የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
17.3K subscribers
306 photos
106 videos
47 files
801 links
ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።
Download Telegram
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
"ሙሐመዱን ረሱሉሏህ" 7 በአቡ ሀይደር በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡ 2. ለነቢይነታቸው ከአላህ ዘንድ የተሰጣቸው ማስረጃ…
"ሙሐመዱን ረሱሉሏህ" 8
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
3. የተላኩት ለመላው የዓለም ህዝብ ነው!!
በቁጥር አንድ ትምሕርታችን ላይ ስለ ነቢይነታቸው በቀደምት ነቢያት፣ መለኮታዊ መጽሐፍትና ሊቃውንት አንደበት የተነገረ ትንቢት በሚለው ስር፡ ለሶስት ተከታታይ ክፍሎች የተነገረላቸውን ትንቢት አይተናል፡፡
በቁጥር ሁለት ላይ ደግሞ፡- ለነቢይነታቸው ከአላህ ዘንድ የተሰጣቸው ማስረጃ (ሙዕጂዛ) የሚለውን፡ ለአራት ተከታታይ ክፍሎች ስንመለከት ቆይተናል፡፡ ዛሬ ደግሞ አላህ ፈቃዱ ከሆነ የተላኩት ለነማነው? የሚለውን እንመለከታለን ኢንሻአላህ፡፡
ነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከቀደምት ነቢያትና መልክተኞች ከሚለያቸው አንዱ ለሁሉም የሰው ዘር መልክተኛ ሆነው መላካቸው ነው፡፡ ከሳቸው በፊት የነበሩት በጠቅላላ የተላኩት ለህዝቦቻቸው ነው፡፡
አላህ በየጊዜው ነቢያትን በተከታታይ ያስነሳ ስለነበር፡ ነቢይ በሞተ ቁጥርም ሌላ ነቢይ ይተካው ስለነበር፡ ለሁሉም ህዝቦች መልክተኛ ከራሳቸው ህዝብ ተልኮላቸዋል (አን-ነሕል 36)፡፡ ከነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በኋላ ግን የሚላክ ነቢይም ሆነ መልክተኛ ባለመኖሩ አላህ የሳቸውን መልክተኝነት ለመላው ህዝብ በማድረግ ነቢይነትን በሳቸው ደመደመው (ሱረቱል አሕዛብ 40)፡፡
عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: " أُعْطِيتُ خَمْسًا لَمْ يُعْطَهُنَّ أَحَدٌ قَبْلِي: …، وَبُعِثْتُ إِلَى النَّاسِ كَافَّةً، وَكَانَ النَّبِيُّ يُبْعَثُ إِلَى قَوْمِهِ خَاصَّةً " رواه البخاري.
ጃቢር ኢብኒ ዐብዲላህ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ከኔ በፊት ለነበሩት (ነቢያት) ያልተሰጣቸው አምስት ነገር ተሰጠኝ፡፡….ለሰዎች ሁሉ መልክተኛ ሆኜ ተላክሁ፡፡ (ከኔ በፊት የነበረ) ነቢይ ግን ለህዝቦቹ ብቻ ይላክ ነበር" (ቡኻሪይ 335)፡፡
ከዚህ በመቀጠል የነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ተልእኮ ለመላው ህዝብ መሆኑን የሚያመላክቱ ማስረጃዎችን እናቀርባለን፡-
ሀ. በቀጥታ ለዓለማት እንደተላኩ መነገሩ፡-
ቅዱስ ቁርኣን ነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለዓለማት መላካቸውን በቀጥታ ቋንቋ እንዲህ በማለት ይገልጻል፡-
" وَمَا أَرْسَلْنَاكَ إِلَّا رَحْمَةً لِلْعَالَمِينَ * قُلْ إِنَّمَا يُوحَى إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَهُكُمْ إِلَهٌ وَاحِدٌ فَهَلْ أَنْتُمْ مُسْلِمُونَ * فَإِنْ تَوَلَّوْا فَقُلْ آذَنْتُكُمْ عَلَى سَوَاءٍ وَإِنْ أَدْرِي أَقَرِيبٌ أَمْ بَعِيدٌ مَا تُوعَدُونَ " سورة الأنبياء 109-107
