ጾመ ፍልሰታ
ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገው ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት ኦርቶዶክሳዊያን የሚጾሙት ጾም ነው።
ፍልሰታ የግዕዝ ቃል ሆኖ ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል።
እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለሆነ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን 48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች።
ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት ወደ መኖሪያ ቤቷ (የዮሐንስ ቤት) መጥተው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች አስከሬኗን ገንዘውና ከፍነው ወስደው
ለመቅበር ወደ ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤ ይህንም ማድረግ
የፈለጉት የሐዋርያት ትምህርት የጌታችን ከሞት መነሣትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ
እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። የፈሩት ይነግሣል የጠሉት ይወርሳል እንዲሉ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት
አይቀሬ ሆኗል።
አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም ታውፊኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ
ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነትና ክብር ለመመስከር በቅቷል።
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ በዕፀ ሕይወት ሥር ይቀመጥ እንጂ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር
ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ዮሐንስ ስለሥጋዋ ነግሯቸዋል።
ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለመኑ ለስድስት ወራት ከአሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህ በኋላም ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው
ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን
አምጥቶ ስለሰጣቸው ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች።
ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት
አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ ፪፥፲/።
እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ ከሀገረ ስብከቱ /ሕንድ/ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ
ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በስተቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት
እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን /የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው።
ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ
ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት
አስረዱት። እርሱ ግን ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን
ለማሳመን መቃብሯን ለማሳየት ወሰዱት ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት
የነበረውን ጨርቅ/ የራሱን ድርሻ አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው ዛሬም ካህናቱ ከእጅ መስቀላቸው ጋር መሐረብ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ
ነው። ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት
በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለሁለተኛ ጊዜ ለሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ
ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል።
በአጠቃላይ የእመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት መታየት፣ የሥጋዋና የነፍሷ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፍልሰት ሲባል ከዚህ የተነሣ የነሐሴ ጾም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ሐዋርያት ያገኙትን በረከት ለማግኘት ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
በዶ/ር ሙሉጌታ ማርቆስ
@And\Haymanot
@And_Haymanot_bot
ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገው ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት ኦርቶዶክሳዊያን የሚጾሙት ጾም ነው።
ፍልሰታ የግዕዝ ቃል ሆኖ ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል።
እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለሆነ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን 48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች።
ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት ወደ መኖሪያ ቤቷ (የዮሐንስ ቤት) መጥተው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች አስከሬኗን ገንዘውና ከፍነው ወስደው
ለመቅበር ወደ ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤ ይህንም ማድረግ
የፈለጉት የሐዋርያት ትምህርት የጌታችን ከሞት መነሣትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ
እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። የፈሩት ይነግሣል የጠሉት ይወርሳል እንዲሉ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት
አይቀሬ ሆኗል።
አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም ታውፊኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ
ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነትና ክብር ለመመስከር በቅቷል።
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ በዕፀ ሕይወት ሥር ይቀመጥ እንጂ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር
ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ዮሐንስ ስለሥጋዋ ነግሯቸዋል።
ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለመኑ ለስድስት ወራት ከአሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህ በኋላም ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው
ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን
አምጥቶ ስለሰጣቸው ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች።
ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት
አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ ፪፥፲/።
እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ ከሀገረ ስብከቱ /ሕንድ/ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ
ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በስተቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት
እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን /የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው።
ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ
ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት
አስረዱት። እርሱ ግን ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን
ለማሳመን መቃብሯን ለማሳየት ወሰዱት ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት
የነበረውን ጨርቅ/ የራሱን ድርሻ አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው ዛሬም ካህናቱ ከእጅ መስቀላቸው ጋር መሐረብ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ
ነው። ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት
በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለሁለተኛ ጊዜ ለሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ
ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል።
በአጠቃላይ የእመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት መታየት፣ የሥጋዋና የነፍሷ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፍልሰት ሲባል ከዚህ የተነሣ የነሐሴ ጾም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ሐዋርያት ያገኙትን በረከት ለማግኘት ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
በዶ/ር ሙሉጌታ ማርቆስ
@And\Haymanot
@And_Haymanot_bot
የያረድ ዉብ ዜማ
የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ ስጦታየ ነሺ / 2/
በምን አንደበቴ እንደምን ባለ ቃል ማርያም ልበልሺ/ 2
ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሺ
ድንግል ሆይ እናተ አምሳያም የለሺ
ማርያም ድንግል እረዳተ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ
ታምርሺን በአይነ አይቻለሁ
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ
አዝ - - -
የእግዚአብሀር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እነም ቢያስፈራኚ
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና
ማርያም ልበልሽ በትህትና
አዝ - - -
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር
ጨለማው ከፊተ ተገፈፈ
ማርያም በምልጃሽ ልበ አረፈ
ከጎነ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ ስጦታየ ነሺ / 2/
በምን አንደበቴ እንደምን ባለ ቃል ማርያም ልበልሺ/ 2
ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሺ
ድንግል ሆይ እናተ አምሳያም የለሺ
ማርያም ድንግል እረዳተ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ
ታምርሺን በአይነ አይቻለሁ
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ
አዝ - - -
የእግዚአብሀር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እነም ቢያስፈራኚ
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና
ማርያም ልበልሽ በትህትና
አዝ - - -
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር
ጨለማው ከፊተ ተገፈፈ
ማርያም በምልጃሽ ልበ አረፈ
ከጎነ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት????
❖ @And_Haymanot ❖
አንድ እህታችን በውሥጥ የላከችልን መልዕክት ነው፡፡
ስለ እመቤታችን ሲነሳ አይናቸው ደም የሚለብሰው የተሃድሶ መናፍቃን ዛሬም ከእናታችን እቅፍ ሊለዩን ተነስተዋል ከጥፋት ትምህርታቸ አንዱ
ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት። በዛ ዘመን ብንኖር ከእኛ መሃል ከአንዳችን ኢየሱስ ይወለድ ነበር ብለው ያስተምራሉ ያምናሉ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስን ከመውለድዋ በፊት በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠች ሴት ናት ።
እንኳን የአምላክ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም አይደለም ማንኛችንም እግዚአብሔር የፈጠረን ፍጡር ወደዚህ አለም ከመምጣታችን በፊት ለምን አላማ እንደምንወለድ
እንኳን ገና ሳንፈጠር እግዚአብሔር ያውቃል:: ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን ኤርምያስ 1:5 እንዲህ ይላል ።
የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ ከማህፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ
ለአህዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ለአምላክ እናት እንድትሆን ገና ሳትፈጠር እግዚአብሔር የመረጣት ሴት ናት።
ከእሷም ባይሆን ከሌላ ይወለድ ነበር ለሚሉ የጥፋት ልጆች ከእግዚአብሔር አላማና ሃሳብ ጋር የተጣሉ የእግዚአብሔርን ሃሳብ በራሳቸው አመለካከት እና ሃሳብ ለመቀየር የሚያስቡ ደፋሮች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም
እንዲወለድ ነበር የእግዚአብሔር አላማ::
ከእሷ ባይሆን ለሚሉት የእግዚአብሔር ሀሳብ ሳይሆን የቀረበት ግዜ የለምና ከእሷ ውጭ ከማንም ሊሆን አይችልም። የእግዚአብሔር ሃሳብ ከቅድስት ድንግል ማርያም እንዲወለድ እንጂ ሌሎች እንደሚፈላሰፉት ከአዳራሽ ጨፋሪዎቻቸው ሴቶች መሃከል ኢየሱስ ሊወለድ አይችልም::
ከፍጥረት ሁሉ ፣የአምላክ እናት እንድትሆን የተመረጠች ቅድስት ማርያም ብቻ ናት። ለመዳናችን ምክንያት ለሆነች ከሴቶች ሁሉ ለተለየች የአምላክ እናት ክብር ይገባታል ።
በተጨማሪም ሊታወቅ የሚገባው ማንኛውም ሠው በነብያትና በሐዋርያት መንገድ መጓዝ ከቻለ ሐዋርያት የደረሱበትን የክብር ደረጃ መድረስ ይችላል፡፡ ነገር ግን በክብር ላይ ክብር ብናገኝ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሠኝ ስራ ብንሠራ እንኳ ድንግል ማርያም የደረሰችበት የክብር ደረጃ ላይ መድረስ
የሚችል ሰው ማንም የለም፡፡ ወደፊትም እንደዚህ አይነት ክብር እና ጸጋ ለማንም አይሰጥም፡፡፡፡
.....ይቆየን ከሰሞኑ እመቤታችን አንዲት ድንግል እናት ሥለመሆኗ በሰፊው እንመለሳለን፡፡
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን
፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖
ከዋክብት የሚያመሰግኑት
በስማቸውም የሚጠራቸው:
የፀጋው ብዛት የማይታወቅ
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን እንደገለጽክላቸው
ለእኛም ግለጽልን።
አሜን አሜን አሜን!!!
