በኢትዮጲያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የልማት ኮሚሽን የማህበረሰብ ልማት ስልጠና ተሰጠ።
ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የአንድ ቀን የማህበረሰብ ልማት ስልጠና ላይ ከአዳማ ከተማ የእድር ማህበራት ፤ ከተለያዩ እምነቶች የመጡ የእምነት አባቶች፤ ከ7 ቀበሌ የተወጣጡ የማህበረሰብ መሪዎች እና መምህራን ተሳታፊ ሆነዋል። ስልጠናውን የሰጡትም የቤተ እምነቱ ልማት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ እምሩ ሙላቱ ነበሩ።
በስልጠናው ላይም በተለያዩ የማህበረሰብ ልማት ዘርፎች ማለትም የኢኮኖሚ አቅም መጎልበት፣ ማህበራዊ ደህንነት፣ የማህበረሰብ ልማት አቀራረብ፣ ትራንስፎርሜሽን፣ ለውጥን ጨምሮ ውይይት የተደረገ ሲሆን ምክትል ኮሚሽነሩም በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እና የልማት ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ሁለንተናዊ አገልግሎት ማካሄድ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት በመስጠት አስገንዝበዋል።
የስልጠናው አላማ ተሳታፊዎች ማህበረሰባቸውን ለማገልገል፣ ልማት ለማምጣት እና ትብብር እና ፈጠራን ለማጎልበት ማህበረሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት ማስታጠቅ እና የማህበረሰብ ልማት የግለሰቦችን እና የህብረተሰቡን አጠቃላይ ህይወት ለማሻሻል ያለውን ጠቀሜታ ማስገንዘብ መሆኑን አቶ ኢዮብ ውብሸት ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል ስትል የኢትዮጲያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በማህበራዊ ትስስር ገጿ ላይ አስፍራለች።
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የአንድ ቀን የማህበረሰብ ልማት ስልጠና ላይ ከአዳማ ከተማ የእድር ማህበራት ፤ ከተለያዩ እምነቶች የመጡ የእምነት አባቶች፤ ከ7 ቀበሌ የተወጣጡ የማህበረሰብ መሪዎች እና መምህራን ተሳታፊ ሆነዋል። ስልጠናውን የሰጡትም የቤተ እምነቱ ልማት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ እምሩ ሙላቱ ነበሩ።
በስልጠናው ላይም በተለያዩ የማህበረሰብ ልማት ዘርፎች ማለትም የኢኮኖሚ አቅም መጎልበት፣ ማህበራዊ ደህንነት፣ የማህበረሰብ ልማት አቀራረብ፣ ትራንስፎርሜሽን፣ ለውጥን ጨምሮ ውይይት የተደረገ ሲሆን ምክትል ኮሚሽነሩም በአንድ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እና የልማት ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ሁለንተናዊ አገልግሎት ማካሄድ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት በመስጠት አስገንዝበዋል።
የስልጠናው አላማ ተሳታፊዎች ማህበረሰባቸውን ለማገልገል፣ ልማት ለማምጣት እና ትብብር እና ፈጠራን ለማጎልበት ማህበረሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት ማስታጠቅ እና የማህበረሰብ ልማት የግለሰቦችን እና የህብረተሰቡን አጠቃላይ ህይወት ለማሻሻል ያለውን ጠቀሜታ ማስገንዘብ መሆኑን አቶ ኢዮብ ውብሸት ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል ስትል የኢትዮጲያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በማህበራዊ ትስስር ገጿ ላይ አስፍራለች።
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
❤3
በአዲስ አበባ መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
ክረምትን አስመልክቶ የተዘጋጀው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና በአዲስ አበባ (5ኪሎ) መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተጀምሯል።
ከሃምሌ 5 እስከ ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 8 ሳምንታት የሚቆየው ስልጠና በዋናነት የጋዜጠኝነት መሰረታዊያን ፤ የዜና አጻጻፍ እና ሀሰተኛ የዜና ስርጭቶችን መቀነስ ፤ ስነጽሁፍ እና ዲጂታል ሚዲያን ጨምሮ ዘጋቢ ፊልምን በተግባር ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
በሚኖሩት ሳምንታት እራሳቸውን በስነምግባር ብቁ አድርገው ቤተክርስቲያንን በዲጅታል ሚዲያ በማገዝ እንዲሁም የሚሰሩትን ስራ በተግባር እንዲያሳድጉ ሊያደርግ የሚችል የስልጠና ጊዜ እንደሚኖር በነበረው የመክፈቻ መረሃ ግብር የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም ደመላሽ ዶላ ተናግረዋል።
