የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ጠቅላላ ጉባኤያት በመካሄድ ላይ መሆናቸው ተገለጸ።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በማካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት ነሃሴ 2 እና 3/2017 ዓ.ም ጉባኤዎቹ በመካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ክልል፤ ሐዋሳ ክልል፤ ዲላና አካባቢው ክልል፤ በንሳ ዳዬ ጊዜያዊ ክልል፤ በሻኪሶ ጊዜያዊ ክልል እና ጅዳ ቆርኬ ጊዜያዊ ክልሎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ጠቅላላ ጉባኤዎች በክልሎቹ ስር ከሚገኙ አጥቢያዎች የተወከሉ መሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
በጠቅላላ ጉባኤው የ2017 ዓ.ም ሪፖርትና የ2018 በጀት አመት እቅድ ሲቀርብ አዳዲስ የመሪዎች ምርጫና ሹመት እንዲሁም በታማኝነት መዋጮአቸውን ለሚከፍሉ አጥቢያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
በመጨረሻም በተጠናቀቀው የበጀት አመት እድገት ያሳዩ 18 ስርጭት ጣቢዎች ለጉባኤያቱ ቀርበው ወደ አጥቢያነት አንዲያድጉ መሪዎቹ አጽድቀዋል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በማካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት ነሃሴ 2 እና 3/2017 ዓ.ም ጉባኤዎቹ በመካከለኛው ስምጥ ሸለቆ ክልል፤ ሐዋሳ ክልል፤ ዲላና አካባቢው ክልል፤ በንሳ ዳዬ ጊዜያዊ ክልል፤ በሻኪሶ ጊዜያዊ ክልል እና ጅዳ ቆርኬ ጊዜያዊ ክልሎች ተካሂደዋል። በእነዚህ ጠቅላላ ጉባኤዎች በክልሎቹ ስር ከሚገኙ አጥቢያዎች የተወከሉ መሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
በጠቅላላ ጉባኤው የ2017 ዓ.ም ሪፖርትና የ2018 በጀት አመት እቅድ ሲቀርብ አዳዲስ የመሪዎች ምርጫና ሹመት እንዲሁም በታማኝነት መዋጮአቸውን ለሚከፍሉ አጥቢያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
በመጨረሻም በተጠናቀቀው የበጀት አመት እድገት ያሳዩ 18 ስርጭት ጣቢዎች ለጉባኤያቱ ቀርበው ወደ አጥቢያነት አንዲያድጉ መሪዎቹ አጽድቀዋል።
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤1🙏1
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዋናው ቢሮ አገልጋዮችና ሰራተኞች ቤተክርስቲያኒቱ ከነሃሴ 1-11/2017 ዓ.ም ያወጀችውን ሀገር አቀፍ ጾምና ጸሎት ተከትሎ በዋናው ቢሮ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ጀምረዋል።
በምድራችን ኢትዮጵያ ሰላም ላይ ትኩረቱን ባደረገው በዚህ ጾምና ጸሎት ጉባኤው በንስሀ እና ምልጃ ልምናውን ለእግዚአብሔር አቅርቧል።
"በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።" 2ኛ ዜና 7÷14
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
በምድራችን ኢትዮጵያ ሰላም ላይ ትኩረቱን ባደረገው በዚህ ጾምና ጸሎት ጉባኤው በንስሀ እና ምልጃ ልምናውን ለእግዚአብሔር አቅርቧል።
"በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።" 2ኛ ዜና 7÷14
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፌስቡክ ገጽ ላይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤9