♥ #ቅድስት_ኄራኒ_ሐዋርያዊት_ሰማዕት ♥
ይህቺ ቅድስት ወጣት መልክ ከደም ግባት: ምግባር
ከሃይማኖት: ስም ከመልካምነት የተባበረላት ሰማዕት
ናት:: #ኄራኒ ማለት "ሰላማዊት: የተወደደች" ማለት
ነው:: አንድም በጥሬው "ሰላምና ፍቅር" ማለት ነው::
ቅድስት ኄራኒ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን በታናሽ
እስያ የንጉሥ #ሉክያኖስ ልጅ ናት:: ከተወለደች ጀምሮ
ስለ ክርስትና ሰምታ አታውቅም:: ምክንያቱም አባቷ
ጣዖት አምላኪ ከመሆኑ ባለፈ ክርስቲያኖችን ይቀጣ ስለ
ነበር ነው::
ልጁን ማንም እንዳያገኛት ሲል ንጉሡ ለቅድስት ኄራኒ
ቤተ መንግስት ሠራላት:: ማንም እንዳይገባ በዙሪያው
12 አጥር አጠረበት:: ጣዖቶቹን እንድታጥን
አገልጋዮችንም ሾመላት::
ምናልባት አጥር ሰውን ሊከለክለው ይችላል::
#እግዚአብሔር ግን እግዚአብሔር ነውና ምንም
አይከለክለውም:: ጌታ ደግሞ ይህቺን ወጣት ለወንጌል
አገልግሎት ይፈልጋታል:: አንድ ቀን አባቷ: ልጁ ምሑር
እንድትሆንለት አለ የተባለ ሽማግሌ ፈላስፋ ቀጠረላት::
ጥበበ እግዚአብሔር ማለት ይሔ ነው:: አባቷ ይሕ
ሽማግሌ ማንን እንደሚያመልክ አልተረዳም:: አረጋዊው
እጅግ የተዋጣለት ክርስቲያን ነው:: ግን ማንም
አያውቅበትም:: አረጋዊው ቅድስት ኄራኒን ዝም ብሎ
ሊሰብካት አልወደደም::
መጀመሪያ በስነ ምግባር አነጻት:: ቀጥሎ ግን "ጌታ ሆይ! ጐዳናህን ምራት" እያለ ይጸልይላት ገባ:: ጌታችን ልመናውን ሰምቶታልና ቅድስቷ አንድ ቀን ግሩም ራዕይን
አየች::
እርሷ ለማዕድ ተቀምጣ ሳለ: የምሥራቅና የምዕራብ
መስኮቶቿም ተከፍተው ሳሉ: በምሥራቁ መስኮት ነጭ
ርግብ በአፏ የወይራ ዝንጣፊ (ቆጽለ ዘይት) ይዛ ገባችና
ማዕዷ ላይ አኑራው ሔደች:: እርሷን ተከትሎ ደግሞ
ንስር በአፉ አክሊል ይዞ ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ሔደ::
በ3ኛው ግን ቁራ: እባብ በአፉ ይዞ በምዕራቡ መስኮት
ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ወጣ:: ቅድስት ኄራኒ ያየችው
ራዕይ ቢጨንቃት ሽማግሌ መምሕሯን "ተርጉምልኝ"
አለችው::
እርሱም "ልጄ ሆይ! ለዘመናት ስጠብቀው የነበረ ምኞቴን ነው ጌታ ያሳየሽ:: የሕልምሽ ትርጉም እንዲህ ነው:- ነጭ ርግብ የመንፈስ ቀዱስ (የሃይማኖት) ምሳሌ
ናት:: የወይራ ዝንጣፊው ደግሞ #ማሕተመ_ጥምቀት
( #ሜሮን ) ነው:: ቁራ የክፉ ነገሥታት ምሳሌ ሲሆን
እባብ የመከራ ምሳሌ ነው::
ንስር ድል የመንሳት ምልክት ሲሆን አክሊል ደግሞ
የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ነው:: ልጄ! ክርስቲያን ሆነሽ
የሚደርስብሽን ሁሉ ጌታ አሳይቶሻል" ብሎ ተርጉሞላት
ተሰናበታት::
እርሷም ወደ ምሥራቅ ዙራ ጸለየች:- "የማላውቅህ
አምላክ ሆይ! ወደ እውነትህ ምራኝ" ስትል ለመነች::
በዚያች ሰዓት የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ አጽናናት::
የሚያጠምቃትም እንደሚልክላት ነገራት::
በዚያን ጊዜ አባቷ ገብቶ "ልጄ! ከመሣፍንቱ ላንዱ ልድርሽ ስለሆነ ምን ትያለሽ?" አላት:: "3 ቀን ስጠኝ" አለችውና ሰጣት:: ወደ ጣዖቶቹ ዕለቱኑ ወርዳ "ላግባ
