አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
568 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቅበላ


#ክፍል_አራት


#ከአዶኒስ

"እኔ ትርፍ ቃል አልወጣኝም ሂሳቤን ስጠኝ ማለት ትርፍ ቃል ነው እንዴ?"

“የምናባሽ ሂሳብ? ገና የሶስት አለብሽ!” አላት ጥርሱን እየነከሰና እያጉረጠረጣባት።

“ገባሽ የኛ አራዳ? የዛሬው ሲቀነስ ገና የሶስት ቀን ይቀርብሻል!"

“ የሶስት ቀን?? - የምን ሶስት ቀን ነው እሱ? . ምንድነው የምታወራው?”

“ባክሽ ሂጂና የምታጃጅይውን አጃጅይ! - የመቼዋ ነሽ በናትሽ?”

“ ኦ ....! የባሰበት መጣ አሉ - እሺ ለማንኛውም ሂሣቤን ስጠኝ::”

“እንዴታ! በጣም ነው እንጂ የምሰጥሽ - በ ...ጣም!”

“ሰውዬ - ምን አለ ነገር ባታመጣ?”

“ኧረ ....? ማስፈራራትሽ ነው?”

“እኔ አላስፈሪራሁህም - ሂሣቤን ስጠኝ፡፡”

“አንቺም ሃያ ብሬን ቁ .....ጭ! - ከዛ በኋላ ሂሣብሽን መጠየቅ ትችያለሽ።"

“ ሃያ ብሬን? ” ግንባሯን አጨመታተረች:: “የምን ሃያ ብር

“ኧረ? አላወቅሺውማ ?”

“የምን ሃያ ብር ሰጥተኸኛል?”

“ ምናባሽ እሰጥሻለሁ - በሆነ ተዓምር ከኪሴ ሞጨለፍሺኝ እንጂ ! ”

· “ከኪሴ?”

አዎ! እንዴትአባሽ አርገሽ እንደሆን ባለፈው ከቦርሳዬ ነጥለሽ ላፍ ያረግሺኝን
ሃያ ብር ቁጭ አርጊያት!”

“እኮ እኔ ካንተ ቦርሳ?”

“አይ የለ ሰይጣን ወሰደው በይኛ! እዚህ መታጠፊያው ላይ ያለችው ሱቅ ዘርዝሬ
ከአንዴም ሁለቴ ቆጥሬ -ቦርሳዬ ውስጥ አስተካክዬ ከትቼ - በቀጥታ ወዳንቺ የገባሁ ሰውዬ - ከዚህ ወጥቼም ወዲህ ወዲያ ሳልል በቀጥታ ወደ ቤት የገባው ሰውዬ ከቦርሳዬ ሃያ ብር ሲጎድል
የት ገባ እንድል ትፈልጊያለሽ? ሟሟ በይኛ ! - እ ? -ተነነ በይኛ!”

“ሰውዬው አብደህ ከሆነ አማኑኤል መሄድ ትችላለህ አሁን ግን ሂሳቤን።"

“ዛሬ ግን ሰራሁልሽ! ልብሴን ከአጠገብሽ ራቅ አድርጌ አስቀመጥኩ! - እንዴት አባሽ ትደርሺበት? አየሽ እንዲ ነኝ እኔ!"

“አሁን ሂሣቤን ትሰጠኛለህ አትሰጠኝም?"

“አልሰጥሽም! - ምናባሽ እንደምታመጪ አያለሁ::

“እኔ ምንም አመጣለሁ አላልኩም - ሂሣቤን ስጠኝ።

“ኧረ ....? ሰጠሁሽ እንዴ? - ገና አሥራ አምስት ብር ይቀርብሻል እኮ ነው ምልሽ! ገና ሶስቴ እመጣልሻለሁ ደስ ባለኝ ቀንና ሰዓት! ”

“ሰውዬ በጉልበትህ አምላክ - ሂሣቤን`

“ ገንዘብ የሌለኝ መስለሽ እንዳይሆን ቦርሳውን እያሳያት “ይኸውልሽ ተመልከች በርሳዬ ውስጥ ያለውን
ብር ግን ሰባራ ሳንቲም አልሰጥሽም! - ሞሽላቃ ሌባ!”
ፀዳል ከላይ እስከ ታች እንደ ማንቀጥቀጥ አደረጋት:: ሥሮቿ መገታተር ጀመሩ:: አገጯ ጥግ ያሉ የመንጋጋ አጥንቶች የትርታ ዓይነት ሁለት ሶስቴ ገባ
ወጣ አሉ፡፡ አተነፋፈሷ ፍጥነት ጨመረ::

ዠሂሣቤን - ስጠኝ::” አለችው ጥርሶቿን ግጥም አድርጋ እንደነከሰች ከንፈሮቿን ብቻ በማንቀሳቀስ::

“ሂጂና የምታስፈራሪውን አስፈራሪ እሺ? - እንኳን አንዲት ኪስ አውላቂ ሌባ ሌላም አያስፈራራኝ! ለመውጣት ዓይነት ብድግ አለ::

“ሂ - ሣ - ቤን! - በንጥቀት ተነስታ በሁለት እጆቿ ጃክቱን ጨመደደችው::

“ሴትዮ ልቀቂኝ! - ሂሣብ ያለብሽ አንቺ ነሽ ማለት አማርኛ አይደለም?” እጆቿን መንጭቆ ጃኬቱን ካስለቀቀ በኋላ ባለ በሌለ ኃይሉ አሽቀንጥሮ አልጋዋ ላይ
ጣላት። “ካሁን ወዲያ ብትጠንጊኝ በእጄ ስበብ እንደምትሆኚ እወቂ!

ፀዳል ከወደቀችበት በግማሽ ቀና አለችና እሳት የምትተነፍስ ዓይነት እያለከለከች እዚያው በዚያው ደም በለበሱ ዐይኖቿ ሰውዬውን አምርራ አየችው:: ወዲያው
ተስፈንጥራ ተነሳችና አስር ጣቶቿን እንዳንጨፈረረች ዘልላ ፊቱ ላይ ተከመረችበት ባልጠበቀው እርምጃዋ
የተደናገጠው ሰው የሸሚዙ ቁልፎች ተበጣጥሰው እስኪወድቁና ፊቱና ደረቱ በቡጥጫዋ እስኪዥጎርጎር ድረስ ታግሎ እንደምንም ከተላቀቃት በኋላ በሰነዘረው
ቡጢ መንጋጭላዋን ሲላት እንደገና እዚያው አልጋዋ ላይ በጀርባዋ ፍንችር ኣለች:: ለመነሳት እየተንገታገተች
ሳለ ሰውዬው ተንደርድሮ ሰውየው ጉብ ይልባትና በሁለት እጆቹ

አንገቷን አንቆ ወደዚያው ደፈቃት:: ፀዳል እጆቹን በእጆቿ ግጥም አድርጋ ይዛ ለማስለቀቅ እየታገለች እግሮቿን አወራጨች፡፡ ለመጮህ ስትሞክር ከታነቀው ጉሮሮዋ ድምፅ አልወጣ አላት:: ጣዕራ ጨመረ።

ማሙሸት ጭንቀት ገባው:: እናቱ በእንግዳዋ ስትበሻቀጥ ስትሰደብም ሆነ ስትደበደብ የመጀመሪያዋ አይደለም:: የተለያዩ ደንበኞቿ በተለያዩ ጊዜያት ይህን
ያደርጋሉ:: ታዲያ እናቱ ምንም ዓይነት ፀብ ውስጥ ብትገባ ራሷ እንደምትወጣውና እሱ በምንም ዓይነት
ከቦታው ንቅንቅ እንዳይል ጥንቱኑ ስላስጠነቀቀችው ለጥ ብሎ ከማዳመጥና ሕመሟን ከመታመም ሌላ ጣልቃ ለመግባት ሞክሮ አያውቅም:: በኋላ በኋላማ ከነገሩ ተደጋጋሚነት የተነሣ እየለመደው ሲመጣ ከበላዩ በሚያዳምጠው ግርግር መሃል ሌሎች ሌሎች ዕለታዊ ፍሬከርሲኪዎችን ማሰላሰል እስከመቻል ደርሷል::
የዛሬው ግን ለየት ያለ ሆነበት:: እናም ክፉኛ ተፈታተነው:: በደረቱ እንደተኛ አንደኛውን ጆሮውን ወደአልጋው ቀስሮ
ማዳመጥና መቁነጥነጥ ጀመረ።

ማሙሽት እየሰማው ካለው ግርግር ብቻ ሰውዬው ፀዳልን በጣም እየጎዳት መሆኑን አልተሳነውም፡፡ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለበት ትንሿ ደመነፍሱ ክፉኛ ጨቀጨቀችው:: ይሁን እንጂ የእናቱን ሕግ መጣሰም የዚያኑ ያህል ስለከበደው እንደምንም ጥርሱን ነከሰ፡፡
የሰውዩው ሁለት እጆች አሁንም በፀዳል ቀጭን አንገት ዙርያ እንደተቆላለፈ ነው።
የሰውየውን እጆች ጭምድድ አድርገው እንደያዙ ጥፍሮቿ ቆዳውን ዘልቀው ገብተዋል።እግሮቿን እያወናጨፈች
የሰውየውን እጆች ከአንገቷ ለማላቀቅና ድምዕ ለማውጣት ጣረች:: ውጪ ድረስ ሊሰማላት የሚችል ድምፅ ማውጣት ግን አሁንም አልሆነላትም ሰውዬው ያምጣል ያለከልካል ከስሩ የሞት የሽረቷን የምትወራጨው ሴት የግምቱን ያህል ቀላል ሆና ያገኛት አይመስልም....

