"12 የሆነው በምክንያት ነው"
# ቅዱሳን መላእክትን መታሰቢያቸውን መዘከራችን -በምክንያት
ነው
#ቅዱስ ሚካኤልን ማክበራችንም - በምክንያት ነው
#ቅዱስ ሚካኤል ዓይኑ ዘርግብ መባሉም - በምክንያት ነው
#ቅዱስ ሚካኤል እርዳን ማለታችን - በምክንያት ነው
# ቅዱስ ሚካኤል በ12 ማክበራችን - በምክንያት ነው
#ቅዱሳን መላእክትን መታሰቢያቸውን መዘከራችን -በምክንያት ነው...... በመጽሐፈ መሳፍንት የሶምሶን እናትና አባት መልአኩ ተገልጦ ልጅን እንደሚወልዱና እርሱም ናዝራዊ እንደሆነ በነገራቸው ጊዜ የሶምሶን አባት ማኑሄ ለመልአኩ " ማኑሄም የእግዚአብሔርን መልአክ ነገርህ በደረሰ ጊዜ መታሰቢያህን እንድናደርግ ስምህ
ማን ነው? አለው" (መጽሐፈ መሳፍንት 13:17) መልአኩም ስሜ ድንቅ
ነው ብሎታል፡፡ እንኳን በሐዲስ ኪዳን በብሉይ እንኳን መላእክት መታሰቢያቸው ይከበራል፡፡
*እስራኤላውያን ከቀሳፊው መልአክ የተረፋበትን ቀን " ይህም ቀን መታሰቢያ ይሁናችሁ፥ ለእግዚአብሔርም በዓል ታደርጉታላችሁ፤ለልጅ ልጃችሁ ሥርዓት ሆኖ ለዘላለም ታደርጉታላችሁ"(ኦ.ዘጸ
12:14) እስራኤላውያን ከቀሳፊው መልአክ የተረፋባትን ቀን
ካከበሩ እኛማ ቅ/አፎምያ በቅ/ሚካኤል መትረፏን ብናከብር እኛም የቅ/
ሚካኤንም ውለታ እንዴት አናከብር !! ጠቢቡም " የጻድቅ መታሰቢያ
ለበረከት ነው፤ የኅጥኣን ስም ግን ይጠፋል። ምሳሌ 10:7)
እውነት ነው የቅ/ሚካኤል መታሰቢያ ለበረከት ነው፡፡
#ቅዱስ ሚካኤል ዓይኑ ዘርግብ መባሉም - በምክንያት ነው
*ለቅ/ሚካኤል የሰውና እንስሳ ዓይነት ዓይን ኖሮት "ዓይኑ ዘርግብ "
የተባለ አይደለም፡፡ይልቁንም የሰው ዓይን የሚያየው ነጩ ያይደለ
ጥቁሩ (ብሌን) ነው፡፡ ርግብ ግን ዓይኗ የሚያየው ነጩም ጥቁሩም
ነው፡ እንዲሁ ቅ/ሚካኤል ሆይ አንተም ያለፈውንም የሚመጣውንም
ማየት ይቻልሀል (በጸጋ ተሰጥቶሀል) ስንል ነው፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ መልአኩ ነጫጭ ልብስ
የለበሱት ማናቸው ባለው ጊዜ ዮሐንስ ሲመልስ " እኔም ጌታ ሆይ፥ አንተ
ታውቃለህ አልሁት አለኝም እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ"ዮሐንስ ራእይ 7:14)
#ቅዱስ ሚካኤል በ12 ማክበራችን - በምክንያት ነው
*ቅ/ገብርኤል በ19 መታሰቡ በምክንያት እንደሆነው የቅ/ሚካኤልም
በ12 መሆኑ በምክንያት ነው፡፡ የቅ/ገብርኤል " መልአኩም መልሶ።
እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም
ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር "የሉቃስ ወንጌል
1:19 ........ ቁጥር "19" ይህ በምክንያት ነው፡፡ የቅ/ሚካኤል
" በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ
ሚካኤል ይነሣል " ትንቢተ ዳንኤል 12:1 ..... ምዕራፍ "12" ይህም በምክንያት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ቀን
መታሰቢያውን እናደርጋለን ስሙንም ከፍከፍ እናደርጋለን ! ቅዱስ ሚካኤል
ያማልደን ዘንድ እንማጸነዋለን .... ምን ማማለድ ብቻ መልአክ አይደል
