የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.67K subscribers
9.59K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል_46ኛው_የሥራ_አስፈጻሚ_ኮሚቴ_ስብሰባ_በጉዲና_ቱምሳ_ሁለገብ_ማሰልጠኛ_ማዕከል_ተካሄደ
ጥር 22 ቀን 2017/ዓ.ም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል 46ኛው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ ማሰልጠኛ ማዕከል አካሄዶዋል። ቄስ ተሾመ አመኑ የአግዚአብሔር ቃል ያካፈሉ ሲሆን በካውንስሉ የተሰሩ የሥራ ሪፖርት ተደምጧል ።ከነዚህም መካከል የካውንስሉ የውጭ ግንኙነት መመሪያ ፣የታሪክ መጽሐፍ ዝግጅት ኮሚቴ ፣የመጽሐፍ ቅዱስ ይዘት ኮሚቴ እና የልጆች ፌሰቲሻል ፕሮግራምን በተመለከተ በነዚህ ርዕሰ ጉዳዬች ሪፖርት ቀርቦዋል።
የካቲት 29-30 ካውንስሉ ከቢሊግርሃም ኢሻንጀልስቲክ አሶሴሽን ጋር በመተባበር በመስቀል አደባባይ ያዘጋጀውን ፕሮግራም በሚመለከት አስካሁን የተሰሩትንና ልሰሩ በሚገባቸው ጉደይ ላይ ውይይት ተደርጓል ።የበዓለ ሃምሳ ቀን አከባበር በኢትዮጵያ ቅድመ ዝግጅትን አስመልክቶ ትልቅ የሆነ ውይይት እና አቅጣጫዎች ተቀምጦአል ።
በዚህ ስብሰባ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችና አሳቦች የተነሱ ሲሆን በካውንስሉ ፕሬዚዳንት ጣሰው ገብሬ(ዶ/ር) ፣በምክትል ፕሬዚዳንት ሐዋርያው ዮሐንስ ግርማ እና በካውንስሉ ጠቅላይ ጸሐፈ ደረጀ ጀምበሩ ምላሽ ተሰጥቶበታል ።ቀጣይ የቦርድ እና የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ ቀን በመወሰን ተጠናቋል ።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
👍2
#የመሠረተ_ክርስቶስ_ቤተክርስቲያን_በታሪኳ_የመጀመሪያዋን_ሴት_ዋና_ጸሐፊ_መረጠች

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ደቡብ አዳማ ክልል ሰባተኛውን ጠቅላላ የመሪዎች ጉባኤ በትላንትናው ያከናወነ ሲሆን በጉባኤው የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ መምህር ገመቹ ደበሎ ተገኝተዋል።

በዕለቱም መሪዎቹ ባደረጉት የክልሉ ዋና ጸሐፊ ምርጫ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት ዋና ጸሐፊ አድርገው ወጣቷን መጋቢ ሻሾ ቱሉን ሾመዋል። በተጨማሪም ጉባኤው ክልሉን ከ9 ዓመታት በላይ ያገለገለውን መጋቢ ዳመነ ደጉን ከባላቤቱ ጋር በጸሎት ባርኮና አመስግኖ ሸኝቷል።

መጋቢ ሻሾ ቱሉ ለቀጣዮቹ አራት አመታት በክልሉ ስር የሚገኙትን ከ69 የሚልቁ አጥቢያዎች የምትመራ ይሆናል ሲሉ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በማህበራዊ ትስስር ላይ ገልጾዋል።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
👍4
#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል_ከmission_of_hope_international_ጋር_ወይይት_አደረገ

ጥር 26 ቀን /2017 ዓ.ም mission of hope international በኬንያ መሰረት አድርጎ እየሰራ ያለ ተቋም ሲሆን በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ስራ ለመስራት በካውንስሉ ቢሮ በመገኘት የውይይትና የምክክር ጊዜ አድርጓል።

እ.ኤ.አ 2000 ዓ.ም 50 ሕፃናትን በመረዳት የትምህርት እድሎችን በማመቻቸት የጀመረ ሲሆን በአሁን ጊዜ በኬንያና በለቤሪያ ከ37 በላይ የሚሆኑ ትምርህት ቤቶችን እና በርካታ ሕፃናትን በመረዳት እያገለገለ ያለ ተቋም ነው።በተደረገው ወይይት ከኬንያና ከአሜሪካ የመጡ 18 የሉካን ቡድን ተገኝተዋል።የካውንስሉ የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ መጋቢ አሸብር ከተማ ካውንስሉ እየሰራ ስላለው ስራ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ውሰጥ ተመሳሳይ ስራዎችን ከካውንስሉ ጋር በመሆን ለመስራት ፍቃደኛ መሆናቸውንና የመጀመሪያውን ምዝገባ በካውንስሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።በሚቀጥሉት ጊዜያቶች የምክክሩ ወጤት ከምን እንደደረሰ የምን ገልጽ የሆናል ሲሉ የካውንስሉ የውጪ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ መጋቢ አሸብር ከተማ ለኢቫንጀሊካል ቴሌቬዥን ገልጸዋል።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://tttttt.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!
👍114🙏1