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ነገ እንጨርሰዋለን መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ብቸኝነት

እልፍኝህ እንዳ'ብርሃም ቤት ፤
አደባባይህ እንደጥምቀት ፤
የሰው አሸን ቢወረው ፣ጠጠር መጣያ ቢገድም፤
ለመሀላህ ካስማ ሚሆን ፣ሲያነቅፍህ የምጠራው ስም፤
ከልቦናህ ሲነጥፍ፣ አንደበትህን ሲያንቀው፤
ብቻህን ነህ ያኔ እወቀው።

🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘

መጋቢት 11 2012
#የጀግና_ሀገር_አይመሽም

"መሽቶብኛል" ብለህ፣ መተኛት አትውደድ
ጀግና ተጓዥ እንጂ ፤ የለም ጀግና መንገድ።
ራሱ ጀግንነት ነው!
ብርሃን እስኪገኝ ፣ በጨለማ መሔድ!!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ቅበላ


#ክፍል_አምስት(የመጨረሻ ክፍል)


#ከአዶኒስ

ውድ ተከታታዮቼ እንዴት ናችሁ ካቅም በላይ በሆነ ችግር በቃሌ አልተገኘሁም የጀመርኩትን መጨረስ አልቻልኩም ለዚህም ይቅርታዬ ባያላችሁበት ይድረስልኝ🙏

....የሰውዬው ሁለት እጆች አሁንም በፀዳል ቀጭን አንገት ዙሪያ እንደተቆላለፉ ነው:: የሷም
የሰውየውን እጆች ጭምድድ አድርገው እንደያዙ ጥፍሮቿ ቆዳውን ዘልቀው ገብተዋል:: እግሮቿን እያወናጨፈች
የሰወዬወን እጆች ከአንገቷ ለማላቀቅና ድምፅ ለማውጣት ጣረች።ውጪ ድረስ ሊሰማላት የሚችል ድምፅ ማውጣት ግን አሁንም አልሆነላትም።ሰውዬው
ያምጣል ያለከልካል ።ከሥሩ የሞት የሽረቷንየምትወራጨውን ሴት የግምቱን ያህል ቀላል ሆና ያገኛት አይመስልም:: ድንገት ያለ የሌለ ኃይሉን አሰባሰበና
ጫናውን ጨመረ:: ፀዳል እየታረደ እንዳለ ዶሮ እግሮቿን አወነጨፈቻቸው:: አናቷን ግራ ቀኝ እያወራልጨች ከአልጋው ጋር ታላጋው ጀመር፡፡

ማሙሸት መቋቋም ተሳነው። በሰራ አካላቱ ያሉ ጅማቶች መወጣጠር ጀመሩ:: የልብ ትርታው አየለ::
የእናቱ ሕግ ከዚህ በላይ አስሮ ሊያቆየው አልቻለም፡፡ኮሽ እንዳይልበት እየተጠነቀቀ በደረቱ፡ ዳግም ወደ አልጋው ጠርዝ በመሳብ የተንዠረገገውን የአልጋ ምንጣፍ ገለጥ አደረገና ዐይኖቹን በጠባቧ ክፍል ከወዲያ ወዲህ አማተረ፡፡
ቅድም ፀዳል ሽንኩርት የከተፈችበት ቢላ እዚያው መክተፊያው ላይ እንደተወችው ነበር፡: ማሙሸት አንዲት ቅፅበት አላጠፋም፡፡ በደረቱ እየተሳበ ከአልጋው ሥር ወጣ፡፡ ቢላውን ለቀም አድርጎ አነሳና እጀታውን በእጆቹ መሃል እያመቻቸ እናቱ ላይ እንደ ጥንብ አንሳ እያጆፈጆፈባት ወዳለው ሰው ተንደረደረ፡፡ እንደደረሰም
በሁለት እጆቹ አጥብቆ የያዘውን ቢላ ከአናቱ በላይ አንስቶከቁልቁል በሰውዬው ማጅራት መሃል ሰካው።

ከየት መጣ ሳይለዉ ማጅራቱ ወስጥ
በተሰነቀረበት ቀዝቃዛ ባዕድ ነገር ለጊዜው ግራ የተጋባው ሰው እዚያው ባቀረቀረበት ዐይኖቹ ፈጠጡ፡፡ ቀስ በቀስም በፀዳል አንገት ዙሪያ ያቆላለፋቸው ጣቶቹ እየላሉ መጡ::
ማሙሸት ወደ በሩ አፈገፈገና ቁና ቁና እየተነፈስ ሁኔታውን መከታተል ጀመረ:: ሰውዬው በዝግታ ከፀዳል ላይ ቀና አለ፡፡ ከማጅራቱ የሚፈሰው ደም ቁልቁል
በጀርባው መውረድ ጀምራል፡፡ ዝግ ባለ እንቅስቃሴ እጆቹን ወደ ማጅራቱ ላከና እጀታው ሲቀር ስለቱ ሙሉ በሙሉ
የገባበትን ቢላ ደባበሰው:: ፀዳል የግንባሯ ሥራሥሮች እንደተገታተሩ በአንድ እጇ ማንቁርቷን እያሻሸችና በሀይል እያሳለች በሌላኛወ እጇ አልጋውን ተደግፋ ከተንጋለለችበት በከፊል ቀና አለች:: ሰውዬው ቢላውን ለመንቀል ይታገላል:: ማሙሸት በሩ ላይ በጀርባው
እንደተለጠፈ አንዴ ሰውዬውን አንዴ እናቱን እያየ ያለከልካል፡፡ የታችኛው ከንፈሩ ይንቀጠቀጣል። ፀዳል
ሳሏ ጋብ እንዳለላት ቆባቸው የተንጠለጠለ ዐይኖቿን እንደምንም ገልጣ ከፊት ለፊቷ ጣረ-ፍዳውን እያየ ያለውን ሰውና በሩጋ ቆሞ የሚብረከረከውን ልጇን በነጎድጓድ
ብልጭታ ፍጥነት እያፈራረቀች ተመለከተቻቸው፡፡

“በል ቶሉ ውጣ ቶሎ ውጣ አላችው ሁለመናውን ጆሮ አድርጎ አፍ አፏን እያየ ለሚጠብቃት ልጇ፡፡ “ቶሎ ውጣና ከዚህ ሰፈር ጥፋ! ማንም ቢጠይቅህ
ትሰማኛለህ?ምንም የሰማኸው ማንም ቢጠይቅህ - ምንም ያየኸው -ምንም የምታውቀው ነገር የለም!
ጨርሶ እዚህ አካባቢ አልነበርክም ማለት ነው! - እሺ?”

ማሙሸት ራሱን በመነቅነቅ እሺታውን ገለፀላት:: “እኮ በል ውጣ! - ውጣ!` አካለበችው - ከትንፋሿ ጋር ቁርጥ
ቁርጥ በሚሉ ቃላት:: ማሙሸት በሚርበተበቱ እጆቹ በሩን ከፈተና ፈትለክ ብሎ በመውጣት ከድቅድቁ ጭለማ
እቅፍ ገባ፡፡

ሰውዬው ድንገት አጓራ።በግራ እጁ ከማጅራቱ በላይ ያለውን አናቱን ደግፎ ይዞ በቀኝ እጁ ቢላውን ለመንቀል እየታገለ የሞት ሞቱን ማሙሸት በከፈተውበርግጥ ወጣ፡፡ መራመድ የተሳነው ዓይነት እዚያው ደጃፉ
ላይ ቆም አለና ማጓራቱን ቀጠለ፡፡

ወዲያው ጩኸቱን በሰሙ ተላላፊዎችና
ከየጉራንጉሩ እየተሯሯጡ በመጡ የመንደሩ ሰዎች የፀዳል ደጃፍ ተጥለቀለቀ:: ወደሚያጓራው ሰው
ለመቅረብ የሞከረ አንድም ሰው የለም። በጥቂት ክንዶች ርቀት ከብበው ጣዕር ላይ ያለውን ሰው በተሻለ ለማየት
ይጋፋሉ፡፡

የሰውዬው ድምፅ እየደከመ መጣ፡፡ ቢላውን ለመንቀል ያደርግ የነበረውን ጥረት ትቶታል:: ደሙ ቁልቁል በሰውነቱ ሙሉ ወርዶ ከመንገዱ የድንጋይ
ንጣፍ ላይ ተንጠባጠበ፡፡ ተጨፍነው የቆዩ አይኖቹን እንደምንም በግማሽ ገለጠና ወደፊት እንደመንቀሳቀስ
ሲል ከፊትለፊቱ የነበሩት ተመልካቾች በሽሽት እየተጋፉ ወደግራና ወደ ቀኝ ተበተኑ። አንድ ሁለቴ እንደተራመደ
በሙሉ ቁመቱ እንደ ደመራ ግንድስ ብሎ ወደቀ፡፡ ሰዎቹ እንደገና የወደቀውን ሰው በቅርበት ለማየት መጋፋት
ግርግሩ ደመቀ፡፡ ተጨማሪ ሰዎች ወደ ሥፍራው መጉረፍ ጀመሩ፡፡ የወደቀው ሰው ምንም እንቅስቃሴ .አይታይበትም:: አሁንም ወደ ሰውዬው በቅጡ ለመቅረብ
የደፈረ የለም:: እያንዳንዱ ሰው በየቆመበት የየራሱን አስተያየት ይወረውራል፡፡

“ሳይሞት አይቀርም! - የታል የሚተነፍሰው? ምናለ በሉኝ ሞቷል!”

“መሞትስ አልሞተም! - ይልቅ ቢላው ይነቀልለት!"

“አአ - ቢላው ከተነቀለማ አለቀለት! - ደሙ ፈስሶ ያልቅ የለ እንዴ? - ይልቅስ እንዲሁ እንዳለ ሆስፒታል ማድረስ ነው!”

“በጭራሽ! . አባዲና ሳይመጣ አንድ ሰው
እንዳይነካው! - ኋላ ጣጣ ውስጥ እንዳትገቡ!”

“አዎ - አሻራ ሳይነሳማ መንካት አይገባም

“ይልቅ ፖሊስ ይጠራ!”

