳልኩህ ካልቨርት ለአንተ የማደርስለትን መልዕክትና፡ በርከት ያለ ገንዘብ ሰጥቶኛል፡፡ መልእክቱን ከመስጠቴ በፊት ግን አንተነትህን ማረጋገጥ አለብኝ፡፡”

“ነኝ..ነኝ ግድ የለም:: ስዩም ነኝ፡፡”

“ዝም ብለህ አዳምጠኝ! ለምጠይቅህ ጥያቄ ብቻ ኣጫጭር መልስ ነው የምፈልገው፡፡” አለ ናትናኤል ሰውየውን ይበልጥ ለማደናገር ቱግ ብሎ:: “ካልቨርት በየትኛው ጣቱ ላይ ነው ቀለበት የሚያደርገው?” ያዘጋጃትን ማስመሰያ ጥያቄ አስቀደሙ:: በአውራጣቱ፡ ላያ ቢለውም ግድ አልነበ
ረውም፡፡ ነገር ግን ወደ ዋናዎቹ ጥያቄዎች ከመግባቱ በፊት የሰውየውን
ጭንቅላት ማሟሸት አለበት፡፡
“ቀለበት አያደርግም ካልቨርት::” አለ ሰውየው በሚያስደንቅ ፍጥነት::

“ጥሩ፡፡ አሁንም ፈጣን መልስ እፈልጋለሁ:: ተጠንቀቅ ብትሳሳት
ወይ ብትጠራጠር፡፡ ብትዘገይ ስልኩን ዘግቼ ነው የምሄደው:: የምፈልገው
ትክክለኛውን ስዩም ነው:: የያዝኩትን በርካታ ገንዘብ ላልሆነ ሰው ማስታቀፍ፣
አልፈልግም:: አድምጥ:: የካዛንቺሷ ሴት ስም ማነው?” ናትናኤል በጭንቀት
ትንፋሹን ያዘ፡፡

“የምሥራች ይልማ!” አለ ሰውየው ሌላ ሰው እንዳይቀድመው የፈራ ይመስል በጥድፊያ፡፡
“የስልክ ቁጥሯስ?” አከታትሉ ጠየቀው፡፡
“ትዝ አይለኝም::?”
“እንግዳው ስዩም አያደለህም፡፡ደህና ዋል።”
“ቆይ! ቆይ አለ ነፍናፋው ድምፅ በጭንቀት ተወጥሮ፡፡ቆይ
ስልኩን እንዳትዘጋው። ”
ማስታወሻዬን ልይ… ቆይ አንዴ. እ…ኤ… አዎ ...ይኸው..”

ናትናኤል ስልኩን በጆርውና በትከሻው መሃል ይዞ ሰውየው የነገረውን የስልክ ቁጥር በወረቀት ላይ ይጽፍ ጀመር፡፡ ድንገት ላይ ከሜክሲኮ አደባባይ አቅጣጫ ኣንድ ነጭ ፎርድ መኪና በከፍተኛ ፍጥነት መጥታ ከቢጫዋ ቁርስ ቤት በር ላይ ቆመች:: ወዲያው ከውስጥ የነበሩ ሁለት ሰዎች በሮቻቸውን እየከፈቱ፡ ወረዱ። ሁለቱም የመኪናዋን በሮች
ለመቆለፍ አንኳን ሳይሞክሩ. እየተጣደፉ ወደ ቁርስ ቤቷ አመሩ። ጥቋቁር ኮትና ሱሪ ለብስው የኮታቸውን ቁልፎች ቆልፈዋቸዋል። ናትናኤል ፈሊጡ ገባው:: ቶሎ ዘዴ መቀየስ እንዳለበት ተረዳ፡፡

“ጥሩ፡፡” አለ ድምፁን ሳይቀይር ረጋ ባለ መንፈስ፡፡ “ስዩም ያለሁት ናዝሬት ነው:: ነገ ከጠዋቱ ልክ በአራት ሰዓት ናዝሬት ከቴሌመኒኬሽን ሕንፃ ፊት ለፊት 'ግሪር ሆቴል' የሚል ቤት አለ እዛ እጠብቅሃለሁ:: ነጭ ኮትና ጥቁር መነጸር አደርጋለሁ፡፡ ፒፓ አጨሳለሁ፡፡ ኣደራ ያወራነውን በምሥጢር ያዘው ናትናኤል ስልኩን ዘግቶ እራቅ ብሎ ይጠባበቅ ጀመር፡፡

ወንዲያው ከቢጫዋ ቁርስ ቤት የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ሁለቱን
ስዎች አስከትሎ ብቅ አለ፡፡ ሦስቱ" ተከታትለው ወደ መኪናዋ ገቡ፡፡
መኪናዋ ግን አልተንቀሳቀሰችም፡፡ ከኋላ የተቀመጠው የላይቤርያው ኤምባሲ
ሾፌር እጆቹን እያወናጨፈ ሲያወራ ሁለቱ ሰዎች ፊታቸውን ወደኋላ መልሰው ሲያዳምጡት ቆዩ፡፡

ከጥቂት ደቂቃዎች ሰኋላ ስዩም ከመኪናዋ ዕርዶ ለብቻው መንገዱን ተሻግሮ ወደ መሥሪያ ቤቱ አቅጣጫ ሲያመራ ነጯ ፎርድ ተጠምዝዛ ሽቅብ በሜክስኮ አደባባይ አቅጣጫ ተፈተለከች፡፡
ፈገግ አለ ናትናኤል፡፡ “ነገ ናዝሬት እንገናኝ” አለ ከራሱ ጋር፡፡ ወዲያው ኪሱ ከቷት የነበረችውን ወረቀት አወጥቶ አነበባት፡፡ ካዛንቺስ የምሥራች ይልማ
የፈለገውን ይኸን ነበር፡፡ስሟንና የስልክ ቁጥሯን፡፡የፈለገውን ሁሉ አግኝቷል።

የላይቤርያው ሾፌር ያለጥርጥር ለበላይ አለቆቹ አስታውቋል፤ ለአብርሃም አለቆች:: ቢሆንም ለጊዜው አትኩሮታቸው ናዝሬት ከተማ ውስጥ ስለሚሆን እዛው ነው የሚሄዱት፡፡ የአውሬውም ጆሮ በአካባቢው ካለ የእውሬውም አይን ናዝሬት ላይ ነው የሚያፈጥ:: ሁሉም ናዝሬት ነው የሚንጋጉት፡፡ አሁን ነው ጊዜው:: አሁን ነው መነቃነቅ ያለባት፡፡

ሃሎ። “ የህዝብ ስልኩ ውስጥ ሳንቲም ጨምሮ ደወለ፡፡
ሃ..ሎው” ሙልቅቅ ያለ የሴት ድምፅ ጆሮው ውስጥ ዥረር አለበት፡፡

“እ... የምሥራች ይልማ ሆቴል ነው. እባኮት…”
“አዎ ነው፡፡ ማንን ላቅርብሎት?” ሙልቅቅቅ አለችበት፡፡

“እንደምንዋልሽ የኔ እመቤት፡፡ እ...ከባህር ዳር ነበር የመጣሁት፡፡
ባልንጀራዬ መስተንግዷችሁን አድንቆ እናንተጋ እንዳርፍ የስልክ ቁጥራችሁን
ሰጥቶኝ ነበር፡፡ እ... ለባለቤቲቱም ደብዳቤ ይዤ ነበር፡፡ ግን ቤታችሁን
ላገኘው አልቻልኩም፡፡ ባክሽ..
“እይውሎት…. " አቋረጠችው:: “ሞቢል ነዳጅ ማደያው አለ አይደል ካዛንቺስ?” የልጅቷ ድምፅ ሲወርድ እንደ ተልባ ነው፡፡
“ያውቁታል...? በቃ በሱጋ ቀጥታ ሲሄዱ እንደዚህ በስተቀኝ ወደ ላይ ወደግራ የሚታጠፍ መንገድ አለ.. አ..ዎ! እሱን ትተው በስተቀኝ ትንሽ እንደሄዱ በትልቁ
'የምሥራች ሆቴል' የሚል ማስታወቂያ አለ፡፡ አጥሩ ሮዝ ቀለም የተቀባ..”
እቅጣጫውን ከነምልክቱ ጥርት አድርጋ ነገረችው::

ናትናኤል ወዲያውነ ታክሲ ተሳፍሮ ወደ ካዛንቺስ በረረ፡፡ እዚያ ሲደርስ ምን እንደሚያደርግ ግን ለራሱም ግልፅ አልሆነለትም:: በሁለት ታክሲ አሳብሮ የምሥራች ሆቴልን ደጃፍ አለፍ እንዳለ የታክሲውን ሂሣብ ከፍሎ ወረደና ጋቢውን ትከሻው ላይ ቆልሎ ዘውዲቱ የገባችለትን አዲሱን ምርኩዙን እያስቀደመ እሱ እየተክተለ መንገድ ባሻገር ያለውን ሆቴል
እያጠና አለፈ፡፡ እራቅ ብሎ ከሄደ በኋላ ከአንድ የአውቶቡስ ፌርማታ ከለላ
አድርጎ ተቀምጦ
👍2
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....ከዘጠኝ ዓመታት በፊት

