ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት
በሕገ ወንጌል (ክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ
ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው:: ቅዱሱ
በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት
ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር:: ይህስ እንደ
ምን ነው ቢሉ:-
የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም
ይባላሉ:: (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ
ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ
እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ:: የወቅቱ ታላቅ
መምሕር ገማልያል ይባል ነበር:: ይህ ሰው በሐዋርያት
ሥራ ምዕራፍ 5:33 ላይ ተጠቅሷል::
በትውፊት ትምሕርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው
በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን: ዻውሎስን: ናትናኤልን:
ኒቆዲሞስን . . .) አስተምሯል:: በጌታችን መዋዕለ
ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ
እየቀረበ ይጨዋወት ነበር:: በፍጻሜውም አምኗል::
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ እስጢፋኖስ
ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ: ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ
ወጣ:: ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ
ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና
በተስፋ ይጠባበቅ ነበር::
በወቅቱ ደግሞ #መጥምቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ የንስሃ
ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ
እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ:: ከእግዚአብሔር ሆኖ
ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ለ6
ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ::
ለ6 ወራት ከቅዱስ #ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በሁዋላ
ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ተጠመቀ::
በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ
እስጢፋኖስ መምሕሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው
ጠየቀው::
"ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው" በሚል
ላከው:: ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ: እጅ ነስቶ ተማረ::
(ሉቃ. 7:18) በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ::
ጌታም ከ72ቱ #አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት
ላከው:: አጋንንትም ተገዙለት:: (ሉቃ. 10:17)
ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን #መድኃኔ_ዓለም ከዋለበት
እየዋለ: ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ:: ምሥጢር
አስተረጐመ:: ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በሁዋላ
ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኩዋል::
በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ #ሐዋርያት
ቅስናን (ዽዽስናን) ተሹሟል:: በበዓለ ሃምሳም
#መንፈስ_ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከ72ቱ አርድእት የእርሱን
ያህል ልሳን የበዛለት: ምሥጢርም የተገለጠለት የለም::
በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ::
በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት
ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ 7
#ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: አልፎም የ6ቱ
ዲያቆናት አለቃ እና የ8ሺው ማሕበር መሪ (አስተዳዳሪ)
ሆኗል::
8ሺ ሰውን ከአጋንንት ፈተና መጠበቅ ምን ያህል ከባድ
እንደ ሆነ ለማወቅ አባቶቻችንን መጠየቅ ነው:: አንድን
ሰው ተቆጣጥሮ ለድኅነት ማብቃት እንኩዋ እጅግ ፈተና
ነው:: መጽሐፍ እንደሚል ግን 'መንፈስ ቅዱስ የሞላበት:
ማሕደረ እግዚአብሔር' ነውና ለእርሱ ተቻለው:: (ሐዋ.
6:5)
አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ 'ሊቀ ዲያቆናት'
ሲባል እንደ ዘመኑ ይመስለን ይሆናል:: እርሱ
በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው:: ዲቁናው ለእርሱ 'በራት
ላይ ዳረጐት' ነው እንጂ እንዲሁ
ዲያቆን ብቻ አይደለም::
ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በሁዋላ ለ 1 ዓመት
ያህል 8ሺውን ማሕበር እየመራ: ወንጌልን እየሰበከ
ቢጋደል #ኦሪት 'እጠፋ እጠፋ': #ወንጌል ደግሞ 'እሰፋ
እሰፋ' አለች:: በዚህ ጊዜ 'ክርስትናን ለማጥፋት
መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው' ብለው
አይሁድ በማመናቸው ሊገልድሉት አስበውም አልቀሩ
ገደሉት::
እርሱ ግን ፊቱ እንደ #እግዚአብሔር መልአክ እያበራ
ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው:: በመጨረሻውም ስለ
እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት:: ደቀ
መዛሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት::
ፍልሠት
ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመታት በሁዋላ
በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበር:: ስሙም
#ሉክያኖስ ይባል ነበር:: በተደጋጋሚ በራዕይ ቅዱሱ
እየተገለጠ "ሥጋየን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ
ለዻዻሱ ነገረው:: ዻዻሱም ደስ ብሎት ካህናትና
ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አጸደ # ገማልያል (የመምሕሩ
ርስት ነው) ሔደ::
ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ::
መላእክት ሲያጥኑ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ዝማሬ
መላእክትም ተሰማ:: ሕዝቡና ዻዻሱም በቅዱስ
እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው: በታላቅ ዝማሬና በሐሴት
ዐጽሙን ከዚያ አውጥተው: በጽርሐ #ጽዮን
(በተቀደሰችው ቤት) አኖሩት::
#እለ_እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተ ክርስቲያን
አንጾለት ወደዚያ አገቡት:: ከ5 ዓመታት በሁዋላም እለ
እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጐን ስለ
ፍቅሩ አኖሩት:: ሚስቱ ወደ ሃገሯ #ቁስጥንጥንያ
ስትመለስ የባሏን ሥጋ መስሏት የቅዱስ እስጢፋኖስን
ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው::
መንገድ ላይ ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው
ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው:: እጅግ ደስ አላት:
አምላክ ለዚህ አድሏታልና:: እርሷም ወስዳ ለታላቁ
ንጉሥ #ቅዱስ_ቆስጠንጢኖስ አስረከበች:: በከተማውም
ታላቅ ሐሴት ተደረገ::
ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም
በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች::
በዚያም ላይ ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ታንጾለታል:: ቅዱስ
እስጢፋኖስ ሲመቱ ጥቅምት 17: ዕረፍቱ ጥር 1:
ፍልሠቱ ደግሞ መስከረም 15 ቀን ነው::
💚💛 አቡነ ኪሮስ ጻድቅ 💛❤️
የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል::
#አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው:: ተወልደው ባደጉባት ሃገር #ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው (ታላቁ #ቴዎዶስዮስ) በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ ( #ገዳመ_አስቄጥስ) መጡ::

እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ #ገብረ_ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ #ቅዱስ_ዳዊት:: አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ #አቡነ_በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል::

ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል:: ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል::
አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ::

ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ30 ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ #እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር::

ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ57 ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ (ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና) በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ::

#ቅዱስ_ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ:: ሥጋቸውን #አባ_ባውማ ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም::
From d/n yordanos abebe
@senkesar @senkesar