ወይስ ይቅርብኝ?" አለቻቸው:: ከቀድሞም በወርቅ
የተለበጡ ድንጋዮች ናቸውና ዝም አሉ:: በሙሉ ቀጥቅጣ
ሰባብራቸው ተመለሰች::
በዘመኑ #ቅዱሳን_ሐዋርያት (በተለይ እነ
#ቅዱስ_ዻውሎስ ) በሕይወተ ሥጋ ነበሩና ከቅዱስ
ዻውሎስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቤቷ እንደ ተዘጋ ገባ::
ክርስትናን ከጥንቱ እስከ ተፍጻሜቱ አስተምሮ አጠመቃት::
በ3ኛው ቀን አባቷ "ምን መከርሽ?" ቢላት "የእኔ ምክር
#መርዓተ_ክርስቶስ (ሰማያዊ ሙሽራ) መሆን ነው"
አለችው:: አባቷ ደነገጠ:: እጅግ ስለ ተናደደ ወደ
አደባባይ አውጥቶ: አስሮ መሬት ላይ ጣላትና በመቶ
የሚቆጠሩ ፈረሶች እንዲረግጧት አደረገ::
በወቅቱ ሰው የሚጠብቀው የአካሏን ቁርጥራጭ ነበር::
ነገር ግን ጌታ ከእርሷ ጋር ነበርና ልብሷ እንኩዋ ጭቃ
አልነካም:: አባቷ ንጉሥ ሉክያኖስና ሠራዊቱ ያዩትን
ማመን አልቻሉም:: ሁሉም ድምጻቸውን ከፍ አድርገው
"ከክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" አሉ:: ቅድስት
ኄራኒ ምንም ሳትናገር ይህንን ሁሉ ሰው ማረከች::
ወዲያውም ንጉሡ መልእክተኛ ልኮ: የቅዱስ ዻውሎስ
ደቀ መዝሙርን አስጠርቶ: ከነ ቤተሰቦቹ ተጠመቀ::
የዚህን ዓለም ክብር ንቆም ንግሥናውን ተወ:: የጸሎት
ሰውም ሆነ:: የቅድስት ኄራኒ ተጋድሎ ግን ቀጠለ::
በአካባቢው የነበረ ንጉሥ መጥቶ የአባቷን መንግስት
ቀማ:: እርሷንም እጅግ አሰቃያት:: እርሱ አልፎ
አርማንዮስ የሚባል ንጉሥ እንዲሁ አሰቃያት:: እርሱም
አለፈ:: ከእርሱ ቀጥሎ የመጣው ንጉሥ ብዙ
መከራዎችን በእርሷ ላይ አደረሰ:: በጦርም ጐኗን ወግቶ
ገደላት::
ከጥቂት ሰዓታት በሁዋላ ግን ልክ ከእንቅልፉ
እንደሚነቃ ሰው ተነስታ ጠራችው:: በጣም ደንግጦ
"አምላክሽ አምላኬ ነው" ሲል አመነ:: ከ30,000 በላይ
ሠራዊቱን ይዞም ተጠመቀ::
ቅድስት ኄራኒ በቀረ ሕይወቷ በስብከተ ወንጌል እስያን
አድርሳለች:: ጌታ አብርቶላት: እርሷም አብርታ: እልፍ
ፍሬን አፍርታ: በዚህች ቀን ዐርፋለች:: የሐዋርያትንም:
የሰማዕታትንም አክሊል ተቀዳጅታለች::
ይህቺ ቅድስት ወጣት መልክ ከደም ግባት: ምግባር
ከሃይማኖት: ስም ከመልካምነት የተባበረላት ሰማዕት
ናት:: #ኄራኒ ማለት "ሰላማዊት: የተወደደች" ማለት
ነው:: አንድም በጥሬው "ሰላምና ፍቅር" ማለት ነው::
ቅድስት ኄራኒ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን በታናሽ
እስያ የንጉሥ #ሉክያኖስ ልጅ ናት:: ከተወለደች ጀምሮ
ስለ ክርስትና ሰምታ አታውቅም:: ምክንያቱም አባቷ
ጣዖት አምላኪ ከመሆኑ ባለፈ ክርስቲያኖችን ይቀጣ ስለ
ነበር ነው::
ልጁን ማንም እንዳያገኛት ሲል ንጉሡ ለቅድስት ኄራኒ
ቤተ መንግስት ሠራላት:: ማንም እንዳይገባ በዙሪያው
12 አጥር አጠረበት:: ጣዖቶቹን እንድታጥን
አገልጋዮችንም ሾመላት::
ምናልባት አጥር ሰውን ሊከለክለው ይችላል::
#እግዚአብሔር ግን እግዚአብሔር ነውና ምንም
አይከለክለውም:: ጌታ ደግሞ ይህቺን ወጣት ለወንጌል
አገልግሎት ይፈልጋታል:: አንድ ቀን አባቷ: ልጁ ምሑር
እንድትሆንለት አለ የተባለ ሽማግሌ ፈላስፋ ቀጠረላት::
ጥበበ እግዚአብሔር ማለት ይሔ ነው:: አባቷ ይሕ
ሽማግሌ ማንን እንደሚያመልክ አልተረዳም:: አረጋዊው
እጅግ የተዋጣለት ክርስቲያን ነው:: ግን ማንም
አያውቅበትም:: አረጋዊው ቅድስት ኄራኒን ዝም ብሎ
ሊሰብካት አልወደደም::
መጀመሪያ በስነ ምግባር አነጻት:: ቀጥሎ ግን "ጌታ ሆይ! ጐዳናህን ምራት" እያለ ይጸልይላት ገባ:: ጌታችን ልመናውን ሰምቶታልና ቅድስቷ አንድ ቀን ግሩም ራዕይን
አየች::
እርሷ ለማዕድ ተቀምጣ ሳለ: የምሥራቅና የምዕራብ
መስኮቶቿም ተከፍተው ሳሉ: በምሥራቁ መስኮት ነጭ
ርግብ በአፏ የወይራ ዝንጣፊ (ቆጽለ ዘይት) ይዛ ገባችና
ማዕዷ ላይ አኑራው ሔደች:: እርሷን ተከትሎ ደግሞ
ንስር በአፉ አክሊል ይዞ ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ሔደ::
በ3ኛው ግን ቁራ: እባብ በአፉ ይዞ በምዕራቡ መስኮት
ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ወጣ:: ቅድስት ኄራኒ ያየችው
ራዕይ ቢጨንቃት ሽማግሌ መምሕሯን "ተርጉምልኝ"
አለችው::
እርሱም "ልጄ ሆይ! ለዘመናት ስጠብቀው የነበረ ምኞቴን ነው ጌታ ያሳየሽ:: የሕልምሽ ትርጉም እንዲህ ነው:- ነጭ ርግብ የመንፈስ ቀዱስ (የሃይማኖት) ምሳሌ
ናት:: የወይራ ዝንጣፊው ደግሞ #ማሕተመ_ጥምቀት
( #ሜሮን ) ነው:: ቁራ የክፉ ነገሥታት ምሳሌ ሲሆን
እባብ የመከራ ምሳሌ ነው::
ንስር ድል የመንሳት ምልክት ሲሆን አክሊል ደግሞ
የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ነው:: ልጄ! ክርስቲያን ሆነሽ
የሚደርስብሽን ሁሉ ጌታ አሳይቶሻል" ብሎ ተርጉሞላት
ተሰናበታት::
እርሷም ወደ ምሥራቅ ዙራ ጸለየች:- "የማላውቅህ
አምላክ ሆይ! ወደ እውነትህ ምራኝ" ስትል ለመነች::
በዚያች ሰዓት የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ አጽናናት::
የሚያጠምቃትም እንደሚልክላት ነገራት::
በዚያን ጊዜ አባቷ ገብቶ "ልጄ! ከመሣፍንቱ ላንዱ ልድርሽ ስለሆነ ምን ትያለሽ?" አላት:: "3 ቀን ስጠኝ" አለችውና ሰጣት:: ወደ ጣዖቶቹ ዕለቱኑ ወርዳ "ላግባ
ወይስ ይቅርብኝ?" አለቻቸው:: ከቀድሞም በወርቅ
የተለበጡ ድንጋዮች ናቸውና ዝም አሉ:: በሙሉ ቀጥቅጣ
ሰባብራቸው ተመለሰች::
በዘመኑ #ቅዱሳን_ሐዋርያት (በተለይ እነ
#ቅዱስ_ዻውሎስ ) በሕይወተ ሥጋ ነበሩና ከቅዱስ
ዻውሎስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቤቷ እንደ ተዘጋ ገባ::
ክርስትናን ከጥንቱ እስከ ተፍጻሜቱ አስተምሮ አጠመቃት::
በ3ኛው ቀን አባቷ "ምን መከርሽ?" ቢላት "የእኔ ምክር
#መርዓተ_ክርስቶስ (ሰማያዊ ሙሽራ) መሆን ነው"
አለችው:: አባቷ ደነገጠ:: እጅግ ስለ ተናደደ ወደ
አደባባይ አውጥቶ: አስሮ መሬት ላይ ጣላትና በመቶ
የሚቆጠሩ ፈረሶች እንዲረግጧት አደረገ::
በወቅቱ ሰው የሚጠብቀው የአካሏን ቁርጥራጭ ነበር::
ነገር ግን ጌታ ከእርሷ ጋር ነበርና ልብሷ እንኩዋ ጭቃ
አልነካም:: አባቷ ንጉሥ ሉክያኖስና ሠራዊቱ ያዩትን
ማመን አልቻሉም:: ሁሉም ድምጻቸውን ከፍ አድርገው
"ከክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" አሉ:: ቅድስት
ኄራኒ ምንም ሳትናገር ይህንን ሁሉ ሰው ማረከች::
ወዲያውም ንጉሡ መልእክተኛ ልኮ: የቅዱስ ዻውሎስ
ደቀ መዝሙርን አስጠርቶ: ከነ ቤተሰቦቹ ተጠመቀ::
የዚህን ዓለም ክብር ንቆም ንግሥናውን ተወ:: የጸሎት
ሰውም ሆነ:: የቅድስት ኄራኒ ተጋድሎ ግን ቀጠለ::
በአካባቢው የነበረ ንጉሥ መጥቶ የአባቷን መንግስት
ቀማ:: እርሷንም እጅግ አሰቃያት:: እርሱ አልፎ
አርማንዮስ የሚባል ንጉሥ እንዲሁ አሰቃያት:: እርሱም
አለፈ:: ከእርሱ ቀጥሎ የመጣው ንጉሥ ብዙ
መከራዎችን በእርሷ ላይ አደረሰ:: በጦርም ጐኗን ወግቶ
ገደላት::
ከጥቂት ሰዓታት በሁዋላ ግን ልክ ከእንቅልፉ
እንደሚነቃ ሰው ተነስታ ጠራችው:: በጣም ደንግጦ
"አምላክሽ አምላኬ ነው" ሲል አመነ:: ከ30,000 በላይ
ሠራዊቱን ይዞም ተጠመቀ::
ቅድስት ኄራኒ በቀረ ሕይወቷ በስብከተ ወንጌል እስያን
አድርሳለች:: ጌታ አብርቶላት: እርሷም አብርታ: እልፍ
ፍሬን አፍርታ: በዚህች ቀን ዐርፋለች:: የሐዋርያትንም:
የሰማዕታትንም አክሊል ተቀዳጅታለች::
♥ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት ♥
በሕገ ወንጌል (ክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ
ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው:: ቅዱሱ
በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት
ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር:: ይህስ እንደ
ምን ነው ቢሉ:-
✝የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም
ይባላሉ:: (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ
ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ
እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ:: የወቅቱ ታላቅ
መምሕር ገማልያል ይባል ነበር:: ይህ ሰው በሐዋርያት
ሥራ ምዕራፍ 5:33 ላይ ተጠቅሷል::
✝በትውፊት ትምሕርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው
በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን: ዻውሎስን: ናትናኤልን:
ኒቆዲሞስን . . .) አስተምሯል:: በጌታችን መዋዕለ
ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ
እየቀረበ ይጨዋወት ነበር:: በፍጻሜውም አምኗል::
✝ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ እስጢፋኖስ
ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ: ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ
ወጣ:: ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ
ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና
በተስፋ ይጠባበቅ ነበር::
✝በወቅቱ ደግሞ #መጥምቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ የንስሃ
ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ
እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ:: ከእግዚአብሔር ሆኖ
ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ለ6
ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ::
✝ለ6 ወራት ከቅዱስ #ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በሁዋላ
ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ተጠመቀ::
በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ
እስጢፋኖስ መምሕሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው
ጠየቀው::
✝"ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው" በሚል
ላከው:: ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ: እጅ ነስቶ ተማረ::
(ሉቃ. 7:18) በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ::
ጌታም ከ72ቱ #አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት
ላከው:: አጋንንትም ተገዙለት:: (ሉቃ. 10:17)
✝ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን #መድኃኔ_ዓለም ከዋለበት
እየዋለ: ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ:: ምሥጢር
አስተረጐመ:: ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በሁዋላ
ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኩዋል::
✝በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ #ሐዋርያት
ቅስናን (ዽዽስናን) ተሹሟል:: በበዓለ ሃምሳም
#መንፈስ_ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከ72ቱ አርድእት የእርሱን
ያህል ልሳን የበዛለት: ምሥጢርም የተገለጠለት የለም::
በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ::
✝በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት
ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ 7
#ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: አልፎም የ6ቱ
ዲያቆናት አለቃ እና የ8ሺው ማሕበር መሪ (አስተዳዳሪ)
ሆኗል::
✝8ሺ ሰውን ከአጋንንት ፈተና መጠበቅ ምን ያህል ከባድ
እንደ ሆነ ለማወቅ አባቶቻችንን መጠየቅ ነው:: አንድን
ሰው ተቆጣጥሮ ለድኅነት ማብቃት እንኩዋ እጅግ ፈተና
ነው:: መጽሐፍ እንደሚል ግን 'መንፈስ ቅዱስ የሞላበት:
ማሕደረ እግዚአብሔር' ነውና ለእርሱ ተቻለው:: (ሐዋ.
6:5)
✝አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ 'ሊቀ ዲያቆናት'
ሲባል እንደ ዘመኑ ይመስለን ይሆናል:: እርሱ
በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው:: ዲቁናው ለእርሱ 'በራት
ላይ ዳረጐት' ነው እንጂ እንዲሁ
ዲያቆን ብቻ አይደለም::
✝ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በሁዋላ ለ 1 ዓመት
ያህል 8ሺውን ማሕበር እየመራ: ወንጌልን እየሰበከ
ቢጋደል #ኦሪት 'እጠፋ እጠፋ': #ወንጌል ደግሞ 'እሰፋ
እሰፋ' አለች:: በዚህ ጊዜ 'ክርስትናን ለማጥፋት
መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው' ብለው
አይሁድ በማመናቸው ሊገልድሉት አስበውም አልቀሩ
ገደሉት::
✝እርሱ ግን ፊቱ እንደ #እግዚአብሔር መልአክ እያበራ
ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው:: በመጨረሻውም ስለ
እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት:: ደቀ
መዛሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት::
♥ ፍልሠት ♥
ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመታት በሁዋላ
በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበር:: ስሙም
#ሉክያኖስ ይባል ነበር:: በተደጋጋሚ በራዕይ ቅዱሱ
እየተገለጠ "ሥጋየን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ
ለዻዻሱ ነገረው:: ዻዻሱም ደስ ብሎት ካህናትና
ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አጸደ # ገማልያል (የመምሕሩ
ርስት ነው) ሔደ::
✝ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ::
መላእክት ሲያጥኑ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ዝማሬ
መላእክትም ተሰማ:: ሕዝቡና ዻዻሱም በቅዱስ
እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው: በታላቅ ዝማሬና በሐሴት
ዐጽሙን ከዚያ አውጥተው: በጽርሐ #ጽዮን
(በተቀደሰችው ቤት) አኖሩት::
✝ #እለ_እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተ ክርስቲያን
አንጾለት ወደዚያ አገቡት:: ከ5 ዓመታት በሁዋላም እለ
እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጐን ስለ
ፍቅሩ አኖሩት:: ሚስቱ ወደ ሃገሯ #ቁስጥንጥንያ
ስትመለስ የባሏን ሥጋ መስሏት የቅዱስ እስጢፋኖስን
ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው::
✝መንገድ ላይ ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው
ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው:: እጅግ ደስ አላት:
አምላክ ለዚህ አድሏታልና:: እርሷም ወስዳ ለታላቁ
ንጉሥ #ቅዱስ_ቆስጠንጢኖስ አስረከበች:: በከተማውም
ታላቅ ሐሴት ተደረገ::
✝ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም
በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች::
በዚያም ላይ ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ታንጾለታል:: ቅዱስ
እስጢፋኖስ ሲመቱ ጥቅምት 17: ዕረፍቱ ጥር 1:
ፍልሠቱ ደግሞ መስከረም 15 ቀን ነው::
በሕገ ወንጌል (ክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ
ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው:: ቅዱሱ
በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት
ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር:: ይህስ እንደ
ምን ነው ቢሉ:-
✝የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም
ይባላሉ:: (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ
ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ
እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ:: የወቅቱ ታላቅ
መምሕር ገማልያል ይባል ነበር:: ይህ ሰው በሐዋርያት
ሥራ ምዕራፍ 5:33 ላይ ተጠቅሷል::
✝በትውፊት ትምሕርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው
በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን: ዻውሎስን: ናትናኤልን:
ኒቆዲሞስን . . .) አስተምሯል:: በጌታችን መዋዕለ
ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ
እየቀረበ ይጨዋወት ነበር:: በፍጻሜውም አምኗል::
✝ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ እስጢፋኖስ
ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ: ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ
ወጣ:: ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ
ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና
በተስፋ ይጠባበቅ ነበር::
✝በወቅቱ ደግሞ #መጥምቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ የንስሃ
ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ
እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ:: ከእግዚአብሔር ሆኖ
ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ለ6
ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ::
✝ለ6 ወራት ከቅዱስ #ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በሁዋላ
ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ተጠመቀ::
በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ
እስጢፋኖስ መምሕሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው
ጠየቀው::
✝"ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው" በሚል
ላከው:: ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ: እጅ ነስቶ ተማረ::
(ሉቃ. 7:18) በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ::
ጌታም ከ72ቱ #አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት
ላከው:: አጋንንትም ተገዙለት:: (ሉቃ. 10:17)
✝ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን #መድኃኔ_ዓለም ከዋለበት
እየዋለ: ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ:: ምሥጢር
አስተረጐመ:: ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በሁዋላ
ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኩዋል::
✝በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ #ሐዋርያት
ቅስናን (ዽዽስናን) ተሹሟል:: በበዓለ ሃምሳም
#መንፈስ_ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከ72ቱ አርድእት የእርሱን
ያህል ልሳን የበዛለት: ምሥጢርም የተገለጠለት የለም::
በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ::
✝በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት
ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ 7
#ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: አልፎም የ6ቱ
ዲያቆናት አለቃ እና የ8ሺው ማሕበር መሪ (አስተዳዳሪ)
ሆኗል::
✝8ሺ ሰውን ከአጋንንት ፈተና መጠበቅ ምን ያህል ከባድ
እንደ ሆነ ለማወቅ አባቶቻችንን መጠየቅ ነው:: አንድን
ሰው ተቆጣጥሮ ለድኅነት ማብቃት እንኩዋ እጅግ ፈተና
ነው:: መጽሐፍ እንደሚል ግን 'መንፈስ ቅዱስ የሞላበት:
ማሕደረ እግዚአብሔር' ነውና ለእርሱ ተቻለው:: (ሐዋ.
