ማንንም አባት አትበሉ´´
በምድር ላይ ማንንም አባት አትበሉ እንዲሁም ማንንም ሊቃውንት አትበሉ ብሎ ጌታ ተናግሯል ለምንድነው ኦርቶዶክሶች “አባቶች” እያላቹ የምትናገሩት ?
መልስ፡- ተቃዋሚዎች የሚያነሱት ጥቅስ በማቴዎስ 23፡9 ላይ ሲሆን
“አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም። አባት ብላችሁ አትጥሩ።” ይላል፡፡ ይህን ጥቅስ ከመጀመሪያው ቁጥር ጀምሮ ልብ ብለን ካነበብነው ክርስቶስ እየተናገረ ያለው
ስለ ፈሪሳውያን ነው፡፡”ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ። “ ማቴ 23፡2-3 ዋናው ጌታችን ሲያስተምር የነበረው አላማ “
እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ።” የሚለውን ነው፡፡ ምክንያቱም ፈሪሳውያን ከተግባር ይልቅ እይታን የሚወዱ እና ከፍ ብልው መታየትን የሚመርጡ አንጂ ሐይማኖትን
ከምግባር ጋር የያዙ ስላልነበሩ ነው፡፡ ክርስቶስም “አባት”.”ሊቃውንት” ብላቹ አትጠሩ ማለቱ እንደ ፈሪሳውያን ለእይታ ከሆነ እና ያለስራ ከሆነ “አባት “ ተብሎ መጠራቱ ይቅርባቹ ብሎ ሲያስተምረን ነው፡፡ ግን ቃሉን ቀጥታ ወስደን ከተረጎምነው እና በምድር ላይ ማንንም አባት ብለን መጥራት የለብንም ካልን የስጋ አባታችንንም “አባት” ብለን መጥራት ልናቆም ነው አንዲሁም ቅዱስ ጳውሎስ በተለያዩ ምዕራፎች ላይ “አባት” እያለ ቅዱሳንን መጥራቱ ስህተት ነው ወደሚል ድምዳሜ ያደርሰናል፡፡ይህ ደግሞ መንፈስ ቅዱስም በእነ ቅዱስ
ጳውሎስ ላይ አድሮ “አባት” ብለው እንዲጽፉ ማድረጉ ስህተት ነው ልንል ነው፡(ሎቱ ስብሐት) ቅዱስ ጳውሎስ ሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ በጣም ብዙ ጊዜ አባቶች እያሉ ጠቅሰዋል።
ለምሳሌ፡- ገላ.1፡14 ''ለአባቶችም ወግ ከመጠን ይልቅ እየቀናሁ...''
ሮሜ 9፡5 ''አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤ ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥...''(እዚህ ላይ እንግዲህ አባቶች የተባሉት እነዳዊት ናቸው)፣ ሮሜ 15፡8 ''ለአባቶች የተሰጠውን የተስፋ ቃል ያጸና
ዘንድ ደግሞም...''ዕብ 7፡4 ''የአባቶች አለቃ አብርሃም ከዘረፋው...''2ኛ ጴጥ 3፡4 ''አባቶች ከሞቱባት ጊዜ፥ ከፍጥረት
መጀመሪያ....'' ፡፡ የወንጌል ሰባኪዎች አባቶች ይባላሉ!1ኛ ቆሮንጦስ 4:15" እንደምወዳቹ 'ልጆቼ'አድርጌ ልገስፃቹ እንጂ ላሳፍራቹ ይህን አልፅፍም በክርስቶስ አእላፍ ሞግዚቶች ቢኖሯቹም ብዙ አባቶች የላቹም እኔ በክርስቶስ ኢየሱስ ወንጌል 'ወልጃችኃለውና..." እንግዲህ ወንድማችን, ቅዱስ ጳውሎስ
በወንጌል ወልጃችኋለው ልጆቼ ናችሁ እያለን እኛ አባታችን ነህ ብለን ብንጠራው ምንድነው ችግሩ? ምንም ችግር የለውም ምክንያቱም ቅዱስ ጳውሎስ ከሱ በፊት የነበሩትን የእምነት
ሰዎች “አባት” ብሎ እንደጠራ እኛ ደገሞ ዛሬ እሱን እና የሱን ፈለግ የተከተሉ እውነተኛ የእምነት አባቶች “አባት” ብለን
እንጠራለን! ስለዚህ የወለደ አባት ይባላል ...በወንጌል የወለደኑንም አባት ይባላሉ! አባት መባል ብቻ ያይደለ እጥፍ
ክብር ይገባቸዋል “በመልካም የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች፥
ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።” ( 1ኛጢሞ5:17 ) ስለዚህ ሊቃውንት ብለን እንደ ክብራቸው እጥፍ ድርብ ክብር እንሰጣቸዋለን! መጽሐፍን
እንዳነበብን ቀጥታ የምንተረጉም ከሆነ እውቀታችን ከአህዘብ አይሻልም! አህዛብ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ በሉቃስ 18፡ 19 ላይ “ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር
በቀር ቸር ማንም የለም።” ብሎ ተናግሯል ብለው ጌታ ስለ ትህትና እና ስጋ ስለመልበሱ የተናገረውን ቃል ቀጥታ ወስደው ክርስቶስ ቸር አይደለም እንደሚሉ እኛም ጥቅሶችን ብቻ ይዘን
ያለ ትርጓሜ የምንጓዝ ከሆነ ክርስትናችንን ጥያቄ ውስጥ ያስገባል፡፡ መጽሀፍም “ፊደል ይገድላል “ ማለቱ ለዚህ ነው!
(source:- Matiwos amare)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
በምድር ላይ ማንንም አባት አትበሉ እንዲሁም ማንንም ሊቃውንት አትበሉ ብሎ ጌታ ተናግሯል ለምንድነው ኦርቶዶክሶች “አባቶች” እያላቹ የምትናገሩት ?
መልስ፡- ተቃዋሚዎች የሚያነሱት ጥቅስ በማቴዎስ 23፡9 ላይ ሲሆን
“አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም። አባት ብላችሁ አትጥሩ።” ይላል፡፡ ይህን ጥቅስ ከመጀመሪያው ቁጥር ጀምሮ ልብ ብለን ካነበብነው ክርስቶስ እየተናገረ ያለው
ስለ ፈሪሳውያን ነው፡፡”ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ። “ ማቴ 23፡2-3 ዋናው ጌታችን ሲያስተምር የነበረው አላማ “
እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ።” የሚለውን ነው፡፡ ምክንያቱም ፈሪሳውያን ከተግባር ይልቅ እይታን የሚወዱ እና ከፍ ብልው መታየትን የሚመርጡ አንጂ ሐይማኖትን
ከምግባር ጋር የያዙ ስላልነበሩ ነው፡፡ ክርስቶስም “አባት”.”ሊቃውንት” ብላቹ አትጠሩ ማለቱ እንደ ፈሪሳውያን ለእይታ ከሆነ እና ያለስራ ከሆነ “አባት “ ተብሎ መጠራቱ ይቅርባቹ ብሎ ሲያስተምረን ነው፡፡ ግን ቃሉን ቀጥታ ወስደን ከተረጎምነው እና በምድር ላይ ማንንም አባት ብለን መጥራት የለብንም ካልን የስጋ አባታችንንም “አባት” ብለን መጥራት ልናቆም ነው አንዲሁም ቅዱስ ጳውሎስ በተለያዩ ምዕራፎች ላይ “አባት” እያለ ቅዱሳንን መጥራቱ ስህተት ነው ወደሚል ድምዳሜ ያደርሰናል፡፡ይህ ደግሞ መንፈስ ቅዱስም በእነ ቅዱስ
ጳውሎስ ላይ አድሮ “አባት” ብለው እንዲጽፉ ማድረጉ ስህተት ነው ልንል ነው፡(ሎቱ ስብሐት) ቅዱስ ጳውሎስ ሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ በጣም ብዙ ጊዜ አባቶች እያሉ ጠቅሰዋል።
ለምሳሌ፡- ገላ.1፡14 ''ለአባቶችም ወግ ከመጠን ይልቅ እየቀናሁ...''
ሮሜ 9፡5 ''አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤ ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥...''(እዚህ ላይ እንግዲህ አባቶች የተባሉት እነዳዊት ናቸው)፣ ሮሜ 15፡8 ''ለአባቶች የተሰጠውን የተስፋ ቃል ያጸና
ዘንድ ደግሞም...''ዕብ 7፡4 ''የአባቶች አለቃ አብርሃም ከዘረፋው...''2ኛ ጴጥ 3፡4 ''አባቶች ከሞቱባት ጊዜ፥ ከፍጥረት
መጀመሪያ....'' ፡፡ የወንጌል ሰባኪዎች አባቶች ይባላሉ!1ኛ ቆሮንጦስ 4:15" እንደምወዳቹ 'ልጆቼ'አድርጌ ልገስፃቹ እንጂ ላሳፍራቹ ይህን አልፅፍም በክርስቶስ አእላፍ ሞግዚቶች ቢኖሯቹም ብዙ አባቶች የላቹም እኔ በክርስቶስ ኢየሱስ ወንጌል 'ወልጃችኃለውና..." እንግዲህ ወንድማችን, ቅዱስ ጳውሎስ
በወንጌል ወልጃችኋለው ልጆቼ ናችሁ እያለን እኛ አባታችን ነህ ብለን ብንጠራው ምንድነው ችግሩ? ምንም ችግር የለውም ምክንያቱም ቅዱስ ጳውሎስ ከሱ በፊት የነበሩትን የእምነት
ሰዎች “አባት” ብሎ እንደጠራ እኛ ደገሞ ዛሬ እሱን እና የሱን ፈለግ የተከተሉ እውነተኛ የእምነት አባቶች “አባት” ብለን
እንጠራለን! ስለዚህ የወለደ አባት ይባላል ...በወንጌል የወለደኑንም አባት ይባላሉ! አባት መባል ብቻ ያይደለ እጥፍ
ክብር ይገባቸዋል “በመልካም የሚያስተዳድሩ ሽማግሌዎች፥
ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙት፥ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።” ( 1ኛጢሞ5:17 ) ስለዚህ ሊቃውንት ብለን እንደ ክብራቸው እጥፍ ድርብ ክብር እንሰጣቸዋለን! መጽሐፍን
እንዳነበብን ቀጥታ የምንተረጉም ከሆነ እውቀታችን ከአህዘብ አይሻልም! አህዛብ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ በሉቃስ 18፡ 19 ላይ “ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር
በቀር ቸር ማንም የለም።” ብሎ ተናግሯል ብለው ጌታ ስለ ትህትና እና ስጋ ስለመልበሱ የተናገረውን ቃል ቀጥታ ወስደው ክርስቶስ ቸር አይደለም እንደሚሉ እኛም ጥቅሶችን ብቻ ይዘን
ያለ ትርጓሜ የምንጓዝ ከሆነ ክርስትናችንን ጥያቄ ውስጥ ያስገባል፡፡ መጽሀፍም “ፊደል ይገድላል “ ማለቱ ለዚህ ነው!
(source:- Matiwos amare)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መላእክት ተጋብተው ኖሩ....?
@And_Haymanot
እውነት መላእክት ከሠው ልጆች ጋር ተጋብተው ልጆች ወልደዋል?
መላእክት ለመሆኑ ሥጋና ደም አላቸው? መፅሐፈ ኩፋሌ 6:9 መላእክት ከሠው ጋር ተጋብተው ልጆች እንደወለዱ ይነግረናል ይህ 80 አሐዱ የእግዚአብሔር ቃል ነው ብለን እንመን?
በመጽሐፍ ቅዱስ አጻጻፍ በነጠላው መልአክ ወይም በብዙ መላክእት ሲባል ሦስት ዓይነት የመላእክት አተረጓጎም አለ፡-
1ኛ. “ቅዱሳን መላእክቱ” (ማቴ 28፡31) በሚልበት ጊዜ የእግዚአብሔር መልእክተኞችን በፊቱ ቆመው የሚያመሰግኑትን (ኢሳ 6፡1-3)፣ የሚጸልዩትንና የሚለምኑትን (ዘካ 1፡12-13፣ ሉቃ 13፡6-9) በፊቱ ቆመው የሚላኩትን (ሉቃ1፡27)፣ ወደ እግዚአብሔር የሰዎችን ጸሎት በእጃቸው የሚያሳርጉትን (ራእይ 8፡3-4)፣ የሚባርኩትን (ዘፍ 48፡16)፣ ሰዎችን የሚጠብቁትን (መዝ 90/91/፡11)፣ ሰዎችን ከክፉ ነገር የሚያድኑትን (መዝ
33/34/፡7)….የሚመለከት ይሆናል፡፡
እነዚህ መላእክት አይበሉም፣ አይጠጡም፣ አያገቡም፣ አይገባም፣ አይታመሙም አይሞቱም፡፡ መንፈሳዊ አካል ነው ያላቸው፡፡ “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ
የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?” እንዲል (ዕብራ 1፡14)፡፡
2ኛ. ርኩሳን መላእክት አሉ፤ እነዚህ የሰዎች ጠላት ናቸው “በርኩሳን መናፍስት” (ማቴ 10፡1) እንዲል፡፡ አፈጣጠራቸውም ከቅዱሳን መላእክት ጋር አንድ ሲሆኑ በኃጢአታቸው ምክንያት ከሰማይ ወደ ምድር ተጥለዋል፤ ሐዋርያው “እግዚአብሔር
ኃጢአትን ላደረጉ መላእክት” (2ኛ ጴጥ 2፡4) ያለው እነዚህን ነው፡፡ በተመሳሳይ ከቅዱሳን መላእክት ጋር በተፈጥሮ አንድ ስለሆኑ ርኩሳን መላእክትም አይበሉም፣ አይጠጡም፣ አያገቡም፣ አይገባም፣ አይታመሙም አይሞቱም፡፡ መንፈሳዊ አካልን ይዘው ሰዎችን ይዋጋሉ፡፡ “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው” (ኤፌ 6፡12)፡፡ ስለእነዚህ ተዋጊዎች ዮሐንስ በራእዩ ሲጽፍ “ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር
ተጣሉ” (ራእይ 12፡3-9) ያለው ውስጥ፡- “ዲያብሎስና ሰይጣን… መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ” እያለ የሚናገረው ቅዱሳን መላእክቱን ሳይሆን ስንፍና የከሰሳቸውን መላእክት ነው “እነሆ፥ በባሪያዎቹ አይታመንም መላእክቱንም ስንፍና ይከስሳቸዋል” (ኢዮብ 4፡18)፡፡ እነዚህ መላእክት
በስንፍናቸው ፈጣሪ የለም ብለው መላእክትን ያስካዱ ስለሆኑ የቅጣት ጊዜ እንደ አላቸው ጌታ ሲናገር፡- “…ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” ይላል
(ማቴ 25፡41) ይህንን ጥቅስ ያየ ሰው “መላእክቱ” ስለሚል ቅዱሳን መላእክቱን ሊመስለው ይችላል፡፡ ምክንያቱም እርሱ የሚያውቀው በጠባቡ “መላእክቱ” ሲባል ቅዱሳን መላእክቱን ብቻ ይሆናል፤ ነገር ግን የሰይጣን አገልጋዮችም መላእክት መባላቸውን ማወቅ ተገቢ ነው፡፡
3ኛ. የተጠየቀው ጥያቄ ላይ የሚመለከት ሲሆን ሰዎች “መላእክት” ወይም “መልአክ” መባላቸውን ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ አሁን መጽሐፍ ቅዱስ ሰውን መልአክ እንደሚል እንይ፡- ቅዱሳን መላእክት ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርቡ እንድንድን የሚተጉ እንጂ ከክርስቶስ ፍቅር የሚለዩን አይደሉም፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ “… መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም
ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥… ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ” (ሮሜ 8፡38-39) ይላል፡፡
አሁን ይህንን “መላእክትም” የሚላቸው የመቅደስ አዛዦችን ነው እንጂ እነ ቅዱስ ገብርኤልን አይደለም፡፡ ሰዎች የሆኑ የመቅደስ አዛዦች አትስበኩ ክርስቶስን አምላክ ነው አትበሉ እያሉ ከአባቱ ጋር ያለውን አንድነቱን የካዱና የሚያስክዱ እንዲህ ብሎ የሚሰብክንም የሚያሳድዱ ስለሆኑ፤ አስቀድሞ ክቡር ዳዊት ይህንን የአንድነት ማሠሪያ ለመበጠስ የሚሹ ስለመሆናቸው “አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ፡፡ ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል” (መዝ 2፡2-3) ብሏል፡፡ በዚህ ቦታ “አለቆችም” የሚለው በግእዙ “መላእክቱኒ” በማለት
ጽፏል፡፡ ይህ አለቆች አዛዦችን የሚመለከት እንጂ ቅዱሳን መላእክትን የሚመለከት አይደለም፡፡ መላእክት ከእግዚአብሔር ፍቅር አይለዩምና፡፡
በተመሳሳይ ለቤተ ክርስቲያኖቻችን አለቆች የሚጠሩበት ስም እንደሆነ ዮሐንስ በተደጋጋሚ እንዲህ ብሏል፡-
“በሰምርኔስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ…መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ” (ራእይ 2፡8-9) “በሰርዴስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። ….ሥራህን አውቃለሁ ሕያው እንደ መሆንህ ስም
አለህ ሞተህማል” (ራእይ 3፡1) “በሎዶቅያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። …እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ
እቀጣቸውማለሁ፤ እንግዲህ ቅና ንስሐም ግባ” (ራእይ 3፡
14-22) በእነዚህ ጥቅሶች መሠረት የቤ/ክ/ን መልአክ የሚባሉት ሰዎች
ናቸው፡፡ ምክንያቱም “መከራ” እና ማጣት በቅዱሳን መላእክት የለም፡፡ ይህ ሰው ስለሆነ “…መከራህንና ድህነትህን
አውቃለሁ” (ራእይ 2፡8-9) ይለዋል፡፡
በተመሳሳይም በቅዱሳን መላእክት መሞት የለም ነገር ግን ይህ
አለቃ ሰው ስለሆነ “ስም አለህ ሞተህማል” (ራእይ 3፡1) የሚለው ሰውን እንጂ ረቂቁን መልአክ አይደለም፡፡
በመጨረሻ የጠቀስነውም “… ንስሐም ግባ” የተባለው መልአክ (ራእይ 3፡14-22) ረቂቁን መልአክ ሳይሆን የሰው ዘር የሆነውን የቤ/ክ/ን አለቃን ነው፡፡ ባጠቃላይ “አለቆች” “መልአክ” ከተባሉ በቅዱስ ጳውሎስ ንግግርም መላእክት ተብለው ሰዎች እንደሚጠሩ ከተማርን፤
በመጽሐፈ ኩፋሌ መላእክት የሚላቸው የሰው ልጆችን እንጂ ረቂቃኑን መላእክት አይደለም፡፡ ረቂቃኑማ “መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም” (ማቴ 22፡30) መባሉ
የታወቀ ነው፡፡ መጽሐፉ ደግሞ “የአዳም ልጆች በምድር ላይ ይበዙ ዘንድ
በጀመሩ ጊዜ እንዲህ ሆነ፤ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው፡፡ የእግዚአብሔር መላእክትም …እነዚያ ላዩአቸው መልከ መልካሞች ነበሩና ከመረጡአቸው ሁሉ ሚስቶች ሊሆኑአቸው ወሰዱአቸው፤ ወንዶች ልጆችንም ወሰዱላቸው..” (ኩፋሌ 6፡9) በሚለው ውስጥ ልብ ብለን ስንመለከት “የእግዚአብሔር
መላእክትም …” የሚላቸው ሰዎችን ነው፡፡ እነዚህ በዘፍጥረት አጻጻፍ “የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን
ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደ ሆኑ አዩ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ” ከሚለው ጋር አንድ ነው (ዘፍ 6፡ 2)፡፡
“የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት በኩፋሌ አጻጻፍ በቅድስና በንጽሕና የኖሩት በመጠሪያ ደረጃ “የእግዚአብሔር መላእክት”
የተባሉትን ሲሆን፤ “የሰውን ሴቶች ልጆች” የተባሉት ደግሞ በኃጢአት የሚኖሩትን ነው፣ በኃጢአት ከሚኖሩት፣ ከአምልኮ እግዚአብሔር ከራቁት ጋራ
በማይመች አካሄድ መጣመድ ስለማይገባ ያ ሁሉ ጥፋት መጥቶባቸዋል፡፡ እነዚያ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ የእግዚአብሔር ልጆች፣ የእግዚአብሔር መላእክት የሚል
የማዕረግ መጠሪያ ሲሰጣቸው፡፡ በአምልኮ ባዕድና በኃጢአት የሚኖሩትን ግን የሰው ልጆች ብቻ በሚል መጠራታቸውን እናስተውል፡፡ እኛም የእግዚአብሔር ልጆች በአጋንንት ላይ አለቆች ነንና መላእክት የሚል መጠሪያ
እንዳለን ልብ ማለት ይገባል፡፡
....ቀጥሏል👇👇
@And_Haymanot
እውነት መላእክት ከሠው ልጆች ጋር ተጋብተው ልጆች ወልደዋል?
መላእክት ለመሆኑ ሥጋና ደም አላቸው? መፅሐፈ ኩፋሌ 6:9 መላእክት ከሠው ጋር ተጋብተው ልጆች እንደወለዱ ይነግረናል ይህ 80 አሐዱ የእግዚአብሔር ቃል ነው ብለን እንመን?