ደስ ያለውንም ያደርግልናል "እርሱም እኔን ባሪያህን ለጌታዬ ለንጉሡ አማ፤ አንተ ጌታዬ ንጉሥ ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ ነህ፤
ደስም ያሰኘህን አድርግ " (መጽ.ሳሙ 19:27)
#ቅዱስ ሚካኤል ረዳትነቱንም ስንመሰክር በምክንያት ነው "
ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም" (ት.ዳን 10:21) .......እናም ከቅዱስ ሚካኤል በረከቱን ያድለን፡፡
(ኢዮብ ዘገነተ ጽጌ ሰኔ 12/2012)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
# ቅዱሳን መላእክትን መታሰቢያቸውን መዘከራችን -በምክንያት
ነው
#ቅዱስ ሚካኤልን ማክበራችንም - በምክንያት ነው
#ቅዱስ ሚካኤል ዓይኑ ዘርግብ መባሉም - በምክንያት ነው
#ቅዱስ ሚካኤል እርዳን ማለታችን - በምክንያት ነው
# ቅዱስ ሚካኤል በ12 ማክበራችን - በምክንያት ነው
#ቅዱሳን መላእክትን መታሰቢያቸውን መዘከራችን -በምክንያት ነው...... በመጽሐፈ መሳፍንት የሶምሶን እናትና አባት መልአኩ ተገልጦ ልጅን እንደሚወልዱና እርሱም ናዝራዊ እንደሆነ በነገራቸው ጊዜ የሶምሶን አባት ማኑሄ ለመልአኩ " ማኑሄም የእግዚአብሔርን መልአክ ነገርህ በደረሰ ጊዜ መታሰቢያህን እንድናደርግ ስምህ
ማን ነው? አለው" (መጽሐፈ መሳፍንት 13:17) መልአኩም ስሜ ድንቅ
ነው ብሎታል፡፡ እንኳን በሐዲስ ኪዳን በብሉይ እንኳን መላእክት መታሰቢያቸው ይከበራል፡፡
*እስራኤላውያን ከቀሳፊው መልአክ የተረፋበትን ቀን " ይህም ቀን መታሰቢያ ይሁናችሁ፥ ለእግዚአብሔርም በዓል ታደርጉታላችሁ፤ለልጅ ልጃችሁ ሥርዓት ሆኖ ለዘላለም ታደርጉታላችሁ"(ኦ.ዘጸ
12:14) እስራኤላውያን ከቀሳፊው መልአክ የተረፋባትን ቀን
ካከበሩ እኛማ ቅ/አፎምያ በቅ/ሚካኤል መትረፏን ብናከብር እኛም የቅ/
ሚካኤንም ውለታ እንዴት አናከብር !! ጠቢቡም " የጻድቅ መታሰቢያ
ለበረከት ነው፤ የኅጥኣን ስም ግን ይጠፋል። ምሳሌ 10:7)
እውነት ነው የቅ/ሚካኤል መታሰቢያ ለበረከት ነው፡፡
#ቅዱስ ሚካኤል ዓይኑ ዘርግብ መባሉም - በምክንያት ነው
*ለቅ/ሚካኤል የሰውና እንስሳ ዓይነት ዓይን ኖሮት "ዓይኑ ዘርግብ "
የተባለ አይደለም፡፡ይልቁንም የሰው ዓይን የሚያየው ነጩ ያይደለ
ጥቁሩ (ብሌን) ነው፡፡ ርግብ ግን ዓይኗ የሚያየው ነጩም ጥቁሩም
ነው፡ እንዲሁ ቅ/ሚካኤል ሆይ አንተም ያለፈውንም የሚመጣውንም
ማየት ይቻልሀል (በጸጋ ተሰጥቶሀል) ስንል ነው፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ መልአኩ ነጫጭ ልብስ
የለበሱት ማናቸው ባለው ጊዜ ዮሐንስ ሲመልስ " እኔም ጌታ ሆይ፥ አንተ
ታውቃለህ አልሁት አለኝም እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ"ዮሐንስ ራእይ 7:14)
#ቅዱስ ሚካኤል በ12 ማክበራችን - በምክንያት ነው
*ቅ/ገብርኤል በ19 መታሰቡ በምክንያት እንደሆነው የቅ/ሚካኤልም
በ12 መሆኑ በምክንያት ነው፡፡ የቅ/ገብርኤል " መልአኩም መልሶ።
እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም
ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር "የሉቃስ ወንጌል
1:19 ........ ቁጥር "19" ይህ በምክንያት ነው፡፡ የቅ/ሚካኤል
" በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ
ሚካኤል ይነሣል " ትንቢተ ዳንኤል 12:1 ..... ምዕራፍ "12" ይህም በምክንያት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በዚህች ቀን
መታሰቢያውን እናደርጋለን ስሙንም ከፍከፍ እናደርጋለን ! ቅዱስ ሚካኤል
ያማልደን ዘንድ እንማጸነዋለን .... ምን ማማለድ ብቻ መልአክ አይደል
ደስ ያለውንም ያደርግልናል "እርሱም እኔን ባሪያህን ለጌታዬ ለንጉሡ አማ፤ አንተ ጌታዬ ንጉሥ ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ ነህ፤
ደስም ያሰኘህን አድርግ " (መጽ.ሳሙ 19:27)
#ቅዱስ ሚካኤል ረዳትነቱንም ስንመሰክር በምክንያት ነው "
ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም" (ት.ዳን 10:21) .......እናም ከቅዱስ ሚካኤል በረከቱን ያድለን፡፡
(ኢዮብ ዘገነተ ጽጌ ሰኔ 12/2012)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ቅዱስ ትውፊት
#ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ሐዋርያት
✞ ቅዱስ ትውፊትን በዘመነ ሐዲስ ስንመለከትም፥ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሦስት ዓመት በላይ ሕዝቡን ደቀ መዛሙርቱን የነበረው በጹሑፍ አልነበረም ቅዱሳን ሐዋርያትም ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበሉት በወረቀት የተጻፈ ነገር አልነበረም ወንጌላውያን ከጌታ በቃል ተምረው በተግባር አይተው ኃላ የሚጽፉትን እየዞሩ አስተማሩ እንጂ አስቀድመው ጽፈው ጠቅሰው አላስተማሩም መጻሕፍት መጻፍ የጀመሩት፥ ቤተ ክርስቲያን በይፋ ከተመሰረተች ከ8 ዓመታት በኃላ ነው (ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት መጀመሪያ የተጻፈው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ሲሆን ይኸውም በ41 ዓ/ም ላይ ነው) እስከዚህ ጊዜ ድረስ ቤተ ክርስቲያን ስትመራ የነበረው በቃልና በተግባራዊ ምልልስ ሲተላለፍ በነበረው ቅዱስ ትውፊት ነው በሌላ አገላለጽ ወንጌል ከመጻፉ በፊት፥ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን በቅዱስ ትውፊት ታውቃለች ወንጌልን ስትኖረው ነበረች
✞ ከጌታችን ጋር ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከዋለበት እየዋሉ፣ ካደረበት እያደሩ ሲየያስተምር፣ ሲጸልይ፣ ሰዎችን ሲያጽናና፣ ድውያነ ስጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስንም በትምህርት ሲፈውስ፣ ሙታነ ሥጋንና ሙታነ ነፍስን ሕይወት ሲሰጣቸው ዐይተዋል፤ ሰምተዋል ሥርዓተ ብሉይን አሳልፎ ሥርዓተ ሐዲስን ሲሠራ ተመልክተዋል ነገር ግን ይህን ሁሉ በትውፊት ለተላውያነ ሐዋርያት (Apostolik Fathers- ተላውያነ ሐዋርያት የሚባሉት ከሐዋርያት በቀጥታ የተማሩ ክርስቲያኖች ናቸው) አስረከቡት እንጂ፥ እነርሱ ራሳቸው እንደነገሩን ሁሉንም አልጻፉልንም የጻፉልን እጅግ ጥቂቱን ብቻ ነው /ዮሐ 21፥25/ ስለዚህ ቅዱስ ትውፊት እያልነን ያለነው፥ እንዲህ አይነቱን በገቢርና በቃል ዕለት ዕለት በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ሕይወት የሚገለጠውና አንድ ጊዜ ለቅዱሳን የተሰጠውን ሃይማኖት ነው /ይሁዳ 3/