"(ሙሐመድ ሆይ!) #ለዓለማትም እዝነት አድርገን እንጅ አልላክንህም። ያ ወደኔ የሚወረደው፣ አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው ማለት ነው፤ ታዲያ እናንተ ፍጹም ታዛዦች ናችሁን? በላቸው። እምቢም ቢሉ (በማወቅ) በእኩልነት ላይ ሆነን (የታዘዝኩትን) አስታወቅኋችሁ፤ የምትስፈራሩበትም ነገር ቅርብ፣ ወይም ሩቅ፣ መሆኑን አላውቅም፤ በላቸው።" (ሱረቱል አንቢያእ 107-109)፡፡
ለ. ለሰዎች ሁሉ በማለት መናገሩ፡-
ሌላው ማስረጃችን፡- አላህ እሳቸውን የላከው ለሰዎች ሁሉ ነው በማለት መናገሩ ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው፡- በየትኛውም ቦታ ሆነ በየትኛውም ጊዜ የሚኖር የሰው ዘር በጠቅላላ የሳቸው ነቢይነት ይመለከተዋል፡ ሊያምንባቸውም ግድ ይላል ማለት ነው፡፡ ቀጣዮቹ ቅዱስ ቁርኣናዊ አንቀጾች ይህን ይበልጥ ያስረዳሉ፡-
" مَا أَصَابَكَ مِنْ حَسَنَةٍ فَمِنَ اللَّهِ وَمَا أَصَابَكَ مِنْ سَيِّئَةٍ فَمِنْ نَفْسِكَ وَأَرْسَلْنَاكَ لِلنَّاسِ رَسُولًا وَكَفَى بِاللَّهِ شَهِيدًا " سورة النساء 79
"ከደግ ነገር የሚያገኝህ ከአላህ (ችሮታ) ነው፤ ከመከራም የሚደርስብህ ከራስህ (ጥፋት የተነሳ) ነው፤ #ለሰዎችም ሁሉ መልክተኛ ኾነህ ላክንህ መስካሪም በአላህ በቃ።" (ሱረቱ-ኒሳእ 79)፡፡
" قُلْ يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنِّي رَسُولُ اللَّهِ إِلَيْكُمْ جَمِيعًا الَّذِي لَهُ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ يُحْيِي وَيُمِيتُ فَآمِنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ النَّبِيِّ الْأُمِّيِّ الَّذِي يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَكَلِمَاتِهِ وَاتَّبِعُوهُ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ " سورة الأعراف 158
"(ሙሐመድ ሆይ!) በላቸው፦ እላንተ ሰዎች ሆይ! እኔ ወደ እናንተ #ወደሁላችሁም የአላህ መልክተኛ ነኝ፤(እርሱም) ያ የሰማይና የምድር ንግስና ለርሱ ብቻ የሆነ ነው፤ እርሱ እንጂ ሌላ አምላክ የለም፤ ሕያው ያደርጋል፤ ይገድላልም፤ በአላህና በዚያም በአላህና በቃላቶቹ በሚያምነው የማይጽፍ የማያነብ ነብይ በሆነው መልክተኛው እመኑ፤ ቅንንም መንገድ ትመሩ ዘንድ ተከተሉት።" (ሱረቱል አዕራፍ 158)፡፡
" وَمَا أَرْسَلْنَاكَ إِلَّا كَافَّةً لِلنَّاسِ بَشِيرًا وَنَذِيرًا وَلَكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ " سورة سبأ 28
"አንተንም #ለሰዎች ሁሉ በመላ፣ አብሳሪና አስፈራሪ አድርገን ቢሆን እንጂ አልላክንህም፤ ግን አብዛኞቹ ሰዎች አያውቁም።" (ሱረቱ ሰበእ 28)፡፡
ሐ. ከዐረቦች ውጪ ያሉትን መጣራታቸው፡-
የነቢዩ ሙሐመድ (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) ሃይማኖታዊ ጥርሪ ዐረቦቹ ላይ ብቻ የተገደበ አልነበረም፡፡ የመጽሐፉ ሰዎችን (አይሁዶችንና ክርስቲያኖችንም) ያቀፈ ነበር፡፡ እነሱንም ወደ ኢስላም ጥርሪ እንዲያደርጉላቸው ታዘዋል፡፡ ይህም ተልእኮአቸው ለመላው የሰው ዘር ለመሆኑ ሌላ አስረጂ ነው፡፡
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
"ሙሐመዱን ረሱሉሏህ" 8 በአቡ ሀይደር በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡ 3. የተላኩት ለመላው የዓለም ህዝብ ነው!! በቁጥር…
"ሙሐመዱን ረሱሉሏህ" 9
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
4. የመጨረሻ ነቢይ ናቸው!!
