ገድለ ተክለሃይማኖት ፫
@And_Haymanot
ጥያቄ ፫
፫. “ከሩቅም ከቅርብም ቢመጣ ወደ መቃብርህ የሄደውን እኔ ወደ መቃብሬ ኢየሩሳሌም እንደ ሄደ አደርገዋለሁ፤ በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተነገረው ልጆችህ ጋራ እኔ እቈጥረዋለሁ፡፡” [ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 193] ማለት ምን ማለት ነው?
+ መልስ፡- ወደ መቃብርህ የመጣውን ወደ መቃብሬ እንደመጣ አደርገዋለሁ ማለት በአንተ አማላጅነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡ ይህም እናንተን የተቀበለ
እኔን ተቀበለ ያለው የወንጌል ቃል በተግባር ሲተረጎም ነው፡፡ + በተክለ ሃይማኖት በመቃብር ላይ በተክለ ሃይማኖት ስም በተሠራው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወደ ሚገኝበት በመምጣት በመጸለይ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት ነው፡፡ የእግዚአብሔር በረከት ወደሚገኝበት ቦታ በመሄድ ዋጋ እንደሚገኝም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡ 2ኛ.ነገ.5፡1፤
ዕብ. 11፡23፤ ሩት. 1፡16-18፡፡
+ “በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን
የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተጻፈው ልጆችህ ጋር እኔ አኖራቸዋለሁ፡፡” የሚለውም ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን መግቢያ
በርነት የበለጠ ያስተምራል እንጂ
አያስቀርም፡፡ በአንተ መታሰቢያ
ዕለት የእኔን ሥጋና ደም ተቀብሎ በአንተ አስተማሪነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡
፬ የመናፍቃን ጥያቄ ከገድለ ተክለሐይማኖት ውስጥ: "እባብን የገደለ ይጽድቃል" ይላል፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሁሉ እባብን እየፈለጉ ለመጽደቅ እባብን መግደል አለባቸው ወይ የሚል ነው። አይ ይህቺ የመናፍቃን ጭንቅላት ትንሽ ብትሰፋ! ወገኖቼ መጸሐፍ ቅዱስ እውርን እውር ቢመራው ተያይዞ ገደል መግባት ነው ይላል:: አንዱ ብርሃን መሆን አለበት:: ዛሬ ብዙ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ታውረዋል፡፡ አባታችን ተክለ ሐይማኖት ይፈውሱዋቸው አሜን :: ወገኖቼ እባብን የገደለ ይጸድቃል ማለት እባብ የተባለ ዲያቢሎስ ነው:: ለምሳሌ ያህል በመዝሙር ምህራፍ 73 ቁጥር 14 እንዲህ ይላል “አንተም የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው፤” ይላል :: ታዲያ አንተ የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ
ሲል ታዲያ እግዚአብሔር ዘንዶ ያለበትን እየሔደ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው ማለት ነውን? አይደለም :: ዘንዶ የተባለው ሰይጣን ነው:: ሰይጣንን ደግሞ እግዚአብሔር በመስቀሉ
ቀጥቅጦታል :: እንዲሁም ገድለ ተክለ ሐይማኖት ላይም እባብን የገደለ ይጽድቃል ሲል ሰይጣንን የገደለ ይጸድቃል ማለቱ ነው :: ሰይጣንን የምንገለው ደግሞ በጾም በጸሎት እና በስግደት ነው:: በነዚህ እባብ (ዲያቢሎስን ) መግደል እንችላለን:: በተጨማሪም ደግሞ ራእይ ዮሐንስ ምህራፍ 12 ቁጥር 7 እንዲህ ይላል፡- “በሰማይም ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና ሰራዊቱ ዘንዶውን ተዋጉት :: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም፤ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም:: ዓለሙን ሁሉ የሚያስት ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፡፡ ወደ ምድርም ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤” ይላል:: ታዲያ ሚካኤልና ቅዱሳን መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ ሲል ከእንስሳ ጋር ተዋጉ ማለት ነውን? አይደለም፡፡ ዘንዶ የተባለው የቀደመው ሰይጣን እርሱ ዲያቢሎስ ነው ይለናል:፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
---------ልቦናን ያድልልን -----------
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
@And_Haymanot
ጥያቄ ፫
፫. “ከሩቅም ከቅርብም ቢመጣ ወደ መቃብርህ የሄደውን እኔ ወደ መቃብሬ ኢየሩሳሌም እንደ ሄደ አደርገዋለሁ፤ በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተነገረው ልጆችህ ጋራ እኔ እቈጥረዋለሁ፡፡” [ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 193] ማለት ምን ማለት ነው?
+ መልስ፡- ወደ መቃብርህ የመጣውን ወደ መቃብሬ እንደመጣ አደርገዋለሁ ማለት በአንተ አማላጅነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡ ይህም እናንተን የተቀበለ
እኔን ተቀበለ ያለው የወንጌል ቃል በተግባር ሲተረጎም ነው፡፡ + በተክለ ሃይማኖት በመቃብር ላይ በተክለ ሃይማኖት ስም በተሠራው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወደ ሚገኝበት በመምጣት በመጸለይ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት ነው፡፡ የእግዚአብሔር በረከት ወደሚገኝበት ቦታ በመሄድ ዋጋ እንደሚገኝም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡ 2ኛ.ነገ.5፡1፤
ዕብ. 11፡23፤ ሩት. 1፡16-18፡፡
+ “በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን
የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተጻፈው ልጆችህ ጋር እኔ አኖራቸዋለሁ፡፡” የሚለውም ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን መግቢያ
በርነት የበለጠ ያስተምራል እንጂ
አያስቀርም፡፡ በአንተ መታሰቢያ
ዕለት የእኔን ሥጋና ደም ተቀብሎ በአንተ አስተማሪነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡
፬ የመናፍቃን ጥያቄ ከገድለ ተክለሐይማኖት ውስጥ: "እባብን የገደለ ይጽድቃል" ይላል፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሁሉ እባብን እየፈለጉ ለመጽደቅ እባብን መግደል አለባቸው ወይ የሚል ነው። አይ ይህቺ የመናፍቃን ጭንቅላት ትንሽ ብትሰፋ! ወገኖቼ መጸሐፍ ቅዱስ እውርን እውር ቢመራው ተያይዞ ገደል መግባት ነው ይላል:: አንዱ ብርሃን መሆን አለበት:: ዛሬ ብዙ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ታውረዋል፡፡ አባታችን ተክለ ሐይማኖት ይፈውሱዋቸው አሜን :: ወገኖቼ እባብን የገደለ ይጸድቃል ማለት እባብ የተባለ ዲያቢሎስ ነው:: ለምሳሌ ያህል በመዝሙር ምህራፍ 73 ቁጥር 14 እንዲህ ይላል “አንተም የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው፤” ይላል :: ታዲያ አንተ የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ
ሲል ታዲያ እግዚአብሔር ዘንዶ ያለበትን እየሔደ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው ማለት ነውን? አይደለም :: ዘንዶ የተባለው ሰይጣን ነው:: ሰይጣንን ደግሞ እግዚአብሔር በመስቀሉ
ቀጥቅጦታል :: እንዲሁም ገድለ ተክለ ሐይማኖት ላይም እባብን የገደለ ይጽድቃል ሲል ሰይጣንን የገደለ ይጸድቃል ማለቱ ነው :: ሰይጣንን የምንገለው ደግሞ በጾም በጸሎት እና በስግደት ነው:: በነዚህ እባብ (ዲያቢሎስን ) መግደል እንችላለን:: በተጨማሪም ደግሞ ራእይ ዮሐንስ ምህራፍ 12 ቁጥር 7 እንዲህ ይላል፡- “በሰማይም ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና ሰራዊቱ ዘንዶውን ተዋጉት :: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም፤ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም:: ዓለሙን ሁሉ የሚያስት ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፡፡ ወደ ምድርም ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤” ይላል:: ታዲያ ሚካኤልና ቅዱሳን መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ ሲል ከእንስሳ ጋር ተዋጉ ማለት ነውን? አይደለም፡፡ ዘንዶ የተባለው የቀደመው ሰይጣን እርሱ ዲያቢሎስ ነው ይለናል:፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
---------ልቦናን ያድልልን -----------
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ገድል_ያወጣል_ከገደል
የገድላት ምንነትና አስፈላጊነት እንዲሁም በገድላት ዙርያ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን የምንዳስስበት ተከታታይ ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ
ክፍል ፩
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@Konobyos
የገድላት ምንነትና አስፈላጊነት እንዲሁም በገድላት ዙርያ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን የምንዳስስበት ተከታታይ ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ
ክፍል ፩
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@Konobyos
፩ ሃይማኖት
#ገድል_ያወጣል_ከገደል የገድላት ምንነትና አስፈላጊነት እንዲሁም በገድላት ዙርያ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን የምንዳስስበት ተከታታይ ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ ክፍል ፩ በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ @Konobyos
ገድል ያወጣል ከገደል
በድጋሜ የቀረበ ስለ ገድል ምንነት በደንብ ለመረዳት ይረዳናል እናም ሁላችንም ልንሰማው ይገባል
👉Wifi ተጠቀሙ ለመስማት
@And_Haymanot
በድጋሜ የቀረበ ስለ ገድል ምንነት በደንብ ለመረዳት ይረዳናል እናም ሁላችንም ልንሰማው ይገባል
👉Wifi ተጠቀሙ ለመስማት
@And_Haymanot
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ገድል_ያወጣል_ከገደል
ክፍል ፪
@And_Haymanot
ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@Konobyos
@And_Haymanot
ክፍል ፪
@And_Haymanot
ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@Konobyos
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
#ገድል_ያወጣል_ከገደል ክፍል ፪ @And_Haymanot ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ @Konobyos @And_Haymanot
ገድል ያወጣል ከገደል ፪
በገድላት መሰረታዊ መረዳት እንዲኖረን የሚረዳ ትምህርት ነውና እነሆ
መልካም ንባብ ተወዳጆች
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በገድላት መሰረታዊ መረዳት እንዲኖረን የሚረዳ ትምህርት ነውና እነሆ
መልካም ንባብ ተወዳጆች
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ነገረ ማርያም
ተወዳጆች እንደምን ቆያችሁን
እነሆ ነገረ ማርያምን በስፋት ልንዳስስ በዝግጅት ላይ ነን በውስጥ በተደጋጋሚ ነገረ ማርያም ላይ ጥያቄ እየደረሰን በመሆኑ ከዚህ በፊት ያነሳናቸውን እንዲሁም እንድናነሳላችሁ የምትፈልጉትን ጥያቄ በ @And_Haymanot_bot በኩል አድርሱን
√ መልእክቶች በብዛት ስለሚላኩልን ሃሳባችሁን ብቻ አስቀምጡልን
የ እናታችን ምልጃ እና ጸሎት አይለየን
@And_Haymanot
ተወዳጆች እንደምን ቆያችሁን
እነሆ ነገረ ማርያምን በስፋት ልንዳስስ በዝግጅት ላይ ነን በውስጥ በተደጋጋሚ ነገረ ማርያም ላይ ጥያቄ እየደረሰን በመሆኑ ከዚህ በፊት ያነሳናቸውን እንዲሁም እንድናነሳላችሁ የምትፈልጉትን ጥያቄ በ @And_Haymanot_bot በኩል አድርሱን
√ መልእክቶች በብዛት ስለሚላኩልን ሃሳባችሁን ብቻ አስቀምጡልን
የ እናታችን ምልጃ እና ጸሎት አይለየን
@And_Haymanot
✞✞ልቦናዬ_በጎ_ነገርን_አወጣ እኔስ የማርያምን ክብር እናገራለሁ ፡፡ በማብዛት አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ፡፡
✞ እኔስ የድንግልን ውዳሴ እናገራለሁ መዘንጋት ባለበት
ቃል በማስረዘም አይደለም በማሳጠር ነው እንጂ .........
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
✞ እኔስ የድንግልን ውዳሴ እናገራለሁ መዘንጋት ባለበት
ቃል በማስረዘም አይደለም በማሳጠር ነው እንጂ .........
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በእንተ ቅድስት ድንግል ማርያም
@And_Haymanot
ከትውልድ ሊቆጠሩ ያልተገባቸው ሐሳውያን የክፋትና የክህደትን ቃል እንደ ጸሎት ደጋግመው ስለሚናገሩና ስለሚጽፉ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም ያሰፈረውን ማስረጃ በአጭሩ እንዘረዝራለን ። በእምነት ያለነውን በእምነታችን ያጽናን በጥፋት መንገድ ያሉትንም ልቦናቸውን ያቅናልን ። አሜን ።
🙏🙏🙏ድንግል ማርያም 🙏🙏🙏
👉 1. ስለ ቅድስናዋ - የቅዱስ አምላክ እናት በመሆኗ [ኢየሱስ የጸነሰችው የወለደች ያሳደገችው የማህጸኗ ፍሬ ስለሆነ (ሉቃ 1:31:42 ፥ 2:7)] ወላዲተ አምላክ እያልን እንጠራታለን ። የቅዱስ አምላክ እናት ድንግል ማርያም ክርስቶስን ያህል መለኮታዊ አካል በማህጸኗ ስለወሰነች ቅድስት ትባላለች ። እኛ ክርስቲያኖችም ቅዱስ የተባልነው ቅዱሱ አምላክ ከርሷ ከተወለደና በቅዱስ ደሙ ከዋጀን በኋላ ነው ። ቅድስት ማርያም በነፍሷም በሥጋዋም ቅድስት ናት ። ሰው የሆነ ሁሉ ኃጢአትን ከመሥራት እንጂ ከማየት ፥ ከማሰብ ፥ ከመናገር የሚነጻ የለም። ርሷ ግን ከማየትና ከመስማት ፥ ከማሰብና ከመናገር ሁሉ ንጽሕት ናት። ስለዚህም ድንግል በክልኤ (በሁለት ወገን ድንግል) ትባላለች። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ከእግዚአብሔር ተልኮ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ ሲላት ፥ የተለየችና የተቀደሰች መሆኗን በምስጋና ቃል መግለጡ ነው ። ቅድስት ኤልሳቤጥም በመንፈስ ቅዱስ ተነድታ ፥ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ብላ በመጮኽ ዳግም አረጋግጣለች ። ስለዚህም የመንፈስ ቅዱስ ቃል ፥ ድንግል ማርያም ቅድስት መትሕተ ፈጣሪ መልዕልተ ፍጡራን እያልን በነፍስ በሥጋ ቅድስት መሆኗን እንመሰክራለን ።
👉 2. ድንግልናዋ - ቅድስት ማርያም እመቤትነትን ከገረድነት ፥ እናትነትን ከድንግልና ጋር አስተባብራ የያዘች ስለሆነችም የክብር ስሟ ድንግል ወእም እም ወዓመት የሚል ነው ። ድንግልናዋም ዘለዓለማዊ ስለሆነ ድንግል ዘለዓለም እንላታለን ። በአይሁድ ዘንድ ንጽሕናና ድንግልና የተወደደ፥ የተለመደ ፥ የተቀደሰም ህግ ነበር ። ይህን ህግ አፍርሶ የሚገኝ ወደ እሳት
ይጣላል ፥ በድንጋይም ተወግሮ ይሞታል። ስለዚህም ወንድ ሚስት እስኪያገባ ፥ ሴቷም ባል እስክታገባ ድረስ በድንግልና መኖር ግዴታቸው ነው ። በመሆኑም እነዚህ ደናግሎች ከጋብቻ በመራቅ ማለት ከሥጋዊ ሥራ ድንግል ይሁኑ እንጂ ከሐሳብ ፥ ከማየት ፥ ከመስማትና ከመናገር ድንግሎች አልነበሩም ። እመቤታችን ድንግል ማርያም ግን በዘመኗ ከነበሩት ደናግል ተለይታ ፥ ከሐሳብ ድንግል ናት ፥ ከማየትና ከመስማት ድንግል ናት ፤ ክፋት ከመሥራትም ድንግል ናት ። ስለዚህም ቤተ ክርስቲያናችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ንጽሕናና ቅድስና በመረዳት "እሞሙ ለሰማዕታት ወእኅቶሙ ለመላእክት ትምክህቶሙ ለወራዙት ወለድንግል" ማለትም "ለሰማዕታት እናታቸው ለመላእክት እህታቸው ለደናግላን ትምክህታቸው"
እያለች ታመሰግናታለች ።
👉 3. ቅድስት ድንግል ማርያም ምስጋና እንዲገባት ፤ እመቤታችን ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ስለሆነች ፥ ዘወትር ምስጋና ይገባታል ። የመጽሐፍ ማስረጃዎቻችንም የሚከተሉት
ናቸው
🙏 ሀ/ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ምስጋና (ሉቃ 1:28)
🙏 ለ/ የቅድስት ኤልሳቤጥ ምስጋና (ሉቃ 1:42-43)
🙏 ሐ/ ትውልድ ሁሉ እንዲያመሰግናት የእመቤታችን የምስክርነት ቃል (ሉቃ 1:48)
🙏 መ/ አንዲት ሴት የተሸከመችህ ማኅጸን ቡርክት ናት አጥብተው ያሳደጉህ ጡቶችም ብሩካን ናቸው በማለት ያቀረበችው ምስጋና (ሉቃ 11:27)
🙏 ሠ/ ቅዱስ ጳውሎስም እግዚአብሔር ያከበረውንና የመረጣቸውን የሚከራከርና የሚወቅስ ማነው? እግዚአብሔር ያጸደቀውንስ የሚኮንን ማነው? በማለቱ (ሮሜ 8:33)
🙏 ረ/ ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ ብሎ መጽሐፍ ስለሚዘንያ (ሮሜ 13:7) እመቤታችን ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል አለች እንጅ የተወሰነ ቀንና የተለየ ህዝብ አልጠቀሰችም ፤ መልአኩም ቡርክት ነሽ አለ እንጂ ነበርሽ ብሎ ስለአለፈው ብቻ አልተናገረም ፤ ቅድስት ኤልሳቤጥም ከሴቶች ሁሉ የተባረክሽ ነሽ አለች እንጅ ነበረሽ አላለችም ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ይኸን ሁሉ አስረጅ ገንዘቧ ስላደረገች ፥ ከቀድሞ ጀምሮ ዛሬም ወደፊትም ንጹሕ ክብርና ምስጋናን ለእመቤታችን በሰፊው ሰጥታ ስታመሰግን ትኖራለች ።
👉 4. ክብር እንደሚገባት:- ቅድስት ድንግል ማርያም ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ እርሷ በማህጸኗ ወስናለችና ፥ ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ የሆነ ክብር አላት ። እንዲህም ከሆነ ከሰማይ ከምድርም እርሷ
ትበልጣለች እርስዋም ትከብራለች ማለትም በሰማይና በምድር ካሉት ከግዙፋኑና ከረቂቃኑ ፍጥረታት ሁሉ እርስዋ ትበልጣለች እርስዋም ትከብራለች ። ልዑልና ኃያል እግዚአብሔር ማህጸኗን ዙፋኑ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን አድሯልና ። እግዚአብሔር በመንፈሱ በሰው ላይ ለማደር እንኳን ሰው አላገኘም ነበር ። ነገር ግን ቅድስት ማርያም በንጽሕና በድንግልና ብትገኝ የልዑል እግዚአብሔር ማኅደር ለመሆን
በቃች ። ስለዚህ ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነ ክብር ተገባት ። ጌታችን ራሱን ከዓለም ግሳንግስ አንጽቶና በድንግልና ጠብቆ ህዝብን ስለንስሐ ያስተምር የነበረውን ዮሐንስን እንኳን፥ ሴቶች ከወለዱት እንደ ዮሐንስ የለም ብሎ ሲመሰክርለት እመቤታችንንማ ከንጽሕናዋ ከድንግልናዋ ጋር የአምላክ እናት ስለሆነች ከሁሉ በላይ እንዴት በበለጠ አትከብር? አምላክ የርሷን ሥጋ ተዋሕዷል ሰውም በዚህ ሥጋና ደም
ከእግዚአብሔር ጋር ታርቆ የእግዚአብሔር መንግሥትን የሚወርስ ሆኗልና በክርስቶስ ደም ድኛለሁ የሚል የሰው ልጅ ሁሉ ሊያከብራት ይገባል ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ከትውልድ ሊቆጠሩ ያልተገባቸው ሐሳውያን የክፋትና የክህደትን ቃል እንደ ጸሎት ደጋግመው ስለሚናገሩና ስለሚጽፉ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም ያሰፈረውን ማስረጃ በአጭሩ እንዘረዝራለን ። በእምነት ያለነውን በእምነታችን ያጽናን በጥፋት መንገድ ያሉትንም ልቦናቸውን ያቅናልን ። አሜን ።
🙏🙏🙏ድንግል ማርያም 🙏🙏🙏
👉 1. ስለ ቅድስናዋ - የቅዱስ አምላክ እናት በመሆኗ [ኢየሱስ የጸነሰችው የወለደች ያሳደገችው የማህጸኗ ፍሬ ስለሆነ (ሉቃ 1:31:42 ፥ 2:7)] ወላዲተ አምላክ እያልን እንጠራታለን ። የቅዱስ አምላክ እናት ድንግል ማርያም ክርስቶስን ያህል መለኮታዊ አካል በማህጸኗ ስለወሰነች ቅድስት ትባላለች ። እኛ ክርስቲያኖችም ቅዱስ የተባልነው ቅዱሱ አምላክ ከርሷ ከተወለደና በቅዱስ ደሙ ከዋጀን በኋላ ነው ። ቅድስት ማርያም በነፍሷም በሥጋዋም ቅድስት ናት ። ሰው የሆነ ሁሉ ኃጢአትን ከመሥራት እንጂ ከማየት ፥ ከማሰብ ፥ ከመናገር የሚነጻ የለም። ርሷ ግን ከማየትና ከመስማት ፥ ከማሰብና ከመናገር ሁሉ ንጽሕት ናት። ስለዚህም ድንግል በክልኤ (በሁለት ወገን ድንግል) ትባላለች። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ከእግዚአብሔር ተልኮ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ ሲላት ፥ የተለየችና የተቀደሰች መሆኗን በምስጋና ቃል መግለጡ ነው ። ቅድስት ኤልሳቤጥም በመንፈስ ቅዱስ ተነድታ ፥ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ብላ በመጮኽ ዳግም አረጋግጣለች ። ስለዚህም የመንፈስ ቅዱስ ቃል ፥ ድንግል ማርያም ቅድስት መትሕተ ፈጣሪ መልዕልተ ፍጡራን እያልን በነፍስ በሥጋ ቅድስት መሆኗን እንመሰክራለን ።
👉 2. ድንግልናዋ - ቅድስት ማርያም እመቤትነትን ከገረድነት ፥ እናትነትን ከድንግልና ጋር አስተባብራ የያዘች ስለሆነችም የክብር ስሟ ድንግል ወእም እም ወዓመት የሚል ነው ። ድንግልናዋም ዘለዓለማዊ ስለሆነ ድንግል ዘለዓለም እንላታለን ። በአይሁድ ዘንድ ንጽሕናና ድንግልና የተወደደ፥ የተለመደ ፥ የተቀደሰም ህግ ነበር ። ይህን ህግ አፍርሶ የሚገኝ ወደ እሳት
ይጣላል ፥ በድንጋይም ተወግሮ ይሞታል። ስለዚህም ወንድ ሚስት እስኪያገባ ፥ ሴቷም ባል እስክታገባ ድረስ በድንግልና መኖር ግዴታቸው ነው ። በመሆኑም እነዚህ ደናግሎች ከጋብቻ በመራቅ ማለት ከሥጋዊ ሥራ ድንግል ይሁኑ እንጂ ከሐሳብ ፥ ከማየት ፥ ከመስማትና ከመናገር ድንግሎች አልነበሩም ። እመቤታችን ድንግል ማርያም ግን በዘመኗ ከነበሩት ደናግል ተለይታ ፥ ከሐሳብ ድንግል ናት ፥ ከማየትና ከመስማት ድንግል ናት ፤ ክፋት ከመሥራትም ድንግል ናት ። ስለዚህም ቤተ ክርስቲያናችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ንጽሕናና ቅድስና በመረዳት "እሞሙ ለሰማዕታት ወእኅቶሙ ለመላእክት ትምክህቶሙ ለወራዙት ወለድንግል" ማለትም "ለሰማዕታት እናታቸው ለመላእክት እህታቸው ለደናግላን ትምክህታቸው"
እያለች ታመሰግናታለች ።
👉 3. ቅድስት ድንግል ማርያም ምስጋና እንዲገባት ፤ እመቤታችን ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች ስለሆነች ፥ ዘወትር ምስጋና ይገባታል ። የመጽሐፍ ማስረጃዎቻችንም የሚከተሉት
ናቸው
🙏 ሀ/ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ምስጋና (ሉቃ 1:28)
🙏 ለ/ የቅድስት ኤልሳቤጥ ምስጋና (ሉቃ 1:42-43)
🙏 ሐ/ ትውልድ ሁሉ እንዲያመሰግናት የእመቤታችን የምስክርነት ቃል (ሉቃ 1:48)
🙏 መ/ አንዲት ሴት የተሸከመችህ ማኅጸን ቡርክት ናት አጥብተው ያሳደጉህ ጡቶችም ብሩካን ናቸው በማለት ያቀረበችው ምስጋና (ሉቃ 11:27)
🙏 ሠ/ ቅዱስ ጳውሎስም እግዚአብሔር ያከበረውንና የመረጣቸውን የሚከራከርና የሚወቅስ ማነው? እግዚአብሔር ያጸደቀውንስ የሚኮንን ማነው? በማለቱ (ሮሜ 8:33)
🙏 ረ/ ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ ብሎ መጽሐፍ ስለሚዘንያ (ሮሜ 13:7) እመቤታችን ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል አለች እንጅ የተወሰነ ቀንና የተለየ ህዝብ አልጠቀሰችም ፤ መልአኩም ቡርክት ነሽ አለ እንጂ ነበርሽ ብሎ ስለአለፈው ብቻ አልተናገረም ፤ ቅድስት ኤልሳቤጥም ከሴቶች ሁሉ የተባረክሽ ነሽ አለች እንጅ ነበረሽ አላለችም ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ይኸን ሁሉ አስረጅ ገንዘቧ ስላደረገች ፥ ከቀድሞ ጀምሮ ዛሬም ወደፊትም ንጹሕ ክብርና ምስጋናን ለእመቤታችን በሰፊው ሰጥታ ስታመሰግን ትኖራለች ።
👉 4. ክብር እንደሚገባት:- ቅድስት ድንግል ማርያም ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ እርሷ በማህጸኗ ወስናለችና ፥ ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ የሆነ ክብር አላት ። እንዲህም ከሆነ ከሰማይ ከምድርም እርሷ
ትበልጣለች እርስዋም ትከብራለች ማለትም በሰማይና በምድር ካሉት ከግዙፋኑና ከረቂቃኑ ፍጥረታት ሁሉ እርስዋ ትበልጣለች እርስዋም ትከብራለች ። ልዑልና ኃያል እግዚአብሔር ማህጸኗን ዙፋኑ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን አድሯልና ። እግዚአብሔር በመንፈሱ በሰው ላይ ለማደር እንኳን ሰው አላገኘም ነበር ። ነገር ግን ቅድስት ማርያም በንጽሕና በድንግልና ብትገኝ የልዑል እግዚአብሔር ማኅደር ለመሆን
በቃች ። ስለዚህ ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነ ክብር ተገባት ። ጌታችን ራሱን ከዓለም ግሳንግስ አንጽቶና በድንግልና ጠብቆ ህዝብን ስለንስሐ ያስተምር የነበረውን ዮሐንስን እንኳን፥ ሴቶች ከወለዱት እንደ ዮሐንስ የለም ብሎ ሲመሰክርለት እመቤታችንንማ ከንጽሕናዋ ከድንግልናዋ ጋር የአምላክ እናት ስለሆነች ከሁሉ በላይ እንዴት በበለጠ አትከብር? አምላክ የርሷን ሥጋ ተዋሕዷል ሰውም በዚህ ሥጋና ደም
ከእግዚአብሔር ጋር ታርቆ የእግዚአብሔር መንግሥትን የሚወርስ ሆኗልና በክርስቶስ ደም ድኛለሁ የሚል የሰው ልጅ ሁሉ ሊያከብራት ይገባል ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት????
❖ @And_Haymanot ❖
አንድ እህታችን በውሥጥ የላከችልን መልዕክት ነው፡፡
ስለ እመቤታችን ሲነሳ የተሃድሶ መናፍቃን ዛሬም ከእናታችን እቅፍ ሊለዩን ተነስተዋል ከጥፋት ትምህርታቸው አንዱ ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት። በዛ ዘመን ብንኖር ከእኛ መሃል ከአንዳችን ኢየሱስ ይወለድ ነበር ብለው ያስተምራሉ ያምናሉ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስን ከመውለድዋ በፊት በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠች ሴት ናት ።
እንኳን የአምላክ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም አይደለም ማንኛችንም እግዚአብሔር የፈጠረን ፍጡር ወደዚህ አለም ከመምጣታችን በፊት ለምን አላማ እንደምንወለድ እንኳን ገና ሳንፈጠር እግዚአብሔር ያውቃል:: ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን ኤርምያስ 1:5 እንዲህ ይላል ።
የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ ከማህፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ ለአህዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ለአምላክ እናት እንድትሆን ገና ሳትፈጠር እግዚአብሔር የመረጣት ሴት ናት። ከእሷም ባይሆን ከሌላ ይወለድ ነበር ለሚሉ የጥፋት ልጆች ከእግዚአብሔር አላማና ሃሳብ ጋር የተጣሉ የእግዚአብሔርን ሃሳብ በራሳቸው አመለካከት እና ሃሳብ ለመቀየር የሚያስቡ ደፋሮች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም
እንዲወለድ ነበር የእግዚአብሔር አላማ::
ከእሷ ባይሆን ለሚሉት የእግዚአብሔር ሀሳብ ሳይሆን የቀረበት ግዜ የለምና ከእሷ ውጭ ከማንም ሊሆን አይችልም። የእግዚአብሔር ሃሳብ ከቅድስት ድንግል ማርያም እንዲወለድ እንጂ ሌሎች እንደሚፈላሰፉት ከአዳራሽ ጨፋሪዎቻቸው ሴቶች መሃከል ኢየሱስ ሊወለድ አይችልም:: ከፍጥረት ሁሉ ፣የአምላክ እናት እንድትሆን የተመረጠች ቅድስት ማርያም ብቻ ናት። ለመዳናችን ምክንያት ለሆነች ከሴቶች ሁሉ ለተለየች የአምላክ እናት ክብር ይገባታል ።
በተጨማሪም ሊታወቅ የሚገባው ማንኛውም ሠው በነብያትና በሐዋርያት መንገድ መጓዝ ከቻለ ሐዋርያት የደረሱበትን የክብር ደረጃ መድረስ ይችላል፡፡ ነገር ግን በክብር ላይ ክብር ብናገኝ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሠኝ ስራ ብንሠራ እንኳ ድንግል ማርያም የደረሰችበት የክብር ደረጃ ላይ መድረስ የሚችል ሰው ማንም የለም፡፡ ወደፊትም እንደዚህ አይነት ክብር እና ጸጋ ለማንም አይሰጥም፡፡፡፡
.....ይቆየን፡፡
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖
ከዋክብት የሚያመሰግኑት
በስማቸውም የሚጠራቸው:
የፀጋው ብዛት የማይታወቅ
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን እንደገለጽክላቸው
ለእኛም ግለጽልን።
አሜን አሜን አሜን!!!
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot_bot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
አንድ እህታችን በውሥጥ የላከችልን መልዕክት ነው፡፡
ስለ እመቤታችን ሲነሳ የተሃድሶ መናፍቃን ዛሬም ከእናታችን እቅፍ ሊለዩን ተነስተዋል ከጥፋት ትምህርታቸው አንዱ ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት። በዛ ዘመን ብንኖር ከእኛ መሃል ከአንዳችን ኢየሱስ ይወለድ ነበር ብለው ያስተምራሉ ያምናሉ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስን ከመውለድዋ በፊት በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠች ሴት ናት ።
እንኳን የአምላክ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም አይደለም ማንኛችንም እግዚአብሔር የፈጠረን ፍጡር ወደዚህ አለም ከመምጣታችን በፊት ለምን አላማ እንደምንወለድ እንኳን ገና ሳንፈጠር እግዚአብሔር ያውቃል:: ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን ኤርምያስ 1:5 እንዲህ ይላል ።
የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ ከማህፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ ለአህዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ለአምላክ እናት እንድትሆን ገና ሳትፈጠር እግዚአብሔር የመረጣት ሴት ናት። ከእሷም ባይሆን ከሌላ ይወለድ ነበር ለሚሉ የጥፋት ልጆች ከእግዚአብሔር አላማና ሃሳብ ጋር የተጣሉ የእግዚአብሔርን ሃሳብ በራሳቸው አመለካከት እና ሃሳብ ለመቀየር የሚያስቡ ደፋሮች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም
እንዲወለድ ነበር የእግዚአብሔር አላማ::
ከእሷ ባይሆን ለሚሉት የእግዚአብሔር ሀሳብ ሳይሆን የቀረበት ግዜ የለምና ከእሷ ውጭ ከማንም ሊሆን አይችልም። የእግዚአብሔር ሃሳብ ከቅድስት ድንግል ማርያም እንዲወለድ እንጂ ሌሎች እንደሚፈላሰፉት ከአዳራሽ ጨፋሪዎቻቸው ሴቶች መሃከል ኢየሱስ ሊወለድ አይችልም:: ከፍጥረት ሁሉ ፣የአምላክ እናት እንድትሆን የተመረጠች ቅድስት ማርያም ብቻ ናት። ለመዳናችን ምክንያት ለሆነች ከሴቶች ሁሉ ለተለየች የአምላክ እናት ክብር ይገባታል ።
በተጨማሪም ሊታወቅ የሚገባው ማንኛውም ሠው በነብያትና በሐዋርያት መንገድ መጓዝ ከቻለ ሐዋርያት የደረሱበትን የክብር ደረጃ መድረስ ይችላል፡፡ ነገር ግን በክብር ላይ ክብር ብናገኝ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሠኝ ስራ ብንሠራ እንኳ ድንግል ማርያም የደረሰችበት የክብር ደረጃ ላይ መድረስ የሚችል ሰው ማንም የለም፡፡ ወደፊትም እንደዚህ አይነት ክብር እና ጸጋ ለማንም አይሰጥም፡፡፡፡
.....ይቆየን፡፡
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖
ከዋክብት የሚያመሰግኑት
በስማቸውም የሚጠራቸው:
የፀጋው ብዛት የማይታወቅ
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን እንደገለጽክላቸው
ለእኛም ግለጽልን።
አሜን አሜን አሜን!!!
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot_bot ❖
‹‹ቤዛ›› ማለት ምን ማለት ነው?
እናታችን ቅድሥት ድንግል ማርያም የአለም ቤዛ ናትን ?
@And_Haymanot
ብዙ ጊዜ ድንግል ማርያም እንዴት የአለም ቤዛ ትሆናለች? ይላሉ፤ በእርግጥ ግን እናታችን ቅድሥት ድንግል ማርያም የአለም ቤዛ ናት ።
‹‹ ቤዛ ›› በቁሙ ሲተረጐም ዋጋ አለው ወይም ጥቅም አለው ማለት ነው ። እንዲሁም ቤዛ የሚለው ቃል "ቤዘወ"፦ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ቤዛ በቁሙ ሲተነተን እንዲህ ማለት ነው ። ዋጋ ፣ ካሳ ፣ ለውጥ ፣ ምትክ፣ሀላፊ ፣ ዋቢ ፣ ዋሥ ፣ መድኅን ፣ ተያዥ ፣ ጥላ ፣ ጋሻ ... ማለትነው ። ቤዛ በደቂቅ አገባብ ሲፈታ ደግሞ ሥለ፣ ፋንታ፣ ምክንያት የሚሆንተብሎም
ይተረጐማል ። አለቃ ኪዳነ ወልደ ክፍሌ መፅሐፍ ሠዋሠው ውግሥ በመዝገበ
ቃላት ሐዲሥ 1948 ዓ ም ገፅ 266፡፡ ወይምደግሞ በሌላ መንገድ ከሣቴ ብርሐን ተሠማ መፅሐፋቸው ቤዛ ሲተረጉሙ እንዲህ ብለው አሥቀምጠውልናል ለውጥ፣ካሣ፣ወይም ደግሞ በአንድ ሠው ላይ መከራና ሞት ተላልፎ መሞትማለት ነው ወይም ታደገኝ ወይም ምትክ ሆነኝ ማለት ነው ወይም ደግሞ ለመከራ ለሞት ለወጠኝ ማለት ነው ወይም ቤዛ ሆነኝ ማለትነው።
የበለጠ ለመረዳት አልያም ቤዛ ሥለሚለው ቃል በደንብ ለማወቅ እነዚህን መፅሐፍቶች መመልከት ይቻላል ። እንደዚሁምቤዛ የሚለው ቃል ፦ ካሣ ፣ የደም ቤዛ ፣ አንዱ ሠው የሠውንደም ሥለሚያፈሠው ለውጥ ወይም ዋጋን ፣ ገንዘብን ፣ ካሣን መሥጠት ወይም መዋጀት ማለት ነው ። ከሣቴ ብርሐን 1951 ዓ.ምገፅ 532
ድንግል ማርያምን ስለምን የአለም ቤዛ እንላታለን? የእመቤታችን ቤዛነትም ከላይ በተረዳነው መሠረት ቤዛ ከሚሉት የትርጓሜ ቃላት መካከል ምትክ፣ ዋሥ፣ምክንያት ... ከሚሉት መካከል ምትክ የሚለውን ስንወስድ
ድንግል ማርያም የህይዋን(ሔዋን) ምትክ በመሆኗ ነው፤ ‹ምክንያት› የሚለውን ስንወስድ ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም ለኛ መዳን ምክንያት ስለሆነች ነው። እግዚአብሔር ለአለም መዳን በድንግል ማርያም ታላቅ ስራን አድርጉአልና ቤዛዊት ዓለም እንላታለን። የድንግል ማርያም በእምነት መታዘዝ ለዓለም መዳን
ምክንያት ሆናለች። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ከስጋዋ ስጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ ዓለምን ስለተቤዤ ቤዛዊት ዓለም እንላታለን። ቤዛ የሚለው ቃል ለሙሴም ተሰጦት እናነባለን። ( የሐዋ ሥራ 7:35) በመልአክ እጅ
እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው። እንግዲህ ይህ የፍጡር ቤዛነት የእግዚአብሔርን ቤዛነት ይሽራልን? አይደለም፡፡ እንዲያውም ቸር እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የሚሰጠውን የባለሟልነት ስጦታ ብዛት ይገልፃል እንጂ፡፡ ሙሴ
ወገኖቹን ከመጥፋት እንደምን አዳናቸው(ተቤዣቸው)(ታደጋቸው)? እንደክርስቶስ ደሙን በማፍሰስ ነውን? አይደለም በእግዚአብሔር ዘንድ ‹ይህን ኀጢአታቸውን
ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን ከጻፍኸው መጽሐፍኽ እባክኽ ደምሰሰኝ›
በማለትየተወደደፀሎቱንበማቅረብእንጂ (ዘጸ.32፤32) ፡፡ ዳዊትም ‹ሙሴ
በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ›› ሲል የገለፀው ይሄንኑ ነው፡፡ስለዚህም
መጽሐፍ የፃድቅሰውፀሎት በስራዋ እጅግ ሃይልን ታደርጋለች ይላል፡፡
የእመቤታችንና የድንግል ማርያም ቤዛነት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርሥቶስ ቤዛነት ጋር ያለው ልዩነትእጅግ የሚራራቅ ነው። ጌታችን በሞቱ የተደረገ ቤዛነት ነው ። እንዲሁም በደሙ ዋጅቶ በሞቱ የተደረገ ቤዛነት ነው። ቤዛ ማለትእራሥን
ሥለሌሎች አሣልፎ መስጠት ማለት ሥለሆነ ጌታችንም ሥለበጐቹ እራሱን አሣልፎ ሠጥቷል ሆኖም የአለም ቤዛ ነው ። ታዲያ የአለምቤዛ ክርስቶስ ከሆነ ድንግል ማርያምስ ቤዛዊት አለም መባሏ ስለምን ነው ቢሉ፦ ክርስቶስ አለምን ሁሉ ከሞት ወደህይወት ያሻገረበት፣ ሃጢአታችንን ሁሉ የደመሰሰበት፣
የሚደመስስበትም ክቡር ደሙ፣ ቅዱስ ስጋው ከእመቤታችን ስለነሳው ነው፤ በዚህም ክርስቶስ ከመወለዱ አንስቶ በቤተልሄም የከብት ግርግም ተጀምሮ፡ በግብፅ ስደቱ በቀራኒዮ ስቃዩና ሞቱ ሁሉ አብራው አለችና በክርስቶስ የድህነት
ስራ ውስጥ የእመቤታችን ስራ ጉልህ ሆኖ ይታያልና ነው፡፡
ለማጠቃል ያክል፡-
ሙሴ ምክንያት ሆኖ ነጻ ያወጣቸው ለጥቂት ነገዶች ወይም ‹ለእስራኤላውያን› ብቻ በመሆኑ‹‹ቤዛ›› ብቻ ተብሏል፡፡ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ግን ምክንያተ ድኅነት ሆና ነጻ ያወጣችው ‹ዓለም ሙሉ› ስለሆነ (ክርስቶስ ለዓለም ሁሉ ተሰቅሏልና) ‹‹ቤዛዊተ ዓለም›› ትባላለች፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን ለቅዱሳንም በጸጋ ተሰጥቷል፤
በመጸሐፍየጸጋ አምላክነት ለቅዱሳን ተሰጥቶ እናያለን ‹እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦እይ፥እኔ ለፈርዖን አምላክ አድርጌኻለኹ›፤ ክርስቶስየዓለም ብርሃን እንደሆነ እንዲሁ ደግሞ ቅዱሳንንም ‹እናንተየዓለም ብርሃን ናችኹ› በማለት በጸጋ የዓለም ብርሃን እንደሚባሉ መጽሐፍ ምስክርነው ( ዘጸ7፤1 ማቴ 5፤14)
የቤተክርስቲያን ትምህርት እንዲህ ነዉ፤ ክብርና ምሥጋና ለቤዛዊት አለም ለእመቤታችን ለቅድሥት ድንግልማርያም ይሁን
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እናታችን ቅድሥት ድንግል ማርያም የአለም ቤዛ ናትን ?