✞ ቅዱስ ትውፊት ዋና ማዕከሉ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በሌላ አገላለጽ ቅዱስ ትውፊት ወንጌል ነው በዘመነ ብሉይ ቢነገር ይወርዳል ይወለዳል ብሎ ነው፤ በዘመነ ሐዲስ ቢነገር ደግሞ ወረደ ተወለደ ብሎ የምስራችን ለትውልድ ሁሉ በቃልም፣ በገቢርም፣ በጹሑፍም የሚያውጅ ነው፤ ቅዱስ ትውፊት "ወንድሞች ሆይ! የሰበክኁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባቹሀለው በከንቱ ካላመናችው በቀር ብታምኑስ በምን ቃል እንደ ሰበክኁላችው አሳስባችኃለው እኔ ደግሞ የተቀበልኩትን ከሁሉ በፊት ሰጠኃችው" እንዲል /1ኛ ቆሮ 15፥1/
# ትውፊትና እድገት
☞ ብዙ ሰዎች ሁልጊዜ የቀደሙትን ከተመለከትን እድገታችንና የትውልዱ የፈጠራ ችሎታ ይቋረጣል ብለው ይሰጋሉ ነገር ግን ትውፊት እድገትን አይገድብም፤ እንዲያውም እድገቱ የተስተካከለ እንዲሆን ያደርጋል
✞ ማደግ ማለት የራስን ትቶ የሌላውን ብቻ መቀበል አይደለም የራስ የሆነውን በአግባቡ መጠቀም ማለት ነው እንጂ እድገታችን እንጀራን አጥፍቶ ፓስታ ብቻ ለምን አንበላም?፣ የሐበሻ ቀሚስን አሣድደን ለምን እርቃንን የሚያጋልጠውን አንለብስም?፣ የዘመን አቆጣጠራችን ይቅርና በአውሮፓ ቀመር ይተካ፣ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ተጥሎ የነሞዛርት ቅኝት ይምጣልን አይነት ከሆነ ጉዟችን ወደ እድገት ሳይሆን አንገትን ቆርጦ ለፀጉር አበጣጠር የመጨነቅ ያህል ነው የራሳችን የሆነውን ወደን አክብረን የበለጠ የሚያድግበትን መንገድ ከሆነ ያ እድገት ተብሎ ሊጠራ ይችላል የሰጎን እንቁላል ስለጠፋ ጉልላት ይቅር አይባልም ሰጎን እናርባ ይባላል እንጂ፤ ካህን ስላጠረን ምእመኑ ይቀድስ አይባልም ልጆቻችንን እናስተምራቸውና ካህን እናድርጋቸው፣ ሹመት እናሰጣቸው ይባላል እንጂ አለም እኮ የሚጓዘው በአንድ አቅጣጫ ብቻ አይደለም በተቃራኒውም ሊያመራ ይችላል የወንጀል አሰራር፣ የውንብድና ኑሮ እየረቀቀና በቴክኖሎጂ እየተደገፈ በመጣ ቁጥር እድገት ብለን ከቆጠርን ተሳስተናል
✞ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ አበው የቀደምት አበው የቤተ ክርስቲያን አሠራር፣ የአምልኮ ስርአቱ፣ ልብሰ ተክህኖውን፣ ጽንአውን፣ ዕጣኑን፣ መንበሩን ወዘተ ከጥንቷ ቤተ መቅደስ ለቤተ ክርስቲያን እንደሚገባ አድርገው ተረከቡት እንጂ በዘመኑ ሰልጥኖ የነበረውን የግሪካዊ- ሮማ ፍልስፍና አልጨመሩበትም ይህም የሆነው ስልጣኔው፣ ፍልስፍናው፣ እውቀቱ ሳይገባቸው ቀርቶ ሳይሆን የዚህ ስጋዊ ፍልስፍና ውጤቱ እግዚአብሔርን መካድ፣ ስጋዊ ፍላጎትን ማርካት፣ ምድራዊ ድሎትን ማደላደል መሆኑን ስለተገነዘቡ ነው ለምሳሌ፦
☞ ሰዓሊያን ስዕለ ቅዱሳንን ሲስሉ ቤተ ክርስቲያን በቃልና በጹሑፍ ያቆየችውን መሠረት አድርገው ገለጡት እንጂ የራሳቸውን አመለካከትና ፍላጎት ተጠቅመው ትውፊትን በመሻር ልቦለድ ስዕል አላቀረቡም