በመጽሐፍ ቅዱስ አጻጻፍ በነጠላው መልአክ ወይም በብዙ መላክእት ሲባል ሦስት ዓይነት የመላእክት አተረጓጎም አለ፡-
1ኛ. “ቅዱሳን መላእክቱ” (ማቴ 28፡31) በሚልበት ጊዜ የእግዚአብሔር መልእክተኞችን በፊቱ ቆመው የሚያመሰግኑትን (ኢሳ 6፡1-3)፣ የሚጸልዩትንና የሚለምኑትን (ዘካ 1፡12-13፣ ሉቃ 13፡6-9) በፊቱ ቆመው የሚላኩትን (ሉቃ1፡27)፣ ወደ እግዚአብሔር የሰዎችን ጸሎት በእጃቸው የሚያሳርጉትን (ራእይ 8፡3-4)፣ የሚባርኩትን (ዘፍ 48፡16)፣ ሰዎችን የሚጠብቁትን (መዝ 90/91/፡11)፣ ሰዎችን ከክፉ ነገር የሚያድኑትን (መዝ
33/34/፡7)….የሚመለከት ይሆናል፡፡
እነዚህ መላእክት አይበሉም፣ አይጠጡም፣ አያገቡም፣ አይገባም፣ አይታመሙም አይሞቱም፡፡ መንፈሳዊ አካል ነው ያላቸው፡፡ “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ
የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?” እንዲል (ዕብራ 1፡14)፡፡
2ኛ. ርኩሳን መላእክት አሉ፤ እነዚህ የሰዎች ጠላት ናቸው “በርኩሳን መናፍስት” (ማቴ 10፡1) እንዲል፡፡ አፈጣጠራቸውም ከቅዱሳን መላእክት ጋር አንድ ሲሆኑ በኃጢአታቸው ምክንያት ከሰማይ ወደ ምድር ተጥለዋል፤ ሐዋርያው “እግዚአብሔር
ኃጢአትን ላደረጉ መላእክት” (2ኛ ጴጥ 2፡4) ያለው እነዚህን ነው፡፡ በተመሳሳይ ከቅዱሳን መላእክት ጋር በተፈጥሮ አንድ ስለሆኑ ርኩሳን መላእክትም አይበሉም፣ አይጠጡም፣ አያገቡም፣ አይገባም፣ አይታመሙም አይሞቱም፡፡ መንፈሳዊ አካልን ይዘው ሰዎችን ይዋጋሉ፡፡ “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው” (ኤፌ 6፡12)፡፡ ስለእነዚህ ተዋጊዎች ዮሐንስ በራእዩ ሲጽፍ “ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር
ተጣሉ” (ራእይ 12፡3-9) ያለው ውስጥ፡- “ዲያብሎስና ሰይጣን… መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ” እያለ የሚናገረው ቅዱሳን መላእክቱን ሳይሆን ስንፍና የከሰሳቸውን መላእክት ነው “እነሆ፥ በባሪያዎቹ አይታመንም መላእክቱንም ስንፍና ይከስሳቸዋል” (ኢዮብ 4፡18)፡፡ እነዚህ መላእክት
በስንፍናቸው ፈጣሪ የለም ብለው መላእክትን ያስካዱ ስለሆኑ የቅጣት ጊዜ እንደ አላቸው ጌታ ሲናገር፡- “…ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” ይላል
(ማቴ 25፡41) ይህንን ጥቅስ ያየ ሰው “መላእክቱ” ስለሚል ቅዱሳን መላእክቱን ሊመስለው ይችላል፡፡ ምክንያቱም እርሱ የሚያውቀው በጠባቡ “መላእክቱ” ሲባል ቅዱሳን መላእክቱን ብቻ ይሆናል፤ ነገር ግን የሰይጣን አገልጋዮችም መላእክት መባላቸውን ማወቅ ተገቢ ነው፡፡
3ኛ. የተጠየቀው ጥያቄ ላይ የሚመለከት ሲሆን ሰዎች “መላእክት” ወይም “መልአክ” መባላቸውን ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ አሁን መጽሐፍ ቅዱስ ሰውን መልአክ እንደሚል እንይ፡- ቅዱሳን መላእክት ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርቡ እንድንድን የሚተጉ እንጂ ከክርስቶስ ፍቅር የሚለዩን አይደሉም፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ “… መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም
ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥… ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ” (ሮሜ 8፡38-39) ይላል፡፡
አሁን ይህንን “መላእክትም” የሚላቸው የመቅደስ አዛዦችን ነው እንጂ እነ ቅዱስ ገብርኤልን አይደለም፡፡ ሰዎች የሆኑ የመቅደስ አዛዦች አትስበኩ ክርስቶስን አምላክ ነው አትበሉ እያሉ ከአባቱ ጋር ያለውን አንድነቱን የካዱና የሚያስክዱ እንዲህ ብሎ የሚሰብክንም የሚያሳድዱ ስለሆኑ፤ አስቀድሞ ክቡር ዳዊት ይህንን የአንድነት ማሠሪያ ለመበጠስ የሚሹ ስለመሆናቸው “አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ፡፡ ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል” (መዝ 2፡2-3) ብሏል፡፡ በዚህ ቦታ “አለቆችም” የሚለው በግእዙ “መላእክቱኒ” በማለት
ጽፏል፡፡ ይህ አለቆች አዛዦችን የሚመለከት እንጂ ቅዱሳን መላእክትን የሚመለከት አይደለም፡፡ መላእክት ከእግዚአብሔር ፍቅር አይለዩምና፡፡
በተመሳሳይ ለቤተ ክርስቲያኖቻችን አለቆች የሚጠሩበት ስም እንደሆነ ዮሐንስ በተደጋጋሚ እንዲህ ብሏል፡-
“በሰምርኔስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ…መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ” (ራእይ 2፡8-9) “በሰርዴስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። ….ሥራህን አውቃለሁ ሕያው እንደ መሆንህ ስም
አለህ ሞተህማል” (ራእይ 3፡1) “በሎዶቅያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። …እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ
እቀጣቸውማለሁ፤ እንግዲህ ቅና ንስሐም ግባ” (ራእይ 3፡
14-22) በእነዚህ ጥቅሶች መሠረት የቤ/ክ/ን መልአክ የሚባሉት ሰዎች
ናቸው፡፡ ምክንያቱም “መከራ” እና ማጣት በቅዱሳን መላእክት የለም፡፡ ይህ ሰው ስለሆነ “…መከራህንና ድህነትህን
አውቃለሁ” (ራእይ 2፡8-9) ይለዋል፡፡
በተመሳሳይም በቅዱሳን መላእክት መሞት የለም ነገር ግን ይህ
አለቃ ሰው ስለሆነ “ስም አለህ ሞተህማል” (ራእይ 3፡1) የሚለው ሰውን እንጂ ረቂቁን መልአክ አይደለም፡፡
በመጨረሻ የጠቀስነውም “… ንስሐም ግባ” የተባለው መልአክ (ራእይ 3፡14-22) ረቂቁን መልአክ ሳይሆን የሰው ዘር የሆነውን የቤ/ክ/ን አለቃን ነው፡፡ ባጠቃላይ “አለቆች” “መልአክ” ከተባሉ በቅዱስ ጳውሎስ ንግግርም መላእክት ተብለው ሰዎች እንደሚጠሩ ከተማርን፤
በመጽሐፈ ኩፋሌ መላእክት የሚላቸው የሰው ልጆችን እንጂ ረቂቃኑን መላእክት አይደለም፡፡ ረቂቃኑማ “መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም” (ማቴ 22፡30) መባሉ
የታወቀ ነው፡፡ መጽሐፉ ደግሞ “የአዳም ልጆች በምድር ላይ ይበዙ ዘንድ
በጀመሩ ጊዜ እንዲህ ሆነ፤ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው፡፡ የእግዚአብሔር መላእክትም …እነዚያ ላዩአቸው መልከ መልካሞች ነበሩና ከመረጡአቸው ሁሉ ሚስቶች ሊሆኑአቸው ወሰዱአቸው፤ ወንዶች ልጆችንም ወሰዱላቸው..” (ኩፋሌ 6፡9) በሚለው ውስጥ ልብ ብለን ስንመለከት “የእግዚአብሔር
መላእክትም …” የሚላቸው ሰዎችን ነው፡፡ እነዚህ በዘፍጥረት አጻጻፍ “የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን
ሴቶች ልጆች መልካሞች እንደ ሆኑ አዩ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ” ከሚለው ጋር አንድ ነው (ዘፍ 6፡ 2)፡፡
“የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት በኩፋሌ አጻጻፍ በቅድስና በንጽሕና የኖሩት በመጠሪያ ደረጃ “የእግዚአብሔር መላእክት”
የተባሉትን ሲሆን፤ “የሰውን ሴቶች ልጆች” የተባሉት ደግሞ በኃጢአት የሚኖሩትን ነው፣ በኃጢአት ከሚኖሩት፣ ከአምልኮ እግዚአብሔር ከራቁት ጋራ
በማይመች አካሄድ መጣመድ ስለማይገባ ያ ሁሉ ጥፋት መጥቶባቸዋል፡፡ እነዚያ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ የእግዚአብሔር ልጆች፣ የእግዚአብሔር መላእክት የሚል
የማዕረግ መጠሪያ ሲሰጣቸው፡፡ በአምልኮ ባዕድና በኃጢአት የሚኖሩትን ግን የሰው ልጆች ብቻ በሚል መጠራታቸውን እናስተውል፡፡ እኛም የእግዚአብሔር ልጆች በአጋንንት ላይ አለቆች ነንና መላእክት የሚል መጠሪያ
እንዳለን ልብ ማለት ይገባል፡፡
....ቀጥሏል👇👇
መላእክት ተጋብተው ኖሩ....?
....(የቀጠለ)
መጽሐፈ ኩፋሌ “መላእክት” ስላለ ብቻ ረቂቃኑን ነው ብለን የምንወድቅ ከሆነ፡-
“መላእክቱንም ስንፍና ይከስሳቸዋል” (ኢዮብ 4፡18)፡፡ የሚለውን ይዘን ቅዱስ ሚካኤልን ስንፍና ይከሰዋል ወደማለት
አዘቅት እንወድቃለን፡፡ “…ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” (ማቴ 25፡41) የሚለውንም አይተን ቅዱስ ገብርኤልና
ቅዱስ ሚካኤል ወደፊት በእሳት ባሕር ይጣላሉ ወደሚል ክህደት
እንወድቃለን፡፡ “… መላእክትም ቢሆኑ..ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን
እንዳይችል ተረድቼአለሁ” (ሮሜ 8፡38-39) የሚለውንም ይዘን ቅዱሳን መላእክት ከአምላክ የሚለዩ ናቸው ወደሚል የስህተት መንገድ እንጓዛለንና እንደ አገባቡ እንፍታው እንጂ፤ ባመጣለን
ተሳስተን ሰውን ወደ ስህተት ከመክተት እንቆጠብ፡፡
እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot
....(የቀጠለ)
መጽሐፈ ኩፋሌ “መላእክት” ስላለ ብቻ ረቂቃኑን ነው ብለን የምንወድቅ ከሆነ፡-
“መላእክቱንም ስንፍና ይከስሳቸዋል” (ኢዮብ 4፡18)፡፡ የሚለውን ይዘን ቅዱስ ሚካኤልን ስንፍና ይከሰዋል ወደማለት
አዘቅት እንወድቃለን፡፡ “…ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” (ማቴ 25፡41) የሚለውንም አይተን ቅዱስ ገብርኤልና
ቅዱስ ሚካኤል ወደፊት በእሳት ባሕር ይጣላሉ ወደሚል ክህደት
እንወድቃለን፡፡ “… መላእክትም ቢሆኑ..ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን
እንዳይችል ተረድቼአለሁ” (ሮሜ 8፡38-39) የሚለውንም ይዘን ቅዱሳን መላእክት ከአምላክ የሚለዩ ናቸው ወደሚል የስህተት መንገድ እንጓዛለንና እንደ አገባቡ እንፍታው እንጂ፤ ባመጣለን
ተሳስተን ሰውን ወደ ስህተት ከመክተት እንቆጠብ፡፡
እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot
❖ መልካም አዲስ አመት አትበሉን!!!!!!!
@And_Haymanot
የ ፳፻፲፩ (2011) ዓ.ም የመልካም ምኞት መግለጫ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያዎች 'መልካም አዲስ አመት' ሲሉ "መልካም አዲስ ገረድ' ማለታቸው መሆኑን ያውቃሉ......
♦ "አመት" ተብሎ በአልፋው "አ" ሲጻፍ ሴት አገልጋይ ገረድን ይገልጻል። ለምሳሌ፦ "ተፈሥሒ ኦ አመት ወእም ድንግል ወሰማይ ሰማያዌ..." /ውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ/ ሲል ገረድ(ሴት አገልጋይ) ና እናት፤ ድንግልና ሰማይ ሆይ ደስ ይበልሽ ማለት ነው።
♦ "ዓመት" ሲሆን ዘመን ይሆናል። "...ርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ።..."/መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ፤ ለሥእርተ ርእስከ(ለራስ ጸጉርህ)/ ሲል ደግሞ "የመጥቅዕና የአበቅቴ መጀመሪያ ርእሰ ዓመት ዮሐንስ ሆይ..." ማለት ነው።
✍ አመት የሚለው በብዙ ቁጥር አእማት ይሆናል። በዕብራይስጥ አማህ፤ በሱሪስት አምታ፤ በዐረብኛ ደግሞ አመት ይለዋል። ትርጓሜውም ሴት ባሪያ፤ ገረድ፤ ደንገጥር ማለት ነው። "...በወፍጮ እግር እስካለችው እስከ ባሪያይቱ..." ዘፀ.11፥5 የሚለውን ግዕዙ "አመት እንተ ትነብር ዲበ ማሕረጽ።" ይለዋል። በዚህ አገባብ አማርኛው "ባሪያይቱ" የሚለውን ግዕዙ "አመት" ይላታል።
✔ ወንዶች ባሪያዎችን "አግብርት" ሲላቸው ሴቶች ባሪያዎችን ደግሞ "አእማት" ይላቸዋል። [ዘፍ.32፥5 ግዕዙን ንባብ ተመልከት]
♦ ዓመት የሚለው ደግሞ በብዙ ቁጥር "ዓመታት" ሲባል ዘመን፥ ዘመናት፥ ብዙ ቀን፥ የዕለታት ድምር ማለት ነው። "በባቢሎን ንጉሥ በብልጣሶር በመጀመሪያው ዓመት" ዳን.7፥1 የሚለውን ግዕዙ "በቀዳሚ ዓመተ መንግሥቱ።" ይለዋል። "የዕድሜህም ቁጥር ብዙ ነውና፥" ኢዮ.38፥21 የሚለውን ግዕዙ "ኊልቆ ዓመታቲከ፥" ይለዋል።
✍ ስለሆነም አንድ ሰው 'እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሰን' ሲል 'እንኳን ለአዲሷ ገረድ አደረሰን' አለ ማለት ነው። ይኼ ደሞ ጸያፍ ነው።
♦ "እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን" ሲል "እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሰን ማለቱ ነው። ይኸውም የተገባ ነው።
✔ መልካም ምኞታችሁን የገለጻችሁ መስሏችሁ 'መልካም አዲስ አመት' አትበሉን!!!!!
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የ ፳፻፲፩ (2011) ዓ.ም የመልካም ምኞት መግለጫ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያዎች 'መልካም አዲስ አመት' ሲሉ "መልካም አዲስ ገረድ' ማለታቸው መሆኑን ያውቃሉ......
♦ "አመት" ተብሎ በአልፋው "አ" ሲጻፍ ሴት አገልጋይ ገረድን ይገልጻል። ለምሳሌ፦ "ተፈሥሒ ኦ አመት ወእም ድንግል ወሰማይ ሰማያዌ..." /ውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ/ ሲል ገረድ(ሴት አገልጋይ) ና እናት፤ ድንግልና ሰማይ ሆይ ደስ ይበልሽ ማለት ነው።
♦ "ዓመት" ሲሆን ዘመን ይሆናል። "...ርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ።..."/መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ፤ ለሥእርተ ርእስከ(ለራስ ጸጉርህ)/ ሲል ደግሞ "የመጥቅዕና የአበቅቴ መጀመሪያ ርእሰ ዓመት ዮሐንስ ሆይ..." ማለት ነው።
✍ አመት የሚለው በብዙ ቁጥር አእማት ይሆናል። በዕብራይስጥ አማህ፤ በሱሪስት አምታ፤ በዐረብኛ ደግሞ አመት ይለዋል። ትርጓሜውም ሴት ባሪያ፤ ገረድ፤ ደንገጥር ማለት ነው። "...በወፍጮ እግር እስካለችው እስከ ባሪያይቱ..." ዘፀ.11፥5 የሚለውን ግዕዙ "አመት እንተ ትነብር ዲበ ማሕረጽ።" ይለዋል። በዚህ አገባብ አማርኛው "ባሪያይቱ" የሚለውን ግዕዙ "አመት" ይላታል።
✔ ወንዶች ባሪያዎችን "አግብርት" ሲላቸው ሴቶች ባሪያዎችን ደግሞ "አእማት" ይላቸዋል። [ዘፍ.32፥5 ግዕዙን ንባብ ተመልከት]
♦ ዓመት የሚለው ደግሞ በብዙ ቁጥር "ዓመታት" ሲባል ዘመን፥ ዘመናት፥ ብዙ ቀን፥ የዕለታት ድምር ማለት ነው። "በባቢሎን ንጉሥ በብልጣሶር በመጀመሪያው ዓመት" ዳን.7፥1 የሚለውን ግዕዙ "በቀዳሚ ዓመተ መንግሥቱ።" ይለዋል። "የዕድሜህም ቁጥር ብዙ ነውና፥" ኢዮ.38፥21 የሚለውን ግዕዙ "ኊልቆ ዓመታቲከ፥" ይለዋል።
✍ ስለሆነም አንድ ሰው 'እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሰን' ሲል 'እንኳን ለአዲሷ ገረድ አደረሰን' አለ ማለት ነው። ይኼ ደሞ ጸያፍ ነው።
♦ "እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን" ሲል "እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሰን ማለቱ ነው። ይኸውም የተገባ ነው።
✔ መልካም ምኞታችሁን የገለጻችሁ መስሏችሁ 'መልካም አዲስ አመት' አትበሉን!!!!!