@And_Haymanot
ብዙ ጊዜ ድንግል ማርያም እንዴት የአለም ቤዛ ትሆናለች? ይላሉ፤ በእርግጥ ግን እናታችን ቅድሥት ድንግል ማርያም የአለም ቤዛ ናት ።
‹‹ ቤዛ ›› በቁሙ ሲተረጐም ዋጋ አለው ወይም ጥቅም አለው ማለት ነው ። እንዲሁም ቤዛ የሚለው ቃል "ቤዘወ"፦ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ቤዛ በቁሙ ሲተነተን እንዲህ ማለት ነው ። ዋጋ ፣ ካሳ ፣ ለውጥ ፣ ምትክ፣ሀላፊ ፣ ዋቢ ፣ ዋሥ ፣ መድኅን ፣ ተያዥ ፣ ጥላ ፣ ጋሻ ... ማለትነው ። ቤዛ በደቂቅ አገባብ ሲፈታ ደግሞ ሥለ፣ ፋንታ፣ ምክንያት የሚሆንተብሎም
ይተረጐማል ። አለቃ ኪዳነ ወልደ ክፍሌ መፅሐፍ ሠዋሠው ውግሥ በመዝገበ
ቃላት ሐዲሥ 1948 ዓ ም ገፅ 266፡፡ ወይምደግሞ በሌላ መንገድ ከሣቴ ብርሐን ተሠማ መፅሐፋቸው ቤዛ ሲተረጉሙ እንዲህ ብለው አሥቀምጠውልናል ለውጥ፣ካሣ፣ወይም ደግሞ በአንድ ሠው ላይ መከራና ሞት ተላልፎ መሞትማለት ነው ወይም ታደገኝ ወይም ምትክ ሆነኝ ማለት ነው ወይም ደግሞ ለመከራ ለሞት ለወጠኝ ማለት ነው ወይም ቤዛ ሆነኝ ማለትነው።
የበለጠ ለመረዳት አልያም ቤዛ ሥለሚለው ቃል በደንብ ለማወቅ እነዚህን መፅሐፍቶች መመልከት ይቻላል ። እንደዚሁምቤዛ የሚለው ቃል ፦ ካሣ ፣ የደም ቤዛ ፣ አንዱ ሠው የሠውንደም ሥለሚያፈሠው ለውጥ ወይም ዋጋን ፣ ገንዘብን ፣ ካሣን መሥጠት ወይም መዋጀት ማለት ነው ። ከሣቴ ብርሐን 1951 ዓ.ምገፅ 532
ድንግል ማርያምን ስለምን የአለም ቤዛ እንላታለን? የእመቤታችን ቤዛነትም ከላይ በተረዳነው መሠረት ቤዛ ከሚሉት የትርጓሜ ቃላት መካከል ምትክ፣ ዋሥ፣ምክንያት ... ከሚሉት መካከል ምትክ የሚለውን ስንወስድ
ድንግል ማርያም የህይዋን(ሔዋን) ምትክ በመሆኗ ነው፤ ‹ምክንያት› የሚለውን ስንወስድ ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም ለኛ መዳን ምክንያት ስለሆነች ነው። እግዚአብሔር ለአለም መዳን በድንግል ማርያም ታላቅ ስራን አድርጉአልና ቤዛዊት ዓለም እንላታለን። የድንግል ማርያም በእምነት መታዘዝ ለዓለም መዳን
ምክንያት ሆናለች። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ከስጋዋ ስጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ ዓለምን ስለተቤዤ ቤዛዊት ዓለም እንላታለን። ቤዛ የሚለው ቃል ለሙሴም ተሰጦት እናነባለን። ( የሐዋ ሥራ 7:35) በመልአክ እጅ
እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው። እንግዲህ ይህ የፍጡር ቤዛነት የእግዚአብሔርን ቤዛነት ይሽራልን? አይደለም፡፡ እንዲያውም ቸር እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የሚሰጠውን የባለሟልነት ስጦታ ብዛት ይገልፃል እንጂ፡፡ ሙሴ
ወገኖቹን ከመጥፋት እንደምን አዳናቸው(ተቤዣቸው)(ታደጋቸው)? እንደክርስቶስ ደሙን በማፍሰስ ነውን? አይደለም በእግዚአብሔር ዘንድ ‹ይህን ኀጢአታቸውን
ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን ከጻፍኸው መጽሐፍኽ እባክኽ ደምሰሰኝ›
በማለትየተወደደፀሎቱንበማቅረብእንጂ (ዘጸ.32፤32) ፡፡ ዳዊትም ‹ሙሴ
በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ›› ሲል የገለፀው ይሄንኑ ነው፡፡ስለዚህም
መጽሐፍ የፃድቅሰውፀሎት በስራዋ እጅግ ሃይልን ታደርጋለች ይላል፡፡
የእመቤታችንና የድንግል ማርያም ቤዛነት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርሥቶስ ቤዛነት ጋር ያለው ልዩነትእጅግ የሚራራቅ ነው። ጌታችን በሞቱ የተደረገ ቤዛነት ነው ። እንዲሁም በደሙ ዋጅቶ በሞቱ የተደረገ ቤዛነት ነው። ቤዛ ማለትእራሥን
ሥለሌሎች አሣልፎ መስጠት ማለት ሥለሆነ ጌታችንም ሥለበጐቹ እራሱን አሣልፎ ሠጥቷል ሆኖም የአለም ቤዛ ነው ። ታዲያ የአለምቤዛ ክርስቶስ ከሆነ ድንግል ማርያምስ ቤዛዊት አለም መባሏ ስለምን ነው ቢሉ፦ ክርስቶስ አለምን ሁሉ ከሞት ወደህይወት ያሻገረበት፣ ሃጢአታችንን ሁሉ የደመሰሰበት፣
የሚደመስስበትም ክቡር ደሙ፣ ቅዱስ ስጋው ከእመቤታችን ስለነሳው ነው፤ በዚህም ክርስቶስ ከመወለዱ አንስቶ በቤተልሄም የከብት ግርግም ተጀምሮ፡ በግብፅ ስደቱ በቀራኒዮ ስቃዩና ሞቱ ሁሉ አብራው አለችና በክርስቶስ የድህነት
ስራ ውስጥ የእመቤታችን ስራ ጉልህ ሆኖ ይታያልና ነው፡፡
ለማጠቃል ያክል፡-
ሙሴ ምክንያት ሆኖ ነጻ ያወጣቸው ለጥቂት ነገዶች ወይም ‹ለእስራኤላውያን› ብቻ በመሆኑ‹‹ቤዛ›› ብቻ ተብሏል፡፡ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ግን ምክንያተ ድኅነት ሆና ነጻ ያወጣችው ‹ዓለም ሙሉ› ስለሆነ (ክርስቶስ ለዓለም ሁሉ ተሰቅሏልና) ‹‹ቤዛዊተ ዓለም›› ትባላለች፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን ለቅዱሳንም በጸጋ ተሰጥቷል፤
በመጸሐፍየጸጋ አምላክነት ለቅዱሳን ተሰጥቶ እናያለን ‹እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦እይ፥እኔ ለፈርዖን አምላክ አድርጌኻለኹ›፤ ክርስቶስየዓለም ብርሃን እንደሆነ እንዲሁ ደግሞ ቅዱሳንንም ‹እናንተየዓለም ብርሃን ናችኹ› በማለት በጸጋ የዓለም ብርሃን እንደሚባሉ መጽሐፍ ምስክርነው ( ዘጸ7፤1 ማቴ 5፤14)
የቤተክርስቲያን ትምህርት እንዲህ ነዉ፤ ክብርና ምሥጋና ለቤዛዊት አለም ለእመቤታችን ለቅድሥት ድንግልማርያም ይሁን
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
🙏1
የሚቀጥለው ርእሳችን
የድንግል ማርያምን ዘልአለማዊ ድንግልና እና ከዮሴፍ ሌሎች ልጆችን ወልዳለች(ላቲ ስብሃት) ለሚሉ በሰፊው በክፍላት እንዳስሳለን
------- #Share --------
ሼር በማድረግ በርቱ ብዙ ሼር ሲደረግ ነውና ለብዙዎች መድረሱን(መነበቡን) አውቀን ሌላ ክፍል የምንለቀው። በተጨማሪም የምናነሳው ርእስ ብዙ ጠያቂን እየፈጠረ ነውና ነፍሳትን ማዳን እና ከተሳሳተ መንገድ ለመመለስ እንትጋ!
🙏አምላከ ድንግል ማርያም ይርዳን 🙏
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
የድንግል ማርያምን ዘልአለማዊ ድንግልና እና ከዮሴፍ ሌሎች ልጆችን ወልዳለች(ላቲ ስብሃት) ለሚሉ በሰፊው በክፍላት እንዳስሳለን
------- #Share --------
ሼር በማድረግ በርቱ ብዙ ሼር ሲደረግ ነውና ለብዙዎች መድረሱን(መነበቡን) አውቀን ሌላ ክፍል የምንለቀው። በተጨማሪም የምናነሳው ርእስ ብዙ ጠያቂን እየፈጠረ ነውና ነፍሳትን ማዳን እና ከተሳሳተ መንገድ ለመመለስ እንትጋ!
🙏አምላከ ድንግል ማርያም ይርዳን 🙏
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?
@And_Haymanot
ይህን ትምህርት የምታነቡ ሁሉ በማስተዋል እና በጽሞና ትረዱ ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡ ለዘመናት የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለመቃወም ዲያቢሎስ ያዘመታቸው መናፍቃን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ሁሉ የማያዳግም መልስ በዝርዝር እና በአንድምታ ቀርቧል ፡፡ ከጌታ ውጭ ከቅዱስ ዮሴፍ ልጅወልዳለች ብለው ለተሰናከሉ ሁሉ በዚሁ አጋጣሚ ስለ ዮሴፍ ማንነት ጭምር ትምህርቱ በጥቂቱ ይዳስሳል መልካም ንባብ ፡-
👉 ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ማነው ?
መናፍቃን ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ከዮሴፍ እንደወለደች ሲናገሩ እንሰማለን ማስረጃ ባይኖረውም ፡፡ ነገር ግን የዮሴፍን ማንነት በጥቂቱም ቢሆን መረዳት ለስህተታቸው ማሰታገሻ መድኃኒት ነውና እነሆ ፡- አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ሀገሩ ናዝሬት ሲሆን ሐናፂም ነጋዴም ነበር ፡፡ ዘሩ ከዳዊት ወገን ነው ፡፡ ሦሰት ሴቶች እና አምሥት ወንዶች ልጆች ነበሩት ፡፡ ልጆቹ ገሚሶቹ ከ12ቱ ሐዋርያት ገሚሶቹ ደግሞ ከ72ቱ አርድዕት ውስጥ የነበሩ ሲሆን ከሚስቱ ጋር 52 ዓመት ፤ ሚስቱ ከሞተች በኋላ
ደግሞ 40 ዓመት ኖሯል ፡፡ በድምሩ 92 ዓመት ከኖረ በኋላ ለእመቤታች ጠባቂ ሆኖ ተመረጠ ፡፡ ከእመቤታችን እና ከጌታ ጋር ደግሞ በስደት ፣ በመከራ 22 ዓመታትን አሳልፏል ፡፡ ሊጠብቃትም ሲመረጥ ከ1,985 ሽማግሌዎች
ውስጥ ዕጣ ደርሶት ነው ፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም የከተሰበሰቡት ሁሉ የርሱ በትር ለሦስት ጊዜ ያህ በተደጋጋሚ አብባና ለምልማ ተገኘች ፡፡ አረጋዊ ዮሴፍ በ114 ዓመቱ ሐምሌ 26 ቀን አርፏል ፡፡ ከማረፉ በፊት ግን ጌታችንን ‹‹ ሥጋዬን በዚህ ምድር አታስቀረው ›› ብሎ ለምኖት ነበርና ዛሬም ድረስ ዮሴፍ መቀበሩን እንጂ ቅዱስ ሥጋው የት እንዳለ የሚያውቅ የለም ጌታ ስለ ጸሎቱ (ስለልመናው) ሰውሮታልና ፡፡ ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ለምን ተመረጠ ? *ይህ ጻድቅና ንጹሕ አረጋዊ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን ሊጠብቅ ስለተመረጠበት ምክንያን አስረጋጭ
ማስረጃዎች እነሆ ፡፡
1ኛ) አገልጋይዋ ተላላኪዋ ሆኖ
ሊጠብቃት ፡፡
2ኛ) መከራዋን እንዲጋራ ፡፡ አንድም ዮሴፍ ዘመዷ ነው መከራን ለብቻ አይዘልቁምና በልጇ አማካኝነት የሚደርስባትን ስደት እና መከራ አብሯት እንዲካለፈል ነው ፡፡ ዝምድናቸው ሲዘረዘር የሚከተለውን ሃቅ ያስረዳናል ፡- + ግንዱ ‹‹ አልዓዛር ›› በሁለት
ወገን የሚከተሉትን ወልዷል ፡-
* ማታን = * ቅስራ*
* ያዕቆብ = * ኢያቄም *
* ዮሴፍ = * ድንግል ማርያም
(የነዚህ የዘር ሐረጋት ግንዱ ከላይ እንዳየነው * አልዓዛር * ነው ስለዚህ የዘር ሃረጋቸው አንድ ነውና ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት አይችልም)
3ኛ) ከመደብደብ ሊያድናት ፡፡ በኦሪ.ዘኁ 5፥19 በተጠቀሰው መሠረት አንዲት ሴት ከባልዋ ውጭ ጸንሳ ብትገኝ ማየ ዘለፋ ያጠጥዋት ነበር ፡፡ እንዲሁም አንዲት ሴት ባል ሳታገባ ብትጸንስ በሙሴ ሕግ መሠረት ደብድበው ይገድሉአት ነበር
፡፡ ስለዚህ እመቤታችን ለዮሴፍ ሳትታጭ ቀርታ ቢሆን ለድብደባ ባበቁአት ነበር ፡፡
4ኛ) ትንቢቱ እንዲፈጸም ነው ፡፡ ጌታ ከዳዊት ቤት እና ወገን እንዲወለድ ኢሳ 11፥1 ፣ 10 ላይ ትንቢት ነበር ፡፡ ዮሴፍም የዳዊት ዘር ነውና ክርስቶስ በዮሴፍ የዳዊት ልጅ ተብሎ እንዲቆጠር ነው ፡፡ ምነው በእናቱ የዳዊት ልጅ አይባልምን? ቢባል አይሁድ ሴትን ከትውልድ ቁጥር አግብተው አይቆጥሩምና ነው ፡፡
5ኛ) ኃይለ አርያማዊት (ከሰማይ ወረደች እንጂ ምድራዊት አይደለችም) የሚሉ ወገኖች ነበሩና ምድራዊት መሆኑኗን ለማጠየቅ ነው ፡፡ ሆኖም
ከምድር መገኘቷን ለመግለጽ እንጂ ድንግል ማርያም በክብሯ ሰማያዊት ናት ፡፡ የባሕርያችን መመኪያ መባሏም ከሰው ዘር መገኘቷን ልብ እንዲሉ ነው ፡፡ ስለዚህ ድንግል ማርያም ለዮሴፍ መታጨቷ ስለዚህ እና ይህን ለመሰለ ምክንያት ነው እንጂ ለሚስትነት አልነበረም ፡፡ አንድም ዮሴፍ እመቤታችን ሊጠብቃት በተመረጠ ጊዜ ጀርባው ጎብጦ ፣ ጉልበቱ ዝሎ ፣ ዓይኑ ሞጭሙጮ ነበር 92 ዓመት አልፎት
ነበር አረጋዊ(ሽማግሌ) መባሉም ለዚህ ነው ፡፡ በሆኑም አረጋዊ ዮሴፍ ስለነዚህ ምክንያት ድንግል ማርያም ሊጠብቃት ተመረጠ እንጂ ሊያገባት አይደለም፡፡ ሊያገባት የተመረጠ ቢሆን ኖሮ ድንግል ማርያም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ ‹‹ ወንድ ስለማላውቅ እንዴት ይሆናል ›› ባላለችውም ነበር ፡፡ ሊያበሥራት የተላከው ለዮሴፍ ከታጨች በኋላ ነውና ፡፡ በዚህም ንግግሯ ለዮሴፍ የታጨችው ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት እንዳልሆነ አረጋግጣለች፡፡ ዛሬ የተነሱ መናፍቀን ምሥጢር ይጎድላቸዋልና ዮሴፍን እንደወጣት ሰው ቆጥረው ድንግል ማርያምን ሊያገባ እንደታጨ በደካማ ጎናቸው ያስባሉ እውነቱ ግን ይሄ ነው ፡፡
ይቆየን ....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
❤ ✞_✞_✞ ❤
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
@And_Haymanot
ይህን ትምህርት የምታነቡ ሁሉ በማስተዋል እና በጽሞና ትረዱ ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡ ለዘመናት የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለመቃወም ዲያቢሎስ ያዘመታቸው መናፍቃን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ሁሉ የማያዳግም መልስ በዝርዝር እና በአንድምታ ቀርቧል ፡፡ ከጌታ ውጭ ከቅዱስ ዮሴፍ ልጅወልዳለች ብለው ለተሰናከሉ ሁሉ በዚሁ አጋጣሚ ስለ ዮሴፍ ማንነት ጭምር ትምህርቱ በጥቂቱ ይዳስሳል መልካም ንባብ ፡-
👉 ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ማነው ?
መናፍቃን ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ከዮሴፍ እንደወለደች ሲናገሩ እንሰማለን ማስረጃ ባይኖረውም ፡፡ ነገር ግን የዮሴፍን ማንነት በጥቂቱም ቢሆን መረዳት ለስህተታቸው ማሰታገሻ መድኃኒት ነውና እነሆ ፡- አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ሀገሩ ናዝሬት ሲሆን ሐናፂም ነጋዴም ነበር ፡፡ ዘሩ ከዳዊት ወገን ነው ፡፡ ሦሰት ሴቶች እና አምሥት ወንዶች ልጆች ነበሩት ፡፡ ልጆቹ ገሚሶቹ ከ12ቱ ሐዋርያት ገሚሶቹ ደግሞ ከ72ቱ አርድዕት ውስጥ የነበሩ ሲሆን ከሚስቱ ጋር 52 ዓመት ፤ ሚስቱ ከሞተች በኋላ
ደግሞ 40 ዓመት ኖሯል ፡፡ በድምሩ 92 ዓመት ከኖረ በኋላ ለእመቤታች ጠባቂ ሆኖ ተመረጠ ፡፡ ከእመቤታችን እና ከጌታ ጋር ደግሞ በስደት ፣ በመከራ 22 ዓመታትን አሳልፏል ፡፡ ሊጠብቃትም ሲመረጥ ከ1,985 ሽማግሌዎች
ውስጥ ዕጣ ደርሶት ነው ፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም የከተሰበሰቡት ሁሉ የርሱ በትር ለሦስት ጊዜ ያህ በተደጋጋሚ አብባና ለምልማ ተገኘች ፡፡ አረጋዊ ዮሴፍ በ114 ዓመቱ ሐምሌ 26 ቀን አርፏል ፡፡ ከማረፉ በፊት ግን ጌታችንን ‹‹ ሥጋዬን በዚህ ምድር አታስቀረው ›› ብሎ ለምኖት ነበርና ዛሬም ድረስ ዮሴፍ መቀበሩን እንጂ ቅዱስ ሥጋው የት እንዳለ የሚያውቅ የለም ጌታ ስለ ጸሎቱ (ስለልመናው) ሰውሮታልና ፡፡ ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ለምን ተመረጠ ? *ይህ ጻድቅና ንጹሕ አረጋዊ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን ሊጠብቅ ስለተመረጠበት ምክንያን አስረጋጭ
ማስረጃዎች እነሆ ፡፡
1ኛ) አገልጋይዋ ተላላኪዋ ሆኖ
ሊጠብቃት ፡፡
2ኛ) መከራዋን እንዲጋራ ፡፡ አንድም ዮሴፍ ዘመዷ ነው መከራን ለብቻ አይዘልቁምና በልጇ አማካኝነት የሚደርስባትን ስደት እና መከራ አብሯት እንዲካለፈል ነው ፡፡ ዝምድናቸው ሲዘረዘር የሚከተለውን ሃቅ ያስረዳናል ፡- + ግንዱ ‹‹ አልዓዛር ›› በሁለት
ወገን የሚከተሉትን ወልዷል ፡-
* ማታን = * ቅስራ*
* ያዕቆብ = * ኢያቄም *
* ዮሴፍ = * ድንግል ማርያም
(የነዚህ የዘር ሐረጋት ግንዱ ከላይ እንዳየነው * አልዓዛር * ነው ስለዚህ የዘር ሃረጋቸው አንድ ነውና ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት አይችልም)
3ኛ) ከመደብደብ ሊያድናት ፡፡ በኦሪ.ዘኁ 5፥19 በተጠቀሰው መሠረት አንዲት ሴት ከባልዋ ውጭ ጸንሳ ብትገኝ ማየ ዘለፋ ያጠጥዋት ነበር ፡፡ እንዲሁም አንዲት ሴት ባል ሳታገባ ብትጸንስ በሙሴ ሕግ መሠረት ደብድበው ይገድሉአት ነበር
፡፡ ስለዚህ እመቤታችን ለዮሴፍ ሳትታጭ ቀርታ ቢሆን ለድብደባ ባበቁአት ነበር ፡፡
4ኛ) ትንቢቱ እንዲፈጸም ነው ፡፡ ጌታ ከዳዊት ቤት እና ወገን እንዲወለድ ኢሳ 11፥1 ፣ 10 ላይ ትንቢት ነበር ፡፡ ዮሴፍም የዳዊት ዘር ነውና ክርስቶስ በዮሴፍ የዳዊት ልጅ ተብሎ እንዲቆጠር ነው ፡፡ ምነው በእናቱ የዳዊት ልጅ አይባልምን? ቢባል አይሁድ ሴትን ከትውልድ ቁጥር አግብተው አይቆጥሩምና ነው ፡፡
5ኛ) ኃይለ አርያማዊት (ከሰማይ ወረደች እንጂ ምድራዊት አይደለችም) የሚሉ ወገኖች ነበሩና ምድራዊት መሆኑኗን ለማጠየቅ ነው ፡፡ ሆኖም
ከምድር መገኘቷን ለመግለጽ እንጂ ድንግል ማርያም በክብሯ ሰማያዊት ናት ፡፡ የባሕርያችን መመኪያ መባሏም ከሰው ዘር መገኘቷን ልብ እንዲሉ ነው ፡፡ ስለዚህ ድንግል ማርያም ለዮሴፍ መታጨቷ ስለዚህ እና ይህን ለመሰለ ምክንያት ነው እንጂ ለሚስትነት አልነበረም ፡፡ አንድም ዮሴፍ እመቤታችን ሊጠብቃት በተመረጠ ጊዜ ጀርባው ጎብጦ ፣ ጉልበቱ ዝሎ ፣ ዓይኑ ሞጭሙጮ ነበር 92 ዓመት አልፎት
ነበር አረጋዊ(ሽማግሌ) መባሉም ለዚህ ነው ፡፡ በሆኑም አረጋዊ ዮሴፍ ስለነዚህ ምክንያት ድንግል ማርያም ሊጠብቃት ተመረጠ እንጂ ሊያገባት አይደለም፡፡ ሊያገባት የተመረጠ ቢሆን ኖሮ ድንግል ማርያም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ ‹‹ ወንድ ስለማላውቅ እንዴት ይሆናል ›› ባላለችውም ነበር ፡፡ ሊያበሥራት የተላከው ለዮሴፍ ከታጨች በኋላ ነውና ፡፡ በዚህም ንግግሯ ለዮሴፍ የታጨችው ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት እንዳልሆነ አረጋግጣለች፡፡ ዛሬ የተነሱ መናፍቀን ምሥጢር ይጎድላቸዋልና ዮሴፍን እንደወጣት ሰው ቆጥረው ድንግል ማርያምን ሊያገባ እንደታጨ በደካማ ጎናቸው ያስባሉ እውነቱ ግን ይሄ ነው ፡፡
ይቆየን ....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
❤ ✞_✞_✞ ❤
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
👏1
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?
