5. "አስ-ሰላም"
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ምስጋና የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ውዳሴና ሰላም፡ የሰላም አለቃና መምህር ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ ይሁን፡፡ ድልና የበላይነት ሐቅን ለማንገስና ሀሰትን ለማርከስ፡ በደልን አጥፎቶ ፍትህን ለማስፈን ዕውቀታቸውን፣ ንብረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ህይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ለሚታገሉት ይሁን፡፡
ሀ. ትርጉሙ፡-
"አስ-ሰላም" የሚለው መለኮታዊ ስም ትርጉሙ፡- የሰላም ባለቤት፤ ነውር አልባ የሚል ነው፡፡
ለ. አመጣጡ፡-
"አስ-ሰላም" የሚለው ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ አንድ ጊዜ ብቻ ተጠቅሷል፡-
" هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ الْمَلِكُ الْقُدُّوسُ السَّلَامُ الْمُؤْمِنُ الْمُهَيْمِنُ الْعَزِيزُ الْجَبَّارُ الْمُتَكَبِّرُ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ " سورة الحشر 23
"እርሱ አላህ ነው፤ ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሡ፤ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ #የሰላም ባለቤቱ ጸጥታን ሰጪው ባሮቹን ጠባቂው አሸናፊው፣ ኀያሉ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።" (ሱረቱል ሐሽር 23)፡፡
ሐ. የምንወስደው ትምሕርት
1. እርሱ አላህ የሰላም ባለቤት መሆኑን፡- ጌታችን "አስ-ሰላም" በመሆኑ ሰላም የሚገኘው ከሱ ዘንድ ብቻ ነው፡፡
" تَحِيَّتُهُمْ يَوْمَ يَلْقَوْنَهُ سَلَامٌ وَأَعَدَّ لَهُمْ أَجْرًا كَرِيمًا " سورة الأحزاب 44
"በሚገናኙት ቀን መከባበሪያቸው ሰላም በመባባል ነው፤ ለነርሱም የከበረን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል።" (ሱረቱል አሕዛብ 44)፡፡
" سَلَامٌ قَوْلًا مِنْ رَبٍّ رَحِيمٍ " سورة يس 58
"(ለነሱም) አዛኝ ከሆነው ጌታ ቃል በቃል ሰላምታ አላቸው።" (ሱረቱ ያሲን 58)፡፡ ሶላታችንን ሰግደን ስናጠናቅቅ ከሶስት ጊዜ "አስተግፊሩላህ" በኋላ የምንለው ዚክርም ይህን ያመላክታል፡-
عَنْ ثَوْبَانَ، قَالَ: كَانَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، إِذَا انْصَرَفَ مِنْ صَلَاتِهِ اسْتَغْفَرَ ثَلَاثًا وَقَالَ: «اللهُمَّ أَنْتَ السَّلَامُ وَمِنْكَ السَّلَامُ، تَبَارَكْتَ ذَا الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ» مسلم.