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
🌻🌻 አበባዩሽ 🌻🌻
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
እሰይ ደስ ደስ ይበላችሁ/2/
ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን/2/
ጌታ አለ ብለን ደስ ብሎን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን/2/
ድንግል አለች ብለን ደስ ብሎን
አበባዮሽ ቅድስት/2/
ባለእንጀሮቼ ቅድስት
ቁሙ በተራ ›ቅድስት ›
በጎ ምግባርን ››ቅድስት
በእምነት እንሥራ ቅድስት ››
ዛሬ ነው ቀኑ ቅድስት ›
መመለሻችን ቅድስት ››
ይቅር እንዲለን ቅድስት ››
ቸሩ አምላካችን ቅድስት ››
አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ/2/
ድንግል ማርያምን ቅድስት
እንለምናት ቅድስት
ምሕረት የሚያሠጥ ቅድስት
ቃልኪዳን አላት ቅድስት
ጭንቀት ይርቃል ቅድስት
ይቀርባል ሰላም ቅድስት
ስሟ ሲጠራ ቅድስት
የድንግል ማርያም ቅድስት
አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ/2/
በሕገ ልቡና ጥንቱን
ፈጣሪን አውቀሸ ጥንቱን
ሕገ ነቢያት ከዓለም
ቀድመሽ ተቀበልሽ ከዓለም
በብሉይ ኪዳን ለጌታ
መሥዋእት አቀረብሽ ለጌታ
ተስፋ ካደረጉት ከአይሁድ
ከእስራኤል ቀድመሽ ከአይሁድ
ሕገ ወንጌልን በፊት
ይዘሽ ተገኘሽ በፊት
ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ጸጋ አለሽ/2/
ስለፈጸምሽ ሦስቱን ሕግጋት የፈጣሪሽን
ካለፈው ስህተት ሁላችን
እንድንመለስ ሁላችን
አዲሱ ዓመት ለሁሉ
መጣ ማቴዎስ ለሁሉ
ይህም ያልፍና በጊዜ
ይመጣል ማርቆስ በጊዜው
ሌላው ይተካል በጊዜው
ዘመነ ሉቃስ በጊዜው
ወልደ ነጎድጓድ በጊዜው
ሲደርስ ዮሐንስ በጊዜው
በየዓመቱ መጥምቁ
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ
አደይ የብርሃን የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ አበራ2/
ኢትዮጵያ ባህል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ/2/
ዘመኑ አልፎ ቅድስት
ሲሄድ ማቴዎስ ቅድስት
አዲሱ ዘመን ቅድስት
ሲመጣ ማርቆስ ቅድስት
እድሜን ጨምሮ ቅድስት
ለሠጠን ጤና ቅድስት
ለመድኀኔዓለም ቅድሰት
ይድረስ ምስጋና ቅድስት
አደይ የብርሃን ጮራ በማርቆስ በራ
እቴ አበባ እቴ አበባዬ አዬ ቅድስት እናቴ
እቴ አበባ ስትለኝ ከርማ አዬ ቅድስት እናቴ
መከረችኝ ደግማ ደጋግማ አዬ ቅድስት እናቴ
ቃሉን ሰማው አድምጥው ብላ እዬ ቅድስት እናቴ
አዬ ቅድስት እናቴ አዬ ቅ. እናቴ/2/
ይሸታል የእጣኑ ጢስ ሲታጠን ከመቅደሱ
በመላእክት ዜማ ካህናት ሲቀድሱ ሲታጠን ከመቅደሱ/2/
ከብረው ይቆዩን ከብርው
ከዓመት አውደ ዓመት ደርሰው
በእምነት በምግባር ጸንተው
ነጽተው ንስሓ ገብተው
ለሥጋ ወደሙ በቅተው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
ከዓመት እከሰ ዓመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትኁት ሠው አክባሪ ሆነው
የፍቅርን ሸማ ለብሰው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
አበባው ለምለም ቄጤማው ለምለም
ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም
አበባው ለምለም ቄጤማው ለምለም
ተዋሕዶ እንዳንቺ የለም
አበባው ለምለም ድንግል ማርያም
ያለአንቺ እመቤት የለም
🌻 @And_Haymanot 🌻
🌻 @And_Haymanot 🌻
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
፩ ኃይማኖት
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻 አበባዩሽ 🌻🌻
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
እሰይ ደስ ደስ ይበላችሁ/2/
ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን/2/
ጌታ አለ ብለን ደስ ብሎን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን/2/
ድንግል አለች ብለን ደስ ብሎን
አበባዮሽ ቅድስት/2/
ባለእንጀሮቼ ቅድስት
ቁሙ በተራ ›ቅድስት ›
በጎ ምግባርን ››ቅድስት
በእምነት እንሥራ ቅድስት ››
ዛሬ ነው ቀኑ ቅድስት ›
መመለሻችን ቅድስት ››
ይቅር እንዲለን ቅድስት ››
ቸሩ አምላካችን ቅድስት ››
አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ/2/
ድንግል ማርያምን ቅድስት
እንለምናት ቅድስት
ምሕረት የሚያሠጥ ቅድስት
ቃልኪዳን አላት ቅድስት
ጭንቀት ይርቃል ቅድስት
ይቀርባል ሰላም ቅድስት
ስሟ ሲጠራ ቅድስት
የድንግል ማርያም ቅድስት
አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ/2/
በሕገ ልቡና ጥንቱን
ፈጣሪን አውቀሸ ጥንቱን
ሕገ ነቢያት ከዓለም
ቀድመሽ ተቀበልሽ ከዓለም
በብሉይ ኪዳን ለጌታ
መሥዋእት አቀረብሽ ለጌታ
ተስፋ ካደረጉት ከአይሁድ
ከእስራኤል ቀድመሽ ከአይሁድ
ሕገ ወንጌልን በፊት
ይዘሽ ተገኘሽ በፊት
ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ጸጋ አለሽ/2/
ስለፈጸምሽ ሦስቱን ሕግጋት የፈጣሪሽን
ካለፈው ስህተት ሁላችን
እንድንመለስ ሁላችን
አዲሱ ዓመት ለሁሉ
መጣ ማቴዎስ ለሁሉ
ይህም ያልፍና በጊዜ
ይመጣል ማርቆስ በጊዜው
ሌላው ይተካል በጊዜው
ዘመነ ሉቃስ በጊዜው
ወልደ ነጎድጓድ በጊዜው
ሲደርስ ዮሐንስ በጊዜው
በየዓመቱ መጥምቁ
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ
አደይ የብርሃን የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ አበራ2/
ኢትዮጵያ ባህል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ/2/
ዘመኑ አልፎ ቅድስት
ሲሄድ ማቴዎስ ቅድስት
አዲሱ ዘመን ቅድስት
ሲመጣ ማርቆስ ቅድስት
እድሜን ጨምሮ ቅድስት
ለሠጠን ጤና ቅድስት
ለመድኀኔዓለም ቅድሰት
ይድረስ ምስጋና ቅድስት
አደይ የብርሃን ጮራ በማርቆስ በራ
እቴ አበባ እቴ አበባዬ አዬ ቅድስት እናቴ
እቴ አበባ ስትለኝ ከርማ አዬ ቅድስት እናቴ
መከረችኝ ደግማ ደጋግማ አዬ ቅድስት እናቴ
ቃሉን ሰማው አድምጥው ብላ እዬ ቅድስት እናቴ
አዬ ቅድስት እናቴ አዬ ቅ. እናቴ/2/
ይሸታል የእጣኑ ጢስ ሲታጠን ከመቅደሱ
በመላእክት ዜማ ካህናት ሲቀድሱ ሲታጠን ከመቅደሱ/2/
ከብረው ይቆዩን ከብርው
ከዓመት አውደ ዓመት ደርሰው
በእምነት በምግባር ጸንተው
ነጽተው ንስሓ ገብተው
ለሥጋ ወደሙ በቅተው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
ከዓመት እከሰ ዓመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትኁት ሠው አክባሪ ሆነው
የፍቅርን ሸማ ለብሰው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
አበባው ለምለም ቄጤማው ለምለም
ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም
አበባው ለምለም ቄጤማው ለምለም
ተዋሕዶ እንዳንቺ የለም
አበባው ለምለም ድንግል ማርያም
ያለአንቺ እመቤት የለም
🌻 @And_Haymanot 🌻
🌻 @And_Haymanot 🌻
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻 🌻
፩ ኃይማኖት
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
🌻🌻🌻🌻🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
🌻🌻
☞ መፅሀፈ ሄኖክ
@And_Haymanot
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት፣ታሪካዊትና ብሄራዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን በአለም ከምትታወቅባቸው አበይት መገለጫዎች ውስጥ በዋቢነት
የሚጠቀሱት በጥንታውያን ብሄራዊው ሊቃውንት ሲወርድ ሲዋረድ ተጠብቀው የቆዩት መፅሀፍቶቿ ዋነኛ ናቸው ከእነርሱም ውስጥ በአለም ላይ እስካሁን የሌለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ተጠብቆ የቆየው መፅሀፈ ሄኖክ አንዱ ነው ፈረንጆቹ በ18ኛው መቶ ክ/ዘመን ድረስ ቤታችን መተው እስኪዘርፉን ድረስ ስለ መፅሀፉ ሙሉ እውቀት አልነበራቸውም ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል እንዲሉ እኛ አንቀላፍተን እነርሱ ነቅተው የወሰዱትን ምስጢር እየበረበሩት ይገኛል በየአመቱ የበቁ ሊቃውንት የሚባሉ እስከ 250 የሚደርሱ በቫቲካን በመፅሀፈ ሄኖክ
ላይ ጉባኤ ይቀመጣሉ የመገኛዋ ምድር ኢትዮጵያ ያላት ተወካይ አንድ ብቻ ነው ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የመፅሀፉ ሙሉ ባለቤት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ግን በጉባኤው ላይ ሰው የላትም እንዲ ጉባኤ የሚሰየምለት መፅሀፈ ሄኖክ ብዙ ይባልለታል እንዲያውም የአውሮፓ ህዳሴ ስኬት የመፅሀፈ ሄኖክን ምስጢር ፈረንጆቹ መፍታታቸው ዋነኛ ምክንያት ነው የሚሉ አሉ ለዚህም በህዳሴው
ዘመን በ18ኛው መቶ ክ/ዘመን ከእኛ ከመሰረቁ ጋር ያያይዙታል ከውጪ በብዙ ብር የምንገዛቸው መድሀኒቶች እራሱ ከመፅሀፉ የተቀዱ እውቀቶች ውጤት ናቸው ይባላል በምእራቡ አለም በተለይ አሁን አሁን መፅሀፈ ሄኖክ ስሙ እጅግ ከበዙ ግኝቶችና ምርምሮች ጋር ይነሳል እንዲያውም ሳይንስ ከገደበው የምድራችን እውቀትም በላይ ይጠቀሙበታል ይባላል ይህን ሁሉ ከውጪ ብንሰማም በሀገር ቤት ግን ምንም የማይባልለት ነውና ለመሆኑ
መፅሀፈ ሄኖክ ምንድነው? ሄኖክስ ማነው? ብለን ጥያቄ እናነሳለን ሄኖክ ማለት ተሀድሶ ማለት ነው (የእናት ጡት ነካሾች የተሀድሶ መናፍቃንን ለመጥቀስ አይደለም) አዳም በምግብ ምክንያት
ብልየትን እንዳመጣ ሄኖክም ከምግብ ተከልክሎ ተሀድሶን አምጥቷልና አንድም ዛሬ በብሉይ ስጋ ገነት እንደገባ እኛም
በሁዋላ ተነስተን በሀዲስ ስጋ መንግስተ ሰማያት እንገባለንና
(ምንጭ፦ መፅሀፈ ሄኖክ አንድምታ ገፅ 1) ሄኖክ የያሬድ ልጅ ነው ልደቱን ወይም የዘር ሀረጉን ስንቆጥር አዳም ሴትን ይወልዳል ሴት ደሞ ሄኖስን ሄኖስ ቃይናንን ይወልዳል ቃይናን ደሞ መላልኤልን መላልኤል ያሬድን ይወልዳል ያሬድ ደሞ ሄኖክን ዘፍ 5:1-22 ሄኖክ የአዳም ሰባተኛ ትውልድ ነው
ስድስተኛው ትውልድ ያሬድ ሄኖክን ወልዶ ሄኖክ ደሞ ከሚስቱ ከእድኒ ማቱሳላን ይወልዳል ሄኖክ ባለ ዘመኑ ሁሉ በፍፁም እምነት እግዚአብሄርን እያገለገለ በምድር ላይ ለ 365 አመት ኖሯል ስለዚህ እንደ መፅሀፍ ቅዱስ አገላለፅ ዘፍ 5:24ላይ ሄኖክም
አካሄዱን ከእግዚአብሄር ጋር ስላደረገ አልተገኘም እግዚአብሄር ወስዶታልና ይላል ስለዚህ ሄኖክ ሞትን ሳይቀምስ ተሰውሮ ወይም ተወስዶ ሄዶዋል ማለት ነው በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ኤሊያስም
ቢያርግ የሄኖክ ግን ይለያል ምክንያቱም ሄኖክ ፓትራሪክ ነው ከጥፋት ውሀ በፊት የነበረ ሰው ነው በዛ ጊዜ የሰው ልጅ በክፋት በነበረበት ጊዜ ሄኖክ ሞትን ሳይቀምስ የጥንት በደል ወይም ምልሀተ ሀጢያት ሳይነካው ሞትን ሳያይ ሄዱዋልና። መፅሀፈ ሄኖክ አምላካዊ ከሚባሉ የመፅሀፍ ቅዱስ ቁጥሮች
በተለይም በኢ/ኦ/ተ//ቤ/ክን በ81 አሀዱ ላይ ያለ ነው አንድ መፅሀፍ አምላካዊ መፅሀፍ ለመባል በትንሹ 5ቱ አእማደ ምስጢርንና 7ቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ማካተት አለበት መፅሀፈ ሄኖክም እነዚን በሚገባ አካቶ ይዟል መፅሀፈ ሄኖክ በትንቢት፣ በታሪክም በተለያየ ገፅታው ጠቃሚ ነው ስለዚህ
አምላካዊ መፅሀፍ ነው በትንፋሰ እግዚአብሄር የተፃፈ ለራሱ ለሄኖክ የተገለፀ ነው የመጀመሪያ ፊደላት መገኘትና ሰማያዊ ምስጢር መገለፅ ጋር ተያይዞ ለሄኖክ የተገለፀለትን ነገር መፅሀፈ ሄኖክ ብለን የምንጠራው ውስጥ አካቶታል ለሄኖክ ጥበብን
በተመለከተ ስለ ፅሁፍ ጥበብ፣ ስለ ስነ-ፈለግ ጥበብ፣ ስለ ክዋክብት፣ ስለ ፀሀይ፣ ስለ ጨረቃ፣ ስለ ወር ስለ ንፋሳት... የመሳሰሉት ሀሳቦች ተገልፀውለት ለመጀመሪያ ጊዜ የጥበብ ሰው ሆኖ የተቀመጠ እንደሆነ በመፅሀፉ ሀሳብ ላይ እናገኘዋለን ከእርሱ
በፊትም ሆነ በሁዋላ እርሱ ያገኘውን ጥበብ ማንም ሰው እንዳላገኘ በራሱ ቃል ምስክርነት ሰጥቷል እንግዲህ እኔ ያየሁትን ራእይ እኔ ያየሁትን ግልፀት ከጥበብ፣ ከእውቀት ጋር በተገናኘ እኔ
እንዳየሁት ማንም አላየም ከሰውም የሚያየው የለም የሚል ሀሳብ
ተፅፎ እናገኛለን።
በመፅሀፈ ሄኖክ ላይ የበቃ እውቀት አለን የሚሉ እንኩዋን በብዙ ጉዳዮች ላይ ይከራከራሉ ከዛም በላይ ግምታዊ ትንታኔ የሚያበዙ ናቸው ከእዚህም አንዱ ሌላው ቀርቶ በፀሀፊው ማንነት ላይ
ጭምር ያለ መስማማታቸው ነው የአዳም ሰባተኛ ትውልድ ሄኖክ
በመላእክት ተመንጥቆ እንደፃፈው የሚስማሙ አሉ ሄኖክ ደሞ የማቱሳላ አባት የኖህ ደሞ ቅድመ አያት ነው እነዚህ ሄኖክ በፈጣሪ በጎ ፍቃድ በመላእክት እርዳታ የተገለፀለትን እውቀት ነው የፃፈው ሲሉ በሌላ ወገን ደግሞ መፅሀፉ በተለያየ ዘመን ተፅፏል
የሚሉም አልታጡም ለዚህም የሚያቀርቡት ምክንያት እየተጨመሩ
የመጡ ምእራፎች አሉ የሚል ነው እነዚህ ወገኖች በቀዳሚነት የሚጠቅሱት ስለመላእክት የሚናገረው ክፍል በቅ/ል/ክ 200 ተፅፏል ሲሉ ተጨመረ የሚሏቸው ደግሞ በአመተ ምህረት
የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ተፅፏል ይላሉ ከፀሀፊው ማንነት ሌላ ተፃፈ የሚሉበት ክፍለ ዘመን ጭምር አንዱ ልዩነታቸው መሆኑን ያሳያል እንዲ ሊቃውንቱ የሚነታረኩበት እስከ አሁን 3 የሚታወቁ መፅሀፈ ሄኖክ አሉ
1ኛው፦ One Henok የሚባለው አምስት ክፍል ያለው በእኛ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ሙሉ እውቅና ያለው ሄኖክ እራሱ እንደፃፈው የሚታመንለት ነው
2ኛው፦ Two Henok ና ስላቨኒክ ሄኖክ የሚባለው ነው በይዘቱ ከግእዙ ሄኖክ(One Henok) የሚለይ መፅሀፍ ነው በስላቪክ ቋንቋ ተፅፎ ተገኝቷል መፅሀፉን ያገኘው ፕ/ር ሶክሎፍ የሚባል ሰው ነው በቤልግሬድ የህዝብ ቤተ መዛግብት ውስጥ ነው ያገኘው አጥኚዎች እንደሚሉት ከግሪክ የተተረጎመ እንዳልሆነ መላምት ይሰጣሉ ይሄ መፅሀፈ ሄኖክ ጎዶሎ ነው
3ኛው፦ Three Henok ተብሎ የሚታወቀው ነው በእብራይስጥ ቋንቋ ነው ተፅፎ የተገኘው ይህ በብዙ አጥኚዎች ቀልብ ሊስብ ያልቻለ መፅሀፍ ነው ምክንያቱም አንደኛ ነገር መፅሀፉ ላይ እራቢ እሽማኤል የተባለ ሰው ከክ/ል/በሁዋላ በ164 አ/ም አካባቢ
እንደፃፈው ይናገራል ስለዚህ ሄኖክ መፅሀፈ ሄኖክን ከፃፈ በሁዋላ የተፃፈ መፅሀፍ ነው ተብሎ ስለሚታመን ትክክለኛውን ለማግኘት ይረዳል ብለው አጥኚዎች ስለማያምኑ ለጥናታቸው መሰረት ያደረጉት መፅሀፈ ሄኖክ አንድ ላይ ወይም የኢትዮጵያው ሄኖክ ላይ
ነው።
የኢትዮጵያው መፅሀፈ ሄኖክ በ5 ክፍል ይከፈላል። እርሱም፦
1ኛው ክፍል ፦ ስለ መላእክት ውድቀት የሚተርከው ክፍል ነው ይሄውም ከምእራፍ1-36 ያለው ክፍል ነው
2ኛው ክፍል፦ ስለ መፅሀፈ ምሳሌ ነው የሚናገረው ይሄውም ከምእራፍ37-71 ያለው ክፍል ነው ስለ አዳም፣ ስለ ሄዋን፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ሙክራብ ስለተለያዩ ነገሮች በምሳሌ እያደረገ
የሚናገርበት ክፍል ነው
3ኛው ክፍል፦ ስለ ቀን አቆጣጠር(Calendar) የሚተርክበት ክፍል ነው ይሄውም ከምእራፍ72-82 ያለው ሀሳብ ነው
4ኛው ክፍል፦ ራእይ ሄኖክ ይባላል ይህ ክፍል ለሄኖክ በእግዚአብሄር ገላጭነት በመላእክት እየተመራ ያየውን ራእይ
የሚናገርበት ክፍል ነው..... 👇👇👇
@And_Haymanot
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊት፣ታሪካዊትና ብሄራዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን በአለም ከምትታወቅባቸው አበይት መገለጫዎች ውስጥ በዋቢነት
የሚጠቀሱት በጥንታውያን ብሄራዊው ሊቃውንት ሲወርድ ሲዋረድ ተጠብቀው የቆዩት መፅሀፍቶቿ ዋነኛ ናቸው ከእነርሱም ውስጥ በአለም ላይ እስካሁን የሌለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ተጠብቆ የቆየው መፅሀፈ ሄኖክ አንዱ ነው ፈረንጆቹ በ18ኛው መቶ ክ/ዘመን ድረስ ቤታችን መተው እስኪዘርፉን ድረስ ስለ መፅሀፉ ሙሉ እውቀት አልነበራቸውም ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል እንዲሉ እኛ አንቀላፍተን እነርሱ ነቅተው የወሰዱትን ምስጢር እየበረበሩት ይገኛል በየአመቱ የበቁ ሊቃውንት የሚባሉ እስከ 250 የሚደርሱ በቫቲካን በመፅሀፈ ሄኖክ
ላይ ጉባኤ ይቀመጣሉ የመገኛዋ ምድር ኢትዮጵያ ያላት ተወካይ አንድ ብቻ ነው ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የመፅሀፉ ሙሉ ባለቤት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ግን በጉባኤው ላይ ሰው የላትም እንዲ ጉባኤ የሚሰየምለት መፅሀፈ ሄኖክ ብዙ ይባልለታል እንዲያውም የአውሮፓ ህዳሴ ስኬት የመፅሀፈ ሄኖክን ምስጢር ፈረንጆቹ መፍታታቸው ዋነኛ ምክንያት ነው የሚሉ አሉ ለዚህም በህዳሴው
