Audio
መጽሐፍ ቅዱስ እና ሳይንስ
Share
👉 ዝግመተ ለውጥ
👉 የአለማችን እድሜ
👉 ዳይኖሰር ነበር?
👉 የቅዱሳት መጽሐፍት ማሥረጃ፡፡...
በመጋቢ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
Join:- @And_Haymanot
መጠኑ 7.3Mb ነውና ሁላችሁም አዳምጡት
Share
👉 ዝግመተ ለውጥ
👉 የአለማችን እድሜ
👉 ዳይኖሰር ነበር?
👉 የቅዱሳት መጽሐፍት ማሥረጃ፡፡...
በመጋቢ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
Join:- @And_Haymanot
መጠኑ 7.3Mb ነውና ሁላችሁም አዳምጡት
ከፕሮቴስታንት ፓስተር ጋር የተደረገ ውይይት ክፍል12… በማር
16፡16 ‹‹ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።›› የሚለው ጥቅስ በእርግጥ ሕጻናትን ማጥመቅን ይከለክላል? ከዚህ በፊት በነበረን
የእህታችን ሐና እና የፕሮቴስታንቱ ፓስተር ተከታታይ ውይይት በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት መካከል ስላለው
የመዳን አስተምሮ ልዩነቶች ማየት ከጀመርን ሰንብተናል በባለፈው በክፍል 11 የመጀመሪያውን እምነትን
መሰረት ያደረገውን ውይይት አጠናቀን ‹‹ነገረ ጥምቀትን›› ጀምረን ነበር ቀጣዩ
እነሆ ብለናል
ለማንበብ 👉 Open
16፡16 ‹‹ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።›› የሚለው ጥቅስ በእርግጥ ሕጻናትን ማጥመቅን ይከለክላል? ከዚህ በፊት በነበረን
የእህታችን ሐና እና የፕሮቴስታንቱ ፓስተር ተከታታይ ውይይት በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት መካከል ስላለው
የመዳን አስተምሮ ልዩነቶች ማየት ከጀመርን ሰንብተናል በባለፈው በክፍል 11 የመጀመሪያውን እምነትን
መሰረት ያደረገውን ውይይት አጠናቀን ‹‹ነገረ ጥምቀትን›› ጀምረን ነበር ቀጣዩ
እነሆ ብለናል
ለማንበብ 👉 Open
አስደሳች ሰበር ዜናዎች {3}
ለመላው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በሙሉ።
✞ የአዲስአበባው ቅዱስ ሲኖዶስ ልኡክ ሰሜን አሜሪካ ካለው ስደተኛው ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ለአንድነት ውይይት ወደ ሐገረ
አሜሪካ ሊጓዝ ነው ፡፡
¶ የተሃድሶ መናፍቃን መከታ የሆነው አጽራረ ቤ/ያኑ ሚሊየነር አቶ ጎይቶም ያይኑ ከአ.አ ስራ አስኪያጅነት ተነሳ፡፡
✞ በአዲስ አበባ ሐገረስብከ ስር በቲም ጎይቶም ስትበዘበዝ የነበረችው ሰዓሊተ ምህረት አስገራሚው የአካውንት ብር
ጉዳይ ፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት
👉 .... See more
ለመላው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በሙሉ።
✞ የአዲስአበባው ቅዱስ ሲኖዶስ ልኡክ ሰሜን አሜሪካ ካለው ስደተኛው ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ለአንድነት ውይይት ወደ ሐገረ
አሜሪካ ሊጓዝ ነው ፡፡
¶ የተሃድሶ መናፍቃን መከታ የሆነው አጽራረ ቤ/ያኑ ሚሊየነር አቶ ጎይቶም ያይኑ ከአ.አ ስራ አስኪያጅነት ተነሳ፡፡
✞ በአዲስ አበባ ሐገረስብከ ስር በቲም ጎይቶም ስትበዘበዝ የነበረችው ሰዓሊተ ምህረት አስገራሚው የአካውንት ብር
ጉዳይ ፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት
👉 .... See more
<... #ለዛቲ_ቤት_ሐነጻ_ወልድ >
፩ ኃይማኖት
( እስኪ ወደ ቀድሞ ነገር እንመለስ )
ቤተ ክርስቲያን ማለት ትርጉሙ
👉ክርስቲያን የሆነን ሰው (1ቆሮ
3፥16፤ገላ1፥13)
👉 2.የክርስቲያኖች ሕብረትና ጉባኤ (ማቴ 18፥17፤ የሐዋ 5፥11፤ ቆላ4፥15)
👉 3.ክርስቲያኖች የሚሰበሰቡበት፥ ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን የሚቀበሉበት
የከበረ የተወደደ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው(ማቴ 16፥16፣ የሐዋ11፥26) የሐዲስ ኪዳንዋ ቤ/ክ በብሉይ አስቀድማ በትንቢት የተነገረች በሐዲስም ራሱ ጌታ በቃሉና በእጁ የሰራት የአማናዊው/እውነተኛው መስዋዕት መሰውያ ናት:: አስቀድሞ
በነብዩ በሚልክያስ "ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና በየስፍራውም ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፥ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ" (ሚልክ1፥11) ተብሎ ነበር:: በብሉይ ዘመን የኦሪት ቤተ መቅደስ፣ ዕጣንና ቁርባን በእስራኤላውያን ዘንድ እንጂ በአሕዛብ ዘንድ ፍጹም አልነበረም!
ስለዚህ ይህ የሚልክያስ ትንቢት በሐዲስ ኪዳን ስጋውና ደሙ ለሚሰጥበት፣ የቅዳሴው ዕጣንም ለሚቀርብበት ቤ/ክ የተነገረ መሆኑ ግልፅ ነው:: ነብዩ ኢሳይያስም "በዚያም ቀን እግዚአብሔር በግብጽ የታወቀ ይሆናል፥ ግብጻውያንም እግዚአብሔርን ያውቃሉ በመሥዋዕትና በቍርባን
ያመልካሉ"ኢሳ19፥21 አለ:: በብሉይ ኪዳን ጊዜ ግብፅ የአሕዛብ ከተማ የነበረች፣ እስራኤላውያን በግብፅ ምድር ሆነው መስዋዕት እንዳይሰው የተከለከለች ሀገር ነበረች:: (ዘፀ 8፥1,29) ስለዚህም ግብጽ ጌታን ያወቀችው በዓመተ ምሕረት ነውና
ኢሳይያስ በትንቢቱ የሚናገረው በዘመነ ሐዲስ ኪዳን በቤተክርስቲያን በቁርባኑና በመስዋዕቱ እንድናከብረው ጌታ
መውደዱን ይገለጥ ዘንድ ነው:: በትንቢት የተነገረው ይፈፅም ዘንድ መሰረትዋም ይመሰርት ዘንድ "አንተ ጴጥሮስ ነህ፥
በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም" በማለት ወልድ ዋሕድ በሚል እምነት እቺን ቤ/ክ ሰራ:: በማይናወፅ ምስክርነት የማትናወፅ ቤ/ክ አቆመ:: በክርስቶስም የማዕዘን ድንጋይነት፣ በጴጥሮስ ዓለትነት፣
በሐዋርያትና በነብያት መሰረትነት መቅደሱን መሰረተ::"በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥
የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው" እንዲል(ኤፌ 2፥20 ፤ 5፥23)::የሐዲስ ኪዳንዋ ቤ/ክ ለሐዲስ ኪዳኑ መስዋዕት የመሰውያው ቦታ ሆና ተሾመች:: "መሰዊያ አለን" እንዳለው ቅዱስ ጳውሎስ (ዕብ13፥10)
...ይቀጥላል
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ኃይማኖት
( እስኪ ወደ ቀድሞ ነገር እንመለስ )
ቤተ ክርስቲያን ማለት ትርጉሙ
👉ክርስቲያን የሆነን ሰው (1ቆሮ
3፥16፤ገላ1፥13)
👉 2.የክርስቲያኖች ሕብረትና ጉባኤ (ማቴ 18፥17፤ የሐዋ 5፥11፤ ቆላ4፥15)
👉 3.ክርስቲያኖች የሚሰበሰቡበት፥ ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን የሚቀበሉበት
የከበረ የተወደደ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው(ማቴ 16፥16፣ የሐዋ11፥26) የሐዲስ ኪዳንዋ ቤ/ክ በብሉይ አስቀድማ በትንቢት የተነገረች በሐዲስም ራሱ ጌታ በቃሉና በእጁ የሰራት የአማናዊው/እውነተኛው መስዋዕት መሰውያ ናት:: አስቀድሞ
በነብዩ በሚልክያስ "ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና በየስፍራውም ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፥ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ" (ሚልክ1፥11) ተብሎ ነበር:: በብሉይ ዘመን የኦሪት ቤተ መቅደስ፣ ዕጣንና ቁርባን በእስራኤላውያን ዘንድ እንጂ በአሕዛብ ዘንድ ፍጹም አልነበረም!
ስለዚህ ይህ የሚልክያስ ትንቢት በሐዲስ ኪዳን ስጋውና ደሙ ለሚሰጥበት፣ የቅዳሴው ዕጣንም ለሚቀርብበት ቤ/ክ የተነገረ መሆኑ ግልፅ ነው:: ነብዩ ኢሳይያስም "በዚያም ቀን እግዚአብሔር በግብጽ የታወቀ ይሆናል፥ ግብጻውያንም እግዚአብሔርን ያውቃሉ በመሥዋዕትና በቍርባን
ያመልካሉ"ኢሳ19፥21 አለ:: በብሉይ ኪዳን ጊዜ ግብፅ የአሕዛብ ከተማ የነበረች፣ እስራኤላውያን በግብፅ ምድር ሆነው መስዋዕት እንዳይሰው የተከለከለች ሀገር ነበረች:: (ዘፀ 8፥1,29) ስለዚህም ግብጽ ጌታን ያወቀችው በዓመተ ምሕረት ነውና
ኢሳይያስ በትንቢቱ የሚናገረው በዘመነ ሐዲስ ኪዳን በቤተክርስቲያን በቁርባኑና በመስዋዕቱ እንድናከብረው ጌታ
መውደዱን ይገለጥ ዘንድ ነው:: በትንቢት የተነገረው ይፈፅም ዘንድ መሰረትዋም ይመሰርት ዘንድ "አንተ ጴጥሮስ ነህ፥
በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም" በማለት ወልድ ዋሕድ በሚል እምነት እቺን ቤ/ክ ሰራ:: በማይናወፅ ምስክርነት የማትናወፅ ቤ/ክ አቆመ:: በክርስቶስም የማዕዘን ድንጋይነት፣ በጴጥሮስ ዓለትነት፣
በሐዋርያትና በነብያት መሰረትነት መቅደሱን መሰረተ::"በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥
የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው" እንዲል(ኤፌ 2፥20 ፤ 5፥23)::የሐዲስ ኪዳንዋ ቤ/ክ ለሐዲስ ኪዳኑ መስዋዕት የመሰውያው ቦታ ሆና ተሾመች:: "መሰዊያ አለን" እንዳለው ቅዱስ ጳውሎስ (ዕብ13፥10)
...ይቀጥላል
@And_Haymanot
@And_Haymanot
....የቀጠለ በመጀመርያው ክ/ዘ ጌታ ካረገ ከ15 ዓመት ብኋላ እመበታችን አርፋ ካረገች ብኋላ 4 ዓመታት እንዳለፉ በ53ዓ.ም ቤተ
ክርስቲያን በጉባኤ መልክ እየሰፋ ሲሄድ ጳውሎስና በርናባስ ባስተማሩባት የፍልጵስዩስ ከተማ ቤ/ክ ይሰራ ዘንድ ግድ ነበር:: በዚህም ሐዋርያት ሱባዔ ይዘው ወደ ጌታ አመለከቱ:: ጌታም
በፊልጶስ ቂሳርያ ለጴጥሮስ በገባለት ቃል ኪዳን መሰረት ሐዋርያትን ለስብከት ከሄዱበት ሀገረ ስብከታቸው በደመና
እየጠራ ፊልጵስዩስ ከሰበሰባቸው ብኋላ አስቀድሞ በነብያት በየቦታው መቅደሱ ይሰራ ዘንድ ባዘዘው መሰረት 3 ድንጋዮችን አንስቶ በእጁ እየለመለሙለት የመጀመርያዋን ቤ/ክ መሰረትዋን
ግድግዳዋንና ጣራዋን ሰርቶ በእናቱ በእናታችን በወዳጁ በእመቤታችን ስም ሰይሞ ስጥቷቸዋል:: ሕንጸተ ቤታም
አከበሩ:: በነጋታው በሰኔ 21 ጌታ ራሱ በሰራት ቤ/ክ ቀድሶ የራሱን ስጋና ደም በማቁረብ ቅዳሴ ቤታን አክብሯል:: ቅዱስ ያሬድ ይህንን ዕለት በማስመልከት "ለዛቲ ቤት ሐነፃ ወልድ
ወፈፀማ መንፈስ ቅዱስ - ይህቺን ቤት ወልድ ሰራት መንፈስ ቅዱስም አጠናቀቃት"አለ:: ይህም ክርስቶስ እንደሰራት፣ መንፈስ ቅዱስም "የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ
ይመራችኋል"እንዲል (ዮሐ16፥13) አጠናቀቃት አለ! መራት ጠበቃት፥ ይመራታል ይጠብቃታል ሲል ነው::....ይቀጥላል
@And_Haymanot
ክርስቲያን በጉባኤ መልክ እየሰፋ ሲሄድ ጳውሎስና በርናባስ ባስተማሩባት የፍልጵስዩስ ከተማ ቤ/ክ ይሰራ ዘንድ ግድ ነበር:: በዚህም ሐዋርያት ሱባዔ ይዘው ወደ ጌታ አመለከቱ:: ጌታም
በፊልጶስ ቂሳርያ ለጴጥሮስ በገባለት ቃል ኪዳን መሰረት ሐዋርያትን ለስብከት ከሄዱበት ሀገረ ስብከታቸው በደመና
እየጠራ ፊልጵስዩስ ከሰበሰባቸው ብኋላ አስቀድሞ በነብያት በየቦታው መቅደሱ ይሰራ ዘንድ ባዘዘው መሰረት 3 ድንጋዮችን አንስቶ በእጁ እየለመለሙለት የመጀመርያዋን ቤ/ክ መሰረትዋን
ግድግዳዋንና ጣራዋን ሰርቶ በእናቱ በእናታችን በወዳጁ በእመቤታችን ስም ሰይሞ ስጥቷቸዋል:: ሕንጸተ ቤታም
አከበሩ:: በነጋታው በሰኔ 21 ጌታ ራሱ በሰራት ቤ/ክ ቀድሶ የራሱን ስጋና ደም በማቁረብ ቅዳሴ ቤታን አክብሯል:: ቅዱስ ያሬድ ይህንን ዕለት በማስመልከት "ለዛቲ ቤት ሐነፃ ወልድ
ወፈፀማ መንፈስ ቅዱስ - ይህቺን ቤት ወልድ ሰራት መንፈስ ቅዱስም አጠናቀቃት"አለ:: ይህም ክርስቶስ እንደሰራት፣ መንፈስ ቅዱስም "የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ
ይመራችኋል"እንዲል (ዮሐ16፥13) አጠናቀቃት አለ! መራት ጠበቃት፥ ይመራታል ይጠብቃታል ሲል ነው::....ይቀጥላል
@And_Haymanot
..... #ለዛቲ_ቤት_ሐነጻ_ወልድ_ወፈፀማ_መንፈስ_ቅዱስ ሰኔ 21
ዛሬ ይህንን የቤ/ክ የመሰራትና የቅዳሴዋ በዓል ስናከብር እቺን
ቤ/ክ ለመጠበቅ ደም የለበሱትን፥ ሊያኖርዋት የሞቱትን፥ ቅርሶችዋን ለመጠበቅ በየዱሩ የአውሬ እራት የሆኑትን በየገደሉም የተረሱትን አባቶች በማስታወስ ነው::ክርስቲያኖች
በድንጋይ ተወግረው ወደ ገደል ቢጣሉም፥ ቆዳቸው ተልጦ ጨው ቢጨመርባቸውም፥ አንገታቸው ተቀልቶ ቁልቁል ቢሰቀሉም ሞታቸው ብዙዎችን እየወለደ፥ ደማቸውም ለራሳቸውና ለብዙዎች ጥምቀት እየሆነ፥ እቺን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለኛ አስረክበዋል:: በእውነት ምስጋና ይገባቸዋል::
ምስጋና- በ9ኛው ክ/ዘ በዮዲት ጉዲት ጊዜ 40 ዓመት ሙሉ በየጫካው
ታቦታቱንና ንዋየ ቅድሳቱን ይዘው ለተሰደዱት አባቶች! ክብር- በ16ኛው ክ/ዘ በአሕመድ ግራኝ ጊዜ ማዕተባችንን አንበጥስም ላሉት ቅዱሳን! ውዳሴ- በ17ኛው ክ/ዘ በንጉስ ሱስንዮስ ለታወጀው ካቶሊካዊ አዋጅ አንቀበልም ብለው ለታረዱት 8000
ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን! ልዕልና- በዘመነ መሳፍንት ቅብዓትንና ጸጋን ተከራክረው በመርታት ተዋሕዶን ለመሰከሩ ሊቃውንት አባቶች! መወደድ- የዛሬዋን ቤ/ክ ለመጠበቅ በየገዳማቱ በጸሎት ለተጠመዱት አበው መነኮሳት፥ የጽድቅም አክሊል ቤ/ክንን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ መናፍቃንንና
ተሐድሶን ለሚቃወሙ መምህራን፥ ምዕመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች! አምልኮና ስግደትም ይቺን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመሰረታት ለትንሳኤው ጌታ ለክርስቶስ ኢየሱስ
ይሁን!!
# ለዛቲ_ቤት_ሐነጻ_ወልድ_ወፈፀማ_መንፈስ_ቅዱስ !!
©Binyam ZeChristos ሰኔ 20 - 2010
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ዛሬ ይህንን የቤ/ክ የመሰራትና የቅዳሴዋ በዓል ስናከብር እቺን
ቤ/ክ ለመጠበቅ ደም የለበሱትን፥ ሊያኖርዋት የሞቱትን፥ ቅርሶችዋን ለመጠበቅ በየዱሩ የአውሬ እራት የሆኑትን በየገደሉም የተረሱትን አባቶች በማስታወስ ነው::ክርስቲያኖች
በድንጋይ ተወግረው ወደ ገደል ቢጣሉም፥ ቆዳቸው ተልጦ ጨው ቢጨመርባቸውም፥ አንገታቸው ተቀልቶ ቁልቁል ቢሰቀሉም ሞታቸው ብዙዎችን እየወለደ፥ ደማቸውም ለራሳቸውና ለብዙዎች ጥምቀት እየሆነ፥ እቺን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለኛ አስረክበዋል:: በእውነት ምስጋና ይገባቸዋል::
ምስጋና- በ9ኛው ክ/ዘ በዮዲት ጉዲት ጊዜ 40 ዓመት ሙሉ በየጫካው
ታቦታቱንና ንዋየ ቅድሳቱን ይዘው ለተሰደዱት አባቶች! ክብር- በ16ኛው ክ/ዘ በአሕመድ ግራኝ ጊዜ ማዕተባችንን አንበጥስም ላሉት ቅዱሳን! ውዳሴ- በ17ኛው ክ/ዘ በንጉስ ሱስንዮስ ለታወጀው ካቶሊካዊ አዋጅ አንቀበልም ብለው ለታረዱት 8000
ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን! ልዕልና- በዘመነ መሳፍንት ቅብዓትንና ጸጋን ተከራክረው በመርታት ተዋሕዶን ለመሰከሩ ሊቃውንት አባቶች! መወደድ- የዛሬዋን ቤ/ክ ለመጠበቅ በየገዳማቱ በጸሎት ለተጠመዱት አበው መነኮሳት፥ የጽድቅም አክሊል ቤ/ክንን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ መናፍቃንንና
ተሐድሶን ለሚቃወሙ መምህራን፥ ምዕመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች! አምልኮና ስግደትም ይቺን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመሰረታት ለትንሳኤው ጌታ ለክርስቶስ ኢየሱስ
ይሁን!!
# ለዛቲ_ቤት_ሐነጻ_ወልድ_ወፈፀማ_መንፈስ_ቅዱስ !!
©Binyam ZeChristos ሰኔ 20 - 2010
@And_Haymanot
@And_Haymanot
[ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ ገደለው]
@And_Haymanot
"ኦርቶዶክስ መልስ ካላት እኛም ጥያቄ አለን" በሚል ርዕስ በተሐድሶ
መናፍቃን በ 2004 ዓ.ም ግንቦት 15 በቅዱስ ሲኖዶስ የተወገዙት እነ
ጽጌ ስጦታው CD ማዘጋጀታቸው ይታወሳል፡፡ ለጥያቄያቸው በግዜው በቂ መልስ የተሠጣቸው ቢሆንም ባለማወቅ የሚፍጨረጨሩ ልጆቻቸው መልስ ይሆን ዘንድ አቅርበነዋል በዚህ CD የጠየቁት አንዱ ጥያቄ በ 81 መጽሐፍ ቅዱስ ላይ "ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ
ገደለው" የሚለውን የሚተች ነበርና በውኑ ትችታቸው ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር ሲመዘን ሚዛን ይደፋልን?
+++ "ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ ገደለው" ማለት ትክክል አይደለምን?
ነጩን ማጥቆር ጣፋጩን ማምረር የሚወዱ የተሐድሶ መናፍቃን
የሚያጠራጥሩበት ጥቅስ ነው:: "ወንድሙ የሚወድደው መስሎት
በየዋህነት የተከተለውን ወንድሙን በገደለው በቃየን መንገድ አትሂድ;
እርሱም በሴት ቀንቶ ወንድሙን ገደለው::" |1ኛ.መቃ.23:1-2; የ2000ዓ.ም ዕትም| የሚለውን በመጥቀስ ሳይሆን ለእኩይ ግብራቸው
በመንቀስ ይተቻሉ:: አርሲሳኑ|መናፍቃኑ| እንደ ማስረጃ የሚያቀርቡት ሐዋርያው ዮሐንስም ቃየን አቤልን ስለገደለበት ሲናገር "ቃየን ስለምን ወንድሙን ገደለው? የእርሱ ስራ ክፉ የወንድሙ ጽድቅ ስለነበረ ነው::"
1ኛ.ዮሐ.3:12 በማለት በልቡ ክፋትና በአቤል መልካምነት የተነሳ እንጂ እንዴት በሴት ምክንያት ነው የገደለው ይባላል? ይላሉ::
መልስ:- አቤልና ቃየን ከአዳምና ከሔዋን ተለይተው ብቻቸውን ለምን
መሥዋዕት አቀረቡ? እግዚአብሔር የሚመለከው በፍጥረት ሁሉ ነው::
ታዲያ አዳምና ሔዋን ስለምን መሥዋዕት አላቀረቡም? እነዚህን ጥያቄዎች የሚመልሱልን መጽሐፈ መቃብያንና መጽሐፈ ኩፋሌ እንዲሁም አዋልድ መጻሕፍት ናቸው:: ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ያለ እነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት ምሉዕ ሊሆኑ አይችሉም ማለት ነው::
በዘፍ.4:17 ላይ "ቃየንም ሚስቱን አወቀ; ጸነሰችም ሄኖህንም ወለደች::" ይላል:: ይህች ሴት ከየት መጣች? ቀድሞ አዳምና ሔዋን የወለዱት ቃየንና አቤል ብቻ መሆናቸውን ገልጾ አልነበረምን? ይህች ሴት ከእነርሱ ጋር ከነበረች እንደ አቤልና እንደ ቃየን ለምን መሥዋዕት
አላቀረበችም? የሚል ጥያቄ ያስነሳል:: አሁን ለምን ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ ገደለው ተብሎ የተገለጸውን እንመልከት:: መጽሐፈ ኩፋሌ ሲገልጽ አባታቸው አዳም ከቃየንና ከአቤል ጋር ሌሎች ሁለት ሴቶች እንደ ተወለዱ ይናገራል:: "ሔዋንም በአምስተኛው ሱባኤ አዋንን ወለደቻት አዳምም በስድስተኛው ሱባኤ ልዋን ወለዳት::" |ኩፋ.5:8| ይላል:: እነዚህ ሴቶች ልጆች ከወንዶች ጋር መንትዮች ሆነው እንደተወለዱ የውዳሴና የቅዳሴ ማርያም አንድምታ እንዲሁም ገድለ
አዳምም|First Book of Adam and Eve Prologue; P.1| ይገልጻል:: መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም እንዲህ ይላል:- "አዳምና ሔዋን ከደብር ቅዱስ ወርደው ከሱ በታች ተቀመጡ:: በዚሁ አዳም ሔዋንን ተገናኛት:: እሷም ፀነሰች:: የመውለጃዋ ጊዜም ደረሰ::
ቃየልንና ሉድንም መንታዎች ወለደች:: ዳግመኛም ሔዋን ፀነሰች:: የመውለጃዋም ጊዜ ደረሰ:: መንታዎቹን አቤልንና አቅሌምያንም ወለደች:: እነዚህ ሁለት ወንዶችና ሁለት ሴቶች የአዳም ልጆች አድገው:: ለጋብቻ ደረሱ:: አዳም ይህን ተመልክቶ ሔዋንን እነሆ
እግዚአብሔር እነዚህ ልጆቻችንን አሳደጋቸው:: ስለዚህ ቃየል የአቤልን
እህት አቅሌምያን ያግባት:: አቤል ደግሞ የቃየልን እህት ሉድን ያግባት አላት:: አዳምና ሔዋን በዚሁ ተስማሙ::" ይላል:: [መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ምዕራፍ አንድ]. በዚህም ምክንያት በአንድነት ያደጉት መንትያ የሆኑት ማለት ከቃየን ጋር አብራ የምትውል|የተወለደች| ና
ከአቤል ጋር አብራ የምትውል|የተወለደች| በአንድነት እንደማይጋቡ አዳም በልቦናው ስላወቀና እግዚአብሔርም ስለ ገለጸለት ሁለቱም
ሴቶች ልጆች ተቀያይረው እንዲጋቡ ፈቀደ:: ገድለ አዳምም ስለዚህ
ሁናቴ ሲገልጽ Then Adam said to her|Eve|, "We will join Abel's sister in marriage to Cain, the Cain's sister to Abel."|Second Book of Adam and Eve; Chapter LXXVIII|. ይላል:: ነገር ግን ቃየን በአባቱ ሃሳብ ስላልተስማማና ስላዘነ
አዳም ወዲያውኑ ያደረገው አቤልና ቃየን በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ነገራቸው:: ይህን ያደረገበት ምክንያት ከአቤል ጋር ያልተወለደችውን መንትያ እግዚአብሔር መሥዋዕቱን ከተቀበለው ከእርሷ ጋር እንዲጋባ ነበር:: "But when Adam saw that the older brother hated the younger, he endeavor f to
soften their hearts, and said to Cain, "O my son, take of the fruits of your sowing and make an offering to God, so that He might forgive you for your wickedness and sin." He said also to Abel, "Take son of your sowing and make an offering and bring it to God, so that He might forgive you for your wickedness and sin."|Second Book of Adam and Eve; Chapter LXVII|. ቃየን
ግን ቀድሞውንም በዚህ ውሳኔ አዝኖ ነበርና ይበልጥ ክፋት ሠራ:: ይህም ለእግዚአብሔር ከፍሬው እንክርዳድ ያለበትን መሥዋዕት ሊቃጠል ነው እንጂ:: እግዚአብሔር ንስሐ እንዲገባ ምክር መከረው:: "ለምንስ ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቆረ? መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚያበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅዋ
ታደባለች; ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው:: አንተ ግን በእርሷ ንገስባት::" |
ዘፍ.4:6-7| ያለው:: ይህም ማለት የአባትህ ሃሳብ የእኔ ነውና ተቀበለው በአባትህ ሃሳብ አትናደድ; አትዘን; የአባትህ ሃሳብ የእኔ ነውና:: ለዚህ ነው የአቤልን መሥዋዕት የተቀበልኩት ሲል ነው:: God would accept Abel's offering. Then God looked at Abel and accepted his offering. ... because of his good heart and pure body. |Second Book of Adam and Eve Chapter LXVII|. ቃየን ወንድሙን ለመግደል ያነሳሳው
የመጀመሪያው ምክንያት በሴት መሆኑን እንረዳለን ማለት ነው:: ለዚህም ነው ገድለ አዳም Cain becomes jealous of Abel because of his sisters. |Chapter LXXVI| ያለው:: ምክንያቱም እግዚአብሔር የአቤልን መሥዋዕት ከተቀበለ የአባቱ የአዳም ፈቃድ በማራራቅ ሊያጋባቸው እንደወሰነ ስላወቀ ይህችን የሚፈልጋት ሴት
ለማግባት ደግሞ ወንድሙን ለመግደል በቅናት ተነሳ:: ገድለ አዳምም
Jealousy overcomes Cain|Chapter LXXVIII| ይላል:: | ዘፍ.4:17; ኩፋ.5:8|. በ 1ኛ.ዮሐ.3:12 ላይ የተገለጸውን ከመቃብያንና ከዘፍጥረት ጋር ሃሳባቸው የተጋጨ አይደለም:: የአቤል ሥራው ወይም ጽድቁ ምን ነበር? የቃየንስ ክፉ ሥራ ምን ነበር? ብለን ብንጠይቅ የመጀመሪያው ምክንያት መሥዋዕት ማቅረባቸው ሊሆን አይችልም:: ነገር ግን ቃየን በአቤል በመቅናቱ ነው:: የቀናበት
ምክንያት ስንመለከት ደግሞ የመጀመሪያው የሚወዳት ሴቷን አቤል
እንደሚያገባት ሲያውቅና የእርሱ
@And_Haymanot
"ኦርቶዶክስ መልስ ካላት እኛም ጥያቄ አለን" በሚል ርዕስ በተሐድሶ
መናፍቃን በ 2004 ዓ.ም ግንቦት 15 በቅዱስ ሲኖዶስ የተወገዙት እነ
ጽጌ ስጦታው CD ማዘጋጀታቸው ይታወሳል፡፡ ለጥያቄያቸው በግዜው በቂ መልስ የተሠጣቸው ቢሆንም ባለማወቅ የሚፍጨረጨሩ ልጆቻቸው መልስ ይሆን ዘንድ አቅርበነዋል በዚህ CD የጠየቁት አንዱ ጥያቄ በ 81 መጽሐፍ ቅዱስ ላይ "ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ
ገደለው" የሚለውን የሚተች ነበርና በውኑ ትችታቸው ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር ሲመዘን ሚዛን ይደፋልን?
+++ "ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ ገደለው" ማለት ትክክል አይደለምን?
ነጩን ማጥቆር ጣፋጩን ማምረር የሚወዱ የተሐድሶ መናፍቃን
የሚያጠራጥሩበት ጥቅስ ነው:: "ወንድሙ የሚወድደው መስሎት
በየዋህነት የተከተለውን ወንድሙን በገደለው በቃየን መንገድ አትሂድ;
እርሱም በሴት ቀንቶ ወንድሙን ገደለው::" |1ኛ.መቃ.23:1-2; የ2000ዓ.ም ዕትም| የሚለውን በመጥቀስ ሳይሆን ለእኩይ ግብራቸው
በመንቀስ ይተቻሉ:: አርሲሳኑ|መናፍቃኑ| እንደ ማስረጃ የሚያቀርቡት ሐዋርያው ዮሐንስም ቃየን አቤልን ስለገደለበት ሲናገር "ቃየን ስለምን ወንድሙን ገደለው? የእርሱ ስራ ክፉ የወንድሙ ጽድቅ ስለነበረ ነው::"
1ኛ.ዮሐ.3:12 በማለት በልቡ ክፋትና በአቤል መልካምነት የተነሳ እንጂ እንዴት በሴት ምክንያት ነው የገደለው ይባላል? ይላሉ::
መልስ:- አቤልና ቃየን ከአዳምና ከሔዋን ተለይተው ብቻቸውን ለምን
መሥዋዕት አቀረቡ? እግዚአብሔር የሚመለከው በፍጥረት ሁሉ ነው::
ታዲያ አዳምና ሔዋን ስለምን መሥዋዕት አላቀረቡም? እነዚህን ጥያቄዎች የሚመልሱልን መጽሐፈ መቃብያንና መጽሐፈ ኩፋሌ እንዲሁም አዋልድ መጻሕፍት ናቸው:: ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ያለ እነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት ምሉዕ ሊሆኑ አይችሉም ማለት ነው::
በዘፍ.4:17 ላይ "ቃየንም ሚስቱን አወቀ; ጸነሰችም ሄኖህንም ወለደች::" ይላል:: ይህች ሴት ከየት መጣች? ቀድሞ አዳምና ሔዋን የወለዱት ቃየንና አቤል ብቻ መሆናቸውን ገልጾ አልነበረምን? ይህች ሴት ከእነርሱ ጋር ከነበረች እንደ አቤልና እንደ ቃየን ለምን መሥዋዕት
አላቀረበችም? የሚል ጥያቄ ያስነሳል:: አሁን ለምን ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ ገደለው ተብሎ የተገለጸውን እንመልከት:: መጽሐፈ ኩፋሌ ሲገልጽ አባታቸው አዳም ከቃየንና ከአቤል ጋር ሌሎች ሁለት ሴቶች እንደ ተወለዱ ይናገራል:: "ሔዋንም በአምስተኛው ሱባኤ አዋንን ወለደቻት አዳምም በስድስተኛው ሱባኤ ልዋን ወለዳት::" |ኩፋ.5:8| ይላል:: እነዚህ ሴቶች ልጆች ከወንዶች ጋር መንትዮች ሆነው እንደተወለዱ የውዳሴና የቅዳሴ ማርያም አንድምታ እንዲሁም ገድለ
አዳምም|First Book of Adam and Eve Prologue; P.1| ይገልጻል:: መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም እንዲህ ይላል:- "አዳምና ሔዋን ከደብር ቅዱስ ወርደው ከሱ በታች ተቀመጡ:: በዚሁ አዳም ሔዋንን ተገናኛት:: እሷም ፀነሰች:: የመውለጃዋ ጊዜም ደረሰ::
ቃየልንና ሉድንም መንታዎች ወለደች:: ዳግመኛም ሔዋን ፀነሰች:: የመውለጃዋም ጊዜ ደረሰ:: መንታዎቹን አቤልንና አቅሌምያንም ወለደች:: እነዚህ ሁለት ወንዶችና ሁለት ሴቶች የአዳም ልጆች አድገው:: ለጋብቻ ደረሱ:: አዳም ይህን ተመልክቶ ሔዋንን እነሆ
እግዚአብሔር እነዚህ ልጆቻችንን አሳደጋቸው:: ስለዚህ ቃየል የአቤልን
እህት አቅሌምያን ያግባት:: አቤል ደግሞ የቃየልን እህት ሉድን ያግባት አላት:: አዳምና ሔዋን በዚሁ ተስማሙ::" ይላል:: [መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ምዕራፍ አንድ]. በዚህም ምክንያት በአንድነት ያደጉት መንትያ የሆኑት ማለት ከቃየን ጋር አብራ የምትውል|የተወለደች| ና
ከአቤል ጋር አብራ የምትውል|የተወለደች| በአንድነት እንደማይጋቡ አዳም በልቦናው ስላወቀና እግዚአብሔርም ስለ ገለጸለት ሁለቱም
ሴቶች ልጆች ተቀያይረው እንዲጋቡ ፈቀደ:: ገድለ አዳምም ስለዚህ
ሁናቴ ሲገልጽ Then Adam said to her|Eve|, "We will join Abel's sister in marriage to Cain, the Cain's sister to Abel."|Second Book of Adam and Eve; Chapter LXXVIII|. ይላል:: ነገር ግን ቃየን በአባቱ ሃሳብ ስላልተስማማና ስላዘነ
አዳም ወዲያውኑ ያደረገው አቤልና ቃየን በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕት እንዲያቀርቡ ነገራቸው:: ይህን ያደረገበት ምክንያት ከአቤል ጋር ያልተወለደችውን መንትያ እግዚአብሔር መሥዋዕቱን ከተቀበለው ከእርሷ ጋር እንዲጋባ ነበር:: "But when Adam saw that the older brother hated the younger, he endeavor f to
soften their hearts, and said to Cain, "O my son, take of the fruits of your sowing and make an offering to God, so that He might forgive you for your wickedness and sin." He said also to Abel, "Take son of your sowing and make an offering and bring it to God, so that He might forgive you for your wickedness and sin."|Second Book of Adam and Eve; Chapter LXVII|. ቃየን
ግን ቀድሞውንም በዚህ ውሳኔ አዝኖ ነበርና ይበልጥ ክፋት ሠራ:: ይህም ለእግዚአብሔር ከፍሬው እንክርዳድ ያለበትን መሥዋዕት ሊቃጠል ነው እንጂ:: እግዚአብሔር ንስሐ እንዲገባ ምክር መከረው:: "ለምንስ ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቆረ? መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚያበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅዋ
ታደባለች; ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው:: አንተ ግን በእርሷ ንገስባት::" |
ዘፍ.4:6-7| ያለው:: ይህም ማለት የአባትህ ሃሳብ የእኔ ነውና ተቀበለው በአባትህ ሃሳብ አትናደድ; አትዘን; የአባትህ ሃሳብ የእኔ ነውና:: ለዚህ ነው የአቤልን መሥዋዕት የተቀበልኩት ሲል ነው:: God would accept Abel's offering. Then God looked at Abel and accepted his offering. ... because of his good heart and pure body. |Second Book of Adam and Eve Chapter LXVII|. ቃየን ወንድሙን ለመግደል ያነሳሳው
የመጀመሪያው ምክንያት በሴት መሆኑን እንረዳለን ማለት ነው:: ለዚህም ነው ገድለ አዳም Cain becomes jealous of Abel because of his sisters. |Chapter LXXVI| ያለው:: ምክንያቱም እግዚአብሔር የአቤልን መሥዋዕት ከተቀበለ የአባቱ የአዳም ፈቃድ በማራራቅ ሊያጋባቸው እንደወሰነ ስላወቀ ይህችን የሚፈልጋት ሴት
ለማግባት ደግሞ ወንድሙን ለመግደል በቅናት ተነሳ:: ገድለ አዳምም
Jealousy overcomes Cain|Chapter LXXVIII| ይላል:: | ዘፍ.4:17; ኩፋ.5:8|. በ 1ኛ.ዮሐ.3:12 ላይ የተገለጸውን ከመቃብያንና ከዘፍጥረት ጋር ሃሳባቸው የተጋጨ አይደለም:: የአቤል ሥራው ወይም ጽድቁ ምን ነበር? የቃየንስ ክፉ ሥራ ምን ነበር? ብለን ብንጠይቅ የመጀመሪያው ምክንያት መሥዋዕት ማቅረባቸው ሊሆን አይችልም:: ነገር ግን ቃየን በአቤል በመቅናቱ ነው:: የቀናበት
ምክንያት ስንመለከት ደግሞ የመጀመሪያው የሚወዳት ሴቷን አቤል
እንደሚያገባት ሲያውቅና የእርሱ
ቃየን አቤልን በሴት ቀንቶ ገደለው?
....የቀጠለ...
እንደማትሆን ሲረዳ በቅናት ወንድሙን ገድሎታል:: ሐሰት በ 4 ደረጃዎች እንደሚሰራ ማለት ነው:: ይህም በመጀመሪያ ከልብ ይጸነሳል; ከዚያም በገጽታ; ከዚያም በቃላት ወይም
በአንደበት በመናገር በመጨረሻም በተግባር እንደምንፈጽመው ማለት
ነው:: ልክ እንደዚህ ሁሉ መጽሐፈ መቃብያን የመጀመሪያውን ምክንያት
የሆነውን በሴት እንደቀና ገለጸው; ቀጥሎ ያለው ደግሞ በኦሪት እንደተገለጸው በመሥዋዕቱ ምክንያት እንደሆነ ገልጾታል:: ሐዋርያው
ዮሐንስ ደግሞ የሦስተኛው የሆነውን የገደለበትን ምክንያትና ውጤቱን
ጽፎታል:: ከዚህም የምንረዳው በተለያየ ክፍሎች የአቤልና የቃየንን ጉዳይ ተካፍለው እንደጻፉት ነው:: እንዲህ ካልሆነማ ቃየን አቤልን የገደለበት ምክንያት በመሥዋዕቱ ነው? ወይስ ክፉ ስራ ስለሠራ ነው? ክፉ ሥራ ተብሎ የተገለጸው ምን ይሆን? ታዲያ መጽሐፈ መቃብያን የመጀመሪያው ምክንያት ወስዶ ቢጽፈው ስህተቱ ምኑ ላይ ነው???? ‹‹ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች እያሳቱና እየሣቱ በክፋት
እየባሱ ይሄዳሉ፤ አንተ ግን በተማርክበትና በተረዳህበት ነገር
ፀንተህ ኑር ከማን እንደተማርከው ታውቃለህና ከህፃንነትም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጽሐፍትን አውቀሃል›› 2ኛ ጢሞ 3፥13-18)
ወሰብሀት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ከክቡር!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
....የቀጠለ...
እንደማትሆን ሲረዳ በቅናት ወንድሙን ገድሎታል:: ሐሰት በ 4 ደረጃዎች እንደሚሰራ ማለት ነው:: ይህም በመጀመሪያ ከልብ ይጸነሳል; ከዚያም በገጽታ; ከዚያም በቃላት ወይም
በአንደበት በመናገር በመጨረሻም በተግባር እንደምንፈጽመው ማለት
ነው:: ልክ እንደዚህ ሁሉ መጽሐፈ መቃብያን የመጀመሪያውን ምክንያት
የሆነውን በሴት እንደቀና ገለጸው; ቀጥሎ ያለው ደግሞ በኦሪት እንደተገለጸው በመሥዋዕቱ ምክንያት እንደሆነ ገልጾታል:: ሐዋርያው
ዮሐንስ ደግሞ የሦስተኛው የሆነውን የገደለበትን ምክንያትና ውጤቱን
ጽፎታል:: ከዚህም የምንረዳው በተለያየ ክፍሎች የአቤልና የቃየንን ጉዳይ ተካፍለው እንደጻፉት ነው:: እንዲህ ካልሆነማ ቃየን አቤልን የገደለበት ምክንያት በመሥዋዕቱ ነው? ወይስ ክፉ ስራ ስለሠራ ነው? ክፉ ሥራ ተብሎ የተገለጸው ምን ይሆን? ታዲያ መጽሐፈ መቃብያን የመጀመሪያው ምክንያት ወስዶ ቢጽፈው ስህተቱ ምኑ ላይ ነው???? ‹‹ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች እያሳቱና እየሣቱ በክፋት
እየባሱ ይሄዳሉ፤ አንተ ግን በተማርክበትና በተረዳህበት ነገር
ፀንተህ ኑር ከማን እንደተማርከው ታውቃለህና ከህፃንነትም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጽሐፍትን አውቀሃል›› 2ኛ ጢሞ 3፥13-18)
ወሰብሀት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ከክቡር!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ወዳጄ ሆይ ለነዳያን የምሰጠው የምመጸውተው ገንዘብ ይብዛልኝ ማለት አይገባህም፤ ልዑል እግዚአብሔር ከኛ ይልቅ የሚረባንን የሚጠቅመንን ያውቃልና፡፡ አንተ ግን ብዙ ገንዘብ ባገኘህ ጊዜ በመሳሳት አንዱን ሁለት ሁለቱን ሦስት ላድርግ ማለት ይመጣብህ እንደሆነ አታውቅምና፡፡ ነገር ግን አንተ ዛሬ የምትሰጥ የምትመጸውት ይመስልሀል፡፡ ሰጥቶ ቢፈትንህ ላኑር፤ ላብዛ አልስጥ፤ ላስቀምጥ በማለት አእምሮህ በተለወጠ ነበር፤ ልክ እንደ አውሎጊስ፤
ይህ አውሎጊስ ወፍጮ እየነጠለ እያለዘበ ያንን እየሸጠ ለልብስ፤ ለቀለብ እያስቀረ ይመጸውት ነበር፡፡ ዳንኤል የሚባል ባሕታዊ ወዳጅ ነበረው፤ ከቤቱ ሒዶ አድሮ እንዲህ ሲያደርግ አይቷል ዕለት ዕለት ይጠይቀው ነበርና፤ በዚህ
በጥቂት ገንዘብ እንዲህ ያደረገ ብዙ ገንዘብ ቢያገኝ ነዳያንን እንደምን በጠቀመ ነበር ብሎ ብዕል እንዲሰጠው ወደ ጌታ አመለከተ፡፡ አይሆንም ይበድለኛል አለው፤ እኔ እዋሰዋለው አይበድልህም አለ፡፡ ከዚህ በኋላ ከዕለታት ባንድ ቀን ወፍጮ ሲነጥል ድስት ሙሉ ወርቅ አገኘ ወስዶ ለንጉሡ አበረከተ፡፡
በዚህ ምክንያት ራስ ቢትወደድነት ሹሞታል፤ ኋላ አውያተ ግፉኣንን/ የተገፉትን ጩኸት/፣ ፅራኀ ነዳያንን/ የነዳያንን ጩኸት/ የማይሰማ ሆነ፡፡ ጌታ፤ ሒዱ ዳንኤልን በምላሱ ስቀሉት ሲል እመቤታችን አማልዳ ስታድነው በራእይ አየ፡፡
ወደዚየሰው ያ ሰው በድሎ ይሆን እስኪ ልሒድና ልጠይቀው ብሎ ሔደ የማያገኘው ሆኖ ሦስት ቀን ያህል ከውጭ አደረ፤ በሦስተኛው ቀን ወደ ውጭ ሲወጣ አየው፡፡ አገኘሁትም አጣሁትም ዛሬ ነው ብሎ ሒዶ ዛቡን ያዘ አስገፍቶት አስደፍቶት ሔደ፡፡ ከዚህ በኋላ እሱ ባወቂ በሕርዩ ይበድላል
አይሆንም ቢለኝ እኔ ባላዋቂ ባሕር አይበድልም አልሁ ብሎ ሒዶ ከሥዕለ ማርያም ተማፅኖ አድናዋለችና እንዲህ አለ፡፡ ......... ተግሳጽ ዘዮሐንስ አፈወርቅ........
Zemaryam zeleke
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ይህ አውሎጊስ ወፍጮ እየነጠለ እያለዘበ ያንን እየሸጠ ለልብስ፤ ለቀለብ እያስቀረ ይመጸውት ነበር፡፡ ዳንኤል የሚባል ባሕታዊ ወዳጅ ነበረው፤ ከቤቱ ሒዶ አድሮ እንዲህ ሲያደርግ አይቷል ዕለት ዕለት ይጠይቀው ነበርና፤ በዚህ
በጥቂት ገንዘብ እንዲህ ያደረገ ብዙ ገንዘብ ቢያገኝ ነዳያንን እንደምን በጠቀመ ነበር ብሎ ብዕል እንዲሰጠው ወደ ጌታ አመለከተ፡፡ አይሆንም ይበድለኛል አለው፤ እኔ እዋሰዋለው አይበድልህም አለ፡፡ ከዚህ በኋላ ከዕለታት ባንድ ቀን ወፍጮ ሲነጥል ድስት ሙሉ ወርቅ አገኘ ወስዶ ለንጉሡ አበረከተ፡፡
በዚህ ምክንያት ራስ ቢትወደድነት ሹሞታል፤ ኋላ አውያተ ግፉኣንን/ የተገፉትን ጩኸት/፣ ፅራኀ ነዳያንን/ የነዳያንን ጩኸት/ የማይሰማ ሆነ፡፡ ጌታ፤ ሒዱ ዳንኤልን በምላሱ ስቀሉት ሲል እመቤታችን አማልዳ ስታድነው በራእይ አየ፡፡
ወደዚየሰው ያ ሰው በድሎ ይሆን እስኪ ልሒድና ልጠይቀው ብሎ ሔደ የማያገኘው ሆኖ ሦስት ቀን ያህል ከውጭ አደረ፤ በሦስተኛው ቀን ወደ ውጭ ሲወጣ አየው፡፡ አገኘሁትም አጣሁትም ዛሬ ነው ብሎ ሒዶ ዛቡን ያዘ አስገፍቶት አስደፍቶት ሔደ፡፡ ከዚህ በኋላ እሱ ባወቂ በሕርዩ ይበድላል
አይሆንም ቢለኝ እኔ ባላዋቂ ባሕር አይበድልም አልሁ ብሎ ሒዶ ከሥዕለ ማርያም ተማፅኖ አድናዋለችና እንዲህ አለ፡፡ ......... ተግሳጽ ዘዮሐንስ አፈወርቅ........
Zemaryam zeleke
@And_Haymanot
@And_Haymanot
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።
በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ቤተሰብ
¶ ሕፃኑም ዮሐንስ በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል። (ሉቃ ፩፥፲፭)
¶ ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ
ሞላባት። (ሉቃ ፩፥፵፩)
¶ አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ።
(ሉቃ ፩፥፷፯)
መጽሐፍ ቅዱስ የዚህን ታላቅ ቤተሰብ ታሪክ በሉቃስ ወንጌል ላይ ካህኑ ዘካርያስ እና ከካህኑ ከአሮን ወገን የሆነች ኤልሳቤጥ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ
በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ በማለት ይገልፃል። የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ታሪክም እንዲህ በሚለው በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ይጀምራል፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ
ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤
ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው
ይመልሳል። እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። (ሉቃ
፩፥፲፭-፲፯) የእግዚአብሔርን ትእዛዝና ሕግጋት እየጠበቀ በቅድስና ይኖር
የነበረው ካህኑ ዘካርያስ ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣውን የቅዱስ ገብርኤል ቃል ባለመስማቱ ሕፃኑ እስከሚወለድ ድረስ
ድዳ እንደሚሆን በአብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ተነገረው። ይወለዳል የተባለው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ
ዮሐንስን የኤልሳቤጥ መፅነስ በቤተሰቡ መካከል ለረጅም ጊዜ ይፈለግ የነበረ ስለነበር ደስታ ሲፈጥር የካህኑ ዘካርያስ ድዳ መሆን ደግሞ ቤተሰቡን የሚያስጨንቅ ሌላ ክስተት ሆነ። ቅድስት
ኤልሳቤጥም ባለመውለዷ ምክንያት በአካባቢው ሰዎች ግን እግዚአብሔር እንዳዘነባትና ልጅ እንደከለከላት ይነገርባት ስለነበር የልምላሜዋ ዘመን ካለፈ በኋላ መፅነስ በመቻሏ ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ
በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል (ሉቃ ፩፥፳፭) በማለት ደስታዋን ገልፃለች። አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ የአዋጅ ነጋሪ ቃል ተብሎ
እንደተነገረው የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካክሉ በማለት ፊት አውራሪ ሆኖ የሚላከውን ቅዱስ ዮሐንስን የፀነሰችው ቅድስት ኤልሳቤጥ
በፀነሰች በስድስተኛው ወር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልትጠይቃት ወደ እርሷ በሔደች ጊዜ እጅግ የሚያስገርም ሁኔታ ተፈጠረ። ይኸውም ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ውስጥ ኾኖ ለቅድስት ድንግል ማርያም እና በማኅፀኗ ላለው ለዓለም መድኃኒት ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰግዷል (ሉቃ.፩፥፳፮-፵፩) ።
ሕፃኑም ከተወለደ በኋላ አባቱ ካህኑ ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ እንደዚህ አለ፦ ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤
እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ ብርሃኑም
በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል። (ሉቃ ፩፥፸፮-፸፱)
በዚያም ዘመን ሄሮድስ የአምላካችን፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ በመፍራቱ የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል የመጀመርያ ውሳኔው ሆነ። (ማቴ. ፪፥፩-፲፮) ቅድስት ኤልሳቤጥም ልጇን ዮሐንስን ይዛ ወደ ምድረ በዳ ተሰደደች። የአዋጅ ነጋሪው ቃል ተብሎ የተነገረለት ቅዱስ ዮሐንስ ጊዜው
ሲደርስ ከነበረበት በረሐ ድምፁን እያሰማ መንግሥተ ሰማያት
ቀርባለችና ንስሐ ግቡ! እያለ እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለው አገር ሁሉ ወጣ። (ሉቃ. ፫፥፫-፮) ። በስብከቱም እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፤ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ኹሉ ይቈረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል፤
ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፤ ምግብም ያለው እንዲሁ ያድርግ፤ ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ፤ በማንም ላይ ግፍ አትሥሩ፤ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፤ ደመወዛችሁም
ይብቃችሁ፤ ይል ነበር። (ሉቃ. ፫፥፯-፲፬) ። የትሕትና አባት የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ ጌታ ሊጠመቅ ወደ እርሱ ሲመጣ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? በማለት የጌታችንን አምላክነት ፍጹም በሆነ
ትሕትና ተናግሯል (ማቴ. ፫፥፲፬) ። ብዙ ተከታይ የነበረውና በስብከቱ የብዙ ሰዎችን ቀልብ የገዛው ቅዱስ ዮሐንስ ስለ
ኢየሱስ ክርስቶስ ሲናገር ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል። (ዮሐ ፫፥፳-፱-፴) በማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር የሚገባውና ከሁሉ የበለጠ ሙሽራ መሆኑን ተናግሯል። መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ካህን፣ መምህር፣ ሐዋርያ፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ እና ሰማዕት ነው። ሊቁም ከሰማይ
መላእክት ወገንም ሆነ በምድር ካሉ ቅዱሳን፣ ነቢያት፣ ካህናት፣ መምህራንና ሐዋርያት መካከል ማንም እንደ ቅዱስ ዮሐንስ መለኮትን ለማጥመቅ የተመረጠ አለመኖሩን በመጥቀስ ዮሐንስ ሆይ ራጉኤል በትጋቱ፣ ኢዮብም በጽድቁ ቢመኙም ሆነ ቢጨነቁ እንደ አንተ የሚነድ እሳትን (መለኮትን) ሊያጠምቁ
አልተቻላቸውም ሲል ተናግሮለታል። (መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ) ።
ሰኔ ፴ ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደበትን ቀን ቤተ ክርስቲያን በቅዳሴ እና ታቦት በማውጣት ታከብራለች። በጌታ የተወደደ እና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ሆኖ አምላክን ለማጥመቅ የታደለው
የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት አይለየን፣ መንፈስ ቅዱስን ተሞልተው ድንቅ ያደረጉና ሕያው ምስክርነትን የሰጡት የመላው ቤተሰብ በረከትም ከሁላችን ጋር ይሁን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ቤተሰብ
¶ ሕፃኑም ዮሐንስ በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል። (ሉቃ ፩፥፲፭)
¶ ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ
ሞላባት። (ሉቃ ፩፥፵፩)
¶ አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ።
(ሉቃ ፩፥፷፯)
መጽሐፍ ቅዱስ የዚህን ታላቅ ቤተሰብ ታሪክ በሉቃስ ወንጌል ላይ ካህኑ ዘካርያስ እና ከካህኑ ከአሮን ወገን የሆነች ኤልሳቤጥ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ
በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ በማለት ይገልፃል። የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ታሪክም እንዲህ በሚለው በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ይጀምራል፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ
ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤
ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው
ይመልሳል። እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። (ሉቃ
፩፥፲፭-፲፯) የእግዚአብሔርን ትእዛዝና ሕግጋት እየጠበቀ በቅድስና ይኖር
የነበረው ካህኑ ዘካርያስ ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣውን የቅዱስ ገብርኤል ቃል ባለመስማቱ ሕፃኑ እስከሚወለድ ድረስ
ድዳ እንደሚሆን በአብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ተነገረው። ይወለዳል የተባለው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ
ዮሐንስን የኤልሳቤጥ መፅነስ በቤተሰቡ መካከል ለረጅም ጊዜ ይፈለግ የነበረ ስለነበር ደስታ ሲፈጥር የካህኑ ዘካርያስ ድዳ መሆን ደግሞ ቤተሰቡን የሚያስጨንቅ ሌላ ክስተት ሆነ። ቅድስት
ኤልሳቤጥም ባለመውለዷ ምክንያት በአካባቢው ሰዎች ግን እግዚአብሔር እንዳዘነባትና ልጅ እንደከለከላት ይነገርባት ስለነበር የልምላሜዋ ዘመን ካለፈ በኋላ መፅነስ በመቻሏ ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ
በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል (ሉቃ ፩፥፳፭) በማለት ደስታዋን ገልፃለች። አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ የአዋጅ ነጋሪ ቃል ተብሎ
እንደተነገረው የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካክሉ በማለት ፊት አውራሪ ሆኖ የሚላከውን ቅዱስ ዮሐንስን የፀነሰችው ቅድስት ኤልሳቤጥ
በፀነሰች በስድስተኛው ወር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልትጠይቃት ወደ እርሷ በሔደች ጊዜ እጅግ የሚያስገርም ሁኔታ ተፈጠረ። ይኸውም ቅዱስ ዮሐንስ በማኅፀን ውስጥ ኾኖ ለቅድስት ድንግል ማርያም እና በማኅፀኗ ላለው ለዓለም መድኃኒት ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰግዷል (ሉቃ.፩፥፳፮-፵፩) ።
ሕፃኑም ከተወለደ በኋላ አባቱ ካህኑ ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ እንደዚህ አለ፦ ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤
እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ ብርሃኑም
በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል። (ሉቃ ፩፥፸፮-፸፱)
በዚያም ዘመን ሄሮድስ የአምላካችን፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ በመፍራቱ የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል የመጀመርያ ውሳኔው ሆነ። (ማቴ. ፪፥፩-፲፮) ቅድስት ኤልሳቤጥም ልጇን ዮሐንስን ይዛ ወደ ምድረ በዳ ተሰደደች። የአዋጅ ነጋሪው ቃል ተብሎ የተነገረለት ቅዱስ ዮሐንስ ጊዜው
ሲደርስ ከነበረበት በረሐ ድምፁን እያሰማ መንግሥተ ሰማያት
ቀርባለችና ንስሐ ግቡ! እያለ እየሰበከ በዮርዳኖስ ዙሪያ ወዳለው አገር ሁሉ ወጣ። (ሉቃ. ፫፥፫-፮) ። በስብከቱም እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፤ መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ኹሉ ይቈረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል፤
ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፤ ምግብም ያለው እንዲሁ ያድርግ፤ ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ፤ በማንም ላይ ግፍ አትሥሩ፤ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፤ ደመወዛችሁም
ይብቃችሁ፤ ይል ነበር። (ሉቃ. ፫፥፯-፲፬) ። የትሕትና አባት የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ ጌታ ሊጠመቅ ወደ እርሱ ሲመጣ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? በማለት የጌታችንን አምላክነት ፍጹም በሆነ
ትሕትና ተናግሯል (ማቴ. ፫፥፲፬) ። ብዙ ተከታይ የነበረውና በስብከቱ የብዙ ሰዎችን ቀልብ የገዛው ቅዱስ ዮሐንስ ስለ
ኢየሱስ ክርስቶስ ሲናገር ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል። (ዮሐ ፫፥፳-፱-፴) በማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር የሚገባውና ከሁሉ የበለጠ ሙሽራ መሆኑን ተናግሯል። መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ካህን፣ መምህር፣ ሐዋርያ፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ እና ሰማዕት ነው። ሊቁም ከሰማይ
መላእክት ወገንም ሆነ በምድር ካሉ ቅዱሳን፣ ነቢያት፣ ካህናት፣ መምህራንና ሐዋርያት መካከል ማንም እንደ ቅዱስ ዮሐንስ መለኮትን ለማጥመቅ የተመረጠ አለመኖሩን በመጥቀስ ዮሐንስ ሆይ ራጉኤል በትጋቱ፣ ኢዮብም በጽድቁ ቢመኙም ሆነ ቢጨነቁ እንደ አንተ የሚነድ እሳትን (መለኮትን) ሊያጠምቁ
አልተቻላቸውም ሲል ተናግሮለታል። (መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ) ።
ሰኔ ፴ ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደበትን ቀን ቤተ ክርስቲያን በቅዳሴ እና ታቦት በማውጣት ታከብራለች። በጌታ የተወደደ እና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ሆኖ አምላክን ለማጥመቅ የታደለው
የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት አይለየን፣ መንፈስ ቅዱስን ተሞልተው ድንቅ ያደረጉና ሕያው ምስክርነትን የሰጡት የመላው ቤተሰብ በረከትም ከሁላችን ጋር ይሁን።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ከሞት በኋላ ያለ ህይወትና የፕሮቴስታንት አስተሳሰብ፡፡
@And_Haymanot
ከሞት በኋላ ስላለ ህይወትና በአጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ምልጃን በተመለከተ ለፕሮቴስታንት ወገኖች ማስረዳት ብንሞክር ጥቅስ የሚል ጥያቄ ይከተላል፡፡ ከዚያ ጥቅሱን ማሳየት ሲጀመር ላለመረታት ስለጥቅሶቹ የተሳሳተ ትርጉም መስጠት ወይም
አልቀበልም ወደ ማለት ይኬዳል፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር በሰጠን ህሊና ነገሩን ማገናዘብ ከጥቅስ ያለፈ ተጨማሪ
ማስተዋል ነውና እንካችሁ፡፡ በውኑ በአጸደ ነፍስ ሆኖ ማማለድ? አለ ወይስ የለም?
የዚህን ጥያቄ መልስ ለማግኘት ቀድሞ መጠየቅ ያለበት የሞት ትርጉምና ከሞት በኋላ ስላለው ሚና ያለን አስተሳሰብና እምነት ነው፡፡ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስለቅዱሳን ያላትን አስተምህሮና እምነት ለመቃወም ብቻ በተሳሳተ መነሻ ላይ ቆሞ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ መድረስ ራስን እንጂ ሌላ ማንንም አይጎዳም፡፡
ሞት ምንድነው? ከሞት በኋላ ያለንስ ሚና?