ከሠውባን (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው፡- የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሶላታቸውን እንዳጠናቀቁ ፡- "አስተግፊሩላህ (አላህ ሆይ ይቅርታህን እጠይቃለሁ) ሶስት ጊዜ፡ ከዛም፡- አላሁምመ አንተ-ሰላም (አላህ ሆይ! አንተ ሰላም ነህ!) ወሚንከ-ሰላም (ሰላምም የሚገኘው ካንተው ነው)… ይሉ ነበር" (ሙስሊም)፡፡
2. አማኞች ሰላምን እንደሚያገኙ፡- ጌታችን አላህ "አስ-ሰላም" በመሆኑ በሱ ላመኑ ባሪያዎቹ ውስታዊና ውጫዊ ሰላም ያጎናጽፋቸዋል፡፡
" فَأْتِيَاهُ فَقُولَا إِنَّا رَسُولَا رَبِّكَ فَأَرْسِلْ مَعَنَا بَنِي إِسْرَائِيلَ وَلَا تُعَذِّبْهُمْ قَدْ جِئْنَاكَ بِآيَةٍ مِنْ رَبِّكَ وَالسَّلَامُ عَلَى مَنِ اتَّبَعَ الْهُدَى " طه 47
"ወደርሱም ኺዱ፤ በሉትም፦ እኛ የጌታህ መልክተኞች ነን፤ የእስራኤልንም ልጆች፣ ከኛ ጋር ልቀቅ፤ አታሰቃያቸውም፤ ከጌታህ በሆነው ታምር በእርግጥ መጥተንሃልና፤ #ሰላምም ቀጥታን በተከተለ ሰው ላይ ይሁን።" (ሱረቱ ጣሀ 47)፡፡
" قُلِ الْحَمْدُ لِلَّهِ وَسَلَامٌ عَلَى عِبَادِهِ الَّذِينَ اصْطَفَى آللَّهُ خَيْرٌ أَمَّا يُشْرِكُونَ " سورة النمل 59
"(ሙሐመድ ሆይ) በል «ምስጋና ለአላህ ይግባው፡፡ በእነዚያም በመረጣቸው ባሮቹ ላይ #ሰላም ይውረድ፡፡ አላህ በላጭ ነውን ወይስ ያ የሚያጋሩት (ጣዖት)፡፡" (ሱረቱ-ነምል 59)፡፡
" وَسَلَامٌ عَلَى الْمُرْسَلِينَ * وَالْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ " سورة الصافات 182-181
"በመልክተኞቹም ላይ #ሰላም ይኹን፤ ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን" (ሱረቱ-ሷፍፋት 181-182)፡፡
3. ጀነት ለመግባት ሰበብ መሆኑን፡- ጌታችን አላህ "አስ-ሰላም" በመሆኑ በዚህ ምድር ላይ እኛ አማኝ ባሪያዎቹ ሰላምታን ማብዛት እንዳለብን ተነግሮናል፡፡ ይህንን የሚያደርግም ጀነት እንደሚገባ ተገልጾአል፡፡ ቀጣዩ ሐዲስም ይሐን ይጠቁማል፡-
عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «لَا تَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ حَتَّى تُؤْمِنُوا، وَلَا تُؤْمِنُوا حَتَّى تَحَابُّوا، أَوَلَا أَدُلُّكُمْ عَلَى شَيْءٍ إِذَا فَعَلْتُمُوهُ تَحَابَبْتُمْ؟ أَفْشُوا السَّلَامَ بَيْنَكُمْ» مسلم.
ከአቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) በተላለፈው ሐዲሥ የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "እስካላመናችሁ ድረስ ጀነትን አትገቡም፣ እስካልተዋደዳችሁ ድረስ አታምኑም፣ ከሰራችሁት ሊያዋድዳችሁ የሚችልን ነገር ላመላክታችሁን? #ሰላምታን በመሐከላችሁ አብዙ" (ሙስሊም)፡፡
በዚህም ምክንያት አንድ ሙስሊም ሌላኛውን ሙስሊም ባገኘው ጊዜ ‹ኢስላማዊ ሰላምታ› እንዲሰጠው ታዝዞአል፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገሩን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ሙስሊም በሙስሊሙ ላይ ስድስት መብቶች አሉት፡፡ ሶሐቦችም (ረዲየላሁ ዐንሁም) ፡- ‹‹የአላህ መልክተኛ ሆይ! ምንድናቸው እነሱ?›› ብለው ሲጠይቁ፡ እሳቸውም፡- ሲያገኘው (አሰላሙ ዐለይኩም..) በማለት ሰላምታ ሊሰጠው…››በማለት መለሱ" (ሙስሊም 2162)፡፡
"እነዚያም በተአምራታችን የሚያምኑት (ወደ አንተ) በመጡ ጊዜ «ሰላም በእናንተ ላይ ይኹን፡፡ ጌታችሁ በነፍሱ ላይ እዝነትን ጻፈ፡፡ እነሆ ከእናንተ ውስጥ በስሕተት ክፉን ሥራ የሠራ ሰው ከዚያም ከእርሱ በኋላ የተጸጸተና ሥራውን ያሳመረ እርሱ (አላህ) መሓሪ አዛኝ ነው» በላቸው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 54)፡፡