# ቅዱስ_ትውፊት_ቅዱስ_ካልሆነው_ትውፊት_እንዴት_ይታወቃል?
✞ በቤተ ክርስቲያን ያለው ሁሉም በትውፊት የተገኘ ላይሆን ይችላል እያንዳንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው ነገርም የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪ መንፈስ ቅዱስ የሰጣት ነው ማለት አይደለም አንዳንድ ሰዋዊ ነገሮችን ልናገኝ እንችላለን ነገር ግን እነዚህ የሰው የሆኑ ነገሮች በራሳቸው ኃጢአት ወይም ስህተት ላይሆኑ ይችላሉ ይሉቁንም ለዋናው የቤተ ክርሱቲያኒቱ ቅዱስ ትውፊት ማቀላጠፊያ ወይም ማስተላለፊያ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ ለምሳሌ፦ ድምጽ ማጉያ፣ መቅረጸ ድምጽ፣ ሲዲ፣ ዲቪዲ፣ እና የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል ስለዚህ ዋናውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ትውፊትና ጊዜአዊው ማቀላጠፊያን ለይተን ልናውቅ ይገባናል
✞ ቤተ ክርስቲያን ማለት የክርስቲያኖች ጉባኤ እንደመሆኗ መጠን፥ እነዚህ ክርስቲያኖችም በተለያየ ግብረ ዓለም ሊያዙ ስለሚችሉ ይህን የዓለም ስራ ይዘው ቢመጡና ግብራቸውን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢያሰርፁ፥ ይህ ክፉ ግብር እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ሊቆጠር አይገባውም በመሆኑም ለቅዱስ ትውፊት ቀኖናዊ መመዘኛ እንዳለው ተረድተን ቅዱሱን ትውፊትና ቅዱስ ያልሆነውን ትውፊት ለይተን ልናውቅ ይገባናል /2ኛ ተሰ 2፥15/ ትውፊት ሁሉ ከሐዋርያት ተያይዞ የመጣና ሐዋርያዊ ቤተ ክርስቲያናዊ ይዘት ያለው መሆን አለበት፤ ከጥንት ጀምሮ በየትም ቦታ፥ ሁል ጊዜ በዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን የታመነ የተጠበቀና በተግባር ላይ የዋለ መሆን አለበት፤ በዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ መለወጥና መቋረጥ ያልተገባው መሆን አለበት
✞ እንደ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምሮ ሃይማኖት የሚቀበሉት ተቀብለውም የሚኖሩት ለቀጣዩ ትውልድም ሳያፋልሱ የሚያስተላልፉት እንጂ በየጊዜው የሚጨመርበት ወይም የሚቀነስበት አይደለም በፕሮቴስታንቱ አለም ደግሞ ከካቶሊካውያኑ ፍጹም ተቃራኒ በመሆን ቅዱስ ትውፊትን አንቀበልም ይላሉ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻውን በቂ እንደሆነ ያስተምራሉ ነገር ግን ይህም ቢሆን ፍፁም የተሳሳተ ትምህርት ነው አንድ ቀላል ምሳሌ እናንሳና ትምህርታቸው ምን ያህል ስህተት እንደሆነ እናሳይ
