፩ ሃይማኖት
8.96K subscribers
246 photos
29 videos
21 files
96 links
ኦርቶዶክሳዊ ምላሾች
የሚቀርቡበት፡፡
👉"፩ ኃይማኖት"👈
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የገሀነም ደጆች አያናውጧትም
✞ እ...ና...ታ...ች...ን
#አ__ት__ታ__ደ__ስ__ም፡፡
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
ለአስተያየት
@And_Haymanot_bot

፩ ሃይማኖት ኤፌ 4፥5
Download Telegram
‹‹ቤዛ›› ማለት ምን ማለት ነው?

እናታችን ቅድሥት ድንግል ማርያም የአለም ቤዛ ናትን ?

@And_Haymanot

ብዙ ጊዜ ድንግል ማርያም እንዴት የአለም ቤዛ ትሆናለች? ይላሉ፤ በእርግጥ ግን እናታችን ቅድሥት ድንግል ማርያም የአለም ቤዛ ናት ።
‹‹ ቤዛ ›› በቁሙ ሲተረጐም ዋጋ አለው ወይም ጥቅም አለው ማለት ነው ። እንዲሁም ቤዛ የሚለው ቃል "ቤዘወ"፦ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ቤዛ በቁሙ ሲተነተን እንዲህ ማለት ነው ። ዋጋ ፣ ካሳ ፣ ለውጥ ፣ ምትክ፣ሀላፊ ፣ ዋቢ ፣ ዋሥ ፣ መድኅን ፣ ተያዥ ፣ ጥላ ፣ ጋሻ ... ማለትነው ። ቤዛ በደቂቅ አገባብ ሲፈታ ደግሞ ሥለ፣ ፋንታ፣ ምክንያት የሚሆንተብሎም
ይተረጐማል ። አለቃ ኪዳነ ወልደ ክፍሌ መፅሐፍ ሠዋሠው ውግሥ በመዝገበ
ቃላት ሐዲሥ 1948 ዓ ም ገፅ 266፡፡ ወይምደግሞ በሌላ መንገድ ከሣቴ ብርሐን ተሠማ መፅሐፋቸው ቤዛ ሲተረጉሙ እንዲህ ብለው አሥቀምጠውልናል ለውጥ፣ካሣ፣ወይም ደግሞ በአንድ ሠው ላይ መከራና ሞት ተላልፎ መሞትማለት ነው ወይም ታደገኝ ወይም ምትክ ሆነኝ ማለት ነው ወይም ደግሞ ለመከራ ለሞት ለወጠኝ ማለት ነው ወይም ቤዛ ሆነኝ ማለትነው።

የበለጠ ለመረዳት አልያም ቤዛ ሥለሚለው ቃል በደንብ ለማወቅ እነዚህን መፅሐፍቶች መመልከት ይቻላል ። እንደዚሁምቤዛ የሚለው ቃል ፦ ካሣ ፣ የደም ቤዛ ፣ አንዱ ሠው የሠውንደም ሥለሚያፈሠው ለውጥ ወይም ዋጋን ፣ ገንዘብን ፣ ካሣን መሥጠት ወይም መዋጀት ማለት ነው ። ከሣቴ ብርሐን 1951 ዓ.ምገፅ 532

ድንግል ማርያምን ስለምን የአለም ቤዛ እንላታለን? የእመቤታችን ቤዛነትም ከላይ በተረዳነው መሠረት ቤዛ ከሚሉት የትርጓሜ ቃላት መካከል ምትክ፣ ዋሥ፣ምክንያት ... ከሚሉት መካከል ምትክ የሚለውን ስንወስድ
ድንግል ማርያም የህይዋን(ሔዋን) ምትክ በመሆኗ ነው፤ ‹ምክንያት› የሚለውን ስንወስድ ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም ለኛ መዳን ምክንያት ስለሆነች ነው። እግዚአብሔር ለአለም መዳን በድንግል ማርያም ታላቅ ስራን አድርጉአልና ቤዛዊት ዓለም እንላታለን። የድንግል ማርያም በእምነት መታዘዝ ለዓለም መዳን
ምክንያት ሆናለች። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ከስጋዋ ስጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነስቶ ዓለምን ስለተቤዤ ቤዛዊት ዓለም እንላታለን። ቤዛ የሚለው ቃል ለሙሴም ተሰጦት እናነባለን። ( የሐዋ ሥራ 7:35) በመልአክ እጅ
እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው። እንግዲህ ይህ የፍጡር ቤዛነት የእግዚአብሔርን ቤዛነት ይሽራልን? አይደለም፡፡ እንዲያውም ቸር እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የሚሰጠውን የባለሟልነት ስጦታ ብዛት ይገልፃል እንጂ፡፡ ሙሴ
ወገኖቹን ከመጥፋት እንደምን አዳናቸው(ተቤዣቸው)(ታደጋቸው)? እንደክርስቶስ ደሙን በማፍሰስ ነውን? አይደለም በእግዚአብሔር ዘንድ ‹ይህን ኀጢአታቸውን
ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን ከጻፍኸው መጽሐፍኽ እባክኽ ደምሰሰኝ›
በማለትየተወደደፀሎቱንበማቅረብእንጂ (ዘጸ.32፤32) ፡፡ ዳዊትም ‹ሙሴ
በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም ኖሮ›› ሲል የገለፀው ይሄንኑ ነው፡፡ስለዚህም
መጽሐፍ የፃድቅሰውፀሎት በስራዋ እጅግ ሃይልን ታደርጋለች ይላል፡፡

የእመቤታችንና የድንግል ማርያም ቤዛነት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርሥቶስ ቤዛነት ጋር ያለው ልዩነትእጅግ የሚራራቅ ነው። ጌታችን በሞቱ የተደረገ ቤዛነት ነው ። እንዲሁም በደሙ ዋጅቶ በሞቱ የተደረገ ቤዛነት ነው። ቤዛ ማለትእራሥን
ሥለሌሎች አሣልፎ መስጠት ማለት ሥለሆነ ጌታችንም ሥለበጐቹ እራሱን አሣልፎ ሠጥቷል ሆኖም የአለም ቤዛ ነው ። ታዲያ የአለምቤዛ ክርስቶስ ከሆነ ድንግል ማርያምስ ቤዛዊት አለም መባሏ ስለምን ነው ቢሉ፦ ክርስቶስ አለምን ሁሉ ከሞት ወደህይወት ያሻገረበት፣ ሃጢአታችንን ሁሉ የደመሰሰበት፣
የሚደመስስበትም ክቡር ደሙ፣ ቅዱስ ስጋው ከእመቤታችን ስለነሳው ነው፤ በዚህም ክርስቶስ ከመወለዱ አንስቶ በቤተልሄም የከብት ግርግም ተጀምሮ፡ በግብፅ ስደቱ በቀራኒዮ ስቃዩና ሞቱ ሁሉ አብራው አለችና በክርስቶስ የድህነት
ስራ ውስጥ የእመቤታችን ስራ ጉልህ ሆኖ ይታያልና ነው፡፡

ለማጠቃል ያክል፡-
ሙሴ ምክንያት ሆኖ ነጻ ያወጣቸው ለጥቂት ነገዶች ወይም ‹ለእስራኤላውያን› ብቻ በመሆኑ‹‹ቤዛ›› ብቻ ተብሏል፡፡ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ግን ምክንያተ ድኅነት ሆና ነጻ ያወጣችው ‹ዓለም ሙሉ› ስለሆነ (ክርስቶስ ለዓለም ሁሉ ተሰቅሏልና) ‹‹ቤዛዊተ ዓለም›› ትባላለች፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን ለቅዱሳንም በጸጋ ተሰጥቷል፤
በመጸሐፍየጸጋ አምላክነት ለቅዱሳን ተሰጥቶ እናያለን ‹እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦እይ፥እኔ ለፈርዖን አምላክ አድርጌኻለኹ›፤ ክርስቶስየዓለም ብርሃን እንደሆነ እንዲሁ ደግሞ ቅዱሳንንም ‹እናንተየዓለም ብርሃን ናችኹ› በማለት በጸጋ የዓለም ብርሃን እንደሚባሉ መጽሐፍ ምስክርነው ( ዘጸ7፤1 ማቴ 5፤14)
የቤተክርስቲያን ትምህርት እንዲህ ነዉ፤ ክብርና ምሥጋና ለቤዛዊት አለም ለእመቤታችን ለቅድሥት ድንግልማርያም ይሁን
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
🙏1
የሚቀጥለው ርእሳችን

የድንግል ማርያምን ዘልአለማዊ ድንግልና እና ከዮሴፍ ሌሎች ልጆችን ወልዳለች(ላቲ ስብሃት) ለሚሉ በሰፊው በክፍላት እንዳስሳለን
------- #Share --------
ሼር በማድረግ በርቱ ብዙ ሼር ሲደረግ ነውና ለብዙዎች መድረሱን(መነበቡን) አውቀን ሌላ ክፍል የምንለቀው። በተጨማሪም የምናነሳው ርእስ ብዙ ጠያቂን እየፈጠረ ነውና ነፍሳትን ማዳን እና ከተሳሳተ መንገድ ለመመለስ እንትጋ!
🙏አምላከ ድንግል ማርያም ይርዳን 🙏
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?

@And_Haymanot

ይህን ትምህርት የምታነቡ ሁሉ በማስተዋል እና በጽሞና ትረዱ ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡ ለዘመናት የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለመቃወም ዲያቢሎስ ያዘመታቸው መናፍቃን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ሁሉ የማያዳግም መልስ በዝርዝር እና በአንድምታ ቀርቧል ፡፡ ከጌታ ውጭ ከቅዱስ ዮሴፍ ልጅወልዳለች ብለው ለተሰናከሉ ሁሉ በዚሁ አጋጣሚ ስለ ዮሴፍ ማንነት ጭምር ትምህርቱ በጥቂቱ ይዳስሳል መልካም ንባብ ፡-

👉 ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ማነው ?

መናፍቃን ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ከዮሴፍ እንደወለደች ሲናገሩ እንሰማለን ማስረጃ ባይኖረውም ፡፡ ነገር ግን የዮሴፍን ማንነት በጥቂቱም ቢሆን መረዳት ለስህተታቸው ማሰታገሻ መድኃኒት ነውና እነሆ ፡- አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ሀገሩ ናዝሬት ሲሆን ሐናፂም ነጋዴም ነበር ፡፡ ዘሩ ከዳዊት ወገን ነው ፡፡ ሦሰት ሴቶች እና አምሥት ወንዶች ልጆች ነበሩት ፡፡ ልጆቹ ገሚሶቹ ከ12ቱ ሐዋርያት ገሚሶቹ ደግሞ ከ72ቱ አርድዕት ውስጥ የነበሩ ሲሆን ከሚስቱ ጋር 52 ዓመት ፤ ሚስቱ ከሞተች በኋላ
ደግሞ 40 ዓመት ኖሯል ፡፡ በድምሩ 92 ዓመት ከኖረ በኋላ ለእመቤታች ጠባቂ ሆኖ ተመረጠ ፡፡ ከእመቤታችን እና ከጌታ ጋር ደግሞ በስደት ፣ በመከራ 22 ዓመታትን አሳልፏል ፡፡ ሊጠብቃትም ሲመረጥ ከ1,985 ሽማግሌዎች
ውስጥ ዕጣ ደርሶት ነው ፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም የከተሰበሰቡት ሁሉ የርሱ በትር ለሦስት ጊዜ ያህ በተደጋጋሚ አብባና ለምልማ ተገኘች ፡፡ አረጋዊ ዮሴፍ በ114 ዓመቱ ሐምሌ 26 ቀን አርፏል ፡፡ ከማረፉ በፊት ግን ጌታችንን ‹‹ ሥጋዬን በዚህ ምድር አታስቀረው ›› ብሎ ለምኖት ነበርና ዛሬም ድረስ ዮሴፍ መቀበሩን እንጂ ቅዱስ ሥጋው የት እንዳለ የሚያውቅ የለም ጌታ ስለ ጸሎቱ (ስለልመናው) ሰውሮታልና ፡፡ ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ለምን ተመረጠ ? *ይህ ጻድቅና ንጹሕ አረጋዊ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን ሊጠብቅ ስለተመረጠበት ምክንያን አስረጋጭ

ማስረጃዎች እነሆ ፡፡

1ኛ) አገልጋይዋ ተላላኪዋ ሆኖ
ሊጠብቃት ፡፡

2ኛ) መከራዋን እንዲጋራ ፡፡ አንድም ዮሴፍ ዘመዷ ነው መከራን ለብቻ አይዘልቁምና በልጇ አማካኝነት የሚደርስባትን ስደት እና መከራ አብሯት እንዲካለፈል ነው ፡፡ ዝምድናቸው ሲዘረዘር የሚከተለውን ሃቅ ያስረዳናል ፡- + ግንዱ ‹‹ አልዓዛር ›› በሁለት
ወገን የሚከተሉትን ወልዷል ፡-
* ማታን = * ቅስራ*
* ያዕቆብ = * ኢያቄም *
* ዮሴፍ = * ድንግል ማርያም
(የነዚህ የዘር ሐረጋት ግንዱ ከላይ እንዳየነው * አልዓዛር * ነው ስለዚህ የዘር ሃረጋቸው አንድ ነውና ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት አይችልም)