ዴሪክ ዊልያምስ ሙሉ መስታወት በሆነው የቢሮ በር አሻግሮ ከእንግዳ
ማረፊያ ክፍል ውስጥ የተቀመጡትን ባል እና ሚስቶችን እየተመለከታቸው
ነው፡፡

ቢሮው ትልቅ እና ውድ በሆኑ እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ የእንግዳ ማረፊያ ክፍሉም ቢሆን ኮርኒሱ ከፍ ብሎ የተሰራ ከመሆኑም በላይ በጥሩ የዲዛይን ባለሙያ እና በደንብ ባጌጡ ሶፋዎች የተሞላ ነው፡፡
ጠረጴዛዎቹ ላይም ላይፍ ስታይል መፅሄቶች ሞልተውታል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገችው ደግሞ የዴሪክ ዊልያምስ አዲሱ ሚስቱ ሎርያን ነች፡፡

“ማሬ ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል” የሚለው
ምክርዋ ዋነኛው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ “ሰዎችን መጀመሪያ ባገኘሃቸው
ጊዜ ነው ልታስደስታቸው የምትችለው ሌላ እድል የለህም” የሚለው ነው።
ዴሪክ የሎርያንን ምክር ተግባራዊ ያደርግ የነበረው ስለምወዳት ነው ብሎ
ያስባል ወይንም ደግሞ ምርጥ ጡቶችና ያበደ መቀመጫ ስላላት እና ሌሎች
ሰዎችን ትታ እሱን በመምረጥዋ ሊሆን ይችላል ብሎ አንዳንዴ ይፈላሰፋል።
ለማንኛውም ይሄ “ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል የሚለው ፍልስፍና ሲሰራ ተመልክቷል። ምክንያቱም አዲሱ ቢሮው ከተሰራ
በኋላ የእሱ ተፈላጊነት በስልሳ ፐርሰንት ጨምሯል። ገቢውም ቢሆን በሶስት
እጥፍ ለማደግ ችሏል፡፡ ምናልባትም ይሄ
ሊሆን የቻለው ሰዎች ለሚያገኙት
አገልግሎት ብዙ ገንዘብ ሲያወጡ ነገሩ እንደሚከናወንላቸው ስለሚያምኑ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንም ሰው ደግሞ እርካሽ የሆነ አገልግሎት አይፈልግም ብላ ሚስቱ የምትነግረው ነገር ትክክል ስለሆነም ሊሆን ይችላል፡፡

የዛሬዎቹ ጥንዶች ግን ለዴሪክ አገልግሎት የከፈሉት ክፍያ ትንሽ
ከመሆኑም በላይ ከዚህ በፊትም ለሰራላቸው የተለያዩ ምርመራዎች
ያልከፈሉት ብዙ ዕዳዎች አለባቸው፡፡ ለምን እንደሆነ አያውቀውም ብቻ
ለእነርሱ ከልብ የመነጨ የሃዘኔታ ስሜት ይሰማዋል። ለምንስ ዛሬ ሊያገኙት
እንደመጡ ሲያስብ ደግሞ ልቡን ፍርሃት ፍርሃት ብሎታል። እነሱ ግን እጅ
ለእጅ ተያይዘው እና ጣቶቻቸውን አቆላልፈው ጎን ለጎን ተቀምጠዋል።

ሰውዬው ተከር ክላንሲ ይባላል፡፡ ጥቅጥቅ ያለ በደንብ የተገነባ ሰውነት
አለው፡፡ ደንዳና አንገቱን ጥብቅ አድርጎ በሸሚዙ ስለቆለፈው የታነቀ ይመስላል፡፡ ካኪ ሱሪ እና ጂንስ ሱሪ ለብሷል፡፡ ወግ አጥባቂ ነገርም ስለሆነ ምናልባት ልብሱን ሲያወልቅ ሰውነቱ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ምልክት የሆነውን ዝሆን ተነቅሶት ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉ ነገሩን በጥንቃቄ እና
በስርአቱ የሚከውን ሰው መሆኑን ፊቱን በማየት ብቻ ማወቅ ይቻላል። ያም
ቢሆን ግን የደረሰበት ከፍተኛ ሀዘን እና ውስጣዊ ሀዘኑን ከፊቱ ላይ ማንበብ
ይቻላል። ዕድሜው በአርባዎቹ አጋማሽ ላይ ቢገኝም ሲታይ ግን የስልሳ
አመት ሽማግሌ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ልጅን በሞት ማጣትን የሚመስል
ከባድ ሀዘን አይገኝም፡፡ ነገር ግን ይህቺን አንድ ልጅህን ጠፍታ ሳትገኝ መቅረትዋ በወላጅ የዋህ ልብም የጠፋችው ልጅ የሆነ ቀን ላይ ተገኝታ ወደ ቤትዋ በመመለስ የወላጆችዋን ስቃይ እንዲያበቃ ታደርጋለች ብሎ መጠበቅን
የመሰለ እጅግ በጣም ስሜትን የሚጎዳ ነገር እንደሌለ ዴሪክ ዊልያምስ በደንብ
ይገባዋል፡፡

ባለቤቱ ሜሪ ግን በጥሩ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ትመስላለች። እርግጥ ነው
እሷም ብትሆን ይደክማታል፤ ያም ሆኖ ግን የልጅዋን ዕጣ ፈንታ ከባሏ በታቃራኒ መልኩ ተቀብላ ነገረ አለሙን ሁሉ ረስታ የተቀመጠች ሴት ሆናለች፡፡ ለዚህም ሊሆን ይችላል በውስጧ የሚገኘውን ስቃይዋን ፊቷ ላይ ማንበብ የማይቻለው፡፡ ይሄ ጥሩ ነው፤ ቢያንስ ከሁለቱ አንዱ እውነታውን ተቀብለውታል ብሎ ዊልያምስ አሰበ፡፡
ለሶስት ሳምንት ያህል ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ ዊሊያምስ የክላንሲን ልጅ
ቻርሎቴን ለመፈለግ ሲኳትን ነበር፡፡
ከመጥፋትዋ በፊት ያሉትን የቻርሎቴ
ውሎዎችን አና ያገኘቻቸውን ሰዎች በማግኘትም ዱካዋን ለመፈለግ ጥረት
ሲያደርግ ቆየ፡፡ ቆንጅየዋ ቻርሎቴ ክላንሲ ረጅም ናት፤ በተለይ ደግሞ ከሃገሬው የሜክሲኮ ሴቶች አንጻር በቀላሉ በምትኖርበት አካባቢ የምትለይ
ቢሆንም ከጠፋችበት ምሽት በኋላ ማንም ሰው አይቷት እንደማያውቅ ነበር
የነገሩት፡፡

በመጀመሪያ ጊዜ ባል እና ሚስቱ የቻርሎቴ ወላጆች ስለ ቻርሎቴ የፍለጋ
ሁኔታ በደንብ አልነገሩትም ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አባቷ ተከር አላንሲ የውጭ ሀገር ፖሊሶች በተለይ ደግሞ የሜክሲኮ ፖሊሶች በሙሉ የማይረቡ ናቸው ብሎ ስለሚያምን ነበር፡፡ ስለዚህም በፍለጋው ላይ ምናልባትም ኤፍ.ቢ.አይ እና በሜክሲኮ የአሜሪካ ቆንስላ በጉዳዩ ላይ ቢገቡበት ልጁ የምትገኝ መስሎት ነበር፡፡ ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ ከሜክሲኮ ፖሊሶች በባሰ መልኩ የልጁን ጉዳይ ችላ ስላሉት ንዴቱን በዚህ
መልኩ ነበር የገለጸለት፡፡

“ስለ ቻርሊ እኮ ምንም ደንታ የላቸውም” ብሎ በመጮህ ነበር ተከር ክላንሲ በሁሉም ነገር ተስፋ ቆርጦ እሱን ለመቅጠር በመጣ ጊዜ የተናገረው
እሷ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ሴት አይደለችም እንዴ? ታዲያ ለምንድነው
በየጥሻው ውስጥ የማይፈልጓት?”

