‹‹ ገንዘብን በከንቱ አትበትን ገንዘብን በቃኝ አልቸገርም አትበል›› (ሲራክ 5፡1፡ 11፡24)
@And_Haymanot
መጽሐፈ ሲራክ ትክክለኛነት ከመሰሎቹ መጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊያን ጋር ሲፈተሸ
የተሃድሶ መናፍቃን ሰማንያ አሃዱ መፅሐፋችንን የተሳሳተ አድርገው ከሚያቀርቡት የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል አንዱ መፅሑፈ ሲራክ ላይ የተጠቀሰውን ቃል በመጥቀስ ነው
ገንዘብን በከንቱ አትበትን ገንዘብን በቃኝ አልቸገርም አትበል....
በከንቱ የሚለው ለማይጠቅም ነገር ለምሳሌ ለስካር ለዘፈን ለኃጢአት አትበትን አታባክን ነው፡፡ ባለፈው የሠራሁትና ያገኘሁት ገንዘብ ይበቃኛል አልቸገርም ብለህ ገንዘብ አላቂ ስለሆነ አልሥራም አትበል ነው፡፡ (መዝ61፡10)፡፤ ገንዘብን ለሚበትኑ ሲናገር ‹‹ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ ከዚያም እያባከነ ገንዘቡን በተነ›› (ሉቃ15፡13)
ይልና ለሚጠቅም ለምጽዋት ደግ ‹‹በተነ ለችግረኞችም ሰጠ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል (መዝ111 (112))9) ይላል፡፡
ለመመጽወትም ሆነ ለሕይወታችን ሠርተን ባለጠጋ መሆንን አንከላከልም ‹‹ የታካች እጅ ችግረኛ ታደርጋለች የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች›› (ምሳ 10፡4) ይህን አምላክ ፈቅዶታል ‹‹
እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ ባለጠግነትንና ሀብትን መስጠቱ ከእርስዋም ይበላና
እድል ፈንታውን ይወስድ ዘንድ በድካሙም ደስ ይለው ዘንድ ማሠልጠኑ ይህ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡ (መክብብ 5፡19) ስለዚህ ሰው ሰርቶ
በደከመበት ሲያከማች እንጂ ቶሎ ለመበልጸግ በሙስና ከሆነ ‹‹ በችኮላ የምትከማች ሀብት ትጎላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች
(ምሳሌ 13፡11) ይላል፡፡ ሀብት እንድናከማች ተነግሯል (ዘዳ 8፡18) ወላጆችም ለልጆች ገንዘብን
በቃኝ ሳይሉ ማከማቸት አለባቸው ‹‹ ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ ሊያገማቹ አይገባቸውም፡፡ (2ኛ ቆሮ 12፡14) ነገር ግን ባከማቹት ሀብት ሊመኩ አይገባም፡፡ ገንዘቡ አንዳይገዛቸው ይጠንቀቁ ‹‹ ጥበብን አግኝ ከሀብትህም ሁሉ ማስተዋልን አትርፍ›› (ምሳ 4፡7)
እንዳለ #ሀብታቸውን_ወደ_ማምለክ_መቀየር_የለበትም፡፡ እየመጸወቱ ወዳጅ ሊያፈሩበት (ሉቃ 16፡9)፤ ሰው
ሲቸገር በቃኝ ሳይሉ በሠሩበት ገንዘብ ሊረዱበት ‹‹የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆንን የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት
ይኖራል›› (1ኛ ዮሐ 3፡17) እንዳለ ገንዘብ ያለው ለሌለው ሊደርስለት በቃኝ ብሎ ያቆመውማ ከየት አምጥቶ ይረዳል ሥራ ሳላቆም ያለውም ያልቀብኛል
ብሎ ስስታም ይሆናልና፣ አንድም አያስፈልገኝም ሳይል ይሥራ ሲል ነው፡፡
‹‹ ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም እንኳ አያስፈልገኝም ሳይል ይሥራ ሲል ነው፡፡ ‹‹ ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ ጎስቋላና ምስኪንም ድሀም እውርም የተራቆትህም መሆንህን ስማታውቅ›› (ራዕይ 3፡17) የሚላቸው ገንዘብን በቃኝ ብለው ባላቸው ብቻ የተኩራሩትን መሆኑን ተገንዝበን ዋናው ‹‹አካሄዳችን ገንዘብ ያለመውደድ ይሁን›› (ዕብራ 13፡5) እንጂ መጽ. ሲራክ ላይ ያለው ቃል ባለፈው ባገኘነው በቃኝ ሳንል ሰርተን ሀብትን ማከማቸት እንደሚገባ የሚናገር ነው፡፡ ለዚህ መጽሀፍ ቅዱስን እርስ በርሱ ለማጋጨት መሞከር ለጥፋት ስለሚሆን፣ ንሰሐ ገብታችሁ ወደ ኦርቶዶክሳዊት (ቀጥተኛዋ) እምነታችሁ ተመለሱ፡፡ ‹‹ ኢትሰቄቀ ለነዋየ አመፃ እስመ አይከል አድኀኖተካ አመ ምንዳቤከ (ለኃላፊ ገንዘብ አትሳሳ በመከራህ ጊዜ አያድንህምና) (ሲራክ 5፡8) የአመጻ ገንዘብ የሚባለው አራጣ በማበደር በቅድሚያ የሚመጣ በማታለል ያገኘኸው ለጌታ ባለመታዘዝ