3ኛ) ከመደብደብ ሊያድናት ፡፡ በኦሪ.ዘኁ 5፥19 በተጠቀሰው መሠረት አንዲት ሴት ከባልዋ ውጭ ጸንሳ ብትገኝ ማየ ዘለፋ ያጠጥዋት ነበር ፡፡ እንዲሁም አንዲት ሴት ባል ሳታገባ ብትጸንስ በሙሴ ሕግ መሠረት ደብድበው ይገድሉአት ነበር
፡፡ ስለዚህ እመቤታችን ለዮሴፍ ሳትታጭ ቀርታ ቢሆን ለድብደባ ባበቁአት ነበር ፡፡

4ኛ) ትንቢቱ እንዲፈጸም ነው ፡፡ ጌታ ከዳዊት ቤት እና ወገን እንዲወለድ ኢሳ 11፥1 ፣ 10 ላይ ትንቢት ነበር ፡፡ ዮሴፍም የዳዊት ዘር ነውና ክርስቶስ በዮሴፍ የዳዊት ልጅ ተብሎ እንዲቆጠር ነው ፡፡ ምነው በእናቱ የዳዊት ልጅ አይባልምን? ቢባል አይሁድ ሴትን ከትውልድ ቁጥር አግብተው አይቆጥሩምና ነው ፡፡

5ኛ) ኃይለ አርያማዊት (ከሰማይ ወረደች እንጂ ምድራዊት አይደለችም) የሚሉ ወገኖች ነበሩና ምድራዊት መሆኑኗን ለማጠየቅ ነው ፡፡ ሆኖም
ከምድር መገኘቷን ለመግለጽ እንጂ ድንግል ማርያም በክብሯ ሰማያዊት ናት ፡፡ የባሕርያችን መመኪያ መባሏም ከሰው ዘር መገኘቷን ልብ እንዲሉ ነው ፡፡ ስለዚህ ድንግል ማርያም ለዮሴፍ መታጨቷ ስለዚህ እና ይህን ለመሰለ ምክንያት ነው እንጂ ለሚስትነት አልነበረም ፡፡ አንድም ዮሴፍ እመቤታችን ሊጠብቃት በተመረጠ ጊዜ ጀርባው ጎብጦ ፣ ጉልበቱ ዝሎ ፣ ዓይኑ ሞጭሙጮ ነበር 92 ዓመት አልፎት
ነበር አረጋዊ(ሽማግሌ) መባሉም ለዚህ ነው ፡፡ በሆኑም አረጋዊ ዮሴፍ ስለነዚህ ምክንያት ድንግል ማርያም ሊጠብቃት ተመረጠ እንጂ ሊያገባት አይደለም፡፡ ሊያገባት የተመረጠ ቢሆን ኖሮ ድንግል ማርያም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ ‹‹ ወንድ ስለማላውቅ እንዴት ይሆናል ›› ባላለችውም ነበር ፡፡ ሊያበሥራት የተላከው ለዮሴፍ ከታጨች በኋላ ነውና ፡፡ በዚህም ንግግሯ ለዮሴፍ የታጨችው ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት እንዳልሆነ አረጋግጣለች፡፡ ዛሬ የተነሱ መናፍቀን ምሥጢር ይጎድላቸዋልና ዮሴፍን እንደወጣት ሰው ቆጥረው ድንግል ማርያምን ሊያገባ እንደታጨ በደካማ ጎናቸው ያስባሉ እውነቱ ግን ይሄ ነው ፡፡
ይቆየን ....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር

፩ ሃይማኖት ተዋህዶ

✞_✞_✞
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
👏1
​​እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?

📕 ክፍል ሁለት

📜 @And_Haymanot

እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት(ወልዳለች) በማለት ኑፋቄያቸውን ለሚዘሩ የተሃድሶዎ መናፍቃን በተከታታይ በዚህ ርእሥ የቤተክርስቲያናችንን ምላሽ ማቅረባችንን ቀጥለናል

@Konobyos

‹‹‹ የእጮኛ ትርጉም ›››

እጮኛ የሚለው ቃል ጠባቂ ማለት ነው፡፡ ሌላ ከሰው ልብ የፈለቀ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም፡፡ 👉ለምሳሌ ‹‹እናንተን ለዘለዓለም ለእኔ እንድትሆኑ አጭቻችኋለሁ ›› ሆሴ 2፥21 ማለት ለጋብቻ ነውን? ያሳዝናል አጣመው ለተረጎሙት፡፡ 👉አሁንም ሐዋርያው ከጌታችን ጋር ስላዋሐዳቸው ‹‹ ለእርሱ አጭቻችኋለሁ›› 2ኛ ቆሮ 11፥3 ማለቱን እናስተውል፡፡
👉እንደገናም ምእመናንን የከበረች ማደርያው ስላደረጋቸው ‹‹ለሰማያዊው ክብር አጭቻችኋለሁ ›› ኤፌ 5፥26 ታዲያ እንዲህ ሲል ላጋባችሁ ነው ማለት ይሆን(ሎቱ ስብሐት) ፡፡
እመቤታችን ንግሥተ ሰማይ ወምድር ነችና በ15 ዓመቷ መለኮት ተዋሐዳት ፡፡ ሲዋሐዳትም ለዮሴፍ ታጨች ሉቃ1፥26፡፡ እንግዲህ እጮኛ ማለት ትርጉሙን ያላወቁ ይወቁ እንላለን ፡፡ ነገር ግን ሰው በራሱ ፍቃድ አይተርጉም !!! ሌላው እጅግ የሚደንቀው ነገር ደግሞ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከመውለዷ በፊት እንጂ ከወለደች በኋላ ዮሴፍ ‹‹ እጮኛ›› ተብሎ በአንድም ስፍራ አለመጠቀሱ ነው
👉ማስረጃ ‹‹ ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ ›› ማቴ 2፥3 እንዲሁም በግብጽ 3 ዓመት ከ3ወር በስደት ከቆዩ በኋላ ይህንኑ ቃል ለዮሴፍ በህልም ተነግሮት ‹‹ ሕጻኑን የሚፈልጉት ሞተዋልና ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ናዝሬት ተመለስ ›› አለው እንጂ እጮኛህን (ሚስትህን) ይዘህ
ተመለስ አላለውም ማቴ 2፥20፡፡

‹‹‹ የበኩር ትርጉም ›››

የበኩር ልጇን ወለደች የሚለው ቃል ብዙዎችን አሳስቷል ፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው በተለምዶ የበኩር ልጅ የሚባሉ የግድ ተከታይ ያላቸው መሆን አለባቸው የሚል አስተሳሰብ በመናፍቃን ክፉ ልቦና ስለሰረጸነው፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የሚባል ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ጋር አይሰራምና እንዲህ ይታረማል
👉፡- ‹‹ እግዚአብሔር ሙሴን ከእስራኤል ልጆች ዘንድ ከሰውም ከእንስሳትም ማኅጸንን የሚከፍት በኩር ሁሉ ለእኔ ቀድስልኝ አለው ›› ዘጸ 13፥1-2 ይህ ቃል እንደሚገልጸው በኩር የሚባሉት ለመጀመርያ ጊዜ ከእናታቸው ማኅጸን የሚወጡ መሆናቸውን እንጂ ግዴታ ተከታይ ሊኖራቸው እንደማይገባ ያረጋግጣል ፡፡ አንድም ብቻ ቢሆን የእናቱም ማኅጸን ለመጀመርያ ጊዜ ከፍቶ ከወጣ ተከታይም ባይኖረው በኩር ነው ፡፡ ይሄ የበኩር ትርጉም ካልገባን ወደ ሌላ ፤ ይልቁን ወደ ማንወጣው አዘቅት መዘፈቃችን አይቀሬ ነው ፡፡
👉ለምሳሌ ቆላስየስ 1፥7 ላይ ስለ ክርስቶስ ሲናገር ‹‹ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኩር ነው ›› ይላል እዚህ ጋር በኩር የሚለው ቃል ተወዳዳሪ ላላቸው ነገሮች የሚጠቀስ ሆኖ ከቀረበ ጌታን ፍጡር አድርጎ ከፍጡራን ጋር አነጻጽሮ እርሱ ከፍጥረታት በፊት ቀደም ብሎ የተፈጠረ ፍጡር ነው እንደማለት ይሆናልና(ሎቱ ስብሐት)፡፡
እንደገናም በኩር የሚለውን ቃል በሥጋዊ ደማዊ ሃሳብ ከተረጎምነው ዕብ 1፥6 ላይ 👉‹‹በኩርን ወደ ዓለም ሲያገባ ›› የሚል ቃል አለ እዚህ ላይ የክርስቶስ በኩር ተብሎ መጠራት አብ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የባሕርይ ልጁን ወደ መሬት ሂድ ፣ ውረድ ተወለድ ፣ ሙት ተሰቀል ብሎ እንደላከው ለመግለጽ ነው ፡፡ ታድያ አብ በኩርን ወደ ዓለም ሲልክ በኩር የሚለው ቃል ተጠቅሷልና አብም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ አለው ማለት ነውን? እናንት ግብዞች መናፍቃን የመጽሐፍን ቃል በግርድፍ መረዳት ምን ያህል እንደሚያስት ይረዱ ድንግል ማርያምን የነኩ እየመሰላቸው ባለቤቱን መንቀፋቸው ያሳፍራል !!!
እርሷስ ክብር ይግባትና በተቃዋሚዎች አፍ አትረክስም እርሱ ባለቤቱ አንዴ አክብሯታልና ፡፡ ‹‹ የበኩር ልጇን ወለደች›› መባሉ መጀመርያና መጨረሻ የሌለውን አምላከ አዶናይ ፣ ልዑለ ባሕርይን ወለደች ማለቱ ነው፡፡

ይቀጥላል
📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@Konobyos
Join
@And_Haymanot
Join
@And_Haymanot

ለሌሎች ሼር በማድረግ ኑፋቄያቸውን አብረን እንዋጋ

የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡ ♥️
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
❖ መልካም አዲስ አመት አትበሉን!!!!!!!

@And_Haymanot

የ ፳፻፲፩ (2011) ዓ.ም የመልካም ምኞት መግለጫ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ማኅበራዊ ሚዲያዎች 'መልካም አዲስ አመት' ሲሉ "መልካም አዲስ ገረድ' ማለታቸው መሆኑን ያውቃሉ......
"አመት" ተብሎ በአልፋው "አ" ሲጻፍ ሴት አገልጋይ ገረድን ይገልጻል። ለምሳሌ፦ "ተፈሥሒ ኦ አመት ወእም ድንግል ወሰማይ ሰማያዌ..." /ውዳሴ ማርያም ዘረቡዕ/ ሲል ገረድ(ሴት አገልጋይ) ና እናት፤ ድንግልና ሰማይ ሆይ ደስ ይበልሽ ማለት ነው።

"ዓመት" ሲሆን ዘመን ይሆናል። "...ርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ።..."/መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ፤ ለሥእርተ ርእስከ(ለራስ ጸጉርህ)/ ሲል ደግሞ "የመጥቅዕና የአበቅቴ መጀመሪያ ርእሰ ዓመት ዮሐንስ ሆይ..." ማለት ነው።

አመት የሚለው በብዙ ቁጥር አእማት ይሆናል። በዕብራይስጥ አማህ፤ በሱሪስት አምታ፤ በዐረብኛ ደግሞ አመት ይለዋል። ትርጓሜውም ሴት ባሪያ፤ ገረድ፤ ደንገጥር ማለት ነው። "...በወፍጮ እግር እስካለችው እስከ ባሪያይቱ..." ዘፀ.11፥5 የሚለውን ግዕዙ "አመት እንተ ትነብር ዲበ ማሕረጽ።" ይለዋል። በዚህ አገባብ አማርኛው "ባሪያይቱ" የሚለውን ግዕዙ "አመት" ይላታል።
ወንዶች ባሪያዎችን "አግብርት" ሲላቸው ሴቶች ባሪያዎችን ደግሞ "አእማት" ይላቸዋል። [ዘፍ.32፥5 ግዕዙን ንባብ ተመልከት]
ዓመት የሚለው ደግሞ በብዙ ቁጥር "ዓመታት" ሲባል ዘመን፥ ዘመናት፥ ብዙ ቀን፥ የዕለታት ድምር ማለት ነው። "በባቢሎን ንጉሥ በብልጣሶር በመጀመሪያው ዓመት" ዳን.7፥1 የሚለውን ግዕዙ "በቀዳሚ ዓመተ መንግሥቱ።" ይለዋል። "የዕድሜህም ቁጥር ብዙ ነውና፥" ኢዮ.38፥21 የሚለውን ግዕዙ "ኊልቆ ዓመታቲከ፥" ይለዋል።

ስለሆነም አንድ ሰው 'እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሰን' ሲል 'እንኳን ለአዲሷ ገረድ አደረሰን' አለ ማለት ነው። ይኼ ደሞ ጸያፍ ነው።
"እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን" ሲል "እንኳን ለአዲሱ ዘመን አደረሰን ማለቱ ነው። ይኸውም የተገባ ነው።
መልካም ምኞታችሁን የገለጻችሁ መስሏችሁ 'መልካም አዲስ አመት' አትበሉን!!!!!
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?