ዘመን በ18ኛው መቶ ክ/ዘመን ከእኛ ከመሰረቁ ጋር ያያይዙታል ከውጪ በብዙ ብር የምንገዛቸው መድሀኒቶች እራሱ ከመፅሀፉ የተቀዱ እውቀቶች ውጤት ናቸው ይባላል በምእራቡ አለም በተለይ አሁን አሁን መፅሀፈ ሄኖክ ስሙ እጅግ ከበዙ ግኝቶችና ምርምሮች ጋር ይነሳል እንዲያውም ሳይንስ ከገደበው የምድራችን እውቀትም በላይ ይጠቀሙበታል ይባላል ይህን ሁሉ ከውጪ ብንሰማም በሀገር ቤት ግን ምንም የማይባልለት ነውና ለመሆኑ
መፅሀፈ ሄኖክ ምንድነው? ሄኖክስ ማነው? ብለን ጥያቄ እናነሳለን ሄኖክ ማለት ተሀድሶ ማለት ነው (የእናት ጡት ነካሾች የተሀድሶ መናፍቃንን ለመጥቀስ አይደለም) አዳም በምግብ ምክንያት
ብልየትን እንዳመጣ ሄኖክም ከምግብ ተከልክሎ ተሀድሶን አምጥቷልና አንድም ዛሬ በብሉይ ስጋ ገነት እንደገባ እኛም
በሁዋላ ተነስተን በሀዲስ ስጋ መንግስተ ሰማያት እንገባለንና
(ምንጭ፦ መፅሀፈ ሄኖክ አንድምታ ገፅ 1) ሄኖክ የያሬድ ልጅ ነው ልደቱን ወይም የዘር ሀረጉን ስንቆጥር አዳም ሴትን ይወልዳል ሴት ደሞ ሄኖስን ሄኖስ ቃይናንን ይወልዳል ቃይናን ደሞ መላልኤልን መላልኤል ያሬድን ይወልዳል ያሬድ ደሞ ሄኖክን ዘፍ 5:1-22 ሄኖክ የአዳም ሰባተኛ ትውልድ ነው
ስድስተኛው ትውልድ ያሬድ ሄኖክን ወልዶ ሄኖክ ደሞ ከሚስቱ ከእድኒ ማቱሳላን ይወልዳል ሄኖክ ባለ ዘመኑ ሁሉ በፍፁም እምነት እግዚአብሄርን እያገለገለ በምድር ላይ ለ 365 አመት ኖሯል ስለዚህ እንደ መፅሀፍ ቅዱስ አገላለፅ ዘፍ 5:24ላይ ሄኖክም
አካሄዱን ከእግዚአብሄር ጋር ስላደረገ አልተገኘም እግዚአብሄር ወስዶታልና ይላል ስለዚህ ሄኖክ ሞትን ሳይቀምስ ተሰውሮ ወይም ተወስዶ ሄዶዋል ማለት ነው በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ኤሊያስም
ቢያርግ የሄኖክ ግን ይለያል ምክንያቱም ሄኖክ ፓትራሪክ ነው ከጥፋት ውሀ በፊት የነበረ ሰው ነው በዛ ጊዜ የሰው ልጅ በክፋት በነበረበት ጊዜ ሄኖክ ሞትን ሳይቀምስ የጥንት በደል ወይም ምልሀተ ሀጢያት ሳይነካው ሞትን ሳያይ ሄዱዋልና። መፅሀፈ ሄኖክ አምላካዊ ከሚባሉ የመፅሀፍ ቅዱስ ቁጥሮች
በተለይም በኢ/ኦ/ተ//ቤ/ክን በ81 አሀዱ ላይ ያለ ነው አንድ መፅሀፍ አምላካዊ መፅሀፍ ለመባል በትንሹ 5ቱ አእማደ ምስጢርንና 7ቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ማካተት አለበት መፅሀፈ ሄኖክም እነዚን በሚገባ አካቶ ይዟል መፅሀፈ ሄኖክ በትንቢት፣ በታሪክም በተለያየ ገፅታው ጠቃሚ ነው ስለዚህ
አምላካዊ መፅሀፍ ነው በትንፋሰ እግዚአብሄር የተፃፈ ለራሱ ለሄኖክ የተገለፀ ነው የመጀመሪያ ፊደላት መገኘትና ሰማያዊ ምስጢር መገለፅ ጋር ተያይዞ ለሄኖክ የተገለፀለትን ነገር መፅሀፈ ሄኖክ ብለን የምንጠራው ውስጥ አካቶታል ለሄኖክ ጥበብን
በተመለከተ ስለ ፅሁፍ ጥበብ፣ ስለ ስነ-ፈለግ ጥበብ፣ ስለ ክዋክብት፣ ስለ ፀሀይ፣ ስለ ጨረቃ፣ ስለ ወር ስለ ንፋሳት... የመሳሰሉት ሀሳቦች ተገልፀውለት ለመጀመሪያ ጊዜ የጥበብ ሰው ሆኖ የተቀመጠ እንደሆነ በመፅሀፉ ሀሳብ ላይ እናገኘዋለን ከእርሱ
በፊትም ሆነ በሁዋላ እርሱ ያገኘውን ጥበብ ማንም ሰው እንዳላገኘ በራሱ ቃል ምስክርነት ሰጥቷል እንግዲህ እኔ ያየሁትን ራእይ እኔ ያየሁትን ግልፀት ከጥበብ፣ ከእውቀት ጋር በተገናኘ እኔ
እንዳየሁት ማንም አላየም ከሰውም የሚያየው የለም የሚል ሀሳብ
ተፅፎ እናገኛለን።
በመፅሀፈ ሄኖክ ላይ የበቃ እውቀት አለን የሚሉ እንኩዋን በብዙ ጉዳዮች ላይ ይከራከራሉ ከዛም በላይ ግምታዊ ትንታኔ የሚያበዙ ናቸው ከእዚህም አንዱ ሌላው ቀርቶ በፀሀፊው ማንነት ላይ
ጭምር ያለ መስማማታቸው ነው የአዳም ሰባተኛ ትውልድ ሄኖክ
በመላእክት ተመንጥቆ እንደፃፈው የሚስማሙ አሉ ሄኖክ ደሞ የማቱሳላ አባት የኖህ ደሞ ቅድመ አያት ነው እነዚህ ሄኖክ በፈጣሪ በጎ ፍቃድ በመላእክት እርዳታ የተገለፀለትን እውቀት ነው የፃፈው ሲሉ በሌላ ወገን ደግሞ መፅሀፉ በተለያየ ዘመን ተፅፏል
የሚሉም አልታጡም ለዚህም የሚያቀርቡት ምክንያት እየተጨመሩ
የመጡ ምእራፎች አሉ የሚል ነው እነዚህ ወገኖች በቀዳሚነት የሚጠቅሱት ስለመላእክት የሚናገረው ክፍል በቅ/ል/ክ 200 ተፅፏል ሲሉ ተጨመረ የሚሏቸው ደግሞ በአመተ ምህረት
የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ተፅፏል ይላሉ ከፀሀፊው ማንነት ሌላ ተፃፈ የሚሉበት ክፍለ ዘመን ጭምር አንዱ ልዩነታቸው መሆኑን ያሳያል እንዲ ሊቃውንቱ የሚነታረኩበት እስከ አሁን 3 የሚታወቁ መፅሀፈ ሄኖክ አሉ
1ኛው፦ One Henok የሚባለው አምስት ክፍል ያለው በእኛ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ሙሉ እውቅና ያለው ሄኖክ እራሱ እንደፃፈው የሚታመንለት ነው
2ኛው፦ Two Henok ና ስላቨኒክ ሄኖክ የሚባለው ነው በይዘቱ ከግእዙ ሄኖክ(One Henok) የሚለይ መፅሀፍ ነው በስላቪክ ቋንቋ ተፅፎ ተገኝቷል መፅሀፉን ያገኘው ፕ/ር ሶክሎፍ የሚባል ሰው ነው በቤልግሬድ የህዝብ ቤተ መዛግብት ውስጥ ነው ያገኘው አጥኚዎች እንደሚሉት ከግሪክ የተተረጎመ እንዳልሆነ መላምት ይሰጣሉ ይሄ መፅሀፈ ሄኖክ ጎዶሎ ነው
3ኛው፦ Three Henok ተብሎ የሚታወቀው ነው በእብራይስጥ ቋንቋ ነው ተፅፎ የተገኘው ይህ በብዙ አጥኚዎች ቀልብ ሊስብ ያልቻለ መፅሀፍ ነው ምክንያቱም አንደኛ ነገር መፅሀፉ ላይ እራቢ እሽማኤል የተባለ ሰው ከክ/ል/በሁዋላ በ164 አ/ም አካባቢ
እንደፃፈው ይናገራል ስለዚህ ሄኖክ መፅሀፈ ሄኖክን ከፃፈ በሁዋላ የተፃፈ መፅሀፍ ነው ተብሎ ስለሚታመን ትክክለኛውን ለማግኘት ይረዳል ብለው አጥኚዎች ስለማያምኑ ለጥናታቸው መሰረት ያደረጉት መፅሀፈ ሄኖክ አንድ ላይ ወይም የኢትዮጵያው ሄኖክ ላይ
ነው።
የኢትዮጵያው መፅሀፈ ሄኖክ በ5 ክፍል ይከፈላል። እርሱም፦
1ኛው ክፍል ፦ ስለ መላእክት ውድቀት የሚተርከው ክፍል ነው ይሄውም ከምእራፍ1-36 ያለው ክፍል ነው
2ኛው ክፍል፦ ስለ መፅሀፈ ምሳሌ ነው የሚናገረው ይሄውም ከምእራፍ37-71 ያለው ክፍል ነው ስለ አዳም፣ ስለ ሄዋን፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ሙክራብ ስለተለያዩ ነገሮች በምሳሌ እያደረገ
የሚናገርበት ክፍል ነው
3ኛው ክፍል፦ ስለ ቀን አቆጣጠር(Calendar) የሚተርክበት ክፍል ነው ይሄውም ከምእራፍ72-82 ያለው ሀሳብ ነው
4ኛው ክፍል፦ ራእይ ሄኖክ ይባላል ይህ ክፍል ለሄኖክ በእግዚአብሄር ገላጭነት በመላእክት እየተመራ ያየውን ራእይ
የሚናገርበት ክፍል ነው..... 👇👇👇
መፅሀፈ ሄኖክ
👆👆👆...5ኛ ክፍል፦ መልዕክተ ሄኖክ ወይም የሄኖክ መልእክት ይባላል ለልጁ ለማቱሳላ ማቱሳላ ደግሞ ከእርሱ በሁዋላ ለሚመጡት ለትውልዶቹ እንዲያስተላልፍ የፃፈለት መልእክት ነው
ስለዚህ ሙሉ የሆነውና ትክክለኛው የሄኖክ መፅሀፍን በተመለከተ
ታማኝ የሆነው የኢትዮጵያው መፅሀፈ ሄኖክ እንደሆነ ብዙ ሊቃውንት ይስማማሉ ለዚህም ነው ምስጢሩን ለመፍታት ጉባኤ እየተቀመጡ የሚመካከሩበት።
ይቀጥላል
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
👆👆👆...5ኛ ክፍል፦ መልዕክተ ሄኖክ ወይም የሄኖክ መልእክት ይባላል ለልጁ ለማቱሳላ ማቱሳላ ደግሞ ከእርሱ በሁዋላ ለሚመጡት ለትውልዶቹ እንዲያስተላልፍ የፃፈለት መልእክት ነው
ስለዚህ ሙሉ የሆነውና ትክክለኛው የሄኖክ መፅሀፍን በተመለከተ
ታማኝ የሆነው የኢትዮጵያው መፅሀፈ ሄኖክ እንደሆነ ብዙ ሊቃውንት ይስማማሉ ለዚህም ነው ምስጢሩን ለመፍታት ጉባኤ እየተቀመጡ የሚመካከሩበት።
ይቀጥላል
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መፅሀፈ ሄኖክ
ክፍል 2
ሄኖክ መፅሀፈ ሄኖክን ከፃፈ በሁዋላ መፅሀፉን ለልጁ ለማቱሳላ ይሰጠዋል ማቱሳላም ለላሜህ ላሜህም ለኖህ ኖህም ከጥፋት ውሀ በሁዋላ ለልጆቹ ይሰጣቸዋል እንዲህ እያለ እስከ ንጉስ
ሰሎሞን ዘመን ይደርሳል በንጉስ ሰሎሞን ጊዜ ኢትዮጵያዊው የንጉስ ሰሎሞን ልጅ ቀዳማዊ ምኒሊክ ታቦተ ፅዮንን ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ይዞ ሲመጣ ይዟቸው ከመጣው መፅሀፍት ውስጥ አንዱ መፅሀፈ ሄኖክ ነው ኢትዮጵያም ይሄን መፅሀፍ ጠብቃው ለብዙ ዘመናት ቆይታለች መፅሀፈ ሄኖክ ከኢትዮጵያ አጠፋፉ መፅሀፈ ሄኖክን ሰርቆ የወሰደው ጀምስ ብሩስ የተባለ ሰው ነው፡፡
@And_Haymanot
ጀምስ ብሩስ የአባይን ምንጭ ያገኘ እየተባለ ት/ቤት ሁሉ ያስተምሩናል ይህ ሰው የሰይጣን አምላኪዎች የምስጢር
ማህበራት አባል ነው በምእራቡ አለም ግን ያልተደበቀው እውነታ መፅሀፈ ሄኖክን ሰርቆ መውሰዱ ነው ፀሀፍቶች በ18ኛው መቶ ክ/ ዘመን ከኢትዮጵያ ስላመጣው መፅሀፍ አለም አወቀው እያሉ ይፅፋሉ እውነታው ግን በሀገር አሳሽነት ወደ ሀገራችን ገብቶ በጣና
ሀይቅ ከሚገኙት ገዳማትና ቤተ ክርስቲያናት ሶስት መፅሀፈ ሄኖኮችን ሰርቆ መውሰዱ ነው ከሶስቱ መፅሀፍት ውስጥ ሁለቱ በእንግሊዝና በፈረንሳይ ቤተ መፅሀፍት ሲገኙ አንዱ በጀምስ ብሩስ እጅ እንደነበረ ተፅፏል የሚገርመው ከኢትዮጵያ የተሰረቀው
መፅሀፈ ሄኖክ የተሟላ መሆኑና ትክክለኛነቱ ባይካድም የተቀዳ ነው
እያሉ ለመቀበል ሲተናነቃቸው ይስተዋላል እውነታውንም ለመሻር
የሚያቀርቡት ሀሳብ ዋነኛው መፅሀፍ ወይም የመጀመሪያው ሄኖክ የፃፈው መፅሀፍ በኢትዮጵያውያን ቋንቋ በግእዝ አይፃፍም ነው የሚሉት እናም አንድም ከግሪክ አልያም ከላቲን ተተርጉሞ
ኢትዮጵያውያን ጠብቀውት ቆይተዋል ባይ ናቸው ነገር ግን የግእዙ መፅሀፈ ሄኖክ ተተርጉሞ ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ ኢትዮጵያው ሙሉ መፅሀፍ በሌላም ቋንቋ ተፅፎ ይገኝ ነበር ዳሩ ግን አልተገኘምና በዚህ እንኩዋን አሳማኝ እንዳልሆነ እንመለከታለን እነሱ
እንደሚሉት ከግሪክ ወይም ከላቲን አልያም ከአራማይክ ቢተረጎም
ኖሮ የኛ ሙሉ እንደሆነው እነሱም ጋር ሙሉ ይገኝ ነበርና። በእርግጥ በኢትዮጵያ የተገኙ ድንቅ ግኝቶችን ምእራባውያን ለመቀበል ሲከብዳቸው ይሄ የመጀመሪያው አይደለም የአክሱም
ሀውልት፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጎንደር ቤተ መንግስት ህንፃዎች በኢትዮጵያውያን አልተገነቡም ሊገነቡም አይችሉም ብለው እውነታው አልዋጥ ብሏቸው ሲከራከሩ
ይደመጣሉ በዚም ተባለ በዚያ የተሟላው መፅሀፈ ሄኖክ በኢትዮጵያ ብቻ መገኘቱን ሊክዱ አይቻላቸውም ከዚህም ከመፅሀፈ ሄኖክ ጋር ኢትዮጵያን ለየት የሚያደርጋት ነገር አለ ይህም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ብቻ ናትና አምላካዊ ነው ብላ በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ያካተተችው እስከ ቅርብ አስርት አመታት የኢትዮጵያ አካል የነበረችው የኤርትራ ቤተ ክርስቲያንም ይህን ትጋራታለች።
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ለምን አምላካዊ መፅሀፍ አደረገችው?
በመጀመሪያ በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ የነብይነት ፀባይ ምንድነው ብለን ስንጠይቅ የሚመጣውን ማየትና ያለፈውን መናገር ነው ሄኖክም እንደ ነብይ ነው ትንቢት ይናገራል ከተናገረውም ነገር ውስጥ ለምሳሌ፦ ስለ ክርስቶስ መወለድ፣ ስለ ዳግም ምፅአትና ስለ መሳሰሉት ነገሮች ተንብዮዋል እነዚ ሁሉ ሄኖክ ከአምላኩ
የተገለፁለት ነገሮች ናቸው ይህንንም ያየው በእግዚአብሄር ገላጭነት በመልአክት መሪነት ነው ትልቁ ሊሰመርበት የሚገባው ነገር ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ኦ/ተ/ቤ/ክን ውጪ አምላካዊ ነው ብላ የተቀበለች ሀገር የለችም ይህንንም አለማድረጋቸው
የሚያስወቅሳቸው ነው። መፅሀፈ ሄኖክ ታማኝነቱን በምንመለከትበት ጊዜ ሀዋርያው ይሁዳ በምእራፍ 1:14 ላይ ሄኖክ የተናገረውን ትንቢት በራሱ መልእክት ላይ ገልፆት ይገኛል ስለዚህ ማንኛውም መፅሀፍ ደግሞ አምላካዊ
ነው ለመባል ማስረጃው በአበው መጠቀሱ ነው ከአበው ደሞ ሀዋርያ የሆነው ይሁዳ ጠቅሶት ይገኛል እንዲሁም በ2ኛ ጴጥ 2:1 ላይ ሄኖካዊ የፅሁፍ ይዘት ያለበትን ፅሁፍ እናገኛለን ይህም ስለ መላእክት መታሰርና ለፍርድ ተጠብቀው መኖራቸውን ቅዱስ
ጴጥሮስ በሚገልፅበት ጊዜ ኖህን መጥቀሱና በመፅሀፈ ሄኖክም ላይ መላእክት እነ አዛዝኤል ለፍርድ መጠበቃቸውን ሄኖክም ጴጥሮስም ገልፀውታል ይሁዳና ጴጥሮስ ከሀዋርያት ናቸው የተጠቀሱት በቀጣይ ደግሞ ስንመለከት ብዙ አበው በተለያዩ ትምህርቶቻቸውና ፁሁፎቻቸው መፅሀፈ ሄኖክን ጠቅሰውታል ከእነዚህም ውስጥ ቅዱስ አውግስጢንና ሰማእቱ ጀስቲን
ይጠቀሳሉ ስለዚህ መፅሀፉ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በአበው መካከል ይከበራል ቤተ ክርስቲያንም ይሄን ባህልና ስርአት ተከትላ ጠብቃው ትገኛለች። ጀምስ ብሩስ የሰረቀው ሶስቱ መፅሀፍት ዛሬ ሰለጠነ የምንለው አለም አጥቶት የነበረውን መፅሀፍ በእጁ ያስገባ ዘንድ እድል ፈጥሮለታል ከግሪክ ወይም ከላቲን ተተረጎመ እያሉ የግእዙን
መሰረተ መነሻ መፅሀፍትነት ለመቀበል ቢተናነቃቸውም ግእዙን ግን ወደ ኢንግሊዘኛ፣ ጀርመንኛና ከ50 በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ምስጢሩን ሊፈቱ ጉባኤ እስከ መመስረት ድረስ ይለፋሉ የመፅሀፉ መገኛ ሀገር ኢትዮጵያ በቅርብ የተገነጠለችው ኤርትራ
ስትጋራት ብቸኛ መለኮታዊ መፅሀፍ አድርጋ በመፅሀፍ ቅዱሷ ውስጥ በማካተት ትለያቸዋለች።።።።። ግን ሌሎቹ ሀገራት መፅሀፈ ሄኖክን መለኮታዊ ወይም አምላካዊ መፅሀፍ አይደለም ብለው ለምን በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ አላካተቱትም???
ይቀጥላል
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክፍል 2
ሄኖክ መፅሀፈ ሄኖክን ከፃፈ በሁዋላ መፅሀፉን ለልጁ ለማቱሳላ ይሰጠዋል ማቱሳላም ለላሜህ ላሜህም ለኖህ ኖህም ከጥፋት ውሀ በሁዋላ ለልጆቹ ይሰጣቸዋል እንዲህ እያለ እስከ ንጉስ
ሰሎሞን ዘመን ይደርሳል በንጉስ ሰሎሞን ጊዜ ኢትዮጵያዊው የንጉስ ሰሎሞን ልጅ ቀዳማዊ ምኒሊክ ታቦተ ፅዮንን ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ይዞ ሲመጣ ይዟቸው ከመጣው መፅሀፍት ውስጥ አንዱ መፅሀፈ ሄኖክ ነው ኢትዮጵያም ይሄን መፅሀፍ ጠብቃው ለብዙ ዘመናት ቆይታለች መፅሀፈ ሄኖክ ከኢትዮጵያ አጠፋፉ መፅሀፈ ሄኖክን ሰርቆ የወሰደው ጀምስ ብሩስ የተባለ ሰው ነው፡፡
@And_Haymanot
ጀምስ ብሩስ የአባይን ምንጭ ያገኘ እየተባለ ት/ቤት ሁሉ ያስተምሩናል ይህ ሰው የሰይጣን አምላኪዎች የምስጢር
ማህበራት አባል ነው በምእራቡ አለም ግን ያልተደበቀው እውነታ መፅሀፈ ሄኖክን ሰርቆ መውሰዱ ነው ፀሀፍቶች በ18ኛው መቶ ክ/ ዘመን ከኢትዮጵያ ስላመጣው መፅሀፍ አለም አወቀው እያሉ ይፅፋሉ እውነታው ግን በሀገር አሳሽነት ወደ ሀገራችን ገብቶ በጣና
ሀይቅ ከሚገኙት ገዳማትና ቤተ ክርስቲያናት ሶስት መፅሀፈ ሄኖኮችን ሰርቆ መውሰዱ ነው ከሶስቱ መፅሀፍት ውስጥ ሁለቱ በእንግሊዝና በፈረንሳይ ቤተ መፅሀፍት ሲገኙ አንዱ በጀምስ ብሩስ እጅ እንደነበረ ተፅፏል የሚገርመው ከኢትዮጵያ የተሰረቀው
መፅሀፈ ሄኖክ የተሟላ መሆኑና ትክክለኛነቱ ባይካድም የተቀዳ ነው
እያሉ ለመቀበል ሲተናነቃቸው ይስተዋላል እውነታውንም ለመሻር
የሚያቀርቡት ሀሳብ ዋነኛው መፅሀፍ ወይም የመጀመሪያው ሄኖክ የፃፈው መፅሀፍ በኢትዮጵያውያን ቋንቋ በግእዝ አይፃፍም ነው የሚሉት እናም አንድም ከግሪክ አልያም ከላቲን ተተርጉሞ
ኢትዮጵያውያን ጠብቀውት ቆይተዋል ባይ ናቸው ነገር ግን የግእዙ መፅሀፈ ሄኖክ ተተርጉሞ ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ ኢትዮጵያው ሙሉ መፅሀፍ በሌላም ቋንቋ ተፅፎ ይገኝ ነበር ዳሩ ግን አልተገኘምና በዚህ እንኩዋን አሳማኝ እንዳልሆነ እንመለከታለን እነሱ
እንደሚሉት ከግሪክ ወይም ከላቲን አልያም ከአራማይክ ቢተረጎም
ኖሮ የኛ ሙሉ እንደሆነው እነሱም ጋር ሙሉ ይገኝ ነበርና። በእርግጥ በኢትዮጵያ የተገኙ ድንቅ ግኝቶችን ምእራባውያን ለመቀበል ሲከብዳቸው ይሄ የመጀመሪያው አይደለም የአክሱም
ሀውልት፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጎንደር ቤተ መንግስት ህንፃዎች በኢትዮጵያውያን አልተገነቡም ሊገነቡም አይችሉም ብለው እውነታው አልዋጥ ብሏቸው ሲከራከሩ
ይደመጣሉ በዚም ተባለ በዚያ የተሟላው መፅሀፈ ሄኖክ በኢትዮጵያ ብቻ መገኘቱን ሊክዱ አይቻላቸውም ከዚህም ከመፅሀፈ ሄኖክ ጋር ኢትዮጵያን ለየት የሚያደርጋት ነገር አለ ይህም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን ብቻ ናትና አምላካዊ ነው ብላ በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ያካተተችው እስከ ቅርብ አስርት አመታት የኢትዮጵያ አካል የነበረችው የኤርትራ ቤተ ክርስቲያንም ይህን ትጋራታለች።
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ለምን አምላካዊ መፅሀፍ አደረገችው?
በመጀመሪያ በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ የነብይነት ፀባይ ምንድነው ብለን ስንጠይቅ የሚመጣውን ማየትና ያለፈውን መናገር ነው ሄኖክም እንደ ነብይ ነው ትንቢት ይናገራል ከተናገረውም ነገር ውስጥ ለምሳሌ፦ ስለ ክርስቶስ መወለድ፣ ስለ ዳግም ምፅአትና ስለ መሳሰሉት ነገሮች ተንብዮዋል እነዚ ሁሉ ሄኖክ ከአምላኩ
የተገለፁለት ነገሮች ናቸው ይህንንም ያየው በእግዚአብሄር ገላጭነት በመልአክት መሪነት ነው ትልቁ ሊሰመርበት የሚገባው ነገር ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ኦ/ተ/ቤ/ክን ውጪ አምላካዊ ነው ብላ የተቀበለች ሀገር የለችም ይህንንም አለማድረጋቸው
የሚያስወቅሳቸው ነው። መፅሀፈ ሄኖክ ታማኝነቱን በምንመለከትበት ጊዜ ሀዋርያው ይሁዳ በምእራፍ 1:14 ላይ ሄኖክ የተናገረውን ትንቢት በራሱ መልእክት ላይ ገልፆት ይገኛል ስለዚህ ማንኛውም መፅሀፍ ደግሞ አምላካዊ
ነው ለመባል ማስረጃው በአበው መጠቀሱ ነው ከአበው ደሞ ሀዋርያ የሆነው ይሁዳ ጠቅሶት ይገኛል እንዲሁም በ2ኛ ጴጥ 2:1 ላይ ሄኖካዊ የፅሁፍ ይዘት ያለበትን ፅሁፍ እናገኛለን ይህም ስለ መላእክት መታሰርና ለፍርድ ተጠብቀው መኖራቸውን ቅዱስ
ጴጥሮስ በሚገልፅበት ጊዜ ኖህን መጥቀሱና በመፅሀፈ ሄኖክም ላይ መላእክት እነ አዛዝኤል ለፍርድ መጠበቃቸውን ሄኖክም ጴጥሮስም ገልፀውታል ይሁዳና ጴጥሮስ ከሀዋርያት ናቸው የተጠቀሱት በቀጣይ ደግሞ ስንመለከት ብዙ አበው በተለያዩ ትምህርቶቻቸውና ፁሁፎቻቸው መፅሀፈ ሄኖክን ጠቅሰውታል ከእነዚህም ውስጥ ቅዱስ አውግስጢንና ሰማእቱ ጀስቲን
ይጠቀሳሉ ስለዚህ መፅሀፉ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በአበው መካከል ይከበራል ቤተ ክርስቲያንም ይሄን ባህልና ስርአት ተከትላ ጠብቃው ትገኛለች። ጀምስ ብሩስ የሰረቀው ሶስቱ መፅሀፍት ዛሬ ሰለጠነ የምንለው አለም አጥቶት የነበረውን መፅሀፍ በእጁ ያስገባ ዘንድ እድል ፈጥሮለታል ከግሪክ ወይም ከላቲን ተተረጎመ እያሉ የግእዙን
መሰረተ መነሻ መፅሀፍትነት ለመቀበል ቢተናነቃቸውም ግእዙን ግን ወደ ኢንግሊዘኛ፣ ጀርመንኛና ከ50 በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ምስጢሩን ሊፈቱ ጉባኤ እስከ መመስረት ድረስ ይለፋሉ የመፅሀፉ መገኛ ሀገር ኢትዮጵያ በቅርብ የተገነጠለችው ኤርትራ
ስትጋራት ብቸኛ መለኮታዊ መፅሀፍ አድርጋ በመፅሀፍ ቅዱሷ ውስጥ በማካተት ትለያቸዋለች።።።።። ግን ሌሎቹ ሀገራት መፅሀፈ ሄኖክን መለኮታዊ ወይም አምላካዊ መፅሀፍ አይደለም ብለው ለምን በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ አላካተቱትም???
ይቀጥላል
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ኃጥእ ነኝ ማለት ብቻ እውነተኛ ትህትና እንዳይደለ በእውነት እናገራለሁ፣ እውነተኛ ትህትናስ ትሩፋት መስራት ነው፡፡
🍃ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ🍃
@And_Haymanot
@AHati_Haymanot
መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንላችሁ
🍃ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ🍃
@And_Haymanot
@AHati_Haymanot
መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንላችሁ
መፅሀፈ ሄኖክ
ክፍል 3
ሌሎች የአለማችን ሀገራት መፅሀፈ ሄኖክን ለምን መለኮታዊ
ወይም አምላካዊ አይደለም ብለው በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ
አላካተቱትም?
ሌሎቹ ሀገራት ወይም ሀይማኖቶች ያላካተቱበት ምክንያት
የአፈንጋጮቹ መላእክት ነገረ ታሪክ ነው በመፅሀፈ ሄኖክ አዛዝኤል
በሚባል መልአክ መሪነት 200 መላእክት ከእግዚአብሄር ትእዛዝ
አፈንግጠው ወደ መሬት ወርደዋል ተብሎ ተፅፏል ወደ መሬት
የወረዱበትም ምክንያት ከሰው ልጆች ፍጥረታት በተለይም
በሴቶች ውበት ተማርከው ነው እናም በሀፀ ዝሙት ተነድፈው
ከሰው ልጆች ጋር ለመዘሞትና ልጆች ለመውለድ ወደ መሬት
ይወርዳሉ ከፈጣሪም ትእዛዝ ስለ አፈነገጡ ላለመካካድ
ተማምለው ወደ ምድር የወረዱበትንም ተራራ ኤርሞን እንዳሉት
ተፅፏል ኤርሞን ማለት አንድ ሆነን ተስማምተናል ላለመካካድ
ተማምለናል ለጥፋታችንም እርግማን ቢመጣብን በአንድነት
እንቀበለዋለን ማለት ነው።
@And_Haymanot
እነዚህ አፈንጋጭ መልአክት ለሰው ልጆች ማሳየት የሌለባቸውን
ክፉ ወይም ባእድ ነገሮችን አሳይተዋቸዋል ከአሳዩዋቸውም ነገሮች
ውስጥ ስለ ምትሀት፣ ስለ ጥንቆላ፣ ስለ ሞአርትና ስለተለያዩ
ነገሮች አስተምረዋቸዋል ከእዚህም በሁዋላ ፍዳቸው
እንደማይዘገይና ፈጥኖ እንደሚመጣ ሄኖክ ወቃሽ ሆኖ እንደቀረበ
የሚያትት ክፍል ነው እናም ይህ ደሞ መለኮታዊ አይደለም
መልአክት ፆታ የላቸውም ስለዚህ አያገቡም በማለት በመፅሀፍ
ቅዱስ ውስጥ እንዳይካተት ምክንያት ሆኗል።
ነገር ግን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለዚህ መልስ አላት እርሱም
ሁለትና ከዚያ በላይ በሚተነተንበት አንድምታ መልአክት በቀጥታ
ወረዱ ከሰው ልጆች ፍጥረታትም ጋር ዝሙት ፈፅመዋል አይደለም
ፍቺው ይህም ታሪክ ከስር መሰረቱ ሲተነተን አዳም በአቤል ፈንታ
ሴትን ይወልዳል የሴት ልጆችም ከቃዬል ልጆች በተለየ
ንፅህናቸውን ጠብቀው ደብረ ቅዱስ በሚባል ቦታ በተባህቶት
ይኖሩ ነበር የቃዬል ልጆች ደግሞ እርስ በእርሳቸው ሲንጠላጠሉ
ማለትም በፍትዎት ሲጫወቱ፣ ሲዳሩ፣ ሲዘፍኑ ይኖሩ ነበር በዚህም
ጊዜ ደቂቀ ሴት\የሴት ልጆች/ የደቂቀ ቃዬል \የቃዬል ልጆች/
በዝሙት ሲንጠላጠሉ በማየታቸው 200 ደቂቀ ሴት ከደብረ
ቅዱሳቸው ወርደው ከደቂቀ ቃዬል ጋር እርስ በእርሳቸው ተጋብተው
ግዙፉን ልጆችን ሊወልዱ ቻሉ ደቂቀ ሴትም ከደቂቀ ቃዬል
ለወለዷቸው ልጆች ለደቂቀ ቃዬል ያልተገለወውን ለምሳሌ፦ ስለ
ጦርት ስልት፣ ስለ ጦር መሳሪያዎች የመስራት ጥበብ፣ ስለ
ቅንድብ መኩዋካል፣ ስለ መአድናት፣ ስለ አለም መለወጥ፣ ስለ
መድሀኒት መቀመም፣ ስለ አፈርን ወደ ብረት መቀየር፣ ስለ ኮኮብ
ቆጠራ፣ ስለ ጊዜ ቀመርና... ስለ መሳሰሉት የበዛ ምስጢራትን
ገልፀውላቸዋል ልብ በሉ ይህ ከፈጣሪ ትእዛዝ ውጪና ለደቂቀ
ቃዬል ያልተገለጠ ነገር ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ የወለዷቸው ልጆች እጅግ በጣም ግዙፋን
መሆናቸው ነው እነዚህንም ግዙፋን ኔፊሊ እያለ ሄኖክ ይጠራቸዋል
ኔፊሊም በእውቀትና በአካል ስለገዘፉ በሰው ልጆች ላይ ገዢ ሆኑ
በምድርም ላይ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ጨርሰው ፊታቸውን ወደ
ሰው ልጆች አዞሩ ደማቸውንም እስከ መጠጣት ደረሱ የሰው
ልጆችም እነሱን መመገብ እስኪያቅታቸው ድረስ የሰውን የላብ
ፍሬ ሁሉ ጨረሱ ከዛን ተመልሰው ሰዎችን ለመብላት ተነሱ
የመላእክቱ ወይም የደቂቀ ሴት ልጆችም በሰው ልጆች ላይ
የሚሰሩት ግፍ በረታ ይህም የሰው ልጆችን ዋይታ አበዛ ዋይታውም
እስከ ሰማየ ሰማያት ዘልቆ ለፈጣሪ ተሰማ እናም ፈጣሪ ኮብላይ
መላእክቱን \ደቂቀ ሴትን/ ይቀጡ ዘንድ እነ ቅዱስ ኡራኤልን ልኮ
በጥልቁ የምድር ጉድጉዋድ በጨለማ ይታሰሩ ዘንድ አደረገ ነገር
ግን ልጆቻቸው የሚፈፅሙት ሀጢአት አልቆመምና በዚህም የተነሳ
የምድርን ፍጥረታት ሁሉ በንፍር ውሀ ሊቀጣ እግዚአብሄር አምላክ
ወሰነ በሚል የኖህን ዘመን የጥፋት ውሀ \ማይ አይህ/ ከስር
መሰረቱ የተነተነው መፅሀፈ ሄኖክ ነው የአዳም አስረኛ ትውልድ
ኖህም ከቤተሰቡና ከተመረጡ የፍጥረታት ዘሮች ጋር እንዴት
እንደሚተርፍ ከፈጣሪ የተነገረውን በማስተላለፍ ፍጥረታት በምድር
ላይ የቀጠሉበትን ትእዛዝንም የፃፈው ሄኖክ ነው።
እናም በመፅሀፈ ሄኖክ ላይ ሄኖክ ኮብላይ መላእክት ብሎ
የጠቀሳቸው የሰማይ መልአክትን ሳይሆን በቅድስና በደብረ ቅዱስ
ይኖሩ የነበሩትን ደቂቀ ሴትን ነው እኚህ ኮብላይ መልአክት\ደቂቀ
ሴት/ ዘፍ 6:4 እንዲ ብሎ ይገልፃቸዋል
በእዚያ ወራት ኔፊሊም በምድር ላይ ነበሩ፤ ደግሞም ከዚያ በሁዋላ
የእግዚአብሄር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች ባገቡ ጊዜ ልጆችን
ወለዱላቸው፤ እነርሱም በድሮ ዘመን ስማቸው የታወቀ ሀያላን
ሆኑ። በማለት የደቂቀ ሴትን ልጆች ልክ እንደ ሄኖክ ኔፊሊ እያለ
ሲጠራቸው የደቂቀ ቃዬል ልጆችን ያገቡትን ደቂቀ ሴትን ደግሞ
የእግዚአብሄር ልጆች እያለ ይጠራቸዋል።
እነደገናም በ2ኛ ጴጥ 2:4-5 ላይ ደግሞ እግዚአብሄር ሀጢአትን
ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ
ጉድጉዋድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው ለቀደመውም
አለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ፅድቅን የሚሰብከውን ኖህን
አድኖ በሀጢአተኞች አለም ላይ የጥፋት ውሀ ካገረገ...እያለ
ኮብላይ መላእክቱን\ደቂቀ ሴት/ ለፍርድ እንደሚጠበቁ የኮብላይ
መላእክቱ ልጆች ላይ ደግሞ ለቀደመው አለም ሳይራራ በኖህ
ዘመን የጥፋት ውሀን እንዳወረደ ይገልፃል።
የሚገርመው ነገር ቃል በቃል ደቂቀ ሴትን መልአክት ብለው
ሄኖክም ቅዱስ ጴጥሮስም ገልፀዋቸዋል ታዲያ ለምን የቅዱስ
ጴጥሮስን መልእክት ተቀብለው የሄኖክን መፅሀፍ አንቀበልም አሉ
ስንል ጥያቄያችን መልስ አያገኝም
ማስተዋል ያለብን ነገር በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዎች መልአክ
እየተባሉ ተጠርተዋል ለዚህም ምስክራችን
ራእ 3:1 በሰርዴስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ፃፍ።
ራእ 3:7 በፊልድልፍያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ፃፍ።
ራእ 3:14 በሎዶቅያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ፃፍ።
ተብሎ እናገኛለን መቼም የሰርዴስ፣ የፊልድልፍያና የሎዶቅያ የቤተ
ክርስቲያን መልአኮች እውነተኛዎቹ ቅዱሳን መላእክት እንዳልሆኑ
እውን ነው ስለዚህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን መፅሀፈ ሄኖክን አምላካዊ
ቃል አድርጋ መቀበሏ ምንም ስህተት የለውም የመፅሀፈ ሄኖክ
ተቃዋሚዎች ግን መፅሀፈ ሄኖክን እያጣጣሉ ምስጢሩን ግን ሊፈቱ
ጉባኤ ይቀመጣሉ ማድረግ ያለባቸው ግን ልክ እንደ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/
ክን አምላካዊ መፅሀፍ ነው ብሎ መቀበል ነው።
ይቀጥላል
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክፍል 3
ሌሎች የአለማችን ሀገራት መፅሀፈ ሄኖክን ለምን መለኮታዊ
ወይም አምላካዊ አይደለም ብለው በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ
አላካተቱትም?
