የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.69K subscribers
9.05K photos
131 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
#የመጽሐፍ_ቅዱስ_ሠራዊት_ዓለም_አቀፍ_ቤተክርስቲያን_በሰሜን_ኢትዮጵያ_በትግራይ_አክሱም_ከተማ በከተማው ውስጥ ለሚገኙት ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰባቸው 1950 ለሚሆኑት ቤተሰቦች (አባወራዎች) የእህል ድጋፍ አደረገች፡፡
በዚህ የድጋፍ አገልግሎት ላይ የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች፣ የሥራ ኃላፊዎች እና የሚዲያ ባለሙያዎችን ያካተተ ቡድን ወደ ስፍራው በመላክ ድጋፋን አድርጋለች። በዚሁ እለት ከከተማው አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ጋር ሰፊ የምክክር ጊዜ የተደረገ ሲሆን ከውይይት በኃላም የተጀመረው የእገዛው አገልግሎት እንደሚቀጥል የቤተክርስቲያኒቱ ዋና መሪ ሐዋርያው ቶማሰ ምትኩ ለከተማው አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ገልጸዋል። በመጨረሻም የአክሱም ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የአደዋ ከተማ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ስላደረጉት ቀና ትብብርና ስላሳዩት ፍቅር ከልብ ልናመሰግናችሁ እንወዳለን ስትል ቤተክርስቲያኒቱ አስታዉቃለች።
የመጽሐፍ ቅዱስ ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://youtu.be/xpENxBMAfr8
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!