4. ወደ ሰላም የሚመራ ጌታ መሆኑን፡- ጌታችን አላህ "አስ-ሰላም" በመሆኑ አማኝ ባሪያዎቹን በዚህ ዱንያ የሰላም መንገድ የሚመራ፡ በአኼራ ደግሞ የሰላም ሀገር ወደሆነችው ጀነት የሚጣራ አምላክ መሆኑን እንረዳለን፡-
"አላህ ውዴታውን የተከተሉትን ሰዎች #የሰላምን መንገዶች በርሱ ይመራቸዋል። በፈቃዱም ከጨለማዎች ወደ ብርሃን ያወጣቸዋል። ወደ ቀጥተኛም መንገድ ይመራቸዋል።" (ሱረቱል ማኢዳህ 16)፡፡
"አላህም ወደ #ሰላም አገር ይጠራል፡፡ የሚሻውንም ሰው ወደ ቀጥተኛው መንገድ ይመራል፡፡" (ሱረቱ ዩኑስ 25)፡፡
"ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ #የሰላም አገር አላቸው፡፡ እርሱም (ጌታህ) ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ረዳታቸው ነው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 127)፡፡
5. የመላእክት አቀባበል መሆኑ፡- አምላካችን አላህ "አስ-ሰላም" የሆነ አምላክ በመሆኑ፡ ነጌ በቂያም ዕለት አማኝ ባሪያዎቹን ወደ ጀነት ሲያስገባቸው መላእክት በየደጃፉ ሆነው የእንኳን ደህና መጣችሁ! ብ
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ምስጋና የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ውዳሴና ሰላም፡ የሰላም አለቃና መምህር ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ ይሁን፡፡ ድልና የበላይነት ሐቅን ለማንገስና ሀሰትን ለማርከስ፡ በደልን አጥፎቶ ፍትህን ለማስፈን ዕውቀታቸውን፣ ንብረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ህይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ለሚታገሉት ይሁን፡፡
ሀ. ትርጉሙ፡-
"አስ-ሰላም" የሚለው መለኮታዊ ስም ትርጉሙ፡- የሰላም ባለቤት፤ ነውር አልባ የሚል ነው፡፡
ለ. አመጣጡ፡-
"አስ-ሰላም" የሚለው ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ አንድ ጊዜ ብቻ ተጠቅሷል፡-
" هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ الْمَلِكُ الْقُدُّوسُ السَّلَامُ الْمُؤْمِنُ الْمُهَيْمِنُ الْعَزِيزُ الْجَبَّارُ الْمُتَكَبِّرُ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ " سورة الحشر 23
"እርሱ አላህ ነው፤ ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሡ፤ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ #የሰላም ባለቤቱ ጸጥታን ሰጪው ባሮቹን ጠባቂው አሸናፊው፣ ኀያሉ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።" (ሱረቱል ሐሽር 23)፡፡
ሐ. የምንወስደው ትምሕርት
1. እርሱ አላህ የሰላም ባለቤት መሆኑን፡- ጌታችን "አስ-ሰላም" በመሆኑ ሰላም የሚገኘው ከሱ ዘንድ ብቻ ነው፡፡
" تَحِيَّتُهُمْ يَوْمَ يَلْقَوْنَهُ سَلَامٌ وَأَعَدَّ لَهُمْ أَجْرًا كَرِيمًا " سورة الأحزاب 44
"በሚገናኙት ቀን መከባበሪያቸው ሰላም በመባባል ነው፤ ለነርሱም የከበረን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል።" (ሱረቱል አሕዛብ 44)፡፡
" سَلَامٌ قَوْلًا مِنْ رَبٍّ رَحِيمٍ " سورة يس 58
"(ለነሱም) አዛኝ ከሆነው ጌታ ቃል በቃል ሰላምታ አላቸው።" (ሱረቱ ያሲን 58)፡፡ ሶላታችንን ሰግደን ስናጠናቅቅ ከሶስት ጊዜ "አስተግፊሩላህ" በኋላ የምንለው ዚክርም ይህን ያመላክታል፡-
عَنْ ثَوْبَانَ، قَالَ: كَانَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، إِذَا انْصَرَفَ مِنْ صَلَاتِهِ اسْتَغْفَرَ ثَلَاثًا وَقَالَ: «اللهُمَّ أَنْتَ السَّلَامُ وَمِنْكَ السَّلَامُ، تَبَارَكْتَ ذَا الْجَلَالِ وَالْإِكْرَامِ» مسلم.