ስልጠናው The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከየደስ ደስ መልቲ ሚዲያ እና ቲኪቆስ ሚዲያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ስልጠና ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ከአዲስ አበባ ባሻገር በሃዋሳ እንደሚጀምር ታውቋል።
መረጃውን ከክርስቲያን ዜና አገኘነው
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
ክረምትን አስመልክቶ የተዘጋጀው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና በአዲስ አበባ (5ኪሎ) መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተጀምሯል።
ከሃምሌ 5 እስከ ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 8 ሳምንታት የሚቆየው ስልጠና በዋናነት የጋዜጠኝነት መሰረታዊያን ፤ የዜና አጻጻፍ እና ሀሰተኛ የዜና ስርጭቶችን መቀነስ ፤ ስነጽሁፍ እና ዲጂታል ሚዲያን ጨምሮ ዘጋቢ ፊልምን በተግባር ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
በሚኖሩት ሳምንታት እራሳቸውን በስነምግባር ብቁ አድርገው ቤተክርስቲያንን በዲጅታል ሚዲያ በማገዝ እንዲሁም የሚሰሩትን ስራ በተግባር እንዲያሳድጉ ሊያደርግ የሚችል የስልጠና ጊዜ እንደሚኖር በነበረው የመክፈቻ መረሃ ግብር የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም ደመላሽ ዶላ ተናግረዋል።
ስልጠናው The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከየደስ ደስ መልቲ ሚዲያ እና ቲኪቆስ ሚዲያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ስልጠና ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ከአዲስ አበባ ባሻገር በሃዋሳ እንደሚጀምር ታውቋል።
መረጃውን ከክርስቲያን ዜና አገኘነው
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
❤1
የመጋቢ ዘማሪ አስፋው መለሰ "አንተን አልጣ እንጂ" 6ኛ የመዝሙር አልበም ተመረቀ።
ዘለግ ላሉ ጊዜያት በዝማሬዎቹ የሚታወቀው መጋቢ አስፋው መለሰ 6ኛውን የመዝሙር አልበም በይፋ አስመርቋል።
በማቴዎስ ወንጌል 6፥31 ላይ መሰረት አድርጎ የተዘጋጀው የአልበሙ የምርቃትና የመዝሙር ድግስ ስነ ስርዓትም በልደታ ጉባኤ እግዚአብሄር ቤተክርስትያን በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል።
"አንተን አልጣ እንጂ" የተሰኘውን ሙሉ አልበም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ሁለት አመት እንደፈጀ የተገለጸ ሲሆን አልበሙ 11 መዝሙሮችን በውስጡ መያዙም ተነግሯል።
ዘማሪ አስፋው መለሰ ቀደም ሲልም ብዙ ዘመን ራራህልኝ ፣ በጅምር አይቀርም ፣ ትናንት ዛሬ አይደለም እና መሰል የአልበም ስራዎችንም ለወንጌል አማኙ ተደራሽ አድርጓል።
በፕሮግራም የቤተክርስቲያኗን አገልጋዩች ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው የወንጌላውያን አማኞችም መታደማቸውን በማህበራዊ ሚድያ ላይ ይፋ የተደረጉ መረጃዎች አመላክተዋል።
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
ዘለግ ላሉ ጊዜያት በዝማሬዎቹ የሚታወቀው መጋቢ አስፋው መለሰ 6ኛውን የመዝሙር አልበም በይፋ አስመርቋል።
በማቴዎስ ወንጌል 6፥31 ላይ መሰረት አድርጎ የተዘጋጀው የአልበሙ የምርቃትና የመዝሙር ድግስ ስነ ስርዓትም በልደታ ጉባኤ እግዚአብሄር ቤተክርስትያን በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል።
"አንተን አልጣ እንጂ" የተሰኘውን ሙሉ አልበም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ሁለት አመት እንደፈጀ የተገለጸ ሲሆን አልበሙ 11 መዝሙሮችን በውስጡ መያዙም ተነግሯል።
ዘማሪ አስፋው መለሰ ቀደም ሲልም ብዙ ዘመን ራራህልኝ ፣ በጅምር አይቀርም ፣ ትናንት ዛሬ አይደለም እና መሰል የአልበም ስራዎችንም ለወንጌል አማኙ ተደራሽ አድርጓል።
በፕሮግራም የቤተክርስቲያኗን አገልጋዩች ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው የወንጌላውያን አማኞችም መታደማቸውን በማህበራዊ ሚድያ ላይ ይፋ የተደረጉ መረጃዎች አመላክተዋል።
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
❤5