፩ ሃይማኖት
8.96K subscribers
246 photos
29 videos
21 files
96 links
ኦርቶዶክሳዊ ምላሾች
የሚቀርቡበት፡፡
👉"፩ ኃይማኖት"👈
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የገሀነም ደጆች አያናውጧትም
✞ እ...ና...ታ...ች...ን
#አ__ት__ታ__ደ__ስ__ም፡፡
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
ለአስተያየት
@And_Haymanot_bot

፩ ሃይማኖት ኤፌ 4፥5
Download Telegram
የካቲት 2 - የበረሃው ኮከብ የአባ ጳውሊ ዕረፍት

@Meserete_Yared_Asasa

በዚህች ቀን በግብጽ በርሃ ታላቅ አምድ ወደቀ፤ ይህም የባህታውያን ሁሉ አለቃቸው የሆነ አባ ጳውሊ ነው። ስርዓተ ብሕትውና በጳውሊ ስርዓተ ምንኩስና በእንጦኒ ተጀምሯል ይላል፤ ጳውሊ አባቱ ባለጸጋ ነበር ሲሞት ለታላቅ ወንድሙ በጴጥሮስ እጅ አድርጎ ኋላ አካለ መጠን ሲያደርስ ከፍለህ ስጠው ብሎት ተናዞ አረፈ፤ አባ ጳውሊ አካለ መጠን ሲደርስ “ደረስሁ ልጅ ፈላሁ ጠጅ” የአባቴን ገንዘብ ከፍለህ ስጠኝ አለው አይሆንም አልሰጥህም አለው ምነው ቢለው ልጅ ነህ ታጠፋዋለህ ብዬ ነው ይለዋል አላጠፋውም ስጠኝ ይለዋል ግድማ ካልኸኝ ብሎ ብዙውን አስቀርቶ ጥቂቱን፤ መልካሙን አስቀርቶ ተራ ተራውን ሰጠው አባ ጳውሊ በዚህ ተበሳጭቶ ዳኛ ጋር ሄደ በመንገድ ላይ አንድ ባለጸጋ ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት አየ አባቴ ባለጸጋ ነበር ሞተ ይሄም ባለጸጋ ነበር ሞተ እኔስ ነገ እሞት የለምን ብሎ ወደ ወንድሙ ተመልሶ ወንድሜ ገንዘቡ ላንተ ይሁን ትቼልሃለው ብሎ ከቤት ወጠ፤ መጀመሪያ ለ 3 ቀን ከመቃብር ቤት ገብቶ ጸለየ በ3ኛው ቀን ከሰማይ ግማሽ ህብስት ወረደለት፤ ገረመው፤ ፈጽሞ ሳይለዩ እንዲህ ከሆነማ ፈጽሞ ቢለዩማ እንደምን ያለ ተአምር በተደረገ ብሎ አናብስት አናምርት አካይስት አቃርብት ካሉበት ነቃዐ ማይ ልምላሜ ዕፅ ከሌለበት ድሩክ ለተአቅቦ ይለዋል ዘር ተክል ከማይገኝበት ከጽኑ በርሃ ገባ፤ የሰው ፊት ሳያይ ለ 80 ዓመት በተጋድሎ ኖሯል። ምግቡን ግማሽ ህብስት በየቀኑ የሚያመጣለት ቁራ ነበር።

የእረፍቱ ቀኑ ሲደርስ ከአባ እንጦንስ ጋር በእግዚያብሔር ፈቃድ ተገናኝተው ብዙ ነገር ተጨዋወቱ በተለይም በኋለኛው ዘመን ስለሚነሱት መነኮሳትና፤ ግብጽ በሙስሊሞች እንደምትወረር ብዙ ምስጢር አወሩ፣ ብዙ ትንቢትም ተናገሩ፤ ከዚህ በኃላ አባ ጳውሊ አስኬማ መልአክ አምጣልኝ ብሎ ይልከዋል፤ አባ እንጦስ ወደ ገዳሙ ሄደ የ2 ቀን ጎዳና ነው ሲመለስ በርሃው ላይ ሰማያውያን መልአክ ሰፍረውበት ሲዘምሩ ሲያመሰግኑ አየ፤ ልብን የሚመስጥ የእጣን መዓዛም አሸተተ፤ ምንድር ነው ? ብሎ አንዱን መልአክ ይጠይቀዋል አባ ጳውሊ ሞቶ ነፍሱን እያሳረግን ነው ይለዋል ይሄን አስኬማ አምጣልኝ ብሎኝ ነበር ምን ላድርገው? ይለዋል፤ ጸሎት አድርሰህ አድርግለት፤ ደግሞም መቃብሩን የሚቆፍሩ አንበሶች ይመጣሉ ቦታውን ለክተህ ስጣቸው አለው፤ ወደ ገዳሙ ሲገባ እጁን መስቀልያ እንደዘረጋ ሞቶ አገኘው የሚጸልይ እንጂ የሞተ አይመስልም ነበር አስኬማውን አድርጎለት ሲያበቃ ከራስጌው ቆሞ ኤልያስ ልበልህ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ልበልህ እያለ አለቀሰለት፤ ሁለት አንበሶች መቃብሩን ቆፈሩለት ገንዞ ቀበረው። 80 ዘመን ሙሉ ለብሶት የኖረው የሰሌን ልብስ ነበረችው ወስዶ ለሊቀ ጳጳሱ ለአባ አትናቴዎስ ሰጠው፤ በዚህች ልብስ አባ አትናቴዎስ ብዙ ተአምራትን ሰረቶበታል ይልቁንም ሙት አስነስቶበታል።
የአባቶቻችን የከበረች በረከታቸው ድል የማትነሳ ረድኤታቸው ጥርጥር የሌለባት ሃይማኖታቸው ከእኛ ጋር ትሁን።

✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
✥┈┈ • ┈┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈ • ┈┈┈••✥
በቀጥታ መልሱ?????

