#ቀን_ገንቢ
ምዕራፍ ፩: ክፍል ፩
የራስ ዋጋ
------------
በአንድ ሰሚናር ውስጥ ሁለት መቶና በላይ ሰዎች በታደሙበት ታዋቂው ንግግር አድረጊ ተጋብዞ በቦታው ተገኝቷል፡፡ ተናጋሪው ለለቱ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት ለማጠናከር ያግዘው ዘንድ ንግግሩን የጀመረው የሃምሣ ብር ኖት በእጁ ይዞ በማሳየት “ከመካከላችሁ ይህንን የሃምሣ ብር ኖት የሚፈልግ ማን ነው!?” ሲል ጠየቃቸው፡፡ ታዳሚውም በተከታታይ ሁሉም እጁን አንድ ባንድ አወጣ፡፡ ተናገሪው ቀጠለ “ከመካከላችሁ ለአንዳችሁ መስጠት እፈልጋለሁ ነገር ግን ከዛ በፊት” አለና የሃምሳ ብር ኖቱን በእጁ በማፋተግ እንዲጨማተር ካደረገ በኋላ “አሁንስ የሚፈልገው ይኖራል!?” ሲል በድጋሜ ጥያቄ አቀረበ፡፡
አሁንም የታዳሚዎች እጅ እፈልጋለሁ በሚል ስሜት ተዘረጋ፡፡ በጣም ጥሩ አለ ተናገሪው እንደዚህ ባደርግስ ብሎ የሃምሣ ብር ኖቱን እግሩ ሥር ጥሎ በጫመው ምድሩ ጋር ካፋተገ በኋላ አሁን “እደምትመለከቱት በጣም ቆሽሿል:: ተጨማትሯልም:: አሁንስ ትትፈልጉታላችሁ!? አሁንም የፈላጊዎች እጅ በአንድነት ተነሳ፡፡ “ወገኖች አሁን በጣም ወሳኝና መሰረታዊ ትምህርት እንደቀሰማችሁ አምናለሁ፡፡ ምንም እንኳን ብሩ ላይ ማናቸውንም ነገር ባደርግበት፣ ባቆሽሸውም፣ ባጨማትረውም፤ ብሩን የራሳችሁ የማድረግ ፍላጎታችሁ እንዳለ ነው፡፡ አልቀነሰም፡፡ ምክንያቱም የብሩ ኖቱ ቢበሳቆልም ቢጎዳም እንደ ብርነቱ የሚሰጠውን ዋጋ ወይም ጠቀሜታ አልቀነሰበትምና፡፡ እስካሁንም ዋጋው ያው ሃመሳ ብር ነው፡፡” አላቸው፡፡
ብዙውን ጊዜ በሕይዎት ውጣውረድ በምናሳልፋቸው ውሳኔዎች ፣ በሚፈጠሩት ክስተቶች መውደቅ መሰነሳቱ፤ መደቆሱ ያለና የሚኖር ነው፡፡ በተፈጠሩት የህይዎት ፈታኝ ክስቶቶች ዋጋ ያጣን ያህል ሊሰማን ይችላል፡፡ ነገር ግን ምንም ይሁን ምን፣ ያለፍንበት የሕይዎት ጎዳና ምንም ያህል አባጣ ጎርባጣም ቢሆን እኛ ማለት እኛ ነንና የእኛነታችንን፣ የራሳችንን ዋጋ አናጣምም ማጣትም የለብንም ፡፡
#ሼር
@yismakeworku
ምዕራፍ ፩: ክፍል ፩
የራስ ዋጋ
------------
በአንድ ሰሚናር ውስጥ ሁለት መቶና በላይ ሰዎች በታደሙበት ታዋቂው ንግግር አድረጊ ተጋብዞ በቦታው ተገኝቷል፡፡ ተናጋሪው ለለቱ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት ለማጠናከር ያግዘው ዘንድ ንግግሩን የጀመረው የሃምሣ ብር ኖት በእጁ ይዞ በማሳየት “ከመካከላችሁ ይህንን የሃምሣ ብር ኖት የሚፈልግ ማን ነው!?” ሲል ጠየቃቸው፡፡ ታዳሚውም በተከታታይ ሁሉም እጁን አንድ ባንድ አወጣ፡፡ ተናገሪው ቀጠለ “ከመካከላችሁ ለአንዳችሁ መስጠት እፈልጋለሁ ነገር ግን ከዛ በፊት” አለና የሃምሳ ብር ኖቱን በእጁ በማፋተግ እንዲጨማተር ካደረገ በኋላ “አሁንስ የሚፈልገው ይኖራል!?” ሲል በድጋሜ ጥያቄ አቀረበ፡፡