📕 ክፍል ሶስት

📜 @And_Haymanot

ተወዳጆች በዚህ ርዕስ ተከታታይ ምላሽ በመዳሰስ ላይ ነን በመሆኑም ሌሎችን ልንገፋበት ወይም ልንተች ያቀረብነው ሳይሆን የጠፋችሁ እህት ወንድሞቼ በማስተዋል እንድትጓዙ ብሎም እንድትነቁም ጭምር ነው፡፡
የማርያም ልጅ ይርዳን

@And_Haymanot

‹‹‹ የ-እስከ-ትርጉም ›››

ሥጋውያኑ ‹‹ እስከን ›› ተገን አድርገው ‹‹ እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም ›› የሚለውን ቃል ፍጻሜ ላለው ነገር በማስገባት ደግመው ደጋግመው ተሰናክለውበታል፡፡ ትርጉሙ(ፍቺው) ግን ይህ አይደለም ፡፡

ለምሳሌ ፡-
👉 1ኛ) የሣኦል ልጅ ሜልኮል ‹‹እስከሞተችበት ›› ቀን ድረስ ልጅ አልወለደችም 2ኛ ሳሙ6፥23 ፡፡ ይህም ማለት እስከመጨረሻው ልጅ አልወለደችም ማለት እንጂ ከሞተች በኋላ ወለደች ለማለት አለመሆኑ የታወቀ ነው ፡፡
👉 2ኛ) ይህም ነገር በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ጆሮ ተሰማ ‹‹ እስከሞቱ›› ድረስ ይህ በደል በእውነት አየሰረይላቸውም ኢሳ 22፥14 ታዲያ የዚህ ትርጉም ከሞቱ በኋላ ይሰረይላቸዋል ማለት ነውን? እስከዘለዓለም አይሰረይላቸውም ለማለት እንጂ፡፡
👉 3ኛ) ከአዳም ጀምሮ ‹‹ እስከሙሴ ›› ድረስ ሞት ነገሠ ሮሜ 5፥14 ታድያ ከሙሴ በኋላ ሞት ቀረ ማለት ነውን?
👉 4ኛ) እግዚአብሐየር ጌታዬን ጠላቶችህ ለእግርህ መረገጫ ‹‹ እስካደርግልህ ›› ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው መዝ101፥1 ታዲያ ጌታችን ጠላቶቹን (አይሁደን) በሥልጣኑ ከረታ በኋላ በአብ ቀኝ መቀመጡ ቀረ ማለት ነው?
👉 5ኛ) እነሆም እኔ ‹‹ እስከ ዓለም ፍጻሜ ›› ድረስ ከእናተ ጋር ነኝ ማቴ28፥20 ከዓለም ፍጻሜ በኋላ ከእናንተ ጋር አይደለሀም ማለት ነውን ?
👉 6ኛ) ቁራውንም ሰደደው እርሱም ወጣ ውሃውም ከምድር ‹‹ እስከሚደርቅ ›› ድረስ ወዲያና ወዲህ ይል ነበር ዘፍ 8፥7 ሲል ውሃው ከደረቀ በኋላ ወዲያና ወዲህ ማለቱን ተወ ማለት ነውን? እንግዲህ ከላይ በተዘረዘረው የእስከ ትርጉም መሠረት በማቴ1፥25 የተጠቀሰው ፍጻሜ የሌለው ‹‹ እስከ ›› መሆኑን ያስረዳል ስለዚህ ዮሴፍ እመቤታችንን እስከ ፍጻሜው ድረስ በግብር አላወቃትም ነበር ማለትነው፡፡ ከዚህ ውጭ በራሱ ፍቃድ የሚረተጉም ሁሉ የረተገመ ይሁን!!!

‹‹‹ የወንድሞች ትርጉም ›››

አዲስ ኪዳን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ጌታችንን ‹‹ ወንድሞቹ ›› እንደሆኑ ከሐዋርያት ወገን የሚጠቅሳቸው አሉ ፡፡ ይህን በመያዝ ብዙ ጥራዝ ነጠቅ አንባቢያን (መናፍቃን) ጌታ ወንድሞች እንዳሉት እና ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ልጅ እንዳላት በማውራት አነስተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀታቸውን ለማንጸባረቅ ይሞክራሉ ፡፡ ነገር ግን ማንም የራሱን ግላዊ ሃሳብ ከማንጸባረቁ በፊት የመጽሐፍ ቅዱስን የአጻጻፍ ዘይቤ መረዳት ያስፈልገዋል እንላለን ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ
👉 1ኛ) በምን ቋንቋ እንደተጻፈ ፣
👉 2ኛ) በማን ባሕልና ዘይቤ እንደተጻፈ ፣
👉 3ኛ) በየትኛው ዘመን እንደተጻፈ አስቀድሞ ማወቅ ለማነበብና ለመረዳት ያስችላል ምክንያቱም ሃይማኖት መሠረታዊ ጉዳይ ነውና !!! መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት ከ40 በላይ ቅዱሳን ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ አብዛኛዎቹ ዕብራውያን ናቸው፡፡ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስን አንብቦ ለመረዳት የዕብራውያንን ባሕል በከፊልም ቢሆን መረዳት ያስፈልጋል ፡፡ ስለዚህም

በዕብራውያን ባሕል ፡-

👉 1ኛ) አብሮ አደግና ዘመዶችን በሥጋ እንኳ ከአንድ እናትና አባት ባይወለዱም ‹‹ ወንድም ›› ይባላሉ ዘፍ 13፥11
👉2ኛ) በሃይማኖት የሚመሳሰሉም ‹‹ወንድሞች ›› ይባላሉ ገላ4፥1 ‹‹ ወንድሞቼ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ››
👉3ኛ) በሕብረት በአንድ (ማህበር) የሚቀመጡ ‹‹ ወንድሞች ›› ይባላሉ ‹‹ ወንድሞች በሕብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው እነሆም ያማረ ነው›› መዝ 133፥1፡፡
በተጨማሪም ሐዋርያት እርስ በርስ ‹‹ ወንድሞች ›› ይባባሉ ነበር ፡፡ ከዚህ በመነሳት ለጌታ ‹‹ ወንድሞቹ ›› ተደርገው የተጠቀሱት ሦስቱ ሐዋርያት በሥጋ የተወለዱ አይደሉም፡፡ ድንግል ማርያምም ከጌታ ውጭ ምንም ዓይነት
ልጅ የላትም !!! ልጅ ብቻም ሳይሆን ልጅ
የመውለድ ሃሳብም የላትም አልነበራትምም !!! በተጨማሪም ወንድሞቹ ተብለው የተጠቀሱት ‹‹ያዕቆብ ›› እና ‹‹ ይሁዳ ›› መልዕክቶቻቸውን ሲጽፉ ‹‹ የጌታ ባሪያ›› እያሉ ጻፉ እንጂ ‹‹ የጌታ ወንድሞች ›› ነን ብለው አልጻፉም
ማስረጃ ፡- የያዕቆብ መልእክት 1፥1 ‹‹የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ››
የይሁዳመልእክት 1፥1 ‹‹ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ የያዕቆብም ወንድም የሆነ ይሁዳ ›› ስለዚህ እነዚህ ሐዋርያት ዮሴፍ ከሟች ሚስቶቹ የወለዳቸውና አብረውት ያደጉ እንጂ ከድንግል ማርያም የተወለዱ አይደሉም ፡፡ ‹‹‹እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም የሚለው ትርጉም ›››
ይህን ቃል በመጥቀስ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከወለደች በኋላ ዮሴፍ በግብር አውቋታል የሚሉ መናፍቃን አሉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከወለደች በኋላ ልጅ ወልዳለች የሚል ቃል አልተጻፈም እንጂ !!! ይህን ቃል መነሻ አድርጎ ለመጀመርያ ጌዜ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን የጠየቀው በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ንጉሥ አርቃድዮስ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አምሥት ነገሮችን ግልጽ አድርጎለታል ፡፡ አርቃድዮስም መልሱን በሚገባ አምኗል ተረድቷል ፡፡ ዛሬም ጥያቄውን በድርቅና ሳይሆን ልክ እንደ አርቃድዮስ በየዋህነት ለጠየቀ ሁሉ መልስ የማያስፈልገው ጥያቄ ነው ፡፡ ሆኖም
ለዚህ ስህተታቸው መልስ መስጠቱ ተገቢ ነውና

አነሆ ፡- ‹‹ የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን አላወቃትም ›› ማለት ፡- ዮሴፍ ድንግል ማርያም ጌታን እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ማን እንደሆነች አላወቃትም(ማንነቷን) አልተረዳም ነበር ለማለት ነው ፡፡ ኋላ ግን ጌታን በወለደች ጊዜ በቤተልሔም እረኞች(ኖሎት) እና መላእክት በአንድነት ሲዘምሩ ፣ የሩቅ ምሥራቅ ነገሥታት(ሰብዓ ሰገል) እጅ መንሻ ይዘው መጥተው ሲሰግዱለት ፣ እንዲሁም ቤተልሔም ላይ የብርሃን ድንኳን ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ሲመለከት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት መሆኗን አወቀ (ተረዳ) እስከዚያች ቀን ድረስ ግን ማለትም ጌታን እስከምትወልድበት ቀን ድረስ ዮሴፍ ድንግል ማርያም የአምላክ
እናት መሆኗን አላወቀም ፣ አልተረዳም ነበር ለማለት ነው ፡፡

አወቀ ማለት በግብር ተገናኘ ማለት አይደለም !!! እንዲህ ከታሰበ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ የሚል ቃል አለ ፡-‹‹ ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጦ ሳለ እንጀራውን አንሥቶ ባረከው፥ ቈርሶም ሰጣቸው፤ ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም››ሉቃ 24፥30-31 ይህም ማለት ጌታችን መሆኑን አወቁ (ተረዱ) ከማለት ውጪ ሌላ ምን ዓይነት ትርጉም ሊኖረው ይችላል ??? (ማዕዱን ቆርሶ እስከሚሰጣቸው ድረስ ግን ጌታን አላወቁትም ነበር)ስለዚህ ማወቅ ማለት መረዳት እንጂ የግድ በግብር መገናኘት ዓይደለም !!
ይቆየን.....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር

፩ ሃይማኖት ተዋህዶ

✞_✞_✞
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?

የመጨረሻ ክፍል

#ማስረጃ
‹‹ ቃየል ሚስቱን አወቀ ጸነሰችም ›› ዘፍጥረት 4፥17 የሚለው ቃል በግብር
እንደቀረባት(እንደተገናኛት) የታወቀ ነው
ምክንያቱም አወቃት ብቻ ብሎ አላቆመም ‹‹ ጸነሰችም ›› ይላልና !!! ነገር ግን ዮሴፍ ድንግል ማርያምን እስክትወልድ ደረስ አላወቃትም ካለ
በኋላ ሌላ ምንም ዓይነት ተቀጽላ ቃል የለውም ፡፡ መናፍቃን በግድ እናጋባ እናዋልድ ካላሉ በቀር ጸነሰችም ወለደችም አላለም አዚያው ላያ ያበቃል አራት ነጥብ ፡፡ ‹‹‹ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ልጅ የላትም ! ›››

ተጨማሪ ማስረጃዎች እነሆ ፡- ሲጀመር መጽሐፍ ቅደስ በአንድም ቦታ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ልጅ አላት አይልም ብሎም አያውቅም !!! መጽሐፍ ቅዱስ እውነቱን እውነት ሐሰቱንም ሐሰት የሚል መጽሐፍ ስለሆነ ያልሆነውን ሆነ አይልም የሆነውንም አይደብቅም !!! ወንጌልን ለዓለም የሰበኩ ቅዱሳን ሐዋርያትም ድንግል ማርያምን ማዕከል አድርገው አስተምረዋልና ከክርስቶስ በኋላ ልጅ ወልዳ ቢሆን ኖሮ ለምን ደበቁን ? ለምሳሌ ጌታችን ሲሰቀል በመስቀል ሥር ሆና ስማልቀሷ ፣ለዮሐንስ ስለመሰጠቷና መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ እርሷ በመሃከላቸው እንደነበረች ሲጽፉ ለምን ከጌታ ሌላ ልጅ መውለዷን አልነገሩንም? ለምንስ ደበቁን? አሁንም በዚህ አቋም ለጸናችሁ መናፍቃን እውን መለኮት ባደረበት ማኅጸን ሰው ያድርበት ይሆን? አዎ ከሆነ ያንተ ኢየሱስ ፍጡር እና ተራ ሰው እንጂ አምላክ አይደለም !!!
የኛ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ባደረበት ማኅጸን ግን ማንም….. !!! ማንም…. !!! ማንም…. !!! አያድርበትም ፡፡ በድጋሚ ልምጣባችሁ እውን ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ውጪ ሌላ ልጅ ያስፈልጋት ይሆን ከዚያ በኋላ ብትወልድም ሰው አምላክ አይሆን? አበው እንኳ ‹‹ ሃምሳ ቢወለድ …… ከተባረከ ይበቃል አንዱ ›› ብለው የለ ታዲያ ድንግል ማርያም ከአንዱ ከብሩክ ልጇ ከክርስቶስ ሌላ ምን ሽታ ትወልድ ይሆን ?


መጽሐፍ ቅዱስ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋን እንዴት እንዳስቀመጠ ተመልከት ፡-
👉1) “እቴ ሙሽራዬ የተቆለፈች ገነት የተዘጋ ምንጭ የታተመች ፈሳሽ ናት”መኃ.ዘሰ 4÷12 (ዳዊት የመንፈስ አባቷ ነውና ልጄ ይላት ነበር ሰሎሞን ደግሞ የዳዊት ልጅ ነውና እህቴ ያላታል የመንፈስ ወንድሟ ነውና)
👉2) “የምስራቁም በር ለዘለዓለም ተዘግቶ ይኖራል ሰውም አይገባበትም እግዚአብሔር አንዴ ገብቶበታልና” ት.ሕዝ 44÷1-2 (ምሥራቅ የተሰኘች ድንግል ማርያም ናት በርሷ ሰማይነት ክርስቶስ ፀሐይ ሆኖ ወጥቷልና) ይህን ቃል ለቤተ መቅደስ ነው ብለህ የምትከራከር ካለህ ‹‹ ለዘለዓለም የተዘጋ ቤ/መ በዚህ ምድር ላይ የለምና እራስህን አታታል!!!
👉3) “ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል” ሉቃ 1÷34(ይህ የእመቤታችን አስደናቂ ንግግር ለወደፊትም እራሷን አቅባ እንደምትኖር የሚያረጋግጥ ቃል ነው ፡፡ አንድም ኃላፊ ግስ ነው የወደፊት ዓላማዋንም ያረጋግጣል) ‹‹‹ እርሱ ብቻ ልጇ እንደሆነ የክርስቶስ ምስክርነት›››
1ኛ) አይሁድ በምቀኝነት ክርስቶስን ሲሰቅሉት ከእግረ መስቀሉ ሥር የተገኘው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ድንግል ማርያም ብቻ ነበሩ ፡፡ እመቤታችን ሌሎች ልጆች ቢኖሯት ኖሮ ‹‹ እነሆ ልጅሽ ›› ብሎ ዮሐንስን ጠብቃት ባላለውም ነበር ፡፡ በዚህ ላይ ዮሐንስም እኮ እናት ነበረችው ፡፡ ነገር ግን ድንግል ማርያም አንድያ ልጇ በመሆኑ ጌታችን ለዮሐንስ አደራ ሰጥቶአታል ፡፡
2ኛ) የኢየሩሳሌም ሴቶች ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ሲያልፍ ተመልክተው አዝነው ሲያለቅሱ ‹‹ ለራሳችሁ እና ለልጆቻችሁ አልቅሱ ›› ተብለዋል እመቤታችንም መስቀል ሥር ሆና ታለቅስ ነበር ታዲያ ለምን ‹‹ ሄደሽ ለልጆችሽ አልቅሺ አላላትም ? ? ?
‹‹‹ ትልቅ እርምት የሚሻው የመናፍቃን ስህተት ›››‹‹ ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን? እኅቶቹስ ሁሉ በእኛ ዘንድ ያሉ አይደሉምን? እንኪያስ ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው? ተሰናከሉበትም›› ማቴ13÷56 የሚለውን ቃል ለማን እንደተነገረ እንኳ ሳያስተውሉ ጭራሽ ድንግል ማርያም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ እንዳላት አድርገው ይህን አሳፋሪ ቃል ሲጠቀሙበት አይቼ እኔም አፈርኩበት !!! የዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ዓላማ አይሁድ ክርስቶስን ወንድሞች አሉት ፤
ዮሴፍ ከሟች ሚስቱ የወለዳቸውን ሁሉ ከድንግል ማርያም ነው ብለው በማሰባቸው ወይም በመናገራቸው ተሰናከሉ(ተሳሳቱ) ማለት ነው ፡፡

👉ታዲያ እነርሱ ክርስቶስ የዮሴፍ ልጅ ነው ፤ ድንግል ማርያምም ሌሎች ልጆች አሏት ብለው በማሰባቸው ተሳሳቱ ከተባለ ለምን አንተ ደግመህ ትሰናከላለህ??? ይህን ስህተታቸውን ሲያስረግጥ ትንሽ ወረድ ብሎ ‹‹ በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም ›› ይላል ፡፡

‹‹‹ ስለ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ ማጠቃለያ ››› እመቤታችን እንደማንኛውም ሴት አይደለችም !!! ክርስቶስን የጸነሰችው ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ሲያበሥራት ነው ፡፡ ‹‹‹ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል ››› በማለት እንደተናገረችው እንደሌሎች ሴቶች በዘር በሩካቤ አይደለምና ነው፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም ‹‹ አንቺ ከሴቶች
ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ›› ሉቃ 13÷9 በማለት እንደተናገረችው፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ኦ ሀገረ እግዚአብሔር ›› (የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ ባንቺ የተደረገው ምንኛ ድንቅ ነው) አንዳለ በእመቤታችን የተደረገው ልዩ ነው ፡፡ ለዚህ ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ አንክሮ(ምሥጋና) ይገባል ፡፡

📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡

@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot

በሚቀጥለው ደግሞ ተአምረ ማርያም መቅድም ላይ ተአምሯን የሰማ ስጋወደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል የሚለውን እንመለከታለን::
"ተአምሯን የሰማ ስጋውን ደሙን እንደ ተቀበለ ይሆንለታል"።

@And_Haymanot
ለተሃድሶ መናፍቃን የተሠጠ መልሥ
(በድጋሚ የቀረበ)
ይህን ፅንሰ ሀሳብ ለመረዳት በመጀመሪያ በመቅደሙ የተፃፈውን
ቃል እንዳለ መመልከት ጠቀሜታ ይኖረዋል። አስቀድመን እንደተናገርን የታወቀ ምክንያት ኋጢአት ደዌ
ካልከለከለው በዚች ቀን ተአምሯን ሰምቶ ስጋውን ደሙን ይቀበል። ስጋውን ደሙን መቀበል ካልተቻለው ተአምሯን ሰምቶ ወደ ቤቱ ይሒድ ስጋውን ደሙን እንደተቀበለ ይሆንለታል ይደረግልኛል
በማለት ቢሰማ ይላል የዚህን አንቀጽ መልዕክት አንድ በአንድ በመተንተን ስንመለከት የሚከተሉትን ሶስት አበይት መልዕክቶች እናገኛለን።

👉ሀ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ፦

ይህ አንቀፅ በመጀመሪያ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በዋናነት የሚያስተላልፈው መልዕክት ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ የሚል ነው። ምክንያቱም በፍትሐ ነገስት ከቀዳም ሥዑር በቀር ቅዳሜ ቅዳሜ እና እሁድ እሁድ በቤተክርስቲያን ተሰብስባችሁ ስጋውን ደሙን ተቀብላችሁ ደስ ይበላችሁ ተብሎ ታዝዟል ይህም ብቻ ብቻ ሳይሆን በበረሃ ያሉ ባህታውያን ሳይቀሩ መልዐከ እግዚአብሔር ስጋወ ደሙን ሰንበት ነው። / በዓላት-ምን ?
ለምን ? እእንዴት ? ገፅ ፵፮ እና ፷፮ / ነገር ግን በስርዐተ ቤተክርስቲያን አንድ ሰው ስጋውን ደሙን እንዳይቀበል ሊያደርጉ የሚችሉ ምክንያቶች ይኖራሉ።
እነዚህም በዚህ አንቀፅ የተገለፁት አንደኛ የታወቀ ምክንያት / እንደ ወሊድ ፤ ሀዘን ፤ ለቅሶ ፤ ...የመሳሰሉት ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ኃጢዐት ነው።
ይከለክሉታል ተብለው ከተጠቁሱት በመጨረሻ የተገለፀው ደግሞ ደዌ ነው። አንድ ሰው በደዌ ምክንያት ነገር ከሰውነቱ እየወጣ፤ ደም እየፈሰሰው ይህን የመሰሉ ነገሮች እያሉበት ስጋወ ደሙን ላይቀበል ይችላል እነዚህ ሁሉ ግን ሰውየውን በቤተክርስቲያን
ቅፅር ተገኝቶ ከመፀለይ፤ ቅዱሳት መፀሀፍትን ምንባባት ከመስማት ግን ላይከለክሉት ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ሰው እነዚህ ምክንያቶች ካልከለከሉት በቀር ስጋወን ደሙን ይቀበል በማለት ወንጌልን ይሰብካል እንጅ ከወንጌል የወጣ ቃል የለውም።

👉 ለ ቤተክርስቲያን አትቅር ፦

ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ስጋውን ደሙን መቀበል ባይቻልህ ግን ስጋውን ደሙን መቀበል አይቻለኝም ብለህ ወደ
ቤተክርስቲያን ከመሄድ አትከልከል የሚለው። ተአምረ ማርያም ከቅዳሴ በፊት ያለው የቤተክርስቲያን የፀሎት
ክፍል አንድ አካል ነው።
መቅድሙም የሚለው ፦
።።።///።።።።///።።።
#ስጋወ_ደሙን_መቀበል_ካልተቻለው_ተአምሯን_ሰምቶ_ወደ_ቤቱ_ይሂድ_ነው
።።።///።።።።///።።።
ይህም ማለት ባትቆርብም ቤተክርስቲያን አትቅር ማለት ነው።በፀሎቱ ትምህርትና በመሳሰለው መርሀግብር ሁሉ ተሳተፍ።
ዕለቱ ሰንበትና በዓላት ከሆነ አንድ ክርስቲያን ቤተክርስቲያን ካልሄደ በዚያም ተገኝቶ ካልተማረ ካላመሰገነ ክርስትናውን በምን ይገልፀዋል ?
በዚህ አገላለፅ ተአምሯን ሰምቶ ወደ ቤቱ ይሂድ የሚለውን በአስተውሎትና በቅንነት ከተመለከትነው የሚናገረው ስለተአምሯ ብቻ አይደለም። ታአምሯን አታስታጉሉ ሲል ወደ ቤተክርስቲያን ሂዳችሁ በዚያ ካለው ባለው አገልግሎት ተሳተፉ ማለት ነው። ምክንያቱም ተአምረ ማርያምን እንዴትና መቸ እንደሚነበብ
እናውቃለን። ከተአምሩም በፊት፤ ከተአምሩም በኋላ ሌሎች ፀሎቶችና
ምንባባት አሉ። ይህን አጠቃላይ አገልግሎት ለምዕመኑ በታወቀ በተረዳ ነገር በዚህ ስያሜ ማስታወቅ ክፋትም ኋጢአትም አይደለም። ሌላው አገልግሎት በዚህ አገላለፅ ለምን ጠሩት ቢባል በትርጓሜ ውዳሴ ማርያም ላይ እንደተፃፈው ሌላውን አገልግሎት በመናቅ ማቅለል ሳይሆን ለእመቤታችን ባላቸው ፍቅር ነው።

👉 ሐ አትጠራጠር፦

ሶስተኛውና የየመጨረሻው የዚህ አንቀፅ መልዕክት በታወቀ ምክንያት
+++ በዚች ዕለት +++ ስጋውን ደሙን መቀበል ባይቻልክ ለሌሎች የተደረገው አይደረግልኝም የዕለቱ በረከት አይደርሰኝም ብለህ አትጠራጠር የሚል ነው። መፀሀፉ የተአምራት መፀሀፍ እንደመሆኑ መጠን ተአምራትም
የሚደረገውና ተአምራትም የሚያሰኛቸው ከዘወትራዊ የህይወት ተግባራትና ድርጊቶች የተለየ ለሰው የማይቻል በእግዚአብሔር ብቻ የሚቻል ነገር መደረጉ በመሆኑ አንተም ይደረግልኛል
በማለት በዕምነት ከፀሎቱ ተካፍለህ ከተአምሯም ሰምተህ ብትሄድ #በዕለቱ የቆረቡትን ሰወች በረከት ታገኛለክ ማለት
ነው። ይህ ደግሞ በቅዱሳት መፀሀፍ የተፃፈ ነው። ራሱ ጌታችን በወንጌሉ የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ዕምነት
ቢኖራችሁ ተራራ ማፍለስ፤ ባህር መክፈል..........
ሌላም ሌላም ትችላላችሁ ሲል አስተምሯል። ይህም በዕምነት ሀይል እግዚአብሔርን በረከተ እግዚአብሔርን
ታገኛላችሁ ከእግዚአብሔር ትገናኛላችሁ ማለት ነው። ስጋወ ደሙ በየሳምንቱ ወይም ከዚህ ባነሰም ይሁን በበዛም
የምንቀበለውም ለዚሁ ሀይለ እግዚአብሔርን ገንዘብ አድርገን ኋጢያታችን አስተስርየን በረከተ ስጋ በረከተ ነፍስ አግኝተን ለመኖር ነው። በዚያች ዕለት አልቻልክ ብሎ ባትቀበል በዕምነትም ይህን ታገኛለክና አትጠራጠር ይሉናል ሊቃውንቱ።
የየመቅደሙ መልዕክት ይኸ ሁኖ ሳለ
"አውቆ የተኛን " ቢቀሰቅሱት አይሰማም እንደሚባለው ሰወችን ሆን ብሎ ለማጠራጠር ከቅዱሳን በረከት ለመለየት አጋንንት በሰወች አድረው ሊቃውንቱ ያላሉትንና ሊሉም ያላሰቡትን
ያቀርባሉ። ቤተክርስትያኒቱ " ስጋውን ደሙን አትቀበሉ " ስጋወ ደሙን መቀበልና ስጋወደሙን ሳይቀበሉ ተአምረ ማርያምን መስማት እኩል ናቸው የሚል ትምህርት አስተምራ አታውቅም እእንዲህም አታምንም።
ተአምሯን የሚሰሙትና የሚያሰሙትም ስጋውን ደሙን የተቀበሉ ወደፊትም የሚቀበሉ ናቸው እንጅ አረማውያን ወይም በስጋወ ደሙ የሚጠራጠሩ አይደሉም።
/// ይደረግልኛል በማለት ቢሰማ /// የሚለው ጊዜ የተገደበ
ነው፡፡ ታዲያ ይህ በዕውኑ ለምዕመኑ መንፈሳዊ ህይወት መጨነቅ ወይስ ለኑፋቄ ሽፋን መፈለግ ???
ምንጭ ትምህርተ ተዋህዶ አፕሊኬሽን።
ልዑል እግዚአብሔር በተዋህዶ በረት እንድንፀና ያድርገን ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ ከሁላችንም ጋር
ይሁን አሜን::
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
Join @And_Haymanot
@And_Haymanot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጥንተ አብሶ እና ምልዓተ ኃጢአት ልዩነቱን ያውቁ ኖሯል?
@Konobyos
በዲ/ን ቴዎድሮስ
@And_Haymanot
@Konobyos
ድንግል ማርያምን እመቤት ማለት የይገባል?