በአመፃ ያገኘኸው ነውና ለኃላፊ ገንዘብ
አትሳሳ አያድንህም ነው፡፡ (መጽሐፍተ ሰሎሞን ወሲራክ ንባቡና ትርጓሜው 1988) ‹‹ አትስረቅ›› ዘዳ 20፡15) ከሚለው ጋር አንድ ነው፡፡
ይህን ሕግ በዐመፃ ገንዘብ የምትሰበስበው ይጠቅመኛል ያድነኛል ብለህ እየሳሳህ አታስቀምጥ፡፡ የዐመፃን ገንዘብ እየሰበሰብክ ከምታስቀምጥ ሳትሳሳ ስጥና ንሰሐ ገብተህ ይህን ግብር ትተል ለድሃ በመስጠት ኃጢአትህን አስቀር ሲል ነው (ዳን 4፡27 ሉቃ 18፡22) ለጥፋት የተዘጋጁ አሕዛብ በአንድ ወቅት ሐረግ እየመዘዙ መጽሐፍ ቅዱስን እርስ በርሱ ለማጋጨት መሞከራቸው የቅርብ ቀን ትውስታ ነው፡፡ አሁን ደግሞ 66ቱን መጽሐፍ ቅዱስ እንቀበላለን 81ዱን አንቀበልም የሚሉ ደግሞ ለማጋጨት መነሣታቸው በግብር መመሳሰላቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ የሚጋጭ የሚመስል ዐረፍተ ነገር በ66ቱም መጽሐፍ
ውስጥም አለ፡፡ ‹‹ የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኸል›› (ያዕ 5፡4)
‹‹ በአራጣ ብዛትና በቅሚያ ሀብቱን የሚያበዛ ለድሃ ለሚራራ ያከማችለታል›› (ምሳሌ 28፡8) አትስረቅ ከሚለው ጋር ይጣላል ብንል ጤነኛ አስተሳሰብ ይሆናልን?
አይሆንም፡፡
#ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት
👇👇👇
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~Share~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~JoIN~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
@And_Haymanot
መጽሐፈ ሲራክ ትክክለኛነት ከመሰሎቹ መጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊያን ጋር ሲፈተሸ
የተሃድሶ መናፍቃን ሰማንያ አሃዱ መፅሐፋችንን የተሳሳተ አድርገው ከሚያቀርቡት የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል አንዱ መፅሑፈ ሲራክ ላይ የተጠቀሰውን ቃል በመጥቀስ ነው
ገንዘብን በከንቱ አትበትን ገንዘብን በቃኝ አልቸገርም አትበል....
በከንቱ የሚለው ለማይጠቅም ነገር ለምሳሌ ለስካር ለዘፈን ለኃጢአት አትበትን አታባክን ነው፡፡ ባለፈው የሠራሁትና ያገኘሁት ገንዘብ ይበቃኛል አልቸገርም ብለህ ገንዘብ አላቂ ስለሆነ አልሥራም አትበል ነው፡፡ (መዝ61፡10)፡፤ ገንዘብን ለሚበትኑ ሲናገር ‹‹ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ ከዚያም እያባከነ ገንዘቡን በተነ›› (ሉቃ15፡13)
ይልና ለሚጠቅም ለምጽዋት ደግ ‹‹በተነ ለችግረኞችም ሰጠ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል (መዝ111 (112))9) ይላል፡፡
ለመመጽወትም ሆነ ለሕይወታችን ሠርተን ባለጠጋ መሆንን አንከላከልም ‹‹ የታካች እጅ ችግረኛ ታደርጋለች የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች›› (ምሳ 10፡4) ይህን አምላክ ፈቅዶታል ‹‹
እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ ባለጠግነትንና ሀብትን መስጠቱ ከእርስዋም ይበላና
እድል ፈንታውን ይወስድ ዘንድ በድካሙም ደስ ይለው ዘንድ ማሠልጠኑ ይህ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡ (መክብብ 5፡19) ስለዚህ ሰው ሰርቶ