ዊልያምስ የተከር ክላንሲ ንዴት ይገባዋል ግን ደግሞ በኤፍ.ቢ.አይ እና በቆንጽላው ጽ/ቤት አልተገረመም፡፡ “አሳዛኙ ነገር ግን ምን መሰላችሁ ቻርሎቴን በደንብ ሊፈልጓት የሚችሉት እሷ የሀብታም ልጅ ወይንም የባለስልጣን ልጅ ብትሆን ነበር፡፡ ስለሆነም የኤፍ ቢ አይ ሰዎች እሷን ለመፈለግ ጊዜያቸውን እና ሀብታቸውን ማውጣት አይፈልጉም፡፡ እሷ
ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እናንተ ስትደውልላችሁ እድሜዋ ከ18 አመት በላይ ነበር፡፡ ብዙ ልጆች ደግሞ በዚህ እድሜያቸው ላይ ለወላጆቻቸው ሳይናገሩ
ከሆነ ሰው ጋር ሊጠፉ ይችላሉ፡፡”

ቻርሊ በፍፁም እንደዚህ ያለ ነገር አታደርግም” አለ ተከር ክላንሲ፡፡በዚያ ላይ ደግሞ ለአመታት ያህል በእኛ ላይ ጨክና ሳታናግረን አትተወንም፡፡” ሲል ሚስቱም ቀጠል አድርጋ “ሚስተር ዊልያምስ የሆነ ነገር ልጃችን ላይ እንደደረሰባት ይታወቀናል” ብላ እምባዋን ታግላ አስቀረችው እና ወይዘሮ ባደን እንደነገረችንኸውን ሜክሲኮ ውስጥ በየአመቱ ቱሪስቶች እና ሌሎች ሰዎች እንደሚታገቱ ነው፡፡”

“ምን አልሽኝ?” ብሎ ዊልያምስ ጠየቀ፡፡

“ቫለንቲና ባደን ናት፡፡ የዊሊ ባደን ሚስት ናት፡፡ የጠፉ ሰዎችን የሚያፈላልጉ የበጎ አድራጎት ድርጅት የከፈተች ናት።ከማንም በላይ ቻርሎቴን ለመፈለግ እገዛ አድርጋልናለች አለው ተከር ክላንሲ፡፡”

ይህንን ሲሰማ በድንገት አንድ ነገር ትዝ አለው ተከር፡፡ የሆነ ማታ ላይ ሁለት ታላላቅ ክለቦች እየተጫወቱ በነበሩበት የእራት ሰዓት ላይ ልጆቻቸውን እንዲያፈላልጉላቸው ሲማጸኑ እንደነበር አስታወሰ፡፡ ያኔ በዚህ የእረፍት ሰዓት ላይ ለሚተላለፉ ማንኛውም ነገሮች በጣም ውድ የሆነ ዋጋ ለቲቪ ጣቢያዎች ተከፍሎ ነው፡፡ ስለዚህም ይህንን የማስታውቂያ ክፍያ የከፈለችው
የዊሊ ባደን ሚስት ቫለንቲና ባደን መሆንዋን ተረዳ፡፡

“በፍፁም ወደዚያ እንድትሄድ ልፈቅድላት አይገባኝም ነበር፡፡” አለ ተከር ክላንሲ በቁጭት፡፡

“ምን መሰለህ ሚስ ባደን በእገታ የተወሰዱ ሰዎችን በማፈላለግና
ለአጋቾቹ የማስለቀቂያ ክፍያ እየከፈለች ታጋቾችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር
እንደምታገኛኝ ነው የምናውቀው፡፡ ይሄው እንግዲህ ስለልጃችን ግን አንድም
ሰው እስካሁን ድረስ የደወለልን የለም፡፡ ይሄ ነገር ጥሩ ይሁን መጥፎ ሊገባን
አልቻለም” አለችው ሜሪ ክላንሲ፡፡

መጥፎ ነው እንጂ ብሎ አሰበ ዊልያምስ ደግሞም ይህቺ ቫለንቲና
ባደን ለቻርሎቴ
👍2🔥1
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል


እናቴም የአባቴን አኳኋንና ለዘብተኛ አነጋገር በመከተል እንደ ወትሮዋ አልተቆጣችኝም

ከየውብነሽ ጋር መገናኘቴን ቀጠልኩ። አባቴ ስለ እኔ ያለውን አስተያየት እምብዛም እንዳልለወጠው አጣራሁ፡፡ እናቴም የእኔን ደጅ ደጅ ማየት ችላ እንዳለችውና እንኳን ከዚያች ከመናጢ ገረድ ጋር አብሮ ያልታየና ስማችንን ያላስጠፋው እንጂ የኋላ ኋላ መመለሱና ልብ መግዛቱ አይቀርም፡፡ እኔም ለጊዜው ንድድ ያለኝ ከገረድ ጋር መዋልና መልከስከሱ ነበር፣ ሌላ ሌላውስ ግድ የለም” ማለቷን የዋህ ተመስዩ ከየውብነሽ ሰማሁ፡፡

ያም ሆነ ይህ አንድ ቀን የእኔንና የየወዲያነሽን ጉዳይ ይፋ ለማውጣት ቆርጬ በምነሣበት ጊዜ ንትርክና ከባድ የቤተሰብ ውዝግብ እንደሚያጋጥመኝ በእርግጠኝነት ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ካለፈ አገደም ከሥራ መልስ በምሳ ሰዓት ወደ ወላጆቼ ቤት እየሄድኩ የሻከረ ሆዳቸውንና
አስተያየታቸውን ደረጃ በደረጃ ለመለወጥ ጥሩ ጥረት አደረግሁ፡፡ ተደጋጋሚ
ሙከራዩ ትንሽ የለውጥ ፍሬ አሳየ፡፡ በተለይም ከእናቴ ጋር የማደርገው ወሬና
ጨዋታ ሁሉ አስደሳች ቅርርብ ፈጠረ፡፡ ትንሽም ፊቷ በኀዘን የሚጠወልግና
የጠራራ ቅጠል የምትመስለው ደህና እደሪ ብዬ ለመሄድ በምነሣበት ጊዜ
ነበር።

አንድ ቀን ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከየውብነሽ ጋር መኝታ ቤቷ ውስጥ
ተቀምጠን ሞቅ ደመቅ ያለ መሬ ስናወራ «አንተ ጌታነህ» አለችኝ፡፡ ዐይኖቿ
የትዝታዋን ክብደት ለማስረዳት እየቦዙ ያነዩ ዱሮ ከዚያች ከገረዳችን ጋር
እንዲያ ስትሆን አባባ ያየኛል፣ ይሰማብኛል ብለሀ አልፈራህም?» ብላ
ታላቅነቴን በማክበር የኃፍረት ሣቅ ሣቀች። ምናልባት አንዳንድ ያልሰማሁትን
ነገር ታሰማኝ ይሆናል በማለት ልበ ግልጽ
ተመስዩ «እንዳልታይና እንዳይሰማብኝ ያልሠራሁትና ያልፈጸምኩት ዘድ አልነበረም። አንቺንም በጣም እፈራሽና እጠራጠርሽ ነበር» አልኩና አልጋዋ ላይ ጣል ያደረገችውን የሰነበተ ጋዜጣ ማገላበጥ ጀመርኩ። አንገቷን ወደ ቀኝ ሰበር አድርጋ የማገላብጠውን
ጋዜጣ እየተመለከተች ግን እኮ እያደር እንዳፈቀርካትና ከወዲያ ወዲህ
እየተመላለሰች በምትሠራበት ጊዜ ዐይኖችህ አብረዋት እንደሚዋትቱ ኣሳምሬ ዐውቅ ነበር፡፡ ከእንጀራ አቅም እንኳ ሌላ ሰው ሲያቀርብልህ ደስ አይልህም ነበር። እሷም የዋዛ ሾላካ አልነበረችም ! ኋላማ ልናባርራት አቅራቢያ
አረማመዷና አነጋገሯ፣ ጸጉር አሠራሯና አለባበሷ ሁሉ በጣም ተሻሽሉ ነበር፡፡
እኔ ከሁሉም ከሁሉም የማይረሳኝ ጠባይዋና ሲያዝዋት እሺ ባይነቷ ነው፡፡ ምን ይሆናል፣ ያ መሳይ መልክ ያለ ቦታው ቀረ፡፡ እሷ የተማረች ሆና ውጪ
ውጪውን ብናገኛት ኖሮ... እኔ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ስለ እሷ አንዳችም ወሬ
ሰምቼ አላውቅም» ብላ አጠናቀቀች። የወሬ ከረጢቷን መፍታቷ ስለ ታወቀኝ
ለጊዜው ውስጣዊ ብስጭቴን ኣፍኜ ባናነሣው ይሻላል ያለፈው አልፏል እንጂ
ብሳሳትም ባልሳሳትም ከዚህ ቤት ስታባርሯት እርጉዝ ነበረች። ቀስ ብላችሁ
ሹክ ብትሉኝ ኖሮ እንደምንም አንዱ ጋ አስጠጋትና ትወልድ ነበር፡፡