“ፖሊስ ምን ይረዳዋል? - አምቡላንስ ነው
መጥራት

ከወዲህም ከወዲያም አስተያየቶች ተዥጎደጎዱ፡፡

በዚህ መሃል ፀዳል በአንድ እጇ ወገቧን እንደያዘች በሌላኛው እጄ ያንኑ ጉርርዋን እያሻሸች በዝግታ ወደ በሯ ብቅ አለች፡፡ ወዲያውኑ የሁላቸውም ትኩረት ሃውልት መስላ በሯ ላይ ወደተገተረችው ሴት ዞረ
ምንም ዓይነት የመደናገጥ ምልክት አይታይባትም፡፡ይልቁንም - ተጋጣሚውን በዝረራ እንዳሸነፈ ሻምፒወን ሰውየውን ቁልቁል እያየች የሚሆነውን የምትጠባበቅ መሰለች፡፡ ከተመልካቾቹ መሃል ወደእሷም ለመቅረብ የደፈረ የለም:: በቅርብ የሚያውቋት ሴት ጎረቤቶቿ ብቻ ከግራም ከቀኝም በጥያቄ አጣደፏት፡፡ ዐይኖቿን ለአፍታ እንኳን ከወደቀው ሰው ላይ ያልነቀለችው ፀዳል የሰዎቹን ጥያቄዎች መመለስ ይቅርና ቀድሞ ነገር የምትሰማቸው
አትመስልም::

ብዙም ሳይቆይ ጥቂት ፖሊሶች እየተጣደፉ ከቦታው ደረሱ። የከበበው ሰው ገለል ገለል አለላቸውና ሰውየውን በቅርበት እያጤኑት ሳለ በሯ ላይ ቆማ
የነበረችው ፀዳል እንደገና ወደ ውስጥ ገባች፡፡ ሰውዬውን አልብሶት የቆየው ጥላዋም እንደ ጥቁር ቬሉ ከኋላዋ
እየተጎተተ ተከትሏት ገባ። ይሄኔ መንገዱ ላይ የተንጋለለው ሰው ከላዩ ጣል ተደርጎበት የነበረ ስስ ከፈን የተነሳለት ዓይነት እንደገና በግልፅ መታየት ጀመረ፡፡

የፀዳልን ወደ ውስጥ መዝለቅ ልብ ያሉት ፖሊሶች እርስበርስ ተጠቋቆሙ። ወዲያው ከመሃከላቸው ሁለቱ ወደ በሯ እንደማምራት ሲቃጣቸው ፀዳል ነጠላ ቢጤ ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጋ እንደገና ብቅ አለች::

ሁለቱ ፖሊሶች ከተቀሩቱ ጋር በፖሊስኛ
ከተንሾካሾኩ በኋላ ወደ ፀዳል አቅጣጫ መንቀሳቀስ እንደጀመሩ እሷው ራሷ በሯን መለስ አደረገችና ወደ እነሱ በማምራት በመሃላቸው አልፋ ከፊት ከፊታቸው
እየመራች የዋናውን መንገድ አቅጣጫ ያዘች።

ሰዉ ወደየመጣበት ተበታተነ።ማሙሸት ብቻ ታጅባ እየተወሰደች ያለችውን እናቱን በርቀት ሲከተላት ቆየ።
በስፋት የተንጣለለው ግራጫ የአስፓልት ጎዳና ፀጥ ረጭ ብሏል:: ቀስ በቀስ በማሙሸትና በእነፀዳል መሃል
ያለው ርቀት እየሰፋ እየሰፋ ሄደ::
👍1
የፖርላማው ሰዓት ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት መሆነን በተለመደው ደወል አሰማ። ማሙሸት ከአንድ መስቀለኛ መንገድ ሲደርስ ቆም አለ፡፡ ድንገት ብንን የማለት ዓይነት ለመጀመሪያ ጊዜ ሁሉም ነገር እውን መሆኑ ታወቀው:: ግራና ቀኝ
ባጀቧት ፖሊሶች መሃል አንገቷን ቀና አድርጋ በሙሉ እርጋታ እየተራመደች ከርቀት የምትታየው እናቱ ይብሱን የኮከብ ያህል ርቃ ግን ደግሞ የዚያኑ ያህል
ከመቼውም በላይ ገዝፋ ታየችው:: ትንሿ ልቡ እዚያው በዚያው ሽብር ሽብር ማለት ጀመረች:: ዐይኖቹ እርጥበት አጋቱ:: ትከሻዋ ላይ ጣል ካደረገችው ነጭ ነጠላዋ ጋር ዕብነበረድ መስላ ከርቀት ትታየው የነበረችው እናቱ ነፋስ ባወከው የተኛ ውኃ ላይ ተንፀባርቆ እንደሚታይ
ምስል ብዥዥዥዥ .....አለችበት።

💫አለቀ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ዘበት_ሊሆን_ነው_ወይ

ዘበት ሊሆን ነው ወይ፤
..................ታሞ ጠበል መሄድ፤
.................................ተሰብሮ ወጌሻ፤
አልጋ የሚይዝ ጠፋ፣
.....................እርሳስ እንደኪኒን፣
................................እየዋጠ አበሻ።

🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘

ጥቅምት 2010
°°°°እማሆይ ፍልስፍና

ከዳተኛው ልቤ - መካድ የለመደ
'እግዜር የለም' አለ አንቱን በወደደ
🔘©ሲራክ 🔘

--------//////_________
#ከዓለም_ ታሪክ_የተዘለለ_አንድ_አንቀጽ

በ1994 ጫማዬ ተሸነቆረ
ለቀጣይ አራት ዓመታት
እንደ ተሸነቆረ ቀረ ፤
ጫማ የተፋው አውራ ጣቴ፣ ውጋት ይሰማው ነበረ

ክሥተትን ሁሉ ጋረደ፣ ያ'ውራ ጣቴ ትንሽ ሕመም
የጫማዬን ሽንቁር ያኽል፣ ጎድላ ታየችኝ ዓለም
ከእኔና ከእግር አምላኬ በቀር፣ ማንም ይህን አላስተዋለም

ሊቃውንት የዓለምን ክሥተት ሲጽፉ
የምድር ወገብ መስመር በሳሎኔ ባለማለፉ
መኖሬን ገደፉ፣

ሁሉም እንደ ፈቃዱ ቢመርጥ የታሪክ ርእስ
አንዱ በፈረንሳይ አብዮት ቀለም ቢጨርስ
አንዱ በግሪክ ቢጀምር
የዓለም ታሪክ አይሟላም የጫማዬን ሽንቁር ሳይጨምር፡፡

🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ማዕዶት


#ክፍል_አንድ


#በየዝና_ወርቁ

“ወይኔ !... ዘንድሮ እንዴት ጉድ ሆንኩ!? አለች ማዕዶት ለራሷ ብቻ በሚሰማ ድምፅ - ራሷን በቁጭት እየነቀነቀችና ገና ሁለት ወር እንኳ ያልሞላው ፅንስ በእጇ ይታወቃት ይመስል ከእምብርቷ በታች ያለ
ሰውነቷን እየዳሰሰች :: ሰሞኑን ሁሉ እንዲህ እየተቆጨችና እየተበሳጨች ነበር የሰነበተችው:ፈ።

ዛሬም የሰነበተባት ጭንቀት እያናወዛት
የምርመራ ውጤቷን ለመስማት በክሊኒኩ የእንግዶች ማረፊያ አግዳሚ ወንበሮች በአንዱ ላይ ተቀምጣለች።ወረፋ አስከባሪዋ ተረኛ ለመጥራት ብቅ ስትል ትደነግጣለች፡፡ ሌላ ሰው ጠርታ ስትመለስ ደግሞ ትጨነቃለች፡፡ ሁለቱ ቀያይ ጉንጮቿ ፍም መስለዋል፡፡
ለወትሮው እንደህፃናት ዐይኖች ጥርት ብለው የሚጉሎት ዐይኖቿ ደፍርሰው ቀጫጭን የደም ስሮች ቅርንጫፎቻቸውን ዘርግተውበታል፡፡ ሳምንቱን ሙሉ
ማበጠሪያ ያልገባበት ፀጉሯ በተከናነበችው ጥቁር ሻርፕ
ቢሸፈንም በግንባሯ ዳርዳር ክርችፍ ብሉ ይታያል፡፡ጭንቀት ያጋለው ሰውነቷ ላብ ማመንጨት ሲጀምር ራሷን ያሳክካት ጀመር፡፡
እንደ እሷ የምርመራ ውጤታቸውን የሚጠብቁ ሰዎች በወረፋ ቁጥራቸው እየተጠሩ ውጤት ወደሚሰማበት ክፍል እየገቡ ይወጣሉ፡፡ ማዕዶትውጤታቸወን ለመገመት ፊታቸወን አተካራ
ታስተወላለች፡፡ አንዳንዶቹ የግንባራቸወን ላብይጠርጋሉ፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ መልዕክት አድርሱ የተባሉ
ይመስል እየተጣደፉ ከግቢ ይወጣሉ፡፡

አንዳንዶቹ ምንም ስሜት አይነበብባቸውም።እንዲህ ፊታቸውን እያነበበች ሁኔታቸውን እያስተዋለች ውጤታቸውን ለመገመት ስትሞክር ትቆይና ሳትወድ ወደ ምትሸሸው ወደ ራሷ ትመለሳለች፡፡ በሃሳቧ የተሰራ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭ የሚል ወረቀት ፊቷ ላይ
ሲደቀን ይዘገንናታል፡፡ እንደመባነን ዐይነት ራሷን በኃይል ትነቀንቃለች:: በሰራ አካላቷ የጭንቀት እሳት ይቀጣጠላል።

“ወይኔ ምን አሳበደኝ? ደግሞ ትክክለኛ ስሜንና አድራሻዬን እንዴት እሰጣለሁ? ምን አደነዘዘኝ? ትላለች።

ደም ከመስጠቷ በፊት የምክር አገልግሎት የሰጠቻት ነርስ የምርመራ ውጤትሽ በምስጢር የሚያዝ
ነው:: መዝገብ ላይ የምናሰፍረው ለስታትስቲክስ እንዲሆን በኮድ ቁጥር ነው:: ካንቺ ፈቃድ ውጭ ለማንም አይነገርም