👉 #ፕሮቴስታንት ፡- ሞት ከምድራዊ ቤተክርስቲያንና ህብረት ፍጹም መለየት ነው፡፡ ከሞት በኋላ አንድ የፕሮቴስታንት አማኝ በምድር ስላለች ቤተክርስቲያንና አማኞች በፍጹም አይመለከተውም፡፡
ምንም ጥያቄ አያነሳም፡፡ አይጸልይምም፡፡ በሞት ምክንያት በሰማይ ያሉ የፕሮቴስታንት አማኞች ከምድራውያኑ ጋር የነበራቸው የግንኙነት ድልድይ ይቋረጣል፡፡ ሞት ፍጹም ወደ ሌላ የማይታወቅ አለም መሔድና በምድር ካለው ሕይወት መለየት
ነው፡፡ በምድር ስላለው ነገር በፍጹም ማወቅ አይችሉም፡፡ ቢችሉም ምንም ሚና የላቸውም፤ በምድር ካለች ቤተክርስቲያን ጋር በፍጹም ይቆራረጣሉ፤ በምድር ያሉትም እንዲሁ የሞቱ ፕሮቴስታንቶችን ፍጹም በሆነ መለየት ይለይዋቸዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ምንም ግንኙነት የለም፡፡ እንደ አለማውያን ሻማ
ከማብራት፣ ሐውልት ከመስራት ያለፈ ሌላ ነገር የለም፤ መንፈሳዊ ግንኙነቱ ፍጹም በሆነ ሁኔታ ይቋረጣል፡፡
👉 #ኦርቶዶክስ ፡- ሞት የቦታ ለውጥ እንጂ የግንኙነት መቋጫ አይደለም፡፡ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሞት ምክንያት በአጸደ ነፍስ ያሉና በምድር ያለች ቤተክርስቲያን ግንኙነት አይቋረጥም፡፡ እለት እለት ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚያስጨንቃቸው
ክርስቲያኖች በስጋ ሲሞቱ፣ ወደ ናፍቆታቸው ወደ ክርስቶስ ሲሔዱ፤ በገነት ሲኖሩ እነርሱ ያዩትን ደስታ፣ ያገኙትን አክሊል፤ በምድር ያሉ ክርስቲያኖችም እንዲያገኙ የበለጠ ይናፍቃሉ፡፡ በምድር ሆነው የራሳቸውንም እድል ፈንታ ባላወቁበት ሁኔታ ስለሌላው ይለምኑ የነበሩ አሁን የናፈቁትን ሲያገኙ ያን ምህረትና ጽድቅ በምድር ያለነውም እንድናገኝ የበለጠ ይተጋሉ፡፡ ልዩነቱ
ቀድሞ በድካምና በትህትና ሆነው ይለምኑ ነበር፤ አሁን ግን ተሸልመዋልና በስልጣን ይለምናሉ፡፡ ቀድሞ የስጋ ድካምና ፈተና ነበረባቸው፣ አሁን ግን ከዚህ ነጻ በመሆናቸው ያለድካም ፍጹም
በሆነ ትጋት እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፤ ስለምድራዊቱም ቤተክርስቲያን ይለምናሉ፡፡
ስለሞትና ከሞት በኋላ ስላለን ሚና በምድር ያለን ኦርቶዶክሳውያንና ፕሮቱስታንቶች እንዲ ባለ ጽንፍ ተለያይተናል፡፡ ፕሮቴስታንቶች ስለሞቱ ወገኖቻቸው የሚሰጡት ትርጉምና ሚና
ኦርቶዶክሳውያን ስለሞቱና በሲኦል ካሉ ነፍሳት እንኳን ያነሰ ነው፡፡ በገነት በጽድቅ ያሉ ቅዱሳን ይቅርና በሲኦል ያሉ ነፍሳት እንኳን ቢሆኑ በዚያ ጽኑ መከራ ሆነው፣ በምድር በኃጢያት ስላለ ስለሚያውቁት ነፍስ ይገዳቸዋል፡፡ ራሳቸውን ማዳን ባይችሉ እንኳን እንደ ነዌ ያለ ልመና ማቅረብ አያቅታቸውምም፡፡ ነዌ
ስለራሱ ውኃ ለምኖ እንደማይቻል ሲረዳ ወዲያው በምድር ያሉ አምስት ወንድሞቹ ትዝ አሉት፡፡ እነርሱ ባለማወቅ ወደዚህ
መከራ እንዳይመጡ ናፈቀ፤ አብርሐምንም ለመነው፡፡ በሲኦል
ሆኖ እንዲህ ስለሌላ ሰው መጨነቅና፣ መለመን ከተቻለ በገነት ሆኖ ቢያንስ የነዌን ያህል እንኳን መጨነቅ፣ መለመን የለም ተብሎ እንዴት ይታሰባል? አንድ ፕሮቴስታንት ከሞትኩ በኋላ ገነትም ብገባ ሲኦልም ብገባ፣ በምድር ስላለችው ቤተክርስቲያን ቢያንስ እንደነዌ ወንድሞቼ ብዬ መጨነቅ፣ መለመን አልችልም ብሎ መደምደም እንዴት ያለ አስተሳሰብ ነው?
ፕሮቴስታንቶች ስለ ሞቱ ወገኖቻቸው የሚሰጡት ትርጉምና ሚና፤ በኛ በኦርቶዶክስሳውያን ዘንድ በገነት ካሉት ቅዱሳን ጋር ሳይሆን በሲኦል ካሉ ኃጥአን ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ኧረ እንዲያውም ያንሳል፡፡ እኛ በገነት ያሉ ቅዱሳን ይቅርና በሲኦል ያሉ ኃጥአን እንኳን በምድር ስላሉ ወንድሞቻቸው ሊጨነቁ፣
ሊለምኑ ይችላሉ እንላለን፡፡ ፕሮቴስታንት ግን ገነት ብንገባ እንኳን እንዲህ አናደርግም፤ በምድር ስላለች ቤተክርስቲያን አንለምንም ብለው ያምናሉ፡፡ የትኛውንም አስተሳሰብና እምነት ማራመድ ይቻላል፡፡ በአስተሳሰባችንና እምነታችን መካከል ግን የዚህን ያህል ልዩነት አለ፡፡ ከራሱ ህይወት ይልቅ ዕለት ዕለት ስለአብያተ ክርስቲያናት ሲጨነቅ የኖረው ቅዱስ ጳውሎስ አክሊል ሲሸለም፣ በገነት ሲሆን፣ ሲጸድቅ፣ ልሔድ ከክርስቶስ ጋር ልሆን እናፍቃለው እንዳለ፣ የሚናፍቀውን ካገኘ በኋላ በምድር ያለነውም ይህንን ክብር እንድናይ፣ የበለጠ ይተጋል፣ ይለምናል፣ እንደ ቀድሞ በትህትናና በድካም ሳይሆን በክብርና በስልጣን
ሆኖ ያለድካም ይተጋል እንጂ፣ ሁሉን እርግፍ አድርጎ ይተወዋል፤ አያገባውም ብሎ ማመን ምን ዓይነት የዋህነት ነው፡፡ ምንስ የሚሉት የመንፈሳዊ ህይወት ብስለት ማጣት ነው፡፡ የፕሮቴስታንት አገልጋይ የነበሩ ግን ከሞቱ በኋላ ፍጹም በሆነ ሁኔታ በምድር ካሉ ወንድሞቻቸው ይለያሉ፡፡ ምድራውያኑም ስለሞቱት ሻማ ከማብራትና ሐውልት ከማሰራት ያለፈ ምንም መንፈሳዊ ግንኙነት የላቸውም፡፡ ስለሆነም ኦርቶዶክሳውያን ስለዚህ ስናስብ የሞቱ ፕሮቴስታንቶች ግን ምን ነካቸው? እንዲህስ ሊሆኑ የሚችሉት የት ቢገቡ ነው? የሚል ጥያቄ ይፈጠርብናል፣ ክርስቶስ ራስ ሆኖ የመሰረታት ቤተክርስቲያንስ
በሞት ምክንያትስ እንዴት እንዲህ ትሆናለች?
በዲ/ን ሸዋፈራው አለነ
Join
👉 @And_Haymanot
👉 @And_Haymanot
@And_Haymanot
ከሞት በኋላ ስላለ ህይወትና በአጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ምልጃን በተመለከተ ለፕሮቴስታንት ወገኖች ማስረዳት ብንሞክር ጥቅስ የሚል ጥያቄ ይከተላል፡፡ ከዚያ ጥቅሱን ማሳየት ሲጀመር ላለመረታት ስለጥቅሶቹ የተሳሳተ ትርጉም መስጠት ወይም
አልቀበልም ወደ ማለት ይኬዳል፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር በሰጠን ህሊና ነገሩን ማገናዘብ ከጥቅስ ያለፈ ተጨማሪ
ማስተዋል ነውና እንካችሁ፡፡ በውኑ በአጸደ ነፍስ ሆኖ ማማለድ? አለ ወይስ የለም?
የዚህን ጥያቄ መልስ ለማግኘት ቀድሞ መጠየቅ ያለበት የሞት ትርጉምና ከሞት በኋላ ስላለው ሚና ያለን አስተሳሰብና እምነት ነው፡፡ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስለቅዱሳን ያላትን አስተምህሮና እምነት ለመቃወም ብቻ በተሳሳተ መነሻ ላይ ቆሞ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ መድረስ ራስን እንጂ ሌላ ማንንም አይጎዳም፡፡
ሞት ምንድነው? ከሞት በኋላ ያለንስ ሚና?
👉 #ፕሮቴስታንት ፡- ሞት ከምድራዊ ቤተክርስቲያንና ህብረት ፍጹም መለየት ነው፡፡ ከሞት በኋላ አንድ የፕሮቴስታንት አማኝ በምድር ስላለች ቤተክርስቲያንና አማኞች በፍጹም አይመለከተውም፡፡
ምንም ጥያቄ አያነሳም፡፡ አይጸልይምም፡፡ በሞት ምክንያት በሰማይ ያሉ የፕሮቴስታንት አማኞች ከምድራውያኑ ጋር የነበራቸው የግንኙነት ድልድይ ይቋረጣል፡፡ ሞት ፍጹም ወደ ሌላ የማይታወቅ አለም መሔድና በምድር ካለው ሕይወት መለየት
ነው፡፡ በምድር ስላለው ነገር በፍጹም ማወቅ አይችሉም፡፡ ቢችሉም ምንም ሚና የላቸውም፤ በምድር ካለች ቤተክርስቲያን ጋር በፍጹም ይቆራረጣሉ፤ በምድር ያሉትም እንዲሁ የሞቱ ፕሮቴስታንቶችን ፍጹም በሆነ መለየት ይለይዋቸዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ምንም ግንኙነት የለም፡፡ እንደ አለማውያን ሻማ
ከማብራት፣ ሐውልት ከመስራት ያለፈ ሌላ ነገር የለም፤ መንፈሳዊ ግንኙነቱ ፍጹም በሆነ ሁኔታ ይቋረጣል፡፡
👉 #ኦርቶዶክስ ፡- ሞት የቦታ ለውጥ እንጂ የግንኙነት መቋጫ አይደለም፡፡ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሞት ምክንያት በአጸደ ነፍስ ያሉና በምድር ያለች ቤተክርስቲያን ግንኙነት አይቋረጥም፡፡ እለት እለት ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚያስጨንቃቸው
ክርስቲያኖች በስጋ ሲሞቱ፣ ወደ ናፍቆታቸው ወደ ክርስቶስ ሲሔዱ፤ በገነት ሲኖሩ እነርሱ ያዩትን ደስታ፣ ያገኙትን አክሊል፤ በምድር ያሉ ክርስቲያኖችም እንዲያገኙ የበለጠ ይናፍቃሉ፡፡ በምድር ሆነው የራሳቸውንም እድል ፈንታ ባላወቁበት ሁኔታ ስለሌላው ይለምኑ የነበሩ አሁን የናፈቁትን ሲያገኙ ያን ምህረትና ጽድቅ በምድር ያለነውም እንድናገኝ የበለጠ ይተጋሉ፡፡ ልዩነቱ
ቀድሞ በድካምና በትህትና ሆነው ይለምኑ ነበር፤ አሁን ግን ተሸልመዋልና በስልጣን ይለምናሉ፡፡ ቀድሞ የስጋ ድካምና ፈተና ነበረባቸው፣ አሁን ግን ከዚህ ነጻ በመሆናቸው ያለድካም ፍጹም
በሆነ ትጋት እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፤ ስለምድራዊቱም ቤተክርስቲያን ይለምናሉ፡፡
ስለሞትና ከሞት በኋላ ስላለን ሚና በምድር ያለን ኦርቶዶክሳውያንና ፕሮቱስታንቶች እንዲ ባለ ጽንፍ ተለያይተናል፡፡ ፕሮቴስታንቶች ስለሞቱ ወገኖቻቸው የሚሰጡት ትርጉምና ሚና
ኦርቶዶክሳውያን ስለሞቱና በሲኦል ካሉ ነፍሳት እንኳን ያነሰ ነው፡፡ በገነት በጽድቅ ያሉ ቅዱሳን ይቅርና በሲኦል ያሉ ነፍሳት እንኳን ቢሆኑ በዚያ ጽኑ መከራ ሆነው፣ በምድር በኃጢያት ስላለ ስለሚያውቁት ነፍስ ይገዳቸዋል፡፡ ራሳቸውን ማዳን ባይችሉ እንኳን እንደ ነዌ ያለ ልመና ማቅረብ አያቅታቸውምም፡፡ ነዌ
ስለራሱ ውኃ ለምኖ እንደማይቻል ሲረዳ ወዲያው በምድር ያሉ አምስት ወንድሞቹ ትዝ አሉት፡፡ እነርሱ ባለማወቅ ወደዚህ
መከራ እንዳይመጡ ናፈቀ፤ አብርሐምንም ለመነው፡፡ በሲኦል
ሆኖ እንዲህ ስለሌላ ሰው መጨነቅና፣ መለመን ከተቻለ በገነት ሆኖ ቢያንስ የነዌን ያህል እንኳን መጨነቅ፣ መለመን የለም ተብሎ እንዴት ይታሰባል? አንድ ፕሮቴስታንት ከሞትኩ በኋላ ገነትም ብገባ ሲኦልም ብገባ፣ በምድር ስላለችው ቤተክርስቲያን ቢያንስ እንደነዌ ወንድሞቼ ብዬ መጨነቅ፣ መለመን አልችልም ብሎ መደምደም እንዴት ያለ አስተሳሰብ ነው?
ፕሮቴስታንቶች ስለ ሞቱ ወገኖቻቸው የሚሰጡት ትርጉምና ሚና፤ በኛ በኦርቶዶክስሳውያን ዘንድ በገነት ካሉት ቅዱሳን ጋር ሳይሆን በሲኦል ካሉ ኃጥአን ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ኧረ እንዲያውም ያንሳል፡፡ እኛ በገነት ያሉ ቅዱሳን ይቅርና በሲኦል ያሉ ኃጥአን እንኳን በምድር ስላሉ ወንድሞቻቸው ሊጨነቁ፣
ሊለምኑ ይችላሉ እንላለን፡፡ ፕሮቴስታንት ግን ገነት ብንገባ እንኳን እንዲህ አናደርግም፤ በምድር ስላለች ቤተክርስቲያን አንለምንም ብለው ያምናሉ፡፡ የትኛውንም አስተሳሰብና እምነት ማራመድ ይቻላል፡፡ በአስተሳሰባችንና እምነታችን መካከል ግን የዚህን ያህል ልዩነት አለ፡፡ ከራሱ ህይወት ይልቅ ዕለት ዕለት ስለአብያተ ክርስቲያናት ሲጨነቅ የኖረው ቅዱስ ጳውሎስ አክሊል ሲሸለም፣ በገነት ሲሆን፣ ሲጸድቅ፣ ልሔድ ከክርስቶስ ጋር ልሆን እናፍቃለው እንዳለ፣ የሚናፍቀውን ካገኘ በኋላ በምድር ያለነውም ይህንን ክብር እንድናይ፣ የበለጠ ይተጋል፣ ይለምናል፣ እንደ ቀድሞ በትህትናና በድካም ሳይሆን በክብርና በስልጣን
ሆኖ ያለድካም ይተጋል እንጂ፣ ሁሉን እርግፍ አድርጎ ይተወዋል፤ አያገባውም ብሎ ማመን ምን ዓይነት የዋህነት ነው፡፡ ምንስ የሚሉት የመንፈሳዊ ህይወት ብስለት ማጣት ነው፡፡ የፕሮቴስታንት አገልጋይ የነበሩ ግን ከሞቱ በኋላ ፍጹም በሆነ ሁኔታ በምድር ካሉ ወንድሞቻቸው ይለያሉ፡፡ ምድራውያኑም ስለሞቱት ሻማ ከማብራትና ሐውልት ከማሰራት ያለፈ ምንም መንፈሳዊ ግንኙነት የላቸውም፡፡ ስለሆነም ኦርቶዶክሳውያን ስለዚህ ስናስብ የሞቱ ፕሮቴስታንቶች ግን ምን ነካቸው? እንዲህስ ሊሆኑ የሚችሉት የት ቢገቡ ነው? የሚል ጥያቄ ይፈጠርብናል፣ ክርስቶስ ራስ ሆኖ የመሰረታት ቤተክርስቲያንስ
በሞት ምክንያትስ እንዴት እንዲህ ትሆናለች?
በዲ/ን ሸዋፈራው አለነ
Join
👉 @And_Haymanot
👉 @And_Haymanot
እባካችሁ አድርሱልኝ:-
ትዝብት 1:- መንፈሳዊ ግሩፖች ላይ አላስፈላጊ ነገሮች ሢለጠፉ(post ሲደረጉ) እናሥተውላለን ይህ ግሩፕ የከፈቱ አድሚኖች ሀላፊነት ቢሆንም አንዳንዶቹ ብዙም የማይገቡና የማይቆጣጠሩ አሉ እናም ተጨማሪ አድሚኖችን ቢያሠሩ መልካም ይመሥለኛል፡፡
2 ሌላው ብዙዎቻችን ባለማሥተዋል ጥሩ መልዕክቶችን ወደ ግሩፖች ሼር በምናደርግበት ጊዜ ምንጫቸውን ብንለይ ... አንዳንድ የመናፍቃንን የማሥታወቅያ ሊንክ የያዙ ጥሩ የሚመሥሉ ፅሑፎችን ሼር ባናደርግ፡፡ ምክንያቱም የነሱን ቻናልና ግሩፕ በሌላ በኩል እያሥተዋወቅንም ጭምር ነውና በማሥተዋል ይሁን ለማለት እወዳለው
3 አድሚኖች የከፈቱበትን አላማ ባይዘነጉ መልካም ነው፡፡ ብዙ ግሩፖች ውይይት አይደረግባቸውም... ምንም ሥራ ሳይሠሩ አባላትን ብቻ ይዘው የተቀመጡ አሉና ይሥሩበት ለማለት እወዳለው፡፡
እግዚአብሔር ያክብርልኝ በርቱ!!
ፀዳለ ማርያም
~~~~~~~~~~~~
ጥሩ ዕይታ ሥለሆነ አቅርበነዋል በዚህ አጋጣሚ ጥሩ የሚሠሩትን ለማመሥገን እንወዳለን ሌሎቻችሁም ሐሳባችሁን አድርሱን
👉 @AHati_Haymanot
እንዲሁም ባለመመቻቸት ግሩፓችሁን መቆጣጠር ያልቻላችሁ አድሚኖችም ተጨማሪ አድሚን ማሠራት ከፈለጋችሁ አናግሩን ሌሎች አድሚኖችን እናገናኛችኋለን፡፡
ወንጌል አይከደን ለአንዲት ተዋህዶ በአንድነት እንሰራለን
@And_Haymanot
ወደ ግሩፖች ሼር በማድረግ ለውጥ እንፍጠር፡፡
@And_Haymanot
ትዝብት 1:- መንፈሳዊ ግሩፖች ላይ አላስፈላጊ ነገሮች ሢለጠፉ(post ሲደረጉ) እናሥተውላለን ይህ ግሩፕ የከፈቱ አድሚኖች ሀላፊነት ቢሆንም አንዳንዶቹ ብዙም የማይገቡና የማይቆጣጠሩ አሉ እናም ተጨማሪ አድሚኖችን ቢያሠሩ መልካም ይመሥለኛል፡፡
2 ሌላው ብዙዎቻችን ባለማሥተዋል ጥሩ መልዕክቶችን ወደ ግሩፖች ሼር በምናደርግበት ጊዜ ምንጫቸውን ብንለይ ... አንዳንድ የመናፍቃንን የማሥታወቅያ ሊንክ የያዙ ጥሩ የሚመሥሉ ፅሑፎችን ሼር ባናደርግ፡፡ ምክንያቱም የነሱን ቻናልና ግሩፕ በሌላ በኩል እያሥተዋወቅንም ጭምር ነውና በማሥተዋል ይሁን ለማለት እወዳለው
3 አድሚኖች የከፈቱበትን አላማ ባይዘነጉ መልካም ነው፡፡ ብዙ ግሩፖች ውይይት አይደረግባቸውም... ምንም ሥራ ሳይሠሩ አባላትን ብቻ ይዘው የተቀመጡ አሉና ይሥሩበት ለማለት እወዳለው፡፡
እግዚአብሔር ያክብርልኝ በርቱ!!
ፀዳለ ማርያም
~~~~~~~~~~~~
ጥሩ ዕይታ ሥለሆነ አቅርበነዋል በዚህ አጋጣሚ ጥሩ የሚሠሩትን ለማመሥገን እንወዳለን ሌሎቻችሁም ሐሳባችሁን አድርሱን
👉 @AHati_Haymanot
እንዲሁም ባለመመቻቸት ግሩፓችሁን መቆጣጠር ያልቻላችሁ አድሚኖችም ተጨማሪ አድሚን ማሠራት ከፈለጋችሁ አናግሩን ሌሎች አድሚኖችን እናገናኛችኋለን፡፡
ወንጌል አይከደን ለአንዲት ተዋህዶ በአንድነት እንሰራለን
@And_Haymanot
ወደ ግሩፖች ሼር በማድረግ ለውጥ እንፍጠር፡፡
@And_Haymanot
"የቅዱስ ጳውሎስ ተፈጥሮ ከእኛ ተፈጥሮ የተለየ አልነበረም፡፡
@And_Haymanot
ነፍሱ ከእኛ ነፍስ የተለየ ተፈጥሮ አልነበራትም፡፡ በዚህ እኛ በምንኖርበት ምድር እንጂ በሌላ ዓለም የሚኖር አልነበረም፡፡ ይኖር የነበረው እኛ በምንኖርበት ተመሳሳይ ዓለም፣ በተመሳሳይ አገር፣ በተመሳሳይ ሕግና ባሕል ቢኾንም ቅሉ፥ እርሱ ግን ከዚህ
በፊት ከነበሩትም፣ አሁን ካሉትም ሰዎች ኹሉ የከበረ የገነነ ነው፡፡ “ቀላሉ ክፉ ምግባርን መሥራት ነው እንጂ ምግባር
ትሩፋት መሥራትስ እጅግ ከባድ ነው” ብለው የሚቃወሙት አሁን ወዴት አሉ? ይህ ቅዱስ ሰው የእነዚህን ሰዎች ስሕተት፡- “የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የኾነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘለዓለም ብዛት ከኹሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናል” በማለት በቃሉ ያፈራርስባቸዋል (2ኛ
ቆሮ.4፡17)፡፡ ተመልከቱ! ቅዱስ ጳውሎስ የተቀበላቸው መከራዎች ቀላል ከኾኑ፥ እርሱ ከተቀበላቸው አንጻር ሲታዩ ተድላና ደስታ የኾኑት የእኛ’ማ እንዴት?
እጅግ የሚያስደንቀው ግን፥ ከመጠን በላይ ቀናኢ ከመኾኑ የተነሣ በጎ ነገርን ሲሠራ ይደርስበት የነበረውን መከራ እንደ ቀላል ማየቱ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ቅዱስ ጳውሎስ (ለበጎ
ምግባሩ) ዋጋ የማያገኝበት ቢሆን እንኳን ምግባራትን ለመፈጸም ወደ ኋላ የማይል መሆኑ ነው፡፡ ከቅንዓቱ በስተጀርባ የሚያስበው ምንም አሳብ የለውም ነበር፡፡ እኛ “የክብር አክሊል ይሰጣችኋል” ተብለን እንኳን ቀናዕያን
ለመኾን ዳተኞች ነን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ግን የክብር አክሊል ባይቀበልበትም እንኳን ምግባራትን ለመፈጸም ይፋጠን ነበር፡፡ ምግባር ትሩፋት በሚሠራበት መንገድ ላይ የትኛውም ዓይነት መከራ ቢያገኘውም እንኳን በትሕትና ይቀበለው ዘንድ ይታገሥ ነበር፡፡ በሰውነቱ ድካም፣ ወይም በሌሎች ሰዎች ተጽዕኖ፣ ወይም
በልማድ ጫና፣ ወይም ይህን በመሰለ በሌላ ነገር ምንም ምን አያመካኝም ነበር፡፡ “እነዚህ ችግሮች ስላሉበኝ” ብሎ
አላመካኘም እንጂ ኃላፊነቶቹ ግን ከወታደር አለቆች ወይም ከምድራውያን ነገሥታት እጅግ የሚልቁ ነበሩ፡፡
እነዚህ ኹሉ ተደራራቢ ኃላፊነቶች፣ በእነርሱ መጠንም መከራዎች የነበሩበት ቢኾንም እንኳን ዕለት ዕለት በምግባር
ያድግ ነበር፡፡ ለቅዱስ ጳውሎስ የመከራ ብዛት ማለት የትጋት መጨመሪያ መሣሪያ ብቻ ነበሩና፡፡ እርሱ ራሱም ከዚህ በላይ የኾነውን፡- “ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ፤ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ” በማለት ነግሮናል (ፊልጵ.3፡13)፡፡ እስከ ሞት በሚያደርስ መከራ ውስጥ ኾኖ
[ነገር ግን ደስተኛ ነው]፥ ሌሎች ሰዎችንም የደስታው ተሳታፊዎች ይኾኑ ዘንድ እንዲህ በማለት ይጠራቸው ነበር፡- “እናንተም ደግሞ እንዲሁ ደስ ይበላችሁ፥ ከእኔም ጋር አብራችሁ ደስ ይበላችሁ” (ፊልጵ.2፡18)፡፡ እርሱም በእያንዳንዷ በምትደርስበት መከራ፣ ጉዳትና እንግልት ሐሴት ያደርግ ነበር፡፡
ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው መልእክቱ ላይ፡- “ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም
በጭንቀትም ደስ ይለኛል” ብሏል (2ኛ ቆሮ.12፡10)፡፡ [መከራዎች] የበጎ ነገር ኹሉ ምንጭ መኾናቸውንና እርሱም
በጠላቶቹ አይበገሬ መንፈሳዊ አርበኛ እንደ ኾነ በማሳየት እነዚህ የፍትሕ መሣሪያዎች መኾናቸውን ተናግሯል፡፡
ቢደበድቡትም፣ ቢያንገላቱትም፣ እጅግም ቢሰድቡት በድል ሰልፍ ላይ እንዳለ ኾኖ፥ ገና በዚህ ምድር እያለ ብዙ የድል አክሊላትን ተቀዳጅቷል፤ ደስ ተሰኝቷል፤ “ነገር ግን በክርስቶስ ኹልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ኹሉ የዕውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይኹን” በማለትም እግዚአብሔርን አመስግኗል (2ኛ ቆሮ.2፡14)፡፡ ቃለ እግዚአብሔርን ስለማስተማር ንቀትን ውርደትንም በመቀበሉ ደስ ይሰኝ ነበር፡፡ እኛ በሕይወት ደስ እንደምንሰኝ እርሱ በሞት
(በመከራ)፣ እኛ በማግኘት ደስ እንደሚለን እርሱ በማጣት፣ እኛ
ከልክ በላይ በኾነ በዕረፍት ሐሴት እንደምናደርግ እርሱ በድካም
በጥረትም፣ እኛ በደስታ እንደምንፍነከነክ እርሱ በኀዘን፣ እኛ በጠላቶቻችን ስንነሣሣ እንደምንረካ እርሱ ግን ለጠላቶቹ በመጸለይ ተድላ ደስታ የሚያደርግ ነበር፡፡
© ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ውዳሴ ጳውሎስ፣ ድርሳን ፪
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ነፍሱ ከእኛ ነፍስ የተለየ ተፈጥሮ አልነበራትም፡፡ በዚህ እኛ በምንኖርበት ምድር እንጂ በሌላ ዓለም የሚኖር አልነበረም፡፡ ይኖር የነበረው እኛ በምንኖርበት ተመሳሳይ ዓለም፣ በተመሳሳይ አገር፣ በተመሳሳይ ሕግና ባሕል ቢኾንም ቅሉ፥ እርሱ ግን ከዚህ
በፊት ከነበሩትም፣ አሁን ካሉትም ሰዎች ኹሉ የከበረ የገነነ ነው፡፡ “ቀላሉ ክፉ ምግባርን መሥራት ነው እንጂ ምግባር
ትሩፋት መሥራትስ እጅግ ከባድ ነው” ብለው የሚቃወሙት አሁን ወዴት አሉ? ይህ ቅዱስ ሰው የእነዚህን ሰዎች ስሕተት፡- “የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የኾነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘለዓለም ብዛት ከኹሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናል” በማለት በቃሉ ያፈራርስባቸዋል (2ኛ
ቆሮ.4፡17)፡፡ ተመልከቱ! ቅዱስ ጳውሎስ የተቀበላቸው መከራዎች ቀላል ከኾኑ፥ እርሱ ከተቀበላቸው አንጻር ሲታዩ ተድላና ደስታ የኾኑት የእኛ’ማ እንዴት?
እጅግ የሚያስደንቀው ግን፥ ከመጠን በላይ ቀናኢ ከመኾኑ የተነሣ በጎ ነገርን ሲሠራ ይደርስበት የነበረውን መከራ እንደ ቀላል ማየቱ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ቅዱስ ጳውሎስ (ለበጎ
ምግባሩ) ዋጋ የማያገኝበት ቢሆን እንኳን ምግባራትን ለመፈጸም ወደ ኋላ የማይል መሆኑ ነው፡፡ ከቅንዓቱ በስተጀርባ የሚያስበው ምንም አሳብ የለውም ነበር፡፡ እኛ “የክብር አክሊል ይሰጣችኋል” ተብለን እንኳን ቀናዕያን
ለመኾን ዳተኞች ነን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ግን የክብር አክሊል ባይቀበልበትም እንኳን ምግባራትን ለመፈጸም ይፋጠን ነበር፡፡ ምግባር ትሩፋት በሚሠራበት መንገድ ላይ የትኛውም ዓይነት መከራ ቢያገኘውም እንኳን በትሕትና ይቀበለው ዘንድ ይታገሥ ነበር፡፡ በሰውነቱ ድካም፣ ወይም በሌሎች ሰዎች ተጽዕኖ፣ ወይም
በልማድ ጫና፣ ወይም ይህን በመሰለ በሌላ ነገር ምንም ምን አያመካኝም ነበር፡፡ “እነዚህ ችግሮች ስላሉበኝ” ብሎ
አላመካኘም እንጂ ኃላፊነቶቹ ግን ከወታደር አለቆች ወይም ከምድራውያን ነገሥታት እጅግ የሚልቁ ነበሩ፡፡
እነዚህ ኹሉ ተደራራቢ ኃላፊነቶች፣ በእነርሱ መጠንም መከራዎች የነበሩበት ቢኾንም እንኳን ዕለት ዕለት በምግባር
ያድግ ነበር፡፡ ለቅዱስ ጳውሎስ የመከራ ብዛት ማለት የትጋት መጨመሪያ መሣሪያ ብቻ ነበሩና፡፡ እርሱ ራሱም ከዚህ በላይ የኾነውን፡- “ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ፤ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ” በማለት ነግሮናል (ፊልጵ.3፡13)፡፡ እስከ ሞት በሚያደርስ መከራ ውስጥ ኾኖ
[ነገር ግን ደስተኛ ነው]፥ ሌሎች ሰዎችንም የደስታው ተሳታፊዎች ይኾኑ ዘንድ እንዲህ በማለት ይጠራቸው ነበር፡- “እናንተም ደግሞ እንዲሁ ደስ ይበላችሁ፥ ከእኔም ጋር አብራችሁ ደስ ይበላችሁ” (ፊልጵ.2፡18)፡፡ እርሱም በእያንዳንዷ በምትደርስበት መከራ፣ ጉዳትና እንግልት ሐሴት ያደርግ ነበር፡፡
ለቆሮንቶስ ሰዎች በላከው መልእክቱ ላይ፡- “ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም
በጭንቀትም ደስ ይለኛል” ብሏል (2ኛ ቆሮ.12፡10)፡፡ [መከራዎች] የበጎ ነገር ኹሉ ምንጭ መኾናቸውንና እርሱም
በጠላቶቹ አይበገሬ መንፈሳዊ አርበኛ እንደ ኾነ በማሳየት እነዚህ የፍትሕ መሣሪያዎች መኾናቸውን ተናግሯል፡፡
ቢደበድቡትም፣ ቢያንገላቱትም፣ እጅግም ቢሰድቡት በድል ሰልፍ ላይ እንዳለ ኾኖ፥ ገና በዚህ ምድር እያለ ብዙ የድል አክሊላትን ተቀዳጅቷል፤ ደስ ተሰኝቷል፤ “ነገር ግን በክርስቶስ ኹልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ኹሉ የዕውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይኹን” በማለትም እግዚአብሔርን አመስግኗል (2ኛ ቆሮ.2፡14)፡፡ ቃለ እግዚአብሔርን ስለማስተማር ንቀትን ውርደትንም በመቀበሉ ደስ ይሰኝ ነበር፡፡ እኛ በሕይወት ደስ እንደምንሰኝ እርሱ በሞት
(በመከራ)፣ እኛ በማግኘት ደስ እንደሚለን እርሱ በማጣት፣ እኛ
ከልክ በላይ በኾነ በዕረፍት ሐሴት እንደምናደርግ እርሱ በድካም
በጥረትም፣ እኛ በደስታ እንደምንፍነከነክ እርሱ በኀዘን፣ እኛ በጠላቶቻችን ስንነሣሣ እንደምንረካ እርሱ ግን ለጠላቶቹ በመጸለይ ተድላ ደስታ የሚያደርግ ነበር፡፡
© ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ውዳሴ ጳውሎስ፣ ድርሳን ፪
@And_Haymanot
ጴጥሮስ ተሰቀለ ጳውሎስ ተሰየፈ
ተዋሕዶ እያለ ኧረ ስንቱ አለፈ
ሌሎችም በእሳት በስቃይ አልፈዋል
ዘመን የማይሽረው ታሪክን ጽፈዋል
🙏እንኳን አደረሳችሁ!🙏
@And_Haymanot
ተዋሕዶ እያለ ኧረ ስንቱ አለፈ
ሌሎችም በእሳት በስቃይ አልፈዋል
ዘመን የማይሽረው ታሪክን ጽፈዋል
🙏እንኳን አደረሳችሁ!🙏
@And_Haymanot
ሥላሴን አመስግኑት
ሥላሴን አመስግኑ (2)
የምድር ፍጥረታት ዘምሩ እልል በሉ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
ምስጋና ይገባል ከምንም በፊት
ዓለማትን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ
ምስጋና ይገባል ጠዋትና ማታ
ኪሩቤል ሱራፌል የሚያመሰግኑት
መላእክት በሰማይ የሚዘምሩለት
እኛም የአዳም ልጆች እንዘምራለን
በሰማይም በምድር እንጠራሃለን
ብራብ በሥላሴ እጠግባለሁኝ
ብጠማም በአምላኬ እረካለሁኝ
ሥላሴ አምባዬ ክብሬም ናቸውና
ሁሌ ይመሩኛል በሕይወት ጎዳና
ሥላሴን አመስግኑ (2)
የምድር ፍጥረታት ዘምሩ እልል በሉ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
ምስጋና ይገባል ከምንም በፊት
ዓለማትን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ
ምስጋና ይገባል ጠዋትና ማታ
ኪሩቤል ሱራፌል የሚያመሰግኑት
መላእክት በሰማይ የሚዘምሩለት
እኛም የአዳም ልጆች እንዘምራለን
በሰማይም በምድር እንጠራሃለን
ብራብ በሥላሴ እጠግባለሁኝ
ብጠማም በአምላኬ እረካለሁኝ
ሥላሴ አምባዬ ክብሬም ናቸውና
ሁሌ ይመሩኛል በሕይወት ጎዳና
👉 https://tttttt.me/Konobyos/29
ወቅታዊ ትምህርት በ ቴሌግራም አጠቃቀማችን እንዲሁም የተለያዩ የእምነት አመለካከቶችን ወንድማችን ገልፆታል አድምጡት
@And_Haymanot
ወቅታዊ ትምህርት በ ቴሌግራም አጠቃቀማችን እንዲሁም የተለያዩ የእምነት አመለካከቶችን ወንድማችን ገልፆታል አድምጡት
@And_Haymanot
Telegram
ኮኖብዮስ
“ፀሎትንና ምልጃን አቀረበ” ዕብ.5:7 ሲል ምን ማለቱ ነው?
እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፡ ይህ ምን ማለት ነው?
.
ይህ ጥቅስ በማያሻማ ሁኔታ የተገለፀው ነገረ ስጋዌ(እስከ መስቀል ድረስ)ነው፡፡ ጌታችን ሊቀ ካህናት ተብሎ ነበርና በስጋው ወራት እንደ ካህናተ ኦሪት የበግና የፍየል ደም ያቀረበ አይደለም፡፡ ይልቁንም ፀሎትን እንደላም ልመናንም እንደበግ አድርጎ አቀረበ፡፡ አንድ ጊዜም ስለሆነ ያቀረበው ግዳጅ የሚፈፀም መሆኑን ሲያጠይቅ “ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ” አቀረበ አለ፡፡ “ከሞት ሊያድነው ወደሚችል” ሲልም ሰው ሁሉ በአንድ አዳም እንደሞተና በጌታም በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በኩል እንደዳነ ስለምእመናን በጌታችን መናገሩ ነው፡፡
“እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት” የሚለው “ወልድ” “በኩር” ሆኖ ሳለ አምላክነት ገንዘቡ ሆኖ ሳለ ፍፁም ሰው በመሆኑ ስለአዳም ያቀረበው ቁርጥ ልመናው ተሰማለት አምላክ ነኝ ልፅልይ አይገባኝም ሳይል ሰው በመሆኑ ታዝዟልና፡፡ ስለመታዘዙም እግዚአብሄርን ስለመፍራቱ ቢል አንድ ነው፡ በአዳም ተገብቶ ነው እንጂ ጌታችን ከመከራ መስቀል በኋላ የሚያማልድ ሆኖ አይደለም፡፡.... ይቆየን
@And_Haymanot
@And_Haymanot
እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፡ ይህ ምን ማለት ነው?
.
ይህ ጥቅስ በማያሻማ ሁኔታ የተገለፀው ነገረ ስጋዌ(እስከ መስቀል ድረስ)ነው፡፡ ጌታችን ሊቀ ካህናት ተብሎ ነበርና በስጋው ወራት እንደ ካህናተ ኦሪት የበግና የፍየል ደም ያቀረበ አይደለም፡፡ ይልቁንም ፀሎትን እንደላም ልመናንም እንደበግ አድርጎ አቀረበ፡፡ አንድ ጊዜም ስለሆነ ያቀረበው ግዳጅ የሚፈፀም መሆኑን ሲያጠይቅ “ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ” አቀረበ አለ፡፡ “ከሞት ሊያድነው ወደሚችል” ሲልም ሰው ሁሉ በአንድ አዳም እንደሞተና በጌታም በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በኩል እንደዳነ ስለምእመናን በጌታችን መናገሩ ነው፡፡
“እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት” የሚለው “ወልድ” “በኩር” ሆኖ ሳለ አምላክነት ገንዘቡ ሆኖ ሳለ ፍፁም ሰው በመሆኑ ስለአዳም ያቀረበው ቁርጥ ልመናው ተሰማለት አምላክ ነኝ ልፅልይ አይገባኝም ሳይል ሰው በመሆኑ ታዝዟልና፡፡ ስለመታዘዙም እግዚአብሄርን ስለመፍራቱ ቢል አንድ ነው፡ በአዳም ተገብቶ ነው እንጂ ጌታችን ከመከራ መስቀል በኋላ የሚያማልድ ሆኖ አይደለም፡፡.... ይቆየን
@And_Haymanot
@And_Haymanot