ይኸንዬ እኔን አባብዬ” ሲል አንቺን ደግሞ ”እቴቴ' እቴ ሸንኮሬ 'እት -አይገኝ” ይልሽ ነበር» አልኳት፡፡ የአሁኑን የ'ወዲያነሽን ሕይወትና ኑሮ የማታውቀዋ እኅቴ ከሁሉም ከሁሉም በጣም የሚያሳዝነኝ» ብላ ቀጠለች፣
«ያነዪ አንተ ወደ ሥራ ወጣ ከማለትu እማዬ በአባባ ከዘራ ታፋ ታፋዋን'
ጀርባ ጀርባዋን ስትደበድባት ኩርምት ብላ ስትደበደብ የወረደባት የዱላ መዓት ነው፡፡ በመጨረሻ የተሰነዘረው ዱላ መኻል እናቷ ላይ በማረፉ ደሟ በጸጉሯ ውስጥ እየተንጀረጀረ ትከሻዋ ላይ ተንጠፈጠፈ፡፡ ነፍስ ይዟትም ይሁን ያሰበችውን እንጃ ከዘራውን ይዛ እለቅም በማለቷ እኔም እናቴን የተዳፈረችብኝና ግብግብ የምትገጥማት ስለመሰለኝ ሁለት ጊዜ በጥፊ አላስኳት።

«እሷ ግን ቀና ብላ አይታ፣ አንቺም? አንቺም? ጨክነሽ ትመቺኝ የውብነሽ? ኣይ ድኃ መሆን!” ያለችኝ ዛሬም አንጀት አንጀቴን ይበላኛል፡፡»
«እሷ ግን በጣም የተንገበገበችውና ያለቀሰችው ከቤት በመባረሯና
በመደብደቧ ሳይሆን እንተን ሳትሰናበትሀና ሳታይህ በመሔዷ ነበር። ከሥራ ስትመለስ መንገድ ላይ ጠብቃ እንዳታግባባሀና በሴት እንባዋ እንዳታታልልህ ከዚህ አካባቢ ያባረርናት በዘበኛ ነበር» ብላ ያን ዚያ ቀደም አሳርሮ
ያከሰለኝን መራራ ነገር እንደገና ጋተችኝ፡፡ የየወዲያነሽ መከራና እንግልት
ሁሉ ከተቀበረበት የትዝብት መቃብር ወጥቶ ነጭ ዓፅሙ ፊት ለፊቴ ተገተረ፡፡ ሌላ ተጨማሪ ነገር በመስማት አንጎሌን ማጥመልመል ስላልፈለግሁ
«ነገ አራት ሰዓት ላይ ዕጓለ ማውታ ስለምሔድ አብረን እንሂድ። ከዚያ በኋላ
ደግሞ ሌላ የማማክርሽ ጉዳይ ስላለ ቀደም ብለሽ ቀበና ድልድይ አጠገብ
ጠብቂኝ ብያት ወጣሁ፡፡

በማግሥቱ እሑድ እኅቴና ባለቤቴ ዕጓለ ማውታ እንዳይገናኙብኝ፡ የወዲያነሽን «እንግዳ ይዤ እመጣለሁና ተዘጋጅተሽ እንድትጠብቂኝ፡ ከዚያ በኋላ እንሔዳለን» ብያት ከቤት ወጣሁ፡፡ መኪና መግዛቴን መላ ቤተሰቦቼ ስላልሰሙ የውብነሽ የምትጠብቀኝ በእግር እንጂ በመኪና ይመጣል ብላ አልነበረም፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ዘግየት ብዬ ቀጠሮእችን ቦታ ስደርስ የውብነሽ ተረከዘ ሹል ጫማ አድርጋ ከጉልበቷ ትንሽ ከፍ ያለ ቀለመ ብዙ የፈረንጅ ቅድ ቀሚስና ነጭ ሸሚዝ ለብሳ ቡናማ ኮረጆዋን አንግታ ድልድዩ አካባቢ ስትጠብቀኝ አገኘኋት። መኪና አጠገቧ ደርሳ በመቆሟ ባለ መኪናውም እኔ መሆኔን ባለማወቋ ፊቷን በቁጣ ከሰከሰች፡፡ እንዳንድ የጎዳና ሴቶች
ለመግደርደር ሲሉ የሚያሳዩት አኳኋን ትዝ አለኝና የየውብነሽ አድራጎት አሣቀኝ፡፡ ወዲያው ወጣ ብዬ ወደ እርሷ ተራመድኩ። ከመኪና ወጥቶ ወደ
እርሷ የሚራመደው ሰው ታላቅ ወንድሟ መሆኑን ስታውቅ የአድናቆት ሣቅ
ሣቀች፡፡

«መኪና ገዛሁ እንዳትለኝ አለችኝ፡፡ «አዎ ገዛሁ እኔም ወጉ ይድረሰኝ ብዬ ገና ሁለተኛ ወሯን መያዟ ነው» አልኩና እየተሣሣቅን ተጨባበጥን፡፡
«የውቤ፣ ይቺንም ታድያ ቤተሰብ እንዳይሰማ፣ እንድ ቀን ሁሉንም ነገር
አጠራቅሜ አቀርበዋለሁ፡፡» «ሌላ ደግሞ ምን የሚነገር አለህ?» ብላ አየችኝ፡፡
«እኔ ገና ብዙ የሚነገር ነገር አለኝ» ብያት መኪና ውስጥ ገብተን መንገድ
ቀጠልን፡፡ በአሥራ አምስት ደቂቃ ውስጥ አግድመት ቁልቁለቱን ጨርሰን
ሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ደረስን፡፡ ለምለሙ መስክ ላይ ትላልቅና ትናንሽ
ልጆች እንደ ጥሬ ፈስሰው ልዩ ልዩ ጨዋታዎች ይጫወታሉ። ከትንንሾቹ
ልጆች መኻል አንድ የግራ ዐይኑ የጠፋችና በዐይን አር የተጨማለቀች
ሰማያዊ ቁምጣና ትከሻው ላይ የተጣፈች እሷኑ መሰል ኮት የለበሰ ልጅ
በሩጫ መጥቶ ጨበጠኝ፡፡ የጋሻዬነህ ጓደኛ ነው:: ከኪሴ ከረሜላ ኣውጥቼ ሰጠሁት። የውብነሽ በድንጋጤ አፏን ከፍታ «ምነው ምን ሆነ? ዐይኑን ምን ነካው? ደኅና አልነበረም እንዴ !?» አለችኝ፡፡
«ይህ እኮ ያ ከዚህ ቀደም ያየሽው የጓደኛዬ ልጅ አይደለም፣ ይኸ ጓደኛዉ ነው:: አሁን ሮጦ ይጠራልናል» አልኩና የደነገጠውን ስሜቷን በደስታ
አደስኩት:: ከረሜላውን ልጦ ጎረሰና ተለይቶን ሔደ። እምብዛም ሳይቆይ
ጋሻነህን ይዞት መጣ፡፡ አንዲት በጣም የጠወለገች ነጭ አበባ ይዞ ነበረ።
እጆቼን ከብብቱ ሥር አስገብቼ በማንሣት ጉንጮቹን ስስም ሁሉም ነገር
ጥሉኝ ጠፋ፡፡ የውብነሽ ቀበል ብላ አገላብጣ ሳመችው:: ቀድሞውንም የሙት ልጅ ነው ብዬ ነግሬያት ስለ ነበር በርኅራኄ ተመለከተችው:: አላስችል ስላላት ዕንባ ተናነቃት። መሐረቧን አውጥቃ ዐይኖቿን አበሰች። «ለመሆኑ ያባቱ ዘመዶች እየመጡ ይጠይቁታል እንዴ?» አለችኝ፡፡ ልጅ ያለው መሆኑን የሰማ አንድም
👍2
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


....“አንተን ለማግኘት ስል ያልገባሁበት ዋሻ፣ያልፈነቀልኩት ድንጋይ አልነበረም፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል?እንደ ሌሎቹ በቀላሉ የምትገኝ ሰው አልሆንክም፡፡ የተፈፀመብኝ ጥቃት ከባድና ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ ልቤ እያወቀው፣ ልቤ እየጠረጠረ ከማይረቡ ምናምንቴዎች ጋር ውለታ ውስጥ ገባሁ። እንዳንተ ስማቸው ያልገነነ፣ ቱስ ቱስ ማለት የጀመሩ ሾላኮች በመሆናቸው ብዙ ገንዘብ ካስወጡኝ በኋላ አንዳች ቁም ነገር ሳይፈፅሙ ሸሽተውኛል ተደብቀውኛል። በዚህ ምክንያት ተበሳጭቼ ቀን ከለሊት አፈላልጌ መልዕክተኛ ልኬብህ በብዙ ድካም ሳገኝህ የተሰማኝ ደስታ
ወደር አልነበረውም፡፡ እንደዚህ በግንባር ልታነጋግረኝ መወሰንህን ስሰማ ደግሞ ደስታዬ እጅግ ከፍተኛ ሆኖ ነበር፡፡ጎንቻ የልቤን የሚፈፅምልኝ ካንተ ወዲያ ሊኖር እንደማይችል ቀድሞውኑ የታወቀ ነው” በማለት አንጀቱን ከበላው በኋላ ዝርዝሩን ይተርክለት ጀመር፡፡