ሌሎቹ ሀገራት ወይም ሀይማኖቶች ያላካተቱበት ምክንያት
የአፈንጋጮቹ መላእክት ነገረ ታሪክ ነው በመፅሀፈ ሄኖክ አዛዝኤል
በሚባል መልአክ መሪነት 200 መላእክት ከእግዚአብሄር ትእዛዝ
አፈንግጠው ወደ መሬት ወርደዋል ተብሎ ተፅፏል ወደ መሬት
የወረዱበትም ምክንያት ከሰው ልጆች ፍጥረታት በተለይም
በሴቶች ውበት ተማርከው ነው እናም በሀፀ ዝሙት ተነድፈው
ከሰው ልጆች ጋር ለመዘሞትና ልጆች ለመውለድ ወደ መሬት
ይወርዳሉ ከፈጣሪም ትእዛዝ ስለ አፈነገጡ ላለመካካድ
ተማምለው ወደ ምድር የወረዱበትንም ተራራ ኤርሞን እንዳሉት
ተፅፏል ኤርሞን ማለት አንድ ሆነን ተስማምተናል ላለመካካድ
ተማምለናል ለጥፋታችንም እርግማን ቢመጣብን በአንድነት
እንቀበለዋለን ማለት ነው።
@And_Haymanot
እነዚህ አፈንጋጭ መልአክት ለሰው ልጆች ማሳየት የሌለባቸውን
ክፉ ወይም ባእድ ነገሮችን አሳይተዋቸዋል ከአሳዩዋቸውም ነገሮች
ውስጥ ስለ ምትሀት፣ ስለ ጥንቆላ፣ ስለ ሞአርትና ስለተለያዩ
ነገሮች አስተምረዋቸዋል ከእዚህም በሁዋላ ፍዳቸው
እንደማይዘገይና ፈጥኖ እንደሚመጣ ሄኖክ ወቃሽ ሆኖ እንደቀረበ
የሚያትት ክፍል ነው እናም ይህ ደሞ መለኮታዊ አይደለም
መልአክት ፆታ የላቸውም ስለዚህ አያገቡም በማለት በመፅሀፍ
ቅዱስ ውስጥ እንዳይካተት ምክንያት ሆኗል።
ነገር ግን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለዚህ መልስ አላት እርሱም
ሁለትና ከዚያ በላይ በሚተነተንበት አንድምታ መልአክት በቀጥታ
ወረዱ ከሰው ልጆች ፍጥረታትም ጋር ዝሙት ፈፅመዋል አይደለም
ፍቺው ይህም ታሪክ ከስር መሰረቱ ሲተነተን አዳም በአቤል ፈንታ
ሴትን ይወልዳል የሴት ልጆችም ከቃዬል ልጆች በተለየ
ንፅህናቸውን ጠብቀው ደብረ ቅዱስ በሚባል ቦታ በተባህቶት
ይኖሩ ነበር የቃዬል ልጆች ደግሞ እርስ በእርሳቸው ሲንጠላጠሉ
ማለትም በፍትዎት ሲጫወቱ፣ ሲዳሩ፣ ሲዘፍኑ ይኖሩ ነበር በዚህም
ጊዜ ደቂቀ ሴት\የሴት ልጆች/ የደቂቀ ቃዬል \የቃዬል ልጆች/
በዝሙት ሲንጠላጠሉ በማየታቸው 200 ደቂቀ ሴት ከደብረ
ቅዱሳቸው ወርደው ከደቂቀ ቃዬል ጋር እርስ በእርሳቸው ተጋብተው
ግዙፉን ልጆችን ሊወልዱ ቻሉ ደቂቀ ሴትም ከደቂቀ ቃዬል
ለወለዷቸው ልጆች ለደቂቀ ቃዬል ያልተገለወውን ለምሳሌ፦ ስለ
ጦርት ስልት፣ ስለ ጦር መሳሪያዎች የመስራት ጥበብ፣ ስለ
ቅንድብ መኩዋካል፣ ስለ መአድናት፣ ስለ አለም መለወጥ፣ ስለ
መድሀኒት መቀመም፣ ስለ አፈርን ወደ ብረት መቀየር፣ ስለ ኮኮብ
ቆጠራ፣ ስለ ጊዜ ቀመርና... ስለ መሳሰሉት የበዛ ምስጢራትን
ገልፀውላቸዋል ልብ በሉ ይህ ከፈጣሪ ትእዛዝ ውጪና ለደቂቀ
ቃዬል ያልተገለጠ ነገር ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ የወለዷቸው ልጆች እጅግ በጣም ግዙፋን
መሆናቸው ነው እነዚህንም ግዙፋን ኔፊሊ እያለ ሄኖክ ይጠራቸዋል
ኔፊሊም በእውቀትና በአካል ስለገዘፉ በሰው ልጆች ላይ ገዢ ሆኑ
በምድርም ላይ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ጨርሰው ፊታቸውን ወደ
ሰው ልጆች አዞሩ ደማቸውንም እስከ መጠጣት ደረሱ የሰው
ልጆችም እነሱን መመገብ እስኪያቅታቸው ድረስ የሰውን የላብ
ፍሬ ሁሉ ጨረሱ ከዛን ተመልሰው ሰዎችን ለመብላት ተነሱ
የመላእክቱ ወይም የደቂቀ ሴት ልጆችም በሰው ልጆች ላይ
የሚሰሩት ግፍ በረታ ይህም የሰው ልጆችን ዋይታ አበዛ ዋይታውም
እስከ ሰማየ ሰማያት ዘልቆ ለፈጣሪ ተሰማ እናም ፈጣሪ ኮብላይ
መላእክቱን \ደቂቀ ሴትን/ ይቀጡ ዘንድ እነ ቅዱስ ኡራኤልን ልኮ
በጥልቁ የምድር ጉድጉዋድ በጨለማ ይታሰሩ ዘንድ አደረገ ነገር
ግን ልጆቻቸው የሚፈፅሙት ሀጢአት አልቆመምና በዚህም የተነሳ
የምድርን ፍጥረታት ሁሉ በንፍር ውሀ ሊቀጣ እግዚአብሄር አምላክ
ወሰነ በሚል የኖህን ዘመን የጥፋት ውሀ \ማይ አይህ/ ከስር
መሰረቱ የተነተነው መፅሀፈ ሄኖክ ነው የአዳም አስረኛ ትውልድ
ኖህም ከቤተሰቡና ከተመረጡ የፍጥረታት ዘሮች ጋር እንዴት
እንደሚተርፍ ከፈጣሪ የተነገረውን በማስተላለፍ ፍጥረታት በምድር
ላይ የቀጠሉበትን ትእዛዝንም የፃፈው ሄኖክ ነው።
እናም በመፅሀፈ ሄኖክ ላይ ሄኖክ ኮብላይ መላእክት ብሎ
የጠቀሳቸው የሰማይ መልአክትን ሳይሆን በቅድስና በደብረ ቅዱስ
ይኖሩ የነበሩትን ደቂቀ ሴትን ነው እኚህ ኮብላይ መልአክት\ደቂቀ
ሴት/ ዘፍ 6:4 እንዲ ብሎ ይገልፃቸዋል
በእዚያ ወራት ኔፊሊም በምድር ላይ ነበሩ፤ ደግሞም ከዚያ በሁዋላ
የእግዚአብሄር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች ባገቡ ጊዜ ልጆችን
ወለዱላቸው፤ እነርሱም በድሮ ዘመን ስማቸው የታወቀ ሀያላን
ሆኑ። በማለት የደቂቀ ሴትን ልጆች ልክ እንደ ሄኖክ ኔፊሊ እያለ
ሲጠራቸው የደቂቀ ቃዬል ልጆችን ያገቡትን ደቂቀ ሴትን ደግሞ
የእግዚአብሄር ልጆች እያለ ይጠራቸዋል።
እነደገናም በ2ኛ ጴጥ 2:4-5 ላይ ደግሞ እግዚአብሄር ሀጢአትን
ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ
ጉድጉዋድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው ለቀደመውም
አለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ፅድቅን የሚሰብከውን ኖህን
አድኖ በሀጢአተኞች አለም ላይ የጥፋት ውሀ ካገረገ...እያለ
ኮብላይ መላእክቱን\ደቂቀ ሴት/ ለፍርድ እንደሚጠበቁ የኮብላይ
መላእክቱ ልጆች ላይ ደግሞ ለቀደመው አለም ሳይራራ በኖህ
ዘመን የጥፋት ውሀን እንዳወረደ ይገልፃል።
የሚገርመው ነገር ቃል በቃል ደቂቀ ሴትን መልአክት ብለው
ሄኖክም ቅዱስ ጴጥሮስም ገልፀዋቸዋል ታዲያ ለምን የቅዱስ
ጴጥሮስን መልእክት ተቀብለው የሄኖክን መፅሀፍ አንቀበልም አሉ
ስንል ጥያቄያችን መልስ አያገኝም
ማስተዋል ያለብን ነገር በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዎች መልአክ
እየተባሉ ተጠርተዋል ለዚህም ምስክራችን
ራእ 3:1 በሰርዴስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ፃፍ።
ራእ 3:7 በፊልድልፍያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ፃፍ።
ራእ 3:14 በሎዶቅያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ፃፍ።
ተብሎ እናገኛለን መቼም የሰርዴስ፣ የፊልድልፍያና የሎዶቅያ የቤተ
ክርስቲያን መልአኮች እውነተኛዎቹ ቅዱሳን መላእክት እንዳልሆኑ
እውን ነው ስለዚህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን መፅሀፈ ሄኖክን አምላካዊ
ቃል አድርጋ መቀበሏ ምንም ስህተት የለውም የመፅሀፈ ሄኖክ
ተቃዋሚዎች ግን መፅሀፈ ሄኖክን እያጣጣሉ ምስጢሩን ግን ሊፈቱ
ጉባኤ ይቀመጣሉ ማድረግ ያለባቸው ግን ልክ እንደ ኢ/ኦ/ተ/ቤ/
ክን አምላካዊ መፅሀፍ ነው ብሎ መቀበል ነው።
ይቀጥላል
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቀጣዩ ርዕሳችን
ለተሐድሶ መናፍቃን የተሠጠ ምላሽ
ዕብ 9
👉 " እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል።
" (ወደ ዕብራውያን 9:28)
👉 የብሉይ ኪዳን እና የሐዲስ ኪዳን ሊቀ ካህናት ልዩነት ምንድነው?
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
ለተሐድሶ መናፍቃን የተሠጠ ምላሽ
ዕብ 9
👉 " እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል።
" (ወደ ዕብራውያን 9:28)
👉 የብሉይ ኪዳን እና የሐዲስ ኪዳን ሊቀ ካህናት ልዩነት ምንድነው?
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
" እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል።" ዕብ 9:28
በ ዘማርያም ዘለቀ
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
በ ዘማርያም ዘለቀ
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
መፅሀፈ ሄኖክ
ክፍል 4
ተወዳጆች መፅሐፈ ሄኖክ ዳሰሳችንን ቀጥለናል በዚህ ክፍልም ሳይንቲስቶች በመፅሐፈ ሄኖክ የሚያቀርቡትን ጥያቄ እንመለከታለን
@And_Haymanot
1ኛ፦ ስናየው ቃሉ ቀጥታ የአዲስ ኪዳን ነው የሚመስለው ስለዚህ የአዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች ክርስትናቸው ተቀባይነት እንዲያገኝ ከፃፉት በሁዋላ የብሉይ ኪዳን ነው አሉ እንጂ በብሉይ ኪዳን ዘመን አልተፃፈም ቃሉ እራሱ የሚናገረው ቀጥታ የአዲስ ኪዳን ቃል ነው እንዴት ይሄ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍ ሊሆን ይችላል ብለው ጥያቄ አቅርበው ነበረ። አምላካችን ልዑለ እግዚአብሄር ግን ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያናችን ምላሽ መስጠት ሳይጠበቅባት ምላሽ ሰቷቸዋል።
ይህም በእስራኤል ሀገር ሙት ባህር በሎጥ ዘመን ሰዶምና ገሞራ በጠፉ ጊዜ በእነሱ ላይ የወረደው እሳትና ዲን ባህር ሲሆን ሙት ባህር ተብሎ ተጠርቷል ይህ ሙት ባህር ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ በብሉይ ኪዳን ዘመን የክርስቶስን መምጣት የሚጠባበቁ ልክ እንደ ፈሪሳውያን፣ ሰዶቃውያን እንደሚባሉት ኤሴዎች የሚባሉም ነበሩ እነዚህ ኤሴዎች ተባትዮን የሚያዘወትሩ ክርስቶስን በገዳም እንጠብቀው ብለው መፅሀፍቶቻቸውን ይዘው ክርስቶስን ሲጠብቁ የኖሩ ናቸው ክርስቶስም ሲመጣ ሳያምኑት እዛው በምድረ በዳ የቀሩ ናቸው።
እናም እነዚህ ኤሴዎች ከክ/ል/በፊት 300 አመት ጀምሮ በሙት ባህር አካባቢ እንደ ገዳም በረሀ ላይ ሲኖሩ ዋሻዎች ነበሩዋቸው መፅሀፍቶቻቸውንም እዛው ቀብረው ይኖሩ ነበር ታዲያ ከዘመናት በሁዋላ በ1947 አ/ም አንድ የአረብ እረኛ ፍየሎች ወደዛ ሄደውበት ፍየሎቹን ሊመልስ ሲሄድ አንድ ፍየል የኖረ ብራና አልበላ ብሏት እያላመጠች ስትጎትት ያያታል ሲያየው መፅሀፍ ነው ለሌላ ሰው ሲያሳየው የትንቢተ ኢሳያስ ክፍል ሆኖ ተገኘ እንደዚህማ ከሆነ ብዙ መፅሀፍቶች ሳይኖረው አይቀርም ተብሎ ቦታው ሲቆፈር ከተገኙት መፅሀፍቶች ውስጥ አንዱ የመፅሀፈ ሄኖክ ክፋይ ሆኖ ተገኘ ያም የመፅሀፈ ሄኖክ ክፋይ በአለም ላይ መፅሀፈ ሄኖክ አለ ከሚሉት ጋር ሲስተያይ (ያው በክፍል 1 እንደጠቀስኩላችው ከኢትዮጵያ ውጪ ሙሉ መፅሀፈ ሄኖክ ያላት ሀገር የለችም) ኢትዮጵያ ካለው ከግእዙ መፅሀፈ ሄኖክ ጋር አንድ አይነት ሆኖ ተገኘ በዚህም መፅሀፈ ሄኖክ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍ መሆኑን እግዚአብሄር አምላካችን መሰከረ።
2ኛ፦ ሳይንቲስቶች ከጠየቁት ጥያቄ ውስጥ ይሄ መፅሀፍ ቅዱስ የምትሉት የተፃፈው በድሮ ዘመን ነው ድሮ ደግሞ የብራና ጥቅልል ነው ያለው በእጅ ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጎም፣ ሲገለበጥና ወደ አለም ሲሰራጭ ኖረ ከኦሪት ጀምሮ ለብዙ ሺ አመታት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ሲገለበጥ የመጀመሪያው መፅሀፍ መሆናቸውን በምን እናውቃለን ተበርዘው ተጨምሮበት ወይም ተቀንሶበት ቢሆንስ ብለው ጠየቁ።
ይህም በ1947 አ/ም የተገኘው የሙት ባህር የቁምራን ዋሻ ጥቅልሎች ወጥተው አሁን ካለው መፅሀፍ ቅዱስ ጋር ሲስተያዩ አንድ አይነት ንባብ ሆኖ ተገኘ መፅሀፈ ሄኖክም ምንም ብረዛ እንዳልደረሰበት ተረጋገጠ።
ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያም መፅሀፍቶች ሳይጠፉባት ጠብቃ እንድትኖር እግዚአብሄር የመረጣት ሀገር መሆኗ ምስክር ሆነ እግዚአብሄር አዋቂ ነው የሚመጣው ትውልድ የመፅሀፍቶች በኩር የሆነውን መፅሀፈ ሄኖክን ይሄማ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍ አይደለም ብሎ እንደሚክድ ስላወቀ በብሉይ ኪዳን ዘመን እንዲቀበር አድርጎ ከ2300 አመታት በሁዋላ በአዲስ ኪዳን ዘመን እንዲወጣ ፈቅዶ መፅሀፈ ሄኖክ በብሉይ ኪዳን ዘመን ያፃፍኩት እኔ ነኝ ብሎ መሰከረ። ይህን የመሰከረ የቅዱሳን አባቶቻችን፣ የቅዱሳን እናቶቻችን የእኛም አምላክ ልኡለ እግዚአብሄር ስሙ የተመሰገነ ይሁን። አሜን።
ይቀጥላል....
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክፍል 4
ተወዳጆች መፅሐፈ ሄኖክ ዳሰሳችንን ቀጥለናል በዚህ ክፍልም ሳይንቲስቶች በመፅሐፈ ሄኖክ የሚያቀርቡትን ጥያቄ እንመለከታለን
@And_Haymanot
1ኛ፦ ስናየው ቃሉ ቀጥታ የአዲስ ኪዳን ነው የሚመስለው ስለዚህ የአዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች ክርስትናቸው ተቀባይነት እንዲያገኝ ከፃፉት በሁዋላ የብሉይ ኪዳን ነው አሉ እንጂ በብሉይ ኪዳን ዘመን አልተፃፈም ቃሉ እራሱ የሚናገረው ቀጥታ የአዲስ ኪዳን ቃል ነው እንዴት ይሄ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍ ሊሆን ይችላል ብለው ጥያቄ አቅርበው ነበረ። አምላካችን ልዑለ እግዚአብሄር ግን ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያናችን ምላሽ መስጠት ሳይጠበቅባት ምላሽ ሰቷቸዋል።
ይህም በእስራኤል ሀገር ሙት ባህር በሎጥ ዘመን ሰዶምና ገሞራ በጠፉ ጊዜ በእነሱ ላይ የወረደው እሳትና ዲን ባህር ሲሆን ሙት ባህር ተብሎ ተጠርቷል ይህ ሙት ባህር ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ በብሉይ ኪዳን ዘመን የክርስቶስን መምጣት የሚጠባበቁ ልክ እንደ ፈሪሳውያን፣ ሰዶቃውያን እንደሚባሉት ኤሴዎች የሚባሉም ነበሩ እነዚህ ኤሴዎች ተባትዮን የሚያዘወትሩ ክርስቶስን በገዳም እንጠብቀው ብለው መፅሀፍቶቻቸውን ይዘው ክርስቶስን ሲጠብቁ የኖሩ ናቸው ክርስቶስም ሲመጣ ሳያምኑት እዛው በምድረ በዳ የቀሩ ናቸው።
እናም እነዚህ ኤሴዎች ከክ/ል/በፊት 300 አመት ጀምሮ በሙት ባህር አካባቢ እንደ ገዳም በረሀ ላይ ሲኖሩ ዋሻዎች ነበሩዋቸው መፅሀፍቶቻቸውንም እዛው ቀብረው ይኖሩ ነበር ታዲያ ከዘመናት በሁዋላ በ1947 አ/ም አንድ የአረብ እረኛ ፍየሎች ወደዛ ሄደውበት ፍየሎቹን ሊመልስ ሲሄድ አንድ ፍየል የኖረ ብራና አልበላ ብሏት እያላመጠች ስትጎትት ያያታል ሲያየው መፅሀፍ ነው ለሌላ ሰው ሲያሳየው የትንቢተ ኢሳያስ ክፍል ሆኖ ተገኘ እንደዚህማ ከሆነ ብዙ መፅሀፍቶች ሳይኖረው አይቀርም ተብሎ ቦታው ሲቆፈር ከተገኙት መፅሀፍቶች ውስጥ አንዱ የመፅሀፈ ሄኖክ ክፋይ ሆኖ ተገኘ ያም የመፅሀፈ ሄኖክ ክፋይ በአለም ላይ መፅሀፈ ሄኖክ አለ ከሚሉት ጋር ሲስተያይ (ያው በክፍል 1 እንደጠቀስኩላችው ከኢትዮጵያ ውጪ ሙሉ መፅሀፈ ሄኖክ ያላት ሀገር የለችም) ኢትዮጵያ ካለው ከግእዙ መፅሀፈ ሄኖክ ጋር አንድ አይነት ሆኖ ተገኘ በዚህም መፅሀፈ ሄኖክ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍ መሆኑን እግዚአብሄር አምላካችን መሰከረ።
2ኛ፦ ሳይንቲስቶች ከጠየቁት ጥያቄ ውስጥ ይሄ መፅሀፍ ቅዱስ የምትሉት የተፃፈው በድሮ ዘመን ነው ድሮ ደግሞ የብራና ጥቅልል ነው ያለው በእጅ ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጎም፣ ሲገለበጥና ወደ አለም ሲሰራጭ ኖረ ከኦሪት ጀምሮ ለብዙ ሺ አመታት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ሲገለበጥ የመጀመሪያው መፅሀፍ መሆናቸውን በምን እናውቃለን ተበርዘው ተጨምሮበት ወይም ተቀንሶበት ቢሆንስ ብለው ጠየቁ።
ይህም በ1947 አ/ም የተገኘው የሙት ባህር የቁምራን ዋሻ ጥቅልሎች ወጥተው አሁን ካለው መፅሀፍ ቅዱስ ጋር ሲስተያዩ አንድ አይነት ንባብ ሆኖ ተገኘ መፅሀፈ ሄኖክም ምንም ብረዛ እንዳልደረሰበት ተረጋገጠ።
ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያም መፅሀፍቶች ሳይጠፉባት ጠብቃ እንድትኖር እግዚአብሄር የመረጣት ሀገር መሆኗ ምስክር ሆነ እግዚአብሄር አዋቂ ነው የሚመጣው ትውልድ የመፅሀፍቶች በኩር የሆነውን መፅሀፈ ሄኖክን ይሄማ የብሉይ ኪዳን መፅሀፍ አይደለም ብሎ እንደሚክድ ስላወቀ በብሉይ ኪዳን ዘመን እንዲቀበር አድርጎ ከ2300 አመታት በሁዋላ በአዲስ ኪዳን ዘመን እንዲወጣ ፈቅዶ መፅሀፈ ሄኖክ በብሉይ ኪዳን ዘመን ያፃፍኩት እኔ ነኝ ብሎ መሰከረ። ይህን የመሰከረ የቅዱሳን አባቶቻችን፣ የቅዱሳን እናቶቻችን የእኛም አምላክ ልኡለ እግዚአብሄር ስሙ የተመሰገነ ይሁን። አሜን።
ይቀጥላል....