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
አንድ እህታችን በውሥጥ የላከችልን መልዕክት ነው፡፡
ስለ እመቤታችን ሲነሳ አይናቸው ደም የሚለብሰው የተሃድሶ መናፍቃን ዛሬም ከእናታችን እቅፍ ሊለዩን ተነስተዋል ከጥፋት ትምህርታቸ አንዱ
ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት። በዛ ዘመን ብንኖር ከእኛ መሃል ከአንዳችን ኢየሱስ ይወለድ ነበር ብለው ያስተምራሉ ያምናሉ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስን ከመውለድዋ በፊት በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠች ሴት ናት ።
እንኳን የአምላክ ማደሪያ የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም አይደለም ማንኛችንም እግዚአብሔር የፈጠረን ፍጡር ወደዚህ አለም ከመምጣታችን በፊት ለምን አላማ እንደምንወለድ
እንኳን ገና ሳንፈጠር እግዚአብሔር ያውቃል:: ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን ኤርምያስ 1:5 እንዲህ ይላል ።
የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ ከማህፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ
ለአህዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።
-ቅድስት ድንግል ማርያም ለአምላክ እናት እንድትሆን ገና ሳትፈጠር እግዚአብሔር የመረጣት ሴት ናት።
ከእሷም ባይሆን ከሌላ ይወለድ ነበር ለሚሉ የጥፋት ልጆች ከእግዚአብሔር አላማና ሃሳብ ጋር የተጣሉ የእግዚአብሔርን ሃሳብ በራሳቸው አመለካከት እና ሃሳብ ለመቀየር የሚያስቡ ደፋሮች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም
እንዲወለድ ነበር የእግዚአብሔር አላማ::
ከእሷ ባይሆን ለሚሉት የእግዚአብሔር ሀሳብ ሳይሆን የቀረበት ግዜ የለምና ከእሷ ውጭ ከማንም ሊሆን አይችልም። የእግዚአብሔር ሃሳብ ከቅድስት ድንግል ማርያም እንዲወለድ እንጂ ሌሎች እንደሚፈላሰፉት ከአዳራሽ ጨፋሪዎቻቸው ሴቶች መሃከል ኢየሱስ ሊወለድ አይችልም::
ከፍጥረት ሁሉ ፣የአምላክ እናት እንድትሆን የተመረጠች ቅድስት ማርያም ብቻ ናት። ለመዳናችን ምክንያት ለሆነች ከሴቶች ሁሉ ለተለየች የአምላክ እናት ክብር ይገባታል ።
በተጨማሪም ሊታወቅ የሚገባው ማንኛውም ሠው በነብያትና በሐዋርያት መንገድ መጓዝ ከቻለ ሐዋርያት የደረሱበትን የክብር ደረጃ መድረስ ይችላል፡፡ ነገር ግን በክብር ላይ ክብር ብናገኝ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሠኝ ስራ ብንሠራ እንኳ ድንግል ማርያም የደረሰችበት የክብር ደረጃ ላይ መድረስ
የሚችል ሰው ማንም የለም፡፡ ወደፊትም እንደዚህ አይነት ክብር እና ጸጋ ለማንም አይሰጥም፡፡፡፡
.....ይቆየን ከሰሞኑ እመቤታችን አንዲት ድንግል እናት ሥለመሆኗ በሰፊው እንመለሳለን፡፡
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን
፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖
ከዋክብት የሚያመሰግኑት
በስማቸውም የሚጠራቸው:
የፀጋው ብዛት የማይታወቅ
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን እንደገለጽክላቸው
ለእኛም ግለጽልን።
አሜን አሜን አሜን!!!
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
❖ @And_Haymanot ❖
ሐይማኖት አይወረስም?
@And_Haymanot
ተወዳጆች የተሃድሶ መናፍቃን ሃይማኖት አያስፈልግም፤አያድንም፤አይወረስም በማለት ብዙዎችን ለማደናገር ይሞክራሉ ከዚህ በፊት በስፋት የዳሰስነው ርዕሳችን ቢሆንም በውስጥ ለጠየቀን ወንድማችን እነሆ ብለናል
ሐይማኖት አይወረስም ላልከን እንዲህ የምናምነውንም እንመሠክራለን! > እንግዲያውስ ከኃይማኖት በላይ ሊያወርሱት እና ሊወርሱት የተገባ የከበረ ነገር በዚች አለም የለም። ሰው መልካም መልካሙን ነገር ለልጆቹ ያወርሳል ከመልካም ስጦታዎች ሁሉ የሚልቀውን የዘላለም ሕይወት የሚገኝበትን ሐይማኖት ከማውረስ የበለጠ ታላቅ ውርስ እንዳውም በጭራሽ አይገኝም።
ሰው በምድር ላይ ለልጆቹ የሚሆን ታላቅ መኖሪያ ቢያወርስ ነገር ግን የዘላለም ሕይወት የሚያገኙበትን ሐይማኖቱን ግን ባያወርስ ምን ይረባቸዋል! ??