“የሹመት ጓደኛዬ ነው። ባላባት ጃኖ ይባላል። በባህላችን በወልገራ የጋብቻ ደንብ እህቴን ስድርለት እሱ ደግሞ በለውጡ እህቱን ድሮልኝ ነበር፡፡ እኔ የሱን እህት በወግ በማዕረግ አክብሬ ነበር የያዝኳት። እሱ ግን እህቴን
እንደ ባሪያ እየረገጠ በደል ሲያበዛባት፣ ሲያሰቃያት ተማረረች። በመጨረሻም የሱ ሚስት የኔ እህት በደሉ አንገሽገሻትና በድንገት ጥላው ጠፋች። ከዚያ በኋላ ሰላም ይነሳኝ፣ ይበጠብጠኝ ጀመር፡፡ እኔ ጥለሽው ጥፊ፣ እኔ ትዳርሽን አፍርሺ ብዬ እንደመከርኳት ሁሉ ሚስቴን መልስልኝ ያለበለዚያ ዝምድናችን ይበላሻል እያለ ያስፈራራኝ ጀመር።መልዕክተኛ በተደጋጋሚ ላከብኝ፡፡ በግንባር ተገናኝተን ተነጋገርን፡፡ ጭቅጭቁ ሲብስብኝ መቆሚያ መቀመጫ ሲያሳጣኝ እህቴን ካለችበት ቦታ አስጠርቼ ላግባባት ሞከርኩ፡፡ ወደ ትዳሯ እንድትመለስ እግሯ ላይ ወድቄ ለመንኳት ወደዚያ የስቃይ ኑሮ ተመለሺ የምትለኝ ከሆነ ህይወቴን አጠፋለሁ ካንተ
ምንም የምፈልገው ነገር የለም በነፃነቴ ውስጥ ግን አትግባ ብላ እያለቀሰች በምሬት መለሰችልኝ፡፡ በጣም አስፈራራችኝ፡፡ ከፍላጎቷ ውጭ እንድትመለስ ባስገድዳት ህይወቷን ታጠፋለች የሚል ፍርሃት አደረብኝ፡፡ያደረኩትን ጥረትና የሰጠችኝን መልስ በዝርዝር አጫወትኩት፡፡ በወዳጅነታችን ውስጥ በፍፁም ቅያሜ እንዳይኖር ለመንኩት። እህቴ ብትሆንም በሱ ሚስት ህይወት ላይ ማዘዝ እንደማልችል አስረዳሁት፡፡ ምን ዋጋ አለው? ድንጋይ ራስ ነው! በፍፁም ማመዛዘን የማይችል ድንጋይ ራስ!! ችግሬን ሊረዳ አልቻለም፡፡ ያንን ሁሉ ልፋቴንና ጥረቴን ዋጋ አሳጥቶት ቂም ቋጠረብኝ፡፡ የኔን ትዳር ለመበጥበጥ፣የኔን ትዳር ለማፍረስ እንቅልፍ አጣ። ለእህቱ በተደጋጋሚ መልዕክተኛ ላከባት፡፡ የሱ እህት ብቸኛ አድርጋኝ ጥላኝ ስትጠፋ፣ ትዳሬን አፍርሳ ስትሄድ አንቺ ግን የሱን ጎጆ ታሞቂያለሽ፡፡ የወንድምሽ በደል የማይሰማሽ ለወንድምሽ የማትቆረቆሪ አህያ
ነሽ።እህቱ ጥላኝ እንደጠፋች ጥለሽው ካልጠፋሽ ዳግመኛ እህት አለችኝ ብዬ አላወራም እያለ ነዘነዛትና ፍቅራችን እንዲደፈርስ ትዳራችን እንዲ ፈራርስ አደረገ፡፡ ከዚያም የምወዳት ሚስቴ ሳልበድላት ምንም ሳላስቀይማት በድንገት.. በድንገት ጥላኝ ጠፋች”

የስድስት ሚስቶች ባል የሆነው ባላባት ቱሬ የሚያወራው ተረት አፉን እንኳን ወለም አላደረገውም ነበር፡፡ የደረሰበት በደል ከፍተኛ መሆኑን ጎንቻ እንዲረዳለትና ቁጭት እንዲያድርበት ለማድረግ ሰሞኑን ሲያጠና የከረመውን ልብ ወለድ እንደ እውነተኛ ታሪክ ሲያወራለት እዚያ የነበሩት በሙሉ አፋቸውን ከፍተው እንደ አዲስ ያዳምጡት ነበር፡፡ በተገላቢጦሽ በጃኖ ላይ የደረሰውን በደል በራሱ ላይ እንደደረስ አድርጎ ጃኖን በዳይ ራሱን ተበዳይ አድርጎ ፊቱን በእንባ ቀረሽ ንዴት ቁጥር ፈታ እያ
ደረገ ማስረዳቱን ቀጠለ።

“ስው ቢበድለኝም ጓደኛዬ ቢከዳኝም እግዚአብሔር አልከዳኝምና በደሌን አይቶ ካለኝ፡፡ ሀዘኔን አይቶ ፈጣሪ አስደሰተኝ፡ እምባዬን አበሰልኝ፡፡ አለላ የመሰለች ልጁን በቦሩ ጃዊ ባላባትነት ውስጥ ጭቃሹም የሆነው አቶ ገመቹ ዳረልኝ፡፡ በዚህ ጊዜ የበለጠ ቅናት አቃጠለው:: እህቱ ጥላኝ እንድትጠፋ፣ ረግጣኝ እንድትሄድ ካደረገ በኋላ ለእህቱ ተቆርቋሪ መስሎ እህቴ የደከመችበትን ንብረት፣ እህቴ ጎንበስ ቀና ብላ ያቆመችውን ጎጆ
ማንም መንገደኛ ገብቶ አይንደላቀቅበትም ሲል ዛተብኝ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ የሱ እህት ይዛልኝ የመጣችው ሰባራ ሳንቲም አልነበረም፡፡ በሞላ በተትረፈረፈ ቤት ገብታ መሞላቀቁ አጥግቧት ጠፋች እንጂ እሷ ያመጣችው አንድም ነገር አልነበረም፡፡ ከኔ ምን ጎድሎ? ምን ጠፍቶ? እሱ ግን ለእህቱ የተቆረቆረ በማስመሰል ለካንስ ሊያጠቃኝ አስቦ ኖሯል፡፡ የሱ እህት ለዚችኛዋ ሚስቴ ገረዷ የእግሯ እጣቢ እንኳ አትሆንም ነበር፡፡ ያጠቃኛል የዚያን አይነት አስከፊ በደል ያደርስብኛል ብዬ በፍፁም ባልጠበኩት ሰዓት ባላባት ጃኖ አጠቃኝ፡፡ ተዘጋጅቶ ዘመድ አዝማዱን አሰባስቦ
ጦሩን ጭኖ በሌሊት ከበበኝ፡ ሚስቴን…. ሚስቴን... በሃይል... ሳልዘጋጅበት.ሳላስበው ...ነጥቆኝ ሄደ” እንባ እየተናነቀው አስረዳ፡፡

እውነተኛው ታሪክ ግን ባላባት ቱሬ እንደሚያወራው ሳይሆን የምስኪኑ
ገበሬ የጃኖን እዚህ ቀረሽ የማትባል እጮኛውን ባላባት ቱሬ በሀብትና በሥልጣኑ ተመክቶ፣ ወላጆቿን በከብትና በገንዘብ ገበራ ዐይናቸውን አሳውሮ የአሥራ ስምንት ዓመቷን ልጃገረድ ሌቱናን ጠልፎ ከወሰዳት በኋላ በባላባትነት ግዛቱ ውስጥ ድል ባለ ሠርግ ያገባት መሆኑ ነው ሀቁ። ገንዘብና ሀብት ባይኖረውም ዛሬ በቱሬ አንደበት የባላባትነት ማዕረግ የተሰጠው ጃኖ የጉልበትና የወኔ ደሃ አልነበረም። እንደ ነፍሱ የሚወዳት እጮኛውን ጉብሏን ሌቱናን ቱሬ በገንዘብ ኃይል አፍኗት ሲሄድ፣ የድንግልነት ክብሯን ሲወስድ እየታየው ገላው እስከሚቃጠል ድረስ በንዴት
ቢጋይም፣ እልህ ቢተናነቀውም አንድ ቀን የሱ አንጡራ ሀብት መሆኗን እንደሚያረጋግጥና እጮኛውን በነጠቅው በቱሬ ላይ አደጋ ጥሎ እንደሚወስዳት ጥርጥር አልነበረውም፡፡ ቱሬ የጓጓው ያንን የቀዘቀዘ ገላውን የም
ታሞቅለትን፣ ብዙ ንብረት ያወጣባትን ቆንጆዋን ሌቱናን ጎንቻ እንዲያስመልስለት ነው። ጎንቻ ተራ ውንብድና አይፈፅምም የሚለውን ዜና በመስማቱ የሌላ ታሪክ እየፈጠረ ገበሬውን ባላባት አድርጎ በመሾም ለመተረክ የተገደደውም ከዚህ እውነታ በመነሳት ነው፡፡