☞ እሑድን እንደ ጌታ ቀን አድርገው ያከብራሉ በብሉይ ኪዳን እንዲከበር የታዘዘው ግን ቅዳሜ ነው /ዘፀ 20፥8/ ቅዳሜን ትተው እሑድን ማክበር ከየት አገኙት? ዳግመኛም የጌታችንን ልደት፣ ጥምቀት፣ ትንሳኤ እንዲሁም በዓለ ኃምሳ አብረውን ያከብራሉ ነገር ግን ይህን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምንም አይገኝም ሌላ ጥያቄም እንጨምር ወደ ዓለም ሁሉ የተሰማሩት ሐዋርያት 12 መሆናቸውን ወንጌል ይነግረናል ነገር ግን ሁሉም ጹሑፍ አልጻፉም አላስተማሩም ማለት ግን አይደለም ታዲያ ትምህርታቸው የት አለ? ትምህርታቸውን የምናገኘው
#ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ሐዋርያት
✞ ቅዱስ ትውፊትን በዘመነ ሐዲስ ስንመለከትም፥ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሦስት ዓመት በላይ ሕዝቡን ደቀ መዛሙርቱን የነበረው በጹሑፍ አልነበረም ቅዱሳን ሐዋርያትም ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበሉት በወረቀት የተጻፈ ነገር አልነበረም ወንጌላውያን ከጌታ በቃል ተምረው በተግባር አይተው ኃላ የሚጽፉትን እየዞሩ አስተማሩ እንጂ አስቀድመው ጽፈው ጠቅሰው አላስተማሩም መጻሕፍት መጻፍ የጀመሩት፥ ቤተ ክርስቲያን በይፋ ከተመሰረተች ከ8 ዓመታት በኃላ ነው (ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት መጀመሪያ የተጻፈው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ሲሆን ይኸውም በ41 ዓ/ም ላይ ነው) እስከዚህ ጊዜ ድረስ ቤተ ክርስቲያን ስትመራ የነበረው በቃልና በተግባራዊ ምልልስ ሲተላለፍ በነበረው ቅዱስ ትውፊት ነው በሌላ አገላለጽ ወንጌል ከመጻፉ በፊት፥ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን በቅዱስ ትውፊት ታውቃለች ወንጌልን ስትኖረው ነበረች
✞ ከጌታችን ጋር ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከዋለበት እየዋሉ፣ ካደረበት እያደሩ ሲየያስተምር፣ ሲጸልይ፣ ሰዎችን ሲያጽናና፣ ድውያነ ስጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስንም በትምህርት ሲፈውስ፣ ሙታነ ሥጋንና ሙታነ ነፍስን ሕይወት ሲሰጣቸው ዐይተዋል፤ ሰምተዋል ሥርዓተ ብሉይን አሳልፎ ሥርዓተ ሐዲስን ሲሠራ ተመልክተዋል ነገር ግን ይህን ሁሉ በትውፊት ለተላውያነ ሐዋርያት (Apostolik Fathers- ተላውያነ ሐዋርያት የሚባሉት ከሐዋርያት በቀጥታ የተማሩ ክርስቲያኖች ናቸው) አስረከቡት እንጂ፥ እነርሱ ራሳቸው እንደነገሩን ሁሉንም አልጻፉልንም የጻፉልን እጅግ ጥቂቱን ብቻ ነው /ዮሐ 21፥25/ ስለዚህ ቅዱስ ትውፊት እያልነን ያለነው፥ እንዲህ አይነቱን በገቢርና በቃል ዕለት ዕለት በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ሕይወት የሚገለጠውና አንድ ጊዜ ለቅዱሳን የተሰጠውን ሃይማኖት ነው /ይሁዳ 3/
