የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
17.3K subscribers
306 photos
106 videos
47 files
801 links
ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።
Download Telegram
ሐ. የምንወስደው ትምሕርት፡-
1. አላህ መኖሩ የተረጋገጠ መሆኑ፡- የፈጣሪ አምላካችን አላህ መኖር ምናባዊ ሳይሆን ፍጹም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡ የሱ መኖር scientifical truth ወይም Historical truth ሳይሆን Universal truth (ተፈጥሮአዊ እውነታ) ነው፡፡ የአላህን መኖር ለማረጋገጥ የከርሰ ምድር ጥናት ወይም የጠፈር ምርምር ወይም የታሪክ ማረጋገጫ አያስፈልግም፡፡ ማንም ሰው በተፈጥሮው ያለ-ምንም ሃይማኖታዊ ተጽእኖ አምኖ የሚቀበለውና የሚያድግበት እውነት ነው፡፡ ስለሆነም ጌታ አላህ "አል-ሐቅ" ተብሎ ይጠራል፡-
"يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنْ كُنْتُمْ فِي رَيْبٍ مِنَ الْبَعْثِ فَإِنَّا خَلَقْنَاكُمْ مِنْ تُرَابٍ ثُمَّ مِنْ نُطْفَةٍ ثُمَّ مِنْ عَلَقَةٍ ثُمَّ مِنْ مُضْغَةٍ مُخَلَّقَةٍ وَغَيْرِ مُخَلَّقَةٍ لِنُبَيِّنَ لَكُمْ وَنُقِرُّ فِي الْأَرْحَامِ مَا نَشَاءُ إِلَى أَجَلٍ مُسَمًّى ثُمَّ نُخْرِجُكُمْ طِفْلًا ثُمَّ لِتَبْلُغُوا أَشُدَّكُمْ وَمِنْكُمْ مَنْ يُتَوَفَّى وَمِنْكُمْ مَنْ يُرَدُّ إِلَى أَرْذَلِ الْعُمُرِ لِكَيْلَا يَعْلَمَ مِنْ بَعْدِ عِلْمٍ شَيْئًا وَتَرَى الْأَرْضَ هَامِدَةً فَإِذَا أَنْزَلْنَا عَلَيْهَا الْمَاءَ اهْتَزَّتْ وَرَبَتْ وَأَنْبَتَتْ مِنْ كُلِّ زَوْجٍ بَهِيجٍ * ذَلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّهُ يُحْيِ الْمَوْتَى وَأَنَّهُ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ " سورة الحج 6-5
"እላንተ ሰዎች ሆይ! ከመቀስቀስ፣ በመጠራጠር ዉስጥ እንደ ሆናችሁ (አፈጣጠራችሁን ተመልከቱ)፤ እኛም ከዐፈር ፈጠርናችሁ ከዚያም ከፍቶት ጠብታ፣ ከዚያም ከረጋ ደም፣ ከዚያም ከቁራጭ፣ ስጋ ፍጥረትዋ ሙሉ ከኾነችና ሙሉ ካልሆነች (ችሎታችንን) ለናንተ ልንገልጽላችሁ ፈጠርናችሁ፤ የምንሻውንም፣ እስከ ተወሰነ ጊዜ ድረስ፣ በማህጸን ዉስጥ እናረጋዋለን ከዚያም ሕጻን ሆናችሁ እናወጣችኋለን። ከዚያም ሙሉ ጥንካሬያችሁን ትደርሱ ዘንድ፣ (እናሳድጋችኋለን)፤ ከናንተም የሚሞት ሰው አለ፤ ከናንተም ከዕውቀት በኋላ፣ ምንንም እንዳያውቅ ወደ ወራዳ ዕድሜ የሚመለስ ሰው አልለ፤ ምድርንም ደረቅ ሆና ታያታለህ፤ በስዋም ላይ ውሃን ባወረድን ጊዜ፣ ትላወሳለች፤ ትነፋለችም፤ ውበት ካለው ቦታ ሁሉ ታበቅላለችም። ይህ፣ አላህ እርሱ #መኖሩ-የተረጋገጠ፤ እርሱም ሙታንን ሕያው የሚያደርግ፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ በመሆኑ ነው።" (ሱረቱል ሐጅ 5-6)፡፡
"ذَلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّ مَا يَدْعُونَ مِنْ دُونِهِ هُوَ الْبَاطِلُ وَأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْعَلِيُّ الْكَبِيرُ " سورة الحج 62
"ይህ አላህ እርሱ #እውነት በመሆኑ ከርሱም ሌላ የሚገዙት ነገር እርሱ ፍጹም ውሽት በመሆኑ አላህም እርሱ የሁሉ በላይ ታላቅ በመሆኑ ነው።" (ሱረቱል ሐጅ 62)፡፡
"يَوْمَئِذٍ يُوَفِّيهِمُ اللَّهُ دِينَهُمُ الْحَقَّ وَيَعْلَمُونَ أَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ الْمُبِينُ " سورة النور 25
"በዚያ ቀን አላህ እውነተኛ ዋጋቸውን ይመላላቸዋል አላህም እርሱ #መኖሩ-የተረጋገጠ (ሁሉን ነገር) ገላጭ መሆኑን ያውቃሉ።" (ሱረቱ-ኑር 25)፡፡
"ذَلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّ مَا يَدْعُونَ مِنْ دُونِهِ الْبَاطِلُ وَأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْعَلِيُّ الْكَبِيرُ " سورة لقمان 30
"ይህ፣ አላህ እርሱ #እውነት፣ ከርሱም ሌላ የሚገዙት (ጣዖት)ውሸት በመሆኑና አላህም እርሱ የበላይ ታላቅ በመኾኑ ነው።" (ሱረቱ ሉቅማን 30)፡፡
2. ንግግሩ እውነት መሆኑን፡- እውነተኛው አምላክ አላህ የሚናገረውም እውነትን ብቻ ነው፡፡ ውሸት እሱ ዘንድ በፍጹም የለም አይታሰብምም፡፡ በንግግርም ከርሱ የበለጠ እውነተኛ የለም፡-
"اللَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ لَيَجْمَعَنَّكُمْ إِلَى يَوْمِ الْقِيَامَةِ لَا رَيْبَ فِيهِ وَمَنْ أَصْدَقُ مِنَ اللَّهِ حَدِيثًا " سورة النساء 87
"አላህ ከርሱ በስተቀር አምላክ የለም፤ ወደ ትንሣኤ ቀን በርሱ ጥርጥር የሌለበት ሲሆን፣ በእርግጥ ይሰበስባችኋል። በንግግርም ከአላህ ይበልጥ #እውነተኛ ማነው?" (ሱረቱ-ኒሳእ 87)፡፡
"وَالَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ سَنُدْخِلُهُمْ جَنَّاتٍ تَجْرِي مِنْ تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا وَعْدَ اللَّهِ حَقًّا وَمَنْ أَصْدَقُ مِنَ اللَّهِ قِيلًا " سورة النساء 122
"እነዚያም ያመኑና በጎ ስራዎችን የሠሩ፣ በስራቸው ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች ዘላለም በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲሆኑ እናገባዋቸዋለን፤ አላህ እውነተኛን ተስፋ ሰጣቸው። በንገገርም ከአላህ ይበልጥ #እውነተኛ ማን ነው?" (ሱረቱ-ኒሳእ 122)፡፡
"وَهُوَ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ بِالْحَقِّ وَيَوْمَ يَقُولُ كُنْ فَيَكُونُ قَوْلُهُ الْحَقُّ وَلَهُ الْمُلْكُ يَوْمَ يُنْفَخُ فِي الصُّورِ عَالِمُ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ وَهُوَ الْحَكِيمُ الْخَبِيرُ " سورة الأنعام 73
"እርሱም ያ ሰማያትንና ምድርን በእውነት የፈጠረ ነው፡፡ «ኹን» የሚልበትንና ወዲያውም የሚኾንበትን ቀን (አስታውስ)፡፡ ቃሉ #እውነት ነው፡፡ በቀንዱም በሚነፋ ቀን ንግሥናው የርሱ ብቻ ነው፡፡ ሩቁንና ቅርቡን ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ጥበበኛው ውስጥ ዐዋቂው ነው፡፡" (ሱረቱል አንዓም 73)፡፡
"وَلَا تَنْفَعُ الشَّفَاعَةُ عِنْدَهُ إِلَّا لِمَنْ أَذِنَ لَهُ حَتَّى إِذَا فُزِّعَ عَنْ قُلُوبِهِمْ قَالُوا مَاذَا قَالَ رَبُّكُمْ قَالُوا الْحَقَّ وَهُوَ الْعَلِيُّ الْكَبِيرُ " سورة سبأ 23
"ምልጃም እርሱ ለፈቀደለት ሰው ብቻ ቢሆን እንጂ፣ እርሱ ዘንድ ምንም አትጠቅምም፤ ከልቦቻቸው ላይ ድንጋጤው በተገለጠም ጊዜ (ተማላጆቹ) ጌታችሁ ምን አለ? ይላሉ፤ (አማላጆቹ) #እውነትን አለ፤ እርሱም ከፍተኛው ታላቁ ጌታ ነው ይላሉ።" (ሱረቱ ሰበእ 23)፡፡