በእርግጥም ጎንቻ ትንሽ ስራ፣ ትልቅ ስራ በሚል የወንጀል አይነትን የሚያማርጥ ቢሆንም ጥሩ ገንዘብ እስካስታቀፉት ድረስ የህፃን ጉሮሮ ከመቀንጠስ ወደ ኋላ የማይል ጨካኝ መሆኑን ቢያውቀው ኖሮ ይሄንን ያክል
መጨነቅ ባላስፈለገው ነበር፡፡

“የፈለከውን ያክል ብር ብትስጠኝ አንድ ተራ ገበሬ ለመግደል አገር
አቋርጬ አልሄድም” ይለኛል ብሎ ስለፈራ እንባውን እየጠራረገ እጅግ ከፍተኛ የሆነ በደል የተፈፀመበት ሰው መስሎ እየተንቀጠቀጠ ኑዛዜውን ቀጠለ፡፡

“ምንም እንኳ እድሜዬ ቢገፋ፣ አቅሜ ቢዳከም አባቴ የወለደኝ ወንድ ጀግና ነበርኩ፡፡ ጃኖ ግን ወንድነቴን ጀግንነቴን ሰልቦታል። ልቤን በሀዘን አኮስምኖታል። ዝናዬን አጉድፎታል። ተኝቶ ሚስቱን ያስነጠቀ ባላባት አሰኝቶ በባላባትነት ግዛቴ ውስጥ አዋርዶኛል። ህዝቡ እንዲንቀኝ፣ እንዳይታዘዘኝ አድርጓል፡፡ ጉልበት በነበረኝ ጊዜ አባርሬ ይዣለሁ። ገድዬ ፎክሬአለሁ።ጃኖ ግን አቅሜ ቢደክም፣ዕድሜ ቢጫጫነኝ ንቆኝ የለበስኩትን ሱሪ አስወልቆ ቀሚስ አልብሶኛል። ጉልበት የእግዚአብሔር መሆኑን
2🥰1
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

....ስድስት ወር ተብሎ የሄደው አስቻለው እንኳን መመለስ ድምፁ እንኳ ሳይሰማ ድፍን ሰባቶ ወረሰ አልፈዋል። ይህ ሁኔታ በዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ ላይ ስጋትና
ጭንቀት ፈጥሮ ያተረማምሳቸው ይዟል ከሁሉም በላይ ደግሞ ሔዋንን።
አስቻለው ወደ አስመራ ሲሄድ ለዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ የገባው ቃል ነበር ቶሎ ቶሎ ደብዳቤ ሊፅፍ ሁኔታዎች በፈቀዱለት መጠን ስልክም ሊደውል ለነገሩ አንዲት ደብዳቤ ፅፏል።ያቺም ብትሆን ገና አስመራ በገባ ሦስተኛ ቀን ላይ ድንገት ወደ አዲስ አበባ የሚመለስ ሰው አግኝቶ ኖሮ ደህና መድረሱን የገለፀበት እንጂ
ዝርዝር የናፍቆት ሀሳብና የተሟላ አድራሻውን የያዘች አልነበረችም። በዚያች ደብዳቤ ላይ የጠለፀው ነገር ቢኖር ወደፊት ቋሚ አድራሻውን ሲያውቅ ሌላ ደብዳቤ እንደሚፅፍና ምናልባት ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ በአውሮፕላን ላይ በነበረበት ወቅት ከሔዋን በመለየቱ ምክንያት ሆዱ ባብቶ በናፍቆት ስሜት ውስጥ ሆኖ የቋጠራቸው እንደሆኑ የሚገመቱ ጥቂት የግጥም ስንኞችን ብቻ ነበር።ያቺ ደብዳቤ ዲላ የደረሰችውም ስትጣጣል ሰንብታ ከተጻፈች ከአንድ ወር በኋላ ነበር፡፡
በቃ ሌላ የለም።
ሔዋን በልቧ ከአንድ ድምዳሜ ላይ ደርሳለች፤ እስቻለው ደህና ባይሆን ነው። ከሚል። የአስቻለውን ደህና አለመሆን ባሰበች ቁጥር ሁለት ነገሮች በሁለት ቦይ እየፈሰሱ በሀሳብ ይወስዷታል። በአንድ በኩል የአስቻለው ደህና አለመሆን
ፍቅሯን ሊያሳጣት ነው የዕድሜ ልክ የመንፈስ ስብራት፡፡ በሌላ በኩል ስለ እሷ "ብልግና" ሸዋዬ ለቤተሰቦቿ የጻፈችባትን ደብዳቤ ታስታውሳለች። ያ ደግሞ የቤተሰቦቿን በተለይም የእናቷን ሆድ እንዳሻከረባት ትገምታለች፡፡ ይህን ሁኔታ ማስቀየር ያስችላል ብላ የምትገምተው የአስቻለውን መልካም ሰውነት ነበር፡፡
እናትና አባቷ አንድ ቀን አስቻለውን ሲያውቁትና መልካም ሰውነቱን ሲረዱት ምርጫዋ ትክክል እንደሆነ በመረዳት የሻከረ ሆዳቸው ይሽርልኛል ብላ ትጓጓ ነበር፡፡አስቻለው ደህና ካልሆነና ምናልባትም ያልተመለሰ እንደሆነ ግን ከሁለት ዛፍ የወደቀች ልትሆን ነው። ጭንቅና ፍርሀቷም ከዚሁ ስጋት ይመነጫል።
ታፈሡ፣ በልሁና መርዕድ የሔዋንን ጭንቀት በብዙ መንገድ ይጋሩታል።
የአስቻለው ደብዳቤ አለመጻፍ፣ ስልክ አለመደወልና የመምጫው ጊዜም በአንድ ወር የዘመኑን እውነታዎች በራሳቸው መንገድ እየተረጎሙ ራሳቸውንም ሆነ ሔዋንን ማፅናናት አልቦዘኑም፡፡ ወትሮም እንደሚያደርጉት ሁሉ ጫት በመቃም ሰበብ ቀደም ሲል በልሁ፤ አሁን ደግሞ ሔዋንና ትርፌ በሚኖሩበት ቤት እየተሰበሰቡ መዋልና ማምሸታቸውን ቀጥለዋል፡፡ በዚያው ሂደት በበርካታ ጉዳዮች ላይ ደጋግመው ይነጋገራሉ፡፡ የአስቻለውን ደብዳቤ አለመጻፍ ጉዳይ ያነሱና ከወቅቱ ሁኔታ ጋር ለማገናዘብ ይሞክራሉ። በዚያን ወቅት መንግስት በፖስታ ቅብብሎሽ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር ያደርግ ነበር። ተቃዋሚዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ምስጢር
ይለዋወጣሉ በሚል ስጋት በተለይ የተጠርጣሪ ሰዎችን ፖስታ እየቀደዱ መንገድ ላይ ያስቀሩ እንደነበር በሰፊው ይታወቃል። በተለይ ከኤርትራ ወደ ሌሎች
የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚላኩ ደብዳቤዎች ለተላከሳቸው ሰዎች የመድረሳቸው ዕድል
አስተማማኝ አልነበረም፡፡ ምናልባት አስቻለውም የሚጽፈው ደብዳቤ መንገድ ላይ ተቀዶ እየቀረ ይሆናል። እሱ ደግሞ የተከፋ ብሶተኛ ነውና ይህንኑ ስሜት በደብዳቤው ላይ አስፍሮ ከተገኘ የባሰ ይጠረጠርና ሁለተኛውም ሦስተኛም ደብዳቤዎቹ የዚሁ ሰለባ እየሆኑ ቀርተው ሊሆን ይችላል በማለት
ግምትና ጥርጣሪዎቹን ይገልፃሉ። ስልክ ያለመደወሉንም ጉዳይ ከዚሁ ከወቅቱ እውነታ ለይተው
አያዩትም።በወቅቱ ከአዲስ አበባም ሆነ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች አስመራን በሽቦ የሚያገናኝ ስልክ አልነበረም፣ በዓመታት ጦርነት ተበጣጥሰው
አልቀዋልና። አማራጭ የመገናኛ መንገዶች ራዲዮና ቴሌ ግራም አሊያም ገመድ አልባ ማይክሮ ዌቭ ስልክ ናቸው። ራዲዮና ቴሌ ግራም ደግሞ ለአብዛኛው ሰው እንደ ልብ አይገኙም፡፡ የማይክሮ ዌብ ስልክም ገና በጅምር የቴክኖሎጂ ደረጃ ላይ ነው
ከሚሰራበት ጊዜ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል። በሚሰራበትም ወቅት ወረፋው አስልቺ ነው፡፡ የእነታፈሡ ግምት ታዲያ አስቻለው በዚህም ቢል በዚያ አልሆንለት እያለ ተቸግሮ ነው›› በሚል ሀሳብ ይደመድማል። የአስቻለው የመመለሻ ጊዜ ማለፉንም ካነሱ ምናልባት የአይሮፕላን ጉዞ ወረፋ አልደርስ ብሎት ይሆናል ከሚል ግምት አያልፍም፡፡
ይህ ሁሉ ምክንያታዊ ትንተና ግን ለሔዋን አይገባትም ትሰማቸዋለች እንጂ አታዳምጣቸውም፡፡ ለእሷ አንድ ነገር ብቻ ግልፅ ነው፤ በቃ አስቻለው አልመጣም ድምፁም አልተሰማም ምክንያቱ ደግሞ ደህና አለመሆኑ ነው። የሚያስጨንቃት የእሱ ደህና አለመሆንና ምናልባትም ያልመጣ እንደሆነ የሚፈጠርባት የመንፈስ ቁስል ነው። የዚህ ሁሉ አጠቃላይ ውጤት ታዲያ ራሷ ተጨንቃ እነታፈሡንም ማስጨነቋ ነው።
ሁኔታዋ ሁሉ ያሳዝናቸው ይዟል።
በልሁ ታዲያ ይህንን ችግር አንድ ቀንም ቢሆን የቀረፈ መስሎት ነው በሙዚቃ ዘና ትልለት ዘንድ የመግቢያ ትኬት መግዛቱ።
በልሁ ትኬቶቹን ይዞ በቀጥታ ያመራው ቀድሞ የእሱ፣ ዛሬ ደግሞ የሔዋንና የትርፌ መኖሪያ ወደ ሆነው ቤት አቅጣጫ ነበር። ነገር ግን ከአንደኛ መንገድ ብዙም ሳይርቅ መርዕድ ከታች በኩል አስፋልቱን ይዞ ወደ ላይ ለመጣው አገኘውና «ትኬት ገዝተሃል?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው፡፡ የምን ትኬት?» አለ መርዕድ በርገግ ብሎ።
«ዛሬ እኮ የፖሊስ ኦርኬስትራ መጥቷል»
ባክህ ተው ለአንድ ቀን ምሽት እሥር ብር ከማወጣ በቋሚነት የምስማው አንድ ካሴት ብገዛ አይሻልም?» አለው።
«እስቲ በልጅ እግርህ ወደነ ሔዋን ልላክህ!»
«ለምን?»
በልሁ ቲኬቶቹን ከኪሱ አውጥቶ እያሳየው «ሔዋንና ትርፌ ዛሬ እንኳ ይዝናኑ ብዬ ትኬት ገዝቼላቸዋለሁ:: ስጣቸውና ስዓቱ ሲደርስ አዳራሹ ድረስ
እንዲመጡ ንገራቸው:: እነሱን አስገብተን እኛ ወደየጉዳያችን እንሄዳለን» አለው።መርዕድ አላቅማማም፣ ቲኬቶቹን ተቀበለውና ሲመለስ የት እንደሚገናኙ ቀጠሮ ይዘው ወደ ሔዋንና ትርፌ ቤት ገሰገሰ፡፡
የሙዚቃ ድግሱ ማስታወቂያ በድምጽ ማጉያ ይነገር በነበረበት ወቅት ብዙዎች ያለ መታደም
አዝማሚያ የሚያመለክት አስተያየት ይሰጡ የነበረ ቢሆንም
በወቅቱ እስከ ሰላሳ ሺህ ህዝብ የሚኖርባት ዲላ ከተማ ውስጥ ከእንድ ሺ በላይ የማይዘውን የህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ የሚሞላ የሙዚቃ አፍቃሪ አልጠፋም፡፡ሰዓቱ ደርሶ ሔዋንን እና ትርፌን በቀጠሩበት ቦታ አግኝተዋቸው ወደ አዳራሹ ይዘዋቸው በመግባት ቦታ ሊያሲዟቸው ቢሞክሩም እነሱ
ቲኬት ስላልያዙ ወደ አዳራሹ ለመግባት ተከለከሉ።በዚያ ምትክ ትዕይንቱ፡ እንዳይርቃቸው ወደፊት ሄደው መቀመጥ እንዳለባቸው
መከሯቸውና እነሱ ወደ ውጭ ተመለሱ።
ሔዋን እና ትርፌ ግን አገባቡ ጭንቅ አላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት ዝግጅትና አዳራሽ ውስጥ ታዳሚ ሁነው አያውቁም፡፡ የዝግጅቱ ተካፋይ ለመሆን የጓጉ ቢሆንም
ሌላ ሰው እንደሚያደርገው ቦታ መርጠው ለመቀመጥ ድፍረቱን አጡ። እንዲያውም
👍10
#ምንትዋብ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።

ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።

አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።

ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።

ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።

“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”

“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-

ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።

ፈገግ አለ።

ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።

እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"

“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።

“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።

አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።

ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።

ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።

ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።

ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።

ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።

ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::

ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።

የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።

ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።

ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።

“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
👍10
#ትኩሳት


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

....ጧት ተነስቼ ቁርስ ከበላሁ በኋላ ከሲልቪ ቤት ወጥቼ ወደ
ሲቴ አመራሁ፡፡ ትላንት “ማታ ባህራም ኪሴ ውስጥ ያስቀመጠውን ወረቀት መንገድ ላይ አነበብኩት፡፡ ኒኮል የፃፈችለት ደብዳቤ ነው
«ውድ ባህራም
«እንዴት ልጀምር? አስቸጋሪ ነው። እወድሀለሁ፣ ከልቤ እወድሀለሁ። አሁን የምነግርህ ነገር የማልወድህ ሊያስመስለኝ
ይችላል። ግን እወድሀለሁ፤ ከልቤ አፈቅርሀለሁ
«ያለሬቮሉሽን መኖር አትችልም። ከኔ ጋር መኖር አትችልም። ስለዚህ እኔን ትተኸኝ መሄድ አለብህ
«እኔ ስለሪቮሉሽን በጭራሽ ሊገባኝ የማይችል ብዙ ብዙ ነገር
አለ። ለምሳሌ ደም ማፍሰስ። ብዙ ተከራክረንበታል፣ ታስታውሳለሁ::
ደጋግመህ አይገባሽም! ስለሪቮሉሽን በጭራሽ አይገቤሽም ብለኸኛል። እውነትክን ነው:: አይገባኝም። ግን በደምብ የገባኝ አንድ ነገር አለ። አንተ ያለ ሬቮሉሽንህ መኖር አትችልም። ስለዚህ መለያየት አለብን።

“ከዚህ ቀጥሎ የምነግርሀ ሊገባህ አይችልም። ስለዚህ እንዲገባህ ለማድረግ አትሞክር። ዝም ብለህ እመነው። ይኸው የማፈቅረው አንተን ነው። የተረገዘው ልጅ ግን ያንተ አይደለም። የሉልሰገድ ነው። ልነግርህ ሞክሬ ነበር። ብዙ ጊዜ ሞከርኩ፣ አቃተኝ፡፡ አሁንም
ቢሆን መነፅራሙ ጓደኛህ ባያግዘኝ ኖሮ አልችልም ነበር