@ዙሪያ ጥምጥም ሳትሄዱ በቀጥታ ቃል በቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ጠቅሳችሁ መልሱን ለሚለው የአርሲሳን(የመናፍቃን) ጥውየት(ጥመት) እንዲህ እንመልስላቸዋ!፦
[[[[[[ @And_Haymanot ]]]]]]]
መጽሐፍ ቅዱስ 66ቱ ብቻ ነው የሚል በራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃል በቃል ተጽፎ አለ??? እኛ የምንቀበለው ስላሉ
የራስ አቋም ጠቅላላ ሀቅ ተደርጎ ሊወሰድ ፈጽሞ አይገባም። "እመቤታችን ድንግል ማርያም ጸልያ ታስምራለች፥
ታድናለች" የሚል ቃል በቃል መጽሐፍ ቅዱሳዊ የተጻፈ ጥቅስ አምጣና ልመን የሚል 'ኢዩ ጩፋ ጋር ልጅህን ውሰድ፥ ፎቶውን ይዘህ ናና ጸልዮ ልጁ ይድንልሃል' ለሚለው ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ ሳያገኝ እንዴት አምኖ ሄደ???
☞ "ግሸን እየሄዳለሁ፥ ጻድቃኔ ማርያም አልቀርም፥ ሽንቁሩ ሚካኤል እጠመቃለሁ፥ ደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እሳለማለሁ።" ለሚለው 'ማርያም ቤተ ክርስቲያን፥
ጻድቅን ሰማዕታት ቤት ሂዱ የሚል ጥቅስ አለ?' ብሎ ሲጠይቅ 'ፓስተር ሱራፌል ጋር፥ እስራኤል ዳንሳ ጋር ሄድኩ፥..." ሲል
መጽሐፍ ቅዱስ ላይ 'ፓስተር እከሌ ጋር ሂድ የሚል አለ?' ቢባል አንዳች መልስ አለው?
☞ የስንት ፓስተሮች ስም በየመንገዱ እየለጠፈ፥ 'እንዳይቀሩ፥ እንዳያመልጦዎ' ለሚለው የአንድም ፓስትር ስም መጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ ሳይኖር፥ 'ፓስተር እገሌ ጸልዮልን ተፈወስኩኝ' ለሚለው ጥቅስ ሳያሳዩን፤ አቡነ ተክለሃይማኖት፥ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ፥ ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ የሚል ስማቸው ቃል በቃልና በጸሎታቸው መዳን እንደሚቻል ቃል በቃል መጽሐፍ ቅዱስ ላይ አምጡ ይሉናል።

❖ እንዳውም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ብቻ በስም የተጠቀሱትን ቅዱሳንን ነው የምንቀበለው የሚሉን ከሆነ፦

፩. መጽሐፍ ቅዱስ ከተጻፈ በኋላ አምላከ ቅዱሳን አምላካችን እግዚአብሔር "ቅዱስ" የሆነ ሰው በቃኝ፤ ገነት መንግሥተ ሰማይ ኮታው ሞልቷል አልቀበለም፥ አትቀበሉ ብሏል??? እንኳን ቅዱሳን በዙ ልንል ቀርቶ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትማ እንሂድ
ከተባለ ሁላችንም ቅዱሳን እንድንሆን ታዘናል። "እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ።" 1ኛጴጥ. 1፥15-16
እንዲል።
፠ ከሊቀ ሐዋርያት ከቅዱስ ጴጥሮስ የበለጠ መምህር ሊያመጡልን ይችላሉ???....በፍጹም!!!...ቆይ ግን እንደ ቃሉ ሰምሮልን ሁላችንም "ቅዱሳን' ብንሆን ሁላችንም ቅዱስ ሆነን 'ኢየሱስን' ከደነው፥ ሸፈነውኮ ማለታችሁ አይቀርም።

፪. መጽሐፍ ቅዱስ በስም ከተጠቀሱ ቅዱሳን ውጭ አንቀበለም.ካሉ መናፍቃኑ ለምን ራሳቸውን 'ቅዱሳን' ብለው ይጠራሉ? ስም ዝርዝራቸው አለ?
☞ ገድል፥ ድርሳን አያስፈልግም፥ ጸረ ወንጌል ነው እያለ 'ፓስተር እገሌ የጻፋት ድንቅ መጽሐፍ ግን የእከሌን ሕይወት
ቀየረ¡' ይሉናል።
☞ ኢዩ ጩፋን ለማግኘት አስፓልት ዳር
ብርድ ሲቀፈቅፈው የሚያድር እኲይ ትውልድ "አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ደጅ የሚያድርን ቅዱስ ሕዝብ መተቸቱ Morally ያስኬዳል? በምን አግባብ?....እስቲ ጥቅስ አምጡልና?!!...
☞ ለጻድቃኔ ማርያም ጠበል(የተቀደሰ ውሃ) ና ጸበል(የተቀደሰ እምነት(አፈር)) ለፈውስ አገልግሎት አውሉት የሚል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ አጥብቆ አምጡ እያለ፤ የተጸለየበት Highland
ውሃና አዮዲን ጨው ግን ያለጥቅስ ውሰድ ይለናል። የነሱ ተኣምራቱ ሁሉ 'ወንጌል' የእኛ ተረት ተረት ነዋ¡¡¡.....
☞ ለምንድነው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሕሮን ሁሉ 'ለእነሱ መልስ በሚሆን መልኩ ቢመለስ' እያልን በ Protestant View ብሎም አስተሳሰብና ስሜት ልክ ቀደን የምንሰፋው?...መናፍቃኑ ይኼን አልቀበልም ስላሉ "እውነት" እነሱ ስላልተቀበሏት ለእነሱ ስትል ሐሰት ትሆናለች?....
☞ የእልህ ወንጌል የለም!....'ኢየሱስ ብቻ ያድናል' ማለት እግዚአብሔር አብስ?....እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስስ?....'አይ እኛ 'ብቻ' ስንልኮ ያለማንም እርዳታ ብቻውን ያድናል!' ለማለት ፈልገን ነው ካሉ ያለማንም እርዳታ ብቻውን ማዳን፥ ሁሉንም
ማድረግ ከቻለ መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። ታዲያ እግዚአብሔር ከሆነና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን ነገር ብቻውን ማድረግ ይችላል ብለው የእውነት
ካመኑበት ምን ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አብ ይለምናል ይሉናል???? ...ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያምና.ቅዱሳን ካላቸው ርጉም ጥላቻ የተነሳ በግብር ይውጣ ይለፍፉታል እንጂ... ማዳን፥ መግደል የአብ፥ የወልድ፥ የመንፈስ ቅዱስ እኩል ሥልጣን እንጂ የወልድ ብቻ አይደለም።