ሁለት ነገርን አደፈረስክ! መጀመሪያ ሐይማኖት ሊወረስ የተፈቀደ መሆኑን ካድክ ሲቀጥል ደግሞ በገዛ ድምዳሜክ ገባህና ሐዋርያት ከሀድያን ናቸው አልክ! እግዚአብሔር ይቅር ይበልህ።
አስቀድመህ በራስህ አላዋቂነት የደመደምከው ድምዳሜ ላይ የተመረጡትን ሁሉ አጋጭተሀል።
በመሰረቱ ሀይማኖት ለሰው ልጆች የተሰጠችው ልንጠብቃት እና ለትውልድም ልናወርሳት ነው።
አብርሃም አባታችን ለአይሁድም ሆነ ለሀዲስ ኪዳን ህዝቦች አባት ነው። ከህግ ለሆኑት የመገረዝ አባት ነበረ። ከእምነት ለሆንነው ደግሞ የእምነት አባት ነው። የፃድቅ አብርሃም
ሕይወት ለእኛ ምሳሌ ነው። አብርሃም እግዚአብሔር ን አመነ ፅድቅም ሆኖ ተቆጠረለት ነገር ግን ይህ ብቻ አልነበረም ጉዳዩ ምክንያቱም እግዚአብሔር ለአብርሃም ትዛዝን ሲሰጠው ልጆችህ ቃል ኪዳኔን እንዲጠብቁ አድርግ በሚል ጠንካራ
ማሰሪያም ጭምር ነው። አብርሃምም በቤቱ ለተወለዱት ልጆች ሁሉ ይህን የእግዚአብሔር ቃልኪዳን ገና በተወለዱ በ8 ቀናቸው ጀምሮ ይፈፅምላቸው ነበር። የእርሱን ሐይማኖት ለልጆቹ ገና በስምንት ቀን ጨቅላነታቸው እያሉ ጀምሮ እንዲቀበሉ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ስለሆነ ነው። ልጆችም በአባቶቻቸው
ሐይማኖት ተወስነው እንዲኖሩ ነው የጌታ ትእዛዝ። ስለዚህ ሐይማኖት ይወረሳል። ከሐይማኖት የበለጠ ለልጅ ሊያወርሱት የሚገባ መተኪያ የሌለው ውድ ነገርስ ከየት ይገኛል???
ዘፍጥረት 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ ቃል ኪዳኔንም በእኔና በአንተ መካከል ከአንተም በኋላ ከዘርህ ጋር በትውልዳቸው ለዘላለም ኪዳን አቆማለሁ፥
#ለአንተና_ከአንተ_በኋላ_ለዘርህ_አምላክ_እሆን_ዘንድ ።
⁸ በእንግድነት የምትኖርባትን ምድር፥ የከነዓን ምድር ሁሉ፥ለዘላለም ግዛት ይሆንህ ዘንድ ለአንተና ከአንተ በኋላ ለዘርህ እሰጣለሁ አምላክም እሆናቸዋለሁ።
⁹ እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ አንተ ደግሞ ቃል ኪዳኔን ትጠብቃለህ፥ አንተ ከአንተም በኋላ ዘርህ በትውልዳቸው።
¹⁰ በእኔና በአንተ መካከል፥ ከአንተም በኋላ በዘርህ መካከል የምትጠብቁት ቃል ኪዳኔ ይህ ነው፤ ከእናንተ ወንድ ሁሉ ይገረዝ።
¹¹ የቍልፈታችሁንም ሥጋ ትገረዛላችሁ፤ በእኔና በእናንተ
መካከል ላለውም ቃል ኪዳን ምልክት ይሆናል።
¹² #የስምንት_ቀን_ልጅ_ይገረዝ ፤ በቤት የተወለደ ወይም ከዘራችሁ ያይደለ በብርም ከእንግዳ ሰው የተገዛ፥ ወንድ ሁሉ በትውልዳችሁ ይገረዝ።
¹³ በቤትህ የተወለደ በብርህም የተገዛ ፈጽሞ ይገረዝ። ቃል ኪዳኔም በሥጋችሁ የዘላለም ቃል ኪዳን ይሆናል።
¹⁴ የቍልፈቱን ሥጋ ያልተገረዘ ቈላፍ ሰው ሁሉ፥ ያች ነፍስ ከወገንዋ ተለይታ ትጥፋ፤ ቃል ኪዳኔን አፍርሳለችና።//
…
ሮሜ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ
አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው።
¹³ የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው
የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም።
¹⁴ ከሕግ የሆኑትስ ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኖአል
የተስፋውም ቃል ተሽሮአል፤
¹⁵ ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት መተላለፍ የለም።
¹⁶-¹⁷ ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ
ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት #የሁላችን #አባት #ነው ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
@And_Haymanot
ተወዳጆች የተሃድሶ መናፍቃን ሃይማኖት አያስፈልግም፤አያድንም፤አይወረስም በማለት ብዙዎችን ለማደናገር ይሞክራሉ ከዚህ በፊት በስፋት የዳሰስነው ርዕሳችን ቢሆንም በውስጥ ለጠየቀን ወንድማችን እነሆ ብለናል
ሐይማኖት አይወረስም ላልከን እንዲህ የምናምነውንም እንመሠክራለን! > እንግዲያውስ ከኃይማኖት በላይ ሊያወርሱት እና ሊወርሱት የተገባ የከበረ ነገር በዚች አለም የለም። ሰው መልካም መልካሙን ነገር ለልጆቹ ያወርሳል ከመልካም ስጦታዎች ሁሉ የሚልቀውን የዘላለም ሕይወት የሚገኝበትን ሐይማኖት ከማውረስ የበለጠ ታላቅ ውርስ እንዳውም በጭራሽ አይገኝም።
ሰው በምድር ላይ ለልጆቹ የሚሆን ታላቅ መኖሪያ ቢያወርስ ነገር ግን የዘላለም ሕይወት የሚያገኙበትን ሐይማኖቱን ግን ባያወርስ ምን ይረባቸዋል! ??
ሁለት ነገርን አደፈረስክ! መጀመሪያ ሐይማኖት ሊወረስ የተፈቀደ መሆኑን ካድክ ሲቀጥል ደግሞ በገዛ ድምዳሜክ ገባህና ሐዋርያት ከሀድያን ናቸው አልክ! እግዚአብሔር ይቅር ይበልህ።
አስቀድመህ በራስህ አላዋቂነት የደመደምከው ድምዳሜ ላይ የተመረጡትን ሁሉ አጋጭተሀል።
በመሰረቱ ሀይማኖት ለሰው ልጆች የተሰጠችው ልንጠብቃት እና ለትውልድም ልናወርሳት ነው።
አብርሃም አባታችን ለአይሁድም ሆነ ለሀዲስ ኪዳን ህዝቦች አባት ነው። ከህግ ለሆኑት የመገረዝ አባት ነበረ። ከእምነት ለሆንነው ደግሞ የእምነት አባት ነው። የፃድቅ አብርሃም
ሕይወት ለእኛ ምሳሌ ነው። አብርሃም እግዚአብሔር ን አመነ ፅድቅም ሆኖ ተቆጠረለት ነገር ግን ይህ ብቻ አልነበረም ጉዳዩ ምክንያቱም እግዚአብሔር ለአብርሃም ትዛዝን ሲሰጠው ልጆችህ ቃል ኪዳኔን እንዲጠብቁ አድርግ በሚል ጠንካራ
ማሰሪያም ጭምር ነው። አብርሃምም በቤቱ ለተወለዱት ልጆች ሁሉ ይህን የእግዚአብሔር ቃልኪዳን ገና በተወለዱ በ8 ቀናቸው ጀምሮ ይፈፅምላቸው ነበር። የእርሱን ሐይማኖት ለልጆቹ ገና በስምንት ቀን ጨቅላነታቸው እያሉ ጀምሮ እንዲቀበሉ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ስለሆነ ነው። ልጆችም በአባቶቻቸው
ሐይማኖት ተወስነው እንዲኖሩ ነው የጌታ ትእዛዝ። ስለዚህ ሐይማኖት ይወረሳል። ከሐይማኖት የበለጠ ለልጅ ሊያወርሱት የሚገባ መተኪያ የሌለው ውድ ነገርስ ከየት ይገኛል???
ዘፍጥረት 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ ቃል ኪዳኔንም በእኔና በአንተ መካከል ከአንተም በኋላ ከዘርህ ጋር በትውልዳቸው ለዘላለም ኪዳን አቆማለሁ፥
#ለአንተና_ከአንተ_በኋላ_ለዘርህ_አምላክ_እሆን_ዘንድ ።
⁸ በእንግድነት የምትኖርባትን ምድር፥ የከነዓን ምድር ሁሉ፥ለዘላለም ግዛት ይሆንህ ዘንድ ለአንተና ከአንተ በኋላ ለዘርህ እሰጣለሁ አምላክም እሆናቸዋለሁ።
⁹ እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ አንተ ደግሞ ቃል ኪዳኔን ትጠብቃለህ፥ አንተ ከአንተም በኋላ ዘርህ በትውልዳቸው።
¹⁰ በእኔና በአንተ መካከል፥ ከአንተም በኋላ በዘርህ መካከል የምትጠብቁት ቃል ኪዳኔ ይህ ነው፤ ከእናንተ ወንድ ሁሉ ይገረዝ።
¹¹ የቍልፈታችሁንም ሥጋ ትገረዛላችሁ፤ በእኔና በእናንተ
መካከል ላለውም ቃል ኪዳን ምልክት ይሆናል።
¹² #የስምንት_ቀን_ልጅ_ይገረዝ ፤ በቤት የተወለደ ወይም ከዘራችሁ ያይደለ በብርም ከእንግዳ ሰው የተገዛ፥ ወንድ ሁሉ በትውልዳችሁ ይገረዝ።
¹³ በቤትህ የተወለደ በብርህም የተገዛ ፈጽሞ ይገረዝ። ቃል ኪዳኔም በሥጋችሁ የዘላለም ቃል ኪዳን ይሆናል።
¹⁴ የቍልፈቱን ሥጋ ያልተገረዘ ቈላፍ ሰው ሁሉ፥ ያች ነፍስ ከወገንዋ ተለይታ ትጥፋ፤ ቃል ኪዳኔን አፍርሳለችና።//
…
ሮሜ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ
አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው።
¹³ የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው
የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም።
¹⁴ ከሕግ የሆኑትስ ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኖአል
የተስፋውም ቃል ተሽሮአል፤
¹⁵ ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት መተላለፍ የለም።
¹⁶-¹⁷ ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም፦ ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ
ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት #የሁላችን #አባት #ነው ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እኔስ እዘምራለሁ
እኔስ እዘምራለሁ ለሥላሴ /2/
ፈጥሮኛለና እና በሥጋ በነፍሴ
እኔስ እዘምራለሁ ለሥላሴ
ሥሉስ ቅዱስ ተብለህ የምትመሰገን
ሰውን ከመከራ ከሞት የምታድን
ነፍሴ ትገዛልህ ትንበርከክልህ
ቅዱስ ፈጣሪዬን አንተን ታምልክህ
አዝ...
በመሐሪነትህ ጠብቀህ ያኖርከኝ
በማዳን ችሎታህ ለዚህ ያደረስከኝ
ለአንተ ለአምላኬ ምስጋና አቀርባለሁ
ስምህን ለዘለዓለም ሁሌም እጠራለሁ
አዝ...
አብርሃም ለአምላኩ በቀና ቢታዘዝ
ሥላሴ ገቡና ቤቱን ባረኩለት
ሣራንም ጎበኛት በእርጅናዋ ጊዜ
ይስሐቅን ሰጧት ዘለዓለም ሥላሴ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እኔስ እዘምራለሁ ለሥላሴ /2/
ፈጥሮኛለና እና በሥጋ በነፍሴ
እኔስ እዘምራለሁ ለሥላሴ
ሥሉስ ቅዱስ ተብለህ የምትመሰገን
ሰውን ከመከራ ከሞት የምታድን
ነፍሴ ትገዛልህ ትንበርከክልህ
ቅዱስ ፈጣሪዬን አንተን ታምልክህ
አዝ...
በመሐሪነትህ ጠብቀህ ያኖርከኝ
በማዳን ችሎታህ ለዚህ ያደረስከኝ
ለአንተ ለአምላኬ ምስጋና አቀርባለሁ
ስምህን ለዘለዓለም ሁሌም እጠራለሁ
አዝ...
አብርሃም ለአምላኩ በቀና ቢታዘዝ
ሥላሴ ገቡና ቤቱን ባረኩለት
ሣራንም ጎበኛት በእርጅናዋ ጊዜ
ይስሐቅን ሰጧት ዘለዓለም ሥላሴ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አዎ መልስ አለን!
ተወዳጆች የተሃድሶ መናፍቃን በፍልሰታ ፆም ዙርያ ለሚጠይቋቸው ጥያቄዎች ኦርቶዶክሳዊ ምላሾችን ይዘንላችሁ ቀርበናል የምትፈልጉትን ርዕስ 👉 Read more በማለት ማንበብ ትችላላችሁ።
ምላሽ የሚፈልጉ የተዋህዶ ልጆች በርካቶች ናቸውና ለሌሎች ሼር ማድረግ አንዘንጋ።
ኦርቶዶክስ መልስ አላት።
@And_Haymanot
በእንተ ቅድስት ድንግል ማርያም
👉 ስለ ቅድስናዋ - የቅዱስ አምላክ እናት በመሆኗ
👉 ስለ ድንግልናዋ
👉 ምስጋና እንደሚገባት
👉 ክብር እንደሚገባት 👉 Read more
👉 የተሐድሶ መናፍቃን የፍልሰታ ጾምን በእጅጉ ይተቹታል:: ሐዋርያዊ ውርርስ የሌለው እንግዳ ትምህርት እንደሆነም ይናገራሉ:: ሲያልፍም እመቤታችን አርጋለች ማለት ስሕተትም ነው ይሉናል፤ ይህንንም ያስተማረው በ 16ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ነው ይላሉ::
👉 ለመሆኑ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት (Assumption of Mary) ትምህርት በኢትዮጵያ ሊቃውንት ብቻ የታወቀ ነው?
