Yismake Worku via @like
ወዳጆቼ በዚህ መድረክ በይበልጥ ምን እንድታገኙ ትሻላችሁ? 👆 ጽሁፍና ግጥሞቼን ✌️ስለኔ ወቅታዊ መረጃዎች
በእናንተ ምርጫ መሰረት እነሆ ፍላጎታችሁን አቀርባለሁ
ከአጥቂ ጋር አታጥቃ
የጨለመ ቢመስል፣ ፀሐዩ ባይወጣ፣ ሌሊቱን ብታየው፣
አይነጋም አትበል፣ ለፅልመያኮሱ ነውና ሚታየው፡፡
ጉረኛ ለጊዜው፣ ለጊዜው ቢጥርም፣
ከአጥቂ ጋር አታጥቃ፣ እንደመሸ አይቀርም፡፡
@yismakeworku
የጨለመ ቢመስል፣ ፀሐዩ ባይወጣ፣ ሌሊቱን ብታየው፣
አይነጋም አትበል፣ ለፅልመያኮሱ ነውና ሚታየው፡፡
ጉረኛ ለጊዜው፣ ለጊዜው ቢጥርም፣
ከአጥቂ ጋር አታጥቃ፣ እንደመሸ አይቀርም፡፡
@yismakeworku
ሁልጊዜም ለእኛ ለተራማጆች ቀኑ ልደታችን ቢሆንም ህዳር 7 ግን የልጄ የልደት ቀኑ ነው። የሰባትን ምስጢር በልጄ ውስጥ ፈለግኩት። እርሱም የበደሉህን ሁሉ ይቅር በል ይላል።
@yismakeworku
@yismakeworku
@yismakeworku
@yismakeworku
ይህች ተራራ አድዋ አካባቢ የምትገኝ ተራራ ናት። ድሮ መንጥረን ጣልያንን እንዳላባረርነው። አሁን ልጇን አዝላ እርቃን የቆመች ተራራ ቀረችን። እንደ ኢትዮጵያ፤ ልጇን አዝላ የምትሰደድ ተራራ።
@yismakeworku
@yismakeworku
👍1
ጠላቴ ይቅርታ
ጠላቴ ሆይ በርታ፣
ተበራታ በርታ፡፡
ፊቴም እንዲወዛ፣
እግሬ እንዲወረዛ፡፡
ጠላቴ ሲበዛ፣
ጦሬም እንዲበዛ፡፡
"ሰው አለሁ እንዲለኝ"
በርታና በድለኝ፡፡
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ እግር የሚወለድፍ፣
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ የሚያስቀድመውን መድፍ፣
ህልሜን ልይዘው ስል፣ እጄን የሚመታ፡፡
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ እግሬን የሚመታ፡፡
ጠላት የሌለው ሰው፣ ቢወጣ ቢወርድም፣
ወይ ህልም አላለመም፣ ወደ ህልሙ አይሄድም፡፡
ውሎዬ እንዲሰምር፣ ቀኔን የሚመቀኝ፣
አዳሬ እንዲሰምር፣ ሌሊት የሚመቀኝ፣
ጠላቴን አትንሳኝ፣
ጠላት አታሳጣኝ፡፡
ተባለ ምኑን ሰው ፣
ጠላት የሌለው ሰው!
እባክህ ፈጣሪ፣ ጥሩ ጠላት ፍጠር፣
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ የሚያስቀድም ጠጠር፡፡
(ይስማዕከ ወርቁ)
ጠላቴ ሆይ በርታ፣
ተበራታ በርታ፡፡
ፊቴም እንዲወዛ፣
እግሬ እንዲወረዛ፡፡
ጠላቴ ሲበዛ፣
ጦሬም እንዲበዛ፡፡
"ሰው አለሁ እንዲለኝ"
በርታና በድለኝ፡፡
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ እግር የሚወለድፍ፣
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ የሚያስቀድመውን መድፍ፣
ህልሜን ልይዘው ስል፣ እጄን የሚመታ፡፡
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ እግሬን የሚመታ፡፡
ጠላት የሌለው ሰው፣ ቢወጣ ቢወርድም፣
ወይ ህልም አላለመም፣ ወደ ህልሙ አይሄድም፡፡
ውሎዬ እንዲሰምር፣ ቀኔን የሚመቀኝ፣
አዳሬ እንዲሰምር፣ ሌሊት የሚመቀኝ፣
ጠላቴን አትንሳኝ፣
ጠላት አታሳጣኝ፡፡
ተባለ ምኑን ሰው ፣
ጠላት የሌለው ሰው!
እባክህ ፈጣሪ፣ ጥሩ ጠላት ፍጠር፣
ወደ ህልሜ ስጓዝ፣ የሚያስቀድም ጠጠር፡፡
(ይስማዕከ ወርቁ)
(አይስበርህ ሀዘን፣
አይዝራህ ሰቀቀን፤
ከመጠበቅ ማዶ፣
ይመጣል ያንተ ቀን፡፡)
ደህንነቱ የሚለው መጽሐፌ ደርሷል፡፡ ጭንቅላቴ ከውጭ ተተርትሮ፣ ከውስጥም እኔ እያማጥኩበት ምጤን እነሆ፡፡ ለማንኛውም የሁላችንም ፈጣሪ ይመስገን ብያለሁ፡፡ በወዳጆቼ ፀሎት እንጂ በእኔ ሥራ አይመስለኝም፡፡ ሁሉን ነገር ፈልፍያለሁ፡፡ የተቻለኝን እነሆ፡፡
@yismakeworku
አይዝራህ ሰቀቀን፤
ከመጠበቅ ማዶ፣
ይመጣል ያንተ ቀን፡፡)
ደህንነቱ የሚለው መጽሐፌ ደርሷል፡፡ ጭንቅላቴ ከውጭ ተተርትሮ፣ ከውስጥም እኔ እያማጥኩበት ምጤን እነሆ፡፡ ለማንኛውም የሁላችንም ፈጣሪ ይመስገን ብያለሁ፡፡ በወዳጆቼ ፀሎት እንጂ በእኔ ሥራ አይመስለኝም፡፡ ሁሉን ነገር ፈልፍያለሁ፡፡ የተቻለኝን እነሆ፡፡
@yismakeworku
👍3