እግዚአብሔር ያድናል ማለት በእግዚአብሔር ኃይል ቅዱስ ጳውሎስ ድንቅ ተኣምራትን አድርጎ አላዳነም ማለት አይደለምኮ!...በተለይም 14 ቅዱሳን መልዕክታቱ ይኼው ቅዱስ ወንጌል ነውና በትክክለኛ ትርጓሜ ለሚገለገልባቸው እስከ ዘላለም ሲያድን ይኖራል። የቅዱስ ጳውሎስ ፲፬ ክታቦቹ ፬ ቱ ወንጌላትን ከደነ? ሸፈነ? የሐዋርያት ሥራ የሚል የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለምን የኢየሱስ ሥራ አይልም ነበረ? የማቴዎስ፥ የማርቆስ፥ የሉቃስ፥ የዮሐንስ ወንጌል መባሉ የክርስቶስ ወንጌል
ባለመባሉ ተከደነ?

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶም ትክክል፥ ሌላውም ቤተ እምነት እንደየራሱ ትክክል ብሎ መቁጠርና ሁሉም የሕይወት መንገድ ማለት ትልቅ ስሕተት ነው። ምክንያቱም ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት Didache (c. 100) በተባለው መጽሐፍ ሲናገሩ በመጀመሪያ ምዕራፍ (Chapter 1) ላይ There are two ways, one of life and one of death በማለት ነው።
እዛም ቤት ችግር የለም፥ እዚህ ብትሆንም ችግር የለም የሚል ወንካራ አካሄድ እጅግ አደገኛ ነው። ፀረ ሐዋርያት አቋም ነውና።
☞ ጥልቅ ንባብን የሚወድ ትውልድ ብንሆን ኖሮ ይኼ ሁሉ
ጥርጥር ባልመጣብንም፥ እንዲህም እርስ በእርስ ባልተጨራረስንም ነበር።
by፡- ዘማርያም ዘለቀ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
Photo
"ዘመቻ ጸረ-ተሐድሶዉ ተጀምሯል!"
** ******** ******
ከቤተክርስትያን በምንፍቅባቸዉ ሲወገዙ የዋሃን ያሉባትንና የመንግስት ካድሬዎችም ሽፋን የሚሰጡላቸዉን የደቡብ ክልልን ተሐድሶ መናፍቃን መፈንጫቸዉ ሊያደርጉ ሰሞኑን
እየተርመሰመሱ ነዉ፡፡ አርባምንጮች ከሰሞኑ ከቤተክርስትያን ተወግዘዉ ነገር ግን የቤተክርስትያን ንዋያት የሆኑትን
በአዳራሻቸዉ መቀለጃቸዉ ሊያደርጉ ሲታትሩ ደርሰዉ ቤተክርስትያናቸዉን አስከብረዋል፡፡ ዘመቻዉ ጎፋ ሳዉላ ደርሶ
እነሆ በዛሬዉ ኪዳነምህረት በምትበግስበት ዕለት ወጣቶች
ኪዳነምህረትን አንግሰዉ ከተማዋን እየዞሩ በሃገር፣ በሚስትና በሐይማኖት ቀልድ የለም! እያሉ ተሐድሶ ላይ የሞት አዋጅ እያወጁ ይገኛሉ፡፡ መሎ ኮዛዎችም ጸረ-ተሐድሶ ዘመቻ ሊጀምሩ እንደሆነም ተነግሯል፡፡

እኛም በያለንበት ሆነን ጸረ ተሐድሶ
ዘመቻዉን እንደግፋለን!! ጎፋዎች ከጎናችሁ ነን! ማንም የፈለገዉን የማመን መብት አለዉ፤ ነገር ግን በቤተክርስትያን ላይ ሲያላግጥ በንዋየ ቅድሳት ላይ
ሲዘባበት ዝምታ አያሻም!!
# በሃገር_በሚስትና_በሐይማኖት_ቀልድ_የለም !

ምንጭ፡ ንሽኩር
16/06/2011 ዓ.ም (ቅዳሜ)
A.A blh
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
Photo
የክተት አዋጁ

የጦርነት አይቀሬነት እና የጣሊያን ጦር ቅብጥብጥነት እያየለ ትግራይን በመውረሩ ኢትዮጵያም ለፍልሚያ ተዘጋጀች። ዝነኛው
የአፄ ምኒልክ የክተት አዋጅም ነጋሪት እየተጎሰመ ተለፈፈ።
“እግዚአብሄር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ
አኖረኝ፤ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡
ከእንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉም ነውና ስለእኔ ሞት
አላዝንም፡፡ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፤ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፤ ሃይማኖትን የሚለውጥ፣ በፊት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባህር አልፎ መጥቷል፡፡ እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ፤ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን
በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ የአገሬ
ሰው ከአሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን
አላስቀየምኸኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ። ጉልበት
የሌለህ ለልጅህ፣ ለምሽትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በሃዘንህ
እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፡፡ አልምርህም፡፡ ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም…”(አፄ ምኒልክ)
@And_Haymanot
የጸሎት ጥበብ