ብላታለች፡፡ መጀመሪያ አምናት ነበር፡፡ ደም ከሰጠች በኋላ ግን የማይታመን ነገር ሆነባት፡፡ በዚያም ላይ ምንም እንኳ ለመመርመር የፈለገችበትን ትክክለኛ
ምክንያት ባትነግራትም ከነርሷ ጋር ረዘም ላለ ጊዜ አውርተዋል፡፡ ከአሁን በኋላ የትም ቦታ ብታገኛት እንደምታውቃት አሰበች፡፡ እና ነርሷ በከተማው ሙሉ
ተባዝታ ታየቻት፡፡ ታክሲ ውስጥ ፣ ገበያ መሀል ፣መዝናኛ ቦታዎች... ምናልባትም እኮ የሚያውቃት ሰው ዘመድም ጓደኛም ጉረቤትም ልትሆን ትችላለች! እንዲህ
ባሰበችው ቁጥር - በአደባባይ መሀል እርቃኗን የቆመች እየመሰላት ሄደ፡፡ እና “እንዲያውም ምስጢር ባይባል
ኖሮ ስራዬ ተብሎ ይወራ ይችል ነበር!» አለች:: እጆቿ በጭንቀት ይንቀጠቀጣሉ፡፡

ወረፋ አስከባሪዋ ግን ብቅ ትልና በተረጋጋ
መንፈስ በቁጥራቸው እየጠራች ትመለሳለች:: ማዕዶት ከከአሁን አሁን ተጠራሁ እያለች በ ጭንቀት
ታስተውላታለች፡፡ የወረፋ ቁጥራቸው ደግሞ ቅደምተከተልና የጠበቀ አይደለም፡፡ እና የሷን ቁጥር እያለፈች
ሌላ ስትጠራ ትባትታለች፡፡

“በቃ ነኝ ፣ ነኝ...” ትላለች፡፡ “
ፖዘቲቭ የሆንነውን ነው ወደኋላ ያቆዩን፡፡ ረዥም ምክር ሊሰጡን፣ እንዳንሸበር
በቂ ጊዜ ሰጥተው ሊያረጋጉን ፣ ለሌሎች እንዳናስተላልፍ ሊያስተምሩን! ... አቤት ፈጣሪዬ! ... ምን አሳበደኝ?
... ምነው እንደሸሸሁት ሳልመረመር ብቀር?...»
“ማዕዶት መጀመሪያ ፍቅረኛዋ ከአያልነህ ጋር በጥል የተለያዩ ወዲህ ለበርካታ

ዓመታት በጥርጣሬና


በ ጥ ንተት እየታመሰች ከወንዶች ርቃ ኖራለች።ተመርምራ ሁኔታዋን ለማወቅ እየፈራችም ብዙ የትዳር አጋጣሚዎቿን ሽሽታ አሳልፋቸዋለች:፡ እምነታችንን
በፈጣሪ አድርገን ሳንመረመር እንጋባ የሚሏትን ወንዶች ትጠራጠራቸዋለች | ትፈራቸውና እርግፍ አድርጋ ትተዋቸዋለች፡፡ “ተመርምረን ነው መጋባት ያለብን የሚለ ሲያጋጥሟት ደግሞ ራሷን ትጠራጠርና መመርመሩን ትፈራና ትጨነቃለች፡፡ ድንገት ቫይረሱ
በደሟውስጥ ቢገኝስ? ከዚያ ወዲያ ህይወትም ዓለምሌላት ሆኖ ይታሰባታል:: እና አያልነህን ትረግምና ሳታገባም ሳትወልድም እንዲሁ መኖርን ትመርጣለች፡፡

አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እንዲሁ ሳታገባ ሳትወልድ ህይወቷ የማለፉ ነገር ያስጨንቃታል፡፡ እናት የመሆን
ፍላጐት ፣ ባለትዳር የመሆን ምኞት ተጠናውቶ ይወተወታታል።ታዲያ ውትወታው እረፍት ሲነሳት ፣ ቀስፎ ሲያስጨንቃት ፣ ዕድሜዋን ታሰላና
«ገና ብዙ ጊዜ አለኝ:: እስከዚያ መድኃኒቱ ይገኝ ይሆናል» ትልና ራሷን ትደልላለች::

በርካታ ወዳጅ ዘመዶቿ ቀጠን ረዘም ያለውንና በአለባበስ አዋቂነቷ ታግዞ የሚዋበውን ተክለ ሰውነቷን፣አጠር ካለው አፍንጫዋ በላይ እንደከዋክብት የሚያበሩትን ዐይኖቿን ፣ ከፊቷ ጋር በሚስማማ ቅርፅ እየተቆረጠች
በካውያ አለስልሳ በምታበጥረው ፀጉሯ የሚፈካውን የደም ገምቦ ገፅታዋን እያስተዋሉ ሳታገባ ጊዜዋ መንጎዱ
ይከነክናቸዋል።
በአንዳንድ አጋጣሚዎች ተደፋፍረው
እንድታገባ ሲመክሯት ግን ምክንያት እየደረደረች ስትከራከር ሃያዎቹን ጨርሳ ወደ ሰላሳዎቹ ተሻግራለች::

ወዳጅ ዘመዶቿን እንዲህ ግራ ይግባቸው እንጂ እሷማ ከአስር ዓመት በፊት በወጣትነት እድሜዋ አግብታ
ጉልበቷ ሳይደክም በሞቀ ፍቅርና ትዳር ልጆቿን የማሳደግ ዕቅድ ነበራት:: ከንግድ ስራ ኮሌጅ በቢሮ ማኔጅመንት በዲኘሎማ ተመርቃ አሁን ከምትሰራበት መስሪያ ቤት እንደተቀጠረች ሰሞን የሠራተኞች ጉዳይ
ኤክስፐርት ከነበረው ከአያልነህ ጋር ተግባቡ:: በፍቅር ተስማምተው ለመጋባት ወሰኑ:: ያንጊዜ የሃያ ሶስት ዓመት ወጣት ነበረች:: እሱም ወደ ሃያዎቹ መገባደጃ
ደርሷል፡፡

በዚያን ዘመን ከኤች.አይ.ቪ ራስን ለመጠበቅ የሚታሰበው ተጋብቶ አንድ ላንድ ተወስኖ በመኖር እንጂ ከጋብቻ በፊት ተመርምሮ ራስን ማወቅ ትኩረት
የሚሰጠው ጉዳይ አልነበረም:: በዚያም ላይ በአብዛኛው ሰው እምነት ኤች.አይ.ቪ የጠጪ ወንዶችና የሴተኛ አዳሪዎች መቅሰፍት ነበር፡፡

የአያልነህ ተግባቢና ቀበጥባጣ ባህሪ ከማዕዶት ጭምትነት ጋር ሲዋሀድ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንኳን
ለነሱ ላያቸውም ወደድኳቸው የሚያሰኝ ህብር ፈጥሮ ነበር፡፡
ተጋብተው ጎጆ ለመውጣት ከሁለቱም ደሞ እየቀነሱ ሲያጠራቅሙ፣ ስለሰርጋቸው ድግስ ፣ ስለዚቤት ዕቃ... እያሰሉ ሲብተከተኩ ሁለት ዓመት አሳለፉ

በመሀከሉ አያልነህ በእድገት የሠራተኛ ማስተዳደሪያ ክፍል ኃላፊ ሆኖ ወደ ናዝሬት ተዛወረ:: ማዕዶት ያገኘው የሁለት መቶ ብር ጭማሪ ቀርቶበት ባይለያዩ ነበር
የፈለገችው:: ለአያልነህ ግን የሞኝ ሀሳብ ሆነበት፤

“እድገት እንዴት እምቢ ይባላል፡፡ እንኳን
ይኼንን ያህል የደሞዝ ልዩነት እያለው አላት::
“ፍቅራችን በመካከላችን እስካለ ድረስ እንኳን ዘጠና ዘጠኝ ኪሎ ሜትር አንድ ሺም ቢሆን ችግር የለውም
ብሎ አግባባት::

የመጀመሪያዎቹን ስድስት ወራት በየሳምንቱ መጨረሻ ያለማቋረጥ እየተገናኙ ጥሩ ጊዜ አሳለፉ፡፡
አያልነህ ሲያስበው ግን ከደመወዛቸው ከወጪ ቀሪ ሆኖ የሚጠራቀመው ገንዘብ እንዲያወም እድገት ሳያገኝ ከነበረው ያንስበት ጀመር:: በዚህ ከቀጠሉ ትዳር
የመመስረታቸው ነገር የህልም እንጀራ ሆኖ ታየው። እና በአስራአምስት ቀን አንድ ጊዜ ቢገናኙ እንደሚሻል በጨዋታ መሀል አነሳባት:: ጠረጠረችውና ተቆጣች።
እንዲያውም ለነገር የማይመች ሆኖባት ነው እንጂ በሱ ተግባቢ ባህርይ ተለያይተዉ መኖራቸወ የበለጠ
እያሳሰባት
👍3
ሄዷል፡፡ እንዲህ ሆነው የመጀመሪያው ዓመት አለቀ::
ኢያልነህና ናዝሬት ተዋሀዱ:: የሚያውቀውና የሚወደው ሰው ብዛት ተወልዶ ያደገባት ከተማ አስመሰላት:: በተለይ እንደ ሴት ጓደኛቸው የግል
ችግራቸውን የሚያዋዩት ሴት ባልደረቦቹ መበራከት ማዕዶትን ቅር ያሰኛት ጀመር፡፡ በአንድ የግል ፋብሪካ ውስጥም ተቀላጥፎ የትርፍ ጊዜ ስራ አገኘ፡፡ የወር ገቢው ጨመረ፡፡ ማዕዶትም ትምህርቷን በስራ አመራር ወደ ዲግሪ ከፍ ለማድረግ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማታው
ክፍለ ጊዜ ጀመረች:: እና ሳያስቡት የሚገናኙበት ጊዜ እያነሰ ሄደ::

መራራቃቸው እየሰፋ ሲሄድ አለመግባባት
ይከሰት ጀመር፡፡ ማዕዶት ችላ አልከኝ ትለዋለች:: ድሮ እንቅስቃሴወን ከወር ገቢ አንፃር እያሰላች የተቆጣጠረችው ይመስላት ነበር፡፡ አሁን ግን ባለትርፍ
ገቢ ሆኗል:: የኤች.አይ.ቪ ወሬም ተስፋፋ:: ናዝሬት ድሬደዋና ባህርዳር ትኩረት እየሳቡ ሄዱ:: ስጋትና ጥርጣሬ
ያነጫንጫት ጀመር:: አያልነህም በበኩሉ እስኪያገኛት ይጓጓ የነበረውን ያህል ንጭንጫን መሳቀቅ ጀመረ::

በዚህ ሁኔታ እያሉ ለፈተና እረፍት ወስዳ
በነበረበት አንድ ቀን ከሰዓት በኋላ ድንገት ናዝሬት ትሄዳለች:: ያሰበችው ከቢሮው ሳይወጣ ደርሳበት አብረው ሲዝናኑ እንዲያመሹ ነበር፡፡ ሆኖም ከአውቶቡስ ተራ ወርዳ በታክሲ ወደ መስሪያ ቤቱ ስትሄድ በእግሩ እየተጣደፈ ቁልቁል ሲወርድ አየችው:: አሁን አሁን
ስታስበው ምነው በጠራሁት ኖሮ!» እያለች ትቆጫለች፡፡ ያን ጊዜ ግን የቅናት ዛር በላይዋ ላይ ሰፍሮ መላቅጧን
ያሳጣት ስለነበር እያመነታች ዝም ብላ ትንሽ ከሄደች በኋላ ድንገት ታክሲውን አስቁማ ወረደች::

ከዚያ በኋላ በርቀት ተከተለችው፡፡ ሄዶ ሄዶ
በቀለ ሞላ ሆቴል ገባ፡፡ ወደኋላ ቀረት ለማለት ሞከረች።አመነታች:: የያዛት የቅናት ዛር ግን ቀላል አልነበረም።
እየገፈተረ ወደ ውስጥ አስገባት:: መናፈሻው በረንዳ ላይ ከምትጠብቀዉ ሴት ጋር ተገናኘ:: ብድግ ብላ
ተቀበለችው:: ሞቅ ባለ ሁኔታ ተጨባብጠው፤ ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙና ስሜት በተሞላበት ሁኔታ የሆነ ነገር ተነጋግረው ተቀመጠ፡፡ ምናልባት ስለዘገየ ይቅርታ እየጠየቃት ሊሆን ይችላል፡፡ ማዕዶት ላይ ተሳፍሮ
ለከረመው የቅናት ዛር ግን እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ምሱ ነበርና ወረደ:: እያስጋለባት ሄደችባቸው።

ሴትዮዋ የመስሪያ ቤቱ ባልደረባ ናት:: ማዕዶትን መጀመሪያ በርቀት ስታያት ከአያልነህ ጋር የመጣች ስለመሰላት ፈገግ አለች:: ቀረብ ስትል ግን ሁኔታዋ
አስደነገጣት:: አያልነህ ድንጋጤና ንዴት ተቀላቅለው ፊቱን ደም አስመሰሉት:: ሆኖም በዚያ ቦታ ላይ ሊደርስበት
የሚችለውን ውርደት ፈርቶ በር ጋታ ተቀበላት፡፡አከታትለም ሴትየዋ ከአለቃዋ ጋር ባለመግባባቷ ምክንያት እየደረሰባት ያለውን ችግር ልትነግረው መሆኑን
ሊተርክላት ሞከረ:: ማ ዕ ዶት ግን መብረ ድም መረጋጋትም አልቻለችም:: ቅናት እያተነነው የሄደው የድሮው ጭምትነቷ ጭራሽ ጠፍቶ የማያውቃት ሴት
ሆናለች::
በዚህ ሁኔታ ላለመቆየት ሴትየዋን አሰናብቶ እሷን ይዟት ወደቤቱ ሄደ:: እንደተጣሉ አመሹ፡፡ ሌሊት ላይ.....

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1👍1
#እንዲሁ_ሲወደድ

እኔ አንቺን ስወድሽ...
አይንሽን ጥርስሽን፤አይደለም አይቼ
በጡት ወይ በዳሌሽ፤አይደለም ጓጉቼ
አይደለም በፀባይ፤ወይም በቁመናሽ
እንዲሁ ወደድኩሽ!
ፈተና አይደለሽም ፤ እኔ አንቺን ማጠናሽ።
መውደዴን ስነግርሽ....
"ምን አይተህ?" አትበይ ፤ ፍቅሬን ለማጓደል
ሳላይ ነው ምወድሽ ፥ ፍቅረሸ እውረሸ አይደል?!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#መቅለጥ_መገፋት

"ቅቤ ተገፍቶ ነው
አናት ላይ የወጣው"
የሚል ቢሂል ይዞ ፤ የሚገፋን በዛ
ከፍታ ነው ካሉን
ካናት ቀልጠን ስንወርድ ፣ ገፊ በኛ ወዛ።
አንዳንዱ እንደዚህ
ራሱን ሊያወዛ ፥ ራሱን ሊኳኩል
አንድ ተረት መዞ ፣ ከአንድ እውነትህ በኩል
ታች ሆኖ ለመውዛት ፣ ይስቅልሃል ከላይ
ተገፍቶ መውጣት ደግ ፣ ቀልጦ መውረድ ስቃይ።
#ማዕዶት


#ክፍል_ሁለት


#በየዝና_ወርቁ

ያመሸበትን ብስጭት ቻል አድርጎ ነገር ሊያበረድ አሰበና ሊያቅፋት እጁን ዘረጋ፣

በዚህ ሁኔታህ በዚ መጥፎ ጊዜ እንዴት ላምንህ እችላለሁ አለች ፤እንዳያቅፉት እጁን እየገፋች።ያመረረች ስላልመሰለው

እንደጠረጠርሺኝ ከሆንኩማ ለአንቺም ከተረፈሽ ቆይቷል ማለት ነው አለ እየሳቀ ከዚያ ሊያቅፋት እንደገና እጁን ዘረጋ ማዕዶት የባሰ እየተናደደች

'አጉል ቀልድ' አለችና ተስፈንጥራ ተነስታ የአልጋውን ልብስና አንዱን ትራስ አንጠልጥላ ሄዳ ሶፈው ላይ ተኛች።የምሯን አልመሰለውም ነበር። የምትመለስ ስለመሰለው ሲጠብቃት እንደቆየ እንቅልፍ ወሰደው ወፍ ሲንጫጫ ተነስታ በበራሪ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰች።

አያልነህ የወደፊቱ ህይወታቸው እንዴት እንደሚቀጥል በጣም አሳሰበው።በዚህ ዓይነት ቢጋቡ ህይወቱ ሰላም እንደሚያጣ ታየው። እና በጋብቻ ከመተሳሰራቸው በፊት ግኑኝነታቸው ቢቋረጥ እንደሚሻል ወሰነ።መአዶት ግን ለመታረቅ ፍቃደኛ አለመሆኗ እርግጠኛ ባትሆንም አያልነህ ሳይደውልላት የሚቀር አልመሰላትምነ ነበር። አለመደወሉ የጠረጠረችው ሁሉ አረጋገጠላት
ምነው ከሱ እንደተለየሁ ወዲያውኑ ጨክኜ በተመረመርኩ፡፡ ቁርጤን አውቄ ህይወቴን አስተካክል ነበር አለች- እንደመባነን እያደረጋት:: ሳታስበው ሃያው
ደቂቃ ነጉዷል:: በእንግዳ ማረፊያው አግዳሚ ወንበሮች ላይ ተኮልኩለው ከነበሩት ብዙ ሰው ሄዷል። እንደገና
ሰዓቱ ሳይታወቃት እንዳያልፍ ሐሳቧን ወረፋ ወደሚጠብቋት ሰዎች መልሳ ፊታቸውን ማጥናት ጀመረች።ብዙዎቹ በአስማት የተያዙ ይመስል ድንዝዝ
ብለው ለየብቻቸው ተቀምጠዋል።

የውጤት መቀበያው ክፍል ተከፈተና ወጣት ወንድና ሴት ፊታቸው በደሰታ በርቶ ወጡ። ደረጃውን እንደወረዱ ሁለቱም ድንገት ተቃቀፉና በደስታ ስሜት
ከንፈር ለከንፈር ተሳሳሙ። እንደገና ተላቀው ዐይን ለዓይን ተያዩና ተቃቀፉ። ከተቀመጡት ሰዎች ከፊሎቹ ነቃ እንደማለት ብለው ደስታቸውን ተጋሩ። አንዳንዶቹም የባሰ ተሳቀቁ። ማዕዶትም ለመጋባት የተመረመሩ መሆናቸውን ገመተችና ራሷን እየወቀሰች ጭብጥ ብላ
ተቀምጣ አስተዋለቻቸው።

ተከትሎ አንድ ውሳኔ ላይ መድረስ እንዳለባት ይሰማት ጀመር።

በዚሁ የተነሳ ባለፈው አመት ከወንዶች እንደምትርቅ አስተውሎ ከቀረባት ሰው ጋር ፍቅር ጀምራ ነበር፡፡ ባህርያቸውን ተጠናንተው ለትዳር እስኪወስኑ
አልፎ አልፎ የገቡበትን ስሜትም ኮንዶምን ተከልለው አሳልፈዋል፡፡ በኋላ ግን ለጋብቻ መተሳሰባቸውን ተከትሉ
በዚህ የተነሳ ባለፈው ዓመት ከወንዶች
ያነሳባትን የእንመርመር ውትወታ መቋቋም ስላቃታት ራቀችው፡፡ እሱም ተመርምሮ በመጋባት አጥብቆ ያምን
ስለነበር ብዙ ጊዜ ሊያሳምናት ሊያደፋፍራት ጣረ።በመጨረሻ እየሸሸችው መሆኗን ሲረዳ ግን የሷን ያህል የተማረ፤ ዘመናዊ ሰው ተመርምሮ ራሱን ለማወቅ የማይደፍርበት ምክንያት ሊገባው አልቻለም።ሰለዚህ ቀደም ብላ ተመርምራ ብታውቅ ነው ብሎ ጠረጠረና
ፈራት። ከዚያም ተዋት።

ብቸኝነት እንደገና ! ዓመት አለፈ...

ማዕዶት ሳይታወቃት ለረዥም ጊዜ ጭብጥ ብላ ተቀምጣ ስለቆየች ሳይሆን አይቀርም ሆዷ ላይ ህመም ተሰማትና ቀና አለች።ከዚያ የተሰማትን ህመም
ለማስታገስ ወደኋላዋ ጋለል ብላ ሆዷን እየዳሰሰች ፍዝዝ ብላ እንደቆየች ሃሳብ ነጥቆ ለማርገዟ ምክንያት ወደሆናትና ማስታወስ ወደማትፈልገው ከሳምሶን ጋር
ወዳሳለፈችው ጊዜ ጭልጥ አርጎ ወሰዳት ...
ከሳምሶን ጋር የተዋወቁት ከሶስት ወራት በፊት ለስብሰባ በአውሮኘላን ወደ ድሬዳዋ ስትሄድ ነበር፡፡ የለበሰው
ሰማያዊ ጅንስ ጃኬትና ሱሪ ሰውነቱ ላይ ልክክ ብሎ ወንዳወንድ ቁመናውን አጉልቶ አውጥቶታል።ቀላል ጓዝ የያዘ የመንገድ ሻንጣውን በትከሻው ላይ አንጠልጥሉ
አነስ ያለ የእንግሊዘኛ መፅሐፍ በእጁ ይዟል፡፡ ንጥረ ንጥር የሚለው አረማመዱ ነጭ እስኒከር ጫማው ውስጥ ስኘሪንግ የተቀበረ አስመስሎታል።ያለ ጉዳይ በሰፊው የመንገደኞች መቆያ ወለል ላይ እየተንሸራሽረ ዐይኖቿን ከሳበው በኋላ በዐይኖቹ ያጫውታት ጀመር፡፡ በመጀመሪያ ላይ “ዐይናውጣ በሚል ተሳዳቢ አስተያየት ገላምጣዋለች::
ዐይኖቿንም ልትነፍገው ሞክራ ነበር፡፡ በኋላ ግን ከዓመት በላይ የወንድ ገላ ነፍጋው የቆየችው ሰውነቷ የመልካም
ቁመናውን ጥሪ የሚቋቋም አልሆነም:: እና የመነሻ ሰዓታቸው ደርሶ ወደ አውሮኘላኑ ሲጓዙ እንደተከተላት
እያወቀች አልራቀችውም:: ተከታትለው ስለገቡ አንድ ላይ ለመቀመጥ አልተቸገሩም:: ገና እንደተቀመጠ
የደህንነት ቀበቶውን እያጠበቀ፣

“ጥሩ ቀን ይመስላል፣ አየሩ ብሩህ ነው” አላት፡ በአዎንታ አረጋገጠችለት:: ከዚያ መፅሃፉን ገለጠና ወደኋላው ለጠጥ ብሎ ማንበብ ጀመረ።
ፀጥ ብሎ ማንበቡን ሲቀጥል ማዕዶት ባልጠበቀችው ድርጊቱ ግራ ተጋብታ የግራ እጁን የቀለበት ጣት መልካት
አደረገች፡፡ ለጌጥ የተደረገ የወርቅ ቀለበት ነው፡፡ የጋብቻ አለመሆኑን አረጋገጠችና ዘና ብላ ተቀመጠች፡፡ በብልጠት
የበለጠችው መሰላት እንጂ እሱም ጣቶቿ ላይ የጋብቻ ቀለበት አለመኖሩን ገና እንግዶች ማረፊያ ወስጥ እያሉ
ነው ያረጋገጠው።

ለአስር ደቂቃ ያህል ከኣሁን አሁን እንደገና
ያናግረኛል ብላ ጠበቀችው መፅሀፉ ላይ አተኩሮ ጭራሽ መኖራንም የረሳ መሰለ፡፡ ተናደደችና ራሷን ከወንበሯ የኋላ መደገፊያ ላይ ጣል አድርጋ ፊቷን በትንሹ ወደሱ አቅጣጫ መለስ አደረገች:: ከዚያ እንቅልፍ እንደያዘው ሰው ዐይኖቿን ጨፈነቻቸው:: ሳምሶን ሁኔታዋ ገባውና
ዘወር ብሎ እያያት፤

ደበርኩሽ አይደል?” አለ፡ ልክ ረዘም ያለ ጊዜ ትውውቅ እንዳላቸው ሁሉ ፈገግ ብሎ:: ጥርሶቹ በንፅህና የተያዙ ናቸው:: ጠቆር ካለው የፊቱ ቆዳና ደፍጠጥ
ብሉ ቀዳዳዎቹ ሰፋ ካሉት አፍንጫው ስር እጅብ ካለው ጢሙ ጋር ህብር ፈጥረዋል:: አነስ ያሉት ዐይኖቹ ንቁ
ናቸው።

ግድየለም አንብብ » አለችው፣ እንቅልፍ
እንደያዘው ሰው ድክምክም ብላ፡፡

“ጥሩ የመንገድ ጓደኛ አይደለህም እያልሽኝ ነው አይደል? አላት መፅሐፍ ባልያዘበት ግራ እጁ ትከሻዋን
መታ አድርጎ እየሳቀ:: ነቃ ብላ እንደ መሳቅ እያለች አየችውና የየሰው ተሰጥኦ ገረማት።የሚያግባባ የሚያላምድ ፊትና ሁኔታ አለው::

"ኖ! ኖ! አንብብ እኔ እተኛለሁ አለችው።
"በአጭር የአውረፕላን ጉዞ ውስጥ ይኄ እንዳልኩት እንዳልኩት ደባሪ እያልሽኝ ነው! »

እንዲህ በክርክር ቢጤ ወሬ ጀመሩና በዚያ ቀጠሉ፡፡ ወደ ድሬዳዋ ለምን እንደምትሄድ ጠየቃት ከፍተኛ ኤክስፐርት መሆኗንና ለስብሰባ እንደምትሄደ
ነግራው የሱን ጠየቀችው:: በመንግስት መስሪያ ቤት ደህና ቦታ ላይ ይሰራ እንደነበርና አሁን ግን የግል ስራ
ለመጀመር ድሬዳዋ ሁኔታዎችን ለማጥናት እየሄደ መሆነን ነገራት፡፡

አውሮኘላኑ ያሬዳዋ አውሮኘላን ማረፊያ ደርሶ ሲለያዩ ፤ አዲስ አበባ ሲመለስ ሊጠያየቁ፡ ተስማምተው በየሞባይል ስልክ ቁጥሮቻቸውን ተለዋወጡ፡፡ በማግስቱ ስብሰባውን ተካፍላ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰች፡፡

ከዚያ በኋላ ማዕዶት ሳምሶን ይደወላል ብላ ስትጠብቅ ሰነበተች።ሳምንት አለፈው፤ አልደወለም፡አስረኛው ቀን ቆጠረች ድምጹን አላሰማትም፡፡
ልትደውልለት ፈለገች:: ጥሩ አልመሰላትም፡፡ ተወችው፡፡በዚህ ሂደት ግን ብዙ አሰበችው:: ባሰበችው ቁጥር ደግሞ አእምሮዋ ውስጥ እየጎላ እየጎላ ቦታ እየያዘ ሄደ::በሶስተኛው ሳምንት ላይ ሳምሶን ደወለ። ጉዳዩ አላልቅ ብሎት ሁለት ጊዜ ድሬዳዋ ደርሶ መመለሱን
ነገራት እያይዞም ራት እስረው እንዲበለ ጋበዛት፡፡

ከስራ በአስራ አንድ ሰዓት ተኩል ስትወጣ መኪና ይዞ በር ላይ ጠበቃት የበዙ ጊዜ ትውውቅ ያላቸው ያህል እየተሳሳቁ ተሳሳሙ፡፡ ደህንነታቸውን በመጠያየቅ
👍3
የጀመሩት ወሬ እንደተነፈሰ የውሃ ግድብ ወለል እያለ ወረደ:: ሰፊና ጨለም ያለ ግቢ ወዳለው ሆቴል ወሰዳት፡፡
መኪናቸው ውስጥ እንደሆኑ ራት አዘዙ:: የሚጠጣ ነገር ጥያቄ ሲቀርብ ፤

ስኘራይት ይሻለኛል አለችው:: ሳቅ አለና፣
ለበላነው ማወራረጃ አምቦ ውሃ እንጠጣ:: ከዚያ በኋላ ግን የፍቅረኞች መጠጥ ማርቲኒ ነው" አላት::
በጣም ዘመናዊ ሰው ነው ብላ አሰበች::

ራታቸውን እያጎረሳት በሉ:: ማርቲኒውን
እየተሳሳሙ መጠጣት ቀጠሉ:: አንድ ከራሷ አንድ ጊዜ ከራሱ ብርጭቆ እያቀናጣ ሲያስጎነጫት ሳታውቀው ብዙ
ጠጣች:: የወንድ ገላ የናፈቀው ገላዋ መጠጡ በፈጠረባት ሞቅታ ታግዞ ለመጋል ጊዜ አልፈጀበትም::

የሚወጡና የሚገቡ መኪናዎች እላያቸው ላይ መብራት እያበሩ ሲያስቸግራቸው ክፍል ውስጥ ገብተው እንደልባቸው ቢሆነ እንደሚሻል ጠየቃት፡፡ ድንገት
ጠረጠረችው።ፈራች። እና

“እኔ ኮ ራሴን አላቀውም ሳሚ” አለችው መሚለማመጥ ቅላፄና በጨዋ ቋንቋ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ምን_አለኝ_ሃገሬ ?

ወፊቷ ካልጮኸች
በወንዜ ዝማሬ
ፊቴን ውርጭ ካስመታው
ከውጪ ማደሬ
ምን አለኝ ...ምን አለኝ
ምን አለኝ ሃገሬ ?