✞ ቅዱስ ትውፊት ዋና ማዕከሉ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በሌላ አገላለጽ ቅዱስ ትውፊት ወንጌል ነው በዘመነ ብሉይ ቢነገር ይወርዳል ይወለዳል ብሎ ነው፤ በዘመነ ሐዲስ ቢነገር ደግሞ ወረደ ተወለደ ብሎ የምስራችን ለትውልድ ሁሉ በቃልም፣ በገቢርም፣ በጹሑፍም የሚያውጅ ነው፤ ቅዱስ ትውፊት "ወንድሞች ሆይ! የሰበክኁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባቹሀለው በከንቱ ካላመናችው በቀር ብታምኑስ በምን ቃል እንደ ሰበክኁላችው አሳስባችኃለው እኔ ደግሞ የተቀበልኩትን ከሁሉ በፊት ሰጠኃችው" እንዲል /1ኛ ቆሮ 15፥1/
# ትውፊትና እድገት
☞ ብዙ ሰዎች ሁልጊዜ የቀደሙትን ከተመለከትን እድገታችንና የትውልዱ የፈጠራ ችሎታ ይቋረጣል ብለው ይሰጋሉ ነገር ግን ትውፊት እድገትን አይገድብም፤ እንዲያውም እድገቱ የተስተካከለ እንዲሆን ያደርጋል
✞ ማደግ ማለት የራስን ትቶ የሌላውን ብቻ መቀበል አይደለም የራስ የሆነውን በአግባቡ መጠቀም ማለት ነው እንጂ እድገታችን እንጀራን አጥፍቶ ፓስታ ብቻ ለምን አንበላም?፣ የሐበሻ ቀሚስን አሣድደን ለምን እርቃንን የሚያጋልጠውን አንለብስም?፣ የዘመን አቆጣጠራችን ይቅርና በአውሮፓ ቀመር ይተካ፣ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ተጥሎ የነሞዛርት ቅኝት ይምጣልን አይነት ከሆነ ጉዟችን ወደ እድገት ሳይሆን አንገትን ቆርጦ ለፀጉር አበጣጠር የመጨነቅ ያህል ነው የራሳችን የሆነውን ወደን አክብረን የበለጠ የሚያድግበትን መንገድ ከሆነ ያ እድገት ተብሎ ሊጠራ ይችላል የሰጎን እንቁላል ስለጠፋ ጉልላት ይቅር አይባልም ሰጎን እናርባ ይባላል እንጂ፤ ካህን ስላጠረን ምእመኑ ይቀድስ አይባልም ልጆቻችንን እናስተምራቸውና ካህን እናድርጋቸው፣ ሹመት እናሰጣቸው ይባላል እንጂ አለም እኮ የሚጓዘው በአንድ አቅጣጫ ብቻ አይደለም በተቃራኒውም ሊያመራ ይችላል የወንጀል አሰራር፣ የውንብድና ኑሮ እየረቀቀና በቴክኖሎጂ እየተደገፈ በመጣ ቁጥር እድገት ብለን ከቆጠርን ተሳስተናል
✞ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ አበው የቀደምት አበው የቤተ ክርስቲያን አሠራር፣ የአምልኮ ስርአቱ፣ ልብሰ ተክህኖውን፣ ጽንአውን፣ ዕጣኑን፣ መንበሩን ወዘተ ከጥንቷ ቤተ መቅደስ ለቤተ ክርስቲያን እንደሚገባ አድርገው ተረከቡት እንጂ በዘመኑ ሰልጥኖ የነበረውን የግሪካዊ- ሮማ ፍልስፍና አልጨመሩበትም ይህም የሆነው ስልጣኔው፣ ፍልስፍናው፣ እውቀቱ ሳይገባቸው ቀርቶ ሳይሆን የዚህ ስጋዊ ፍልስፍና ውጤቱ እግዚአብሔርን መካድ፣ ስጋዊ ፍላጎትን ማርካት፣ ምድራዊ ድሎትን ማደላደል መሆኑን ስለተገነዘቡ ነው ለምሳሌ፦
☞ ሰዓሊያን ስዕለ ቅዱሳንን ሲስሉ ቤተ ክርስቲያን በቃልና በጹሑፍ ያቆየችውን መሠረት አድርገው ገለጡት እንጂ የራሳቸውን አመለካከትና ፍላጎት ተጠቅመው ትውፊትን በመሻር ልቦለድ ስዕል አላቀረቡም