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገርን የተማረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን እንደሚገባ’ው አድርጎ ሲያነጋግረው ከዚያን ጊዜ አንሥቶ መልአክ ይኾናል፡፡ ነፍስ ከፈቃዳተ ሥጋ ሰንሰለት ነጻ
የምትወጣው በዚህ መንገድ ነውና፤ ሕሊና ከፍ ከፍ የሚለው በዚህ መንገድ ነውና፤ ማደሪያችን ወደ ሰማይ የሚሻገረው በዚህ መንገድ ነውና፤ አንድ ሰው ግብረ ዓለምን የሚንቀው በዚህ መንገድ ነውና፤ አንድ ሰው የቱንም ያህል ነዳይ ወይም ባሪያ ወይም ተራ ወይም ዝቅ ያለ ቢኾንም እንኳን በንጉሡ ዙፋን
ፊት የሚቆመው በዚህ መንገድ ነውና፡፡ እግዚአብሔር የሚመለከተው የንግግርን ውበት ወይም የቃልን ርቱዕነት ሳይኾን
የመንፈስን ንጹህነት ነውና፡፡ በዚህ መንገድ መጥተን ወደ አእምሮአችን የመጣውን ብንናገርም እንኳን፥ ጸሎታችን ግዳጅ የሚፈጽም ኾኖልን እንመለሳለን፡፡

እንግዲህ ይህን ማድረግ ምን ያህል ቀላል እንደ ኾነ ታስተውላለህን? በዚህ ዓለም ሰዎች ዘንድ አንድ ሰው ሌላውን
ሰው ለመለመን የንግግር ክህሎት (ብልሐት) ያሻዋል፡፡ የሚለመነው ሰው በቀላሉ የማይገኝ ከኾነ ደግሞ አጃቢዎቹን ማሳመን ይኖርበታል፡፡ ጥሮ ለፍቶ ካገኘው በኋላም ጉዳዩን በዝርዝር ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እግዚአብሔርን ለማናገር ግን የዚሁ ተቃራኒ ነው፡፡ ከተሰበረ ልብ በቀር ሌላ ምንም ምን አያስፈልግም፤ ወደ እርሱ ለመቅረብ የሚከለክል ማንም
አይኖርም፡፡ “እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ ሩቅ አምላክ አይደለሁም” ይላልና (ኤር.23፡23)፡፡ የምንርቀው እኛ ነን እንጂ እርሱ ዘወትር ቅርብ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ለማነጋገር የንግግር ክህሎት (ብልሐት) አያስፈልገንም የምለውስ ለምንድን ነው? እንዲያውም ብዙ ጊዜ ድምፅም ቢኾን አያስፈልገንም፡፡ አንተ በልብህ ብትናገርና
እግዚአብሔርን ማናገር እንዲገባ’ህ ብታናግረው እርሱ ጸሎትህን ለመስማት ዘንበል ይላል፡፡ ሙሴ ጸሎቱ የተሰማው
በዚህ መንገድ ነውና፤ ሐና ጸሎትዋ የተሰማው በዚህ መንገድ ነውና፡፡ ወደ እግዚአብሔር እንዳይቀርቡ ብሎ ሕዝቡን ለማራቅ የሚቆም ወታደር የለም፤ አሁን ሰዓቱ አይደለም ብሎ የሚከለክል ዘበኛም የለም፡፡ እግዚአብሔርም፡- “አሁን ላነጋግርህ አልችልም፤ ሌላ ጊዜ ተመለስ” አይልም፡፡ ይልቅ ልታነጋግረው
በመጣህበት ቅጽበት አንተን ለመስማት ይቆማል፡፡ የምሳ ሰዓትም ቢኾን፣ የእራት ሰዓትም ቢኾን፣ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜም
ቢኾን፣ በገበያ ቦታም ቢኾን፣ በመንገድ ላይም ቢኾን፣ በባሕር ውስጥም ቢኾን፣ በዳኛ ፊት በምትቆምበት በችሎት ፊትም
ቢኾን፥ እግዚአብሔርን ብትጠራው መጥራት እንደሚገባህ አድርገህ እስከ ጠራኸው ድረስ ጸሎትህን እንዳይሰማ
የሚከለክለው ግድግዳ የለም፡፡
ምንጭ፡- ገ/እግዚአብሔር ኪደ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
"ጾም እና አሳ "

@And_Haymanot
አሳን በጾም ለምን አንበላም? አሳን በተመለከተ ብዙ ግዜ ጥያቄ ይነሳል፤ በፆም አሳ ለምን አንበላም? ጌታ ለሐዋርያቱ አሳን አበርክቶ ሰቷቸዋል፤
ሐዋርያቱም አሳ በልተዋል፤ ደግሞም እኮ በድሮ ግዜ አሳ ይበላ ነበር ይህ አሁን የመጣ ታሪክ ነው ይሉናል ለምን አሳን በጾም አንበላም ብለው ብዙ ግዜ ይጠይቁናል። ለመሆኑ አሳን በጾም ለምን አንበላም?
ሁለተኛ የሚያነሱት ሀሳብ አሳ ደም የለውም ከተራክቦ ነፃ የሆነ እንስሳ ነው ስለዚህ በፆም ወቅት ይበላል ይላሉ።
እውነታው ግን ይሄ ነው መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በሚጾምበት ወቅት ሐዋሪያት አይጾሙም ነበር። በእምነታቸውም መሉ አልነበሩም ሐዋሪያት ለመጀመሪያ ጊዜ ጾምን የጾሙት ጌታች ኢየሱስ ክርስቶስ በአረገ
ጊዜ በተነሳ በ40ቀን በአረገ በ10 ቀን ጰራቂለጦስ መንፈስቅዱስ ለሁሉም ሐዋሪያት ከላከላቸው በኋላ ወደ ዓለም ሂዳችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀመዝሙርቴ
አድርጓቸው ብሎ ሲያዛቸው ለአገልግሎት ከመሰመራታችን
ስራችን የታቀና ይሆን ዘንድ እንፁም ብለው ለአንድ ወር ያክል ፆሙ የሐዋሪያት ፆም ብለን ከበዓለ ሀምሳ በኋላ የምንፆመው ፆም ማለት ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አሳ በፆም ወቅት
እንደማይበላ ሁሌም ታስተምራለች ከዚህ በፊትም ዛሬም ወደ ፊትም ታስተምራለች "ጅሮ ያለው" ይስማ እንዲል ቅዱስ
ወንጌል ። ምዕመናን በፆም ወቅት እኮ ይሄ ይበላል ይሄ አይበላም የምንለበት ወቅት አይደለም። ፆም የስጋ ፍላጎታችንን ለነፍስ የምናስገዛበት ወቅት ነው። አሳ ከፍተኛ ፕሮቲን እንዳለው የማይካድ ሀቅ ነው ታዲያ ከፍተኛ ፕሮቲን እንዳለው ካውቅን በፆም ወቅት ከበላነው ምኑን ፆምነው ስጋችን እየደለብነው
ነፍሳችን እየከሳች ነው። ጾም እኮ ጊዚያዊ የሆነወን ስጋን ዘለዓለማዊ ለሆነችውለነፍስ ማስገዛት ነው።