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መፅሀፈ ሄኖክ
ክፍል 5
#የእናት_ጡት_ነካሾች_የተሀድሶ_መናፍቃን_በመፅሀፈ_ሄኖክ_ላይ_ከሚያነሱት_ጥያቄ_ውስጥ_በጥቂቱ
1፦ ሄኖክ ስለ ኖህ በተናገረው ትንቢት
ላይ
1.1፦ የመፅሀፈ ሄኖክ አዘጋጆች ለኖህ ስም የማውጣቱን ስራ ለሄኖክ አድርገውታል መፅሀፍ ቅዱስ ግን የሚለው በዘፍ 5:28 ላይ ላሜህም መቶ ሰማንያ ሁለት አመት ኖረ ልጅንም ወለደ
ስሙንም እግዚአብሄር በረገማት ምድር ከተግባራችንና ከእጅ ስራችን ይህ ያሳርፈናል ሲህ ኖህ ብሎ ጠራው ነው የሚለው ብለው የማያውቁትን ይቀባጥራሉ የሚገርመው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ብትሆን ለኖህ ስም
ያወጣለት ላሜህ እንደሆነ ነው የምታስተምረው ነገርግን ሄኖክ ለልጁ ለማቱሳላ የላሜህ ልጅ ኖህ ተብሎ እንዲጠራ አስቀድሞ ነግሮታል እስኪ አንድ ጥያቄ እንጠይቃቸው እግዚአብሄር ከረገማት ምድር ከተግባራችንና ከእጅ ስራችን ይህ ያሳርፈናል ሲል ኖህ
ብሎ ጠራው ተብሏል ላሜህ ይህን የተናገረው የወደፊት ጉዳይ ነው ይህ የወደፊት ጉዳይ ደግሞ ላሜህ ነብይ ካልሆነ በስተቀር እንዴት ሊተነብይ ቻለ? ላሜህ ነብይ ነው ብሎ ደግሞ መፅሀፍ
ቅዱስ አይናገርም ታዲያ እግዚአብሄር ምድሪቱን እንደሚረግማትና ኖህ ከዚህ እንደሚያሳርፋቸው ከዚህ በፊት ካልተነገረው በቀር ስለ ጉዳዩ እንዴት አወቀ? የዚህ ጥያቄ ምላሽ ሄኖክ ለልጁ ለማቱሳላ የላሜህ ልጅ ኖህ ተብሎ እንዲጠራ አስቀድሞ ነግሮታል ነው።
ስለዚህ መፅሀፈ ሄኖክ ይህን ሁሉ በማወቁ ሊመሰገንና እውነተኛ
መፅሀፍ ሊያስብለው እንጂ እንሱ እንደሚሉት የተሳሳቱ ሰዎች
የፃፉት መፅሀፍ አይደለም።
1.2 ኖህን በሄኖ 41:2 ላይ ሰውነቱም እንደ እንቁ ነጭ ሆኖ እንደ ፅጌሬዳም ቀይ ነው የራሱም ጠጉር እንደነጭ ብዝት ነው የተሸራሼ ነው አይኖቹም ያማሩ ናቸው ይላል እንደ እንቁ ነጭ እንደ ፅጌሬዳ ቀይ ካለ ከሁለቱ የትኛውን እንደሚመስል ግልፅ አይደለም ብለው
እንዲው ለመቃወም ሲሉ ብቻ መፅሀፈ ሄኖክን ይቃወማሉ፡፡ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምላሽ ግን ኖህ ምን ያህል ያማረና ልዩ እንደሆነ ለማሳየት ተፈልጎ ይህ አይነት አገላለፅ መፅሀፈ ሄኖክ
ተጠቀመ እንጂ ከሁለቱ የትኛው አይነት ነው የሚል ጥያቄ አያስነሳም ምክንያቱም እንደዚህ አይነት አገላለፅ በሌሎችም የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ ተፅፎ እናገኛለንና ለምሳሌ፦ በመኋ
2:1 ላይ እኔ የሳሮን ፅጌሬዳ የቆላም አበባ ነኝ በእሾህም መካከል
እንዳለ የሱፍ አበባ እንዲሁ ወዳጄ በቆነጃጅት መካከል ናት ይላል እዚህ ላይ እኛ የትኛው አበባ የሳሮን ፅጌሬዳ፣ የቆላም አበባ ወይስ የሱፍ አበባ ብለን ብንጠይቅ መልስ አናገኝም ነገር ግን
የክርስቶስን ውበት ምን ያህል ያማረ እንደሆነ ለመግለፅ ተፈልጎ እንጂ ወይ የሳሮን ፅጌሬዳ፣ ወይ የቆላም አበባ አልያም የሱፍ አበባ ሆኖ አይደለም ስለዚህ መፅሀፈ ሄኖክን ከጠየቁ ለስም
እናምንበታለን ከሚሉት ከ66ቱ ውስጥም እነዚህን መጠየቅ አለባቸው ለተጨማሪ የእንደዚህ አይነት አገላለፅ መኋ 6:10ን
ያንብቡት።
2ኛ፦ ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል
በሄኖ 6:4ላይ ዲያብሎስን የሚበቀለው አጋንንትንም የሚበቀላቸው ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ራጉኤል ነው ይላል እንደሚታወቀው ደሞ
በቀል የእግዚአብሄር ድርሻ ነው በመሆኑም ማናችንም እንዳንበቀልና በቀልን ሁሉ ለእርሱ እንድንተው ታዘናል የበቀል እርምጃ የሚወስደው ፍጡር መልአክ ወይም ራጉኤል ሳይሆን
እግዚአብሄር ነው ስለዚህ መፅሀፈ ሄኖክ የሚበቀለው ራጉኤል ማለቱ ስህተት ነው ብለው ለእግዚአብሄር የተቆረቆሩ በመምሰል ለግብር አባታቸው ለዲያብሎስ በመቆርቆር ይጠይቃሉ
የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መልስ ግን ከቁጥር 1 ጀምሮ የቅዱሳን መላእክት ስማቸውና የተሰጣቸው የስራ ድርሻና ሹመትን ያሳያል ይህን ትልቅ ሹመት የሰጣቸው ደግሞ እግዚአብሄር ነው
ከተሰጣቸው ድርሻ መካከል አንዱ ዲያብሎስን መበቀል ነው ይህ
በቀል ተብሎ የተገለፀው በእግዚአብሄር ላይ ያመፁትን እግዚአብሄር ሊቀጣ ወይም ሊበቀል ሲፈልግ ቅዱሳን መላእክቱን ልኮ በእነርሱ አማካኝነት ይገስፃቸዋል ማለት ነው መረዳት ያለብን
ቅዱስ ራጉኤል ብቻ ለዚህ ተልእኮ ይላካል ማለት አይደለም ነገር ግን ይብለጥ የዚህ መልአክ መገለጫው ይህ በመሆኑ ነው ቅዱሳን መላእክት በፀሎታቸውና በምልጃቸው እኛን እንደሚራዱን ሁሉ ለመበቀልም ሊላኩ ይችላሉ።
ለምሳሌ፦ ህዝቅያስ እግዚአብሄር ከሰናክሬም እጅ እንዲያድነው ሲፀልይ "በህያው አምላክ ላይ ይገዳደር ዘንድ የላከውን የሰናክሬምን ቃል m ስማ... እግዚአብሄር እንደሆንን ያውቁ ዘንድ
ከእጁ አድነን" በማለት ይፀልያል ኢሳ 37:17-20 ላይ በፀሎቱ የጠየቀው እግዚአብሄርን ቢሆንም ሰራዊቱን ያጠፋለት ግን የእግዚአብሄር መልአክ ነው የእግዚአብሄር መልአክ መጣ
ከአሶራውያንም ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደለ ይላል ቁጥር 36 ላይ ስለዚህ ይህ ክፍል የሚያሳየው ሁሉን ፍርድ የሚፈርደው እግዚአብሄር ቢሆንም ፍርዱ እውን የሚሆነው ደግሞ
በተሾሙ መላእክት በኩል እንደሆነ ነው
ሌላው ደሞ ማንኛችንም እንዳንበቀል በቀልን ሁሉ ለእርሱ እንድንተው ታዘናል ብለዋል ይህን ትእዛዝ ግን እንዴት ለመላእክት ሊሰጡት እንደቻሉ ሊገባን አልቻለም ምክንያቱም ይህ ቃል
የተነገረው ለሰው ልጆች ነው የሰው ልጆች አኗኗርና የቅዱሳን መላእክት አኗኗር ደግሞ የተለያየ ነው አይ ለመላእክትም ለሰውም የተሰጠ ህግ ነው ካሉ ደግሞ እኛ በዝሙት መንፈስ ወደሴት እንዳናይ፣ ከአንድ በላይ እንዳናገባ፣እናትና አባታችንን እንድናከብር
መፆም እንደሚገባንና የመሳሰሉ ህጎችን እነሱም መፈፀም አለባቸው የሚል ሌላ የስህተት ትምህርት ውስጥ ስለሚገቡ
ስህተታቸውን እንዲያጤኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትመክራለች የማትታደስ ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያናችን በቀል የእግዚአብሄር መሆኑን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም ጠንቅቃ የምታውቅ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡
ማጠቃለያ፦ የተሀድሶ መናፍቃን በ81 አሀዱና መፅሀፈ ሄኖክ ላይ ለሚያነሱት ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ በእንተ ሰማንያ አንድ አሀዱ የሚለውን መፅሀፍ እየጋበዝኩዋችው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን መፅሀፈ ሄኖክን አምላካዊ መፅሀፍ አድርጋ መቀበሏና ጠብቃ ማቆየቷ
ሊያስመሰግናት፣ ትክክለኛ ሀይማኖት መሆኗ ሊመሰከርላት ይገባል እንጂ በተቃራኒው ቤተ ክርስቲያናችንንና መፅሀፈ ሄኖክን መንቀፍ ትልቅ ስህተት ነው ስለዚህ ተጠራጣሪ ወገኖች ስለ ማንኛውም የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት ወደ ኦርቶዶክሳዊ ቤተ
ክርስቲያናችን ቀርበው ጠይቀው ማወቅና መረዳት ይኖርባቸዋል ።
የአባታችን የቅዱስ ሄኖክ ረድኤት በረከት ይደርብን አሜን።
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ክፍል 5
#የእናት_ጡት_ነካሾች_የተሀድሶ_መናፍቃን_በመፅሀፈ_ሄኖክ_ላይ_ከሚያነሱት_ጥያቄ_ውስጥ_በጥቂቱ
1፦ ሄኖክ ስለ ኖህ በተናገረው ትንቢት
ላይ
1.1፦ የመፅሀፈ ሄኖክ አዘጋጆች ለኖህ ስም የማውጣቱን ስራ ለሄኖክ አድርገውታል መፅሀፍ ቅዱስ ግን የሚለው በዘፍ 5:28 ላይ ላሜህም መቶ ሰማንያ ሁለት አመት ኖረ ልጅንም ወለደ
ስሙንም እግዚአብሄር በረገማት ምድር ከተግባራችንና ከእጅ ስራችን ይህ ያሳርፈናል ሲህ ኖህ ብሎ ጠራው ነው የሚለው ብለው የማያውቁትን ይቀባጥራሉ የሚገርመው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ብትሆን ለኖህ ስም
ያወጣለት ላሜህ እንደሆነ ነው የምታስተምረው ነገርግን ሄኖክ ለልጁ ለማቱሳላ የላሜህ ልጅ ኖህ ተብሎ እንዲጠራ አስቀድሞ ነግሮታል እስኪ አንድ ጥያቄ እንጠይቃቸው እግዚአብሄር ከረገማት ምድር ከተግባራችንና ከእጅ ስራችን ይህ ያሳርፈናል ሲል ኖህ
ብሎ ጠራው ተብሏል ላሜህ ይህን የተናገረው የወደፊት ጉዳይ ነው ይህ የወደፊት ጉዳይ ደግሞ ላሜህ ነብይ ካልሆነ በስተቀር እንዴት ሊተነብይ ቻለ? ላሜህ ነብይ ነው ብሎ ደግሞ መፅሀፍ
ቅዱስ አይናገርም ታዲያ እግዚአብሄር ምድሪቱን እንደሚረግማትና ኖህ ከዚህ እንደሚያሳርፋቸው ከዚህ በፊት ካልተነገረው በቀር ስለ ጉዳዩ እንዴት አወቀ? የዚህ ጥያቄ ምላሽ ሄኖክ ለልጁ ለማቱሳላ የላሜህ ልጅ ኖህ ተብሎ እንዲጠራ አስቀድሞ ነግሮታል ነው።
ስለዚህ መፅሀፈ ሄኖክ ይህን ሁሉ በማወቁ ሊመሰገንና እውነተኛ
መፅሀፍ ሊያስብለው እንጂ እንሱ እንደሚሉት የተሳሳቱ ሰዎች
የፃፉት መፅሀፍ አይደለም።
1.2 ኖህን በሄኖ 41:2 ላይ ሰውነቱም እንደ እንቁ ነጭ ሆኖ እንደ ፅጌሬዳም ቀይ ነው የራሱም ጠጉር እንደነጭ ብዝት ነው የተሸራሼ ነው አይኖቹም ያማሩ ናቸው ይላል እንደ እንቁ ነጭ እንደ ፅጌሬዳ ቀይ ካለ ከሁለቱ የትኛውን እንደሚመስል ግልፅ አይደለም ብለው
እንዲው ለመቃወም ሲሉ ብቻ መፅሀፈ ሄኖክን ይቃወማሉ፡፡ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምላሽ ግን ኖህ ምን ያህል ያማረና ልዩ እንደሆነ ለማሳየት ተፈልጎ ይህ አይነት አገላለፅ መፅሀፈ ሄኖክ
ተጠቀመ እንጂ ከሁለቱ የትኛው አይነት ነው የሚል ጥያቄ አያስነሳም ምክንያቱም እንደዚህ አይነት አገላለፅ በሌሎችም የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ ተፅፎ እናገኛለንና ለምሳሌ፦ በመኋ
2:1 ላይ እኔ የሳሮን ፅጌሬዳ የቆላም አበባ ነኝ በእሾህም መካከል
እንዳለ የሱፍ አበባ እንዲሁ ወዳጄ በቆነጃጅት መካከል ናት ይላል እዚህ ላይ እኛ የትኛው አበባ የሳሮን ፅጌሬዳ፣ የቆላም አበባ ወይስ የሱፍ አበባ ብለን ብንጠይቅ መልስ አናገኝም ነገር ግን
የክርስቶስን ውበት ምን ያህል ያማረ እንደሆነ ለመግለፅ ተፈልጎ እንጂ ወይ የሳሮን ፅጌሬዳ፣ ወይ የቆላም አበባ አልያም የሱፍ አበባ ሆኖ አይደለም ስለዚህ መፅሀፈ ሄኖክን ከጠየቁ ለስም
እናምንበታለን ከሚሉት ከ66ቱ ውስጥም እነዚህን መጠየቅ አለባቸው ለተጨማሪ የእንደዚህ አይነት አገላለፅ መኋ 6:10ን
ያንብቡት።
2ኛ፦ ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል
በሄኖ 6:4ላይ ዲያብሎስን የሚበቀለው አጋንንትንም የሚበቀላቸው ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ራጉኤል ነው ይላል እንደሚታወቀው ደሞ
በቀል የእግዚአብሄር ድርሻ ነው በመሆኑም ማናችንም እንዳንበቀልና በቀልን ሁሉ ለእርሱ እንድንተው ታዘናል የበቀል እርምጃ የሚወስደው ፍጡር መልአክ ወይም ራጉኤል ሳይሆን
እግዚአብሄር ነው ስለዚህ መፅሀፈ ሄኖክ የሚበቀለው ራጉኤል ማለቱ ስህተት ነው ብለው ለእግዚአብሄር የተቆረቆሩ በመምሰል ለግብር አባታቸው ለዲያብሎስ በመቆርቆር ይጠይቃሉ
የቅድስት ቤተ ክርስቲያን መልስ ግን ከቁጥር 1 ጀምሮ የቅዱሳን መላእክት ስማቸውና የተሰጣቸው የስራ ድርሻና ሹመትን ያሳያል ይህን ትልቅ ሹመት የሰጣቸው ደግሞ እግዚአብሄር ነው
ከተሰጣቸው ድርሻ መካከል አንዱ ዲያብሎስን መበቀል ነው ይህ
በቀል ተብሎ የተገለፀው በእግዚአብሄር ላይ ያመፁትን እግዚአብሄር ሊቀጣ ወይም ሊበቀል ሲፈልግ ቅዱሳን መላእክቱን ልኮ በእነርሱ አማካኝነት ይገስፃቸዋል ማለት ነው መረዳት ያለብን
ቅዱስ ራጉኤል ብቻ ለዚህ ተልእኮ ይላካል ማለት አይደለም ነገር ግን ይብለጥ የዚህ መልአክ መገለጫው ይህ በመሆኑ ነው ቅዱሳን መላእክት በፀሎታቸውና በምልጃቸው እኛን እንደሚራዱን ሁሉ ለመበቀልም ሊላኩ ይችላሉ።
ለምሳሌ፦ ህዝቅያስ እግዚአብሄር ከሰናክሬም እጅ እንዲያድነው ሲፀልይ "በህያው አምላክ ላይ ይገዳደር ዘንድ የላከውን የሰናክሬምን ቃል m ስማ... እግዚአብሄር እንደሆንን ያውቁ ዘንድ
ከእጁ አድነን" በማለት ይፀልያል ኢሳ 37:17-20 ላይ በፀሎቱ የጠየቀው እግዚአብሄርን ቢሆንም ሰራዊቱን ያጠፋለት ግን የእግዚአብሄር መልአክ ነው የእግዚአብሄር መልአክ መጣ
ከአሶራውያንም ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደለ ይላል ቁጥር 36 ላይ ስለዚህ ይህ ክፍል የሚያሳየው ሁሉን ፍርድ የሚፈርደው እግዚአብሄር ቢሆንም ፍርዱ እውን የሚሆነው ደግሞ
በተሾሙ መላእክት በኩል እንደሆነ ነው
ሌላው ደሞ ማንኛችንም እንዳንበቀል በቀልን ሁሉ ለእርሱ እንድንተው ታዘናል ብለዋል ይህን ትእዛዝ ግን እንዴት ለመላእክት ሊሰጡት እንደቻሉ ሊገባን አልቻለም ምክንያቱም ይህ ቃል
የተነገረው ለሰው ልጆች ነው የሰው ልጆች አኗኗርና የቅዱሳን መላእክት አኗኗር ደግሞ የተለያየ ነው አይ ለመላእክትም ለሰውም የተሰጠ ህግ ነው ካሉ ደግሞ እኛ በዝሙት መንፈስ ወደሴት እንዳናይ፣ ከአንድ በላይ እንዳናገባ፣እናትና አባታችንን እንድናከብር
መፆም እንደሚገባንና የመሳሰሉ ህጎችን እነሱም መፈፀም አለባቸው የሚል ሌላ የስህተት ትምህርት ውስጥ ስለሚገቡ
ስህተታቸውን እንዲያጤኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትመክራለች የማትታደስ ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያናችን በቀል የእግዚአብሄር መሆኑን ብቻ ሳይሆን ሌላውንም ጠንቅቃ የምታውቅ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡
ማጠቃለያ፦ የተሀድሶ መናፍቃን በ81 አሀዱና መፅሀፈ ሄኖክ ላይ ለሚያነሱት ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ በእንተ ሰማንያ አንድ አሀዱ የሚለውን መፅሀፍ እየጋበዝኩዋችው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን መፅሀፈ ሄኖክን አምላካዊ መፅሀፍ አድርጋ መቀበሏና ጠብቃ ማቆየቷ
ሊያስመሰግናት፣ ትክክለኛ ሀይማኖት መሆኗ ሊመሰከርላት ይገባል እንጂ በተቃራኒው ቤተ ክርስቲያናችንንና መፅሀፈ ሄኖክን መንቀፍ ትልቅ ስህተት ነው ስለዚህ ተጠራጣሪ ወገኖች ስለ ማንኛውም የቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት ወደ ኦርቶዶክሳዊ ቤተ
ክርስቲያናችን ቀርበው ጠይቀው ማወቅና መረዳት ይኖርባቸዋል ።
የአባታችን የቅዱስ ሄኖክ ረድኤት በረከት ይደርብን አሜን።
ወስብሀት ለእግዚአብሄር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
👍1
✞መስቀል✞
@And_Haymanot
✞ ተወዳጆች በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም
አደረሰን!!! አደረሳችው ✞
የተሃድሶ መናፍቃን መስቀልን ከምልክትነት ባለፈ አያከብሩትም፣ አያማትቡም፣ አይሳለሙም፣ አይባረኩበትም እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ
በመስቀል እናማትባለን፣ በኃያልነቱ እናምናለን፣ ከጠላት እንመካበታለን፣ ዲያብሎስን እናሸንፍበታለን፣ እንሳለመዋለንም ነገር ግን ለሃራጥቃውያን ምላሽ ይሆን ዘንድ የመስቀልን ክብር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንመልከት።
✞ መስቀል በኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ
እንደ ታቦትና ስዕል ከፍተኛ ክብርና ቦታ ያለው ነው
👉✞ መስቀል የክርስቶስ ምልክት ነው፡፡ ጌታችን ስለ ዓለም መጨረሻ ሲናገር "የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል"።
ብሏል /ማቴ 24፥30/ የሰው ልጅ ምልክት የተባለ መስቀል
መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም አስተምረዋል ጌታችን በትምህርቱ መስቀልን ከክርስቲያኖች ሕይወትና ጉዞ ጋር አያይዞም አስተምሯል፦ ☞
ማቴ 16፥24 ላይ "እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ
መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ"። ☞ ሉቃ 14፥27 ላይ ደግሞ"ማንም መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም"።
✞ ጌታችን ከሙታን በተነሣ ጊዜ በመቃብሩ አካባቢ የነበሩት
መላእክት ጌታችንን የጠሩት በመስቀሉ ነው" እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና" /ማቴ 28፥5/
👉✞ ሐዋርያትም ጌታችንን በመስቀሉ ይገልጡት ነበር "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ" / ገላ 6፥14/
በመስቀል ስናማትብ የእግዚአብሔርን የማዳን ስራ እንመሰክራለን #በኒቅያ_ጉባኤ በ325 ዓ/ም በተወሰነው መሠረት ከግምባራችን ወደ ሆዳችን ስናማትብ የጌታችንን ከሰማየ ሰማየት ወርዶ ከድንግል ማርያም መወለዱን፣ ከግራ ወደ ቀኝ ስናማትብ ደግም ከሲዖል ወደ ገነት እኛን ማስገባቱን እንመሰክራለን "የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ
ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና" /1ኛ ቆሮ 1፥18/
❖ ቅዱስ ሄሬኔዎስ፦ "በእንጨት ምክንያት ለዕዳ ተሰጠን፤ በእንጨት ምክንያትም ከዕዳችን ነጻ ሆንን" በማለት
እንዳስተማረው መስቀል ከዕዳ ነፃ የሆንንበት ነው
✞ በብሉይ ኪዳን ሕዝበ እስራኤል ከአማሌቃውያን ጋር በተዋጉ
ጊዜ ሙሴ እጁን ዘርግቶ በመስቀል አምሳል ቆሞ ነበር "ሙሴ እጁን ባነሳ ጊዜ እስራኤላውያን ድል ያደርጉ ነበር፤ እጁን ባወረደ ጊዜም አማሌቅ ድል ያደርጉ ነበር" /ዘፀ 17፥8-16/ መስቀል
በሙሴ እጅ በምሳሌው ይህን ያህል ኃይል ከነበረው በክርስቶስ ደም ከተዋጀ በኃላ አማናዊውማ እንዴት ታላቅ የሆነ ኃይል አያደርግ
✞ ያዕቆብ ኤፍሬምን እና ምናሴን ሲባርክ በመስቀል አምሳል ነው "ኤፍሬምንም በቀኙ በእስራኤል ግራ፣ ምናሴንም በግራው በእስራኤል ቀኝ አደረገው፤ እስራኤልም ቀኝ እጁን ዘርግቶ በኤፍሬም ራስ ላይ/በግራው/ ግራ እጁንም በምናሴ ላይ አኖረ/
በቀኙ በቆመው/ እጆቹንም አስተላለፈ"። /ዘፍ 48፥13/ በብሉይ ኪዳን የነበረው ያዕቆብ በመስቀል የባረከው በረከት ለልጆቹ ደርሶላቸዋል፤ ታዲያ በሐዲስ የሚገኙ ካህናት በመስቀል
የሚባርኩት በረከትማ እንዴት አይደርስ
👉✞ ሕዝ 9፥4 ላይ "እግዚአብሔርም። በከተማይቱ በኢየሩሳሌም
መካከል እለፍ፥ በመካከልዋም ስለ ተሠራው ርኵሰት ሁሉ በሚያለቅሱና በሚተክዙ ሰዎች ግምባር ላይ ምልክት ጻፍ አለው"። ይላል በአማርኛ "ምልክት" የተባለው በግሪኩ "tau" የተባለው ምልክት ነው ይህም በእንግሊዝኛው የ"ተ" ቅርጽ ያለው ምልክት ነው።
✞ ጣት የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው በሉቃስ ወንጌል 11፥20 ላይ ☞ "እኔ ግን በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ" ያለውን የማቴዎስ ወንጌል 12፥28 ግን ☞ "እኔ ግን
በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ" ብሎታል