ከሠውባን (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው፡- የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሶላታቸውን እንዳጠናቀቁ ፡- "አስተግፊሩላህ (አላህ ሆይ ይቅርታህን እጠይቃለሁ) ሶስት ጊዜ፡ ከዛም፡- አላሁምመ አንተ-ሰላም (አላህ ሆይ! አንተ ሰላም ነህ!) ወሚንከ-ሰላም (ሰላምም የሚገኘው ካንተው ነው)… ይሉ ነበር" (ሙስሊም)፡፡
2. አማኞች ሰላምን እንደሚያገኙ፡- ጌታችን አላህ "አስ-ሰላም" በመሆኑ በሱ ላመኑ ባሪያዎቹ ውስታዊና ውጫዊ ሰላም ያጎናጽፋቸዋል፡፡
" فَأْتِيَاهُ فَقُولَا إِنَّا رَسُولَا رَبِّكَ فَأَرْسِلْ مَعَنَا بَنِي إِسْرَائِيلَ وَلَا تُعَذِّبْهُمْ قَدْ جِئْنَاكَ بِآيَةٍ مِنْ رَبِّكَ وَالسَّلَامُ عَلَى مَنِ اتَّبَعَ الْهُدَى " طه 47
"ወደርሱም ኺዱ፤ በሉትም፦ እኛ የጌታህ መልክተኞች ነን፤ የእስራኤልንም ልጆች፣ ከኛ ጋር ልቀቅ፤ አታሰቃያቸውም፤ ከጌታህ በሆነው ታምር በእርግጥ መጥተንሃልና፤ #ሰላምም ቀጥታን በተከተለ ሰው ላይ ይሁን።" (ሱረቱ ጣሀ 47)፡፡
" قُلِ الْحَمْدُ لِلَّهِ وَسَلَامٌ عَلَى عِبَادِهِ الَّذِينَ اصْطَفَى آللَّهُ خَيْرٌ أَمَّا يُشْرِكُونَ " سورة النمل 59
"(ሙሐመድ ሆይ) በል «ምስጋና ለአላህ ይግባው፡፡ በእነዚያም በመረጣቸው ባሮቹ ላይ #ሰላም ይውረድ፡፡ አላህ በላጭ ነውን ወይስ ያ የሚያጋሩት (ጣዖት)፡፡" (ሱረቱ-ነምል 59)፡፡
" وَسَلَامٌ عَلَى الْمُرْسَلِينَ * وَالْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ " سورة الصافات 182-181
"በመልክተኞቹም ላይ #ሰላም ይኹን፤ ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን" (ሱረቱ-ሷፍፋት 181-182)፡፡
3. ጀነት ለመግባት ሰበብ መሆኑን፡- ጌታችን አላህ "አስ-ሰላም" በመሆኑ በዚህ ምድር ላይ እኛ አማኝ ባሪያዎቹ ሰላምታን ማብዛት እንዳለብን ተነግሮናል፡፡ ይህንን የሚያደርግም ጀነት እንደሚገባ ተገልጾአል፡፡ ቀጣዩ ሐዲስም ይሐን ይጠቁማል፡-
عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «لَا تَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ حَتَّى تُؤْمِنُوا، وَلَا تُؤْمِنُوا حَتَّى تَحَابُّوا، أَوَلَا أَدُلُّكُمْ عَلَى شَيْءٍ إِذَا فَعَلْتُمُوهُ تَحَابَبْتُمْ؟ أَفْشُوا السَّلَامَ بَيْنَكُمْ» مسلم.
ከአቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) በተላለፈው ሐዲሥ የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "እስካላመናችሁ ድረስ ጀነትን አትገቡም፣ እስካልተዋደዳችሁ ድረስ አታምኑም፣ ከሰራችሁት ሊያዋድዳችሁ የሚችልን ነገር ላመላክታችሁን? #ሰላምታን በመሐከላችሁ አብዙ" (ሙስሊም)፡፡
በዚህም ምክንያት አንድ ሙስሊም ሌላኛውን ሙስሊም ባገኘው ጊዜ ‹ኢስላማዊ ሰላምታ› እንዲሰጠው ታዝዞአል፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገሩን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ሙስሊም በሙስሊሙ ላይ ስድስት መብቶች አሉት፡፡ ሶሐቦችም (ረዲየላሁ ዐንሁም) ፡- ‹‹የአላህ መልክተኛ ሆይ! ምንድናቸው እነሱ?›› ብለው ሲጠይቁ፡ እሳቸውም፡- ሲያገኘው (አሰላሙ ዐለይኩም..) በማለት ሰላምታ ሊሰጠው…››በማለት መለሱ" (ሙስሊም 2162)፡፡
"እነዚያም በተአምራታችን የሚያምኑት (ወደ አንተ) በመጡ ጊዜ «ሰላም በእናንተ ላይ ይኹን፡፡ ጌታችሁ በነፍሱ ላይ እዝነትን ጻፈ፡፡ እነሆ ከእናንተ ውስጥ በስሕተት ክፉን ሥራ የሠራ ሰው ከዚያም ከእርሱ በኋላ የተጸጸተና ሥራውን ያሳመረ እርሱ (አላህ) መሓሪ አዛኝ ነው» በላቸው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 54)፡፡
4. ወደ ሰላም የሚመራ ጌታ መሆኑን፡- ጌታችን አላህ "አስ-ሰላም" በመሆኑ አማኝ ባሪያዎቹን በዚህ ዱንያ የሰላም መንገድ የሚመራ፡ በአኼራ ደግሞ የሰላም ሀገር ወደሆነችው ጀነት የሚጣራ አምላክ መሆኑን እንረዳለን፡-
"አላህ ውዴታውን የተከተሉትን ሰዎች #የሰላምን መንገዶች በርሱ ይመራቸዋል። በፈቃዱም ከጨለማዎች ወደ ብርሃን ያወጣቸዋል። ወደ ቀጥተኛም መንገድ ይመራቸዋል።" (ሱረቱል ማኢዳህ 16)፡፡
"አላህም ወደ #ሰላም አገር ይጠራል፡፡ የሚሻውንም ሰው ወደ ቀጥተኛው መንገድ ይመራል፡፡" (ሱረቱ ዩኑስ 25)፡፡
"ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ #የሰላም አገር አላቸው፡፡ እርሱም (ጌታህ) ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ረዳታቸው ነው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 127)፡፡
5. የመላእክት አቀባበል መሆኑ፡- አምላካችን አላህ "አስ-ሰላም" የሆነ አምላክ በመሆኑ፡ ነጌ በቂያም ዕለት አማኝ ባሪያዎቹን ወደ ጀነት ሲያስገባቸው መላእክት በየደጃፉ ሆነው የእንኳን ደህና መጣችሁ! ብ