አሁንም የታዳሚዎች እጅ እፈልጋለሁ በሚል ስሜት ተዘረጋ፡፡ በጣም ጥሩ አለ ተናገሪው እንደዚህ ባደርግስ ብሎ የሃምሣ ብር ኖቱን እግሩ ሥር ጥሎ በጫመው ምድሩ ጋር ካፋተገ በኋላ አሁን “እደምትመለከቱት በጣም ቆሽሿል:: ተጨማትሯልም:: አሁንስ ትትፈልጉታላችሁ!? አሁንም የፈላጊዎች እጅ በአንድነት ተነሳ፡፡ “ወገኖች አሁን በጣም ወሳኝና መሰረታዊ ትምህርት እንደቀሰማችሁ አምናለሁ፡፡ ምንም እንኳን ብሩ ላይ ማናቸውንም ነገር ባደርግበት፣ ባቆሽሸውም፣ ባጨማትረውም፤ ብሩን የራሳችሁ የማድረግ ፍላጎታችሁ እንዳለ ነው፡፡ አልቀነሰም፡፡ ምክንያቱም የብሩ ኖቱ ቢበሳቆልም ቢጎዳም እንደ ብርነቱ የሚሰጠውን ዋጋ ወይም ጠቀሜታ አልቀነሰበትምና፡፡ እስካሁንም ዋጋው ያው ሃመሳ ብር ነው፡፡” አላቸው፡፡
ብዙውን ጊዜ በሕይዎት ውጣውረድ በምናሳልፋቸው ውሳኔዎች ፣ በሚፈጠሩት ክስተቶች መውደቅ መሰነሳቱ፤ መደቆሱ ያለና የሚኖር ነው፡፡ በተፈጠሩት የህይዎት ፈታኝ ክስቶቶች ዋጋ ያጣን ያህል ሊሰማን ይችላል፡፡ ነገር ግን ምንም ይሁን ምን፣ ያለፍንበት የሕይዎት ጎዳና ምንም ያህል አባጣ ጎርባጣም ቢሆን እኛ ማለት እኛ ነንና የእኛነታችንን፣ የራሳችንን ዋጋ አናጣምም ማጣትም የለብንም ፡፡
#ሼር
@yismakeworku
👍177❤47🔥5
#ቀን_ገንቢ
ምዕራፍ ፩ : ክፍል ፪
ሁለት ዘሮች
--------------
ሁለት ዘሮች ናቸው፡፡ በአካባቢው የተፈጠረ ንፋስ ከቅርፊታቸው ነጥሎ እያንሳፈፈ አጓጉዞ በላመ፣ በለሰለሰ አፈር ላይ ጎን ለጎን ቀላቀላቸው፡፡ ዘሮቹም ከለሰለሰ አፈር ላይ ማረፋቸውን በተረዱ ጊዜ በጉርብትና መንፈስ ውይይት ጀመሩ፡፡
አንደኛው ዘር፡ “በዚህ በእንደዚ ለመብቀን በተዘጋጀ ማሳ ላይ ሳርፍማ መብቀን እፈልጋለሁ፡፡ ሥሮቼንም ወደ ጥልቁ አፈር በመላክ፤ ቅርንጫፎቼን ከምድር በላይ ከፍ አድርጌ እንደ ባነር በመዘርጋት የበልግ ወራት መድረሱን፤ ልምላሜ መምጣቱን ማወጅ ይገባኛል፡፡ የጠዋቷን ፀሐይም የተፈጥሮ ስጦጣየን መመገብ ይገባኛል እፈልጋለሁም፡፡” ሲል ሀሳብን ለባልጀራው ሰነዘረለት፡፡ እናም በቅሎ ማደግ ጀመረ፡፡
ሁለተኛው ዘርም በፈንታው እንዲህ አለ፡ መጀመሪያ ሀሳቡን ህምምም.. ሲል በመደመም ጀመረ፡፡ “ስሬን ወደ ጥልቁ አፈር ብለቀው በዛ ጨለማ ውስጥ ምን እንደሚገጥመኝ ከየት አውቅና ነው! ጉንቁሎቼን ባጎነቁልስ የቀንድ አውጣ ምግብ መሆኔ አይደለምን! እንዲሁም ደግሞ አበቦቼን ባፈነድቃቸው ህፃናቶች ቆርጠው ምድር ላይ በመጣል መጫዎቻ ያደርጉኛል፡፡ ስለሆነም ከዚህ ሁሉ የምጠበቅበት ምቹ ሁኔታ እስኪፈጠር መጠበቁ የተሻለ ሳይሆን አይቀርም” ሲል የመብቀል የሕይወት ተልዕኮውን ገታው፡፡