በደከመበት ሲያከማች እንጂ ቶሎ ለመበልጸግ በሙስና ከሆነ ‹‹ በችኮላ የምትከማች ሀብት ትጎላለች ጥቂት በጥቂት የተከማቸች ግን ትበዛለች
(ምሳሌ 13፡11) ይላል፡፡ ሀብት እንድናከማች ተነግሯል (ዘዳ 8፡18) ወላጆችም ለልጆች ገንዘብን
በቃኝ ሳይሉ ማከማቸት አለባቸው ‹‹ ወላጆች ለልጆች እንጂ ልጆች ለወላጆች ገንዘብ ሊያገማቹ አይገባቸውም፡፡ (2ኛ ቆሮ 12፡14) ነገር ግን ባከማቹት ሀብት ሊመኩ አይገባም፡፡ ገንዘቡ አንዳይገዛቸው ይጠንቀቁ ‹‹ ጥበብን አግኝ ከሀብትህም ሁሉ ማስተዋልን አትርፍ›› (ምሳ 4፡7)
እንዳለ #ሀብታቸውን_ወደ_ማምለክ_መቀየር_የለበትም፡፡ እየመጸወቱ ወዳጅ ሊያፈሩበት (ሉቃ 16፡9)፤ ሰው
ሲቸገር በቃኝ ሳይሉ በሠሩበት ገንዘብ ሊረዱበት ‹‹የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆንን የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት
ይኖራል›› (1ኛ ዮሐ 3፡17) እንዳለ ገንዘብ ያለው ለሌለው ሊደርስለት በቃኝ ብሎ ያቆመውማ ከየት አምጥቶ ይረዳል ሥራ ሳላቆም ያለውም ያልቀብኛል
ብሎ ስስታም ይሆናልና፣ አንድም አያስፈልገኝም ሳይል ይሥራ ሲል ነው፡፡
‹‹ ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም እንኳ አያስፈልገኝም ሳይል ይሥራ ሲል ነው፡፡ ‹‹ ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ ጎስቋላና ምስኪንም ድሀም እውርም የተራቆትህም መሆንህን ስማታውቅ›› (ራዕይ 3፡17) የሚላቸው ገንዘብን በቃኝ ብለው ባላቸው ብቻ የተኩራሩትን መሆኑን ተገንዝበን ዋናው ‹‹አካሄዳችን ገንዘብ ያለመውደድ ይሁን›› (ዕብራ 13፡5) እንጂ መጽ. ሲራክ ላይ ያለው ቃል ባለፈው ባገኘነው በቃኝ ሳንል ሰርተን ሀብትን ማከማቸት እንደሚገባ የሚናገር ነው፡፡ ለዚህ መጽሀፍ ቅዱስን እርስ በርሱ ለማጋጨት መሞከር ለጥፋት ስለሚሆን፣ ንሰሐ ገብታችሁ ወደ ኦርቶዶክሳዊት (ቀጥተኛዋ) እምነታችሁ ተመለሱ፡፡ ‹‹ ኢትሰቄቀ ለነዋየ አመፃ እስመ አይከል አድኀኖተካ አመ ምንዳቤከ (ለኃላፊ ገንዘብ አትሳሳ በመከራህ ጊዜ አያድንህምና) (ሲራክ 5፡8) የአመጻ ገንዘብ የሚባለው አራጣ በማበደር በቅድሚያ የሚመጣ በማታለል ያገኘኸው ለጌታ ባለመታዘዝ
በአመፃ ያገኘኸው ነውና ለኃላፊ ገንዘብ
አትሳሳ አያድንህም ነው፡፡ (መጽሐፍተ ሰሎሞን ወሲራክ ንባቡና ትርጓሜው 1988) ‹‹ አትስረቅ›› ዘዳ 20፡15) ከሚለው ጋር አንድ ነው፡፡
ይህን ሕግ በዐመፃ ገንዘብ የምትሰበስበው ይጠቅመኛል ያድነኛል ብለህ እየሳሳህ አታስቀምጥ፡፡ የዐመፃን ገንዘብ እየሰበሰብክ ከምታስቀምጥ ሳትሳሳ ስጥና ንሰሐ ገብተህ ይህን ግብር ትተል ለድሃ በመስጠት ኃጢአትህን አስቀር ሲል ነው (ዳን 4፡27 ሉቃ 18፡22) ለጥፋት የተዘጋጁ አሕዛብ በአንድ ወቅት ሐረግ እየመዘዙ መጽሐፍ ቅዱስን እርስ በርሱ ለማጋጨት መሞከራቸው የቅርብ ቀን ትውስታ ነው፡፡ አሁን ደግሞ 66ቱን መጽሐፍ ቅዱስ እንቀበላለን 81ዱን አንቀበልም የሚሉ ደግሞ ለማጋጨት መነሣታቸው በግብር መመሳሰላቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ የሚጋጭ የሚመስል ዐረፍተ ነገር በ66ቱም መጽሐፍ
ውስጥም አለ፡፡ ‹‹ የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኸል›› (ያዕ 5፡4)
‹‹ በአራጣ ብዛትና በቅሚያ ሀብቱን የሚያበዛ ለድሃ ለሚራራ ያከማችለታል›› (ምሳሌ 28፡8) አትስረቅ ከሚለው ጋር ይጣላል ብንል ጤነኛ አስተሳሰብ ይሆናልን?
አይሆንም፡፡
#ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት
👇👇👇
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~Share~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~JoIN~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