በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ ክልል የባሌ ጎባ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።
"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የቤተ እምነቱ ም/"ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው፣ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ላይም በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩትና የአሁኑ የኢ/ወ/አ/ክ/ህ ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ጻዲቁ አብዶ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል፡፡ እንዲሁም ከመጋቢ ጻዲቁ ጋር ከጅማሬው ጀምሮ አብሮ ወንጌልን የሰበኩትና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡
የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡ በዓል ላይ የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ ለታላቅ ደስታና መጽናናት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ
"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የቤተ እምነቱ ም/"ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው፣ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ላይም በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩትና የአሁኑ የኢ/ወ/አ/ክ/ህ ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ጻዲቁ አብዶ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል፡፡ እንዲሁም ከመጋቢ ጻዲቁ ጋር ከጅማሬው ጀምሮ አብሮ ወንጌልን የሰበኩትና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡
የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡ በዓል ላይ የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ ለታላቅ ደስታና መጽናናት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ
በዓለም አቀፍ የሚሽን ጉባኤ ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በፕሬዚደንቷ መወከሏን አስታወቀች።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጨመሮ የተለያዩ አለም አቀፍ አብያተክርስቲያናት በመስራች አባልነት በሚመሩት አለም አቀፍ የሚሽን ጉባኤ (International Mission Association/#IMA) አዘጋጅነት በማዕከላዊ አሜሪካ ሁንዱራስ ዋና ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ስብሰባ ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በፕሬዚዳንቷ ተወክላለች።
በያዝነው ሳምንት በጀመረውና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ የቤተክርስቲያን መሪዎች በወንጌል አገልግሎት ዙሪያ እየመከሩ በሚገኙበት ስብሰባ ላይ የታደሙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በጉባኤው የቤተክርስቲያኒቱን የወንጌል እንቅስቃሴ ልምድ ከማካፈል በተጨማሪ በሌሎች አለማት ያለውን የወንጌል ተልዕኮ አካሄድ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ጋር የሚለዋወጡ ይሆናል።
ይህ ጉባኤ ለቤተክርስቲያኒቱ ልምድ ከመለዋወጥ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚኖራት የወንጌል ተጽዕኖ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ይታስባል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የማህበራዊ ሚድያ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጨመሮ የተለያዩ አለም አቀፍ አብያተክርስቲያናት በመስራች አባልነት በሚመሩት አለም አቀፍ የሚሽን ጉባኤ (International Mission Association/#IMA) አዘጋጅነት በማዕከላዊ አሜሪካ ሁንዱራስ ዋና ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ስብሰባ ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በፕሬዚዳንቷ ተወክላለች።
በያዝነው ሳምንት በጀመረውና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ የቤተክርስቲያን መሪዎች በወንጌል አገልግሎት ዙሪያ እየመከሩ በሚገኙበት ስብሰባ ላይ የታደሙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በጉባኤው የቤተክርስቲያኒቱን የወንጌል እንቅስቃሴ ልምድ ከማካፈል በተጨማሪ በሌሎች አለማት ያለውን የወንጌል ተልዕኮ አካሄድ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ጋር የሚለዋወጡ ይሆናል።
