YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.84K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ቤት እየፈረሰ ነው!

• አራት ልጆቼን ይዤ ጎዳና ላይ ወድቂያለሁ
• ከ 3ሺህ 685 ሕገወጥ ቤቶችን እያፈረስኩ ነው - የለገጣፎ ከንቲባ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ

ለገጣፎ የካ ዳሌ ሠፈር ‹‹አካባቢው ለጤና ተቋማትና ለትምህርት ቤት መስሪያ ይፈለጋል›› በሚል ምክንያት የነዋሪዎች ቤት እየፈረሰ ነው፡፡

የለገጣፎ አስተዳደር፤ ከንቲባ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ - በዚህ ሳምንት 3 ሺህ ቤቶች እንደሚያፈርስ እና በቀጣይም 12 ሺህ ሕገ ወጥ ቤቶች መኖራቸውን እነርሱም መፍረሳቸው አይቀርም ሲል ለ#OMN ተናግረዋል።

የአራት ልጆች እናት እንዲህ አለች …

‹‹ሕጋዊ ነን፡፡ የአፈር መሬት ግብር 97/98 ዓ.ም. ገብረናል፡፡ መብራት እንዲሁም ዉሃ ገብቶልናል፡፡ … የቤት ቁጥርም ተሰጥቶናል፡፡ ይሄው ተመልከተኝ አራት ልጆቼን ይዤ ጎዳና ላይ ወድቂያለሁ፡፡ ከመኖሪያ ቤታቸን አፈናቅሎ ቦታው ለ #Green Area ይፈለጋል ማለት ምን ማለት ነው? … መንግስት ‹‹ዜጎችን ከጎዳና እያነሳሁ ነው›› እያለ ከነልጆቼ ወደ ጎዳና መወርወር ምን ማለት ነው?›› በእንባ እያፈሰሰች …

ምንጭ:- ጌጡ ተመስገን
@YeneTube @FikerAssefa
#OMN ትናንት በኦኤምኤን የተላለፈን መልዕክት እየመረመረ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን መንግስት የሃሳብ ነጻነት በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲያድግ የፖለቲካ ምህዳሩን ቢያሰፋም አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ፈር እየለቀቁ እንደመጡ መመልከቱን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ገልጿል።

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንደሰን አንዷለም እንዳሉት፥ ተቋሙ በሁሉም ዘርፍ የሚዲያ ነጻነት እንዲረጋገጥና የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደቱን ለማገዝ ኢ ፍትሀዊ ሀሳቦች ሲተላለፉ በተለያየ መንገድ ለመፍታት እየጣረ ነው።

ባለፉት ስድስት ወራትም ለ49 የመገናኛ ብዙሃን ግብረ መልስ መሰጠቱን ጠቅሰው፥ ለአራት መገናኛ ብዙሃን ደግሞ የማስጠንቀቂያ መልዕክት በስልክና በደብዳቤ እንዲደርሳቸው ተደርጓል ብለዋል።

በሂደቱ የተወሰኑ ለውጦች ቢታዩም ከህገ መንግስቱም ሆነ ከብሮድካስት ባለስልጣን አዋጅ ተጻራሪ በሆነ መንገድ የሚጓዙ መገናኛ ብዙሃን መኖራቸውንም አንስተዋል።

አያይዘውም ባለስልጣኑ ከአንድነት ይልቅ ልዩነት ላይ ያተኮሩ እና ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ መገናኛ ብዙሃንን እንደማይታገስ አስረድተዋል።

ከዚህ አንጻርም ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩና ቁርሾ የሚፈጥሩ ሃሳቦችን በሚያስተላልፉ መገናኛ ብዙሃን ላይ በአዋጁ መሰረት እርምጃ መውሰድ እንደሚጀምርም ተናግረዋል።
ትናንት በኦ ኤም ኤን የህዝቦችን አንድነት የሚሸረሽርና ቁርሾን የሚፈጥር መልዕክት ሙሉ ተንቀሳቃሽ ምስል ባለስልጣኑ እንደደረሰውም ገልጸዋል።

አሁን ላይ መልዕክቱ በባለሙያዎችና አመራሮች እየተገመገመ ሲሆን፥ በአጭር ጊዜ መረጃውን በማጥራት ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግም አውስተዋል።

በማጣራት ሂደት ውስጥ የሚገኙ ውጤቶች የሚያስጠይቁ ሆነው ከተገኙም እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።

Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
የአርቲስት ሃጫሉ ሽኝት ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ወደ ትውልድ ስፍራው አምቦ!

በሺዎች የሚቆጠሩ የአርቲስቱ አድናቂዎች አሸኛኘት እያደረጉለት ይገኛሉ።

#OMN
@YeneTube @FikerAssefa