# ቅዱስ_ትውፊት_ቅዱስ_ካልሆነው_ትውፊት_እንዴት_ይታወቃል?
✞ በቤተ ክርስቲያን ያለው ሁሉም በትውፊት የተገኘ ላይሆን ይችላል እያንዳንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው ነገርም የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪ መንፈስ ቅዱስ የሰጣት ነው ማለት አይደለም አንዳንድ ሰዋዊ ነገሮችን ልናገኝ እንችላለን ነገር ግን እነዚህ የሰው የሆኑ ነገሮች በራሳቸው ኃጢአት ወይም ስህተት ላይሆኑ ይችላሉ ይሉቁንም ለዋናው የቤተ ክርሱቲያኒቱ ቅዱስ ትውፊት ማቀላጠፊያ ወይም ማስተላለፊያ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ ለምሳሌ፦ ድምጽ ማጉያ፣ መቅረጸ ድምጽ፣ ሲዲ፣ ዲቪዲ፣ እና የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል ስለዚህ ዋናውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ትውፊትና ጊዜአዊው ማቀላጠፊያን ለይተን ልናውቅ ይገባናል
✞ ቤተ ክርስቲያን ማለት የክርስቲያኖች ጉባኤ እንደመሆኗ መጠን፥ እነዚህ ክርስቲያኖችም በተለያየ ግብረ ዓለም ሊያዙ ስለሚችሉ ይህን የዓለም ስራ ይዘው ቢመጡና ግብራቸውን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢያሰርፁ፥ ይህ ክፉ ግብር እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ሊቆጠር አይገባውም በመሆኑም ለቅዱስ ትውፊት ቀኖናዊ መመዘኛ እንዳለው ተረድተን ቅዱሱን ትውፊትና ቅዱስ ያልሆነውን ትውፊት ለይተን ልናውቅ ይገባናል /2ኛ ተሰ 2፥15/ ትውፊት ሁሉ ከሐዋርያት ተያይዞ የመጣና ሐዋርያዊ ቤተ ክርስቲያናዊ ይዘት ያለው መሆን አለበት፤ ከጥንት ጀምሮ በየትም ቦታ፥ ሁል ጊዜ በዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን የታመነ የተጠበቀና በተግባር ላይ የዋለ መሆን አለበት፤ በዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ መለወጥና መቋረጥ ያልተገባው መሆን አለበት
✞ እንደ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምሮ ሃይማኖት የሚቀበሉት ተቀብለውም የሚኖሩት ለቀጣዩ ትውልድም ሳያፋልሱ የሚያስተላልፉት እንጂ በየጊዜው የሚጨመርበት ወይም የሚቀነስበት አይደለም በፕሮቴስታንቱ አለም ደግሞ ከካቶሊካውያኑ ፍጹም ተቃራኒ በመሆን ቅዱስ ትውፊትን አንቀበልም ይላሉ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻውን በቂ እንደሆነ ያስተምራሉ ነገር ግን ይህም ቢሆን ፍፁም የተሳሳተ ትምህርት ነው አንድ ቀላል ምሳሌ እናንሳና ትምህርታቸው ምን ያህል ስህተት እንደሆነ እናሳይ
☞ እሑድን እንደ ጌታ ቀን አድርገው ያከብራሉ በብሉይ ኪዳን እንዲከበር የታዘዘው ግን ቅዳሜ ነው /ዘፀ 20፥8/ ቅዳሜን ትተው እሑድን ማክበር ከየት አገኙት? ዳግመኛም የጌታችንን ልደት፣ ጥምቀት፣ ትንሳኤ እንዲሁም በዓለ ኃምሳ አብረውን ያከብራሉ ነገር ግን ይህን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምንም አይገኝም ሌላ ጥያቄም እንጨምር ወደ ዓለም ሁሉ የተሰማሩት ሐዋርያት 12 መሆናቸውን ወንጌል ይነግረናል ነገር ግን ሁሉም ጹሑፍ አልጻፉም አላስተማሩም ማለት ግን አይደለም ታዲያ ትምህርታቸው የት አለ? ትምህርታቸውን የምናገኘው