💚💛 ቅድስት ሣራ ብጽዕት💛❤️
አበው እናታችን ሣራን " #ቡርክተ_ማሕጸን " ይሏታል::
(የቅዱሱ ዘር የይስሐቅ እናት ናትና) በዚያውም ላይ የደጉ
ሰው የአብርሃም ሚስት ናት:: ልክ በዓለም ታሪክ "ከጠንካራና
ስኬታማ ወንዶች ጀርባ ጠንካራ ሴቶች አሉ" እንደሚባለው
ከአብርሃም አባታችን ስኬታማ የቅድስና ሕይወት ጀርባ
ብጽዕት ሣራ አለች::
ለአብርሃም አባታችን መጽሐፍ የተናገረው ክብር ሁሉ
ለቅድስት ሣራ ይገባታል:: አንድም ገንዘቧ ነው:: ቅድስቷ እናት
ደጉ አብርሃምን ያገባችው ገና በከላውዴዎን (በ2ቱ ወንዞች
መካከል) ሳለ ነው:: ገና ከልጅነቷ ጀምራ አብርሃምን "ጌታየ"
እያለች ታገለግለው እንደ ነበር ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል::
(1ዼጥ. 3:5)
በዚህም ከብራበታለች: ገናበታለች እንጂ አልተጐዳችበትም::
አብርሃም ወደ ካራን ሲወጣ "ለምን?" አላላችም:: እንዲሁ
ለፈቃደ እግዚአብሔር ታዘዘች እንጂ:: በካራን ታራን ቀብረው:
በፈጣሪ ትዕዛዝ ወደ #ከነዓን ሲፈልሱም ቅድስት ሣራ
አልተቃወመችም::
ለፈጣሪዋ ትዕዛዝና ለባሏ ስትል ርስቷን: ሃገሯን: ዘመዶቿን
ሁሉ ትታ ሔዳለች:: ይሔውም በጐ ምናኔ ነው:: እናታችን ሳራ
በከነዓን የተመቸ ነገር አልገጠማትም:: ከአንዴም ሁለቴ
በረሃብና በድርቅ ምክንያት ወደ ግብጽ እና #ጌራራ ተሰደዋል::
በዚያም ፈርዖን "እነካለሁ" ቢል እግዚአብሔር ተቆጥቶ:
ፈርኦንንና ግብጽን በደዌ መታ:: በዚህም ክብረ ሣራን
ተመለከትን:: ከስደት መልስም በኬብሮን (በተመሳቀለ
መንገድ ላይ) ድንኩዋን ሠርተው የወጣ የወረደውን ሲያበሉ:
እንግዳ ሲቀበሉ ኑረዋል::
(ልብ በሉልኝ ይህን ትጋትና ደግነት ያሳየችውን ቅድስት ሣራን
ልናከብራት ይገባል)
እድሜ ዘመኗን ያሳለፈችው እንግዳ በመቀበል:
እግዚአብሔርን በማምለክ ነው:: ምንም እንኩዋ ማሕጸኗ
ለጊዜው ቢዘጋ ተስፋ አልቆረጠችም:: ለአብርሃምም ከአጋር እንዲወልድ ፈቃድ ሰጥታለች:: ዕድሜዋ 89 ዓመት በሆነ ጊዜ ሰይጣን እንግዳ እንዳይመጣ ለ3 ቀናት ቢያስቀርባቸው እንደ ባሏ እርሷም 3 ቀናትን ያለ ምግብ አሣልፋለች:: በ3ኛው ቀን ሥላሴን በቤቷ
አስተናግዳለች:: ስለ ክብሯም ከ3 መሥፈሪያ ዱቄት ለውሳ
ያዘጋጀችውን እንጐቻ ሥላሴ በልተውላታል:: (ምንም ሥላሴ
ምግብን ባይመገቡም)
የሥላሴ በዚያች ድንኩዋን ውስጥ መስተናገድ ታላቅ
ምሥጢር አለው:: ከግብዣው በሁዋላም እግዚአብሔር አለ:-
"አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ . . . እንዲሁ ከርሞ
እመለሳለሁ: ሣራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች" አለው::
ያን ጊዜ ሣራ በውሳጤ ሐይመት (በድኩዋኑ ውስጥ) ሆና
ሰምታ ሣቀች:: ለምን ሳቀች ቢሉ:- እጅግ ደስ ቢላት! አንድም
ቢገርማት:: ይሕስ በምን ይታወቃል ቢሉ:- ልጇ " #ይስሐቅ "
የተባለው "ለእናቱ ሣቅን: ደስታን ያመጣ" ለማለት ነውና::
ሥላሴም:- "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ: እንዘ ትብል
ዓዲየኑ እስከ ይእዜ: ወእግዚእየኑ ልሕቀ: ቦኑ ነገር ዘይሰዓኖ
ለእግዚአብሔር - ሣራን ምን አሳቃት? ለእግዚአብሔርስ
የሚሳነው ነገር አለን" ብለዋል::
ቅድስት ሣራ በ90 ዓመቷ ይስሐቅን ወልዳ በቀሪ ዘመኖቿ
በደስታ ኑራለች:: በዚህች ቀንም በመልካም ሽምግልና ዐርፋ:
አባታችን #አብርሃም ከታላቅ ሐዘን ጋር ቀብሯታል:: ሐዋርያው
#ቅዱስ_ዻውሎስ ብጽዕት ሣራን በበጐ ምሳሌ መስሏታል::
(ዕብ. 11:11)
አበው እናታችን ሣራን " #ቡርክተ_ማሕጸን " ይሏታል::
(የቅዱሱ ዘር የይስሐቅ እናት ናትና) በዚያውም ላይ የደጉ
ሰው የአብርሃም ሚስት ናት:: ልክ በዓለም ታሪክ "ከጠንካራና
ስኬታማ ወንዶች ጀርባ ጠንካራ ሴቶች አሉ" እንደሚባለው
ከአብርሃም አባታችን ስኬታማ የቅድስና ሕይወት ጀርባ
ብጽዕት ሣራ አለች::
ለአብርሃም አባታችን መጽሐፍ የተናገረው ክብር ሁሉ
ለቅድስት ሣራ ይገባታል:: አንድም ገንዘቧ ነው:: ቅድስቷ እናት
ደጉ አብርሃምን ያገባችው ገና በከላውዴዎን (በ2ቱ ወንዞች
መካከል) ሳለ ነው:: ገና ከልጅነቷ ጀምራ አብርሃምን "ጌታየ"
እያለች ታገለግለው እንደ ነበር ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል::
(1ዼጥ. 3:5)
በዚህም ከብራበታለች: ገናበታለች እንጂ አልተጐዳችበትም::
አብርሃም ወደ ካራን ሲወጣ "ለምን?" አላላችም:: እንዲሁ
ለፈቃደ እግዚአብሔር ታዘዘች እንጂ:: በካራን ታራን ቀብረው:
በፈጣሪ ትዕዛዝ ወደ #ከነዓን ሲፈልሱም ቅድስት ሣራ
አልተቃወመችም::
ለፈጣሪዋ ትዕዛዝና ለባሏ ስትል ርስቷን: ሃገሯን: ዘመዶቿን
ሁሉ ትታ ሔዳለች:: ይሔውም በጐ ምናኔ ነው:: እናታችን ሳራ
በከነዓን የተመቸ ነገር አልገጠማትም:: ከአንዴም ሁለቴ
በረሃብና በድርቅ ምክንያት ወደ ግብጽ እና #ጌራራ ተሰደዋል::
በዚያም ፈርዖን "እነካለሁ" ቢል እግዚአብሔር ተቆጥቶ:
ፈርኦንንና ግብጽን በደዌ መታ:: በዚህም ክብረ ሣራን
ተመለከትን:: ከስደት መልስም በኬብሮን (በተመሳቀለ
መንገድ ላይ) ድንኩዋን ሠርተው የወጣ የወረደውን ሲያበሉ:
እንግዳ ሲቀበሉ ኑረዋል::
(ልብ በሉልኝ ይህን ትጋትና ደግነት ያሳየችውን ቅድስት ሣራን
ልናከብራት ይገባል)
እድሜ ዘመኗን ያሳለፈችው እንግዳ በመቀበል:
እግዚአብሔርን በማምለክ ነው:: ምንም እንኩዋ ማሕጸኗ
ለጊዜው ቢዘጋ ተስፋ አልቆረጠችም:: ለአብርሃምም ከአጋር እንዲወልድ ፈቃድ ሰጥታለች:: ዕድሜዋ 89 ዓመት በሆነ ጊዜ ሰይጣን እንግዳ እንዳይመጣ ለ3 ቀናት ቢያስቀርባቸው እንደ ባሏ እርሷም 3 ቀናትን ያለ ምግብ አሣልፋለች:: በ3ኛው ቀን ሥላሴን በቤቷ
አስተናግዳለች:: ስለ ክብሯም ከ3 መሥፈሪያ ዱቄት ለውሳ
ያዘጋጀችውን እንጐቻ ሥላሴ በልተውላታል:: (ምንም ሥላሴ
ምግብን ባይመገቡም)
የሥላሴ በዚያች ድንኩዋን ውስጥ መስተናገድ ታላቅ
ምሥጢር አለው:: ከግብዣው በሁዋላም እግዚአብሔር አለ:-
"አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ . . . እንዲሁ ከርሞ
እመለሳለሁ: ሣራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች" አለው::
ያን ጊዜ ሣራ በውሳጤ ሐይመት (በድኩዋኑ ውስጥ) ሆና
ሰምታ ሣቀች:: ለምን ሳቀች ቢሉ:- እጅግ ደስ ቢላት! አንድም
ቢገርማት:: ይሕስ በምን ይታወቃል ቢሉ:- ልጇ " #ይስሐቅ "
የተባለው "ለእናቱ ሣቅን: ደስታን ያመጣ" ለማለት ነውና::
ሥላሴም:- "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ: እንዘ ትብል
ዓዲየኑ እስከ ይእዜ: ወእግዚእየኑ ልሕቀ: ቦኑ ነገር ዘይሰዓኖ
ለእግዚአብሔር - ሣራን ምን አሳቃት? ለእግዚአብሔርስ
የሚሳነው ነገር አለን" ብለዋል::
ቅድስት ሣራ በ90 ዓመቷ ይስሐቅን ወልዳ በቀሪ ዘመኖቿ
በደስታ ኑራለች:: በዚህች ቀንም በመልካም ሽምግልና ዐርፋ:
አባታችን #አብርሃም ከታላቅ ሐዘን ጋር ቀብሯታል:: ሐዋርያው
#ቅዱስ_ዻውሎስ ብጽዕት ሣራን በበጐ ምሳሌ መስሏታል::
(ዕብ. 11:11)