ይህ ጉባኤ ለቤተክርስቲያኒቱ ልምድ ከመለዋወጥ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚኖራት የወንጌል ተጽዕኖ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ይታስባል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የማህበራዊ ሚድያ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤5👍3
በናይጄሪያ በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ በተፈጸመ ጥቃት አማክኝነት 5 ክርስቲያኖች መገደላቸው ተገለጸ።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች የሚገኙባት ናይጂሪያ የክርስቲያኖች ግድያ የተመለደ እየሆነባት መጥቷል። አርብ ቀን በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ በነበሩ አማኞች ላይ በደረሰ ጥቃት አማካኝነት 5 ክርስቲያኖች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን 3 ሰዎች ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ በሰሜን ምስራቃዊዋ የናይጄሪያ ግዛት ካዱና ወደ 110 የሚጠጉ ክርስቲያኖች ታግተዋል።
በካጁር አውራጃ ቪክቶር ዊኒንግ ኦል የተሰኘች ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላይ በፉላኒ ታጣቂዎች በደረሰ ጥቃት አማካኝነት ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና በጸሎት ላይ የነበሩ ክርስቲያኖች ላይ ጥቃት የተፈጸመው።በካጁሪ አውራጃ በተፈጸመ ጥቃት ምክንያት ከታገቱት ሰዎች መካከል የማህበረሰብ መሪዎች የሚገኙበት ሲሆን እገታው የሚደረገውም ብዙ የወንጌል አማኞች በሚገኙባቸው መንደሮች ላይ ነው።
በናይጄሪያ እና በሳሄል ቀጠና በሚሊይን የሚቆጠሩ እና የእስልምና እምነት የሚከተሉ ፉላኒዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛዎቹ ፉላኒዎች ጽንፈኛ አቋምን የሚያራምዱ አይደሉም፡ ሆኖም እንዳንድ የፉላኒ ጎሳዎች ጽንፈኛ የሆነ ሐይማኖተኝነትን የሚያራምዱ መሆናቸውን ዓለም አቀፍ የክርስቲያኖች መብት ተሟጋቾች ይጠቅሳሉ።
በናይጄሪያ የሚገኙ ክርስቲያን መሪዎች በሀገሪቱ ማዕከላዊ ክፍል ላይ ክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ጥቃት የክርስቲያኖችን መሬትን መንጠቅን ያለመ ነው በማለት ይሞግታሉ፤ ለዚህም እንደ ምክንያት ሚነሳው የፉላኒ ታጣቂዎች የያዙት ቦታ በበረሀማነት አማካኝነት ለከብቶቻቸው የማይመች እየሆነ መምጣቱ ነው።
በዚህ እና ተያያዥ ምክንያቶችም በዓለማችን ላይ በዓመት ክርስቲያን በመሆናቸው ምክንያት ከሚገደሉ ሰዎች 69 በመቶ የሚሆኑት ሕይወታቸው የሚያልፈው በናይጄሪያ ነው።
በደቡባዊ ናይጄሪያም ለክርስቲያኖች አስጊ የሆኑ ጽንፈኛ ቡድኖች ብቅ ማለት መጀመራቸውን ተከትሎ በሰሜናዊ ናይጂሪያ የሚገኙ ክርስቲያኖች እያስተናገዱ ያሉት ጥቃት በደቡብ ናይጄርያ ላሉትም ስጋትን መጫሩ አልቀርም።
መረጃውን ከክርስቲያን ቱዴይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
በሚሊየን የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች የሚገኙባት ናይጂሪያ የክርስቲያኖች ግድያ የተመለደ እየሆነባት መጥቷል። አርብ ቀን በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ በነበሩ አማኞች ላይ በደረሰ ጥቃት አማካኝነት 5 ክርስቲያኖች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን 3 ሰዎች ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ በሰሜን ምስራቃዊዋ የናይጄሪያ ግዛት ካዱና ወደ 110 የሚጠጉ ክርስቲያኖች ታግተዋል።
በካጁር አውራጃ ቪክቶር ዊኒንግ ኦል የተሰኘች ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላይ በፉላኒ ታጣቂዎች በደረሰ ጥቃት አማካኝነት ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና በጸሎት ላይ የነበሩ ክርስቲያኖች ላይ ጥቃት የተፈጸመው።በካጁሪ አውራጃ በተፈጸመ ጥቃት ምክንያት ከታገቱት ሰዎች መካከል የማህበረሰብ መሪዎች የሚገኙበት ሲሆን እገታው የሚደረገውም ብዙ የወንጌል አማኞች በሚገኙባቸው መንደሮች ላይ ነው።
በናይጄሪያ እና በሳሄል ቀጠና በሚሊይን የሚቆጠሩ እና የእስልምና እምነት የሚከተሉ ፉላኒዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛዎቹ ፉላኒዎች ጽንፈኛ አቋምን የሚያራምዱ አይደሉም፡ ሆኖም እንዳንድ የፉላኒ ጎሳዎች ጽንፈኛ የሆነ ሐይማኖተኝነትን የሚያራምዱ መሆናቸውን ዓለም አቀፍ የክርስቲያኖች መብት ተሟጋቾች ይጠቅሳሉ።
በናይጄሪያ የሚገኙ ክርስቲያን መሪዎች በሀገሪቱ ማዕከላዊ ክፍል ላይ ክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ጥቃት የክርስቲያኖችን መሬትን መንጠቅን ያለመ ነው በማለት ይሞግታሉ፤ ለዚህም እንደ ምክንያት ሚነሳው የፉላኒ ታጣቂዎች የያዙት ቦታ በበረሀማነት አማካኝነት ለከብቶቻቸው የማይመች እየሆነ መምጣቱ ነው።
በዚህ እና ተያያዥ ምክንያቶችም በዓለማችን ላይ በዓመት ክርስቲያን በመሆናቸው ምክንያት ከሚገደሉ ሰዎች 69 በመቶ የሚሆኑት ሕይወታቸው የሚያልፈው በናይጄሪያ ነው።
በደቡባዊ ናይጄሪያም ለክርስቲያኖች አስጊ የሆኑ ጽንፈኛ ቡድኖች ብቅ ማለት መጀመራቸውን ተከትሎ በሰሜናዊ ናይጂሪያ የሚገኙ ክርስቲያኖች እያስተናገዱ ያሉት ጥቃት በደቡብ ናይጄርያ ላሉትም ስጋትን መጫሩ አልቀርም።
መረጃውን ከክርስቲያን ቱዴይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤2