፩ ሃይማኖት
8.92K subscribers
246 photos
29 videos
21 files
96 links
ኦርቶዶክሳዊ ምላሾች
የሚቀርቡበት፡፡
👉"፩ ኃይማኖት"👈
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የገሀነም ደጆች አያናውጧትም
✞ እ...ና...ታ...ች...ን
#አ__ት__ታ__ደ__ስ__ም፡፡
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
ለአስተያየት
@And_Haymanot_bot

፩ ሃይማኖት ኤፌ 4፥5
Download Telegram
​​ለማርያም

@And_Haymanot

ለማርያም/2/ 
እንዘምራለን ለዘለዓለም/2/ 
የተዘጋች ደጅ ለዘለዓለም 
ሕዝቅኤል ብሏል  ለዘለዓለም
ንጽሕት ናት በእውነት ለዘለዓለም
በፍጹም ድንግል  ለዘለዓለም
አብነት አድርገን  ለዘለዓለም
እኛም እርሷን ለዘላለም 
በፍጹም ፍቅር አንዘምራለን /2/ 
የዋህት ርግብ ለዘለዓለም 
ሰላም አብሳሪ ለዘለዓለም 
ጨለማ ሕይወቴ ለዘለዓለም 
በርሃንን አብሪ ለዘለዓለም 
እማጸንሻለሁ ለዘለዓለም 
ድንግል ለነፍሴ ለዘለዓለም 
አደራ ቅድስት አንቺ ነሽ ዋሴ /2/ 
እጅግ የበዛ ነው ለዘለዓለም 
ያለኝ ፍቀር ለዘለዓለም 
አይወሰንም ለዘለዓለም 
አይነገርም ለዘለዓለም 
በእርሷ ደስ ይለኛል ለዘለዓለም 
ሐሴት አደርጋለሁ ለዘለዓለም 
ሰሟን እየጠራሁ እዘምራለሁ/2/ 
ነይ ነይ ስላት ለዘለዓለም 
ቀንና ሌሊት ለዘለዓለም 
አትለየኝም ለዘለዓለም 
ለእኔስ ቅርቤናት ለዘለዓለም
እጹብ እጹብ ብለው ለዘለዓለም 
እመሰገኗት ለዘለዓለም 
ክብሯን ሊገልጹት ቢያጥራቸው ቃላት /2/
ጌታ ሆይ ከአንተ ጋር ያልነበርኩበት ዘመን ብዙ ነው አንተ ግን ከእኔ ጋር ያለነበርክበት ዘመን የለም ›› ቅዱስ አውግስጢኖስ
@And_Haymanot
መልካም ዕለተ ሰንበት
👉 ታቦትን ሌሎች ሃገራት እንዴት ይጠቀሙታል ?

