በዓለም አቀፍ የሚሽን ጉባኤ ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በፕሬዚደንቷ መወከሏን አስታወቀች።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጨመሮ የተለያዩ አለም አቀፍ አብያተክርስቲያናት በመስራች አባልነት በሚመሩት አለም አቀፍ የሚሽን ጉባኤ (International Mission Association/#IMA) አዘጋጅነት በማዕከላዊ አሜሪካ ሁንዱራስ ዋና ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ስብሰባ ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በፕሬዚዳንቷ ተወክላለች።
በያዝነው ሳምንት በጀመረውና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ የቤተክርስቲያን መሪዎች በወንጌል አገልግሎት ዙሪያ እየመከሩ በሚገኙበት ስብሰባ ላይ የታደሙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በጉባኤው የቤተክርስቲያኒቱን የወንጌል እንቅስቃሴ ልምድ ከማካፈል በተጨማሪ በሌሎች አለማት ያለውን የወንጌል ተልዕኮ አካሄድ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ጋር የሚለዋወጡ ይሆናል።
ይህ ጉባኤ ለቤተክርስቲያኒቱ ልምድ ከመለዋወጥ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚኖራት የወንጌል ተጽዕኖ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ይታስባል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የማህበራዊ ሚድያ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጨመሮ የተለያዩ አለም አቀፍ አብያተክርስቲያናት በመስራች አባልነት በሚመሩት አለም አቀፍ የሚሽን ጉባኤ (International Mission Association/#IMA) አዘጋጅነት በማዕከላዊ አሜሪካ ሁንዱራስ ዋና ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ስብሰባ ላይ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በፕሬዚዳንቷ ተወክላለች።
በያዝነው ሳምንት በጀመረውና ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ የቤተክርስቲያን መሪዎች በወንጌል አገልግሎት ዙሪያ እየመከሩ በሚገኙበት ስብሰባ ላይ የታደሙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በጉባኤው የቤተክርስቲያኒቱን የወንጌል እንቅስቃሴ ልምድ ከማካፈል በተጨማሪ በሌሎች አለማት ያለውን የወንጌል ተልዕኮ አካሄድ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ጋር የሚለዋወጡ ይሆናል።
ይህ ጉባኤ ለቤተክርስቲያኒቱ ልምድ ከመለዋወጥ ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚኖራት የወንጌል ተጽዕኖ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ይታስባል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የማህበራዊ ሚድያ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤5👍3