👉 ትዛታው ሳሙኤልን ዕርገተ ማርያምን ሲነቅፍ የተሰጠ ምላሽ 👉 Read more
ስለ እመቤታችን ዕርገት የሚያትት በPdf የተዘጋጀ 👉 Read more
የተሃድሶ ሲናፍቃን ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት በዛ ዘመን ብንኖር ከእኛ መሃል ከአንዳችን ኢየሱስ ይወለድ ነበር ብለው ያስተምራሉ ያምናሉ። 👉 Read more
ተአምሯን የሰማ ስጋውን ደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል 👉 Read more
የድንግልን ትንሣኤ በኩረ ፕሮቴስታንት የኾነው ማርቲን ሉተር እንኳን በአንክሮ ያምናል ታድያ የዛሬዎቹ ስለምን ካዱ???? 👉 Read more
ድንግል ማርያምን ጨካኝ ለማድረግ የሚባዛው መልዕክት 👉 Read more
💗 "ቅድስት ድንግል ማርያምን መውደድ ከሚገባኝ መጠን በላይ አልፌ ወድጄያት ይሆን? ብለህ ሥጋት አይግባህ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ከወደዳት በላይ ልትወዳት አትችልምና" 💗
ቅዱስ ማክሲሚሊያን ኮልብ
@And_Haymanot
💗 "ለሚያምን(ለማመን) ይኼ የሚጸን(የሚከብድ) ነገር አይደለም/ To believe this is no doubtful matter/." ዕርገተ ማርያም(Assumption of Mary)💗
መልካም ፆም
፩ ሃይማኖት የቴሌግራም ቻናል
Share Share Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ተወዳጆች የተሃድሶ መናፍቃን በፍልሰታ ፆም ዙርያ ለሚጠይቋቸው ጥያቄዎች ኦርቶዶክሳዊ ምላሾችን ይዘንላችሁ ቀርበናል የምትፈልጉትን ርዕስ 👉 Read more በማለት ማንበብ ትችላላችሁ።
ምላሽ የሚፈልጉ የተዋህዶ ልጆች በርካቶች ናቸውና ለሌሎች ሼር ማድረግ አንዘንጋ።
ኦርቶዶክስ መልስ አላት።
@And_Haymanot
በእንተ ቅድስት ድንግል ማርያም
👉 ስለ ቅድስናዋ - የቅዱስ አምላክ እናት በመሆኗ
👉 ስለ ድንግልናዋ
👉 ምስጋና እንደሚገባት
👉 ክብር እንደሚገባት 👉 Read more
👉 የተሐድሶ መናፍቃን የፍልሰታ ጾምን በእጅጉ ይተቹታል:: ሐዋርያዊ ውርርስ የሌለው እንግዳ ትምህርት እንደሆነም ይናገራሉ:: ሲያልፍም እመቤታችን አርጋለች ማለት ስሕተትም ነው ይሉናል፤ ይህንንም ያስተማረው በ 16ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ነው ይላሉ::
👉 ለመሆኑ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት (Assumption of Mary) ትምህርት በኢትዮጵያ ሊቃውንት ብቻ የታወቀ ነው?
👉 ትዛታው ሳሙኤልን ዕርገተ ማርያምን ሲነቅፍ የተሰጠ ምላሽ 👉 Read more
ስለ እመቤታችን ዕርገት የሚያትት በPdf የተዘጋጀ 👉 Read more
የተሃድሶ ሲናፍቃን ማርያም እንደማንኛችንም አይነት ሴት ናት በዛ ዘመን ብንኖር ከእኛ መሃል ከአንዳችን ኢየሱስ ይወለድ ነበር ብለው ያስተምራሉ ያምናሉ። 👉 Read more
ተአምሯን የሰማ ስጋውን ደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል 👉 Read more
የድንግልን ትንሣኤ በኩረ ፕሮቴስታንት የኾነው ማርቲን ሉተር እንኳን በአንክሮ ያምናል ታድያ የዛሬዎቹ ስለምን ካዱ???? 👉 Read more
ድንግል ማርያምን ጨካኝ ለማድረግ የሚባዛው መልዕክት 👉 Read more
💗 "ቅድስት ድንግል ማርያምን መውደድ ከሚገባኝ መጠን በላይ አልፌ ወድጄያት ይሆን? ብለህ ሥጋት አይግባህ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ከወደዳት በላይ ልትወዳት አትችልምና" 💗
ቅዱስ ማክሲሚሊያን ኮልብ
@And_Haymanot
💗 "ለሚያምን(ለማመን) ይኼ የሚጸን(የሚከብድ) ነገር አይደለም/ To believe this is no doubtful matter/." ዕርገተ ማርያም(Assumption of Mary)💗
መልካም ፆም
፩ ሃይማኖት የቴሌግራም ቻናል
Share Share Share
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አንተም አንቺም እኔም
ያገባናል!!!
ቤተ ክርስቲያን ዋስትናዋ ይጠበቅ
ቤተ ክርስቲያን ለጠፉ ንብረቶች ካሳ ይከፈላት
በቤተ ክርስቲያን ውድመት ያደረሱ በህግ ይጠየቁ
የቤተ ክርስቲያን አባቶች መውገር ይቁም
የቤተ ክርስቲያን ልጆች ምእመናን ማሳደድ ይቁም
በተደጋጋሚ በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ላለው ውድመት
ከንፈር ከመምጠት የዘለለ ነገር ተደርጎ አያውቅም እናት
ስትበደል እናት ስትከፋ እናት ስትቃጠል ዳር ሆኖ ማየት
የሚያስችል አንጀት እንዴት ሊኖረን ቻለ?? ከላይ እስከታች
በኃይለኛ እንቅልፍ ተወስደን ስንት ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ?
ስንት መንጋ ተሰደደ? ስንት ካህናት ተገደሉ? ስንት ምዕመናን
ታረዱ? ሚልዮኖች ሳይፈልጉ ወደ ሌላ በረት ገቡ?
የኢትዮጵያ መሰረት ኢትዮጵያን በዓለም ከፍ ያደረገች ቤተ ክርስቲያን ስደተኛ ትሁን?? አገልጋዮች ምእመናን በስጋት
የሚኖሩ እንዲሁኑ ለምን ተፈረደባቸው??
ህዝብን አንድ አድርጋ የኖረች ትውልዱ በዘር ሳይከፋፈል በኢትዮጵያዊነቱ እንዲኮራና እንዲተዛዘን አድርጋ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራ ፊደል ቀርጻ ብራና ድጣ ቀለም በጥብጣ
መሀይምነትን አጥፍታ ዓለም የሚኮራበትን ቅርስ አክሱም
ላሊበላ ፋሲል የመሳሰሉትን ድንቅ ቅርሶች አበርክታ ዳር ድንበሩን አስጠብቃ በኖረች ለምን ይሄ ሁሉ ውድመት ሲደርስ ተመልካች ለምን ጠፋ??
መፍትሔ እስኪገኝ ድረስ ዝም አንልም!!
እኛ የድርሻችንን ከተወጣን ስራውን የሚሰራው ፈጣሪ ነው የኛን ድርሻ ግን እኛ እንወጣ ዳር እንቁም በጸሎትም
በእውቀትም በምንችለው ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንቁም ለኛ ቤት ሌላ የሚቆረቆር የለምና በጋራ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን እንጠይቅ የጠብታ ውሃ ድንጋይ ትሰብራለችና እንተባበር !!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ያገባናል!!!
ቤተ ክርስቲያን ዋስትናዋ ይጠበቅ
ቤተ ክርስቲያን ለጠፉ ንብረቶች ካሳ ይከፈላት
በቤተ ክርስቲያን ውድመት ያደረሱ በህግ ይጠየቁ
የቤተ ክርስቲያን አባቶች መውገር ይቁም
የቤተ ክርስቲያን ልጆች ምእመናን ማሳደድ ይቁም
በተደጋጋሚ በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ላለው ውድመት
ከንፈር ከመምጠት የዘለለ ነገር ተደርጎ አያውቅም እናት
ስትበደል እናት ስትከፋ እናት ስትቃጠል ዳር ሆኖ ማየት
የሚያስችል አንጀት እንዴት ሊኖረን ቻለ?? ከላይ እስከታች
በኃይለኛ እንቅልፍ ተወስደን ስንት ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ?
ስንት መንጋ ተሰደደ? ስንት ካህናት ተገደሉ? ስንት ምዕመናን
ታረዱ? ሚልዮኖች ሳይፈልጉ ወደ ሌላ በረት ገቡ?
የኢትዮጵያ መሰረት ኢትዮጵያን በዓለም ከፍ ያደረገች ቤተ ክርስቲያን ስደተኛ ትሁን?? አገልጋዮች ምእመናን በስጋት
የሚኖሩ እንዲሁኑ ለምን ተፈረደባቸው??