@And_Haymanot

የተሀድሶ መናፍቃን ታቦት በሀገራችን ብቻ ያለና ሌሎች ሀገራት በተለይም አምስቱ አብያተ ቤተክርስቲያናትም ጭምር እንደሌለ አድርገው ሲቃወሙ እንመለከታለን
✞✞ በኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት(oriental crurch) ታቦት የተለመደ ህግ ነው፡፡ ሥጋና ደሙንም የሚፈትቱት በታቦቱ ላይ ነው፡፡ ክርስቲያኖች አንድ ሊያውቁት የሚገባው ትልቁ ነገር በብሉይ ኪዳን የነበረው የታቦት አገልግሎት የበጎችና የጥጆች ደም በቅድስተ ቅዱሳን ፊት ለፊት የመሠዋት ስርዓት #ነበር፡፡ ይህም በእውነተኛ አምላካችንና መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደም ተወግዶ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ ይለናል ዕብ 9:12 የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እኛን ከሃጢአት ሁሉ በማጠብ የቀደመውን መስዋዕት አስወግዶ እርሱ መስዋዕት ሆኖ ከብሯል፡፡፡፡ በታቦቱም ላይ የማዳኑን ምሥጢር በመግለፅ ሰዎች ሁሉ ሥጋውን በልተው ደሙን ጠጥተው እንዲድኑ ይናገራል፡፡ ዮሐ 6:54
ይህን እውነት በመያዝ ታቦት በብሉይ ኪዳን የነበረ አገልግሎትና በአዲስ ኪዳን ያለው አገልግሎት ልዩነቱን በትክክል መረዳት ያሥፈልጋል፡፡
ለምሳሌ ግብጻውያን ታቦቱን #ሉሕ ይሉታል ፅላት ሠሌዳ ማለት ነው ያለሱ ሥጋና ደሙን አይፈትቱም፡፡ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ተብለው የሚጠሩ የግሪክ የሩሲያ፣የሮማኒያ ሌሎችም ወደ ክርስትና የተመለሱት ከአረማዊነት ስለሆነ የታቦቱን ምሥጢር አያውቁትም በታቦቱ ፈንታ ከመንበር የማይነሳ እንደ ታቦት የሚከብር የጌታ የስቅለቱ ወይም የግንዘቱ ሥዕል ያለበት የነጭ ሐር መጎናፀፊያ አላቸው፡፡ ያለሡም ሥጋና ደሙን አይፈትቱም፡፡ ይህንንም በጽርዕ "እንደምኒሲዩን" ይሉታል፡፡ "ህንየተ ታቦት" ማለት ነው፡፡ የሮማ ካቶሊኮች 'ሜንሳ' Mensa ይሉታል፡፡ ጠረጴዛ ማለት ነው፡፡ ከአምስቱ አብያተ ክርስቲያናት በቀር አዲስ ቤ/ክርስቲያን በሚሠራበት ጊዜ የአጽመ ቅዱሳን ሽራፊ እንዲቀመጥ ያዛል..... በታቦት ዙርያ ለማንበብ
👉 https://tttttt.me/And_Haymanot/361