📕 ክፍል ሁለት
📜 @And_Haymanot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት(ወልዳለች) በማለት ኑፋቄያቸውን ለሚዘሩ የተሃድሶዎ መናፍቃን በተከታታይ በዚህ ርእሥ የቤተክርስቲያናችንን ምላሽ ማቅረባችንን ቀጥለናል
@Konobyos
✍‹‹‹ የእጮኛ ትርጉም ›››
እጮኛ የሚለው ቃል ጠባቂ ማለት ነው፡፡ ሌላ ከሰው ልብ የፈለቀ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም፡፡ 👉ለምሳሌ ‹‹እናንተን ለዘለዓለም ለእኔ እንድትሆኑ አጭቻችኋለሁ ›› ሆሴ 2፥21 ማለት ለጋብቻ ነውን? ያሳዝናል አጣመው ለተረጎሙት፡፡ 👉አሁንም ሐዋርያው ከጌታችን ጋር ስላዋሐዳቸው ‹‹ ለእርሱ አጭቻችኋለሁ›› 2ኛ ቆሮ 11፥3 ማለቱን እናስተውል፡፡
👉እንደገናም ምእመናንን የከበረች ማደርያው ስላደረጋቸው ‹‹ለሰማያዊው ክብር አጭቻችኋለሁ ›› ኤፌ 5፥26 ታዲያ እንዲህ ሲል ላጋባችሁ ነው ማለት ይሆን(ሎቱ ስብሐት) ፡፡
እመቤታችን ንግሥተ ሰማይ ወምድር ነችና በ15 ዓመቷ መለኮት ተዋሐዳት ፡፡ ሲዋሐዳትም ለዮሴፍ ታጨች ሉቃ1፥26፡፡ እንግዲህ እጮኛ ማለት ትርጉሙን ያላወቁ ይወቁ እንላለን ፡፡ ነገር ግን ሰው በራሱ ፍቃድ አይተርጉም !!! ሌላው እጅግ የሚደንቀው ነገር ደግሞ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከመውለዷ በፊት እንጂ ከወለደች በኋላ ዮሴፍ ‹‹ እጮኛ›› ተብሎ በአንድም ስፍራ አለመጠቀሱ ነው
👉ማስረጃ ‹‹ ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ ›› ማቴ 2፥3 እንዲሁም በግብጽ 3 ዓመት ከ3ወር በስደት ከቆዩ በኋላ ይህንኑ ቃል ለዮሴፍ በህልም ተነግሮት ‹‹ ሕጻኑን የሚፈልጉት ሞተዋልና ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ናዝሬት ተመለስ ›› አለው እንጂ እጮኛህን (ሚስትህን) ይዘህ
ተመለስ አላለውም ማቴ 2፥20፡፡
✍‹‹‹ የበኩር ትርጉም ›››
የበኩር ልጇን ወለደች የሚለው ቃል ብዙዎችን አሳስቷል ፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው በተለምዶ የበኩር ልጅ የሚባሉ የግድ ተከታይ ያላቸው መሆን አለባቸው የሚል አስተሳሰብ በመናፍቃን ክፉ ልቦና ስለሰረጸነው፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የሚባል ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ጋር አይሰራምና እንዲህ ይታረማል
👉፡- ‹‹ እግዚአብሔር ሙሴን ከእስራኤል ልጆች ዘንድ ከሰውም ከእንስሳትም ማኅጸንን የሚከፍት በኩር ሁሉ ለእኔ ቀድስልኝ አለው ›› ዘጸ 13፥1-2 ይህ ቃል እንደሚገልጸው በኩር የሚባሉት ለመጀመርያ ጊዜ ከእናታቸው ማኅጸን የሚወጡ መሆናቸውን እንጂ ግዴታ ተከታይ ሊኖራቸው እንደማይገባ ያረጋግጣል ፡፡ አንድም ብቻ ቢሆን የእናቱም ማኅጸን ለመጀመርያ ጊዜ ከፍቶ ከወጣ ተከታይም ባይኖረው በኩር ነው ፡፡ ይሄ የበኩር ትርጉም ካልገባን ወደ ሌላ ፤ ይልቁን ወደ ማንወጣው አዘቅት መዘፈቃችን አይቀሬ ነው ፡፡
👉ለምሳሌ ቆላስየስ 1፥7 ላይ ስለ ክርስቶስ ሲናገር ‹‹ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኩር ነው ›› ይላል እዚህ ጋር በኩር የሚለው ቃል ተወዳዳሪ ላላቸው ነገሮች የሚጠቀስ ሆኖ ከቀረበ ጌታን ፍጡር አድርጎ ከፍጡራን ጋር አነጻጽሮ እርሱ ከፍጥረታት በፊት ቀደም ብሎ የተፈጠረ ፍጡር ነው እንደማለት ይሆናልና(ሎቱ ስብሐት)፡፡
እንደገናም በኩር የሚለውን ቃል በሥጋዊ ደማዊ ሃሳብ ከተረጎምነው ዕብ 1፥6 ላይ 👉‹‹በኩርን ወደ ዓለም ሲያገባ ›› የሚል ቃል አለ እዚህ ላይ የክርስቶስ በኩር ተብሎ መጠራት አብ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የባሕርይ ልጁን ወደ መሬት ሂድ ፣ ውረድ ተወለድ ፣ ሙት ተሰቀል ብሎ እንደላከው ለመግለጽ ነው ፡፡ ታድያ አብ በኩርን ወደ ዓለም ሲልክ በኩር የሚለው ቃል ተጠቅሷልና አብም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ አለው ማለት ነውን? እናንት ግብዞች መናፍቃን የመጽሐፍን ቃል በግርድፍ መረዳት ምን ያህል እንደሚያስት ይረዱ ድንግል ማርያምን የነኩ እየመሰላቸው ባለቤቱን መንቀፋቸው ያሳፍራል !!!
እርሷስ ክብር ይግባትና በተቃዋሚዎች አፍ አትረክስም እርሱ ባለቤቱ አንዴ አክብሯታልና ፡፡ ‹‹ የበኩር ልጇን ወለደች›› መባሉ መጀመርያና መጨረሻ የሌለውን አምላከ አዶናይ ፣ ልዑለ ባሕርይን ወለደች ማለቱ ነው፡፡
ይቀጥላል
📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@Konobyos
Join
@And_Haymanot
Join
@And_Haymanot
ለሌሎች ሼር በማድረግ ኑፋቄያቸውን አብረን እንዋጋ
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡ ♥️
📕 ክፍል ሁለት
📜 @And_Haymanot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት(ወልዳለች) በማለት ኑፋቄያቸውን ለሚዘሩ የተሃድሶዎ መናፍቃን በተከታታይ በዚህ ርእሥ የቤተክርስቲያናችንን ምላሽ ማቅረባችንን ቀጥለናል
@Konobyos
✍‹‹‹ የእጮኛ ትርጉም ›››
እጮኛ የሚለው ቃል ጠባቂ ማለት ነው፡፡ ሌላ ከሰው ልብ የፈለቀ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም፡፡ 👉ለምሳሌ ‹‹እናንተን ለዘለዓለም ለእኔ እንድትሆኑ አጭቻችኋለሁ ›› ሆሴ 2፥21 ማለት ለጋብቻ ነውን? ያሳዝናል አጣመው ለተረጎሙት፡፡ 👉አሁንም ሐዋርያው ከጌታችን ጋር ስላዋሐዳቸው ‹‹ ለእርሱ አጭቻችኋለሁ›› 2ኛ ቆሮ 11፥3 ማለቱን እናስተውል፡፡
👉እንደገናም ምእመናንን የከበረች ማደርያው ስላደረጋቸው ‹‹ለሰማያዊው ክብር አጭቻችኋለሁ ›› ኤፌ 5፥26 ታዲያ እንዲህ ሲል ላጋባችሁ ነው ማለት ይሆን(ሎቱ ስብሐት) ፡፡
እመቤታችን ንግሥተ ሰማይ ወምድር ነችና በ15 ዓመቷ መለኮት ተዋሐዳት ፡፡ ሲዋሐዳትም ለዮሴፍ ታጨች ሉቃ1፥26፡፡ እንግዲህ እጮኛ ማለት ትርጉሙን ያላወቁ ይወቁ እንላለን ፡፡ ነገር ግን ሰው በራሱ ፍቃድ አይተርጉም !!! ሌላው እጅግ የሚደንቀው ነገር ደግሞ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከመውለዷ በፊት እንጂ ከወለደች በኋላ ዮሴፍ ‹‹ እጮኛ›› ተብሎ በአንድም ስፍራ አለመጠቀሱ ነው
👉ማስረጃ ‹‹ ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ ›› ማቴ 2፥3 እንዲሁም በግብጽ 3 ዓመት ከ3ወር በስደት ከቆዩ በኋላ ይህንኑ ቃል ለዮሴፍ በህልም ተነግሮት ‹‹ ሕጻኑን የሚፈልጉት ሞተዋልና ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ናዝሬት ተመለስ ›› አለው እንጂ እጮኛህን (ሚስትህን) ይዘህ
ተመለስ አላለውም ማቴ 2፥20፡፡
✍‹‹‹ የበኩር ትርጉም ›››
የበኩር ልጇን ወለደች የሚለው ቃል ብዙዎችን አሳስቷል ፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው በተለምዶ የበኩር ልጅ የሚባሉ የግድ ተከታይ ያላቸው መሆን አለባቸው የሚል አስተሳሰብ በመናፍቃን ክፉ ልቦና ስለሰረጸነው፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የሚባል ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ጋር አይሰራምና እንዲህ ይታረማል
👉፡- ‹‹ እግዚአብሔር ሙሴን ከእስራኤል ልጆች ዘንድ ከሰውም ከእንስሳትም ማኅጸንን የሚከፍት በኩር ሁሉ ለእኔ ቀድስልኝ አለው ›› ዘጸ 13፥1-2 ይህ ቃል እንደሚገልጸው በኩር የሚባሉት ለመጀመርያ ጊዜ ከእናታቸው ማኅጸን የሚወጡ መሆናቸውን እንጂ ግዴታ ተከታይ ሊኖራቸው እንደማይገባ ያረጋግጣል ፡፡ አንድም ብቻ ቢሆን የእናቱም ማኅጸን ለመጀመርያ ጊዜ ከፍቶ ከወጣ ተከታይም ባይኖረው በኩር ነው ፡፡ ይሄ የበኩር ትርጉም ካልገባን ወደ ሌላ ፤ ይልቁን ወደ ማንወጣው አዘቅት መዘፈቃችን አይቀሬ ነው ፡፡
👉ለምሳሌ ቆላስየስ 1፥7 ላይ ስለ ክርስቶስ ሲናገር ‹‹ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኩር ነው ›› ይላል እዚህ ጋር በኩር የሚለው ቃል ተወዳዳሪ ላላቸው ነገሮች የሚጠቀስ ሆኖ ከቀረበ ጌታን ፍጡር አድርጎ ከፍጡራን ጋር አነጻጽሮ እርሱ ከፍጥረታት በፊት ቀደም ብሎ የተፈጠረ ፍጡር ነው እንደማለት ይሆናልና(ሎቱ ስብሐት)፡፡
እንደገናም በኩር የሚለውን ቃል በሥጋዊ ደማዊ ሃሳብ ከተረጎምነው ዕብ 1፥6 ላይ 👉‹‹በኩርን ወደ ዓለም ሲያገባ ›› የሚል ቃል አለ እዚህ ላይ የክርስቶስ በኩር ተብሎ መጠራት አብ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የባሕርይ ልጁን ወደ መሬት ሂድ ፣ ውረድ ተወለድ ፣ ሙት ተሰቀል ብሎ እንደላከው ለመግለጽ ነው ፡፡ ታድያ አብ በኩርን ወደ ዓለም ሲልክ በኩር የሚለው ቃል ተጠቅሷልና አብም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ አለው ማለት ነውን? እናንት ግብዞች መናፍቃን የመጽሐፍን ቃል በግርድፍ መረዳት ምን ያህል እንደሚያስት ይረዱ ድንግል ማርያምን የነኩ እየመሰላቸው ባለቤቱን መንቀፋቸው ያሳፍራል !!!
እርሷስ ክብር ይግባትና በተቃዋሚዎች አፍ አትረክስም እርሱ ባለቤቱ አንዴ አክብሯታልና ፡፡ ‹‹ የበኩር ልጇን ወለደች›› መባሉ መጀመርያና መጨረሻ የሌለውን አምላከ አዶናይ ፣ ልዑለ ባሕርይን ወለደች ማለቱ ነው፡፡
ይቀጥላል
📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@Konobyos
Join
@And_Haymanot
Join
@And_Haymanot
ለሌሎች ሼር በማድረግ ኑፋቄያቸውን አብረን እንዋጋ
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡ ♥️
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
❖ መልካም አዲስ አመት አትበሉን!!!!!!!
@And_Haymanot
የ ፳፻፲፩ (2011) ዓ.ም የመልካም ምኞት መግለጫ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያዎች 'መልካም አዲስ አመት' ሲሉ "መልካም አዲስ ገረድ' ማለታቸው መሆኑን ያውቃሉ......
♦ "አመት" ተብሎ በአልፋው "አ" ሲጻፍ ሴት አገልጋይ ገረድን ይገልጻል። ለምሳሌ፦ "ተፈሥሒ ኦ አመት ወእም ድንግል ወሰማይ ሰማያዌ..." /ውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ/ ሲል ገረድ(ሴት አገልጋይ) ና እናት፤ ድንግልና ሰማይ ሆይ ደስ ይበልሽ ማለት ነው።
♦ "ዓመት" ሲሆን ዘመን ይሆናል። "...ርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ።..."/መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ፤ ለሥእርተ ርእስከ(ለራስ ጸጉርህ)/ ሲል ደግሞ "የመጥቅዕና የአበቅቴ መጀመሪያ ርእሰ ዓመት ዮሐንስ ሆይ..." ማለት ነው።
✍ አመት የሚለው በብዙ ቁጥር አእማት ይሆናል። በዕብራይስጥ አማህ፤ በሱሪስት አምታ፤ በዐረብኛ ደግሞ አመት ይለዋል። ትርጓሜውም ሴት ባሪያ፤ ገረድ፤ ደንገጥር ማለት ነው። "...በወፍጮ እግር እስካለችው እስከ ባሪያይቱ..." ዘፀ.11፥5 የሚለውን ግዕዙ "አመት እንተ ትነብር ዲበ ማሕረጽ።" ይለዋል። በዚህ አገባብ አማርኛው "ባሪያይቱ" የሚለውን ግዕዙ "አመት" ይላታል።
✔ ወንዶች ባሪያዎችን "አግብርት" ሲላቸው ሴቶች ባሪያዎችን ደግሞ "አእማት" ይላቸዋል። [ዘፍ.32፥5 ግዕዙን ንባብ ተመልከት]
♦ ዓመት የሚለው ደግሞ በብዙ ቁጥር "ዓመታት" ሲባል ዘመን፥ ዘመናት፥ ብዙ ቀን፥ የዕለታት ድምር ማለት ነው። "በባቢሎን ንጉሥ በብልጣሶር በመጀመሪያው ዓመት" ዳን.7፥1 የሚለውን ግዕዙ "በቀዳሚ ዓመተ መንግሥቱ።" ይለዋል። "የዕድሜህም ቁጥር ብዙ ነውና፥" ኢዮ.38፥21 የሚለውን ግዕዙ "ኊልቆ ዓመታቲከ፥" ይለዋል።
✍ ስለሆነም አንድ ሰው 'እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሰን' ሲል 'እንኳን ለአዲሷ ገረድ አደረሰን' አለ ማለት ነው። ይኼ ደሞ ጸያፍ ነው።
♦ "እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን" ሲል "እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሰን ማለቱ ነው። ይኸውም የተገባ ነው።
✔ መልካም ምኞታችሁን የገለጻችሁ መስሏችሁ 'መልካም አዲስ አመት' አትበሉን!!!!!
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የ ፳፻፲፩ (2011) ዓ.ም የመልካም ምኞት መግለጫ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያዎች 'መልካም አዲስ አመት' ሲሉ "መልካም አዲስ ገረድ' ማለታቸው መሆኑን ያውቃሉ......
♦ "አመት" ተብሎ በአልፋው "አ" ሲጻፍ ሴት አገልጋይ ገረድን ይገልጻል። ለምሳሌ፦ "ተፈሥሒ ኦ አመት ወእም ድንግል ወሰማይ ሰማያዌ..." /ውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ/ ሲል ገረድ(ሴት አገልጋይ) ና እናት፤ ድንግልና ሰማይ ሆይ ደስ ይበልሽ ማለት ነው።
♦ "ዓመት" ሲሆን ዘመን ይሆናል። "...ርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ።..."/መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ፤ ለሥእርተ ርእስከ(ለራስ ጸጉርህ)/ ሲል ደግሞ "የመጥቅዕና የአበቅቴ መጀመሪያ ርእሰ ዓመት ዮሐንስ ሆይ..." ማለት ነው።
✍ አመት የሚለው በብዙ ቁጥር አእማት ይሆናል። በዕብራይስጥ አማህ፤ በሱሪስት አምታ፤ በዐረብኛ ደግሞ አመት ይለዋል። ትርጓሜውም ሴት ባሪያ፤ ገረድ፤ ደንገጥር ማለት ነው። "...በወፍጮ እግር እስካለችው እስከ ባሪያይቱ..." ዘፀ.11፥5 የሚለውን ግዕዙ "አመት እንተ ትነብር ዲበ ማሕረጽ።" ይለዋል። በዚህ አገባብ አማርኛው "ባሪያይቱ" የሚለውን ግዕዙ "አመት" ይላታል።
✔ ወንዶች ባሪያዎችን "አግብርት" ሲላቸው ሴቶች ባሪያዎችን ደግሞ "አእማት" ይላቸዋል። [ዘፍ.32፥5 ግዕዙን ንባብ ተመልከት]
♦ ዓመት የሚለው ደግሞ በብዙ ቁጥር "ዓመታት" ሲባል ዘመን፥ ዘመናት፥ ብዙ ቀን፥ የዕለታት ድምር ማለት ነው። "በባቢሎን ንጉሥ በብልጣሶር በመጀመሪያው ዓመት" ዳን.7፥1 የሚለውን ግዕዙ "በቀዳሚ ዓመተ መንግሥቱ።" ይለዋል። "የዕድሜህም ቁጥር ብዙ ነውና፥" ኢዮ.38፥21 የሚለውን ግዕዙ "ኊልቆ ዓመታቲከ፥" ይለዋል።
✍ ስለሆነም አንድ ሰው 'እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሰን' ሲል 'እንኳን ለአዲሷ ገረድ አደረሰን' አለ ማለት ነው። ይኼ ደሞ ጸያፍ ነው።
♦ "እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን" ሲል "እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሰን ማለቱ ነው። ይኸውም የተገባ ነው።
✔ መልካም ምኞታችሁን የገለጻችሁ መስሏችሁ 'መልካም አዲስ አመት' አትበሉን!!!!!