ኢትብልሁ ሥጋ ዘእንበለ አሳ ይለናል በቀኖና ቤ/ተ/ክ ይህም ሥጋ አትብሉ አሳን ጭምር ማለት ነው።ሌሎች ግን ሥጋ አትብሉ ከአሳ በቀር ብለው ተርጉመውታል ይህ ግን ልክ
አይደለም። ዘእንበለ የሚለው ግዕዝ ጭምር ወይም በቀር ተብሎ ይተረጎማል። ምሳሌ እናቅርብ፦ “እግዚአብሔር ፈጠረ ኩሉ አለም ዘእንበለ ትል” ሲል እግዚአብሔር አለምን ሁሉ ፈጠረ ትልን ጭምር ይባላል እንጂ ከትል በቀር አይባልም። ስለዚህም
አሳን ጭምር አትብሉ ማለት ይሆናል ማለት ነው።
318ቱ ርቱሃነ ሐይማኖት አበው አባቶቻችን በጾም ክርክር ቢነሳ ለጾም አድሉ ከመብል አለመብላት እጅግ ይሻላልና ብለው አልፈዋል።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለፍርድ በዳግም ምፅአት ሲመጣ ለፍርድ የምትቆመው ስጋችን ሳይሆን ነፍሳችን ናት። ስጋችንን ለነፍሳችን አስገዝተን በቀኙ ቁመን ተስፋ የምናደርጋትን
መንግስተ ሰማይትን እንድንወርስ የአምላካችን ቅዱስ ፍቃዱ
ይሁን
✞ፆሙን የፍቅር የበረከት የረድኤት ያድርግልን✞
@And_Haymanot
@And_Haymanot
"ለኦርቶድክሳውያን መልዕክት!"

@And_Haymanot

ይሄ የህዝብና ቤት ቆጠራን አስመልክቶ ብጽዕ አቡነ አብርሃም ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ያስተላለፉት መልዕክት ነው። ወገኖቻችንንም በማሳወቅ ኦርቶዶክሳዊ ግዴታችን ነው!!

👉 "ከፊታችን የሕዝብና ቤት ቆጠራ አለ፡፡ አደራ እምነትን/ ሃይማኖትን በተመለከተ ስትሞሉ ክርስቲያን ብቻ እንዳትሉ፤ ብዙ አይነት ክርስቲያን አለ፡፡ መሙላት ያለባችሁ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ / ክርስቲያን በሚል ይሁን፡፡ ይህንንም ለሌሎችም አድርሱ…" ብፁዕ አቡነ አብረሃም የባ/ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ።


@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቃል …ብቻ ሲናገር የሞተ ይነሳል
ቃል… ብቻ ሲናገር ድውኝ ይፈወሳል
ቃል… ብቻ ሲናገር የእውር አይን ይበራል
ቃል… ብቻ ሲናገር ለምፃሙ ይነፃል
ቃል …ብቻ ሲናገር ንፋሱ ፀጥ ይላል
ቃል… ብቻ ሲናገር ባህር ይከፈላል
የድንግል ማርያም ልጅ ክብሩ ይስፋ።
…አይኖቼ ማዳኑን አይተዋልና
ይገበዋል ክብርና ምስጋና።
ማዳንህን የሚወዱ ሁልጊዜ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ
【መዝሙር 89:14】
አሜን ክብር ለድንግል ማርያም ልጅ ለክርስቶስ ኢየሱስ ይሁን።
※ እግዚአብሔር ታላቅ ነው
@And_Haymanot
@And_Haymanot
✞በጌቴ ሴማኔ✞

በጌቴ ሴማኔ፣ በአትክልቱ ቦታ(2)
ለእኛ ሲል ጌታችን፣ በዓለም ተንገላታ(2)

አዳምና ሔዋን፣ ባጠፉት ጥፋት(2)
እኛም ነበረብን፣ የዘላለም ሞት(2)
መስቀል ተሸክሞ፣ ሲወጣ ተራራ(2)
ይገርፉት ነበረ፣ ሁሉም በየተራ(2)
ድንግል አልቻለችም፣ እንባዋን ልትገታ(2)
እያየች በመስቀል፣ ልጇ ሲንገላታ(2)
በአምላክነቱ፣ ሳይፈርድባቸው(2)
እንዲ ሲል ፀለየ፣ አባት ሆይ ማራቸው(2)
በረቂቅ ሥልጣኑ፣ ሁሉን የፈጠረ(2)
በሰዎች ተገርፎ፣ ሞተ ተቀበረ(2)
ፍቅሩን የገለጸው፣ ተወልዶ በስጋ(2)
ኢየሱስ ጌታ ነው፣ አልፋና ኦሜጋ(2)
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ቅድሰት (የዐቢይ ጾም ሁለተኛ)

@And_Haymanot

ቅድሰት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ስያሜውም ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው፡፡ ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን ታስተምርበታለች ፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ ፤ የሚነበቡ መልዕክታት ፤የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ ቅድስት የሚያስተምሩ ናቸው፡፡
‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ መጻሕፍትም የባሕርይ ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ ‹‹ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡( ኢሳ 6፡1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) እኛም ቅዱስ ልጁ በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡ የቅድስና ምንጭ ፡ ቅድስናን የሚሰጥ እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ቅዱስ›› የሚለው ቃል ለሰዎች፡ ለመላእክት ፡ ለቦታ ፡ለዕቃ፡ ለዕለታት ቢቀጸልም ቅድስናቸው በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡ ይህም የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም ይህንን ሲያስተምረን ነው፡፡ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን ፤ ለውርደት ሳይሆን ለክብር፤ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ ለሞት ሳይሆን ለሕይወት ነው፡፡ የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም ምግባርና ሃማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡
ብርሃን ከጨለማ ጽድቅ ከኃጢአት ጋር ኅብረት የለውምና ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር ይጠበቅብናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹እግዚአብሔር ለቅድስና እንጂ ለርኩሰት አልጠራንምና›› ያለንም ለዚህ ነው፡፡ /1ተሰ 4÷7/ እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን አላማ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች እንዲህ ገልጾላቸዋል ‹‹በክርስቶስ ኢየሱስ ሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ይመስገን፡፡ ብሎ ካመሰገነ በኋላ ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳን ንጹሐንና ያለነውር በፍቅር ያደርገን ዘንድ ለእርሱ መረጠን›› ኤፌ 1፡3-4 አስቀድሞ ስለወደደንና ስላከበረንም ከሌሎች ፍጥረታት በተለየ መልኩ የሚያስፈልገንን ሁሉ አዘጋጅቶ በእጆቹ ካበጀን በኋላ የሥነ ፍጥረት ዘውድ አድርጎ በገነት አኖረን ፡፡( ዘፍ 1፡26፤መዝ 8፡1)
የቀደመው አዳም አታድርግ የተባለውን በማድረጉ በንዝህላልነትና በስንፍና በከይሲ ዲያብሎስም ምክር ተዋረደ፡፡ በሞተ ሥጋ ላይም ሞተ ነፍስ ፤በርዕደተ መቃብር ላይ ርዕደተ ሲኦል ተፈረደበት፡ በባሕርዩ ሞት ገባበት፡ ተዳደፈ፡፡ ክፉ ፍትወታት የሚያጠቁትና የሚያሸንፉት የዲያብሎስና የኃጢአት ባርያ ሆነ፡፡ በማይለወጥ ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ግን ጠፍተን እንድንቀር አልተወንም፡፡ በሰጠን ተስፋ፡በተቆጠረው ሱባኤና በተነገረው ትንቢት መሰረት ዘመኑ ሲደርስ በተዋህዶ ሰው ሆነ፤ የተዋረደ ሥጋችንን አከበረ፡፡ በከበረ ደሙ ዋጀን፤ ከኃጢአታችን አጠበን፡፡ በእርሱ ምክንያት የእግዚአብሔር ልጆች ተባልን ፡፡ጌታችንና መድኃኒታችን ሰው የሆነውና ለመዳናችን የሆነውን ዋጋ ሁሉ የከፈለው ለእኛ ያለውን ፍቅርና ለኃጢአት ያለውን ጥላቻ ለእኛ ለማሳየት ነው፡፡ ‹‹ ነገር ግን የኃጢአትን ሥራ ይሽር ዘንድ ከእርሱ ጋር የተሰቀለውን አሮጌውን ሰውነታችን እንደሆነ ይህን እናውቃለን ›› የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ (ሮሜ 6፡6) እኛን ወደ ቀደመ ክብራችን ለመመለስ የተከፈለውም ዋጋ ታላቅ ከሆነው የጋብቻ ምስጢር ጋር በማያያዝ እንዲህ ገልፆታል ‹‹ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው ቤተ ክርሰቲያን ራስዋ አዳኝዋም እንደሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ ነውና … ወንዶችም ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደዳት ራሱንም ስለእርስዋ ቤዛ አድርጎ እንደሰጠላት ሚስቶቻቸውን ይውደዱ፡፡ በውኃ ጥምቀትና በቃሉ ይቀድሳትና ያነጻት ዘንድ የነጻችና የተቀደሰች ትሆን ዘንድ እንጂ በላይዋ እድፈት ወይም ርኩሰት እንዳይገኝባት ቤተ ክስቲያኑን ለእርሱ የከበረች ያደርጋት ዘንድ…›› ኤፌ 5፡23-28 ስለዚህ ጌታችን በደሙ ኃጢአታችንን እንደ ቸርነቱ ይቅር ብሎናል፡፡ኤፌ 1፡7 ከእንግዲህ የራሳችን አይደለንም፡፡ በሰውነታችንም ኃጢአትና ዐመፃን ልናደርግበት አይገባም፡፡‹‹በዚህ በሚሞት ሥጋችሁ ኃጢአት አታንግሷት፤ ለምኞቱ እሺ አትበሉት፡፡ ከሙታን ተለይቶ እንደተነሳ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጉ እንጂ ሰውነታችሁን ለኃጢአት የዐመፅ የጦር መሣሪያ አታድርጉት፤ ሰውነታችሁንም ለእግዚአብሔር የጽድቅ የጦር መሣሪያ አድርጉ››ተብለናል፡፡ (ሮሜ6፡12-13)
የተወደዳችሁ ምዕመናን እግዚአብሔር ደስ ብሎት የሚቀበለውን ህይወት ለመኖር አንፈልጋለን ፡፡ ለመሆኑ ይህ ሊሆን የሚችለው እንዴት ብንመላለስ ነው? መልሱን ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ቢኖር የእርሱ አምልኮቱ ከንቱ ነው፡፡ ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ወላጆች የሌሉአቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በችግራቸው መጠየቅ በዓለምም ከሚገኝ ርኩሰት ሰውነትን መጠበቅ ነው፡፡›› በማለት ይመልስልናል( ያዕ 1፡26-27)፡፡ በክርስቶስ ደም የተቀደሰና የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆነውን ሰውነታችንን በዓለም ከሚገኝ ርኩሰት መጠበቅ የሰማያዊ ርስት ወራሾች ያደርገናል፡፡ በዓለም የሚገኘውን ርኩሰትም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የሥጋ ሥራ›› በማለት ገልጾታል፡፡ ‹‹እርሱም ዝሙት፣ርኩሰት፣መዳራት፣ጣዖት ማምለክ፣ሥራይ ማድረግ፣ መጣላት፣ ኩራት፣ የምንዝር ጌጥ፣ ቅናት፣ ቁጣ፣ ጥርጥር፣ ፉክክር፣ምቀኝነት፣ መጋደል፣ ስካር ፣ይህንም የመሰለ ሁሉ ነው፡፡›› እነዚህን የሚያደርጉ ሰዎችም ከመንግስተ እግዚአብሔር በአፍአ ወይም በውጭ እንደሚቀሩ ሲያስረዳ ‹‹አስቀድሜ እንደነገርኋችሁ ይህን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግስት አያይም›› ብሏል ( ገላ5፡19)።
በሕይወታችን ሁሉ የምግባርና የሃይማኖት ፍሬ አፍርተን መገኘት ለቅድስና የጠራንን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ነው፡፡ እነዚህንም ነገሮች ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የመንፈስ ፍሬዎች ›› ብሏቸዋል፡፡ እነርሱም ‹‹ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግስት፣ ምጽዋት፣ ቸርነት፣ እምነት፣ ገርነት ንጽሕና›› ናቸው፡፡ ገላ 5፡22 እግዚአብሔር ማደርያው ይሆን ዘንድ የመረጠውን ሰውነታችንን እርሱ የሚከብርበትን ሥራ ልናደርግበት ያስፈልጋል፡፡ ‹‹በሕይወት የሚኖሩትም ስለ እነርሱ ቤዛ ሆኖ ለሞተውና ለተነሣውም እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው የሚኖሩ እንዳይሆኑ እርሱ ስለሁሉ ቤዛ ሆኖ ሞተ›› እንደተባለ በሕይወታችን ሁሉ ፋቃዱን በመመርመርና በመፈጸም በቅድስና ልንኖር ይገባናል፡፡ 2ቆሮ 5፡15 ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)፡፡ ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ ፣በማኅበራዊ ኑሯችን፣ በምንበላው ምግብ፣ በምንለብሰው ልብስ፣ በንግግራችንና በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን በማድረግ እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን
በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ ፣ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር ይገባናል(ዕብ 12፡1)። ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@And_Haymanot
@And_Haymanot
ምኩራብ ሙሉ ንባቡን ለማንበብ
👉 https://tttttt.me/And_Haymanot/1313
Share Share
@And_Haymanot
** ምኩራብ ***