ኦርቶዶክስ መልስ አላት
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የማርያም ልጅ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የጌቶች ሁሉ ጌታ ነው
@And_Haymanot
ከዲላ፡-
የዲላ ደብረገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ን ሊቃነ ጳጳሳት ሊቃውንተ ቤ/ን ሰባኪያን ወንጌል ዘማሪያንና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት
ግንቦት 12/2010 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
የመልአኩ በረከት አይለየን
​​የፓስተሩ ጉድ
ይሄ ሰውየ አባ ጴጥሮስ ይባል የነበረ አሁን ፓስተር ሁኖ ቸርች ያቋቋመ ቦሌ አራብሳ ጎንዶሚንየም የሚኖር ዛሬ
ደግሞ በተክሊል አግብቶ ከች አለ ከምንኩስና ወደ ምንፍቅና ከምንፍቅና ወደተክሊል ቆቡን ጥሎ ክዶ በተክሊል ተዳረ ደግሞ ቦሌ አራብሳ አካባቢ የምትኖሩ ክርስቲያኖች ከዚህ ከሀዲ #ተጠበቁ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ሰላም ተወዳጆች በውሥጥ በጠየቃችሁን መሠረት ዛሬ ተከታታይ የውይይት መድረክን በድጋሜ ማቅረባችንን እንቀጥላለን ሙሉ ወይይቱን በ @Tewahdo_Haymanote ቻናል የምናቀርበው ሲሆን የሚለቀቁ ክፍሎችን በዙሁ ቻናል በ @And_Haymanot ሊንኩን እናቀርብላችኃለን፡፡
እነሆ ለዛሬ ክፍል ፩
@And_Haymanot
የኦርቶዶክሳዊ እና የፕሮቴስታንታዊ
የመዳን ትምህርት ልዩነት ላይ
ከፕሮቴስታንት ፓስተር ጋር የተደረገ
ውይይት…ሰው ሲያምን ‹‹ይድናል››
ወይስ ‹‹ድኗል››ይባላል? ክፍል 01/ስለ ነገረ እምነት/ July 16, 2014 at 3:57am የዚህ ጽሁፍ ዓላማ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖች በየመንገዱና በየቤቱ በየመስሪያ ቤቱ እና በየትምህረት ቤቱ በተደጋጋሚ ለሚነሱት የፕሮቴስታንት ጥያቄዎች ቀድመው በማወቅ መልስ ለመስጠት እንዲችሉ ማድረግ ነው፡፡ የጽሁፉ መነሻ የሶሪያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ የማስተማር መንገድ ሲሆን በውርስ ትርጉም አቀራረብ ለእኛ እንዲስማማ አድርጌ ለማቅረብ ሞክሪያለው
@Tewahdo_Haymanote
ሃና፡-ፓስተር እንዴት አለህ... ና ተቀመጥ መቼም ሰላም ነህ
ብዬ አስባለው
ፓስተር፡-እኔ በክርስቶስ ቡራኬ በጣሙን
ሰላም ነኝ ጌታ ይመስገን
ሃና፡-ዛሬ ምን እግር ጣለህ በሰላም ነው
ፓስተር፡- ሁሉም በእግዚአብሔር ጸጋ
ጥሩ እሄደ ነው፡፡ ነገር ግን እኔ ዛሬ የመጣሁት ጌታን እንደግል አዳኝ በመቀበል ድነሸ በስሙ በመጠመቅ
የመንፈስ ቅዱስን ቅባት እንድተቀቢ ነው
ሃና፡-እኔ ጌታዬን አምኜ በስሙ
ከተጠምኩ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ
ከተቀበልኩ በጣም ቆይቻለው ፓስተር፡-ጌታ ይመስገን….. ያ ግን በሕጻንነትሽ የተጠመቅሽው ነው፡፡እሱ በቂ አይደለም፡፡የእግዚአብሔር ልጅ
ለመሆን ደግሞ መጀመሪያ ካመነሽ በኋላ ነው መጠመቅ ያለብሽ በሕጻናነት
እድሜሽ ደግሞ እምነት ሊኖርሽ አይችልም…ጌታን እንደግል
አዳኝ አድርገሽ መቀበል አለብሽ ይሄ ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምሮ ነው
ሃና፡-መልካም……ለመነጋገር
እንዲያመቸን ቅደም ተከተል ብናስይዘው