ባለፈው ክፍል ስምንት ላይ በቁጥር ሦስት ስር የነቢዩ ሙሐመድን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ተልእኮ በተመለከተ፡ የተላኩት ለመላው የሰው ዘር መሆኑን በሰፊው ተመልክተናል፡፡ ዛሬ የምንመለከተው ደግሞ፡ እሳቸው ከነቢያትና ከመልክተኞች የመጨረሻና መደምደሚያ መሆናቸውን ነው፡፡ ከሳቸው በኋላ የሚነሳ የአላህ ነቢይም ሆነ መልክተኛ የለም፡፡ የሚወርድ መለኮታዊ መጽሐፍም የለም፡፡ ነቢይነት በሳቸው እንደተደመደመው ሁሉ፡ መለኮታዊ መጻሕፍትም በቅዱስ ቁርኣን ተደምድመዋል፡፡ ይህን አቋም በተመለከተ የሚናገሩ ቁርኣዊና ነቢያዊ ሐዲሦችን እንመለከታለን ኢንሻአላህ፡-
1. ከቅዱስ ቁርኣን፡-
ሀ. በግልጽ መደምደሚያ ማለቱ፡-
" مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا " سورة الأحزاب 40.
"ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፤ ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው፤ አላህም በነገሩ ሁላ ዐዋቂ ነው።" (ሱረቱል አሕዛብ 40)፡፡
በዚህ አንቀጽ ውስጥ ‹‹የነቢዮች መደምደሚያ›› የሚለው ኃይለ-ቃል፡ ነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከአላህ ነቢያት የመጨረሻውና መደምደሚያ ነቢይ እንደሆኑ በግልጽ የሚያስረዳ ነው፡፡ በመሆኑም ከሳቸው በኋላ የሚመጣ የአላህ ነቢይ የለም፡፡ የሚወርድ አዲስ መለኮታዊ መጽሐፍም የለም፡፡
ለ. የቁርኣን አስጠንቃቂነት አለመገደቡ፡-
" قُلْ أَيُّ شَيْءٍ أَكْبَرُ شَهَادَةً قُلِ اللَّهُ شَهِيدٌ بَيْنِي وَبَيْنَكُمْ وَأُوحِيَ إِلَيَّ هَذَا الْقُرْآنُ لِأُنْذِرَكُمْ بِهِ وَمَنْ بَلَغَ أَئِنَّكُمْ لَتَشْهَدُونَ أَنَّ مَعَ اللَّهِ آلِهَةً أُخْرَى قُلْ لَا أَشْهَدُ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَهٌ وَاحِدٌ وَإِنَّنِي بَرِيءٌ مِمَّا تُشْرِكُونَ " سورة الأنعام 19.
"«በምስክርነት ከነገሩ ሁሉ ይበልጥ ታላቅ ማነው» በላቸው፡፡ (ሌላ መልስ የለምና) «አላህ ነው፡፡ በእኔና በእናንተ መካከል መስካሪ ነው፡፡ ይህም ቁርኣን እናንተንና የደረሰውን ሰው ሁሉ በርሱ ላስፈራራበት ወደኔ ተወረደ፡፡ ከአላህ ጋር ሌሎች አማልክት መኖራቸውን እናንተ ትመሰክራላችሁን» በላቸው፡፡ «እኔ አልመሰክርም» በላቸው፡፡ «እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 19)፡፡
በዚህ አንቀጽ መሰረት፡ ምስክርነቱ ከሁሉም በላጭ የሆነው አላህ፡ ለሳቸው ነቢይነት የሱ ምስክርነት በቂ እንደሆነ ይገልጻል፡፡ በመቀጠልም የቁርኣንን አስጠንቃቂነት ያለ ቦታና ጊዜ ገደብ እስከመጨረሻው ዘመን ቀጣይነት እንዳለው አስረዳ፡፡ በጥቅሱ ውስጥ ‹‹እናንተንና የደረሰውን ሰው ሁሉ›› የሚለው ቃል ትልቅ አስረጂ ነው፡፡
‹‹እናንተን›› ብሎ ሲናገር፡ በወቅቱ የነበሩ ሶሓባዎችን የሚጠቁም ሲሆን፡ ‹‹የደረሰውን ሰው ሁሉ›› የሚለው ደግሞ፡ ከዛ በኋላ የሚመጡ ትውልዶች፡ በየትኛውም ዘመን ይኑሩ በየትኛውም ቦታ፡ የቁርኣን መልክት ከደረሳቸው፡ ቁርኣን ለነሱ አስጠንቃቂ ነው፡፡ ሊያምኑበት ግድ ይላል ማለት ነው፡፡
በዚህ መሰረትም ‹‹የደረሰውን ሰው ሁሉ›› በማለቱ የቁርኣን አስጠንቃቂነት በጊዜም ሆነ በቦታ ካልተገደበ፡ የሳቸው ነቢይነትም የመጨረሻና መደምደሚያ ለመሆኑ በቂ ማስረጃ ነው፡፡ ከሳቸው በኋላ ሌላ ነቢይ ወይም መልክተኛ የሚመጣ ቢሆን ኖሮ፡ የቁርኣን አስጠንቃቂነት እስከዛ ነቢይ ድረስ ብቻ ነበር የሚሆነው፡፡ ከዛ በኋላ አዲስ የመጣውን ነቢይ መከተል ግድ ይሆናል፡፡ አሁን ግን የቁርኣን አስጠንቃቂነት በቦታም ሆነ በዘመን ሳይገደብ ‹‹የደረሰውን ሰው ሁሉ›› የሚመለከት ከሆነ፡ አዲስ ነቢይም ሆነ አዲስ መጽሐፍ አይወርድም ማለት ነው፡፡
ሐ. የመልክቱ ዓለም አቀፋዊነት፡-
" قُلْ يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنِّي رَسُولُ اللَّهِ إِلَيْكُمْ جَمِيعًا الَّذِي لَهُ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ يُحْيِي وَيُمِيتُ فَآمِنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ النَّبِيِّ الْأُمِّيِّ الَّذِي يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَكَلِمَاتِهِ وَاتَّبِعُوهُ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ " سورة الأعراف 158
"(ሙሐመድ ሆይ!) በላቸው፦ እላንተ ሰዎች ሆይ! እኔ ወደ እናንተ #ወደሁላችሁም የአላህ መልክተኛ ነኝ፤(እርሱም) ያ የሰማይና የምድር ንግስና ለርሱ ብቻ የሆነ ነው፤ እርሱ እንጂ ሌላ አምላክ የለም፤ ሕያው ያደርጋል፤ ይገድላልም፤ በአላህና በዚያም በአላህና በቃላቶቹ በሚያምነው የማይጽፍ የማያነብ ነብይ በሆነው መልክተኛው እመኑ፤ ቅንንም መንገድ ትመሩ ዘንድ ተከተሉት።" (ሱረቱል አዕራፍ 158)፡፡
ይህ አንቀጽ የነቢዩ ሙሐመድን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ተልእኮ ዐለም-አቀፋዊነት ያስረዳል፡፡ ለመላው የሰው ዘር የተላኩ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ በተለይ ‹‹ወደ ሁላችሁም›› የሚለው ቃል፡ በወቅቱ የነበሩትንም ወደፊት የሚመጡትንም ሰዎች ይመለከታል፡፡ በሌላ አነጋጋር እሳቸው የነቢያት መደምደሚ መሆናቸውን ይገልጻል ማለት ነው፡፡
መ. ዲኑ የተሟላ መመሪያን ማቀፉ፡-
"...الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا..." سورة المائدة 3.
"…ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ…" (ሱረቱል ማኢዳህ 3)፡፡
በዚህ አንቀጽ ስር አላህ በባሪዎቹ ላይ የዋለውን ጸጋ በማውሳት ለጋስነቱን ይገልጻል፡፡ ከጸጋዎቹም አንዱ ለዚህ ኡምማ ዲኑን ከመመሪያ አንጻር የተሟላ አድርጎ መስጠቱን በመግለጽ ነው፡፡ በርግጥም ይህ ዲን ሙሉ ነው፡፡ ለመንፈሳዊ ህይወትም ሆነ ለስጋዊ ኖሮ አስፈላጊውን ህግ በተሟላ መልኩ አቅፏል፡፡ ምንም አይነት ጭማሬን አይቀበልም፡፡ የጎደለው ነገር የለምና፡፡ ህጉ በየትኛውም ቦታና በየትኛውም ዘመን፡ ለየትኛውም አይነት ህዝብ ስራ ላይ መዋል ይችላል፡፡
ታዲያ የነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሸሪዓህ ፍጹም የተሟላ መመሪያን ያቀፈ ህግ ከሆነ፡ ሌላ ነቢይ የሚመጣበት፡ ሌላ መለኮታዊ መጽሐፍት የሚወርድበት ምክንያት ምንድነው? በርግጥም ሌላ አዲስ ነቢይ አይመጣም!!