@And_Haymanot

በዓብይ ፆም ከ<<ቅድስት>>ቀጥሎ ያለው የእሁድ ሰንበትና የተያያዘው ሳምንት << ምኩራብ >>ይባላል።<<ቤተ
መቅደስ>>ወይም ክርስትናን ከእግዚአብሔር የተቀበሉ ወገኖች
ተሰብስበው ወደ ፈጣሪያቸው የሚፀልዩበትና በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት ለመላው የሰው ዘር የተሰጡትን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋዎች የሚያገኙበት የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የሚቀበሉበት ቦታ <<ቤተ ክርስቲያን>> እንደሚባል ማለት ነው።
በህገ ኦሪቱ እምነት ጸንተው የቀጠሉት አይሁድ ዛሬም የጸሎት ቦታቸውን << ምኩራብ >>እያሉ ይጠሩታል።
የዚህ ስያሜ ሚስጢር እንደሌሎቹ ሁሉ ስፋትና ጥልቀት አለው። ይኸውም እግዚአብሔር አብ እውነተኛና የተቀደሰ ማደሪያው ይሆን ዘንድ ጥንቱንም በመለኮታዊ ቸርነቱና ጥበቡ የሠራው
ኋላም በመጨረሻ ዘመን በልጁ መስዋዕትነትና የምሕረት ቃልኪዳን ለሥርየት አብቅቶና በትንሳኤ ሕይወት አድሶ ለዘለዓለማዊ ህልውና ያዘጋጀው <<ቤት>> ወይም <<ሕንፃ>>
በፍጡር እጅና በተፈጥሮ ቁሳቁሶች የተሰራውን ሳይሆንእርሱ በአርአያውና በመልኩ የፈጠረው ራሱ <<ሰው>>መሆኑ ተረጋግጦ የሚታወስበት የሚነገርበትና የሚታወቅበት ሰሞን ከዚች ዕለተ እሁድ ጀምሮ ባለው ሳምንት በመሆኑ ነው።
1ኛቆሮ.3፥16፣ዘፍ.1፥26 ይህንም እውነታ ደቀ መዛሙርቱ የሆኑት ሐዋርያት ሳይቀሩ የተረዱትና የተገነዘቡት መምህራቸው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በመስቀል መከራ ሞቶ ከተነሣ መንፈስ ቅዱስም ከወረደላቸውና ካደረባቸው በኋላ መሆኑን በዕለቱ የሚዘመረው፤የሚሰበከውና
የሚነበበው የነበያቱ ትንቢትና የአዲስ ኪዳኑ ምስራች እንዲህ በሚሉ ቃላት እያብራሩ ያመለክታሉ፦ <<እስመ ቅንዓተ ቤትከ በልአኒ ትእይርቶሙ ለእለ ይትዔብሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻእክዋ በጾም ለነፍስየ።>> ማለትም
<<የቤትህ ቅናት በልታኛለችና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ
ወድቋልና ሰውነቴን በጾም ቀጣኋት።>>ዮሐ.2፥16
ደግሞም የአይሁድ የፋሲካቸው በዓል ቀርቦ ነበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ በሙክራብም
ላሙን፣በጉን ርግቡን የሚሸጡትንም የሚገዙትንም ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ ከገመድ የተሰራ አለንጋን አበጀ። በጉን ላሙንም ሁሉንም ከሙኩራብ አስወጣ። የለዋጮችንም ወርቅ
በተነ፤መደርደሪያቸውንም አፈረሰ። የርግብ ሻጮችንም ወንበር ገለበጠ። ርግብ ሻጮችንም ይህን ከዚህ አውጡ ወዲያ በሉ የአባቴን ቤት የገበያ ቦታ አታድርጉት አላቸው።ማቴ.21፥12
ደቀ መዛሙርቱም <<የቤትህ ቅናት በላኝ>> የሚል ቃል ተጽፎ እንዳለ አስታወሱ። አይሁድም መልሰው ለዚህ ድርጊትህ ምን ምልክትን ታሳያለህ አሉት።ጌታችንም ኢየሱስም ይህን ቤተ
መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛውም ቀን አነሳዋለው ብሎ መለሰላቸው። አይሁድም ይህን ቤተ መቅደስ በአርባ ስድስት ዓመታት ተሠራ አንተስ በሦስት ቀኖች ውስጥ ታነሳዋለህን አሉት። እርሱ ግን<<ቤት>>ስለተባለው ስለሰውነቱ ቤተ መቅደስ ነገራቸው።

ከሙታን በተነሳ ጊዜም ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንደነገራቸው አሰቡ በመጻሕፍት ቃል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በነገራቸው ነገርም አመኑ። ዮሐ.2፥19-23 ታላቅ ምሥጢራዊ መልዕክት ያለውን ይህን የአምላክ ቃል
ለማጠናከር ተያይዘው ከሚጠቀሱት የቅዱሳን መጻሕፍት ቃላት መካከል እንዲህ የሚሉት ይገኛሉ።
<<አንትሙሰ ሕንፃ እግዚአብሔር አንትሙ!...ኢተአምሩኑ ከመ
ታቦቱ ለ እግዚአብሔር አንትሙ ወመንፈሰ እግዚአብሔር ኅዱር
ላዕሌክሙ። >>ማለትም << የእግዚአብሔር ሕንፃ ናችሁ...እናንተ የእግዚአብሔር ታቦቱ ቤተ መቅደሱም
እንደሆናችሁ የእግዚአብሔር መንፈስም አድሮባችሁ እንደሚኖር አታውቁምን? ማንም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል። የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና ያውም እናንተ ናችሁ።1ኛ ቆሮ.1፥16 ወይስ
ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁትና በእናንተ የሚኖረው
የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደሆነ አታውቁምን?... የእግዚአብሔር ታቦትንስ በጣዖት ቤት የሚያኖር ማን ነው? እኛ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነንና።>> << ምኩራብ >> በተባለው በዚህ እለተ እሁድና ተያይዞ ባለው
ሳምንት ውስጥ የእነዚህ ምስጢራውያት ቃላት ማጠቃለያ ፍቺ ተብራርቶና ተስፋፍቶ ይነገርበታል። ሰው የሆነውን አምላክ እንዲያ እንደ እሳት ያቃጠለው ቅንዓት የተነሳሳበት የሰዎች እጅ በሠራውና<< የእግዚአብሔር ቤተ
መቅደስ >>ተብሎ የርኩሰት ተግባር የተፈፀመበት በሚዘመርበት ሕንፃ ውስጥ ሲካሄድ ባየው አሳዛኝ ሁኔታ አለመሆኑ ይግለጽበታል።
ነገር ግን ራሱ እግዚአብሔር የዘለዓለም ማደሪያው ይሆን ዘንድ በመልኩ ፈጥሮ ያነፀው ሰብአዊው አካል የክፋት መንፈስ
መፈንጫና መጫወቻ ሆኖ መኖሩን በማወቁ መሆኑ ይነገራል። እንዲሁም ከገበያ የርኩሰት መደብርነት አጥርቶ በቅድስናው ያነፃው ይን ሰው የሠራውንና የሚያፈርሰውን በድን ህንፃ ሳይሆን፤ራሱ የለበሰውን የሰውነት አካል የመሰለውን የሰውን ሁሉ ሕያው ልቡና የመሆኑ ምሥራች ይታወጅበታል።
ለዚህ የእግዚአብሔር እውነት ቅዱስ እስጢፋኖስ <<ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት እኔም በሦስተኛው ቀን አነሳዋለው።>> ብሎ የተናገረውን የራሱን ቃል ራሱ የፈፀመውን ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስን በመምሰል የመጀመሪያው መስካሪ ሆኖ በሰማዕትነት
ተሰውቶበታል። ይህም <<ሰማይ ዙፋኔ ነው።ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት።ለእኔ ምን አይነት ቤትን ትሰራላችሁ ይላል ጌታ ወይስ የማርፍበት ሥፍራ ምንድን ነው?ይህንስ ሁሉ እጄ የሰራችው
አይደለምን?እንዳለ ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም።>> ሲል ይኸው ሰማዕት የነብዩን እየጠቀሰ በተናገረው ደግሞም ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ እምላክ እርሱ የሰማይና
የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም። እርሱ ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም። በሚለው በሐዋርያው ቃል ተረጋግጧል።ዮሐ.7፥47
የሰንበት ረድኤትና በረከት ይደርብን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክቡር ይቆየን።
ምንጭ፦የኢየሱስ ክርስቶስ ጾምና ስቃዩ ከዘወረደ እስከ ጰራቅሊጦስ ከሚለው መጽሐፍ
አዘጋጅ፦ ሊቀ ኅሩያን የማነብርሃን ገበየው
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ከፊታችን የሕዝብና ቤት🏘 ቆጠራ አለ፡፡ አደራ እምነትን/ሐይማኖትን በተመለከተ ስትሞሉ ክርስቲያን ብቻ እንዳትሉ፤ ብዙ አይነት ክርስቲያን አለ፡፡

መሙላት ያለባችሁ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ / ክርስቲያን በሚል ይሁን፡፡ ይህንንም ለሌሎችም አድርሱ…
👉"ብፁዕ አቡነ አብረሃም
Share
@And_Haymanot