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#ስጋና_እድሜ

ስጋ ከድሜ ጋራ መንታዎች ነበሩ
አንዴ ተወለዱ አንዱ ተፈጠሩ
እድሜ እንዳሻው እልፍ አእላፍ ሲቆጠር
ስጋ ግን ተገታ ማረፊያው ሆነ አፈር፡፡

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#ማዕዶት


#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፋል)


#በየዝና_ወርቁ

“እኔ ኮ ራሴን አላቀውም ሳሚ” አለችው በሚለማመጥ ቅላፄና በጨዋ ቋንቋ፡፡

ምንድን ነው የማታውቂው” ? አላት ግር
እንደመሰኘት ብሎ፡፡
«ኤች.አይ.ቪ ምርመራ ነዋ »አለችው::
«እኔም ወደውጭ አገር ስሄድ ተመርምሬ ነፃ መሆኔን ካወቅሁ ዓመት አልፎኛል፡፡ እንደገና ማድረግ ይኖርብኛል።

ይጠቀማል፡፡ ካልሆነ ግን እንደማዕዶት ዓይነት ያማረ
መልክና ቁመና ያላቸውና ረጋ ያሉ ሴቶችን ሲያገኝ

“ምንድ ነወ

“ታዲያ! አለችው - የምርመራ ነገር ሲነሳ ደፋር ለመምሰል ብትጣጣርም ፍርሃቷ ከውስጧ ማንሰራራት ጀምሯል።

«ታዲያማ ሰው የሚመረመረው፤ አስገዳጅ ሁኔታ ሲያጋጥመው ወይም ደግሞ ሲያገባ ወይም ልጅ ሊወልድ
ሲፈልግ ነው› አላት::
“ካልሆነስ?” አለችው - አንደበቷ እየጐለደፈባት፡፡
“መቼም እንዳንቺ የተማረ ሰው ኮንዶም አላቅም አይለኝም አላት በቀልድ ቃና እየሳቀ….ሳምሶን የሷን አቅጣጫ ተከትሎ ስለ ኮንዶም አወራ እንጂ በመሰረቱ ኮንዶም መጠቀም አይወድም::
አንዳንድ ጊዜ እንዲሁ አይቶ ወይም ሁኔታቸውን ታዝቦ የሚጠራጠራቸው ሴቶች ሊያጋጥሙት ብቻ ሳይወድ ይጠቀማል ካልሆነ ግን እንደ ማእዶት ያማረ መልክና ጠቁመናል ቁመና ያላቸውና ረጋ ያሉ ሴቶችን ሲያገኝ በነሱ በኩል ግፊቱን ካልመጣ እሱ አያስበውም። ስሜቱን
አርክቶ ማገናዘብ ሲጀምር ነው “ጭንቀት የሚሰማው፡፡በሌላ ጊዜ ግን መልሶ ያደርገዋል፡፡
ማዕዶት አነጋገሩን እስተዋለችና ጥሩ ግንዛቤ እንዳለው ገመተች፡፡ ለሷም ቢሆን ጥሩ ነገር እንደሆነ አሰበች፡፡ “ለጊዜው እሱ እንዳለው በኮንዶም እንቆያለን፡፡
ለመጋባት ስንወስን ደግሞ በቃ በመጀመሪያ ሳልነግረው ተደብቄ እመረምራለሁ። ፈጣሪ ረድቶኝ ነፃ ከሆንኩ
አብረን እንመረመራለን፡፡ ቫይረሱ ቢገኝብኝስ ... " ሐሳቧን መጨረስ አቃታት።ሰውነቷ ተንዘፈዘፈ....

መኪናቸው ውስጥ እንዳሉ ቦዩን ጠራውና
መኝታ ክፍል ተከራየ:: ወደዚያው ሲሄዱ
ብርጭቆዎቻቸውንና ጠርሙሱን ቦዩ ይዞ ተከተላቸው፡፡
እንደገቡ ሳምሶን ኮሞዲኖውን ከፈት አድርጎ ኮንዶም ሲያረጋግጥ አየችው:: ተረጋጋች።
ልብሶቻቸውን አውልቀው አልጋው ውስጥ ገቡ:: ትንሽ እንደተሳሳሙ ከኮሞዲኖው ውስጥ አንድ ፖኬት ኮንዶም
አወጣና ከውስጡ አንዱን ነጥሎ ጐረደው:: ቀሪውን ደግሞ ኮሞዲኖው ላይ አስቀመጠው:: ከዚያ ማሽጊያውን
ከፍቶ የውስጡን መዘዘና መብራቱን አጠፋው።

“መብራት አትወድም? አለችው።

“አዎ አላት - ድምጹም ድንገት ስልቱን አጣባት፡፡ስሜት ይዟቸው እልም አለ… በመጨረሻ አንሶላውን ከውስጥ ጎተተና አሸርጦ ወደ መታጠቢያ ቤት ሄደ፡፡
ታጥቦ እንደተመለሰ መለኪያው ውስጥ የነበረው ማርቲኒ በአንድ ትንፋሽ ጨለጠውና ሌላ ቀዳ:: የቀዳውን
ምንም ሳያናግራት ጨለጠው።

ግራ ተጋብታ አየችው:: ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ብሩህ ፈገግታ የነበረው ፊቱ ዳምኗል፡፡እንደገና ሲቀዳ
ፈራችውና ፤

“እንሂድ እየመሸ ነው አለች

አትጠውጪም? አላት- ስልቱን ባጣ ድምጽ፡፡

«በቃኝ» አለች - ለመልበስ እየተነሳች:: ለባበሱ ወጥተው ወደ ሳምሶን መኪና ሄዱ::
በቀጠሉት ሶስት ሳምንታት ሶስት ጊዜ ተገናኝተን ተመሳሳይ ሁኔታ አሳልፈዋል:: ማዕዶት ከድሮው ባህሪዋ በተለየ ሁኔታ ከሱ ጋር ስትሆን ሞቅ እስኪላት መጠጣት መጀመሯ ታውቋታል። ግን እያቀበጠ ስለሚያጠጣ ደስ ይላታል፡፡ እንደ ህፃን ስሜቱን መደበቅ የማይችል
መሆኑን እያስተዋለችም አብረውት ለመኖር የማይከብድ ዓይነት ሆኖባት ለማይቀረው የእንመርመር ጥያቄ
እንዲያበረታት ፈጣሪዋን እየተማፀነች ለጋብቻ ተመኝተዋለች

ድንገት ግን ያልጠበቀችው ነገር ተከሰተ፡፡ የወር አበባዋ በቀኑ ሳይመጣ ቀረ፡፡ ግራ ቢገባት መምጫ ቀኑን ኣዛብቶ የማያውቀውን የወር አበባዋን ሳምንት ሙሉ በተስፋ ጠበቀችው።መቅረቱን ስታረጋግጥ ብርክ ያዛት።

በስሜት ውስጥ ሆነን ሳናውቀውየተፈጠረ ስህተት ይኖር ይሆን?! ይኼ አደጋ ነው! ወይ በኔ ወይ
በሱ ላይ የመጣ እያለች አንጎራጎረች :: ልጁንም' ኮ ላይቀበለኝ ፣ ላያምነኝ ይችላል» ብላ አሰበችና ልትነግረው
ፈራች፡፡ እየቆየች ስታስበው ስታብላላው ግን ከመንገር ሌላ አማራጭ አጣችለት:: ሁለታችንም ሳናስበው የወደቅንበት አደጋ ላይ መወያየትና መፍትሄ መፈለግ
አለብን " አለች - ልትነግረው ወሰነችና ደውላ ለማታ ፕሮግራም አስያዘችው።

እንደሌለቹ ቀናት የመዝናናት ስሜት
አልነበራትም ራት መብላት አቅቷት መጠጣትም አስጠልቷት ስለነበር አሞኛል ብላ ዋሸችው:: ከዚያም
ብዙ ሳይቆዩ መብራቱን አጠፋው:: እሱ ስሜት ውስጥ ገብቷል፡፡ እሷግን ሀሳቧ ግራ በገባት ነገር እየተሰረቀ
አስቸግራት በስሜት ልትከተለው አልቻለችም፡፡ እና እሱን ለማስደሰት ብቻ እንደሚፈልገው እየሆነችለት ሳለ
መሀከል ላይ የተለየ ነገር ተሰማት:: ድንገት ጠረጠረችው።ድንጋጤ አስፈንጥራት ተነሳችና መብራቱን ቦግ አድርጋ አበራችው::ሳምሶን ኮንዶሙን በእጁ እንዳንጠለጠለው
ክው ብሎ ቀረ:: ማዕዶትም አንገቱን አንቃ ተንቀጠቀጠች። ከዚያ አንገቱን ለቃ ተስፋ በቆረጠ መንፈስ ፍራሹን እየደበደበችና፤
“አንተ አውሬ ነህ! ጭራቅ ነህ! ተኩሰህ እንደገደልከኝ ቁጣረው..... ምነው? ምን በደልኩህ?...” እያለች ትራሱ ላይ ተደፍታ ተንሰቀሰቀች፡፡ ሳምሶን ድንጋጤው መለስ
ሲልለት ፤

ምን እንዲህ ያደርግሻል? አንቺ ብቻ ነሽ ለህይወትሽ የምታስቢ? እኔ ከማንም ጋር የምጋደም መሰለሽ? ሰው መርጫ ነው" አለ በላይ ሆኖ እንደመቆጣት' እያደረገው
ከአፈርኩ አይመልሰኝ ዓይነት።

“የጅል ወግህን ተወውና ይኼንን ተንኮል የፈፀምክብኝ እውነት ተመርምረህ ቫይረሱ እንዳለብህ ሳታውቅ ከሆነ
ነገ እንመርመር " አለችው - እልህ እያንቀጠቀጣት፡፡

ሳምሶን ትኩር አድርጎ አያትና፤

“ይቻላል አለ - ትከሻዎቹን ከፍ አድርጎ ቁልቁል እየለቀቃቸው:: ዐይኖቹ ውስጥ ግን ፍርሃት በጉልህ ነግሶ ታየ።
እንደተኮራረፉ ልብሶቻቸውን ለብሰው ወጡ፡፡

በማግስቱ ለመመርመር ከተቃጠሩበት አሁን ውጤቷን እየጠበቀችበት ካለው ክሊኒክ ከሰዓቱ ቀድማ ደረሰች፡፡ ለዘመናት የራቀ የመሰላትን ያህል ጊዜ ጠብቃው ሲቀርባት በሞባይል ስልኳ ሞባይል ስልኩ ላይ ደወለችለት። ዘጋባት:: ሰዓቱ ሶስት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ግማሽ ሰዓት አሳልፏል:: ትንሽ ቆየችና ሞክረች። መልሶ ዘጋባት፡፡ ብርክ እንደያዛት ተስፋ ቆርጣ በየመንገዱ እንባዋን ለመዋጥ እየታገለች በኮንትራት ታክሲ ወደቤቷ ሄደች መሥሪያ ቤቷ ደውላ መታመሟን ለአለቃዋ አሳውቀችና ተኛች፡፡ ከሰዓት በኋላ ለሳምሶን በሱቅ ስልክ ደወለችለት
አነሳውና እሷ መሆኗን ሲያውቅ ዘጋባት፡፡
ደጋግማ ሞከረች፡፡ ሊያናግራት ፈቃደኛ አልሆነም…

ማዕዶት የተፈጠረውን ነገር እንደክፉ ቅዥት ስትባንን ለቀናት አሰበችው::
ሳምሶንን ለማግኘት የምታደርገው ጥረትም ጥቅም የሌለው ሆነባት፡፡ ከዚህ ወዲያ ባገኘውስ ምን ያደርግልኛ
ል? ጠላቴን የልጄ አባት አድርጌ አልቀበለው አለችናእርግፍ አድርጋ ተወችው::
እያደር ግን ለራሷ ከመጨነቅ አልፋ በማህፀኗ ውስጥ ስላለው ልጅ ማሰብ ጀመረችና ትናንት ደሟን ለምርመራ ሰጠች….
ማዕዶት የሰመጠችበትን የትዝታ ባህር ዋኝታ ስትጨርስ ያው የተጠናወታት ቫይረሱ ቢገኝብኝስ የሚለው ጭንቀት በውስጧ እያንሰራራ ነበር ። እና
የኤች አይ ቪ ቫይረስ ሰውነቷን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ሲበላው ቤተሰቦቿ እንኳ ሊያስታምሟት ሲሳቀቁ ፣ከወዳጅ ዘመዶቿ መሀል ተነጥላ ብቻዋን ስትንጠራወዝ ታያት፡፡ በውስጧ የጭንቀት ትኩሳት ተሰራጨ፡፡
ጨምድዶ። ከያዛት ጭንቀት ለመውጣት እያባ ት : ንቀት እየተወራጨች ! 'ቢኖርብኝም ቫይረስ ላለባቸው
2👍1
የሚረዳ የእድሜ ማራዘሚያ መድሃኒት አገራችን ገብቷል ይባላል ለምን ያህል ጊዜ እንደሚያቆየኝ ባላውቅም፡፡ ደግሞም ከእውነታ ጋር መኖር ይቻል ይመስለኛ ል።እንዲያወም ባላወቀው ነበር የምጎዳወ ! ! አለች
ከሚያንገላታት ጭፍን ፍርሃት ለመወጣት
ከተቀመጠችበት ተነስታ እየተንጎራደደች

ለጥቂት ጊዜ ወደላይና ወደ ታች ስትንጎራደድ እንደቆየች የወረፋ ቁጥራ ተጠራ:: በድንጋጤ ውሃ ሆነቾ ዐይኖቿ ስለጨለመባት ወንበሩ ላይ ተመልሳ
ቁጭ አለች። ወዲያዉ ግን ሚዛኗን ለመጠበቅ እየተጠነቀቀች ወደተጠራችበት ክፍል ገባች፡፡
የምክር አገልግሎት የምትሰጠው ነርስ በፈገግታ ተቀበለቻት:: ማዕዶት ጭንቀቷ እንዳይታወቅባት የተረጋጋች ለመምሰል እየሞከረች ለሰላምታ ያህል እጅ
ነስታ ወንበሩ ላይ ተቀመጠች።

ነርሷ ፤ ማዕዶት ደም ከመስጠቷ በፊት ከሞላችው ፎርም ላይ የትምህርት ደረጃዋንና ራሷን ለማወቅ ብቻ
ለመመርመር መፈለጓን አንብባ ስለነበር፡

“ጎበዝ! ! አለች-አተካራ እያስተዋለቻት::
አያይዛም “አንድ ሰው ተማረ የሚባለው የነገሮችን ትክክለኛ ገፅታ ለማወቅና ለማገናዘብ ሲጥር ነው፡፡ በጭፍኑ ፣ በስሜቱ ብቻ እየተመራ የሚጓዝ ከሆነ መማሩ ዋጋ የለውም አለቻት መንፈስን በሚያረጋጋ ፈገግታዋ ግርማ ሞገስ ተላብሳ፡ የማዕዶት ልብ ግን ምቱን ጨምሯል በጣም የሚያሳዝንሽ ነገር አብዛኞቹ በክፍተኛ የትምህርት ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎችም እንኳ አንድ አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ካልገቡ በስተቀር ራሳቸውን
ለማወቅና ለማዘጋጀት ብለው አይመረመሩም:: ነርሷ በሚያቀራርብ እንደበት የሚሰማትን ትገልፅላት ቀጠለች:: ማእዶት ግን ትዕግስት አጣች፡፡ የነርሷ ሁኔታ እሷን ለመርዶ የማዘጋጀት ዓይነት ሆነባት:: እና፤

«ሲስተር ሰመጀመሪያ ውጤቴን ልወቀው እለች ረጋ ለማለት የሞከረችው ሁሉ እየከዳት፡፡ ጭንቀቷፊቷ ላይ ወለል ብሎ
ይታያል፡፡ ነርሷ የለመደችው ሁኔታ ስለነበር ፈገግ አለችና ፤

ቫይረሱ በደምሽ ውስጥ አልተገኘም አለች፡፡

ማዕዶት በህልም ዓለም ውስጥ ያለች መሰላት።እና አንደበቷ ታስሮ የባሰውኑ ሃውልት መሰለች።የዓመታት ጭንቀቷ ..

ነርሷ የማዕዶትን ሁኔታ እያስተዋለች ፤

“ይኼ ግን ምን ማለት እንደሆነ መቼም
«ከቫይረሱ ነፃ ነሽ አይደል ያልሽኝ? አለች
ታውቂያለሽ፤- አለች እውነት እየተጠራጠረች።
«ቫይረሱ ዊንዶ ፔሬድ ወይም የመደበቂያ ጊዜ አለሁ፡፡ ስለዚህ በምርመራ ውጤት የሚገለፀው ከሶስት ወር በፊት ያለው ሁኔታ ነው፡፡ ከሶስት ወር ወዲህ
የምትጠራጠሪው ለቫይረሰ የሚያጋልጥ ሁኔታ ካለ ወር በኋላ እንደገና ተመርምረሽ ታረጋግጪያለሽ፡፡ ለወደፊቱም ቢሆን ከምታገቢው ሰው
ጋር እንድ ላይ በግንባር ቀርበሽ ነው ውጤታችሁን መስማት ያለብሽ:: የሀሰት ማስረጃዎች መኖራቸው ተደርሶበታል አለቻት። ፈገግታዋና ግርማ ሞገሷ ፊቷ
ላይ ወለል እንዳለ ነው።

ማዕዶት ግን ደስታም ቁጭትም ተደባልቀው ስሜቷን አሳክሩትና እስከመጨረሻው አላዳመጠቻትም፡፡

ጭንቀት- እንደገና!

💫አለቀ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#እናት

ድህነቱ ይዞኝ
ችግሩ በዝቶብኝ
የማስበው ሳጣ ርሃብ ጠንቶብኝ
ዘመድ ጓደኞቼ ሁሉም ርቀውኝ
ሞትን ስሻት ላልኖር ካልጋዬ ተኝቼ
አለው ከማልለው የቁም ሞቴን ሞቼ
ድንገት ከሞት ነቃሁ የእናት ድምጽ ሰምቼ
በችግር ሃዘኔ ሁለተኛ ሟቼ
ስትለኝ ተሰማኝ “የነገ ተስፋዬ
ሀገር ተረካቢ የደስታ ጓዳዬ
የመኖሬ ትርጉም ብቸኛ አላማዬ”
እኔም ተፈወስኩ አስተዋሽ በማግኘቴ
የሞቴ ተጋሪ የኔ ማንነቴ
ሆና ያሳደገችኝ
እናትና አባቴ
የኔ አባባዋ
የኔዋ እናቴ።

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#ድሮና_ዘንድሮ

#ድሮ

ረጋ ባለችው በህይወት መስላል
ገሚሱ ይወጣል ገሚሱ ይወርዳል
#ዘንድሮ

ጥሉ ማለፍ ሆኖ
የኑሮ ልማድ
ከፍ ከፍ እያለ
አንደኛው ሲሄድ
ከፊቱ ሲቀጥል
ከኋላው ሲንድ
የሱ ደቀ - መዝሙር
ስለሚያጣ ምርጫ
ተንሳፎ ይነጉዳል
በነፋስ አቅጣጫ፡፡

🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
“አጋው ነህ ወይስ ሺናሻ
ቅማንቴ ነህ ወይ ፈላሻ
ስምህ የሆነብን ግርሻ
ግራ ጎንደር ነህ መተከል
ባላዋቂ የምላስ ቅርስ ' የዘር ንፍገት ስትቀበል '
ያለ ዕዳህ ስምህ ሲበከል
እምትችል እማትበቀል ፡ እማትሞት እማትነቀል...”
ከ “ይድረስ ለወንድሜ ለማላውቅህ?

🔘ጸጋዬ ገብረ መድኅን🔘

ከእሳት ወይ አበባ