@And_Haymanot

የተሃድሶ መናፍቃን በነገረ ድንግል ማርያም ላይ ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች መካከል ቅድስተ ቅዱሳን እናታችንን እመቤት ማለታችን ኢ-መፅሐፍ ቅዱሳዊ አድርገው ይቃወማሉ፡፡ እናት ቤተክርስቲያናችን መፅሐፍ ቅዱስን አብነት አድርጋ ታስተምራለች፡፡

ሲጀምር " እመቤት " ማለት በአንድ ቤተሰብ መካከል አስተዳዳሪና ኃላፊ የሆነች የታላቅ ሴት መጠሪያ መሆኑን
መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል እንጂ መናፍቃን እንደሚሉት ፍፁም ስህተት የሆነ ሴቶች የማይጠሩበት ስም አይደለም ፤እንኳን ጸጋን ሁሉ ለተመላች ፣ ከሴቶች ሁሉ ለተለየች ፣ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይቅርና ብዙ ሴቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው እመቤት ተብለው ተጠርተዋል ።

እስቲ ለአብነት ከመጽሐፉ እየጠቀስን እንይ ፦
፨ የአብርሃም ሚስት ሣራ እመቤት ተብላለች" እርሱም ወደ አጋር ገባ፥ አረገዘችም እንዳረገዘችም
ባየች ጊዜ እመቤትዋን በዓይንዋ አቃለለች።" እንዲል ዘፍ 16 : 4
አጋር ከሣራ ተለይታ በኮበለለች ጊዜ
" የእግዚአብሔር መልአክም ወደ እመቤትሽ ተመለሺ፥ ከእጅዋም በታች ሆነሽ ተገዥ አላት።"ይላል ዘፍ 16 : 9
ወዳጄ የእግዚአብሔር መልአክ የሰው
ልጅ እመቤት ተብሎ ባይጠራ ኖሮ ወደ እመቤትሽ ይል ነበር ?
፨ ወዳጄ የእግዚአብሔር ቃል አገልጋይ ቀጥራ የምታሰራዋን ሴት ምን ብሎ ነው የሚጠራት ?
° የንእማንን ሚስት ታገለግል የነበረችው ብላቴና " [ እመቤትዋንም ] ጌታዬ በሰማርያ ካለው ከነቢዩ ፊት ቢደርስ ኖሮ ከለምጹ በፈወሰው ነበር አለቻት። " 2ኛ. ነገ5 : 3
፨ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ያገልጋይቱ ዓይን ወደ እመቤቷ ነው ይለናል ።
° " እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ የባሪያይቱም ዓይን ወደ [ እመቤትዋ ] እጅ እንደ
ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው። " መዝ 124 :2
፨ ጠቢቡ ሰለሞንም እንዲህ ይላል ፦
° " በሦስት ነገር ምድር ትናወጣለች፥ አራተኛውንም
ትሸከም ዘንድ አይቻላትም።
፨ ባሪያ በነገሠ ጊዜ ፣
፨ ሰነፍም እንጀራ በጠገበ ጊዜ፥
፨ የተጠላች ሴት ባል ባገኘች ጊዜ፥
፨ ሴት ባሪያም [ እመቤቷን ] በወረሰች ጊዜ። "መ. ምሳ 30 : 21 - 23
ወዳጄ ይሄ ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ ተጽፎ ሳለ ፤ ወይ ሳያነቡ ወይ ሳይጠይቁ ገና ለገና እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመቃወም ሲባል ብቻ "ለወንድ ጌታ ለሴት እመቤት እንላለን ይሄ አባባል ፍጹም ስህተት ነው " የሚለውን የአጋንንት ስብከት ከየት
አመጣችሁት ? እውነት እናንተ እንደምትሉት ቢሆን ኖሮ እነሣራ ፣ የንእማን ሚስት እና ሌሎቹም ሴቶች ለምን እመቤት ተባሉ ? እመቤት ማለት የማይገባ ከሆነ የእግዚአብሔር መልአክ ፣ ቅዱስ ዳዊት ፣ ጠቢቡ ሰለሞን
ሴቶቹን ለምን እመቤት ብለው ጠሯቸው ? ነው መጽሐፉ ተሳስቶ ይሆን ?
መቼም ምክንያት እየፈጠሩ ለመካድ ለማስካድ እንጂ ለማመን አልተፈጠራችሁምና ይሄ በብሉይ ኪዳን እንጂ በአዲስ ኪዳን አይባልም ካላችሁ ማስረጃ ልስጥ ፤ ወዳጄ ፍቁረ እግዚ ቅዱስ ዮሐንስ 2ኛ የዮሐንስ መልእክቱን የጻፈው ለማነው ? አታቀውቁትም እንጂ ሲጀመር ብታውቁት ቃሉን እንደዚህ አንጋዳችሁ አወላግዳችሁ ባልጻፋችሁም
ነበር ፤ ታሪኩ ሰፊ ሲሆን ነገር ላለማርዘምና ቀጥታ ለጥያቄው
መልስ ለመስጠት ያህል ብቻ ቅዱስ ዮሐንስ ይቺን ሁለተኛ መልእክቱን የጻፈው ጣኦት ያመልኩ የነበሩ የነገሥታቱንና
የመኳንንቱን ልጆች ሞግዚት ሆና ታሳድግ ለነበረችው ሮምና ለምትባል ሴት ነው ።
ቅዱስ ዮሐንስና አብሮኮሮስ አስተምረው አሳምነው አጥምቀው ከአምልኮ ጣኦት ወደ ወገኛይቱ ወደ ክርስትና እምነት ከመለሷት በኃላ ለስብከት ወደ ሌላ አገር ይሄዳሉ፤ ከሄዱም በኃላ ግን በእምነቷ እንድትጸና እና እንድትበረታ ሲል ይቺን ሁለተኛይቱ የተባለችውን የዮሐንስ መልእክቱን የጻፈላት ። ወዳጄ ቅዱስ ዮሐንስ ለዚህች በነገሥታቱና በመኮንንቱ ቤት በሰራተኝነት ፣ በሞግዚትነት ለምታገለግለው ሮምና
ለተባለችው መልእክቱን ሲጽፍ ምን እንዳላት ታውቃለህ ? [ እመቤት ሆይ ] እያለ ነበር አክብሮ ይጠራት የነበረው ።
እስቲ የጻፈውን ቃል በቃል እንየው ፦
" በእኛ ስለሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ስለሚሆን እውነት፥ እኔ ሽማግሌው በእውነት ለምወዳቸውና እኔ ብቻ
ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ደግሞ ለሚወዱአቸው ለተመረጠች እመቤትና ለልጆችዋ "ይላል 2ኛ.ዮሐ 1 : 1 - 2
ወዳጄ እመቤት ብቻ አይደለም ያላት
" የተመረጠች እመቤት " ማለቱን አስተውል ። ሲቀጥል ቁ. 5 ላይ
" አሁንም፥ እመቤት ሆይ፥ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ እለምንሻለሁ፤ ይህች ከመጀመሪያ በእኛ ዘንድ የነበረች
ትእዛዝ ናት እንጂ አዲስ ትእዛዝን እንደምጽፍልሽ አይደለም። "ይላታል 2ኛ. ዮሐ 1 : 5 ወዳጄ የሕግ ፍጻሜና የምትበልጠው ጸጋ የተባለች ፍቅር
ይኖራቸው ዘንድ ሲጽፍላት
" እመቤት ሆይ ... እለምንሻለሁ " ብሎ ሲማጸናት ታያለህ ?
ታዲያ እንደ እናንተ አገላለጽ የሰው ልጅ ጌታና እመቤት ተብሎ የማይጠራ ፍጹም የሆነ ስህተት ከሆነ ቅዱስ ዮሐንስ ሮምናን ለምን እመቤት ሆይ እያለ ጠራት ? እናንተ ከዮሐንስ ትበልጣላችሁ?
አናንተ ናችሁ እኛ ነን በመጽሐፍ ቅዱስ የማናምነው? ከላይ ያየናቸው የብዙ ሴቶች እና የሮምና እመቤት መባል
ፍጹም ስህተት ያልሆነ ፤ የሰማይና የምድር ንጉሥ እናት የሆነች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እመቤት መባል እንዴት ሆኖ ነው ፍጹም ስህተት የሚሆነው ?

በአዳምና በሔዋን አማካኝነት ወደ ዓለም የገባውን መርገም የሻረ ጌታ እግዚአብሔር ከእርሷ በመወለዱ እመቤታችንን እግዝእተ በዙኃን [ የብዙኅን እመቤት ]
ትባላለች ። እንዲሁም ዓለም ሁሉ በዳነበት በክርስቶስ የማዳን ሥራ ያመንን ክርስቲያኖች ሁሉ በክርስቶስ አንድ
ቤተሰብ በመሆናችን ቅድስት እናቱ ድንግል ማርያምእመቤታችን ናት ።
ወዳጄ ፦ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ እመቤታችን እንደ ሌሎቹ ሴቶች እመቤት ብቻ አላላትም ንግስት
እንጂ !" በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ
ትቆማለች ......
የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ ( ይለምናሉ ይማጸናሉ )......
በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ፥ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ ...... ......
[ ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ ] " ይላታል መዝ 45 : 9 - 17
ወዳጄ የትንቢቱ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ ራሷ እመቤታችን ምን እንዳለች እንይ
" እነሆም ከዛሬ ጀምሮ [ ትውልድ ሁሉ ] ብፅዕት ይሉኛል " ሉቃ 1 : 48
ይቺ በንጉሡ ቀን የምትቆም ፣ የምድር አሕዛብ ሁሉ በፊቷ የሚማጸኗት ፣ በአባቶሽች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ
የተባለች ፣ ገዢ አርጋ የመሾም ስልጣን የተሰጣት ፣ ትውልድ ሁሉ ስሟን የሚጠሯት የሚያመሰግኗት ንግስት
ማነች ? ለስም አጠራሯ ክብር ምስጋና ይግባትና የንጉሡ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል አይደለችምን ?
ልበ አምላክ የተባለ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ ሰው ሁሉ እናታችን እንደሚላትም ተናግሯል
"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤
እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
ሲል መዝ 88 : 5 ጌታም በእለተ አርብ ተሰቅሎ ሳለ እመቤታችንን ለዮሐንስ
" እናትህ እነኋት " በማለት በሱ አንጻር ለዓለም ሁሉ እናትና እመቤት እርጎ ሰቶናል ዮሐ19 : 27
ፍቁረ እግዚ ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዮ ያያት ፦ " ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፣
ፀሐይን ተጐናጽፋ
1
፣ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት ፣ በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት
አንዲት ሴት ነበረች......
እርስዋም ፀንሳ ነበር፥ ምጥም ተይዛ ልትወልድ ተጭንቃ ጮኸች......
ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕፃንዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ። አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸው ዘንድ ያለውን
ልጅ ወንድ ልጅ ወለደች "ራዕ 12 : 1-5
ሲል የገለጻት የከበረች ሴት ማነች ?
ከንግስቲቱ ከእመቤታችን ውጭ ፀሐይን የተጎናጸፈች ፣ ጨረቃን ከእግሯ በታች ያደረገች ፣ በራሷ ላይ አሥራ
ሁለት አክሊል የደፋች ፣ አሕዛብን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛውን ጌታ የወለደች ማናት ? ወዳጄ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው ግሩምና ድንቅ አርጎ ፣ የዚህ ዓለም ገዢ ( ጌታ ) አርጎ እንደፈጠረው ሳታውቁ ነው ፤ ወንድ ጌታ ሴት እመቤት ልትባል አይገባም ፍጹም ስህተት ነው የምትሉት ? የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ
ተፈጠረ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ታውቃላችሁ? እግዚአብሔር የሰማይና የምድር ገዢ ( ጌታ ) እንደሆነ ሁሉ ሰውም የዚህ ዓለም ገዢ ( ጌታ ) ሆኖ ተፈጠረ ማለት ነው ።
" እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ
የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።"
እንዲል ዘፍ 1 : 26 በተለይ " ይግዙ " የምትለዋ ቃል የወንዱን ጌትነት የሴቷን እመቤትነት የሚያሳይ ቃል ነው ።
አንተ ሰነፍ እንኳን የከበረው የሰው ልጅ አይደለም ሰይጣን ዲያቢሎስ የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ እንደሚባል
እንኳን አታውቅም ? " አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም
ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል " እንዲል
ዮሐንስ 12 : 31 , 2ኛ. ቆሮ 4 : 4
መቼም ይሄንን የማታውቅ ደካማ ሰይጣን ዲያቢሎስ ለምን የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ ተባለ ? ተብለህ
ብትጠየቅ የባጥ የቋጡን እየቀባጠርክ ሰው ስታደክም ትውላለህ እንጂ መልስ የለህም ፤ የጸጋው ዙፋን የምስጢሩ ግምጃ ቤት ከሆነች ከተዋህዶ ተማር ፦
ሰይጣን ዲያቢሎስ የዚህ የጨለማው ዓለም ገዢ የተባለው ፤ የዚህች ዓለም ገዢ የሰው ልጅ የፈጣሪውን ትዕዛዝ አፍርሶና ኃጢአት ሰርቶ ስለበደለ ራሱን ለሰይጣን ከማስገዛቱም በላይ የሚገዛትን ዓለም ይዞ በሰይጣን
ቁጥጥር ሥር በመዋሉ ዓለማችን ከጌታዋ [ ከሰው ልጅ ] ጋር ለሰይጣን ተገዢ በመሆኗ ነው ሰይጣን ዲያቢሎስ
የዚህ ዓለም ገዢ ለመባል የበቃው ።
መቼም አናንተ አይታክቴ ሰው ናችሁና ሌላ ሰይጣናዊ ምክንያት እንደምትፈጥሩ አብሬ ስለኖርኩ ፀባያችሁን ልቅም አርጌ አቀዋለሁ ፣
የማታውቁትን ቢነግሯችሁ አትቀበሉም እሺ ተናገሩ ብትባሉ መልስ የላችሁም ፤ አሁንም እኔ ቤተ ክርስቲያን ያስተማረችኝን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያገኘሁትን እውነተኛውን ነገርኳችሁ ልክ አይደለም የምትሉ ከሆነ እሺ እስቲ
አስተምሩን ቅዱስ ዮሐንስ ሁለተኛ መልእክቱን ለማነው የጻፈው ?