ህዝብን አንድ አድርጋ የኖረች ትውልዱ በዘር ሳይከፋፈል በኢትዮጵያዊነቱ እንዲኮራና እንዲተዛዘን አድርጋ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራ ፊደል ቀርጻ ብራና ድጣ ቀለም በጥብጣ
መሀይምነትን አጥፍታ ዓለም የሚኮራበትን ቅርስ አክሱም
ላሊበላ ፋሲል የመሳሰሉትን ድንቅ ቅርሶች አበርክታ ዳር ድንበሩን አስጠብቃ በኖረች ለምን ይሄ ሁሉ ውድመት ሲደርስ ተመልካች ለምን ጠፋ??
መፍትሔ እስኪገኝ ድረስ ዝም አንልም!!
እኛ የድርሻችንን ከተወጣን ስራውን የሚሰራው ፈጣሪ ነው የኛን ድርሻ ግን እኛ እንወጣ ዳር እንቁም በጸሎትም
በእውቀትም በምንችለው ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን ዘብ እንቁም ለኛ ቤት ሌላ የሚቆረቆር የለምና በጋራ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን እንጠይቅ የጠብታ ውሃ ድንጋይ ትሰብራለችና እንተባበር !!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ይድረስ ለዘረኞች
🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏
⛪ ቤተ ክርስቲያን ኦሮሞ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን አማራ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ትግራይ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ጉምዝ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን አፋር አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሱማሌ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሲዳማ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ጉራጌ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ስልጤ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ወላይታ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ጋንቤላ አይለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሀድያ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ኮንሶ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሀመር አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ምድራዊት አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሰማያዊት ናት
⛪ ቤተክርስቲያን ክርስቶሳዊት ናት
⛪ ቤተ ክርስቲያን አምላካዊት ናት
⛪ ቤተ ክርስቲያን ህያዊት ናት
⛪ ቤተ ክርስቲያን በዘር የተመሰረተች አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተመሰረተች ናት እንጅ ስለዚህ
⛪ ቤተ ክርስቲያን የብሔር አይደለችም የእግዚአብሔር ቤት እንጂ
🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏
አምኖ ለመጣው ሁሉ ኦሮሞ አማራ ደቡብ ትግሬ ሳትል ለሁሉ እኩል ታስተምራለች እኩል ሲሞት ትፈታለች እንግዲህ ሰው በዘር ሲተራመስ ቤተ ክርስቲያንን ኢላማ ማድረግ ተገቢ
አይደለም ቤተ ክርስቲያን መንግስተ እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንጅ መንግስተ ምድርን ዘርን አሰብክም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ዓይን ብሌናችን እንጠብቃት መንግሥተ
ሰማያትን የምናይባት ናትና።
@And_Haymanot
በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤
ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና። ገላትያ 3:26-28
(መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏
⛪ ቤተ ክርስቲያን ኦሮሞ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን አማራ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ትግራይ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ጉምዝ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን አፋር አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሱማሌ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሲዳማ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ጉራጌ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ስልጤ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ወላይታ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ጋንቤላ አይለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሀድያ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ኮንሶ አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሀመር አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ምድራዊት አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን ሰማያዊት ናት
⛪ ቤተክርስቲያን ክርስቶሳዊት ናት
⛪ ቤተ ክርስቲያን አምላካዊት ናት
⛪ ቤተ ክርስቲያን ህያዊት ናት
⛪ ቤተ ክርስቲያን በዘር የተመሰረተች አይደለችም
⛪ ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተመሰረተች ናት እንጅ ስለዚህ
⛪ ቤተ ክርስቲያን የብሔር አይደለችም የእግዚአብሔር ቤት እንጂ
🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏 🙏
አምኖ ለመጣው ሁሉ ኦሮሞ አማራ ደቡብ ትግሬ ሳትል ለሁሉ እኩል ታስተምራለች እኩል ሲሞት ትፈታለች እንግዲህ ሰው በዘር ሲተራመስ ቤተ ክርስቲያንን ኢላማ ማድረግ ተገቢ
አይደለም ቤተ ክርስቲያን መንግስተ እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንጅ መንግስተ ምድርን ዘርን አሰብክም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ዓይን ብሌናችን እንጠብቃት መንግሥተ
ሰማያትን የምናይባት ናትና።
@And_Haymanot
በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤
ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና። ገላትያ 3:26-28
(መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ጎንደር
⛪ ቤተ ክርስቲያን አምኖ ለመጣው ሁሉ ኦሮሞ አማራ ደቡብ ትግሬ ሳትል ለሁሉ እኩል ታስተምራለች እኩል ሲሞት ትፈታለች እንግዲህ ሰው በዘር ሲተራመስ ቤተ ክርስቲያንን ኢላማ ማድረግ ተገቢ
አይደለም ቤተ ክርስቲያን መንግስተ እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንጅ መንግስተ ምድርን ዘርን አሰብክም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን እየደረሰባት ካለው ፈተናና ወደፌት ከሚደርስባት ፈተና እንደ ዓይን ብሌናችን እንዴት እንደምንጠብቃት ለመወያየት
በዕለተ ሰንበት በ19/12/2011
ከቀኑ 4:00 ጀምሮ ልዩ ጉባኤ ተዘጋጅቷል ስለሆነም እርስዎና ሌሎች ጓደኞችዎን በመጋበዝ በሰ/ት/ቤታችን አዳራሽ እንገናኝ
የደ/ስ/ ቀኃ ኢየሱስ ሰ/ት/ቤት ጎንደር
ወላጅ እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
⛪ ቤተ ክርስቲያን አምኖ ለመጣው ሁሉ ኦሮሞ አማራ ደቡብ ትግሬ ሳትል ለሁሉ እኩል ታስተምራለች እኩል ሲሞት ትፈታለች እንግዲህ ሰው በዘር ሲተራመስ ቤተ ክርስቲያንን ኢላማ ማድረግ ተገቢ
አይደለም ቤተ ክርስቲያን መንግስተ እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንጅ መንግስተ ምድርን ዘርን አሰብክም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን እየደረሰባት ካለው ፈተናና ወደፌት ከሚደርስባት ፈተና እንደ ዓይን ብሌናችን እንዴት እንደምንጠብቃት ለመወያየት
በዕለተ ሰንበት በ19/12/2011
ከቀኑ 4:00 ጀምሮ ልዩ ጉባኤ ተዘጋጅቷል ስለሆነም እርስዎና ሌሎች ጓደኞችዎን በመጋበዝ በሰ/ት/ቤታችን አዳራሽ እንገናኝ
የደ/ስ/ ቀኃ ኢየሱስ ሰ/ት/ቤት ጎንደር
ወላጅ እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በየገዳማቱ
ዘማሪ ይልማ
በየገዳማቱ በየበረሃው ውስጥ
ስለተሰደዱት ፍቅርህን በመምረጥ
የዓለም ውደቂ ምናምንቴ ሆነው
ስለ ፍቅርህ ሲሉ ክብራቸውን ትተው
እግዚአብሔር ሆይ ማረን /2/
አዝ---------------//
የዓለም ውዳቂ ጉድፍ በተባሉት
በምድር እየኖሩ በጽድቅ ህይወት ባሉት
ዓለም አና አምሮቷን ትተው በመነኑት
ኢየሱስ ሆይ ማረን እግዚአብሔር ሆይ ማረን /2/
አዝ---------------//
ህያዋን በሆኑት እስከ ዘለዓለም
ከኢየሱስ ጋራ ሞተው በመስቀል ዓለም
ዓለም የናቃቸው እነርሱም የናቁት
አምላክ እራራልን አትጨክን በእውነት /2/
ዝማሬያችንን ይቀበልልን
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ዘማሪ ይልማ
በየገዳማቱ በየበረሃው ውስጥ
ስለተሰደዱት ፍቅርህን በመምረጥ
የዓለም ውደቂ ምናምንቴ ሆነው
ስለ ፍቅርህ ሲሉ ክብራቸውን ትተው
እግዚአብሔር ሆይ ማረን /2/
አዝ---------------//
የዓለም ውዳቂ ጉድፍ በተባሉት
በምድር እየኖሩ በጽድቅ ህይወት ባሉት
ዓለም አና አምሮቷን ትተው በመነኑት
ኢየሱስ ሆይ ማረን እግዚአብሔር ሆይ ማረን /2/
አዝ---------------//
ህያዋን በሆኑት እስከ ዘለዓለም
ከኢየሱስ ጋራ ሞተው በመስቀል ዓለም
ዓለም የናቃቸው እነርሱም የናቁት
አምላክ እራራልን አትጨክን በእውነት /2/
ዝማሬያችንን ይቀበልልን
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ሳልፆም ሊፈሰክ ነው
አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር" 🙏
================
ከናንተው የተላከ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር" 🙏
================
ከናንተው የተላከ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ኪዳነ ምህረት
@And_Haymanot
ቢዘገይም… ብዙዎች ድንግል እናቱን ኪዳነ ምህረት ስንል ግራ ሲጋቡ አስተውላለሁ። በእርግጥም ግራ ቢጋቡ አይደንቅም ምክንያቱም ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስን ጠንቅቆ መረዳትና የመንፈስ ቅዱስ ድጋፍ ይፈልጋልና። በብሉይ አማናዊው መሥዋት ከመሰዋቱ
በፊት “የሥርየት መክደኛ” በእንግሊዘኛው ደግሞ “mercy seat` እንዲህም ሲባል “የምህረት ዙፋን" የሚባል ክፍል ያለው የቃል ኪዳኑ ታቦት ነበር። እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳን በማድረጉ በታቦቱ ላይ ተገልጦ ሙሴን ያነጋገረው ካህናቱን መሥዋዕታቸውን ይቀበል ነበር። ይህ መገለጥ ግን ከሰዎች ልጆች ጋር ፍጹም እርቅ መፈጸሙን የሚያሳይ አልነበረም። ነገር ግን በዚህ ሕዝቡ ይጽናና ራሱንም ለበለጠ የትንሣኤ ሕይወት ያዘጋጀው ነበር። ምክንያቱም ለአባታቸው ለአብርሃም የገባውን ቃል ኪዳን እንደማያጥፍ ያምኑ ነበርና። በሠውና በእግዚአብሔር መካከል እርቅ የወረደው ግን ድንግል እናቱን የቃል ኪዳኑ ታቦት አድርጎ ሥጋና ደም ተካፍሎ ሰው ሲሆን ነው። ያኔ በሰውና በእግዚአብሔር በሰውና በመላእክት በሰውና በሰው መካከል የነበረው ጠብ ፍጻሜ አገኘ። እርቅን ከሰው ጋር በተዋሕዶ ከፈጸመ በኋላ በሰው ልጆች ላይ ሰልጥኖ
የነበረውን ዲያብሎስ ከድንግል እናቱ በተካፈለው ሰውነት በመስቀሉ ድል ነሳው። ድል መንሳትንም ለእኛ ሰጠን። ስለዚህ እርቅ የወረደልን ተስፋ መንግሥተ ሰማያት የተሰጠን እርሷንና
ሥጋዋን ለራሱ የቃልኪዳን ታቦቱ በማደረግ ስለሆነ ድንግል እናቱን ኪዳነ ምህረት እንላታለን። ምክንያቱም ምህረትና እርቅ ለሰው ልጆች ሁሉ ሆኖአልና። እርሱ እግዚአብሔር ቃል ከእርሷ ከድንግል እናቱ ሥጋና ነፍስ
ነስቶ ባሕርያችንን ለብሶ በእርሱም ለፍጥረቱ ተገልጦ በእኛ ላይ የተፈረደውን ፍርድ በራሱ ተቀብሎ ዲያብሎስን ድል ነስቶ በእርሱ ያመኑትን እርሱን ተስፋ የሚያደርጉትን ከቅዱሳን
መላእክት ጉባኤ ደመራቸው፡፡ ያመኑትንም በጥምቀት እርሱን
ለብሰን እንድንነሣ በማድረግ ከቅዱሳን ጉባኤ እንድንደመር አደረገን፡፡ ሰውነታችንን መቅደሱ በማድረግ ሕጉንም በመንፈስ ቅዱስ በልቡናችን ሰሌዳ ላይ ጻፈልን፡፡ እነዚህንና ሌሎች
በረከቶችን ሊሰጠን የወደደው ከድንግል እናቱ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነበር፡፡ ስለዚህም ድንግል እናቱ መንፈስ ቅዱስ አናግሩዋት “በእኔ ታላቅ ሥራን አድርጎአልና እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይሉኛል” ብላ ከፍ አድርጋ ተናገረች፡፡ ስለዚህ ነው ኪዳነ ምሕረት መባልዋ፤ በእርሷ እርቅ ወርዶአልና።
በነቢዩም “ ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው
ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፤ እኔ አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል፡፡”(ዕብ.8፡10) የሚለው ቃል በእኛ የተፈጸመው በድንግል ማርያም ነው፡፡ እንዲህም ስለሆነ ቅዱስ ጳውሎስ
“እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት
ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው”ብሎ ጽፎልናል፡፡ (2ቆሮ.3፡3)ይህን በማን አገኘነው ብንባል በክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የድንግል እናቱን ሥጋና ደም ሳይካፈል ባይወለድ ኖሮ ይህ የምህረት ቃል ኪዳን በእኛና በክርስቶስ መካከል ባልተፈጸመ ነበር፡፡ እናም አጥርቶ ለመረደት የሚፈለግ ቅድስት እናቱን ኪዳነ ምህረት የማለታችን ዋናው
ምክንያት ሰውነቷን የምህረት ቃል ኪዳን ታቦት በማደረግ ከርሷ በነሣው ሥጋ ዓለሙ መዳኑ ነው።... ይቆየን
