YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#የኦህዴድ/ኢህአዴግ ሊቀመንበር እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ አህመድ በ9ኛው የኦህዴድ ድርጅታዊ ጉባኤ ላይ ካስተላለፉት #መልዕክት መካከል፦⤵️⤵️

📌ወደተሻለ አሸናፊነት ለመሸጋገር ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦችን በማቀፍ በጋራ ልንሰራ ይገባል።

📌በኦሮሞ ስም ተደራጅታችሁ ያላችሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡን ከሚከፋፍሉ ድርጊቶች ተቆጥባችሁ አንድነቱን በሚያጠናክሩ ላይ ልታተኩሩ ይገባል።
የገነባናትን ሀገር ትተን በጥቃቅን ጉዳዮች አንጠመድ።

📌ከመበታተን ወጥተን በአሸናፊነት መንፈስ ሀገሪቷን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ ልንረባረብ ይገባል።
©fbc
@yenetube @mycase27
#የኦህዴድ እና የኢህአዴግ ሊቀመንበር እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር #ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በጅማ እየተካሄደ ባለው የኦህዴድ 9ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ላይ #ከተናገሩት የተወሰዱ #ዋና ዋና ነጥቦች:-⤵️⤵️

➡️ ኢትዮጵያን እንገነባለን፣ አፍሪካን እንገነባለን፣ ማንም ኃይል ደግሞ ከዚህ ሊያቆመን አይችልም፡፡

➡️ ኦሮሞ ማቀፍን፣ እናት የሌላቸውን ልጆች ማሳደግን ነው ያስተማረን፣ ኦሮሞ ከተዋጋ ያሸንፋል እንጂ ሰውን መግደልን አላስተማረንም፡፡

➡️ የዚህ አገር አንድነት ለማስጠበቅ ኦሮሞ ኃላፊነት አለበት፡፡

➡️ ኢትዮጵያ ከጠላት ጋር ባደረገችው ጦርነቶች ውስጥ ኦሮሞ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

➡️አባጅፋር ለኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያም ጭምር አርቀው የሚያስቡ ነበሩ፡፡

➡️ አሁን ባለንበት ዘመን በትናንትናው ስልት ማሸነፍ አይቻልም፡፡

➡️ ኦሮሞ አገር መምራት አይችልም የሚሉን አሉ፤ ኦሮሞ አገር መምራት ብቻ ሳይሆን አገር መገንባት ይችላል፤ ኦሮሞ ገዳን ለዓለም እንደ ሰጠ ሁሉ፣ ኦሮሞ በቅርቡ አዲስ ፍልስፍና ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ሰጥቶ ሊያሳያቸው ይፈልጋል፡፡

➡️ የሚዲያ ጦርነት፣ የጦር ሜዳ ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ጦርነት ማድረግ ስለምንችል ጠላቶቻችን ሁለት ሶስቴ ማሰብ አላባችሁ እንላለን፡፡

➡️ ከጠላት ጋር ሆናችሁ የኦሮሞ ትግልን ወደኋላ ለመመለስ ያሰባችሁ ካላችሁ ከጠላት ለይተን አናያችሁም፡፡

➡️ የህግ የበላይነት የማስከበር ኃላፊነት ለማንም አሳልፈን አንሰጥም፡፡

➡️ ከዚህ በኋላ በኦሮሞ ስም መነገድ አይቻልም፡፡

➡️ አስራ አምስት፣ ሃያ ሆኖ ለኦሮሞ መታገል አያስፈልግም፤ ከበዛ ሁለት ሶስት ፓርቲዎች ለኦሮሞ በቂ ናቸው፡፡

➡️ አብሮ መቆም ማለት ጠዋት ጠዋት እዚህ መቆም ከሰዓት፣ ከሰዓት ደግሞ እዚያ መቆም ማለት አይደለም፡፡

➡️ ከሁሉም ኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በጋራ በአንድነት ተባብረን መስራት አለብን፡፡

➡️ ኦሮሞነት በርካታ ነገሮችን አስተምሮናል ፤ በገዳ ስርዓት መሰረት ብሔር ብሔረሰቦችን አቅፈን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል፡፡

➡️ዋናው መልዕክት አሸናፊን ሀሳብ መያዝ ነው
©ebc
@yenetube @mycase27