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?
📕 ክፍል ሶስት
📜 @And_Haymanot
ተወዳጆች በዚህ ርዕስ ተከታታይ ምላሽ በመዳሰስ ላይ ነን በመሆኑም ሌሎችን ልንገፋበት ወይም ልንተች ያቀረብነው ሳይሆን የጠፋችሁ እህት ወንድሞቼ በማስተዋል እንድትጓዙ ብሎም እንድትነቁም ጭምር ነው፡፡
የማርያም ልጅ ይርዳን
@And_Haymanot
‹‹‹ የ-እስከ-ትርጉም ›››
ሥጋውያኑ ‹‹ እስከን ›› ተገን አድርገው ‹‹ እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም ›› የሚለውን ቃል ፍጻሜ ላለው ነገር በማስገባት ደግመው ደጋግመው ተሰናክለውበታል፡፡ ትርጉሙ(ፍቺው) ግን ይህ አይደለም ፡፡
ለምሳሌ ፡-
👉 1ኛ) የሣኦል ልጅ ሜልኮል ‹‹እስከሞተችበት ›› ቀን ድረስ ልጅ አልወለደችም 2ኛ ሳሙ6፥23 ፡፡ ይህም ማለት እስከመጨረሻው ልጅ አልወለደችም ማለት እንጂ ከሞተች በኋላ ወለደች ለማለት አለመሆኑ የታወቀ ነው ፡፡
👉 2ኛ) ይህም ነገር በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ጆሮ ተሰማ ‹‹ እስከሞቱ›› ድረስ ይህ በደል በእውነት አየሰረይላቸውም ኢሳ 22፥14 ታዲያ የዚህ ትርጉም ከሞቱ በኋላ ይሰረይላቸዋል ማለት ነውን? እስከዘለዓለም አይሰረይላቸውም ለማለት እንጂ፡፡
👉 3ኛ) ከአዳም ጀምሮ ‹‹ እስከሙሴ ›› ድረስ ሞት ነገሠ ሮሜ 5፥14 ታድያ ከሙሴ በኋላ ሞት ቀረ ማለት ነውን?
👉 4ኛ) እግዚአብሐየር ጌታዬን ጠላቶችህ ለእግርህ መረገጫ ‹‹ እስካደርግልህ ›› ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው መዝ101፥1 ታዲያ ጌታችን ጠላቶቹን (አይሁደን) በሥልጣኑ ከረታ በኋላ በአብ ቀኝ መቀመጡ ቀረ ማለት ነው?
👉 5ኛ) እነሆም እኔ ‹‹ እስከ ዓለም ፍጻሜ ›› ድረስ ከእናተ ጋር ነኝ ማቴ28፥20 ከዓለም ፍጻሜ በኋላ ከእናንተ ጋር አይደለሀም ማለት ነውን ?
👉 6ኛ) ቁራውንም ሰደደው እርሱም ወጣ ውሃውም ከምድር ‹‹ እስከሚደርቅ ›› ድረስ ወዲያና ወዲህ ይል ነበር ዘፍ 8፥7 ሲል ውሃው ከደረቀ በኋላ ወዲያና ወዲህ ማለቱን ተወ ማለት ነውን? እንግዲህ ከላይ በተዘረዘረው የእስከ ትርጉም መሠረት በማቴ1፥25 የተጠቀሰው ፍጻሜ የሌለው ‹‹ እስከ ›› መሆኑን ያስረዳል ስለዚህ ዮሴፍ እመቤታችንን እስከ ፍጻሜው ድረስ በግብር አላወቃትም ነበር ማለትነው፡፡ ከዚህ ውጭ በራሱ ፍቃድ የሚረተጉም ሁሉ የረተገመ ይሁን!!!
‹‹‹ የወንድሞች ትርጉም ›››
አዲስ ኪዳን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ጌታችንን ‹‹ ወንድሞቹ ›› እንደሆኑ ከሐዋርያት ወገን የሚጠቅሳቸው አሉ ፡፡ ይህን በመያዝ ብዙ ጥራዝ ነጠቅ አንባቢያን (መናፍቃን) ጌታ ወንድሞች እንዳሉት እና ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ልጅ እንዳላት በማውራት አነስተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀታቸውን ለማንጸባረቅ ይሞክራሉ ፡፡ ነገር ግን ማንም የራሱን ግላዊ ሃሳብ ከማንጸባረቁ በፊት የመጽሐፍ ቅዱስን የአጻጻፍ ዘይቤ መረዳት ያስፈልገዋል እንላለን ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ
👉 1ኛ) በምን ቋንቋ እንደተጻፈ ፣
👉 2ኛ) በማን ባሕልና ዘይቤ እንደተጻፈ ፣
👉 3ኛ) በየትኛው ዘመን እንደተጻፈ አስቀድሞ ማወቅ ለማነበብና ለመረዳት ያስችላል ምክንያቱም ሃይማኖት መሠረታዊ ጉዳይ ነውና !!! መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት ከ40 በላይ ቅዱሳን ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ አብዛኛዎቹ ዕብራውያን ናቸው፡፡ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ ለመረዳት የዕብራውያንን ባሕል በከፊልም ቢሆን መረዳት ያስፈልጋል ፡፡ ስለዚህም
በዕብራውያን ባሕል ፡-
👉 1ኛ) አብሮ አደግና ዘመዶችን በሥጋ እንኳ ከአንድ እናትና አባት ባይወለዱም ‹‹ ወንድም ›› ይባላሉ ዘፍ 13፥11
👉2ኛ) በሃይማኖት የሚመሳሰሉም ‹‹ወንድሞች ›› ይባላሉ ገላ4፥1 ‹‹ ወንድሞቼ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ››
👉3ኛ) በሕብረት በአንድ (ማህበር) የሚቀመጡ ‹‹ ወንድሞች ›› ይባላሉ ‹‹ ወንድሞች በሕብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው እነሆም ያማረ ነው›› መዝ 133፥1፡፡
በተጨማሪም ሐዋርያት እርስ በርስ ‹‹ ወንድሞች ›› ይባባሉ ነበር ፡፡ ከዚህ በመነሳት ለጌታ ‹‹ ወንድሞቹ ›› ተደርገው የተጠቀሱት ሦስቱ ሐዋርያት በሥጋ የተወለዱ አይደሉም፡፡ ድንግል ማርያምም ከጌታ ውጭ ምንም ዓይነት
ልጅ የላትም !!! ልጅ ብቻም ሳይሆን ልጅ
የመውለድ ሃሳብም የላትም አልነበራትምም !!! በተጨማሪም ወንድሞቹ ተብለው የተጠቀሱት ‹‹ያዕቆብ ›› እና ‹‹ ይሁዳ ›› መልዕክቶቻቸውን ሲጽፉ ‹‹ የጌታ ባሪያ›› እያሉ ጻፉ እንጂ ‹‹ የጌታ ወንድሞች ›› ነን ብለው አልጻፉም
ማስረጃ ፡- የያዕቆብ መልእክት 1፥1 ‹‹የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ››
የይሁዳመልእክት 1፥1 ‹‹ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ የያዕቆብም ወንድም የሆነ ይሁዳ ›› ስለዚህ እነዚህ ሐዋርያት ዮሴፍ ከሟች ሚስቶቹ የወለዳቸውና አብረውት ያደጉ እንጂ ከድንግል ማርያም የተወለዱ አይደሉም ፡፡ ‹‹‹እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም የሚለው ትርጉም ›››
ይህን ቃል በመጥቀስ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከወለደች በኋላ ዮሴፍ በግብር አውቋታል የሚሉ መናፍቃን አሉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከወለደች በኋላ ልጅ ወልዳለች የሚል ቃል አልተጻፈም እንጂ !!! ይህን ቃል መነሻ አድርጎ ለመጀመርያ ጌዜ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን የጠየቀው በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ንጉሥ አርቃድዮስ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አምሥት ነገሮችን ግልጽ አድርጎለታል ፡፡ አርቃድዮስም መልሱን በሚገባ አምኗል ተረድቷል ፡፡ ዛሬም ጥያቄውን በድርቅና ሳይሆን ልክ እንደ አርቃድዮስ በየዋህነት ለጠየቀ ሁሉ መልስ የማያስፈልገው ጥያቄ ነው ፡፡ ሆኖም
ለዚህ ስህተታቸው መልስ መስጠቱ ተገቢ ነውና
አነሆ ፡- ‹‹ የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን አላወቃትም ›› ማለት ፡- ዮሴፍ ድንግል ማርያም ጌታን እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ማን እንደሆነች አላወቃትም(ማንነቷን) አልተረዳም ነበር ለማለት ነው ፡፡ ኋላ ግን ጌታን በወለደች ጊዜ በቤተልሔም እረኞች(ኖሎት) እና መላእክት በአንድነት ሲዘምሩ ፣ የሩቅ ምሥራቅ ነገሥታት(ሰብዓ ሰገል) እጅ መንሻ ይዘው መጥተው ሲሰግዱለት ፣ እንዲሁም ቤተልሔም ላይ የብርሃን ድንኳን ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ሲመለከት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት መሆኗን አወቀ (ተረዳ) እስከዚያች ቀን ድረስ ግን ማለትም ጌታን እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ዮሴፍ ድንግል ማርያም የአምላክ
እናት መሆኗን አላወቀም ፣ አልተረዳም ነበር ለማለት ነው ፡፡
አወቀ ማለት በግብር ተገናኘ ማለት አይደለም !!! እንዲህ ከታሰበ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ የሚል ቃል አለ ፡-‹‹ ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጦ ሳለ እንጀራውን አንሥቶ ባረከው፥ ቈርሶም ሰጣቸው፤ ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም››ሉቃ 24፥30-31 ይህም ማለት ጌታችን መሆኑን አወቁ (ተረዱ) ከማለት ውጪ ሌላ ምን ዓይነት ትርጉም ሊኖረው ይችላል ??? (ማዕዱን ቆርሶ እስከሚሰጣቸው ድረስ ግን ጌታን አላወቁትም ነበር)ስለዚህ ማወቅ ማለት መረዳት እንጂ የግድ በግብር መገናኘት ዓይደለም !!
ይቆየን.....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
❤ ✞_✞_✞ ❤
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
📕 ክፍል ሶስት
📜 @And_Haymanot
ተወዳጆች በዚህ ርዕስ ተከታታይ ምላሽ በመዳሰስ ላይ ነን በመሆኑም ሌሎችን ልንገፋበት ወይም ልንተች ያቀረብነው ሳይሆን የጠፋችሁ እህት ወንድሞቼ በማስተዋል እንድትጓዙ ብሎም እንድትነቁም ጭምር ነው፡፡
የማርያም ልጅ ይርዳን
@And_Haymanot
‹‹‹ የ-እስከ-ትርጉም ›››
ሥጋውያኑ ‹‹ እስከን ›› ተገን አድርገው ‹‹ እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም ›› የሚለውን ቃል ፍጻሜ ላለው ነገር በማስገባት ደግመው ደጋግመው ተሰናክለውበታል፡፡ ትርጉሙ(ፍቺው) ግን ይህ አይደለም ፡፡
ለምሳሌ ፡-
👉 1ኛ) የሣኦል ልጅ ሜልኮል ‹‹እስከሞተችበት ›› ቀን ድረስ ልጅ አልወለደችም 2ኛ ሳሙ6፥23 ፡፡ ይህም ማለት እስከመጨረሻው ልጅ አልወለደችም ማለት እንጂ ከሞተች በኋላ ወለደች ለማለት አለመሆኑ የታወቀ ነው ፡፡
👉 2ኛ) ይህም ነገር በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ጆሮ ተሰማ ‹‹ እስከሞቱ›› ድረስ ይህ በደል በእውነት አየሰረይላቸውም ኢሳ 22፥14 ታዲያ የዚህ ትርጉም ከሞቱ በኋላ ይሰረይላቸዋል ማለት ነውን? እስከዘለዓለም አይሰረይላቸውም ለማለት እንጂ፡፡
👉 3ኛ) ከአዳም ጀምሮ ‹‹ እስከሙሴ ›› ድረስ ሞት ነገሠ ሮሜ 5፥14 ታድያ ከሙሴ በኋላ ሞት ቀረ ማለት ነውን?
👉 4ኛ) እግዚአብሐየር ጌታዬን ጠላቶችህ ለእግርህ መረገጫ ‹‹ እስካደርግልህ ›› ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው መዝ101፥1 ታዲያ ጌታችን ጠላቶቹን (አይሁደን) በሥልጣኑ ከረታ በኋላ በአብ ቀኝ መቀመጡ ቀረ ማለት ነው?
👉 5ኛ) እነሆም እኔ ‹‹ እስከ ዓለም ፍጻሜ ›› ድረስ ከእናተ ጋር ነኝ ማቴ28፥20 ከዓለም ፍጻሜ በኋላ ከእናንተ ጋር አይደለሀም ማለት ነውን ?
👉 6ኛ) ቁራውንም ሰደደው እርሱም ወጣ ውሃውም ከምድር ‹‹ እስከሚደርቅ ›› ድረስ ወዲያና ወዲህ ይል ነበር ዘፍ 8፥7 ሲል ውሃው ከደረቀ በኋላ ወዲያና ወዲህ ማለቱን ተወ ማለት ነውን? እንግዲህ ከላይ በተዘረዘረው የእስከ ትርጉም መሠረት በማቴ1፥25 የተጠቀሰው ፍጻሜ የሌለው ‹‹ እስከ ›› መሆኑን ያስረዳል ስለዚህ ዮሴፍ እመቤታችንን እስከ ፍጻሜው ድረስ በግብር አላወቃትም ነበር ማለትነው፡፡ ከዚህ ውጭ በራሱ ፍቃድ የሚረተጉም ሁሉ የረተገመ ይሁን!!!
‹‹‹ የወንድሞች ትርጉም ›››
አዲስ ኪዳን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ጌታችንን ‹‹ ወንድሞቹ ›› እንደሆኑ ከሐዋርያት ወገን የሚጠቅሳቸው አሉ ፡፡ ይህን በመያዝ ብዙ ጥራዝ ነጠቅ አንባቢያን (መናፍቃን) ጌታ ወንድሞች እንዳሉት እና ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ልጅ እንዳላት በማውራት አነስተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀታቸውን ለማንጸባረቅ ይሞክራሉ ፡፡ ነገር ግን ማንም የራሱን ግላዊ ሃሳብ ከማንጸባረቁ በፊት የመጽሐፍ ቅዱስን የአጻጻፍ ዘይቤ መረዳት ያስፈልገዋል እንላለን ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ
👉 1ኛ) በምን ቋንቋ እንደተጻፈ ፣
👉 2ኛ) በማን ባሕልና ዘይቤ እንደተጻፈ ፣
👉 3ኛ) በየትኛው ዘመን እንደተጻፈ አስቀድሞ ማወቅ ለማነበብና ለመረዳት ያስችላል ምክንያቱም ሃይማኖት መሠረታዊ ጉዳይ ነውና !!! መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት ከ40 በላይ ቅዱሳን ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ አብዛኛዎቹ ዕብራውያን ናቸው፡፡ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ ለመረዳት የዕብራውያንን ባሕል በከፊልም ቢሆን መረዳት ያስፈልጋል ፡፡ ስለዚህም
በዕብራውያን ባሕል ፡-
👉 1ኛ) አብሮ አደግና ዘመዶችን በሥጋ እንኳ ከአንድ እናትና አባት ባይወለዱም ‹‹ ወንድም ›› ይባላሉ ዘፍ 13፥11
👉2ኛ) በሃይማኖት የሚመሳሰሉም ‹‹ወንድሞች ›› ይባላሉ ገላ4፥1 ‹‹ ወንድሞቼ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ››
👉3ኛ) በሕብረት በአንድ (ማህበር) የሚቀመጡ ‹‹ ወንድሞች ›› ይባላሉ ‹‹ ወንድሞች በሕብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው እነሆም ያማረ ነው›› መዝ 133፥1፡፡
በተጨማሪም ሐዋርያት እርስ በርስ ‹‹ ወንድሞች ›› ይባባሉ ነበር ፡፡ ከዚህ በመነሳት ለጌታ ‹‹ ወንድሞቹ ›› ተደርገው የተጠቀሱት ሦስቱ ሐዋርያት በሥጋ የተወለዱ አይደሉም፡፡ ድንግል ማርያምም ከጌታ ውጭ ምንም ዓይነት
ልጅ የላትም !!! ልጅ ብቻም ሳይሆን ልጅ
የመውለድ ሃሳብም የላትም አልነበራትምም !!! በተጨማሪም ወንድሞቹ ተብለው የተጠቀሱት ‹‹ያዕቆብ ›› እና ‹‹ ይሁዳ ›› መልዕክቶቻቸውን ሲጽፉ ‹‹ የጌታ ባሪያ›› እያሉ ጻፉ እንጂ ‹‹ የጌታ ወንድሞች ›› ነን ብለው አልጻፉም
ማስረጃ ፡- የያዕቆብ መልእክት 1፥1 ‹‹የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ››
የይሁዳመልእክት 1፥1 ‹‹ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ የያዕቆብም ወንድም የሆነ ይሁዳ ›› ስለዚህ እነዚህ ሐዋርያት ዮሴፍ ከሟች ሚስቶቹ የወለዳቸውና አብረውት ያደጉ እንጂ ከድንግል ማርያም የተወለዱ አይደሉም ፡፡ ‹‹‹እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም የሚለው ትርጉም ›››
ይህን ቃል በመጥቀስ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከወለደች በኋላ ዮሴፍ በግብር አውቋታል የሚሉ መናፍቃን አሉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከወለደች በኋላ ልጅ ወልዳለች የሚል ቃል አልተጻፈም እንጂ !!! ይህን ቃል መነሻ አድርጎ ለመጀመርያ ጌዜ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን የጠየቀው በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ንጉሥ አርቃድዮስ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አምሥት ነገሮችን ግልጽ አድርጎለታል ፡፡ አርቃድዮስም መልሱን በሚገባ አምኗል ተረድቷል ፡፡ ዛሬም ጥያቄውን በድርቅና ሳይሆን ልክ እንደ አርቃድዮስ በየዋህነት ለጠየቀ ሁሉ መልስ የማያስፈልገው ጥያቄ ነው ፡፡ ሆኖም
ለዚህ ስህተታቸው መልስ መስጠቱ ተገቢ ነውና
አነሆ ፡- ‹‹ የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን አላወቃትም ›› ማለት ፡- ዮሴፍ ድንግል ማርያም ጌታን እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ማን እንደሆነች አላወቃትም(ማንነቷን) አልተረዳም ነበር ለማለት ነው ፡፡ ኋላ ግን ጌታን በወለደች ጊዜ በቤተልሔም እረኞች(ኖሎት) እና መላእክት በአንድነት ሲዘምሩ ፣ የሩቅ ምሥራቅ ነገሥታት(ሰብዓ ሰገል) እጅ መንሻ ይዘው መጥተው ሲሰግዱለት ፣ እንዲሁም ቤተልሔም ላይ የብርሃን ድንኳን ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ሲመለከት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት መሆኗን አወቀ (ተረዳ) እስከዚያች ቀን ድረስ ግን ማለትም ጌታን እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ዮሴፍ ድንግል ማርያም የአምላክ
እናት መሆኗን አላወቀም ፣ አልተረዳም ነበር ለማለት ነው ፡፡
አወቀ ማለት በግብር ተገናኘ ማለት አይደለም !!! እንዲህ ከታሰበ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ የሚል ቃል አለ ፡-‹‹ ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጦ ሳለ እንጀራውን አንሥቶ ባረከው፥ ቈርሶም ሰጣቸው፤ ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም››ሉቃ 24፥30-31 ይህም ማለት ጌታችን መሆኑን አወቁ (ተረዱ) ከማለት ውጪ ሌላ ምን ዓይነት ትርጉም ሊኖረው ይችላል ??? (ማዕዱን ቆርሶ እስከሚሰጣቸው ድረስ ግን ጌታን አላወቁትም ነበር)ስለዚህ ማወቅ ማለት መረዳት እንጂ የግድ በግብር መገናኘት ዓይደለም !!
ይቆየን.....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
❤ ✞_✞_✞ ❤
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?