ይሻላል ምክንያቱም አንተ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምሮ ነው እያልክ የምትለውን አሳብ እኔ በግሌ የምትናገረው አሳብ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆኑን አሳይሃለው
ፓስተር፡- ይቻላል እሺ እንነጋገር
ሃና፡-መጀመሪያ ስለመዳን ትርጋሜ እንስጥ… ፓስተር ለአንተ መዳን ምን ማለት ነው እንዴትስ ነው የሚገኘው?
ፓስተር፡-መዳን ማለት የዘላለም
ሕይወት ማግኘት ማለት ሲሆን..ጌታ
ኢየሱስን እንደግል አዳኝ አድርጎ
የተቀበለ ሁሉ..ባመነ ጊዜ ያገኘዋል ሃና፡-መዳን ማለት የዘላለም
ሕይወት ማግኘት…. መንግስተ ሰማያትን
ለመውረስ መብቃት..መጽደቅ … ማለት
ነው ፡፡በዚህ ልዩነት የለኝንም ግን ፓስተር ሰው ስላመነ ብቻ ድኗል እንላለን ወይስ ከመዳን መንገድ ውስጥ ገብታል…ማለቴ እምነት የመዳን መንገድ ነው ወይስ የመጨረሻው የመዳን ማረጋገጫ… በሌላ መልኩ እስቲ እንየው ….ለምሳሌ አንተ ለምን መልዕክት እኔ ጋር መጣህ?
ፓስተር፡-ጌታን እንደግል አዳኝ አድርገሽ አምነሽ እንድትድኚ ነዋ
ሃና፡- አንተስ ፓስተር ድነኋል?
ፓስተር፡-ሃሌ ሉያ ጌታ ይመስገን እኔ
ድኛለው
ሃና፡- እንዴት አድረገህ?
ፓስተር፡ይሄ ይጠየቃል…ጌታን እንደግል አዳኝ አድርጌ በማንኩ ቀን ጊዜ እና ሰዓት ነዋ
ሃና፡-አንዱ ልዩነታችን ከዚህ ይጀምራል… መጽሐፍ ቅዱስ አንተ ከምትለው አሳብ የተለየ ነው
ፓስተር፡- እንዴት? ..እስቲ አስረጂኝ ሃና፡- መልካም..ይሔውልህ
መጽሐፍ ቅዱስ…ሰው ሲያምን ዳነ አይልም…
ፓስተር፡ታዲያ ምንድነው የሚለው?
ሃና፡- ይድናል ነው የሚለው
ፓስተር- ታዲያ ‹‹ዳነ›› በሚለውና
‹‹በይድናል›› መካከል ምንድነው ልዩነቱ?
ሃና፡-‹‹ዳነ›› ማለት የተጠናቀቀ ነገርን
ሲያመለክት ‹‹ይድናል›› ግን ሂደትን
ይወክላል በመሆኑም መዳን በእምነት
ቅጽበት ሳይሆን በሂደት የሚገኝ እንደሆነ
ያረጋግጣል ለማንኛውም ጥቅሶችን እንያቸው….
ፓስተር ፡- መልካም ይቻላል..ሃሌ ሉያ
ሃና፡- ‹‹ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥
ያላመነ ግን ይፈረድበታል።››በማር16፡
16 ጌታ ‹‹ይድናል›› ነው ያለው ‹‹ድናል›› አላለም… በሐዋርያት
ዘመን ወደ ክርስትና እምነት የሚገቡትን ሰዎች እንዲህ ነው መጽሐፍ
ቅዱስ የሚገልጠው ‹‹ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር››ነው የሚለው ሐዋ2፡47 ‹‹የሚድኑትን›› ነው የሚለው
‹‹‹የዳኑት›› አይልም
ፓስታር፡- የዳኑትን ነው የሚለው የእኔ
መጽሐፍ ቅዱስ
ሃና፡-ፓስተር አስጨርሰኝ..የእኔ መጽሐፍ
ቅዱስ ነው ያልከው? ፓስተር፡- አዎ
ሃና፡-ፓስተር ሲጀመር መጽሐፍ ቅዱስ
ያንተ አይደለም
ፓስተር፡-ማለት የፈለኩትን አልገባሽም
ሃና ፡-አሁን እኔ ልናገር ኋላ ታስረዳኛለህ….. ጊዜ አለን… በደንብ በሁሉም ነገር ላይ እንነጋገራለን…ምንም
የምናስቀረው ነገር አይኖርም …ዋናው
ትልቁ ነገር አንተ በእጅ ያለውን መጽሐፍ
ቅዱስ ነው…‹‹የእኔ›› እንዳልከው..ብዙ
‹‹የእኔ›› የሚባሉ ‹‹የግለሰቦች
ትርጓሜ›› የአዛነፏቸው ብዙ አይነት መጽሐፍ ቅዱሳት ተፈጥረዋል..
በእርግጠኝነት አንተ የያዝከው…
በ1927 የታተመውን GOOD NEWS BIBLE ነው አይደል
ፓስተር ፡- አዎ
ሃና - አንተ የያዝከው GOOD NEWS BIBLE were being saved >> እና
አዲሱ ዓለም አቀፍ ትርጋሜ/ New
International Version/
‹‹ who were being saved›› ቢልም
በአስራ 16ኛው ክፍለ ዘመን
የታተመውን የመጀመሪያውን ጥንታዊውን ‹‹KING JAMES
VERSION ››ብናይ እንዲህ ነው
የሚለው ‹‹ should be saved ››
ሌላም ልጨምር ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ
‹‹የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥
ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።››1ኛ ቆሮ 1፡18 ለእኛ ‹‹ለምንድን›› ነው ብሎ የገለጠው
‹‹ለዳንን›› አላለም በዚህ ጥቅስ ቅዱስ
ጳውሎስ ራሱን ከሚድን እንጂ ከዳነ
ወገን አድርጎ አለመግለጡን ያሳውቃል
የሚገርመው ልክ እንደቅድሙ የመጀመሪያውን‹‹KING JAMES
VERSION ››ብናይ እንዲህ ነው
የሚለው ‹‹ Who are saved›› ነገር ግን አንተ የያዝከው በ1927 የታተመውን
GOOD NEWS BIBLE ‹‹Who are
being saved›› ሲለው New International Version
ላይም በድጋሚ ‹‹who are being saved ›› ብሎ ቀይሮታል አየህ ፓስተር የእናንተ የፕሮቴስታንቱ ዓለም መጽሐፍ ቅዱስን በአዲስ ትርጋሜ ስም ለአስተምሮታችሁ ደጋፊ እንዲሆን እየበረዛችሁት ነው
ፓስተር፡-ጌታ ይገስጽሽ…. እኛ እንደዚህ
አይደለም ያደረግነው…..ሰው
እንዲረዳው በቀላል ቋንቋ ነው ትርጋሜ
የሰጠነው…. ለጌታ ክብር ይሁን
ሃና፡- መልካም ….ቀላል ትርጋሜ ማለት ‹‹ይድናል›› የሚለውን ‹‹ድናል››
በማለት በመቀየር ነው ?አየህ መጽሐፍ
ቅዱስ ሰው ሲያምን ይድናል ማለቱ
ለመዳን እምነት መጀመሪያ እንጂ
መደምደሚያ አለመሆኑን ሰው የሚድነው በሂደት እንጂ በቅጽበት ባመነ ጊዜ አለመሆኑን ያረጋግጣል…እናንተ
ግን በእምነት ብቻ የመዳን መንገድ
ይገኛል ለማለት እና እምነት የመዳን
ፍጻሜ በማስመሰል..ቅዱስ ቃሉን
‹‹ድኗል›› እያላችሁ ቀይራችሁታል
በዚህ አሳባቹ ሰው ለመዳን ማመን ብቻ በቂ ነው....ቤ/ክ በመዳን አስተዋጽኦ
ማለት….ምስጢራተ ቤ/ክ ለመዳን
ድርሻ አልባ አድርጋችሁታል
ለምሳሌ ቅዱስ ጴጥሮስ በመጀመሪያው
ቀን ስብከቱ << የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል።>>የሐዋ 2:21 ነው
ያለው.. ‹‹ድናል›› አይልም…ስለሆነም መዳን ሂደት እንጂ ቅጽበታዊ ድርጊት
አይደለም
ፓስተር፡-...👇👇
👍1
ፓስተር፡-በወኅኒ ቤት ውስጥ ጠባቂው
ለጳውሎስና እና ሲላስ ‹‹እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል?›› ብሎ ለጠየቀው ‹‹በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ›› ሐዋ16፡30 አይደል ያለው
ሃና፡-መልካም ጥሩ ጥያቄ ነው…ነገር ግን ‹‹እመን…..ትድናላችሁ›› ማለት ውጤትን እንጂ ጊዜን ይገልጣል
እንዴ….ለምሳሌ አንተ ልጆችህ መዝናኛ
ውሰዱኝ ብለው ቢጠይቁ…እሺ ትሄዳላችሁ ብለህ ብትመልስ…..ቀጣዩ
የልጆችህ ጥያቄ ምን ይሆናል ብለህ
ታስባለህ
ፓስተር፡- ወደ ሽርሽር መቼ ነው
የምትወስደን ብለው ይጠይቁኛል
ሃና፡- እግዚአብሔር ይስጥልኝ….. ‹‹በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ›› ሐዋ16፡30 ማለት ‹‹ትድናላችሁ›› የሚለው ቃል በማመን መዳን የሚገኝበትን መንገድ ያመለክታል እንጂ ማመን የመዳን ጉዞ ፍጻሜን አያመለክትም፡፡
ፓስተር፡-እኔ እዚህ ላይ ጥያቄ አለኝ
ሃና፡- ጥያቄህን ቀጥል…….እኔም መልሳለው ፓስተሩ መጠየቁን ቀጥሏል እኛም ክፍል ሁለትን ማቅረባችንን እንቀጥላለን 👍
Share ማድረግ እንዳይረሳ
@And_Haymanot
@Tewahdo_Haymanote
@And_Haymanot
@Tewahdo_Haymanote
​​ገድሉ ተአምራቱ

@And_Haymanot

ገድሉ ተአምራቱ እጅግ ብዙ ነው 
ጣኦትን አዋርዶ የተሸለመው 
የተዋሕዶ ኮከብ ተክለሐዋርያ 
አባ ተክለ ሃይማኖት ዘኢትዮጵያ 
አዝ ------------------ 
ዳግማዊ ዮሐንስ ጠፈር የታጠቀ 
ንጹሕ ባህታዊ ጠላት ያስጨነቀ 
የጸጋ ዘአብ ፍሬ ዛፍ ሆኖ በቀለ 
በደብረ ሊባኖስ መናኝ አስከተለ 
አዝ --------------------- 
ደካማ መስሏቸው በአንድ እግሩ ቢያዩት 
ባላስድስት ክንፉ ጻድቁ የእኔ አባት 
እርሱስ አንበሳ ነው ትናገር ደብረ አስቦ 
ሌጌዎን ሲዋረድ እፍረት ተከናንቦ 
አዝ ----------- 
ከካህናት መካከል ኅሩይ ነው አቡዬ 
መጣው ከገዳምህ ልሳለለምህ ብዬ 
ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ተክለሃይማኖት 
ወልድ ዋሕድ ብለህ ምድሪቱን ቀደስካት 
አዝ ----------------- 
የባረከው ውኃ የረገጥከው መሬት 
ጥላህ ያረፈበት ሆንዋል ጸበል እምነት 
ኑና ተመልከቱ ድውያን ሲፈቱ 
ይሰብካል ተክለአብ ዛሬም እንደጥንቱ 
አዝ ------------------
@And_Haymanot
@And_Haymanot
aaa.jpeg
1.1 MB
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መንፈሳዊ ጉዞ በመርከብ....
@And_Haymanot
በቤቱ ያጽናችሁ!
ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ አብረው ይፀልያሉ አንደኛው ፀሎቱ ተመለሰለት አንደኛው ሳይመለስለት ቀረ። በዚህ ጊዜ ፀሎቱ ያልተመለሰለት ሰው "ጌታ ሆይ ሁለታችንም እኩል ፀልየን ለእርሱ ሰጥተኸው ለእኔ ከለከልኝ ለምንድ ነው?" አለው። እግዚዘብሔርም "ለእርሱ ባልሰጠው ይጠፋል፣ ላንተ ከሰጠሁህ ደግሞ ትጠፋለህ" አለው ይባላል። እግዚአብሔር ከራሳችን በላይ እኛን ያውቀናል። ለአንዳችን በመስጠት፣ አንዳችንን በመከልከል ዕድሜያችንን ያረዝመዋል። መስጠቱም መንሳቱም ሁለቱም በፍቅር ነውና በልመናችን
በፀሎታችን የአንተ ፈቃድ ይሁንልን ማለት ተገቢ ነው። ስለሁሉም የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን። አሜን!! (በሶሎሞን አያሌው)
Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ለመላው የተዋሕዶ ቤተሰቦች እኔ በምእራብ ሸዋ ሐገረ ስብከት በፊሊዶሮ ቅድስት ልደታ ማርያም ሰንበት ተማሪ ስሆን ለዚህ ግሩብ ተከታታዮች ቤተክርስቲያናችን ዛሬ ማለትም ግንቦት 15/2010 ዓ/ም በሙስሊም ተከባ መስጅድ ሰርተዉ ከባድ ሁኔታ ላይ እንገኛለን ዛሬም ብዙ ሕዝብ አልቋል እነሱም እናቃጥላለን ብለዉ እየፎከሩ ናቸዉ፡፡ እባካችሁ በልደታ በማርያም ቤተክርስቲያኗን እንታደግ የመጨረሻው ዘመን አስከፊ ነዉና አደራ አደራ አደራ ላልሰሙት አሰሙ፡፡ አድራሻ ኮልፌ ሰዋስወ ብርሐን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ተሻግሮ ፊሊዶሮ ቅድስት ልደታ ማርያም፡፡
@And_Haymanot
ፀልዩ በእንተ ሰላም ቤተክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ
ሐዋርያት ርትዕት በኅበ እግዚአብሔር! የሐዋርያት ጉባኤ
ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም
እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
አስተያትና መረጃን ለማቀበል
👉 @AHati_Haymanot
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለይተን እንወቅ

ከተሃድሶዎች ጋር ያለንን መሰረታዊ ልዩነታችንን ካላወቅን
እንጠፋለን
@And_Haymanot
ተሃድሶዎች ማርያምን እንወዳታለን ሊሉ ይችላሉ ለማዘናጋትም ይላሉም፡፡ እንወዳታለን ስላሉ ከእምነት ያልወጡ
እንዳይመስላችሁ፡፡ መውደድ አለመውደድ አይደለም
የሚያለያየን፡፡ ማየት ያለባችሁ
ስላማላጅነቷ መመስከርና ማመናቸውን ነው ስለዘላለማዊ ድንግልናዋ መመስከርና ማመናቸውን ነው
የአዳም በደል(ጥንተ አብሶ) ያልነካት ንጽህት ዘር መሆኗን መመስከርና ማመናቸውን ነው፡፡ [ተሃድሶዎች በእነዚህ በስስቱ ነገሮች(በአማላጅነቷ፣
በዘላለማዊ ድንግልናዋ፣ ከጥንተ አብሶ ነፃ መሆኗ) በፍፁም አያምኑም ቢሞቱም አይመሰክሩም]

መውደድማ ፕሮቴስታንቶችም እንወዳታለን ይላሉ፤ ያው አለ
አይደል በጌታ የተፈጠረን ፍጡር መጥላት ስለሌለብን... 😁 😁

እናስታውስ የተሐድሶ መናፍቃን ከፕሮቴስታን ትምህርት ጋር ምንም ልዩነት የላቸውም ከእናት ተዋህዶ ትምህርት ጋርም አንድነት የላቸውም፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ፈራጅ ነው የኛ ጌታ

@And_Haymanot

ተወዳጆች በ social Media የእመቤታችን ተአምር ነው ሀብት እንዲኖርህ አባዛው ካልሆነ ሥራህ ኑሮህ ይዘበራረቃል የሚል የሀሠት መልእክት እንደመብዛቱ ከማባዛት እንቆጠብ መንፈስን እንመርምር እያልን ዛሬ ደሞ በውስጥ ላደረሣችሁን ተመሣሣይ የሀሠት መልእክት ጥንቃቄ እንድታደርጉ አቅርበነዋል፡፡ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት አይደለምና ከማባዛት እንቆጠብ ለማለት እንወዳለ
@And_Haymanot
የእግዚአብሔርን
መምጫ #ማንም አያውቅም ነገር ግን እግዚአብሔር መላእክቱን ትላንት ማታ መለከት ሊያስነፋ ነበር ይለናል፡፡
ይቀጥልና ጌታችን በሰማይ #ወድቆ_እያነባ_ለመነ
ዛሬም በመሥቀል እንደተሠቀለው ደሙ ይፈሳል ..... ይለናል፡፡
ተወዳጆች ይህ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነውን? በዚህ የሀሰት ትምህርት ላይ የተጠቀሠው ሰው የጌታን መምጫ ሊጠቁምም ይቃጣዋል፡፡ ከዚህ በፊት በተደረጉ በፕሮቴስታንቱ አለም ያሉ የሐሰት ትንቢቶችን መመልከት ለዚህ ማሳያ ናቸው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን እንዲህ ይለናል
" ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም።"
(የማቴዎስ ወንጌል 24:36)
" ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 24:42)
(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት ምዕ. 3)

" #ጌታችን_በሰማይ_ወድቆ_እያነባ_ለመነ ዛሬም በመሥቀል እንደተሠቀለው ደሙ ይፈሳል ..... " ይህስ የጌታን የማዳን ስራ ከማወቅ የመጣ ነውን? ይህን የጠቀሡት ዛሬም ላይ አማላጃችን ነው ለማለት ቢሆንም ጌታችን ግን አንድ ግዜ የማስታረቅን ስራ ፈፅሞ በግርማው ተቀምጧል እንጂ እነሱ እንደሚሉት ዛሬም በእለተ አርብ እንደተሠቀለ ሆኖ ደሙ እየፈሰሰ ማራቸው አይልም
" እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤"
(ወደ ዕብራውያን 1:3)
" እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም #ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።"
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5:19)
እንግዲህ ምን እንላለን የጌታን ማንነት ባለማወቅ ዛሬም እየወደቀ ይለምናል ማለት ትልቅ ክህደት ነው

(ወደ ዕብራውያን ምዕ. 9)
----------
25፤ ሊቀ ካህናትም በየዓመቱ የሌላውን ደም ይዞ ወደ ቅድስት እንደሚገባ፥ ራሱን #ብዙ_ጊዜ_ሊያቀርብ_አልገባም
26፤ እንዲህ ቢሆንስ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር፤ አሁን ግን በዓለም ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል።
https://tttttt.me/And_Haymanot/541
ይቆየን....
ለጠፉት ልቦናን ይስጥልን
"ማራናታ"
@And_Haymanot
@And_Haymanot

በክርስቶስ ማንነት ለሚጠይቁት ጥያቄም እነሆ ምላሽ 👉 https://tttttt.me/And_Haymanot/288
4_5789494294419079492
<unknown>
"እንዳያስቷችሁ ተጠንቀቁ"
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጂ አማላጅ አይደለም፡፡ የሱን ማንነት ባለማወቅ እንዲህ ለሚጠፉት ልቦናን ይስጥልን - https://tttttt.me/And_Haymanot/538
በክርስቶስ ማንነት ለሚጠይቁት ጥያቄም እነሆ ምላሽ 👉 https://tttttt.me/And_Haymanot/288
ድረስልን
በቃ ብሎን ጌታ ግፍ እና መከራ
ይላክልን አንተን እስቲ እኛን አብስራ ።
ዘመናችን ሆኗል እንደ ዓመተ ፍዳ
ድረስልን ማልደህ ገብርኤል ፈጣኑ ድሆቹን ተራዳ ።
[ዳንኤል ግርማ ]
@And_Haymanot
የመልአኩ ተራዳይነት አይለየን
መልካም ዕለተ ሰንበት
ድንግል ማርያምን በዮሀንስ በኩል በቀራንዮ አደባባይ በእናትነት ለሁላችን ተሠጠችን ብሎ መቀበል ለከበዳቸው ነገር ግን ራዕይ በዮሀንስ በኩል ለሁላችን ተሠጠን ሲባል ለተቀበሉ ከፍሎ አማኝ (የእናቱ ጠላቶች) ለሆኑት ልብ ይስጥልን!
@And_Haymanot
የቀራንዮ_ስጦታችን
❤️ 21 ❤️
❤️ ለእናትነቷ ❤️
@And_Haymanot
ማርያም ማርያም
ማርያም ማርያም
ማርያም ማርያም
ማርያም ማርያም
ለ8,10 እና 12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ እህትና ወንድሞቻችን የምታስቡበትን አእምሮ የምታስተውሉበትን ልቦና ፣ እንዲሁም የሚያረጋጋን መንፈስ እግዚአብሔር ያድላችሁ፡፡ ድንግል ማርያም ከናንተ ጋር ትሁን፡፡
መልካም ፈተና
@And_Haymanot
፩ ኃይማኖት
ተዓምራትን ማድርግ ትፈልጋላችሁ??

@And_Haymanot

እንግዲያውስ፦
👉 በዘፈን የደነቆረን ጆሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፤
👉ሴትን በመመኘት የታወረውን ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አዲርጉት፤
👉 በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፤
👉 ወደ ኃጢዓት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አዲርጉት፤
👉 ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፋር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፤
ከታዓምራት ኹሉ የበለጠ ተዓምር ይህ ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@And_Haymanot
መልካም ዕለተ ሰንበት
ክፍል 07 ውይይት ቀጥሏል ..ጌታን እንደግል አዳኝ አድርጋችሁ ተቀበሉ ‹‹accept Jesus Christ as your personal savior››የሚለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው? ከዚህ በፊት በነበሩን ተከታታይ ስድስት ክፍሎች…ከአንድ ፕሮቴስታንት ፓስተር ጋር ሶሪያዊታ የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ሐና ባደረገችው ውይይት…..አንድ ሰው በክርስቶስ
ሲያምን ይድናል? ወይስ ድኗል? ፣ መዳን በቅጽበት ነው ወይስ በሂደት የሚገኝ ? ስለሚሉ እና በመጨረሻም በቅርቡ የፕሮቴስታንቱ ዓለም መሪዎች ራሳቸውን ‹‹ሐዋርያ›› አድርገው መጥራታቸው ተገቢ ስላለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት ባደረገ ውይይት ተመልክተን ነበር፡፡ ለዛሬ ደግሞ በየመንገዱ ለመዳን በተደጋጋሚ “Have you accepted Jesus Christ as your personal savior?” የሚለውን የፕሮቴስታንቱን አስተምሮ በጣም በጥልቀት በተከታታይ እናያለን
ለማንበብ
👉 https://tttttt.me/Tewahdo_Haymanote/111
~~~~~~~~~~
ለአስተያየት 👉 @AHati_Haymanot
Join 👇
@And_Haymanot
@And_Haymanot