እኛም በጣታችን ስናማትብ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሰይጣንን ድል ለመንሣት ማማተባችን ነው አስቀድሞም ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝ 59፥4 ላይ "ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥
ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው" ብሎ የተናገረለት ከዲያብሎስ ቀስት የምናመልጥበት ምልክት መስቀል ነው።
ስለዚህ ተወዳጆች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መስቀልን የምታከብረው፣ የምትሳለመው፣
የምታማትበው... መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርጋ እንጂ የተሃድሶ መናፍቃን እንደሚሉት በተራ የእንጨት ፍቅር አይደለም በመሆንኑ የተሃድሶ መናፍቃኑ ከስህተት ጎዳና ተመልሰው ወደ ቀጥተኛዋና ርትዒት ወደ ሆነችው ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያናችን
ይመለሱ ዘንድ የቤተ ክርስቲያናችን ጸሎት ነው።
❖ ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
❖ በዓለም ጥበብ ለሚኖሩ እውነት ተስኗቸው
❖ ለጠቢብ ሰው በመንፈስ የሚኖር
❖ የመዳን ቀን እውነተኛ አርማ ነው
❖ ከገሃነም እሳት የሚያድን ነው
✞ አምላከ ቅዱሳን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ጽላት ላይ
ይጻፍልን!!! አሜን
✞✞✞
#ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት
👇👇👇
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~Share~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~JoIN~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
@And_Haymanot
✞ ተወዳጆች በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም
አደረሰን!!! አደረሳችው ✞
የተሃድሶ መናፍቃን መስቀልን ከምልክትነት ባለፈ አያከብሩትም፣ አያማትቡም፣ አይሳለሙም፣ አይባረኩበትም እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ
በመስቀል እናማትባለን፣ በኃያልነቱ እናምናለን፣ ከጠላት እንመካበታለን፣ ዲያብሎስን እናሸንፍበታለን፣ እንሳለመዋለንም ነገር ግን ለሃራጥቃውያን ምላሽ ይሆን ዘንድ የመስቀልን ክብር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንመልከት።
✞ መስቀል በኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ
እንደ ታቦትና ስዕል ከፍተኛ ክብርና ቦታ ያለው ነው
👉✞ መስቀል የክርስቶስ ምልክት ነው፡፡ ጌታችን ስለ ዓለም መጨረሻ ሲናገር "የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል"።
ብሏል /ማቴ 24፥30/ የሰው ልጅ ምልክት የተባለ መስቀል
መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም አስተምረዋል ጌታችን በትምህርቱ መስቀልን ከክርስቲያኖች ሕይወትና ጉዞ ጋር አያይዞም አስተምሯል፦ ☞
ማቴ 16፥24 ላይ "እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ
መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ"። ☞ ሉቃ 14፥27 ላይ ደግሞ"ማንም መስቀሉን ተሸክሞ በኋላዬ የማይመጣ፥ ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም"።
✞ ጌታችን ከሙታን በተነሣ ጊዜ በመቃብሩ አካባቢ የነበሩት
መላእክት ጌታችንን የጠሩት በመስቀሉ ነው" እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና" /ማቴ 28፥5/
👉✞ ሐዋርያትም ጌታችንን በመስቀሉ ይገልጡት ነበር "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ" / ገላ 6፥14/
በመስቀል ስናማትብ የእግዚአብሔርን የማዳን ስራ እንመሰክራለን #በኒቅያ_ጉባኤ በ325 ዓ/ም በተወሰነው መሠረት ከግምባራችን ወደ ሆዳችን ስናማትብ የጌታችንን ከሰማየ ሰማየት ወርዶ ከድንግል ማርያም መወለዱን፣ ከግራ ወደ ቀኝ ስናማትብ ደግም ከሲዖል ወደ ገነት እኛን ማስገባቱን እንመሰክራለን "የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ
ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና" /1ኛ ቆሮ 1፥18/
❖ ቅዱስ ሄሬኔዎስ፦ "በእንጨት ምክንያት ለዕዳ ተሰጠን፤ በእንጨት ምክንያትም ከዕዳችን ነጻ ሆንን" በማለት
እንዳስተማረው መስቀል ከዕዳ ነፃ የሆንንበት ነው
✞ በብሉይ ኪዳን ሕዝበ እስራኤል ከአማሌቃውያን ጋር በተዋጉ
ጊዜ ሙሴ እጁን ዘርግቶ በመስቀል አምሳል ቆሞ ነበር "ሙሴ እጁን ባነሳ ጊዜ እስራኤላውያን ድል ያደርጉ ነበር፤ እጁን ባወረደ ጊዜም አማሌቅ ድል ያደርጉ ነበር" /ዘፀ 17፥8-16/ መስቀል
በሙሴ እጅ በምሳሌው ይህን ያህል ኃይል ከነበረው በክርስቶስ ደም ከተዋጀ በኃላ አማናዊውማ እንዴት ታላቅ የሆነ ኃይል አያደርግ
✞ ያዕቆብ ኤፍሬምን እና ምናሴን ሲባርክ በመስቀል አምሳል ነው "ኤፍሬምንም በቀኙ በእስራኤል ግራ፣ ምናሴንም በግራው በእስራኤል ቀኝ አደረገው፤ እስራኤልም ቀኝ እጁን ዘርግቶ በኤፍሬም ራስ ላይ/በግራው/ ግራ እጁንም በምናሴ ላይ አኖረ/
በቀኙ በቆመው/ እጆቹንም አስተላለፈ"። /ዘፍ 48፥13/ በብሉይ ኪዳን የነበረው ያዕቆብ በመስቀል የባረከው በረከት ለልጆቹ ደርሶላቸዋል፤ ታዲያ በሐዲስ የሚገኙ ካህናት በመስቀል
የሚባርኩት በረከትማ እንዴት አይደርስ
👉✞ ሕዝ 9፥4 ላይ "እግዚአብሔርም። በከተማይቱ በኢየሩሳሌም
መካከል እለፍ፥ በመካከልዋም ስለ ተሠራው ርኵሰት ሁሉ በሚያለቅሱና በሚተክዙ ሰዎች ግምባር ላይ ምልክት ጻፍ አለው"። ይላል በአማርኛ "ምልክት" የተባለው በግሪኩ "tau" የተባለው ምልክት ነው ይህም በእንግሊዝኛው የ"ተ" ቅርጽ ያለው ምልክት ነው።
✞ ጣት የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው በሉቃስ ወንጌል 11፥20 ላይ ☞ "እኔ ግን በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ" ያለውን የማቴዎስ ወንጌል 12፥28 ግን ☞ "እኔ ግን
በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ" ብሎታል
እኛም በጣታችን ስናማትብ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሰይጣንን ድል ለመንሣት ማማተባችን ነው አስቀድሞም ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝ 59፥4 ላይ "ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥
ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው" ብሎ የተናገረለት ከዲያብሎስ ቀስት የምናመልጥበት ምልክት መስቀል ነው።
ስለዚህ ተወዳጆች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መስቀልን የምታከብረው፣ የምትሳለመው፣
የምታማትበው... መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርጋ እንጂ የተሃድሶ መናፍቃን እንደሚሉት በተራ የእንጨት ፍቅር አይደለም በመሆንኑ የተሃድሶ መናፍቃኑ ከስህተት ጎዳና ተመልሰው ወደ ቀጥተኛዋና ርትዒት ወደ ሆነችው ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያናችን
ይመለሱ ዘንድ የቤተ ክርስቲያናችን ጸሎት ነው።
❖ ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
❖ በዓለም ጥበብ ለሚኖሩ እውነት ተስኗቸው
❖ ለጠቢብ ሰው በመንፈስ የሚኖር
❖ የመዳን ቀን እውነተኛ አርማ ነው
❖ ከገሃነም እሳት የሚያድን ነው
✞ አምላከ ቅዱሳን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ጽላት ላይ
ይጻፍልን!!! አሜን
✞✞✞
#ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት
👇👇👇
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~Share~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~JoIN~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
መስቀል በኢትዮጵያ
✞ ተወዳጆች በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን!!! አደረሳችው ✞
❖ "ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ" ገላ 6፥14 ❖
@And_Haymanot
✍ ኢትዮጵያ ሃገራችን የክርስቲያን ደሴት ከመባሏም በላይ የእግዚአብሔር ቸርነት ያላት የበረከት የረድኤት ሀገር ናት ይኽም የጌታ ግማደ መስቀል በ14ኛው ክፍለ ዘመን በአጼ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል
☞ አመጣጡም የኢትዮጵያ ነገሥታት የግብጽ ካሊፋዎች ሀገረ ገዥዎች በኃይል ይጋፏቸው ስለነበር የግብጽ ሀገር ገዥዎች ደግሞ የግብጽን ክርስቲያኖች (ኮፕታውያን) ያሰቃዩአቸው ነበር ስለዚህ ይህ አለመግባባት እንዲወገድና የግብጽ ክርስቲያኖች ዕረፍት እንዲያገኙ በማሠብ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ አቡነ ዮሐንስ ከግብጽ የአህናስ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስንና አባ ማዕምር የሚባሉ ሉዑካን ወደ ኢትዮጵያ መጡ በዚያን ጊዜ አጼ ሠይፈ አርዕደ አርፈው የልጃቸው ልጅ አጼ ዳዊት ነግሠው ነበር እነዚህ ልዑካን በኢትዮጵያውያንና በግብጻውያን ነገስታት መካከል ያለውን ቅራኔ አስወግደው ሲመለሱ አጼ ዳዊት በነበራቸው ቀና መንፈስ አቡነ ዮሐንስ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ እሌኒ ንግስት አስቆፍራ ከአስወጣችው ከጌታ ግማደ መስቀል ክፋይ ለበረከት እንዲልኩላቸው ወርቅ፣ አልማዝ፣ ገጸ በረከት አስጭነው ወደ ኢየሩሳሌም መልዕክተኞችን ላኩ መልእክተኞቹም ኢየሩሳሌም ደርሰው ገጸ በረከቱን ለፓትርያርኩ ከሰጡ በኃላ ፓትርያርኩ፦
፩፦ የጌታን ግማደ መስቀል፣ የቀኝ በኩሉን ክፋይ
፪፦ ጌታ ላይ አይሁድ የጫኑበትን (ያረጉለት) አክሊለ ሶኩን
፫፦ ቅዱስ ሉቃስ የሳላት ምስለ ፍቁር ወልዳ የእመቤታችን ስዕል ላኩላቸው።
✍ መልዕክተኞቹም ተቀብለው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አጼ ዳዊት መልእክተኞቹን ለመቀበል ሲሄዱ የተቀመጡባት ባዝራ ፈረስ ጥላቸው መሞታቸውን ታሪካቸው ይናገራል መስቀሉ ወደ ሀገራችን የገባው #መስከረም 10 ቀን ነው መስቀሉ የተቀመጠው መስከረም 21 ቀን በወሎ ክፍለ ሃገር በግሸን ማርያም ነው
✍ በዚህ ሁኔታ የገባው የጌታ መስቀል ዛሬም ድረስ ተአምራዊ ነው ይህም ሀገራችን ኢትዮጵያን ለመስቀል ያላትን ታላቅ አክብሮትና ፍቅር የገለጸችበት አብይ ምስክር ነው ሕዝቡም ለመስቀል ያለውን ፍቅርና አክብሮት ለመግለጽ ይነቀሰዋል፣ በልብሱ ላይ ይጠልፈዋል ይህ ደግሞ የሚያሳየው መስቀል በኢትዮጵያውያን ዘንድ ምን ያህል ክብር እንዳለው ነው።
☞ ከተለያዩ ማዕድናት የሚሰራው መስቀል ትርጉም፦
✍ መስቀል ከተለያዩ ማዕድናት ሊሰራ ይችላል መስቀሉ የሚሰራባቸው ማዕድናት የራሳቸው ባህርያት እንዳላቸው ሁሉ ምሳሌውን ለመግለጽ ብቁ ናቸው ብለው አባቶች ያስቀመጡትን ማየት ይገባል።
✝ ከብረት ቢሰራ ክርስቶስ የተቸነከረበትን ችንካር ለማመልከት ነው
✝ ከወርቅ ቢሰራ ወርቅ ንጹህ እንደሆነ ክርስቶስን ንጹሀ ባህርይ እድፈት የሌለብህ ጽኑ አንተ ነህ ብሎ ለመመስከር ነው
✝ ከእንጨት ቢሰራ ክርስቶስ የተሰቀለው በዕጽ በእንጨት ላይ መሆኑን ለማመልከት ነው
✝ ከብር ቢሰራ ተስፋን፣ ዕድልን ያመለክታል ይኸውም ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነ ቤዛን በደሙ ከፍሏልና በእርሱ ተስፋ እንድናደርግ ያመለክተናል
✍ መስቀል ለእኛ ክርስቲያኖች ኃይላችን፣ ጽንዐችን፣ ቤዛችን፣ መድኃኒታችን ነው "የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና" /1ኛ ቆሮ 1፥18/ ለቅዱስ መስቀል ክብርና ስግደት ይገባል ምክንያቱም በመዝ 131፥7 ላይ "እግሮቹ በሚቆሙበት ሥፍራ እንሰግዳለን" ተብሎ ተጽፏልና።
❖ ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
❖ በዓለም ጥበብ ለሚኖሩ እውነት ተስኗቸው
❖ ለጠቢብ ሰው በመንፈስ የሚኖር
❖ የመዳን ቀን እውነተኛ አርማ ነው
❖ ከገሃነም እሳት የሚያድን ነው
✔ ያለ መስቀል ክርስትና ያለ ተጋድሎ ቅድስና የለም!!! ✔
✞ አምላከ ቅዱሳን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ጽላት ላይ ይጻፍልን!!! አሜን ✞✞✞
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN & Share
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
✞ ተወዳጆች በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን!!! አደረሳችው ✞
❖ "ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ" ገላ 6፥14 ❖
@And_Haymanot
✍ ኢትዮጵያ ሃገራችን የክርስቲያን ደሴት ከመባሏም በላይ የእግዚአብሔር ቸርነት ያላት የበረከት የረድኤት ሀገር ናት ይኽም የጌታ ግማደ መስቀል በ14ኛው ክፍለ ዘመን በአጼ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል
☞ አመጣጡም የኢትዮጵያ ነገሥታት የግብጽ ካሊፋዎች ሀገረ ገዥዎች በኃይል ይጋፏቸው ስለነበር የግብጽ ሀገር ገዥዎች ደግሞ የግብጽን ክርስቲያኖች (ኮፕታውያን) ያሰቃዩአቸው ነበር ስለዚህ ይህ አለመግባባት እንዲወገድና የግብጽ ክርስቲያኖች ዕረፍት እንዲያገኙ በማሠብ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ አቡነ ዮሐንስ ከግብጽ የአህናስ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስንና አባ ማዕምር የሚባሉ ሉዑካን ወደ ኢትዮጵያ መጡ በዚያን ጊዜ አጼ ሠይፈ አርዕደ አርፈው የልጃቸው ልጅ አጼ ዳዊት ነግሠው ነበር እነዚህ ልዑካን በኢትዮጵያውያንና በግብጻውያን ነገስታት መካከል ያለውን ቅራኔ አስወግደው ሲመለሱ አጼ ዳዊት በነበራቸው ቀና መንፈስ አቡነ ዮሐንስ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ እሌኒ ንግስት አስቆፍራ ከአስወጣችው ከጌታ ግማደ መስቀል ክፋይ ለበረከት እንዲልኩላቸው ወርቅ፣ አልማዝ፣ ገጸ በረከት አስጭነው ወደ ኢየሩሳሌም መልዕክተኞችን ላኩ መልእክተኞቹም ኢየሩሳሌም ደርሰው ገጸ በረከቱን ለፓትርያርኩ ከሰጡ በኃላ ፓትርያርኩ፦
፩፦ የጌታን ግማደ መስቀል፣ የቀኝ በኩሉን ክፋይ
፪፦ ጌታ ላይ አይሁድ የጫኑበትን (ያረጉለት) አክሊለ ሶኩን
፫፦ ቅዱስ ሉቃስ የሳላት ምስለ ፍቁር ወልዳ የእመቤታችን ስዕል ላኩላቸው።
✍ መልዕክተኞቹም ተቀብለው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አጼ ዳዊት መልእክተኞቹን ለመቀበል ሲሄዱ የተቀመጡባት ባዝራ ፈረስ ጥላቸው መሞታቸውን ታሪካቸው ይናገራል መስቀሉ ወደ ሀገራችን የገባው #መስከረም 10 ቀን ነው መስቀሉ የተቀመጠው መስከረም 21 ቀን በወሎ ክፍለ ሃገር በግሸን ማርያም ነው
✍ በዚህ ሁኔታ የገባው የጌታ መስቀል ዛሬም ድረስ ተአምራዊ ነው ይህም ሀገራችን ኢትዮጵያን ለመስቀል ያላትን ታላቅ አክብሮትና ፍቅር የገለጸችበት አብይ ምስክር ነው ሕዝቡም ለመስቀል ያለውን ፍቅርና አክብሮት ለመግለጽ ይነቀሰዋል፣ በልብሱ ላይ ይጠልፈዋል ይህ ደግሞ የሚያሳየው መስቀል በኢትዮጵያውያን ዘንድ ምን ያህል ክብር እንዳለው ነው።
☞ ከተለያዩ ማዕድናት የሚሰራው መስቀል ትርጉም፦
✍ መስቀል ከተለያዩ ማዕድናት ሊሰራ ይችላል መስቀሉ የሚሰራባቸው ማዕድናት የራሳቸው ባህርያት እንዳላቸው ሁሉ ምሳሌውን ለመግለጽ ብቁ ናቸው ብለው አባቶች ያስቀመጡትን ማየት ይገባል።
✝ ከብረት ቢሰራ ክርስቶስ የተቸነከረበትን ችንካር ለማመልከት ነው
✝ ከወርቅ ቢሰራ ወርቅ ንጹህ እንደሆነ ክርስቶስን ንጹሀ ባህርይ እድፈት የሌለብህ ጽኑ አንተ ነህ ብሎ ለመመስከር ነው
✝ ከእንጨት ቢሰራ ክርስቶስ የተሰቀለው በዕጽ በእንጨት ላይ መሆኑን ለማመልከት ነው
✝ ከብር ቢሰራ ተስፋን፣ ዕድልን ያመለክታል ይኸውም ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነ ቤዛን በደሙ ከፍሏልና በእርሱ ተስፋ እንድናደርግ ያመለክተናል
✍ መስቀል ለእኛ ክርስቲያኖች ኃይላችን፣ ጽንዐችን፣ ቤዛችን፣ መድኃኒታችን ነው "የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና" /1ኛ ቆሮ 1፥18/ ለቅዱስ መስቀል ክብርና ስግደት ይገባል ምክንያቱም በመዝ 131፥7 ላይ "እግሮቹ በሚቆሙበት ሥፍራ እንሰግዳለን" ተብሎ ተጽፏልና።
❖ ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
❖ በዓለም ጥበብ ለሚኖሩ እውነት ተስኗቸው
❖ ለጠቢብ ሰው በመንፈስ የሚኖር
❖ የመዳን ቀን እውነተኛ አርማ ነው
❖ ከገሃነም እሳት የሚያድን ነው
✔ ያለ መስቀል ክርስትና ያለ ተጋድሎ ቅድስና የለም!!! ✔
✞ አምላከ ቅዱሳን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ጽላት ላይ ይጻፍልን!!! አሜን ✞✞✞
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN & Share
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
መስቀል አበባ
መስቀል አበባ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
መስቀል አበባ ተቀብሮ ሲኖር አደይ አበባ ሥነ ስቅለቱ
መስቀል አበባ እሌኒ አገኘች አደይ አበባ ደገኛይቱ
መስቀል አበባ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
መስቀል አበባ ጥራጊ ሞልተው አደይ አበባ አይሁድ በክፋት
መስቀል አበባ ጢሱ ሰገደ አደይ አበባ መስቀሉ ካለበት
መስቀል አበባ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
መስቀል አበባ ወንዙ ጅረቱ አደይ አበባ ሸለቆ ዱሩ
መስቀል አበባ አሸብርቀው ደምቀው አደይ አበባ ላንተ መሰከሩ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
መስቀል አበባ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
መስቀል አበባ ተቀብሮ ሲኖር አደይ አበባ ሥነ ስቅለቱ
መስቀል አበባ እሌኒ አገኘች አደይ አበባ ደገኛይቱ
መስቀል አበባ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
መስቀል አበባ ጥራጊ ሞልተው አደይ አበባ አይሁድ በክፋት
መስቀል አበባ ጢሱ ሰገደ አደይ አበባ መስቀሉ ካለበት
መስቀል አበባ ውብ አበባ
አደይ አበባ ነሽ ውብ አበባ
መስቀል አበባ ወንዙ ጅረቱ አደይ አበባ ሸለቆ ዱሩ
መስቀል አበባ አሸብርቀው ደምቀው አደይ አበባ ላንተ መሰከሩ
@And_Haymanot
@And_Haymanot