የመጨረሻ ክፍል
#ማስረጃ
‹‹ ቃየል ሚስቱን አወቀ ጸነሰችም ›› ዘፍጥረት 4፥17 የሚለው ቃል በግብር
እንደቀረባት(እንደተገናኛት) የታወቀ ነው
ምክንያቱም አወቃት ብቻ ብሎ አላቆመም ‹‹ ጸነሰችም ›› ይላልና !!! ነገር ግን ዮሴፍ ድንግል ማርያምን እስክትወልድ ደረስ አላወቃትም ካለ
በኋላ ሌላ ምንም ዓይነት ተቀጽላ ቃል የለውም ፡፡ መናፍቃን በግድ እናጋባ እናዋልድ ካላሉ በቀር ጸነሰችም ወለደችም አላለም አዚያው ላያ ያበቃል አራት ነጥብ ፡፡ ‹‹‹ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ልጅ የላትም ! ›››
ተጨማሪ ማስረጃዎች እነሆ ፡- ሲጀመር መጽሐፍ ቅደስ በአንድም ቦታ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ልጅ አላት አይልም ብሎም አያውቅም !!! መጽሐፍ ቅዱስ እውነቱን እውነት ሐሰቱንም ሐሰት የሚል መጽሐፍ ስለሆነ ያልሆነውን ሆነ አይልም የሆነውንም አይደብቅም !!! ወንጌልን ለዓለም የሰበኩ ቅዱሳን ሐዋርያትም ድንግል ማርያምን ማዕከል አድርገው አስተምረዋልና ከክርስቶስ በኋላ ልጅ ወልዳ ቢሆን ኖሮ ለምን ደበቁን ? ለምሳሌ ጌታችን ሲሰቀል በመስቀል ሥር ሆና ስማልቀሷ ፣ለዮሐንስ ስለመሰጠቷና መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ እርሷ በመሃከላቸው እንደነበረች ሲጽፉ ለምን ከጌታ ሌላ ልጅ መውለዷን አልነገሩንም? ለምንስ ደበቁን? አሁንም በዚህ አቋም ለጸናችሁ መናፍቃን እውን መለኮት ባደረበት ማኅጸን ሰው ያድርበት ይሆን? አዎ ከሆነ ያንተ ኢየሱስ ፍጡር እና ተራ ሰው እንጂ አምላክ አይደለም !!!
የኛ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ባደረበት ማኅጸን ግን ማንም….. !!! ማንም…. !!! ማንም…. !!! አያድርበትም ፡፡ በድጋሚ ልምጣባችሁ እውን ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ሌላ ልጅ ያስፈልጋት ይሆን ከዚያ በኋላ ብትወልድም ሰው አምላክ አይሆን? አበው እንኳ ‹‹ ሃምሳ ቢወለድ …… ከተባረከ ይበቃል አንዱ ›› ብለው የለ ታዲያ ድንግል ማርያም ከአንዱ ከብሩክ ልጇ ከክርስቶስ ሌላ ምን ሽታ ትወልድ ይሆን ?
መጽሐፍ ቅዱስ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋን እንዴት እንዳስቀመጠ ተመልከት ፡-
👉1) “እቴ ሙሽራዬ የተቆለፈች ገነት የተዘጋ ምንጭ የታተመች ፈሳሽ ናት”መኃ.ዘሰ 4÷12 (ዳዊት የመንፈስ አባቷ ነውና ልጄ ይላት ነበር ሰሎሞን ደግሞ የዳዊት ልጅ ነውና እህቴ ያላታል የመንፈስ ወንድሟ ነውና)
👉2) “የምስራቁም በር ለዘለዓለም ተዘግቶ ይኖራል ሰውም አይገባበትም እግዚአብሔር አንዴ ገብቶበታልና” ት.ሕዝ 44÷1-2 (ምሥራቅ የተሰኘች ድንግል ማርያም ናት በርሷ ሰማይነት ክርስቶስ ፀሐይ ሆኖ ወጥቷልና) ይህን ቃል ለቤተ መቅደስ ነው ብለህ የምትከራከር ካለህ ‹‹ ለዘለዓለም የተዘጋ ቤ/መ በዚህ ምድር ላይ የለምና እራስህን አታታል!!!
👉3) “ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል” ሉቃ 1÷34(ይህ የእመቤታችን አስደናቂ ንግግር ለወደፊትም እራሷን አቅባ እንደምትኖር የሚያረጋግጥ ቃል ነው ፡፡ አንድም ኃላፊ ግስ ነው የወደፊት ዓላማዋንም ያረጋግጣል) ‹‹‹ እርሱ ብቻ ልጇ እንደሆነ የክርስቶስ ምስክርነት›››
1ኛ) አይሁድ በምቀኝነት ክርስቶስን ሲሰቅሉት ከእግረ መስቀሉ ሥር የተገኘው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ድንግል ማርያም ብቻ ነበሩ ፡፡ እመቤታችን ሌሎች ልጆች ቢኖሯት ኖሮ ‹‹ እነሆ ልጅሽ ›› ብሎ ዮሐንስን ጠብቃት ባላለውም ነበር ፡፡ በዚህ ላይ ዮሐንስም እኮ እናት ነበረችው ፡፡ ነገር ግን ድንግል ማርያም አንድያ ልጇ በመሆኑ ጌታችን ለዮሐንስ አደራ ሰጥቶአታል ፡፡
2ኛ) የኢየሩሳሌም ሴቶች ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ሲያልፍ ተመልክተው አዝነው ሲያለቅሱ ‹‹ ለራሳችሁ እና ለልጆቻችሁ አልቅሱ ›› ተብለዋል እመቤታችንም መስቀል ሥር ሆና ታለቅስ ነበር ታዲያ ለምን ‹‹ ሄደሽ ለልጆችሽ አልቅሺ አላላትም ? ? ?
‹‹‹ ትልቅ እርምት የሚሻው የመናፍቃን ስህተት ›››‹‹ ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን? እኅቶቹስ ሁሉ በእኛ ዘንድ ያሉ አይደሉምን? እንኪያስ ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው? ተሰናከሉበትም›› ማቴ13÷56 የሚለውን ቃል ለማን እንደተነገረ እንኳ ሳያስተውሉ ጭራሽ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ እንዳላት አድርገው ይህን አሳፋሪ ቃል ሲጠቀሙበት አይቼ እኔም አፈርኩበት !!! የዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ዓላማ አይሁድ ክርስቶስን ወንድሞች አሉት ፤
ዮሴፍ ከሟች ሚስቱ የወለዳቸውን ሁሉ ከድንግል ማርያም ነው ብለው በማሰባቸው ወይም በመናገራቸው ተሰናከሉ(ተሳሳቱ) ማለት ነው ፡፡
👉ታዲያ እነርሱ ክርስቶስ የዮሴፍ ልጅ ነው ፤ ድንግል ማርያምም ሌሎች ልጆች አሏት ብለው በማሰባቸው ተሳሳቱ ከተባለ ለምን አንተ ደግመህ ትሰናከላለህ??? ይህን ስህተታቸውን ሲያስረግጥ ትንሽ ወረድ ብሎ ‹‹ በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም ›› ይላል ፡፡
‹‹‹ ስለ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ ማጠቃለያ ››› እመቤታችን እንደማንኛውም ሴት አይደለችም !!! ክርስቶስን የጸነሰችው ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ሲያበሥራት ነው ፡፡ ‹‹‹ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል ››› በማለት እንደተናገረችው እንደሌሎች ሴቶች በዘር በሩካቤ አይደለምና ነው፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም ‹‹ አንቺ ከሴቶች
ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ›› ሉቃ 13÷9 በማለት እንደተናገረችው፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ኦ ሀገረ እግዚአብሔር ›› (የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ ባንቺ የተደረገው ምንኛ ድንቅ ነው) አንዳለ በእመቤታችን የተደረገው ልዩ ነው ፡፡ ለዚህ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ አንክሮ(ምሥጋና) ይገባል ፡፡
📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በሚቀጥለው ደግሞ ተአምረ ማርያም መቅድም ላይ ተአምሯን የሰማ ስጋወደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል የሚለውን እንመለከታለን::
የመጨረሻ ክፍል
#ማስረጃ
‹‹ ቃየል ሚስቱን አወቀ ጸነሰችም ›› ዘፍጥረት 4፥17 የሚለው ቃል በግብር
እንደቀረባት(እንደተገናኛት) የታወቀ ነው
ምክንያቱም አወቃት ብቻ ብሎ አላቆመም ‹‹ ጸነሰችም ›› ይላልና !!! ነገር ግን ዮሴፍ ድንግል ማርያምን እስክትወልድ ደረስ አላወቃትም ካለ
በኋላ ሌላ ምንም ዓይነት ተቀጽላ ቃል የለውም ፡፡ መናፍቃን በግድ እናጋባ እናዋልድ ካላሉ በቀር ጸነሰችም ወለደችም አላለም አዚያው ላያ ያበቃል አራት ነጥብ ፡፡ ‹‹‹ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ልጅ የላትም ! ›››
ተጨማሪ ማስረጃዎች እነሆ ፡- ሲጀመር መጽሐፍ ቅደስ በአንድም ቦታ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ልጅ አላት አይልም ብሎም አያውቅም !!! መጽሐፍ ቅዱስ እውነቱን እውነት ሐሰቱንም ሐሰት የሚል መጽሐፍ ስለሆነ ያልሆነውን ሆነ አይልም የሆነውንም አይደብቅም !!! ወንጌልን ለዓለም የሰበኩ ቅዱሳን ሐዋርያትም ድንግል ማርያምን ማዕከል አድርገው አስተምረዋልና ከክርስቶስ በኋላ ልጅ ወልዳ ቢሆን ኖሮ ለምን ደበቁን ? ለምሳሌ ጌታችን ሲሰቀል በመስቀል ሥር ሆና ስማልቀሷ ፣ለዮሐንስ ስለመሰጠቷና መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ እርሷ በመሃከላቸው እንደነበረች ሲጽፉ ለምን ከጌታ ሌላ ልጅ መውለዷን አልነገሩንም? ለምንስ ደበቁን? አሁንም በዚህ አቋም ለጸናችሁ መናፍቃን እውን መለኮት ባደረበት ማኅጸን ሰው ያድርበት ይሆን? አዎ ከሆነ ያንተ ኢየሱስ ፍጡር እና ተራ ሰው እንጂ አምላክ አይደለም !!!
የኛ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ባደረበት ማኅጸን ግን ማንም….. !!! ማንም…. !!! ማንም…. !!! አያድርበትም ፡፡ በድጋሚ ልምጣባችሁ እውን ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ሌላ ልጅ ያስፈልጋት ይሆን ከዚያ በኋላ ብትወልድም ሰው አምላክ አይሆን? አበው እንኳ ‹‹ ሃምሳ ቢወለድ …… ከተባረከ ይበቃል አንዱ ›› ብለው የለ ታዲያ ድንግል ማርያም ከአንዱ ከብሩክ ልጇ ከክርስቶስ ሌላ ምን ሽታ ትወልድ ይሆን ?
መጽሐፍ ቅዱስ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋን እንዴት እንዳስቀመጠ ተመልከት ፡-
👉1) “እቴ ሙሽራዬ የተቆለፈች ገነት የተዘጋ ምንጭ የታተመች ፈሳሽ ናት”መኃ.ዘሰ 4÷12 (ዳዊት የመንፈስ አባቷ ነውና ልጄ ይላት ነበር ሰሎሞን ደግሞ የዳዊት ልጅ ነውና እህቴ ያላታል የመንፈስ ወንድሟ ነውና)
👉2) “የምስራቁም በር ለዘለዓለም ተዘግቶ ይኖራል ሰውም አይገባበትም እግዚአብሔር አንዴ ገብቶበታልና” ት.ሕዝ 44÷1-2 (ምሥራቅ የተሰኘች ድንግል ማርያም ናት በርሷ ሰማይነት ክርስቶስ ፀሐይ ሆኖ ወጥቷልና) ይህን ቃል ለቤተ መቅደስ ነው ብለህ የምትከራከር ካለህ ‹‹ ለዘለዓለም የተዘጋ ቤ/መ በዚህ ምድር ላይ የለምና እራስህን አታታል!!!
👉3) “ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል” ሉቃ 1÷34(ይህ የእመቤታችን አስደናቂ ንግግር ለወደፊትም እራሷን አቅባ እንደምትኖር የሚያረጋግጥ ቃል ነው ፡፡ አንድም ኃላፊ ግስ ነው የወደፊት ዓላማዋንም ያረጋግጣል) ‹‹‹ እርሱ ብቻ ልጇ እንደሆነ የክርስቶስ ምስክርነት›››
1ኛ) አይሁድ በምቀኝነት ክርስቶስን ሲሰቅሉት ከእግረ መስቀሉ ሥር የተገኘው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ድንግል ማርያም ብቻ ነበሩ ፡፡ እመቤታችን ሌሎች ልጆች ቢኖሯት ኖሮ ‹‹ እነሆ ልጅሽ ›› ብሎ ዮሐንስን ጠብቃት ባላለውም ነበር ፡፡ በዚህ ላይ ዮሐንስም እኮ እናት ነበረችው ፡፡ ነገር ግን ድንግል ማርያም አንድያ ልጇ በመሆኑ ጌታችን ለዮሐንስ አደራ ሰጥቶአታል ፡፡
2ኛ) የኢየሩሳሌም ሴቶች ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ሲያልፍ ተመልክተው አዝነው ሲያለቅሱ ‹‹ ለራሳችሁ እና ለልጆቻችሁ አልቅሱ ›› ተብለዋል እመቤታችንም መስቀል ሥር ሆና ታለቅስ ነበር ታዲያ ለምን ‹‹ ሄደሽ ለልጆችሽ አልቅሺ አላላትም ? ? ?
‹‹‹ ትልቅ እርምት የሚሻው የመናፍቃን ስህተት ›››‹‹ ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን? እኅቶቹስ ሁሉ በእኛ ዘንድ ያሉ አይደሉምን? እንኪያስ ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው? ተሰናከሉበትም›› ማቴ13÷56 የሚለውን ቃል ለማን እንደተነገረ እንኳ ሳያስተውሉ ጭራሽ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ እንዳላት አድርገው ይህን አሳፋሪ ቃል ሲጠቀሙበት አይቼ እኔም አፈርኩበት !!! የዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ዓላማ አይሁድ ክርስቶስን ወንድሞች አሉት ፤
ዮሴፍ ከሟች ሚስቱ የወለዳቸውን ሁሉ ከድንግል ማርያም ነው ብለው በማሰባቸው ወይም በመናገራቸው ተሰናከሉ(ተሳሳቱ) ማለት ነው ፡፡
👉ታዲያ እነርሱ ክርስቶስ የዮሴፍ ልጅ ነው ፤ ድንግል ማርያምም ሌሎች ልጆች አሏት ብለው በማሰባቸው ተሳሳቱ ከተባለ ለምን አንተ ደግመህ ትሰናከላለህ??? ይህን ስህተታቸውን ሲያስረግጥ ትንሽ ወረድ ብሎ ‹‹ በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም ›› ይላል ፡፡
‹‹‹ ስለ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ ማጠቃለያ ››› እመቤታችን እንደማንኛውም ሴት አይደለችም !!! ክርስቶስን የጸነሰችው ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ሲያበሥራት ነው ፡፡ ‹‹‹ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል ››› በማለት እንደተናገረችው እንደሌሎች ሴቶች በዘር በሩካቤ አይደለምና ነው፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም ‹‹ አንቺ ከሴቶች
ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ›› ሉቃ 13÷9 በማለት እንደተናገረችው፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ኦ ሀገረ እግዚአብሔር ›› (የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ ባንቺ የተደረገው ምንኛ ድንቅ ነው) አንዳለ በእመቤታችን የተደረገው ልዩ ነው ፡፡ ለዚህ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ አንክሮ(ምሥጋና) ይገባል ፡፡
📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በሚቀጥለው ደግሞ ተአምረ ማርያም መቅድም ላይ ተአምሯን የሰማ ስጋወደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል የሚለውን እንመለከታለን::
"ተአምሯን የሰማ ስጋውን ደሙን እንደ ተቀበለ ይሆንለታል"።
@And_Haymanot
ለተሃድሶ መናፍቃን የተሠጠ መልሥ
(በድጋሚ የቀረበ)
ይህን ፅንሰ ሀሳብ ለመረዳት በመጀመሪያ በመቅደሙ የተፃፈውን
ቃል እንዳለ መመልከት ጠቀሜታ ይኖረዋል። አስቀድመን እንደተናገርን የታወቀ ምክንያት ኋጢአት ደዌ
ካልከለከለው በዚች ቀን ተአምሯን ሰምቶ ስጋውን ደሙን ይቀበል። ስጋውን ደሙን መቀበል ካልተቻለው ተአምሯን ሰምቶ ወደ ቤቱ ይሒድ ስጋውን ደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል ይደረግልኛል
በማለት ቢሰማ ይላል የዚህን አንቀጽ መልዕክት አንድ በአንድ በመተንተን ስንመለከት የሚከተሉትን ሶስት አበይት መልዕክቶች እናገኛለን።
👉ሀ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ፦
ይህ አንቀፅ በመጀመሪያ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በዋናነት የሚያስተላልፈው መልዕክት ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ የሚል ነው። ምክንያቱም በፍትሐ ነገስት ከቀዳም ሥዑር በቀር ቅዳሜ ቅዳሜ እና እሁድ እሁድ በቤተክርስቲያን ተሰብስባችሁ ስጋውን ደሙን ተቀብላችሁ ደስ ይበላችሁ ተብሎ ታዝዟል ይህም ብቻ ብቻ ሳይሆን በበረሃ ያሉ ባህታውያን ሳይቀሩ መልዐከ እግዚአብሔር ስጋወ ደሙን ሰንበት ነው። / በዓላት-ምን ?
ለምን ? እእንዴት ? ገፅ ፵፮ እና ፷፮ / ነገር ግን በስርዐተ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው ስጋውን ደሙን እንዳይቀበል ሊያደርጉ የሚችሉ ምክንያቶች ይኖራሉ።
እነዚህም በዚህ አንቀፅ የተገለፁት አንደኛ የታወቀ ምክንያት / እንደ ወሊድ ፤ ሀዘን ፤ ለቅሶ ፤ ...የመሳሰሉት ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ኃጢዐት ነው።
ይከለክሉታል ተብለው ከተጠቁሱት በመጨረሻ የተገለፀው ደግሞ ደዌ ነው። አንድ ሰው በደዌ ምክንያት ነገር ከሰውነቱ እየወጣ፤ ደም እየፈሰሰው ይህን የመሰሉ ነገሮች እያሉበት ስጋወ ደሙን ላይቀበል ይችላል እነዚህ ሁሉ ግን ሰውየውን በቤተክርስቲያን
ቅፅር ተገኝቶ ከመፀለይ፤ ቅዱሳት መፀሀፍትን ምንባባት ከመስማት ግን ላይከለክሉት ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ሰው እነዚህ ምክንያቶች ካልከለከሉት በቀር ስጋወን ደሙን ይቀበል በማለት ወንጌልን ይሰብካል እንጅ ከወንጌል የወጣ ቃል የለውም።
👉 ለ ቤተክርስቲያን አትቅር ፦
ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ስጋውን ደሙን መቀበል ባይቻልህ ግን ስጋውን ደሙን መቀበል አይቻለኝም ብለህ ወደ
ቤተክርስቲያን ከመሄድ አትከልከል የሚለው። ተአምረ ማርያም ከቅዳሴ በፊት ያለው የቤተክርስቲያን የፀሎት
ክፍል አንድ አካል ነው።
መቅድሙም የሚለው ፦
።።።///።።።።///።።።
#ስጋወ_ደሙን_መቀበል_ካልተቻለው_ተአምሯን_ሰምቶ_ወደ_ቤቱ_ይሂድ_ነው።
።።።///።።።።///።።።
ይህም ማለት ባትቆርብም ቤተክርስቲያን አትቅር ማለት ነው።በፀሎቱ ትምህርትና በመሳሰለው መርሀግብር ሁሉ ተሳተፍ።
ዕለቱ ሰንበትና በዓላት ከሆነ አንድ ክርስቲያን ቤተክርስቲያን ካልሄደ በዚያም ተገኝቶ ካልተማረ ካላመሰገነ ክርስትናውን በምን ይገልፀዋል ?
በዚህ አገላለፅ ተአምሯን ሰምቶ ወደ ቤቱ ይሂድ የሚለውን በአስተውሎትና በቅንነት ከተመለከትነው የሚናገረው ስለተአምሯ ብቻ አይደለም። ታአምሯን አታስታጉሉ ሲል ወደ ቤተክርስቲያን ሂዳችሁ በዚያ ካለው ባለው አገልግሎት ተሳተፉ ማለት ነው። ምክንያቱም ተአምረ ማርያምን እንዴትና መቸ እንደሚነበብ
እናውቃለን። ከተአምሩም በፊት፤ ከተአምሩም በኋላ ሌሎች ፀሎቶችና
ምንባባት አሉ። ይህን አጠቃላይ አገልግሎት ለምዕመኑ በታወቀ በተረዳ ነገር በዚህ ስያሜ ማስታወቅ ክፋትም ኋጢአትም አይደለም። ሌላው አገልግሎት በዚህ አገላለፅ ለምን ጠሩት ቢባል በትርጓሜ ውዳሴ ማርያም ላይ እንደተፃፈው ሌላውን አገልግሎት በመናቅ ማቅለል ሳይሆን ለእመቤታችን ባላቸው ፍቅር ነው።
👉 ሐ አትጠራጠር፦
ሶስተኛውና የየመጨረሻው የዚህ አንቀፅ መልዕክት በታወቀ ምክንያት
+++ በዚች ዕለት +++ ስጋውን ደሙን መቀበል ባይቻልክ ለሌሎች የተደረገው አይደረግልኝም የዕለቱ በረከት አይደርሰኝም ብለህ አትጠራጠር የሚል ነው። መፀሀፉ የተአምራት መፀሀፍ እንደመሆኑ መጠን ተአምራትም
የሚደረገውና ተአምራትም የሚያሰኛቸው ከዘወትራዊ የህይወት ተግባራትና ድርጊቶች የተለየ ለሰው የማይቻል በእግዚአብሔር ብቻ የሚቻል ነገር መደረጉ በመሆኑ አንተም ይደረግልኛል
በማለት በዕምነት ከፀሎቱ ተካፍለህ ከተአምሯም ሰምተህ ብትሄድ #በዕለቱ የቆረቡትን ሰወች በረከት ታገኛለክ ማለት
ነው። ይህ ደግሞ በቅዱሳት መፀሀፍ የተፃፈ ነው። ራሱ ጌታችን በወንጌሉ የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ዕምነት
ቢኖራችሁ ተራራ ማፍለስ፤ ባህር መክፈል..........
ሌላም ሌላም ትችላላችሁ ሲል አስተምሯል። ይህም በዕምነት ሀይል እግዚአብሔርን በረከተ እግዚአብሔርን
ታገኛላችሁ ከእግዚአብሔር ትገናኛላችሁ ማለት ነው። ስጋወ ደሙ በየሳምንቱ ወይም ከዚህ ባነሰም ይሁን በበዛም
የምንቀበለውም ለዚሁ ሀይለ እግዚአብሔርን ገንዘብ አድርገን ኋጢያታችን አስተስርየን በረከተ ስጋ በረከተ ነፍስ አግኝተን ለመኖር ነው። በዚያች ዕለት አልቻልክ ብሎ ባትቀበል በዕምነትም ይህን ታገኛለክና አትጠራጠር ይሉናል ሊቃውንቱ።
የየመቅደሙ መልዕክት ይኸ ሁኖ ሳለ
"አውቆ የተኛን " ቢቀሰቅሱት አይሰማም እንደሚባለው ሰወችን ሆን ብሎ ለማጠራጠር ከቅዱሳን በረከት ለመለየት አጋንንት በሰወች አድረው ሊቃውንቱ ያላሉትንና ሊሉም ያላሰቡትን
ያቀርባሉ። ቤተክርስትያኒቱ " ስጋውን ደሙን አትቀበሉ " ስጋወ ደሙን መቀበልና ስጋወደሙን ሳይቀበሉ ተአምረ ማርያምን መስማት እኩል ናቸው የሚል ትምህርት አስተምራ አታውቅም እእንዲህም አታምንም።
ተአምሯን የሚሰሙትና የሚያሰሙትም ስጋውን ደሙን የተቀበሉ ወደፊትም የሚቀበሉ ናቸው እንጅ አረማውያን ወይም በስጋወ ደሙ የሚጠራጠሩ አይደሉም።
/// ይደረግልኛል በማለት ቢሰማ /// የሚለው ጊዜ የተገደበ
ነው፡፡ ታዲያ ይህ በዕውኑ ለምዕመኑ መንፈሳዊ ህይወት መጨነቅ ወይስ ለኑፋቄ ሽፋን መፈለግ ???
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ አፕሊኬሽን።
ልዑል እግዚአብሔር በተዋህዶ በረት እንድንፀና ያድርገን ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ ከሁላችንም ጋር
ይሁን አሜን::
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ለተሃድሶ መናፍቃን የተሠጠ መልሥ
(በድጋሚ የቀረበ)
ይህን ፅንሰ ሀሳብ ለመረዳት በመጀመሪያ በመቅደሙ የተፃፈውን
ቃል እንዳለ መመልከት ጠቀሜታ ይኖረዋል። አስቀድመን እንደተናገርን የታወቀ ምክንያት ኋጢአት ደዌ
ካልከለከለው በዚች ቀን ተአምሯን ሰምቶ ስጋውን ደሙን ይቀበል። ስጋውን ደሙን መቀበል ካልተቻለው ተአምሯን ሰምቶ ወደ ቤቱ ይሒድ ስጋውን ደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል ይደረግልኛል
በማለት ቢሰማ ይላል የዚህን አንቀጽ መልዕክት አንድ በአንድ በመተንተን ስንመለከት የሚከተሉትን ሶስት አበይት መልዕክቶች እናገኛለን።
👉ሀ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ፦
ይህ አንቀፅ በመጀመሪያ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በዋናነት የሚያስተላልፈው መልዕክት ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ የሚል ነው። ምክንያቱም በፍትሐ ነገስት ከቀዳም ሥዑር በቀር ቅዳሜ ቅዳሜ እና እሁድ እሁድ በቤተክርስቲያን ተሰብስባችሁ ስጋውን ደሙን ተቀብላችሁ ደስ ይበላችሁ ተብሎ ታዝዟል ይህም ብቻ ብቻ ሳይሆን በበረሃ ያሉ ባህታውያን ሳይቀሩ መልዐከ እግዚአብሔር ስጋወ ደሙን ሰንበት ነው። / በዓላት-ምን ?
ለምን ? እእንዴት ? ገፅ ፵፮ እና ፷፮ / ነገር ግን በስርዐተ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው ስጋውን ደሙን እንዳይቀበል ሊያደርጉ የሚችሉ ምክንያቶች ይኖራሉ።
እነዚህም በዚህ አንቀፅ የተገለፁት አንደኛ የታወቀ ምክንያት / እንደ ወሊድ ፤ ሀዘን ፤ ለቅሶ ፤ ...የመሳሰሉት ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ኃጢዐት ነው።
ይከለክሉታል ተብለው ከተጠቁሱት በመጨረሻ የተገለፀው ደግሞ ደዌ ነው። አንድ ሰው በደዌ ምክንያት ነገር ከሰውነቱ እየወጣ፤ ደም እየፈሰሰው ይህን የመሰሉ ነገሮች እያሉበት ስጋወ ደሙን ላይቀበል ይችላል እነዚህ ሁሉ ግን ሰውየውን በቤተክርስቲያን
ቅፅር ተገኝቶ ከመፀለይ፤ ቅዱሳት መፀሀፍትን ምንባባት ከመስማት ግን ላይከለክሉት ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ሰው እነዚህ ምክንያቶች ካልከለከሉት በቀር ስጋወን ደሙን ይቀበል በማለት ወንጌልን ይሰብካል እንጅ ከወንጌል የወጣ ቃል የለውም።
👉 ለ ቤተክርስቲያን አትቅር ፦
ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ስጋውን ደሙን መቀበል ባይቻልህ ግን ስጋውን ደሙን መቀበል አይቻለኝም ብለህ ወደ
ቤተክርስቲያን ከመሄድ አትከልከል የሚለው። ተአምረ ማርያም ከቅዳሴ በፊት ያለው የቤተክርስቲያን የፀሎት
ክፍል አንድ አካል ነው።
መቅድሙም የሚለው ፦
።።።///።።።።///።።።
#ስጋወ_ደሙን_መቀበል_ካልተቻለው_ተአምሯን_ሰምቶ_ወደ_ቤቱ_ይሂድ_ነው።
።።።///።።።።///።።።
ይህም ማለት ባትቆርብም ቤተክርስቲያን አትቅር ማለት ነው።በፀሎቱ ትምህርትና በመሳሰለው መርሀግብር ሁሉ ተሳተፍ።
ዕለቱ ሰንበትና በዓላት ከሆነ አንድ ክርስቲያን ቤተክርስቲያን ካልሄደ በዚያም ተገኝቶ ካልተማረ ካላመሰገነ ክርስትናውን በምን ይገልፀዋል ?
በዚህ አገላለፅ ተአምሯን ሰምቶ ወደ ቤቱ ይሂድ የሚለውን በአስተውሎትና በቅንነት ከተመለከትነው የሚናገረው ስለተአምሯ ብቻ አይደለም። ታአምሯን አታስታጉሉ ሲል ወደ ቤተክርስቲያን ሂዳችሁ በዚያ ካለው ባለው አገልግሎት ተሳተፉ ማለት ነው። ምክንያቱም ተአምረ ማርያምን እንዴትና መቸ እንደሚነበብ
እናውቃለን። ከተአምሩም በፊት፤ ከተአምሩም በኋላ ሌሎች ፀሎቶችና
ምንባባት አሉ። ይህን አጠቃላይ አገልግሎት ለምዕመኑ በታወቀ በተረዳ ነገር በዚህ ስያሜ ማስታወቅ ክፋትም ኋጢአትም አይደለም። ሌላው አገልግሎት በዚህ አገላለፅ ለምን ጠሩት ቢባል በትርጓሜ ውዳሴ ማርያም ላይ እንደተፃፈው ሌላውን አገልግሎት በመናቅ ማቅለል ሳይሆን ለእመቤታችን ባላቸው ፍቅር ነው።
👉 ሐ አትጠራጠር፦
ሶስተኛውና የየመጨረሻው የዚህ አንቀፅ መልዕክት በታወቀ ምክንያት
+++ በዚች ዕለት +++ ስጋውን ደሙን መቀበል ባይቻልክ ለሌሎች የተደረገው አይደረግልኝም የዕለቱ በረከት አይደርሰኝም ብለህ አትጠራጠር የሚል ነው። መፀሀፉ የተአምራት መፀሀፍ እንደመሆኑ መጠን ተአምራትም
የሚደረገውና ተአምራትም የሚያሰኛቸው ከዘወትራዊ የህይወት ተግባራትና ድርጊቶች የተለየ ለሰው የማይቻል በእግዚአብሔር ብቻ የሚቻል ነገር መደረጉ በመሆኑ አንተም ይደረግልኛል
በማለት በዕምነት ከፀሎቱ ተካፍለህ ከተአምሯም ሰምተህ ብትሄድ #በዕለቱ የቆረቡትን ሰወች በረከት ታገኛለክ ማለት
ነው። ይህ ደግሞ በቅዱሳት መፀሀፍ የተፃፈ ነው። ራሱ ጌታችን በወንጌሉ የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ዕምነት
ቢኖራችሁ ተራራ ማፍለስ፤ ባህር መክፈል..........
ሌላም ሌላም ትችላላችሁ ሲል አስተምሯል። ይህም በዕምነት ሀይል እግዚአብሔርን በረከተ እግዚአብሔርን
ታገኛላችሁ ከእግዚአብሔር ትገናኛላችሁ ማለት ነው። ስጋወ ደሙ በየሳምንቱ ወይም ከዚህ ባነሰም ይሁን በበዛም
የምንቀበለውም ለዚሁ ሀይለ እግዚአብሔርን ገንዘብ አድርገን ኋጢያታችን አስተስርየን በረከተ ስጋ በረከተ ነፍስ አግኝተን ለመኖር ነው። በዚያች ዕለት አልቻልክ ብሎ ባትቀበል በዕምነትም ይህን ታገኛለክና አትጠራጠር ይሉናል ሊቃውንቱ።
የየመቅደሙ መልዕክት ይኸ ሁኖ ሳለ
"አውቆ የተኛን " ቢቀሰቅሱት አይሰማም እንደሚባለው ሰወችን ሆን ብሎ ለማጠራጠር ከቅዱሳን በረከት ለመለየት አጋንንት በሰወች አድረው ሊቃውንቱ ያላሉትንና ሊሉም ያላሰቡትን
ያቀርባሉ። ቤተክርስትያኒቱ " ስጋውን ደሙን አትቀበሉ " ስጋወ ደሙን መቀበልና ስጋወደሙን ሳይቀበሉ ተአምረ ማርያምን መስማት እኩል ናቸው የሚል ትምህርት አስተምራ አታውቅም እእንዲህም አታምንም።
ተአምሯን የሚሰሙትና የሚያሰሙትም ስጋውን ደሙን የተቀበሉ ወደፊትም የሚቀበሉ ናቸው እንጅ አረማውያን ወይም በስጋወ ደሙ የሚጠራጠሩ አይደሉም።
/// ይደረግልኛል በማለት ቢሰማ /// የሚለው ጊዜ የተገደበ
ነው፡፡ ታዲያ ይህ በዕውኑ ለምዕመኑ መንፈሳዊ ህይወት መጨነቅ ወይስ ለኑፋቄ ሽፋን መፈለግ ???
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ አፕሊኬሽን።
ልዑል እግዚአብሔር በተዋህዶ በረት እንድንፀና ያድርገን ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ ከሁላችንም ጋር
ይሁን አሜን::
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
ድንግል ማርያምን እመቤት ማለት የይገባል?
@And_Haymanot
የተሃድሶ መናፍቃን በነገረ ድንግል ማርያም ላይ ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች መካከል ቅድስተ ቅዱሳን እናታችንን እመቤት ማለታችን ኢ-መፅሐፍ ቅዱሳዊ አድርገው ይቃወማሉ፡፡ እናት ቤተክርስቲያናችን መፅሐፍ ቅዱስን አብነት አድርጋ ታስተምራለች፡፡
ሲጀምር " እመቤት " ማለት በአንድ ቤተሰብ መካከል አስተዳዳሪና ኃላፊ የሆነች የታላቅ ሴት መጠሪያ መሆኑን
መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል እንጂ መናፍቃን እንደሚሉት ፍፁም ስህተት የሆነ ሴቶች የማይጠሩበት ስም አይደለም ፤እንኳን ጸጋን ሁሉ ለተመላች ፣ ከሴቶች ሁሉ ለተለየች ፣ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይቅርና ብዙ ሴቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው እመቤት ተብለው ተጠርተዋል ።
እስቲ ለአብነት ከመጽሐፉ እየጠቀስን እንይ ፦
፨ የአብርሃም ሚስት ሣራ እመቤት ተብላለች" እርሱም ወደ አጋር ገባ፥ አረገዘችም እንዳረገዘችም
ባየች ጊዜ እመቤትዋን በዓይንዋ አቃለለች።" እንዲል ዘፍ 16 : 4
አጋር ከሣራ ተለይታ በኮበለለች ጊዜ
" የእግዚአብሔር መልአክም ወደ እመቤትሽ ተመለሺ፥ ከእጅዋም በታች ሆነሽ ተገዥ አላት።"ይላል ዘፍ 16 : 9
ወዳጄ የእግዚአብሔር መልአክ የሰው
ልጅ እመቤት ተብሎ ባይጠራ ኖሮ ወደ እመቤትሽ ይል ነበር ?
፨ ወዳጄ የእግዚአብሔር ቃል አገልጋይ ቀጥራ የምታሰራዋን ሴት ምን ብሎ ነው የሚጠራት ?
° የንእማንን ሚስት ታገለግል የነበረችው ብላቴና " [ እመቤትዋንም ] ጌታዬ በሰማርያ ካለው ከነቢዩ ፊት ቢደርስ ኖሮ ከለምጹ በፈወሰው ነበር አለቻት። " 2ኛ. ነገ5 : 3
፨ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ያገልጋይቱ ዓይን ወደ እመቤቷ ነው ይለናል ።
° " እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ የባሪያይቱም ዓይን ወደ [ እመቤትዋ ] እጅ እንደ
ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው። " መዝ 124 :2
፨ ጠቢቡ ሰለሞንም እንዲህ ይላል ፦
° " በሦስት ነገር ምድር ትናወጣለች፥ አራተኛውንም
ትሸከም ዘንድ አይቻላትም።
፨ ባሪያ በነገሠ ጊዜ ፣
፨ ሰነፍም እንጀራ በጠገበ ጊዜ፥
፨ የተጠላች ሴት ባል ባገኘች ጊዜ፥
፨ ሴት ባሪያም [ እመቤቷን ] በወረሰች ጊዜ። "መ. ምሳ 30 : 21 - 23
ወዳጄ ይሄ ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ተጽፎ ሳለ ፤ ወይ ሳያነቡ ወይ ሳይጠይቁ ገና ለገና እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመቃወም ሲባል ብቻ "ለወንድ ጌታ ለሴት እመቤት እንላለን ይሄ አባባል ፍጹም ስህተት ነው " የሚለውን የአጋንንት ስብከት ከየት
አመጣችሁት ? እውነት እናንተ እንደምትሉት ቢሆን ኖሮ እነሣራ ፣ የንእማን ሚስት እና ሌሎቹም ሴቶች ለምን እመቤት ተባሉ ? እመቤት ማለት የማይገባ ከሆነ የእግዚአብሔር መልአክ ፣ ቅዱስ ዳዊት ፣ ጠቢቡ ሰለሞን
ሴቶቹን ለምን እመቤት ብለው ጠሯቸው ? ነው መጽሐፉ ተሳስቶ ይሆን ?
መቼም ምክንያት እየፈጠሩ ለመካድ ለማስካድ እንጂ ለማመን አልተፈጠራችሁምና ይሄ በብሉይ ኪዳን እንጂ በአዲስ ኪዳን አይባልም ካላችሁ ማስረጃ ልስጥ ፤ ወዳጄ ፍቁረ እግዚ ቅዱስ ዮሐንስ 2ኛ የዮሐንስ መልእክቱን የጻፈው ለማነው ? አታቀውቁትም እንጂ ሲጀመር ብታውቁት ቃሉን እንደዚህ አንጋዳችሁ አወላግዳችሁ ባልጻፋችሁም
ነበር ፤ ታሪኩ ሰፊ ሲሆን ነገር ላለማርዘምና ቀጥታ ለጥያቄው
መልስ ለመስጠት ያህል ብቻ ቅዱስ ዮሐንስ ይቺን ሁለተኛ መልእክቱን የጻፈው ጣኦት ያመልኩ የነበሩ የነገሥታቱንና
የመኳንንቱን ልጆች ሞግዚት ሆና ታሳድግ ለነበረችው ሮምና ለምትባል ሴት ነው ።
ቅዱስ ዮሐንስና አብሮኮሮስ አስተምረው አሳምነው አጥምቀው ከአምልኮ ጣኦት ወደ ወገኛይቱ ወደ ክርስትና እምነት ከመለሷት በኃላ ለስብከት ወደ ሌላ አገር ይሄዳሉ፤ ከሄዱም በኃላ ግን በእምነቷ እንድትጸና እና እንድትበረታ ሲል ይቺን ሁለተኛይቱ የተባለችውን የዮሐንስ መልእክቱን የጻፈላት ። ወዳጄ ቅዱስ ዮሐንስ ለዚህች በነገሥታቱና በመኮንንቱ ቤት በሰራተኝነት ፣ በሞግዚትነት ለምታገለግለው ሮምና
ለተባለችው መልእክቱን ሲጽፍ ምን እንዳላት ታውቃለህ ? [ እመቤት ሆይ ] እያለ ነበር አክብሮ ይጠራት የነበረው ።
እስቲ የጻፈውን ቃል በቃል እንየው ፦
" በእኛ ስለሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ስለሚሆን እውነት፥ እኔ ሽማግሌው በእውነት ለምወዳቸውና እኔ ብቻ
ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ደግሞ ለሚወዱአቸው ለተመረጠች እመቤትና ለልጆችዋ "ይላል 2ኛ.ዮሐ 1 : 1 - 2
ወዳጄ እመቤት ብቻ አይደለም ያላት
" የተመረጠች እመቤት " ማለቱን አስተውል ። ሲቀጥል ቁ. 5 ላይ
" አሁንም፥ እመቤት ሆይ፥ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ እለምንሻለሁ፤ ይህች ከመጀመሪያ በእኛ ዘንድ የነበረች
ትእዛዝ ናት እንጂ አዲስ ትእዛዝን እንደምጽፍልሽ አይደለም። "ይላታል 2ኛ. ዮሐ 1 : 5 ወዳጄ የሕግ ፍጻሜና የምትበልጠው ጸጋ የተባለች ፍቅር
ይኖራቸው ዘንድ ሲጽፍላት
" እመቤት ሆይ ... እለምንሻለሁ " ብሎ ሲማጸናት ታያለህ ?
ታዲያ እንደ እናንተ አገላለጽ የሰው ልጅ ጌታና እመቤት ተብሎ የማይጠራ ፍጹም የሆነ ስህተት ከሆነ ቅዱስ ዮሐንስ ሮምናን ለምን እመቤት ሆይ እያለ ጠራት ? እናንተ ከዮሐንስ ትበልጣላችሁ?
አናንተ ናችሁ እኛ ነን በመጽሐፍ ቅዱስ የማናምነው? ከላይ ያየናቸው የብዙ ሴቶች እና የሮምና እመቤት መባል
ፍጹም ስህተት ያልሆነ ፤ የሰማይና የምድር ንጉሥ እናት የሆነች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እመቤት መባል እንዴት ሆኖ ነው ፍጹም ስህተት የሚሆነው ?
በአዳምና በሔዋን አማካኝነት ወደ ዓለም የገባውን መርገም የሻረ ጌታ እግዚአብሔር ከእርሷ በመወለዱ እመቤታችንን እግዝእተ በዙኃን [ የብዙኅን እመቤት ]
ትባላለች ። እንዲሁም ዓለም ሁሉ በዳነበት በክርስቶስ የማዳን ሥራ ያመንን ክርስቲያኖች ሁሉ በክርስቶስ አንድ
ቤተሰብ በመሆናችን ቅድስት እናቱ ድንግል ማርያምእመቤታችን ናት ።
ወዳጄ ፦ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ እመቤታችን እንደ ሌሎቹ ሴቶች እመቤት ብቻ አላላትም ንግስት
እንጂ !" በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ
ትቆማለች ......
የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ ( ይለምናሉ ይማጸናሉ )......
በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ ...... ......
[ ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ ] " ይላታል መዝ 45 : 9 - 17
ወዳጄ የትንቢቱ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ ራሷ እመቤታችን ምን እንዳለች እንይ
" እነሆም ከዛሬ ጀምሮ [ ትውልድ ሁሉ ] ብፅዕት ይሉኛል " ሉቃ 1 : 48
ይቺ በንጉሡ ቀን የምትቆም ፣ የምድር አሕዛብ ሁሉ በፊቷ የሚማጸኗት ፣ በአባቶሽች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ
የተባለች ፣ ገዢ አርጋ የመሾም ስልጣን የተሰጣት ፣ ትውልድ ሁሉ ስሟን የሚጠሯት የሚያመሰግኗት ንግስት
ማነች ? ለስም አጠራሯ ክብር ምስጋና ይግባትና የንጉሡ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል አይደለችምን ?
ልበ አምላክ የተባለ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ ሰው ሁሉ እናታችን እንደሚላትም ተናግሯል
"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤
እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
ሲል መዝ 88 : 5 ጌታም በእለተ አርብ ተሰቅሎ ሳለ እመቤታችንን ለዮሐንስ
" እናትህ እነኋት " በማለት በሱ አንጻር ለዓለም ሁሉ እናትና እመቤት እርጎ ሰቶናል ዮሐ19 : 27
ፍቁረ እግዚ ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዮ ያያት ፦ " ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፣
ፀሐይን ተጐናጽፋ
@And_Haymanot
የተሃድሶ መናፍቃን በነገረ ድንግል ማርያም ላይ ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች መካከል ቅድስተ ቅዱሳን እናታችንን እመቤት ማለታችን ኢ-መፅሐፍ ቅዱሳዊ አድርገው ይቃወማሉ፡፡ እናት ቤተክርስቲያናችን መፅሐፍ ቅዱስን አብነት አድርጋ ታስተምራለች፡፡
ሲጀምር " እመቤት " ማለት በአንድ ቤተሰብ መካከል አስተዳዳሪና ኃላፊ የሆነች የታላቅ ሴት መጠሪያ መሆኑን
መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል እንጂ መናፍቃን እንደሚሉት ፍፁም ስህተት የሆነ ሴቶች የማይጠሩበት ስም አይደለም ፤እንኳን ጸጋን ሁሉ ለተመላች ፣ ከሴቶች ሁሉ ለተለየች ፣ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይቅርና ብዙ ሴቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው እመቤት ተብለው ተጠርተዋል ።
እስቲ ለአብነት ከመጽሐፉ እየጠቀስን እንይ ፦
፨ የአብርሃም ሚስት ሣራ እመቤት ተብላለች" እርሱም ወደ አጋር ገባ፥ አረገዘችም እንዳረገዘችም
ባየች ጊዜ እመቤትዋን በዓይንዋ አቃለለች።" እንዲል ዘፍ 16 : 4
አጋር ከሣራ ተለይታ በኮበለለች ጊዜ
" የእግዚአብሔር መልአክም ወደ እመቤትሽ ተመለሺ፥ ከእጅዋም በታች ሆነሽ ተገዥ አላት።"ይላል ዘፍ 16 : 9
ወዳጄ የእግዚአብሔር መልአክ የሰው
ልጅ እመቤት ተብሎ ባይጠራ ኖሮ ወደ እመቤትሽ ይል ነበር ?
፨ ወዳጄ የእግዚአብሔር ቃል አገልጋይ ቀጥራ የምታሰራዋን ሴት ምን ብሎ ነው የሚጠራት ?
° የንእማንን ሚስት ታገለግል የነበረችው ብላቴና " [ እመቤትዋንም ] ጌታዬ በሰማርያ ካለው ከነቢዩ ፊት ቢደርስ ኖሮ ከለምጹ በፈወሰው ነበር አለቻት። " 2ኛ. ነገ5 : 3
፨ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ያገልጋይቱ ዓይን ወደ እመቤቷ ነው ይለናል ።
° " እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ የባሪያይቱም ዓይን ወደ [ እመቤትዋ ] እጅ እንደ
ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው። " መዝ 124 :2
፨ ጠቢቡ ሰለሞንም እንዲህ ይላል ፦
° " በሦስት ነገር ምድር ትናወጣለች፥ አራተኛውንም
ትሸከም ዘንድ አይቻላትም።
፨ ባሪያ በነገሠ ጊዜ ፣
፨ ሰነፍም እንጀራ በጠገበ ጊዜ፥
፨ የተጠላች ሴት ባል ባገኘች ጊዜ፥
፨ ሴት ባሪያም [ እመቤቷን ] በወረሰች ጊዜ። "መ. ምሳ 30 : 21 - 23
ወዳጄ ይሄ ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ተጽፎ ሳለ ፤ ወይ ሳያነቡ ወይ ሳይጠይቁ ገና ለገና እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመቃወም ሲባል ብቻ "ለወንድ ጌታ ለሴት እመቤት እንላለን ይሄ አባባል ፍጹም ስህተት ነው " የሚለውን የአጋንንት ስብከት ከየት
አመጣችሁት ? እውነት እናንተ እንደምትሉት ቢሆን ኖሮ እነሣራ ፣ የንእማን ሚስት እና ሌሎቹም ሴቶች ለምን እመቤት ተባሉ ? እመቤት ማለት የማይገባ ከሆነ የእግዚአብሔር መልአክ ፣ ቅዱስ ዳዊት ፣ ጠቢቡ ሰለሞን
ሴቶቹን ለምን እመቤት ብለው ጠሯቸው ? ነው መጽሐፉ ተሳስቶ ይሆን ?
መቼም ምክንያት እየፈጠሩ ለመካድ ለማስካድ እንጂ ለማመን አልተፈጠራችሁምና ይሄ በብሉይ ኪዳን እንጂ በአዲስ ኪዳን አይባልም ካላችሁ ማስረጃ ልስጥ ፤ ወዳጄ ፍቁረ እግዚ ቅዱስ ዮሐንስ 2ኛ የዮሐንስ መልእክቱን የጻፈው ለማነው ? አታቀውቁትም እንጂ ሲጀመር ብታውቁት ቃሉን እንደዚህ አንጋዳችሁ አወላግዳችሁ ባልጻፋችሁም
ነበር ፤ ታሪኩ ሰፊ ሲሆን ነገር ላለማርዘምና ቀጥታ ለጥያቄው
መልስ ለመስጠት ያህል ብቻ ቅዱስ ዮሐንስ ይቺን ሁለተኛ መልእክቱን የጻፈው ጣኦት ያመልኩ የነበሩ የነገሥታቱንና
የመኳንንቱን ልጆች ሞግዚት ሆና ታሳድግ ለነበረችው ሮምና ለምትባል ሴት ነው ።
ቅዱስ ዮሐንስና አብሮኮሮስ አስተምረው አሳምነው አጥምቀው ከአምልኮ ጣኦት ወደ ወገኛይቱ ወደ ክርስትና እምነት ከመለሷት በኃላ ለስብከት ወደ ሌላ አገር ይሄዳሉ፤ ከሄዱም በኃላ ግን በእምነቷ እንድትጸና እና እንድትበረታ ሲል ይቺን ሁለተኛይቱ የተባለችውን የዮሐንስ መልእክቱን የጻፈላት ። ወዳጄ ቅዱስ ዮሐንስ ለዚህች በነገሥታቱና በመኮንንቱ ቤት በሰራተኝነት ፣ በሞግዚትነት ለምታገለግለው ሮምና
ለተባለችው መልእክቱን ሲጽፍ ምን እንዳላት ታውቃለህ ? [ እመቤት ሆይ ] እያለ ነበር አክብሮ ይጠራት የነበረው ።
እስቲ የጻፈውን ቃል በቃል እንየው ፦
" በእኛ ስለሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ስለሚሆን እውነት፥ እኔ ሽማግሌው በእውነት ለምወዳቸውና እኔ ብቻ
ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ደግሞ ለሚወዱአቸው ለተመረጠች እመቤትና ለልጆችዋ "ይላል 2ኛ.ዮሐ 1 : 1 - 2
ወዳጄ እመቤት ብቻ አይደለም ያላት
" የተመረጠች እመቤት " ማለቱን አስተውል ። ሲቀጥል ቁ. 5 ላይ
" አሁንም፥ እመቤት ሆይ፥ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ እለምንሻለሁ፤ ይህች ከመጀመሪያ በእኛ ዘንድ የነበረች
ትእዛዝ ናት እንጂ አዲስ ትእዛዝን እንደምጽፍልሽ አይደለም። "ይላታል 2ኛ. ዮሐ 1 : 5 ወዳጄ የሕግ ፍጻሜና የምትበልጠው ጸጋ የተባለች ፍቅር
ይኖራቸው ዘንድ ሲጽፍላት
" እመቤት ሆይ ... እለምንሻለሁ " ብሎ ሲማጸናት ታያለህ ?
ታዲያ እንደ እናንተ አገላለጽ የሰው ልጅ ጌታና እመቤት ተብሎ የማይጠራ ፍጹም የሆነ ስህተት ከሆነ ቅዱስ ዮሐንስ ሮምናን ለምን እመቤት ሆይ እያለ ጠራት ? እናንተ ከዮሐንስ ትበልጣላችሁ?
አናንተ ናችሁ እኛ ነን በመጽሐፍ ቅዱስ የማናምነው? ከላይ ያየናቸው የብዙ ሴቶች እና የሮምና እመቤት መባል
ፍጹም ስህተት ያልሆነ ፤ የሰማይና የምድር ንጉሥ እናት የሆነች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እመቤት መባል እንዴት ሆኖ ነው ፍጹም ስህተት የሚሆነው ?
በአዳምና በሔዋን አማካኝነት ወደ ዓለም የገባውን መርገም የሻረ ጌታ እግዚአብሔር ከእርሷ በመወለዱ እመቤታችንን እግዝእተ በዙኃን [ የብዙኅን እመቤት ]
ትባላለች ። እንዲሁም ዓለም ሁሉ በዳነበት በክርስቶስ የማዳን ሥራ ያመንን ክርስቲያኖች ሁሉ በክርስቶስ አንድ
ቤተሰብ በመሆናችን ቅድስት እናቱ ድንግል ማርያምእመቤታችን ናት ።
ወዳጄ ፦ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ እመቤታችን እንደ ሌሎቹ ሴቶች እመቤት ብቻ አላላትም ንግስት
እንጂ !" በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ
ትቆማለች ......
የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ ( ይለምናሉ ይማጸናሉ )......
በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ ...... ......
[ ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ ] " ይላታል መዝ 45 : 9 - 17
ወዳጄ የትንቢቱ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ ራሷ እመቤታችን ምን እንዳለች እንይ
" እነሆም ከዛሬ ጀምሮ [ ትውልድ ሁሉ ] ብፅዕት ይሉኛል " ሉቃ 1 : 48
ይቺ በንጉሡ ቀን የምትቆም ፣ የምድር አሕዛብ ሁሉ በፊቷ የሚማጸኗት ፣ በአባቶሽች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ
የተባለች ፣ ገዢ አርጋ የመሾም ስልጣን የተሰጣት ፣ ትውልድ ሁሉ ስሟን የሚጠሯት የሚያመሰግኗት ንግስት
ማነች ? ለስም አጠራሯ ክብር ምስጋና ይግባትና የንጉሡ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል አይደለችምን ?
ልበ አምላክ የተባለ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ ሰው ሁሉ እናታችን እንደሚላትም ተናግሯል
"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤
እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
ሲል መዝ 88 : 5 ጌታም በእለተ አርብ ተሰቅሎ ሳለ እመቤታችንን ለዮሐንስ
" እናትህ እነኋት " በማለት በሱ አንጻር ለዓለም ሁሉ እናትና እመቤት እርጎ ሰቶናል ዮሐ19 : 27
ፍቁረ እግዚ ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዮ ያያት ፦ " ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፣
ፀሐይን ተጐናጽፋ
❤1
፣ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት ፣ በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት
አንዲት ሴት ነበረች......
እርስዋም ፀንሳ ነበር፥ ምጥም ተይዛ ልትወልድ ተጭንቃ ጮኸች......
ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕፃንዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ። አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸው ዘንድ ያለውን
ልጅ ወንድ ልጅ ወለደች "ራዕ 12 : 1-5
ሲል የገለጻት የከበረች ሴት ማነች ?
ከንግስቲቱ ከእመቤታችን ውጭ ፀሐይን የተጎናጸፈች ፣ ጨረቃን ከእግሯ በታች ያደረገች ፣ በራሷ ላይ አሥራ
ሁለት አክሊል የደፋች ፣ አሕዛብን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛውን ጌታ የወለደች ማናት ? ወዳጄ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ግሩምና ድንቅ አርጎ ፣ የዚህ ዓለም ገዢ ( ጌታ ) አርጎ እንደፈጠረው ሳታውቁ ነው ፤ ወንድ ጌታ ሴት እመቤት ልትባል አይገባም ፍጹም ስህተት ነው የምትሉት ? የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ
ተፈጠረ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ታውቃላችሁ? እግዚአብሔር የሰማይና የምድር ገዢ ( ጌታ ) እንደሆነ ሁሉ ሰውም የዚህ ዓለም ገዢ ( ጌታ ) ሆኖ ተፈጠረ ማለት ነው ።
" እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ
የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።"
እንዲል ዘፍ 1 : 26 በተለይ " ይግዙ " የምትለዋ ቃል የወንዱን ጌትነት የሴቷን እመቤትነት የሚያሳይ ቃል ነው ።
አንተ ሰነፍ እንኳን የከበረው የሰው ልጅ አይደለም ሰይጣን ዲያቢሎስ የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ እንደሚባል
እንኳን አታውቅም ? " አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም
ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል " እንዲል
ዮሐንስ 12 : 31 , 2ኛ. ቆሮ 4 : 4
መቼም ይሄንን የማታውቅ ደካማ ሰይጣን ዲያቢሎስ ለምን የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ ተባለ ? ተብለህ
ብትጠየቅ የባጥ የቋጡን እየቀባጠርክ ሰው ስታደክም ትውላለህ እንጂ መልስ የለህም ፤ የጸጋው ዙፋን የምስጢሩ ግምጃ ቤት ከሆነች ከተዋህዶ ተማር ፦
ሰይጣን ዲያቢሎስ የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ የተባለው ፤ የዚህች ዓለም ገዢ የሰው ልጅ የፈጣሪውን ትዕዛዝ አፍርሶና ኃጢአት ሰርቶ ስለበደለ ራሱን ለሰይጣን ከማስገዛቱም በላይ የሚገዛትን ዓለም ይዞ በሰይጣን
ቁጥጥር ሥር በመዋሉ ዓለማችን ከጌታዋ [ ከሰው ልጅ ] ጋር ለሰይጣን ተገዢ በመሆኗ ነው ሰይጣን ዲያቢሎስ
የዚህ ዓለም ገዢ ለመባል የበቃው ።
መቼም አናንተ አይታክቴ ሰው ናችሁና ሌላ ሰይጣናዊ ምክንያት እንደምትፈጥሩ አብሬ ስለኖርኩ ፀባያችሁን ልቅም አርጌ አቀዋለሁ ፣
የማታውቁትን ቢነግሯችሁ አትቀበሉም እሺ ተናገሩ ብትባሉ መልስ የላችሁም ፤ አሁንም እኔ ቤተ ክርስቲያን ያስተማረችኝን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያገኘሁትን እውነተኛውን ነገርኳችሁ ልክ አይደለም የምትሉ ከሆነ እሺ እስቲ
አስተምሩን ቅዱስ ዮሐንስ ሁለተኛ መልእክቱን ለማነው የጻፈው ?
ለምን እመቤት ሆይ አላት ? ንግሥት የተባለች ማናት ? ለምን ንግስት ተባለች ? የልጅ ልጅ ስሟን የሚጠራው
ትውልድ ሁሉ ብጽእት የሚሏት ? በንጉሱ ቀኝ ያለችው የምድር አህዛብ በፊቷ የሚማልሉላት ? ፀሐይን የተጎናጸፈች ፣ ጨረቃን የተጫማች ፣ አሥራ ሁለቱን
ከዋክብት እንደ አክሊል የደፋች ይቺ የከበረች ሴት ማናት ?
ይቆየን
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
አንዲት ሴት ነበረች......
እርስዋም ፀንሳ ነበር፥ ምጥም ተይዛ ልትወልድ ተጭንቃ ጮኸች......
ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕፃንዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ። አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸው ዘንድ ያለውን
ልጅ ወንድ ልጅ ወለደች "ራዕ 12 : 1-5
ሲል የገለጻት የከበረች ሴት ማነች ?
ከንግስቲቱ ከእመቤታችን ውጭ ፀሐይን የተጎናጸፈች ፣ ጨረቃን ከእግሯ በታች ያደረገች ፣ በራሷ ላይ አሥራ
ሁለት አክሊል የደፋች ፣ አሕዛብን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛውን ጌታ የወለደች ማናት ? ወዳጄ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ግሩምና ድንቅ አርጎ ፣ የዚህ ዓለም ገዢ ( ጌታ ) አርጎ እንደፈጠረው ሳታውቁ ነው ፤ ወንድ ጌታ ሴት እመቤት ልትባል አይገባም ፍጹም ስህተት ነው የምትሉት ? የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ
ተፈጠረ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ታውቃላችሁ? እግዚአብሔር የሰማይና የምድር ገዢ ( ጌታ ) እንደሆነ ሁሉ ሰውም የዚህ ዓለም ገዢ ( ጌታ ) ሆኖ ተፈጠረ ማለት ነው ።
" እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ
የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።"
እንዲል ዘፍ 1 : 26 በተለይ " ይግዙ " የምትለዋ ቃል የወንዱን ጌትነት የሴቷን እመቤትነት የሚያሳይ ቃል ነው ።
አንተ ሰነፍ እንኳን የከበረው የሰው ልጅ አይደለም ሰይጣን ዲያቢሎስ የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ እንደሚባል
እንኳን አታውቅም ? " አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም
ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል " እንዲል
ዮሐንስ 12 : 31 , 2ኛ. ቆሮ 4 : 4
መቼም ይሄንን የማታውቅ ደካማ ሰይጣን ዲያቢሎስ ለምን የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ ተባለ ? ተብለህ
ብትጠየቅ የባጥ የቋጡን እየቀባጠርክ ሰው ስታደክም ትውላለህ እንጂ መልስ የለህም ፤ የጸጋው ዙፋን የምስጢሩ ግምጃ ቤት ከሆነች ከተዋህዶ ተማር ፦
ሰይጣን ዲያቢሎስ የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ የተባለው ፤ የዚህች ዓለም ገዢ የሰው ልጅ የፈጣሪውን ትዕዛዝ አፍርሶና ኃጢአት ሰርቶ ስለበደለ ራሱን ለሰይጣን ከማስገዛቱም በላይ የሚገዛትን ዓለም ይዞ በሰይጣን
ቁጥጥር ሥር በመዋሉ ዓለማችን ከጌታዋ [ ከሰው ልጅ ] ጋር ለሰይጣን ተገዢ በመሆኗ ነው ሰይጣን ዲያቢሎስ
የዚህ ዓለም ገዢ ለመባል የበቃው ።
መቼም አናንተ አይታክቴ ሰው ናችሁና ሌላ ሰይጣናዊ ምክንያት እንደምትፈጥሩ አብሬ ስለኖርኩ ፀባያችሁን ልቅም አርጌ አቀዋለሁ ፣
የማታውቁትን ቢነግሯችሁ አትቀበሉም እሺ ተናገሩ ብትባሉ መልስ የላችሁም ፤ አሁንም እኔ ቤተ ክርስቲያን ያስተማረችኝን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያገኘሁትን እውነተኛውን ነገርኳችሁ ልክ አይደለም የምትሉ ከሆነ እሺ እስቲ
አስተምሩን ቅዱስ ዮሐንስ ሁለተኛ መልእክቱን ለማነው የጻፈው ?
ለምን እመቤት ሆይ አላት ? ንግሥት የተባለች ማናት ? ለምን ንግስት ተባለች ? የልጅ ልጅ ስሟን የሚጠራው
ትውልድ ሁሉ ብጽእት የሚሏት ? በንጉሱ ቀኝ ያለችው የምድር አህዛብ በፊቷ የሚማልሉላት ? ፀሐይን የተጎናጸፈች ፣ ጨረቃን የተጫማች ፣ አሥራ ሁለቱን
ከዋክብት እንደ አክሊል የደፋች ይቺ የከበረች ሴት ማናት ?
ይቆየን
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት