ውበትን መገዘት
ከፊቷ ፀዳል ላይ ጥላ ዐይኑን ጥሎ
እድሜ ጅምር ማድያት ከመልኳ ላይ ስሎ
ዘመኗ በክንዷ ደርሶ እያሸለበ
ጊዜ ደም ግባቷን ገልጦ እያነበበ ::
ውበቷን ልትገዝት ትነሳለች ፎቶ . . .
የሳር መንገድ ወገብ ይቀራል በፎቶ
ተውርጋራጊ ዳሌ ይታተማል ጎልቶ ::
ፎቶ አንሺው ጨነቀው ፣
ያልተኖረ ዘመን የሚል የአኳሏን ቃል
ከምን ላይ ያስቀምጠው ::
©መቅደስ ሞጎስ
https://tttttt.me/GitemSitem
#መቅደስ_ሞገስ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #poetrylovers #artinaddis
ከፊቷ ፀዳል ላይ ጥላ ዐይኑን ጥሎ
እድሜ ጅምር ማድያት ከመልኳ ላይ ስሎ
ዘመኗ በክንዷ ደርሶ እያሸለበ
ጊዜ ደም ግባቷን ገልጦ እያነበበ ::
ውበቷን ልትገዝት ትነሳለች ፎቶ . . .
የሳር መንገድ ወገብ ይቀራል በፎቶ
ተውርጋራጊ ዳሌ ይታተማል ጎልቶ ::
ፎቶ አንሺው ጨነቀው ፣
ያልተኖረ ዘመን የሚል የአኳሏን ቃል
ከምን ላይ ያስቀምጠው ::
©መቅደስ ሞጎስ
https://tttttt.me/GitemSitem
#መቅደስ_ሞገስ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #poetry #poetrylovers #artinaddis
Telegram
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ።
ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን።
We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን።
We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
አበባ ናት
ለጋ ቀንበጥ
በአረንጓዴ ዘንግነቷ
ከሩቅ የምትታይ
ውሃን ነሷት የምራቃቸውን ጠብታ እንኳ ነፈጓት !
ጠደቀች
አፈር ነሷት የምትደላደለበት
ጠደቀች
በውበቷ አሰማመረቻቸው
በፍቅሯ አቅበጠበጠቻቸው
እስትንፋሷን እፍፍ ብላ ህይወት ዘራች
የመጣችው በምክንያት ነው
ልታኖር
ያላኖሯትን
ልታደላድል
የጎረበጧትን
ፍቅር ሆነችላቸው
ህይወት ሆነችላቸው
ውበት ሆነችላችው
ሲሆንላት ፈክታ ፍንድቅድቅ ብላ
ደሞ እየጠወለገች እየሞተችም
ጠደቀች
እየረገፈች ጠደቀች
ሞቷም ውበት ነው::
ትገርመኛለች !!!
እውነቷን ያሠረችበት ዘመኗ ግን ብዙም አይደል
አጃኢብ እላለሁ ሁሌም ሳስባት !
©መቅደስ ሞገስ
#Mekdes_Moges #መቅደስ_ሞገስ #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers
ለጋ ቀንበጥ
በአረንጓዴ ዘንግነቷ
ከሩቅ የምትታይ
ውሃን ነሷት የምራቃቸውን ጠብታ እንኳ ነፈጓት !
ጠደቀች
አፈር ነሷት የምትደላደለበት
ጠደቀች
በውበቷ አሰማመረቻቸው
በፍቅሯ አቅበጠበጠቻቸው
እስትንፋሷን እፍፍ ብላ ህይወት ዘራች
የመጣችው በምክንያት ነው
ልታኖር
ያላኖሯትን
ልታደላድል
የጎረበጧትን
ፍቅር ሆነችላቸው
ህይወት ሆነችላቸው
ውበት ሆነችላችው
ሲሆንላት ፈክታ ፍንድቅድቅ ብላ
ደሞ እየጠወለገች እየሞተችም
ጠደቀች
እየረገፈች ጠደቀች
ሞቷም ውበት ነው::
ትገርመኛለች !!!
እውነቷን ያሠረችበት ዘመኗ ግን ብዙም አይደል
አጃኢብ እላለሁ ሁሌም ሳስባት !
©መቅደስ ሞገስ
#Mekdes_Moges #መቅደስ_ሞገስ #ዲበኩሉ_ጌታ #የምድር_ዘላለም #ግጥምሲጥም3 #ግጥማዊቅዳሜ #artinaddis #poetry #poetrylovers