6:5)
✝አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ 'ሊቀ ዲያቆናት'
ሲባል እንደ ዘመኑ ይመስለን ይሆናል:: እርሱ
በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው:: ዲቁናው ለእርሱ 'በራት
ላይ ዳረጐት' ነው እንጂ እንዲሁ
ዲያቆን ብቻ አይደለም::
✝ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በሁዋላ ለ 1 ዓመት
ያህል 8ሺውን ማሕበር እየመራ: ወንጌልን እየሰበከ
ቢጋደል #ኦሪት 'እጠፋ እጠፋ': #ወንጌል ደግሞ 'እሰፋ
እሰፋ' አለች:: በዚህ ጊዜ 'ክርስትናን ለማጥፋት
መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው' ብለው
አይሁድ በማመናቸው ሊገልድሉት አስበውም አልቀሩ
ገደሉት::
✝እርሱ ግን ፊቱ እንደ #እግዚአብሔር መልአክ እያበራ
ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው:: በመጨረሻውም ስለ
እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት:: ደቀ
መዛሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት::
♥ ፍልሠት ♥
ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመታት በሁዋላ
በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበር:: ስሙም
#ሉክያኖስ ይባል ነበር:: በተደጋጋሚ በራዕይ ቅዱሱ
እየተገለጠ "ሥጋየን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ
ለዻዻሱ ነገረው:: ዻዻሱም ደስ ብሎት ካህናትና
ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አጸደ # ገማልያል (የመምሕሩ
ርስት ነው) ሔደ::
✝ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ::
መላእክት ሲያጥኑ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ዝማሬ
መላእክትም ተሰማ:: ሕዝቡና ዻዻሱም በቅዱስ
እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው: በታላቅ ዝማሬና በሐሴት
ዐጽሙን ከዚያ አውጥተው: በጽርሐ #ጽዮን
(በተቀደሰችው ቤት) አኖሩት::
✝ #እለ_እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተ ክርስቲያን
አንጾለት ወደዚያ አገቡት:: ከ5 ዓመታት በሁዋላም እለ
እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጐን ስለ
ፍቅሩ አኖሩት:: ሚስቱ ወደ ሃገሯ #ቁስጥንጥንያ
ስትመለስ የባሏን ሥጋ መስሏት የቅዱስ እስጢፋኖስን
ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው::
✝መንገድ ላይ ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው
ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው:: እጅግ ደስ አላት:
አምላክ ለዚህ አድሏታልና:: እርሷም ወስዳ ለታላቁ
ንጉሥ #ቅዱስ_ቆስጠንጢኖስ አስረከበች:: በከተማውም
ታላቅ ሐሴት ተደረገ::
✝ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም
በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች::
በዚያም ላይ ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ታንጾለታል:: ቅዱስ
እስጢፋኖስ ሲመቱ ጥቅምት 17: ዕረፍቱ ጥር 1:
ፍልሠቱ ደግሞ መስከረም 15 ቀን ነው::