አዝናለሁ:: ስላደረስኩብህ ሁሉ ችግር በጣም አዝናለሁ።
ብትችል በልብህ ይቅር በለኝ። ባትችል ጥላኝ፡፡ ብቻ ሂድና
ሬቮሉሽንህ ውስጥ ኑር። ደስታ ሊስጥህ የሚችል እሱ ብቻ ነው።
በሄድክበት ይቅናህ፡፡ ደህና ሁን።
ያንተ ኒኮል።
P S ልታገኘኝ አትሞክር። አታገኘኝም። ልሰናበትህ ባለመቻሌ አዝናለሁ። ግን ፊትህ ላይ ቂም ማየት እፈራለሁ። ደህና ሁን። ይህን ደብዳቢ ሶስት ጊዜ ደጋግሜ አነበብኩት፡፡ ኒኮል ለምን
ፃፈችው ይህን? ቀዳደድኩት። ቁርጥራጮቹን በተንኳቸው:: ሲቲ ሄጄ ገላዬን ታጥቤ፣ ልብሴን ቀይሬ ወደ ኒኮል ቤት ሄድኩ አልጋዋ ላይ ተጋድማ ሲጋራ እያጨሰች ሙዚቃ ትሰማለች ታቹን ነጭ ክሮሽ እንደ ሸማኔ ጥለት የከበበው ቡና አይነት ቀሚስ ለብሳለች። ስገባ ፈገግ እያለች
«እንኳን መጣህ! ጭር ብሎኝ ነበር» አለችኝ
ደህና ነሽ?
«ደህና ነኝ፡፡ በጣም ደህና ነኝ። ግን ሌላ ሰው ማየት
አልፈልግም። እባክህን በሩን ቆልፈው።
ቆልፌው ስመጣ፣ የተጋደመችበት አልጋ ላይ እንድቀሙጥ በእጇ አመለከተችኝ። ጥፍሮቿ ሀምራዊ ተቀብተው ያብለጨልጫሉ።
ተቀመጥኩ፣ አየሁዋት። በጣም የተለወጠች መሰለኝ፡፡ ከንፈሮቿ እንደ ጥፍርቿ ሀምራዊ መሳይ ቀለም ተቀብተዋል፡ ቅንድቦቿን ወደ ሰማያዊ የሚወስድ ጥቁር ቀለም አድምቋቸዋል፣ ከግምባሯ ንጣት ጋር ሲታዩ በጣም ያምራሉ። የአይኖቿ ቆዳ ልክ የአይኖቿን
የሚመስል ውሀ እረንጓዴ ኩል ተቀብቶ፣ አይኖቿ ውስጥ ተነክሮ
የወጣ ይመስላል። ከመጠን በላይ አምሮባታል። ከጥንታዊት
ግብፃዊት ጋር ያለሁ መሰለኝ። ፀጉሯ እንደ ድሮው አመዳም
አይደለም፡ ንፁህ ቡናማ ቀለም ተነክሯል
«ምን ነካሽ?» አልኳት
«ምነው?»
«እንደዚህ የምታምሪ አይመስለኝም ነበር»
"Merci
«እውነት ግን ምንድነው?» አልኳት
«እንደዚህ ነኝ፡፡ ሳዝን ሰው እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። አሁን
ያዘንኩ እመስላለሁ?»
በጭራሽ
«ለዚህ ነው አይኔንም የተኳልኩት፣ ፀጉሬንም የተነከርኩት»
«አዝነሻል?»
«እንደ ዛሬም አዝኜ አላውቅ፡፡ ሲሄድ ደህና ዋል አለህ?»
«አዎን»
የፃፍኩለትን አሳየህ?»
«አዎን፡፡ ለምን ፃፍሽው?»
«እንዴት እንደፃፍኩት ልንገርህ?»
«ንገሪኝ»
«ከትላንት ወድያ ማታ፣ እንደዚህ ተጋድሜ ሙዚቃ ስሰማ፣
አንድ ሰው መጣ፡ መልኩ ሰው ይመስላል እንጂ እንደኔና እንዳንተ
ህዋሳቱ ውስጥ ደም እንደሚፈስ ልምልልህ አልችልም። ምናልባት
ከነሀስ የተሰራ ሰው ሊሆንም ይችላል። ረዥም ቀጭን ነው፡ መነፅር ያረጋል። ግምባር የለውም፡ ከአይኑ ቀጥሎ አናቱ ይመጣል፡፡ ድምፁ ወፍራም ከመሆኑ የተነሳ ከሆዱ እንጂ ከጉሮሮው የሚወጣ
አይመስልም»
«ጠልተሽዋል እ?»
«መጥላት አይደለም፡፡ ፈራሁት። ቀፈፈኝ፡፡ አየህ፣ ገባና
በወፍራም ድምፁ
ኮል ማለት እርስዎ ነዎት?» አለኝ
ነኝ» አልኩት
“ጥሩ። እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ተልኬ የመጣሁ ነኝ
«ታድያ እኔ ከኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ምን አለኝ?
«እርስዎ አይናገሩ፡፡ ጊዜ የለኝም» አለኝ፡፡ ድምፁ በጭራሽ
አይለዋወጥም፡፡ ምንም ነገር ሲናገር በዚያው በወፍራም ድምፅ ነው
“የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ ባህራምን ይፈልገዋል፡፡ በጣም
ይፈልገዋል። እኔን ፓርቲው ልኮኛል። ከትእዛዝ ጋር፡፡ ወያም
ባህራምን ይዘኸው ና፣ ወይም ገድለኸው ተመለስ ተብያለህ
ግደለው? ለምን?» አልኩት
ቀላል ምክንያት፡፡ የኛን ምስጢር ያውቃል፡፡ ምስጢራችንን
በሙሉ ያውቃል፡፡ ስለዚህ፣ ወይም ከኔ ጋር ይምጣል፡ ወይም
ይሞታል። ሌላ ምርጫ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር አለ» አለኝ
ምን?»
ባህራም አልመጣም የሚለው በእርስዎ ምክንያት ነው:: እርስዎ
ባይኖሩ ይመጣል፡፡ ስለዚህ እርስዎ እንዳይኖሩ ማድረግ፡፡»
ሆዱ እየፈራ፤ «እንዴት?» አልኩት
«መግደል» አለኝና፣ ከኪሱ አንድ የታጠፈ ጩቤ አወጣ፡፡ ጫን
ሲለው ጩቤው እንደ ብልጭታ ክፍት አለ ሻህን ልግደለው!' አለኝና፤ ያንን የኢራን
ስእል አመለከተኝ፡፡ ባህራም ነው እዚያ የለጠፈው፡፡ ልተኛ ስልና ልነሳ ስል፣ ሻህ እንዲታየኝ እፈልጋለሁ ብሎ ሰቀለው::»
ግድግዳው ላይ የኢራን ሻህ የጦር ጠቅላይ አዛዥ የማእረግ
ልብሱን ለብሶ ቆሞ በከለር የተነሳው ትልቅ ፎቶ አለ
"ለምሳሌ ሻህ እርስዎ ነዎት። ጉሮሮውን ይመልከተቱ" አለና
ጩቤዋን ወረወራት። የሻህ ጉሮሮ ላይ ስክት አለች። ሰውየው ወደ
ስእሉ ሄዶ ጩቤውን ነቀለና አጥፎ ኪሱ ከተተ መንገድ ላይ እርስዎ ሲራመዱ ወይም ሲሮጡ እኔ በፈጣን መኪና እየሄድኩ ጩቤ ብወረውር፣ ጉሮሮዎትን እልስተውም፡፡ ገባዎት?» አለኝ። በድምፁ ሊያስፈራራኝ በጭራሽ አልሞከረም፡ ልክ የጂኦሜትሪ ፕሮብሌም እንደሚያስረዳኝ ያህል ነበር ገባኝ» አልኩት። እንደዚያን ጊዜ ፈርቼ አላውቅም
«ለባህራም ይንገሩት»
«ምን ብዩ?»
«ያረገዝኩት ካንተ አይደለም፣ ይበሉት
«ታድያ ከማን ነው ልበለው?»
« እንደፈለጉ። ለምሳሌ እጀምሺድ ወይም ከሉልሰገድ ነው
ሊሉት ይችላሉ፡፡ እነሱን ሊጠይቃቸው አይችልም»
«እሺ» አልኩና ደብዳቤውን ፃፈኩ። አጣጥፎ ኪሱ ሲከተው
«ባሀራም ይህንን ካነበበ በኋላም ከርስዎ ጋር መሄድ ባይፈቅድስ?»
አልኩት
«እምቢ አይልም»
«ቢልስ?»
«እገድለዋለሁ። ደህና እደሩ» አለኝና ወጣ። እንደሱ ያለ
ከሰውነት የራቀ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም
ኒኮል ዝም አለች፡፡ ዝም ብዬ እየኋት። በጣም ታምራለች።
ውሀ እረንጓዴ ኩሏና ሀምራዊ የከንፈር ቀለሟ የፈርኦን ዘመን
ግብፃዊት አስመስሏታል። ሳቅ አለች
«ምነው ትኩር ብለህ ታየኛለህ?»
«አማርሽኝ» አልኳት። ውስጡን ደነገጥኩ። እንደዚህ ለማለት
አላሰብኩም ነበር። ውሀ አረንጓዴ ቆዳ ሽፍን ግልጥ በሚያደርጋቸው
ውህ እረንጓዴ እይኖቿ አየችኝ፡፡ ሀምራዊ ከናፍሯ በፈገግታ
ተላቀቁ። እጄን ጉልበቷ ላይ አሳረፍኩ፣ አልከለከለችኝም
«ጫማዬን ላወልቅ ነው» አልኳት
👍285