አንሶሻል ዘለዓለሜ
አካል ሥጋ ጠቦሻል
ረቂቅ ነፍስ በግዘፍሽ
ከአንቺ በልጦ ምን ይዘሻል?
(ጥልመት ድ'ቅድቅ
ብርሃን ድ'ብቅ
እ'ርስት
ዝን'ግት
.
ሕዋ ዐይንሽ ላይ
ንጋቴን ልታጋፍሪበት
ያንቺን ጀንበር መሸበት....
ዝም
ዝም
ዝም
ጭልም!)
አንቺን አልፌ ሁሉን
ሁሉን ሳልፈው ተመለስሁኝ
መኖሪያሽ ነኝ የምለው
ለካስ ነዋሪሽ ነበርሁኝ
(አድማስ እኔ
ብርሃኔ እ'ጥፍ
ጥልመት አንቺ ጥ'ልፍ
ብ'ርር
ክ'ንፍ!
አልነገሩኝ አልተረዳሁ
ስበት ብርሃንን እንዲያሸንፍ!
ሳብሺኝ! ል'ጥፍ!
ቦግ...እልም
ዳግም ዝም!)
ዘለዓለሜ አንሶሽ
መሆኔ ጠቦሽ
ከእኔ ገዝፈሽ
እኔን ያዝሺኝ።
ጥልመትሽ ሁሉን ቢሞላ
አድማስ ሙሉ አበራሺኝ።
..ተንጸባረቅሁ
..ነገሥሁብሽ!
(የማይሆንን አደረግነው
በቅጽበት ሁሌን ኖርነው
...ከዕለታት ጠይም
መልከ መልካሙ ላይ
ሁሉን የሚያህልን
አንድ ነጥብ ሰማይ
አቅፈነው አደርን
ነቅተን ሕልሞች ሆንን
አንቺን አልፌ ዓለሙን
ዓለሙን ሳልፍ ተመለስሁ
አንቺን ሳልፍ - አንቺ ሁሉን
ቀኔ ሲያልፈኝ
አንቺ ሁሌ - አንቺ አሁን
ሆንሁሽና ሆንሁት ሁሉን!
ከዕለታት አንቺ ዕለት
ሰማዩን አቀፍሁት
ተሸከምሁ ሁለንታ
ደቃቃ አሁን ላይ
ዘለዓለም ተረታ...)
አንሶሻል ዘለዓለሜ
(በማን ዐይን ተመዝኖ)
ጠቦሻል ሥጋ አካሌ
(በማን አንጻር ተነጻጽሮ)
የመውደዴን ልኬት
ከመዘንሽው በእነሱ አቅም
ከአሁን ሌላ አልወድሽም
(በእነሱ ዘለዓለም
አሁን የለም!)
ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #MarkOs #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays
አካል ሥጋ ጠቦሻል
ረቂቅ ነፍስ በግዘፍሽ
ከአንቺ በልጦ ምን ይዘሻል?
(ጥልመት ድ'ቅድቅ
ብርሃን ድ'ብቅ
እ'ርስት
ዝን'ግት
.
ሕዋ ዐይንሽ ላይ
ንጋቴን ልታጋፍሪበት
ያንቺን ጀንበር መሸበት....
ዝም
ዝም
ዝም
ጭልም!)
አንቺን አልፌ ሁሉን
ሁሉን ሳልፈው ተመለስሁኝ
መኖሪያሽ ነኝ የምለው
ለካስ ነዋሪሽ ነበርሁኝ
(አድማስ እኔ
ብርሃኔ እ'ጥፍ
ጥልመት አንቺ ጥ'ልፍ
ብ'ርር
ክ'ንፍ!
አልነገሩኝ አልተረዳሁ
ስበት ብርሃንን እንዲያሸንፍ!
ሳብሺኝ! ል'ጥፍ!
ቦግ...እልም
ዳግም ዝም!)
ዘለዓለሜ አንሶሽ
መሆኔ ጠቦሽ
ከእኔ ገዝፈሽ
እኔን ያዝሺኝ።
ጥልመትሽ ሁሉን ቢሞላ
አድማስ ሙሉ አበራሺኝ።
..ተንጸባረቅሁ
..ነገሥሁብሽ!
(የማይሆንን አደረግነው
በቅጽበት ሁሌን ኖርነው
...ከዕለታት ጠይም
መልከ መልካሙ ላይ
ሁሉን የሚያህልን
አንድ ነጥብ ሰማይ
አቅፈነው አደርን
ነቅተን ሕልሞች ሆንን
አንቺን አልፌ ዓለሙን
ዓለሙን ሳልፍ ተመለስሁ
አንቺን ሳልፍ - አንቺ ሁሉን
ቀኔ ሲያልፈኝ
አንቺ ሁሌ - አንቺ አሁን
ሆንሁሽና ሆንሁት ሁሉን!
ከዕለታት አንቺ ዕለት
ሰማዩን አቀፍሁት
ተሸከምሁ ሁለንታ
ደቃቃ አሁን ላይ
ዘለዓለም ተረታ...)
አንሶሻል ዘለዓለሜ
(በማን ዐይን ተመዝኖ)
ጠቦሻል ሥጋ አካሌ
(በማን አንጻር ተነጻጽሮ)
የመውደዴን ልኬት
ከመዘንሽው በእነሱ አቅም
ከአሁን ሌላ አልወድሽም
(በእነሱ ዘለዓለም
አሁን የለም!)
ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል
#ማርቆስ_ዘመንበረ_ልዑል #MarkOs #ግጥምሲጥም #gitemsitem #ግጥማዊቅዳሜ #poeticsaturdays