በመምህር ሽመልስ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
@And_Haymanot
ቢዘገይም… ብዙዎች ድንግል እናቱን ኪዳነ ምህረት ስንል ግራ ሲጋቡ አስተውላለሁ። በእርግጥም ግራ ቢጋቡ አይደንቅም ምክንያቱም ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስን ጠንቅቆ መረዳትና የመንፈስ ቅዱስ ድጋፍ ይፈልጋልና። በብሉይ አማናዊው መሥዋት ከመሰዋቱ
በፊት “የሥርየት መክደኛ” በእንግሊዘኛው ደግሞ “mercy seat` እንዲህም ሲባል “የምህረት ዙፋን" የሚባል ክፍል ያለው የቃል ኪዳኑ ታቦት ነበር። እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳን በማድረጉ በታቦቱ ላይ ተገልጦ ሙሴን ያነጋገረው ካህናቱን መሥዋዕታቸውን ይቀበል ነበር። ይህ መገለጥ ግን ከሰዎች ልጆች ጋር ፍጹም እርቅ መፈጸሙን የሚያሳይ አልነበረም። ነገር ግን በዚህ ሕዝቡ ይጽናና ራሱንም ለበለጠ የትንሣኤ ሕይወት ያዘጋጀው ነበር። ምክንያቱም ለአባታቸው ለአብርሃም የገባውን ቃል ኪዳን እንደማያጥፍ ያምኑ ነበርና። በሠውና በእግዚአብሔር መካከል እርቅ የወረደው ግን ድንግል እናቱን የቃል ኪዳኑ ታቦት አድርጎ ሥጋና ደም ተካፍሎ ሰው ሲሆን ነው። ያኔ በሰውና በእግዚአብሔር በሰውና በመላእክት በሰውና በሰው መካከል የነበረው ጠብ ፍጻሜ አገኘ። እርቅን ከሰው ጋር በተዋሕዶ ከፈጸመ በኋላ በሰው ልጆች ላይ ሰልጥኖ
የነበረውን ዲያብሎስ ከድንግል እናቱ በተካፈለው ሰውነት በመስቀሉ ድል ነሳው። ድል መንሳትንም ለእኛ ሰጠን። ስለዚህ እርቅ የወረደልን ተስፋ መንግሥተ ሰማያት የተሰጠን እርሷንና
ሥጋዋን ለራሱ የቃልኪዳን ታቦቱ በማደረግ ስለሆነ ድንግል እናቱን ኪዳነ ምህረት እንላታለን። ምክንያቱም ምህረትና እርቅ ለሰው ልጆች ሁሉ ሆኖአልና። እርሱ እግዚአብሔር ቃል ከእርሷ ከድንግል እናቱ ሥጋና ነፍስ
ነስቶ ባሕርያችንን ለብሶ በእርሱም ለፍጥረቱ ተገልጦ በእኛ ላይ የተፈረደውን ፍርድ በራሱ ተቀብሎ ዲያብሎስን ድል ነስቶ በእርሱ ያመኑትን እርሱን ተስፋ የሚያደርጉትን ከቅዱሳን
መላእክት ጉባኤ ደመራቸው፡፡ ያመኑትንም በጥምቀት እርሱን
ለብሰን እንድንነሣ በማድረግ ከቅዱሳን ጉባኤ እንድንደመር አደረገን፡፡ ሰውነታችንን መቅደሱ በማድረግ ሕጉንም በመንፈስ ቅዱስ በልቡናችን ሰሌዳ ላይ ጻፈልን፡፡ እነዚህንና ሌሎች
በረከቶችን ሊሰጠን የወደደው ከድንግል እናቱ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነበር፡፡ ስለዚህም ድንግል እናቱ መንፈስ ቅዱስ አናግሩዋት “በእኔ ታላቅ ሥራን አድርጎአልና እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይሉኛል” ብላ ከፍ አድርጋ ተናገረች፡፡ ስለዚህ ነው ኪዳነ ምሕረት መባልዋ፤ በእርሷ እርቅ ወርዶአልና።
በነቢዩም “ ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው
ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፤ እኔ አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል፡፡”(ዕብ.8፡10) የሚለው ቃል በእኛ የተፈጸመው በድንግል ማርያም ነው፡፡ እንዲህም ስለሆነ ቅዱስ ጳውሎስ
“እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት
ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው”ብሎ ጽፎልናል፡፡ (2ቆሮ.3፡3)ይህን በማን አገኘነው ብንባል በክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የድንግል እናቱን ሥጋና ደም ሳይካፈል ባይወለድ ኖሮ ይህ የምህረት ቃል ኪዳን በእኛና በክርስቶስ መካከል ባልተፈጸመ ነበር፡፡ እናም አጥርቶ ለመረደት የሚፈለግ ቅድስት እናቱን ኪዳነ ምህረት የማለታችን ዋናው
ምክንያት ሰውነቷን የምህረት ቃል ኪዳን ታቦት በማደረግ ከርሷ በነሣው ሥጋ ዓለሙ መዳኑ ነው።... ይቆየን
በመምህር ሽመልስ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
Forwarded from መሠረተ ያሬድ ሰ/ት/ቤት ዘአሣሣ
✝የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ✝
"ያልተሟሸ ሸክላና ሰንበት ትምህርት ቤት ያልገባ ወጣት አንድ ናቸው።" ብፁዕ አቡነ ሰላማ
✍ እነሆ የአሳሳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል #መሠረት_ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት #የ40ኛ_ዓመት_የልደት_በዓልን ምክንያት በማድረግ ከጳጉሜ 1-3 2011 ዓ/ም ድረስ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ ተዘጋጅቷል እርሶም ወዳጅ ዘመዶን በመጋበዝ የእግዚአብሔር ቃል ይሰሙ ዘንድ ተጋብዘዋል በእለቱም፦
☞ መጋቢ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
☞ ዘማሪ ዲያቆን ፍሬዘር ደሳለኝ
☞ ዘማሪ ቶማስ {መሰንቆ}... ተጋብዘዋል በመሆኑም የነፍሶን ማዕድ ተመግበው የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ልደት አብረን እናከብር ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እናሳስባለን።
#አሳድገሽኛል_ቤቴና_ውበቴ
#አልለይም_ካንቺ_እስከ_እለተ_ሞቴ
#የፀጋው_ግምጃ_ቤት_ክብሬና_ማዕረጌ
#ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የዘላለም_ቤቴ
#ሰንበት_ትምህርት_ቤት_ክብሬና_ውበቴ
✞ የአባቶቻችንን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ሰንበት ትምህርት ቤታችንን ይጠብቅልን!!!✞ አሜን!!! ✞✞✞
"ያልተሟሸ ሸክላና ሰንበት ትምህርት ቤት ያልገባ ወጣት አንድ ናቸው።" ብፁዕ አቡነ ሰላማ
✍ እነሆ የአሳሳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል #መሠረት_ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት #የ40ኛ_ዓመት_የልደት_በዓልን ምክንያት በማድረግ ከጳጉሜ 1-3 2011 ዓ/ም ድረስ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ ተዘጋጅቷል እርሶም ወዳጅ ዘመዶን በመጋበዝ የእግዚአብሔር ቃል ይሰሙ ዘንድ ተጋብዘዋል በእለቱም፦
☞ መጋቢ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ
☞ ዘማሪ ዲያቆን ፍሬዘር ደሳለኝ
☞ ዘማሪ ቶማስ {መሰንቆ}... ተጋብዘዋል በመሆኑም የነፍሶን ማዕድ ተመግበው የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ልደት አብረን እናከብር ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እናሳስባለን።
#አሳድገሽኛል_ቤቴና_ውበቴ
#አልለይም_ካንቺ_እስከ_እለተ_ሞቴ
#የፀጋው_ግምጃ_ቤት_ክብሬና_ማዕረጌ
#ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የዘላለም_ቤቴ
#ሰንበት_ትምህርት_ቤት_ክብሬና_ውበቴ
✞ የአባቶቻችንን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ሰንበት ትምህርት ቤታችንን ይጠብቅልን!!!✞ አሜን!!! ✞✞✞
❤1