የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ 6ኛ የመዝሙር አልበም ለምርቃት በቃ።
በተለያዩ ጊዜያት በዝማሬዎቹ የሚታወቀው ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ በቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ 6ኛውን የመዝሙር አልበም በይፋ አስመርቋል።
የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ የአፋን ኦሮሞ አልበም “በራ በራኮ” የሚሰኝ ሲሆን አልበሙ 13 መዝሙሮችን በውስጡ መያዙም ተነግሯል።
ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከ20 አመታት በላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በታማኝነት በማገልገሉ የሚታወቅ ሲሆን በፕሮግራሙም የኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ፕረዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ጨምሮ የቤተክርስቲያን አገልጋዩች እና ጥሪ የተደረገላቸው የወንጌላውያን አማኞችም ታድመዋል።
ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ ቀደም ሲልም “ኢኝ ዳሬ ጎትኒ፣ ኡቱ ባድኔ ካናን ዱራ፣ አታሚን ጋላኒ ና ኢቲሳ”በተሰኙ የመዝሙር አልበሞችን ለወንጌል አማኙ ተደራሽ አድርጓል።
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
በተለያዩ ጊዜያት በዝማሬዎቹ የሚታወቀው ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ በቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ 6ኛውን የመዝሙር አልበም በይፋ አስመርቋል።
የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ የአፋን ኦሮሞ አልበም “በራ በራኮ” የሚሰኝ ሲሆን አልበሙ 13 መዝሙሮችን በውስጡ መያዙም ተነግሯል።
ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከ20 አመታት በላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በታማኝነት በማገልገሉ የሚታወቅ ሲሆን በፕሮግራሙም የኢት./ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ፕረዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ጨምሮ የቤተክርስቲያን አገልጋዩች እና ጥሪ የተደረገላቸው የወንጌላውያን አማኞችም ታድመዋል።
ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ ቀደም ሲልም “ኢኝ ዳሬ ጎትኒ፣ ኡቱ ባድኔ ካናን ዱራ፣ አታሚን ጋላኒ ና ኢቲሳ”በተሰኙ የመዝሙር አልበሞችን ለወንጌል አማኙ ተደራሽ አድርጓል።
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
❤7
የፉላኒ ታጣቂዎች በባፕቲስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ባደረሱት ጥቃት የቤተ ክርስቲያኒቱ መጋቢ እና አባል መገደላቸው ተገለጸ።
በባፕቲስት ቤተ ክርስቲያን ሰኞ ከሰዓት በተደረገ የአምልኮ መርሃግብር ላይ ፤ በአባላት ላይ በተከፈተ ተኩስ አማካኝነት የቤተ ክርስቲያኒቱ መጋቢ እና አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባል ሕይወታቸው አልፏል።
ይህም ጥቃት የደረሰው በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ፤ ያሪቦሪ መንደር በቤጌ ባብቲስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው።
በቦታው የነበሩ ምስክሮች 20 የፉላኒ ታጣቂዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ተኩስ እንደከፈቱ የተናገሩ ሲሆን መጋቢውን እና አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባል ከመግደላቸውም ባለፈ አንዲት ሴትን አግተው መውሰዳቸውን አሳውቀዋል።
በናይጄሪያ ማዕከላዊ ክፍል ላይ በያዝነው ዓመት ከፍተኛ የሆነ የክርስቲያኖች ግድያ እየተሰተዋለ የሚገኝ ሲሆን በባለፈው ወር ብቻ የፉላኒ ታጣቂዎች 20 ክርስቲያኖች ገድለዋል።
በባለፉት 2 ወራት በፉላኒ ታጣቂዎች አማካኝነት ሕይወታቸን ያጡ ክርስቲያኖች ቁጥር ከ80 አልፏል።
የአከባቢው ባለስልጣን የሆኑት አማላዉ ሳሙኤል የተፈጠረውን ጥቃት ሰብዓዊነት የጎደለው ነው በማለት ያወገዙት ሲሆን ጥቃት አድራሾቹ በወድቅት እየመጡ ንጹሐን መግደላቸውን እና ጣሪያ ሸንቁሮ እስከመግባት ድረስ የሚያደርሱት ጥቃት ገደብ እንዳጣለት ተናግረዋል።
ናይጄሪያ እንደ ኦፕን ዶርስ 2025 ወርልድ ዋች ሊስት ደረጃ መሰረት በዓለማችን ክርስቲያኖች በመግደል አንደኛ ደረጃ የያዘች ሲሆን በዓመቱ ውስጥ በዓለማችን ክርስቶስን በመከተላቸው ምክንያት ከተገደሉት 4,476 ሰዎች መካከል 3,100 የሚሆኑት የተገደሉት በናይጄርያ ነው።
የግድያውም መንስኤ ጽንፈኛ ሀይማኖታዊ አመለካከት እና ክርስቲያኖችን በማፈናቀል መሬታቸውን ለመውሰድ የሚደረግ ጥረት እንደሆነ ይታመናል።
መረጃውን ከፕሪሚየር ክርስቲያን ኒውስ አገኘነው።
አማኑኤል ዴቢሶ ፤ ኢቫንጀሊካል ቲቪ
በባፕቲስት ቤተ ክርስቲያን ሰኞ ከሰዓት በተደረገ የአምልኮ መርሃግብር ላይ ፤ በአባላት ላይ በተከፈተ ተኩስ አማካኝነት የቤተ ክርስቲያኒቱ መጋቢ እና አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባል ሕይወታቸው አልፏል።
ይህም ጥቃት የደረሰው በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ፤ ያሪቦሪ መንደር በቤጌ ባብቲስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው።
በቦታው የነበሩ ምስክሮች 20 የፉላኒ ታጣቂዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ተኩስ እንደከፈቱ የተናገሩ ሲሆን መጋቢውን እና አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባል ከመግደላቸውም ባለፈ አንዲት ሴትን አግተው መውሰዳቸውን አሳውቀዋል።
በናይጄሪያ ማዕከላዊ ክፍል ላይ በያዝነው ዓመት ከፍተኛ የሆነ የክርስቲያኖች ግድያ እየተሰተዋለ የሚገኝ ሲሆን በባለፈው ወር ብቻ የፉላኒ ታጣቂዎች 20 ክርስቲያኖች ገድለዋል።
በባለፉት 2 ወራት በፉላኒ ታጣቂዎች አማካኝነት ሕይወታቸን ያጡ ክርስቲያኖች ቁጥር ከ80 አልፏል።
የአከባቢው ባለስልጣን የሆኑት አማላዉ ሳሙኤል የተፈጠረውን ጥቃት ሰብዓዊነት የጎደለው ነው በማለት ያወገዙት ሲሆን ጥቃት አድራሾቹ በወድቅት እየመጡ ንጹሐን መግደላቸውን እና ጣሪያ ሸንቁሮ እስከመግባት ድረስ የሚያደርሱት ጥቃት ገደብ እንዳጣለት ተናግረዋል።
ናይጄሪያ እንደ ኦፕን ዶርስ 2025 ወርልድ ዋች ሊስት ደረጃ መሰረት በዓለማችን ክርስቲያኖች በመግደል አንደኛ ደረጃ የያዘች ሲሆን በዓመቱ ውስጥ በዓለማችን ክርስቶስን በመከተላቸው ምክንያት ከተገደሉት 4,476 ሰዎች መካከል 3,100 የሚሆኑት የተገደሉት በናይጄርያ ነው።
የግድያውም መንስኤ ጽንፈኛ ሀይማኖታዊ አመለካከት እና ክርስቲያኖችን በማፈናቀል መሬታቸውን ለመውሰድ የሚደረግ ጥረት እንደሆነ ይታመናል።
መረጃውን ከፕሪሚየር ክርስቲያን ኒውስ አገኘነው።
አማኑኤል ዴቢሶ ፤ ኢቫንጀሊካል ቲቪ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዮን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የደቡብ ክላስተር፤ ዛሬ በደቡብ ሲኖዶስ አዘጋጅነት በዲላ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።
ሥልጠናውም ላለፉት ሶስት ዓመታት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በተለያዩ አርዕስት ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን የማጠቃለያ ዓመት በሆነው የአራተኛው ዓመት ስልጠና "ደቀመዛሙርትን፣ ደቀመዛሙርት አድራጊዎችን እና መሪዎችን ማባዛት" በሚል ዋና ዐርስት ላይ መሠረት በማድረግ በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ክላስተሮች ሥልጠናው በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በዚህም የክላስተር ሥልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ 14 ሲኖዶሶች የመጡ በሲኖዶስ፣ በሰበካ እና በማህበረ ምዕመናን የሚያገለግሉ መሪዎች እና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በመካፈል ላይ ይገኛሉ።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዩንና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል፣ የአዲስ አበባ ሲኖዶስ ኘሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ጽጌ በረሃ እና የቤተክርስቲያኒቱ የካምፓስ አገልግሎትና ከተማ ወንጌል ማዳረስ የሥራ ክፍል አስተባባሪ የሆኑት ቄስ ወርቁ ኤባ ሥልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የደቡብ ክላስተር፤ ዛሬ በደቡብ ሲኖዶስ አዘጋጅነት በዲላ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።
ሥልጠናውም ላለፉት ሶስት ዓመታት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በተለያዩ አርዕስት ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን የማጠቃለያ ዓመት በሆነው የአራተኛው ዓመት ስልጠና "ደቀመዛሙርትን፣ ደቀመዛሙርት አድራጊዎችን እና መሪዎችን ማባዛት" በሚል ዋና ዐርስት ላይ መሠረት በማድረግ በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ክላስተሮች ሥልጠናው በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በዚህም የክላስተር ሥልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ 14 ሲኖዶሶች የመጡ በሲኖዶስ፣ በሰበካ እና በማህበረ ምዕመናን የሚያገለግሉ መሪዎች እና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በመካፈል ላይ ይገኛሉ።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዩንና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል፣ የአዲስ አበባ ሲኖዶስ ኘሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ጽጌ በረሃ እና የቤተክርስቲያኒቱ የካምፓስ አገልግሎትና ከተማ ወንጌል ማዳረስ የሥራ ክፍል አስተባባሪ የሆኑት ቄስ ወርቁ ኤባ ሥልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን