የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍ እና ልማት ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች እና ለኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ወጣቶች በዘላቂ ሠላም ግንባታ ዘርፍ የወጣቶች ተሳትፎን ለማሳደግ የሚረዳ የግንዛቤ ማስጨበጥ እና የምክክር ስልጠና መድረክ በሀዋሳ ከተማ አካሄዷል፡፡
በስልጠናውም 60 ሰልጣኞች የተገኙ ሲሆኑ ሰልጣኞች የመጡትም ከሆሳዕና ፣ ከሀላባ ፣ ወራቤ ፣ ሻሽመኔ ፣ ከወላይታ ሶዶ፣ ከሀዋሳ/ስዳማ እና አረባምንጭ አከባቢ ከሚገኙ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት እና ከቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ነው፡፡
ስለ ግጭት አፈታት ፣ ሠላም ግንባታ እና የተለያዩ የሠላም ጉዳዮችን በተመለከተ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ለ60 ወጣቶች ስልጣና ተሰጥቷል፡፡ ወጣቶች በመንፈሳዊ እና በሠላም ግንበታ ዘረፍ ያለቸውን ሚና በማንሳት ይህ ዓለም እንዳያሸንፋቸው በእግዚአብሔር ቃል እውነት መሞላት እና መታጠቅ እንደሚያስፈልግ የገለጹት በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና የወጣቶች አገልግሎት አስተባበሪ ወንጌላዊ ያቆብ በዛብህ ናቸው፡፡
የወጣቶች ተሳትፎ ለዘላቂ ሠላም ግንባታ ወሳኝ ሲሆን ወጣቶች የሠላም ግንበታ ቁልፍ ባለድርሻ አካል ናቸው ብለው በሁሉም ቦታ የሠላም መሳሪያ በመሆን የመጪወን ትውልድ ተስፋ ማደስ አለባቸው ሲሉ ለሰልጣኝ ወጣቶች የአደራ መልዕክትቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኮሚሽኑ የጄስራ ፕሮጀክት ኃላፊ/ማናጀር አቶ እንደለ ወ/ሳማያት ወጣቶች የግጭትን አስከፊነትን በማወቅ ከግጭት ይልቅ ለሠላም እንድሰሩ መክረዋል፡፡ ይህም እንደ ግለሰብ እና እንደ ማህበረሰብ ሁሉም ለዘላቂ ሠላም መስራት አለብን ብለዋል፡፡
በስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም ከስልጠናው ጠቃሚ ልምድ መቅሰማቸውን ገልጸው ስልጠናው እንዴት ከሌሎች ኃይማኖቶች እና ማህበረሰብ ጋር በሠላም ተከባብረን መኖር እንዳለብን አቅጣጫ ያሳየ እና ጠቃሚ ልምድ ያገኘንበት ነው ሲሉም ገልጾዋል፡፡
መረጃውን ከአገልግሎት ክፍሉ አገኘነው
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
በስልጠናውም 60 ሰልጣኞች የተገኙ ሲሆኑ ሰልጣኞች የመጡትም ከሆሳዕና ፣ ከሀላባ ፣ ወራቤ ፣ ሻሽመኔ ፣ ከወላይታ ሶዶ፣ ከሀዋሳ/ስዳማ እና አረባምንጭ አከባቢ ከሚገኙ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት እና ከቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ነው፡፡
ስለ ግጭት አፈታት ፣ ሠላም ግንባታ እና የተለያዩ የሠላም ጉዳዮችን በተመለከተ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ለ60 ወጣቶች ስልጣና ተሰጥቷል፡፡ ወጣቶች በመንፈሳዊ እና በሠላም ግንበታ ዘረፍ ያለቸውን ሚና በማንሳት ይህ ዓለም እንዳያሸንፋቸው በእግዚአብሔር ቃል እውነት መሞላት እና መታጠቅ እንደሚያስፈልግ የገለጹት በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና የወጣቶች አገልግሎት አስተባበሪ ወንጌላዊ ያቆብ በዛብህ ናቸው፡፡
የወጣቶች ተሳትፎ ለዘላቂ ሠላም ግንባታ ወሳኝ ሲሆን ወጣቶች የሠላም ግንበታ ቁልፍ ባለድርሻ አካል ናቸው ብለው በሁሉም ቦታ የሠላም መሳሪያ በመሆን የመጪወን ትውልድ ተስፋ ማደስ አለባቸው ሲሉ ለሰልጣኝ ወጣቶች የአደራ መልዕክትቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኮሚሽኑ የጄስራ ፕሮጀክት ኃላፊ/ማናጀር አቶ እንደለ ወ/ሳማያት ወጣቶች የግጭትን አስከፊነትን በማወቅ ከግጭት ይልቅ ለሠላም እንድሰሩ መክረዋል፡፡ ይህም እንደ ግለሰብ እና እንደ ማህበረሰብ ሁሉም ለዘላቂ ሠላም መስራት አለብን ብለዋል፡፡
በስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም ከስልጠናው ጠቃሚ ልምድ መቅሰማቸውን ገልጸው ስልጠናው እንዴት ከሌሎች ኃይማኖቶች እና ማህበረሰብ ጋር በሠላም ተከባብረን መኖር እንዳለብን አቅጣጫ ያሳየ እና ጠቃሚ ልምድ ያገኘንበት ነው ሲሉም ገልጾዋል፡፡
መረጃውን ከአገልግሎት ክፍሉ አገኘነው
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