ይህን ሀሳባቸውን ከተነጋገሩ ከሰዓታት በኋላ በአካባቢው ምግቧን ፍለጋ ምድርን ስትጭር የነበረች ዶሮ ለመብቀል ምቹ ሁኔታን ሲጠብቅ የነበረውን ዘር አገኘችና ተመገበችው፡፡ ሥራን ለመስራት የማይመጣን ምቹ ሁኔታን መተበቅ ስራ እንዳንሰራ ከማድረግ ውጪ የሚፈጥረው ፋይዳ የለውም፡፡ እንቅፋትም እስከመጨረሻው ስለማየውቅ በዓለማችን እስካሁን ተሰሩ ወሳይኝ የሚባሉ ስራዎች በሙሉ በችግር ውስጥ እንጅ በተደላደለ ሁኔታ እንደልሆነ አብዛኛው መረጃ ይናገራል፡፡ There is no ideal condition for everything we can do what we have to do even in adverse condition.
/ምስጋናው ግሸን/
#ሼር
@yismakeworku
ምዕራፍ ፩ : ክፍል ፪
ሁለት ዘሮች
--------------
ሁለት ዘሮች ናቸው፡፡ በአካባቢው የተፈጠረ ንፋስ ከቅርፊታቸው ነጥሎ እያንሳፈፈ አጓጉዞ በላመ፣ በለሰለሰ አፈር ላይ ጎን ለጎን ቀላቀላቸው፡፡ ዘሮቹም ከለሰለሰ አፈር ላይ ማረፋቸውን በተረዱ ጊዜ በጉርብትና መንፈስ ውይይት ጀመሩ፡፡
አንደኛው ዘር፡ “በዚህ በእንደዚ ለመብቀን በተዘጋጀ ማሳ ላይ ሳርፍማ መብቀን እፈልጋለሁ፡፡ ሥሮቼንም ወደ ጥልቁ አፈር በመላክ፤ ቅርንጫፎቼን ከምድር በላይ ከፍ አድርጌ እንደ ባነር በመዘርጋት የበልግ ወራት መድረሱን፤ ልምላሜ መምጣቱን ማወጅ ይገባኛል፡፡ የጠዋቷን ፀሐይም የተፈጥሮ ስጦጣየን መመገብ ይገባኛል እፈልጋለሁም፡፡” ሲል ሀሳብን ለባልጀራው ሰነዘረለት፡፡ እናም በቅሎ ማደግ ጀመረ፡፡
ሁለተኛው ዘርም በፈንታው እንዲህ አለ፡ መጀመሪያ ሀሳቡን ህምምም.. ሲል በመደመም ጀመረ፡፡ “ስሬን ወደ ጥልቁ አፈር ብለቀው በዛ ጨለማ ውስጥ ምን እንደሚገጥመኝ ከየት አውቅና ነው! ጉንቁሎቼን ባጎነቁልስ የቀንድ አውጣ ምግብ መሆኔ አይደለምን! እንዲሁም ደግሞ አበቦቼን ባፈነድቃቸው ህፃናቶች ቆርጠው ምድር ላይ በመጣል መጫዎቻ ያደርጉኛል፡፡ ስለሆነም ከዚህ ሁሉ የምጠበቅበት ምቹ ሁኔታ እስኪፈጠር መጠበቁ የተሻለ ሳይሆን አይቀርም” ሲል የመብቀል የሕይወት ተልዕኮውን ገታው፡፡
ይህን ሀሳባቸውን ከተነጋገሩ ከሰዓታት በኋላ በአካባቢው ምግቧን ፍለጋ ምድርን ስትጭር የነበረች ዶሮ ለመብቀል ምቹ ሁኔታን ሲጠብቅ የነበረውን ዘር አገኘችና ተመገበችው፡፡ ሥራን ለመስራት የማይመጣን ምቹ ሁኔታን መተበቅ ስራ እንዳንሰራ ከማድረግ ውጪ የሚፈጥረው ፋይዳ የለውም፡፡ እንቅፋትም እስከመጨረሻው ስለማየውቅ በዓለማችን እስካሁን ተሰሩ ወሳይኝ የሚባሉ ስራዎች በሙሉ በችግር ውስጥ እንጅ በተደላደለ ሁኔታ እንደልሆነ አብዛኛው መረጃ ይናገራል፡፡ There is no ideal condition for everything we can do what we have to do even in adverse condition.
/ምስጋናው ግሸን/
#ሼር
@yismakeworku
👍79❤44
#ቀን_ገንቢ
ምዕራፍ ፩ : ክፍል ፫
የሰው ልጅ የልምምድ ውጤት ነው። በልምምድ እንጅ በመወለድ ብቻ ሰው መሆን አይችልም። ከማፍቀር እስከ መቆርቆር ይለማመዳል። ማፍቀርን ያህል ያህል ነገር እንኳ አውቆ አይወለድም። እርሱን ብቻ አይደለም፤ መጥላትን ሳይቀር ይለማመዳል። ከማወቅ እስከ መናቅ፣ ከመወለድ እስከ መታነቅ፤ ከመድቀቅ እስከማድቀቅ፤ ከመጋባት እስከ መፍታት፤ ከስንፈት እስከ ጥረት ... ከመርመጥመጥ እስከ መፈርጠጥ፣ ከቆመጥ እስከ ነፍጥ...ተለማምዶት እንጅ ተሰጥቶት አይደለም። ከክህደት እስከ እምነት ካልተለማመደ አይችልም።
ከራሱ ያገኘው ማንነት የለውም። ሁሉም በሂደት እና በልምምድ የመጣ ነው። መልኩን ቆላ ሲወርድና ደጋ ሲወጣ ይቀያየራል። ልቡን በየግድሙ ይጥላል። ቀልቡን መቋጠሪያ የለውም። በመለማመድ አሁን የደረሰበትን እንጅ ወደፊት የሚሄድበትን ማንም ሊያውቅ አይችልም።
~ከክቡር ድንጋይ መፅሀፍ የተወሰደ
@yismakeworku
ምዕራፍ ፩ : ክፍል ፫
የሰው ልጅ የልምምድ ውጤት ነው። በልምምድ እንጅ በመወለድ ብቻ ሰው መሆን አይችልም። ከማፍቀር እስከ መቆርቆር ይለማመዳል። ማፍቀርን ያህል ያህል ነገር እንኳ አውቆ አይወለድም። እርሱን ብቻ አይደለም፤ መጥላትን ሳይቀር ይለማመዳል። ከማወቅ እስከ መናቅ፣ ከመወለድ እስከ መታነቅ፤ ከመድቀቅ እስከማድቀቅ፤ ከመጋባት እስከ መፍታት፤ ከስንፈት እስከ ጥረት ... ከመርመጥመጥ እስከ መፈርጠጥ፣ ከቆመጥ እስከ ነፍጥ...ተለማምዶት እንጅ ተሰጥቶት አይደለም። ከክህደት እስከ እምነት ካልተለማመደ አይችልም።
ከራሱ ያገኘው ማንነት የለውም። ሁሉም በሂደት እና በልምምድ የመጣ ነው። መልኩን ቆላ ሲወርድና ደጋ ሲወጣ ይቀያየራል። ልቡን በየግድሙ ይጥላል። ቀልቡን መቋጠሪያ የለውም። በመለማመድ አሁን የደረሰበትን እንጅ ወደፊት የሚሄድበትን ማንም ሊያውቅ አይችልም።
~ከክቡር ድንጋይ መፅሀፍ የተወሰደ
@yismakeworku
👍117❤24🔥9