ለምን እመቤት ሆይ አላት ? ንግሥት የተባለች ማናት ? ለምን ንግስት ተባለች ? የልጅ ልጅ ስሟን የሚጠራው
ትውልድ ሁሉ ብጽእት የሚሏት ? በንጉሱ ቀኝ ያለችው የምድር አህዛብ በፊቷ የሚማልሉላት ? ፀሐይን የተጎናጸፈች ፣ ጨረቃን የተጫማች ፣ አሥራ ሁለቱን
ከዋክብት እንደ አክሊል የደፋች ይቺ የከበረች ሴት ማናት ?
ይቆየን
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
ድንግል ማርያምን እመቤት ማለት ይገባል? 👆👆
💗 "ቅድስት ድንግል ማርያምን መውደድ ከሚገባኝ መጠን በላይ አልፌ ወድጄያት ይሆን? ብለህ ሥጋት አይግባህ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ከወደዳት በላይ ልትወዳት አትችልምና" 💗
ቅዱስ ማክሲሚሊያን ኮልብ
@And_Haymanot
🕯''የመላእክት እህት''

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለምን እህተ መላእክት ትባላለች?

እመቤታችን እህተ መላእክት ተብላ ትጠራለች፡፡ ሊቁ አባ ህርያቆስ ‹‹እህተ መላእክት፤ እመ ሰማዕታት፤ ወእግዝዕተ ፃድቃን እያለ ሲጠራት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ደግሞ ‹‹እህተ መላእክት ወእመ ኩሉ ሕዝብ … የመላእክት እህት የህዝቡ ሁሉ እናት›› ብለዋታል፡፡ አባ ህርያቆስም ሆነ አባ ጊዮርጊስ እመቤታችን የሰማዕታት፤ የፃድቃን የህዝቡ ሁሉ እናት ብለው ሲጠሯት እንዴው በራሳቸው ሳይሆን ‹‹እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ (ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላል) መዝ (፹፮÷፭) የሚለውን ፍፃሜው ለድንግል ማርያም የሆነውን ቃለ ትንቢት በማስታወስና ‹‹እነኋት እናትህ›› ዮሐ (፲፱÷፪፭) በማለት ጌታችን ድንግልን በዮሐንስ ወኪልነት ከዕፀ መስቀሉ ስር ለተገኙ ክርስትያኖች በእናትነት የሰጠበትን ቃል ኪዳን በማሰብ ነው፡፡ እህተ መላዕክት ሲሏትም በምክንያት ነው፡-

🕯,ከንጽህና_አንፃር

ቅዱሳን መላእክት በባህርያቸው ንፁሐን ንኡዳን ክቡራን ናቸው፡፡ የረከሱ ፍጥረታትን በምልጃቸው ያስምራሉ እንጂ እነሱ ራሳቸው አይረክሱም፡፡ ከሃጢአት ያልተመለሱ ልበ ደንዳኖችን ሊገስጹ አሊያም እንደሰዶምና ገሞራ ሊቀጡ ይላካሉ እንጂ እነሱ ሀጥያት አይሰሩም፡፡ በአምልኮ እግዚአብሔር ፀንተው በምስጋና ተግተው በተሰጣቸው ስፍራ (በኢዮር፤ በራማ፤በኤረር፤ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት፣በመንበረ መንግስት ) በንፅህና በቅድስና ዘለአለም እስከ ዘለአለም ይኖራሉ፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ መላዕክት በንፅህና በቅድስና ኖራለች፡፡ንፅሕናዋም በሁለት መንገድ ይገለፃል፡፡ አንደኛው ‹‹ ሞት በአንድ ሰው በአዳም ምክንያት ወደ ዓለም ገባ እንዳለ ቅ/ጳውሎስ ሁሉ በአዳምና በልጆቹ ላይ በወረደ መርገመ ሃጥያት(ጥንተ አብሶ) ሲረክስ እመቤታችን ግን ይህ የቀደመ መርገም ያልነካት ንፅህት መሆኗ ነው፡፡ ኢሳ ፩÷፲፱ (የዚህን ምሳሌ በዘመነ ጌዲዮን መ/መሳ ፮÷፴፮ -፵ ይመለከቱ፡፡) 2ተኛው ከሃልዮ ከነቢብ ከገቢር ሀጥያት የነፃች በስጋም በነፍስ ሀጥያት ያላወቃት (ማርያም ድንግል ንፅህተ ስጋ ወነፍስ እንዳለ ደራሲው በመልክአ ማርያም) መሆኗ ነው ፡፡ ይህንንም ቅ/ ገብርኤል (ቡርክት አንቲ እም አንስት… ከሴቶች ሁሉ ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ) በማለት መስክሮላታል፡፡ ይህ ፍፁም ንጽህናዋን አምላክ ተመለከተና በማህፀኗ አደረ በስጋም ወለደችው፡፡ እንግዲህ የድንግል ማርያም ንጽህና እንደ መላዕክቱ የባህርይና ለሁሉም ወገን በመሆኑ በንጽህና ለምትመስላቸው የመላዕክት እህት ተባለች፡፡

🕯,ከግብር_አንጻር

የእግዚአብሔርን የክብር ዙፋን የሚሸከሙ ኪሩብ (በብዙ ኪሩቤል) መላዕክት ናቸው፡፡ እነዚህ መላዕክት እግዚአብሔር ለቅዱሳን እንደታያቸው እሳታዊውን ዙፋን በደመና ይሸከማሉ፡፡ ፯ የእሳት መጋረጃዎች በዙፋኑ ዙሪያ ተከልለዋል፡፡ እመቤታችን በማኅጸኗ ዙፋንነት በሆዷ ያስቀመጠችው ያን ኪሩቤል የሚሸከሙትን እሳተ መለኮት ነው፡፡ በሰማያዊው ዙፋን ፯ የእሳት መጋረጃዎች ጌታን እንደከለሉት በድንግል ማህጸን ዙፋን በተቀመጠ ጊዜ በ፯ቱ ባህርያተ ሰብእ (፫ቱ ባህርያተ ነፍስና ፬ቱ ባህርያተ ሥጋ አምላክነቱን ሰወረ፡፡ በመሆኑም በሰማይ ዙፋኑን ለሚሸከሙ መላዕክት (ኪሩብ) አምላክን ፱ወር ከ፭ቀን በማህጸኗ ዙፋንነት ያስተናገደች እመቤታችን እህታቸው ተባለች፡፡ አንድም መላእክት ዘወትር በዙፋኑ ፊት ቆመው በፍርሐትና በመንቀጥቀጥ ቅዱስ፣ ቅዱስ ፣ቅዱስ እያሉ ያመሰግኑታል፡፡ ይማጸኑታል እመቤታችንም በአማላጅነት በንጉሱ ቀኝ ትቆማለችና እህታቸው ተባለች፡፡ ‹‹ወትቀውም ንግሥት በየማንከ… ንግስቲቱ በቀኝህ ትቆማለች እንዲል›› መዝ.፵፬፡፱

🕯,ከምልጃና_ከመዳን_ሰራ_አንፃር

መዳን በእግዚአብሔር በማመን እና ህጉን ትዛዛቱን በመፈፀም ነው ፡፡ እግዚአብሔርም እንዳንጠፋ ስለሚፈልግ በእርሱ ለምናምን ለእኛ ብዙ የድህነት መንገዶችን ሰጥቶናል ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ምልጃ በዋነኝነት ሚጠቀስ ነው፡፡ ድህነት እና ንስሐን በተመለከተ መላእክትንና ድንግልን የሚያመሳስላቸው ነገር አለ፡፡ ሁለቱም የሰው ልጅ በንስሐ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለስ አጥብቀው ይሻሉ፡፡ ተመልሶ ወደ ህፅነ እግዚአብሔር ሲገባም ደስ ይሰኛሉ፡፡ በአንዲት ነፍስ መዳን በሰማይ መላእክት ዘንድ ታለቅ ደስታ እንደሚሆን መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ድንግል ማርያምም የሰው ልጅ ብቻም ሳይሆን ፍጥረት ሁሉ ቢፅድቅላት ደስ የምትሰኝ ርህርህት እናት ናት፡፡ ስለዚህ ድንግል ማርያምም ሆኑ መላእክት ፍጡራን እንዲድኑ ካላቸው ጽኑዕ መሻት የተነሳ ዘወትር በጌታ ፊት ምልጃን ያቀርባሉ፡፡ ጸሎታቸውም መና የሚቀር ሳይሆን በቅድስናቸው ብዛት ካገኙት ሞገስ የተነሳ እግዚአብሔር የሚሹትን ስለሚፈፅምላቸው ሀይል ያለው ነው፡፡ ያዕ ፭፡፲፮ ስለሆነም ስለዚህ የምልጃና የድህነት ስራ ድንግል ማርያም የመላእክት እህት ተባለች ፡፡ በአጠቃላይ ድንግል ማርያም እህተ መላእክት ስትባል ከላይ ባነሳናቸው ምክንያቶች መሆኑን ልብ ልንል ይገባል፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
​​✞ መስቀሉ አበራ ✞

እዮሐ አበባዬ መስከረም ጠባዬ(፪)
መስከረም ሲጠባ ተተክሎ ደመራ
ህዝበ ኢትዮጵያን እዩት ችቦውን ሲያበራ
በታላቁ ብርሃን በመስቀል ደመራ(፪)

በኃጢአት ጨለማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተውጠን ሳለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የክርስቶስ መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ብርሃን ሆነልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ትምህርተ መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሆኖን ላመንነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በቃሉ ለምንድን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የእግዚአብሔር ኃይል ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

✞ መስቀል ባንዲራችን
የነጻነት አርማችን(፪)

በኢየሩሳሌም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አይሁድ አብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ያዳናቸውን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አናውቅም ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የድሉን መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ከመሬት ቀብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስሏቸው ነበር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ውጦ የሚያስቀረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በቀራንዮ ጎልጎታ
ጠላታችን ድል ተመታ(፪)

ንግሥቲቷ እሌኒ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በጣም የታደለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ደመራን አቁማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ፍለጋ ጀመረች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀለ ክርስቶስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ወዴት ነው እያለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በጣን ጢስ ተመርታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀሉን አገኘች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል መከታ
ቆስጠንጢኖስ ድል ተመታ(፪)

ነገር ግን መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተቀብሮ አልቀረም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተራራ አፍርሶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጠላት አሳፈረ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ሲወጣ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ታላቅ ሁካታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ድውይ ሲፈወስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አንካሳው ዳነ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሙታን ተነሱ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ይመስገን ጌታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ
ክርስቲያኖች እልል በሉ (፪)

መስቀል መከታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ይሁን ጋሻችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
እንዳይደፈር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ዳር ድንበራችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኢትዮጵያ ኑሪ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በእምነት ፀንተሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጌታ በመስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የባረከሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀሉ አበራ
እንደ ፀሀይ ጮራ (፪)

መስቀሉን አምነን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተሳልመነዋል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ከክብሩ ዙፋን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በእርሱ ባርኮናል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
እንሰግድለታለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የፀጋ ስግደት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በእርሱ ላይ ስላለ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኃይለ መለኮት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል የእኛ ጋሻ
የዲያብሎስ ድል መንሻ (፪)

የኢትዮጵያን መኩሪያ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኑ ተመልከቱልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የመስቀሉን ብርሃን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ነፀብራቁን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
እፀ መስቀሉ ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የእኛ መከታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የተሰጠን ለእኛ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ምልክታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል እንመካለን
እንድንበታለን(፪)

የዳዊት ልጅ ያዕቆብ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የሀገራችን ኩራት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የኢትዮጵያ ንጉሥ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጌታን የሚፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሀገሪቱን ሲዞር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ድካሙን ሳይፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ብርሐን እያበራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ፍቅር
በእኛ ላይ ይደር(፪)

መናገሻ እንጦጦ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የረር አምባ አመራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ሲፈለግ ሰንብቶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የመስቀል ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ጊሸን ላይ አገኘ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የአምባሰል ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ግማደ መስቀሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አርፏል ከዚያ ስፍራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል መስቀላችን
የክርስቲያን ኃይላችን(፪)

የመስቀል ለታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
የደመራው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ኢትዮጵያውያን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተደስተው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በሀገር ልብሳቸው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
አምረው ደምቀው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
በአደባባዩ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ተሰብስበው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
ይዘምራሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
መስቀል ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ደመራ
በኢትዮጵያ ሲያበራ(፪)

@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
"ሰይጣን የማይነካው ዕቃ "

በአንድ ሐገር ድንገት የአንድ" ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ ። ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም። አንበሳ ላለ አንበሳ፣ ነብር ላለ ነብር፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን፣ የጠፋብኝን ዕቃ
ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል። እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው። መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ። ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ፣ አንዴ ነብር፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ። የበዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሱ ደረሰ። ንጉሱ ደግሞ ክርስቲያን
ቢሆንም ከመጸሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየተት የሚሮጥ ሰው ነበር። ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሰራው ምትሐት
መታለሉ የማይቀር ነው። ስለዚህ ይህ ንጉስ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ።
ይህንን የሰሙ የንጉሱ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ። ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር
አልቆጠራቸውም። እሱ የጠንቋይ ትርዒት ማየት ቀጠለ። "እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ" ማለቱን ቀጠለ በነገሩ ያዘኑት "ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው " ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው። ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም። ጭራሽ
እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው። " የሰይጣን ስራ ነው አትበሉ፤ ቅናት ነው ይኼማ,,,, ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!"አላቸው። ጠንቋዩ «የፈለጉትን ላምጣልውት,,,,,ምን ይፈልጋሉ,,,, " የሞተ ዘመድ አለዎት,,,,, ወይስ ከቤትዎ,,,, » አላቸው በኩራት። ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ። « እንግዲያውስ የፈለኩትን ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና » አሉት።
ይህን ግዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት። በካህኑ ፊት ወደቀ። ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል። መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም።
አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም
አይወድም ይላሉ።
የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ «ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ»
@And_Haymanot
«በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን!»
በዲ/ን ሔኖክ ሙላት
"ከሞት ባሻገር" የተወሰደ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
"ልጇ ነው አምላኳ"
@በእንተ ዲያቆናት(ስለ ዲያቆናት)

የቅድስትና ሐዋርያዊት ኵላዊት ኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍት ምን ይላሉ?
፩. ዲያቆንም ኾነ ቄስ ሰሞነኛም ይኹን አይኹን፤ ለመቀደስም ኾነ ለጸሎት ቤተ መቅደስ ውስጥ መግባት ያለባቸው ሌሊት ነው። ሥርዐተ ቅዳሴ እንዲህ ይላላ፦
👌 "ሌሊት ለጸሎት ያልመጡ ቀሳውስትና ዲያቆናት ወደ ቤተ መቅደስ ይገቡ ዘንድ ያገለግሉም ዘንድ አይገባቸውም። ይኽን ትእዛዝ ቢደፋፈሩ ግን ከሕግ ትእዛዝ የወጡ ይኾናል።" [ሥርዐተ ቅዳሴ]
፪. ብዙዎቹ ዲያቆናት ልብሰ ተክህኖ ለብሶ መቀደስ፥ ሰዓታትና ማኅሌት መቆምና በንግሥ ሰዓት መስቀልና ቃጭል ይዘው ቅድመ ታቦት መኼድ እንጂ የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር መረዳት የስብከተ ወንጌል ግብር ብቻ ይመስላቸው። ፍጹም ስሕተት ነው። ከመቀደስ ባለፈ እውነተኛውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት
መማር፥ መረዳት፤ ከክህደት ትምህርት አንጥሮ መገንዘብም የመለየት ኃላፊነት አለባቸው።
➺ቅጥረኛ ስለኾንኩ እንጂ...በሚል ሳይፈልገው የሚቀድስ፦ ከታማኝ አገልጋይ ጋር ምን አንድነት አለው?
➾ቅባት ከተዋሕዶ ጋራ፥ ኑፋቄ ከአሚን(ከእምነት) ጋራ፥ ምርግትና ከጥንቆላ ጋራ፥ አውደ ነገሥት ከፍትሐ ነገሥት ጋር፥ ክህደት ከእውነተኛዋ ኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ትምህርት ጋር፤ ምንም ኅብረት እንደሌላቸው አንጥሮ፥ ኵልል አድርጎ የመረዳት የማስረዳትም ግዴታ አለባቸው። ለዚኽም ነው፦
👌"የቤተ ክርስቲያን መብራት አገልጋዮቹዋም የምትኾኑ ዲያቆናት ኾይ ተኵላ ከበግ ጋራ፤ ጭላት(ጭልፊ) ከርግብ ጋራ፤ ክርዳድ ከስንዴ ጋራ እንዳይኖር ከውስጥዋ ንቀሉ፤[ቅዳሴ አትናቴዎስ] እንዲል።
፫. ደጀ ሰላም፦ የሰላም ደጅ ናት። የዲያቆናት አብነት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ መጽሐፈ ገድሉ ላይ "የቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ አምላክ እግዚአብሔርም የዚኽን ሰው የንስሓ እንባ ተመልክቶ ይቅር አለው። ይኽ ሰውም በዚያች ቤተ ክርስቲያን ደጀ ሰላም ተቀምጦ የደረሰበትን ለሚገባውና ለሚወጣው ኹሉ መሰከረ።" [ገድለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ዘወርኃ መጋቢት]
✍️ አኹንማ የተጣሉ የሚታረቁባት፦ የሰላም ደጅ የተሰኘችው "ደጀ ሰላም" ድረስ ቢራና ዘር ማንዘሮቹ ገብተው "ምን ይኹንልህ?!" ብለን ግሮሰሪ አደረግነው። በርግጥ መጠጥ ፈጽሞ የተከለከለ ባይኾንም፤ አብዝቶ መጠጣት ግን የተገባ አለመኾኑ ለኹላችንም ግልጽ ነው። ደጀ ሰላም "የሰላም ደጅ" እንጂ 'የቢራዎች ደጅ' አይደለችምና ባይገባ ይመከራል።
✍️በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ተፈቅደው ነገር ግን ከማይበረታቱ ነገሮች አንዱ መጠጥ ነው። ፈጽሞ አይጠጣም፥ ርኵስ ነው ባንልም የማይጠጣ የተሻለ አደረገ።
➣"ከስካር ተጠበቁ ሙሴ በኦሪት ዘሌዋውያን እንዳይሰክሩ አዟቸዋል። እንዲሁ እናንተ ኤጲስቆጶሳት ቀሳውስትና ዲያቆናት መጠጥን ከማብዛትና ከስካር ተጠበቁ፤ መዳራት፣ ዝሙት፣ ስግብግብነት፣ ሰውን መስደብና ማስቀየም፣ መታበይ፣ በሐሰት መማል፣ ብዙ ቁም ነገሮችን መዘንጋትና ሌሎችም ከስካር የሚመነጩ ናቸው።"[መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፲፤ ቍጥር 56]
➛"ከስካርና ወይንን ከማብዛት ተጠበቁ፤ ቃለ እግዚአብሔር የሠፈረባቸውን መጻሕፍት መጠጣትን አዘውትሩ እንጂ።" [ዝኒ ከማሁ(Ibid) ቍጥር 57]
፬. የበቁ ዲያቆናት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በቅድስና ሥጋወደሙን ለመለወጥ ሲወርድ ማየት ይችላሉ።
➤"ካህን የመንፈስ ቅዱስን ፀጋ ላክ ባለጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለመስዋዕትነት በቀረቡ ፅዋዕና ሕብስት ላይ መንፈስ ቅዱስ ይወርዳል፤ ዲያቆናት በቅድስና ሥጋወደሙን ለመለወጥ ሲወርድ ማየት ይችላሉ። የዲያቆናት ክብር በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም። ቅዱስ እስጢፋኖስ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ የክብር ቦታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሊሠጠው እንደቻለ ለነሱም ይሠጣል።"
[መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፲፩፤ ቍጥር 33]
፭. ዛሬ ላይ ዲያቆናት የት ይገኛሉ? ምን ሲያደርጉ ይገኛሉ? ክቡር ዲያቆን ሆይ! "ዙረታም" ነኝ ካልክ የት መዞር እንዳለብህ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲህ ይመክሩናል።
➣"ዲያቆናት የክርስቲያኖችን የመኖሪያ ቤት ወዳለበት ኹሉ እየዞሩ የተቸገሩትን ኹሉ ይጎብኙ፤ ችግራቸውንም ይመልከቱ። ጥዋትም ኾነ ማታ ምእመናኑ በስንፍና እንዳይያዙ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲተጉ ያነቃቁዋቸዋል። በሠርክ በጧትና በማታም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሁል ጊዜ እየኼዱ ያመስግኑት፤ እግዚአብሔር የዕለት ብርሃን ነው፤ ኹሉንም ይረዳል።" [መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፱፤ ቍጥር 66]
፮. ዲያቆናት ምንም ዓይነት ጉቦ መቀበል፥ በደም ግባት ማዳላት፤ ድሀን አይቶ ባላየ ማለፍ፤ ዝም ብሎ ስለ ሴትና ወንድ በማውራት ዋዛ ፈዛዛ በመስማት- ነገረ ዘርቅ መስማት የለባቸውም።
➤ "እናንተም የመንጋዎች ጠባቆችና ዲያቆናት ሆይ መማለጃ በመቀበልና ፊት አይቶ በማድላት ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን ታወጡት ዘንድ በደል በሌለው በንጹህ ሰው ላይ ነገር ሥራንና የሐሰት ነገርን ትሰሙ ዘንድ አይገባም። እንደዚህ ያለ ሥራ የሚሠሩ ሰዎች የዲያብሎስ ወዳጆች ይኾናሉና።" [መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፲፥ ቍጥር 55]
➣ "ዲያቆናት ድኆች ሳይለምኗቸው ፈቃዳቸውን ሊያደርጉላቸው አገባብ ነው።"[መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፲፮፥ ቍጥር 55]
፯. ዲያቆን በድቁና የተካነ ካህን ነው። ቄስም በቅስና የተካነ ካህን ነውና በአጠቃላይ ማኅበረ ካህናት አይደለም በfb በሕዝባውያን መዋኛ ገንዳዎች እንዲዋኙና ለሕዝባውያን ገላቸውን እንዲያሳዩና ተገላልጠው እንዲታዩ፥ ቁንጣ፥ ጃፖኒ፣ ጥብቅብቅ የሚያደርጉ አልባሳት አድርጎ ውጭ መታየት ፈጽሞ አይፈቀድላቸውምና....
✍️ "አንተ ግን ትታጠብ ዘንድ በወደድህ ጊዜ የሕፃንነትህን ደም ግባትና የሰውነትህን ማማር እንዳያዩ በአንተም እንዳይሰናከሉ። አንተም እንዳትበድል፤ በእነርሱም እንዳትሰነካከል፤ ሴቶች ወደሚታጠቡበት መታጠቢያ ቤት አትግባ።"[መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፪]
👌ጸጉር አቆራረጥንም በተመለከተ ለምዕመናን ሲገልጽ የቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችን የሕግና የሥርዓት መጽሐፍ የሆነው ፍትሕ መንፈሳዊ ወሥጋዊ "በተፈጠርህ ጊዜ እግዚአብሔር በሰጠህ መልክ ላይ መልክ አትጨምር። ያድግ ዘንድ ፀጉርህን አትከባከበው ተላጨው እንጂ አታሳድገው። ወጥመዳቸው ቅርብ የሆነ ሴቶችን ወደ አንተ ያመጣብህ ዘንድ አታሳምረው። ረቂቅ ልብስ አትልበስ፤ ይህች ስሕተትን ታመጣለችና፤ ቀለም የተቀባ ጫማ አትጫማ፤ በጣቶችህ የወርቅ ቀለበትን አታድርግ፤ ይህ ሁሉ የዝሙት ምልክት ነውና። ጠጉርህን ግልስልስ ብጥር አታድርገው፤ አትሠራው፤ " [ፍትሕ መንፈሳዊ፤ አንቀጽ ፲፩፤ ገጽ. 123] ካለ ለካህናቱ እንዴት ጥብቅ ይሆን???
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@And_Haymanot
👍1
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
አስታርቂኝ


አስታርቂኝ ድንግል ማርያም /2/ 
ከልጅሽ /3/ ከመድኃኔዓለም 

አስታርቂኝ ኃጢአትን ሰርቼ 
አስታርቂኝ ጫካ ውስጥ ቆሜአለው 
አስታርቂኝ ሥራዬ አሳፍሮኝ 
አስታርቂኝ ዘወትር አነባለው 
አስታርቂኝ ልጄ አዳም ብሎ 
አስታርቂኝ አምላኬ ሲጠራ 
አስታርቂኝ እነሆኝ ለማለት 
አስታርቂኝ አንደበቴ ፈራ 
አዝ ------------ 
አስታርቂኝ ሀብትን ተካፍዬ 
አስታርቂኝ ከገዛ አባቴ 
አስታርቂኝ ከቤቴ ኮበለልኩ 
አስታርቂኝ ይሻለኛል ብዬ 
አስታርቂኝ ገፍቼ ወጥቼ 
አስታርቂኝ የቤቴን ገበታ 
አስታርቂኝ ልበላ ተመኘሁ 
አስታርቂኝ የእንስሳት ገፈራ 
አዝ--------- 
አስታርቂኝ ወደ አባቴ ልሂድ 
አስታርቂኝ አሁን ተነሥቼ 
አስታርቂኝ ይቅርታ ልጠይቅ 
አስታርቂኝ እግሩ ስር ወድቄ 
አስታርቂኝ ልጅነቴ ቀርቶ 
አስታርቂኝ አድርገኝ ባርያህ 
አስታርቂኝ ከሞያተኞችህ 
አስታርቂኝ እንደ አንዱ ቆጥረህ 
አዝ ------ 
አስታርቂኝ ገና ሩቅ ሳለው 
አስታርቂኝ አባቴ አይቶኝ 
አስታርቂኝ ወደእኔ ሮጦ 
አስታርቂኝ አቅፎ ነው የሳመኝ 
አስታርቂኝ ጠፍቶ የነበረው 
አስታርቂኝ ተገኘልኝ አለ 
አስታርቂኝ ሞቶ የነበረው 
አስታርቂኝ ደግሞ ሕያው ሆነ 
@And_Haymanot
@And_Haymanot
                    
ቅዱስ ትውፊት

#ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ሐዋርያት

✞ ቅዱስ ትውፊትን በዘመነ ሐዲስ ስንመለከትም፥ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሦስት ዓመት በላይ ሕዝቡን ደቀ መዛሙርቱን የነበረው በጹሑፍ አልነበረም ቅዱሳን ሐዋርያትም ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበሉት በወረቀት የተጻፈ ነገር አልነበረም ወንጌላውያን ከጌታ በቃል ተምረው በተግባር አይተው ኃላ የሚጽፉትን እየዞሩ አስተማሩ እንጂ አስቀድመው ጽፈው ጠቅሰው አላስተማሩም መጻሕፍት መጻፍ የጀመሩት፥ ቤተ ክርስቲያን በይፋ ከተመሰረተች ከ8 ዓመታት በኃላ ነው (ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት መጀመሪያ የተጻፈው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ሲሆን ይኸውም በ41 ዓ/ም ላይ ነው) እስከዚህ ጊዜ ድረስ ቤተ ክርስቲያን ስትመራ የነበረው በቃልና በተግባራዊ ምልልስ ሲተላለፍ በነበረው ቅዱስ ትውፊት ነው በሌላ አገላለጽ ወንጌል ከመጻፉ በፊት፥ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን በቅዱስ ትውፊት ታውቃለች ወንጌልን ስትኖረው ነበረች

✞ ከጌታችን ጋር ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከዋለበት እየዋሉ፣ ካደረበት እያደሩ ሲየያስተምር፣ ሲጸልይ፣ ሰዎችን ሲያጽናና፣ ድውያነ ስጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስንም በትምህርት ሲፈውስ፣ ሙታነ ሥጋንና ሙታነ ነፍስን ሕይወት ሲሰጣቸው ዐይተዋል፤ ሰምተዋል ሥርዓተ ብሉይን አሳልፎ ሥርዓተ ሐዲስን ሲሠራ ተመልክተዋል ነገር ግን ይህን ሁሉ በትውፊት ለተላውያነ ሐዋርያት (Apostolik Fathers- ተላውያነ ሐዋርያት የሚባሉት ከሐዋርያት በቀጥታ የተማሩ ክርስቲያኖች ናቸው) አስረከቡት እንጂ፥ እነርሱ ራሳቸው እንደነገሩን ሁሉንም አልጻፉልንም የጻፉልን እጅግ ጥቂቱን ብቻ ነው /ዮሐ 21፥25/ ስለዚህ ቅዱስ ትውፊት እያልነን ያለነው፥ እንዲህ አይነቱን በገቢርና በቃል ዕለት ዕለት በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ሕይወት የሚገለጠውና አንድ ጊዜ ለቅዱሳን የተሰጠውን ሃይማኖት ነው /ይሁዳ 3/

✞ ቅዱስ ትውፊት ዋና ማዕከሉ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በሌላ አገላለጽ ቅዱስ ትውፊት ወንጌል ነው በዘመነ ብሉይ ቢነገር ይወርዳል ይወለዳል ብሎ ነው፤ በዘመነ ሐዲስ ቢነገር ደግሞ ወረደ ተወለደ ብሎ የምስራችን ለትውልድ ሁሉ በቃልም፣ በገቢርም፣ በጹሑፍም የሚያውጅ ነው፤ ቅዱስ ትውፊት "ወንድሞች ሆይ! የሰበክኁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባቹሀለው በከንቱ ካላመናችው በቀር ብታምኑስ በምን ቃል እንደ ሰበክኁላችው አሳስባችኃለው እኔ ደግሞ የተቀበልኩትን ከሁሉ በፊት ሰጠኃችው" እንዲል /1ኛ ቆሮ 15፥1/

# ትውፊትና እድገት

☞ ብዙ ሰዎች ሁልጊዜ የቀደሙትን ከተመለከትን እድገታችንና የትውልዱ የፈጠራ ችሎታ ይቋረጣል ብለው ይሰጋሉ ነገር ግን ትውፊት እድገትን አይገድብም፤ እንዲያውም እድገቱ የተስተካከለ እንዲሆን ያደርጋል

✞ ማደግ ማለት የራስን ትቶ የሌላውን ብቻ መቀበል አይደለም የራስ የሆነውን በአግባቡ መጠቀም ማለት ነው እንጂ እድገታችን እንጀራን አጥፍቶ ፓስታ ብቻ ለምን አንበላም?፣ የሐበሻ ቀሚስን አሣድደን ለምን እርቃንን የሚያጋልጠውን አንለብስም?፣ የዘመን አቆጣጠራችን ይቅርና በአውሮፓ ቀመር ይተካ፣ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ተጥሎ የነሞዛርት ቅኝት ይምጣልን አይነት ከሆነ ጉዟችን ወደ እድገት ሳይሆን አንገትን ቆርጦ ለፀጉር አበጣጠር የመጨነቅ ያህል ነው የራሳችን የሆነውን ወደን አክብረን የበለጠ የሚያድግበትን መንገድ ከሆነ ያ እድገት ተብሎ ሊጠራ ይችላል የሰጎን እንቁላል ስለጠፋ ጉልላት ይቅር አይባልም ሰጎን እናርባ ይባላል እንጂ፤ ካህን ስላጠረን ምእመኑ ይቀድስ አይባልም ልጆቻችንን እናስተምራቸውና ካህን እናድርጋቸው፣ ሹመት እናሰጣቸው ይባላል እንጂ አለም እኮ የሚጓዘው በአንድ አቅጣጫ ብቻ አይደለም በተቃራኒውም ሊያመራ ይችላል የወንጀል አሰራር፣ የውንብድና ኑሮ እየረቀቀና በቴክኖሎጂ እየተደገፈ በመጣ ቁጥር እድገት ብለን ከቆጠርን ተሳስተናል

✞ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ አበው የቀደምት አበው የቤተ ክርስቲያን አሠራር፣ የአምልኮ ስርአቱ፣ ልብሰ ተክህኖውን፣ ጽንአውን፣ ዕጣኑን፣ መንበሩን ወዘተ ከጥንቷ ቤተ መቅደስ ለቤተ ክርስቲያን እንደሚገባ አድርገው ተረከቡት እንጂ በዘመኑ ሰልጥኖ የነበረውን የግሪካዊ- ሮማ ፍልስፍና አልጨመሩበትም ይህም የሆነው ስልጣኔው፣ ፍልስፍናው፣ እውቀቱ ሳይገባቸው ቀርቶ ሳይሆን የዚህ ስጋዊ ፍልስፍና ውጤቱ እግዚአብሔርን መካድ፣ ስጋዊ ፍላጎትን ማርካት፣ ምድራዊ ድሎትን ማደላደል መሆኑን ስለተገነዘቡ ነው ለምሳሌ፦
☞ ሰዓሊያን ስዕለ ቅዱሳንን ሲስሉ ቤተ ክርስቲያን በቃልና በጹሑፍ ያቆየችውን መሠረት አድርገው ገለጡት እንጂ የራሳቸውን አመለካከትና ፍላጎት ተጠቅመው ትውፊትን በመሻር ልቦለድ ስዕል አላቀረቡም

# ቅዱስ_ትውፊት_ቅዱስ_ካልሆነው_ትውፊት_እንዴት_ይታወቃል?

✞ በቤተ ክርስቲያን ያለው ሁሉም በትውፊት የተገኘ ላይሆን ይችላል እያንዳንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው ነገርም የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪ መንፈስ ቅዱስ የሰጣት ነው ማለት አይደለም አንዳንድ ሰዋዊ ነገሮችን ልናገኝ እንችላለን ነገር ግን እነዚህ የሰው የሆኑ ነገሮች በራሳቸው ኃጢአት ወይም ስህተት ላይሆኑ ይችላሉ ይሉቁንም ለዋናው የቤተ ክርሱቲያኒቱ ቅዱስ ትውፊት ማቀላጠፊያ ወይም ማስተላለፊያ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ ለምሳሌ፦ ድምጽ ማጉያ፣ መቅረጸ ድምጽ፣ ሲዲ፣ ዲቪዲ፣ እና የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል ስለዚህ ዋናውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ትውፊትና ጊዜአዊው ማቀላጠፊያን ለይተን ልናውቅ ይገባናል

✞ ቤተ ክርስቲያን ማለት የክርስቲያኖች ጉባኤ እንደመሆኗ መጠን፥ እነዚህ ክርስቲያኖችም በተለያየ ግብረ ዓለም ሊያዙ ስለሚችሉ ይህን የዓለም ስራ ይዘው ቢመጡና ግብራቸውን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢያሰርፁ፥ ይህ ክፉ ግብር እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ሊቆጠር አይገባውም በመሆኑም ለቅዱስ ትውፊት ቀኖናዊ መመዘኛ እንዳለው ተረድተን ቅዱሱን ትውፊትና ቅዱስ ያልሆነውን ትውፊት ለይተን ልናውቅ ይገባናል /2ኛ ተሰ 2፥15/ ትውፊት ሁሉ ከሐዋርያት ተያይዞ የመጣና ሐዋርያዊ ቤተ ክርስቲያናዊ ይዘት ያለው መሆን አለበት፤ ከጥንት ጀምሮ በየትም ቦታ፥ ሁል ጊዜ በዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን የታመነ የተጠበቀና በተግባር ላይ የዋለ መሆን አለበት፤ በዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ መለወጥና መቋረጥ ያልተገባው መሆን አለበት

✞ እንደ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምሮ ሃይማኖት የሚቀበሉት ተቀብለውም የሚኖሩት ለቀጣዩ ትውልድም ሳያፋልሱ የሚያስተላልፉት እንጂ በየጊዜው የሚጨመርበት ወይም የሚቀነስበት አይደለም በፕሮቴስታንቱ አለም ደግሞ ከካቶሊካውያኑ ፍጹም ተቃራኒ በመሆን ቅዱስ ትውፊትን አንቀበልም ይላሉ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻውን በቂ እንደሆነ ያስተምራሉ ነገር ግን ይህም ቢሆን ፍፁም የተሳሳተ ትምህርት ነው አንድ ቀላል ምሳሌ እናንሳና ትምህርታቸው ምን ያህል ስህተት እንደሆነ እናሳይ
☞ እሑድን እንደ ጌታ ቀን አድርገው ያከብራሉ በብሉይ ኪዳን እንዲከበር የታዘዘው ግን ቅዳሜ ነው /ዘፀ 20፥8/ ቅዳሜን ትተው እሑድን ማክበር ከየት አገኙት? ዳግመኛም የጌታችንን ልደት፣ ጥምቀት፣ ትንሳኤ እንዲሁም በዓለ ኃምሳ አብረውን ያከብራሉ ነገር ግን ይህን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምንም አይገኝም ሌላ ጥያቄም እንጨምር ወደ ዓለም ሁሉ የተሰማሩት ሐዋርያት 12 መሆናቸውን ወንጌል ይነግረናል ነገር ግን ሁሉም ጹሑፍ አልጻፉም አላስተማሩም ማለት ግን አይደለም ታዲያ ትምህርታቸው የት አለ? ትምህርታቸውን የምናገኘው