እስራኤል ውስጥ የሚኖር አንድ #ኤርትራዊ ስደተኛ #የአንድ_ሚሊዮን ሸክል ወይም የ278 ሺህ ዶላር ሎተሪ ወጣለት።
እድለኛው ብዙ ካርዶች ገዝቶ ለሰዓታት ሲፍቅ ከቆየ በኋላ አሸናፊውን ቁጥር ማግኘቱን ሎተሪው የተገዛበት ደቡብ ቴላቪቭ የሚገኘው ኪዮስክ ባለቤት ቻናል 12 ለተባለ ጣቢያ ተናግረዋል። ሎተሪው እንደወጣለት ሲታወቅ እሱም ሆነ በኪዮስኩ ውስጥ የነበሩት ለጊዜው መደንገጣቸውን የተናገሩት የክዮስኩ ባለቤት ስደተኛው ስንት ካርዶችን እንደገዛ ግን አልገለጹም።
ስደተኛው ቁጥራቸው ያልተገለፀ ካርዶችን ገዝቶ እድሉን ሲሞክር አጠገቡ የነበረው ጓደኛው በቃህ ቢለውም ካርዶቹን መፋቅ መቀጠሉንም ተናግረዋል። የጀርመን ዜና አገልግሎት እንደዘገበው በክዮስኩ ውስጥ የተቀረጸ ቪድዮ እድለኛው ኤርትራዊ በክዮስኩ ውስጥ የነበሩትን ሰዎች በደስታ ሲያቅፍ እና ሲጨብጥ ያሳያል።
ምንጭ:- Dw
@YeneTube @FikerAssefa
እድለኛው ብዙ ካርዶች ገዝቶ ለሰዓታት ሲፍቅ ከቆየ በኋላ አሸናፊውን ቁጥር ማግኘቱን ሎተሪው የተገዛበት ደቡብ ቴላቪቭ የሚገኘው ኪዮስክ ባለቤት ቻናል 12 ለተባለ ጣቢያ ተናግረዋል። ሎተሪው እንደወጣለት ሲታወቅ እሱም ሆነ በኪዮስኩ ውስጥ የነበሩት ለጊዜው መደንገጣቸውን የተናገሩት የክዮስኩ ባለቤት ስደተኛው ስንት ካርዶችን እንደገዛ ግን አልገለጹም።
ስደተኛው ቁጥራቸው ያልተገለፀ ካርዶችን ገዝቶ እድሉን ሲሞክር አጠገቡ የነበረው ጓደኛው በቃህ ቢለውም ካርዶቹን መፋቅ መቀጠሉንም ተናግረዋል። የጀርመን ዜና አገልግሎት እንደዘገበው በክዮስኩ ውስጥ የተቀረጸ ቪድዮ እድለኛው ኤርትራዊ በክዮስኩ ውስጥ የነበሩትን ሰዎች በደስታ ሲያቅፍ እና ሲጨብጥ ያሳያል።
ምንጭ:- Dw
@YeneTube @FikerAssefa
የኒፕሲ ሐስል ገዳይ ተያዘ!
በአባቱ #ኤርትራዊ እንደሆነ የተነገረው የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ #ኒፕሲ_ሐስልን ገድሏል ተብሎ የተጠረጠረው ግለሰብን ፖሊስ #መያዙን አስታወቀ።
ባለስልጣናት እንዳሉት ኤሪክ ሆልደር የተባለው ግለሰብ ከእሁድ ዕለቱ ጥቃት ጋር በተያያዘ በፖሊስ ሲፈለግ ነበር። ኒፕሲ ሐስል በተሰነዘረበት ጥቃት የተገደለው የእራሱ በሆነው የልብስ መደብር አቅራቢያ ነበር።በጥቃቱ ሌሎች ሁለት ሰዎች የመቁሰል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
እሁድ ዕለት በተከፈተበት ተኩስ የተገደለው የራፕ ሙዚቀኛው ኒፕሲ ሐስልን ለማሰብ በተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ላይ በርካታ አድናቂዎቹ የተገኙ ሲሆን በስፍራው በተፈጠረ መጨናነቅ ቢያንስ 19 ሠዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ ገልጿል።
ትክክለኛ መጠሪያው ኤርሚያስ ዳቪድሰን አስገዶም የሆነው ኒፕሲ ሐስል በደቡባዊ ሎስአንጀለስ ውስጥ ያደገ ሲሆን በታዳጊነት እድሜው የአንድ የጎዳና ላይ የወሮበሎች ቡድን አባል ነበረ።
በኋላ ላይ ግን ከቡድኑ በመውጣት በዙሪያው ያለን ማህበረሰብን ማስተባበርና መርዳት ጀምሮ በጥበብ ሥራዎች ውስጥም አስተዋጽኦን ሲያበረክት ቆይቷል።ከመገደሉ ቀደም ብሎ በትዊተር ገጹ ላይ “ጠንካራ ጠላት ካለህ መባረክ ነው” ሲል አስፍሮ ነበር።
ምንጭ፡BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአባቱ #ኤርትራዊ እንደሆነ የተነገረው የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ #ኒፕሲ_ሐስልን ገድሏል ተብሎ የተጠረጠረው ግለሰብን ፖሊስ #መያዙን አስታወቀ።
ባለስልጣናት እንዳሉት ኤሪክ ሆልደር የተባለው ግለሰብ ከእሁድ ዕለቱ ጥቃት ጋር በተያያዘ በፖሊስ ሲፈለግ ነበር። ኒፕሲ ሐስል በተሰነዘረበት ጥቃት የተገደለው የእራሱ በሆነው የልብስ መደብር አቅራቢያ ነበር።በጥቃቱ ሌሎች ሁለት ሰዎች የመቁሰል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
እሁድ ዕለት በተከፈተበት ተኩስ የተገደለው የራፕ ሙዚቀኛው ኒፕሲ ሐስልን ለማሰብ በተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ላይ በርካታ አድናቂዎቹ የተገኙ ሲሆን በስፍራው በተፈጠረ መጨናነቅ ቢያንስ 19 ሠዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ ገልጿል።
ትክክለኛ መጠሪያው ኤርሚያስ ዳቪድሰን አስገዶም የሆነው ኒፕሲ ሐስል በደቡባዊ ሎስአንጀለስ ውስጥ ያደገ ሲሆን በታዳጊነት እድሜው የአንድ የጎዳና ላይ የወሮበሎች ቡድን አባል ነበረ።
በኋላ ላይ ግን ከቡድኑ በመውጣት በዙሪያው ያለን ማህበረሰብን ማስተባበርና መርዳት ጀምሮ በጥበብ ሥራዎች ውስጥም አስተዋጽኦን ሲያበረክት ቆይቷል።ከመገደሉ ቀደም ብሎ በትዊተር ገጹ ላይ “ጠንካራ ጠላት ካለህ መባረክ ነው” ሲል አስፍሮ ነበር።
ምንጭ፡BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ቫይረሱ እንዳለባቸው የተረጋገጠው ዘጠኙም ግለሰቦች የጉዞ ታሪክ ያላቸው ናቸው።
➡️ከግለሰቦቹ መካከል #ሰባቱ ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ፤ አንድ #ኤርትራዊ ቀሪዋ ደግሞ የ #ህንድ ዜግነት ያላት ናት።
➡️አራቱ ኢትዮጵያዊያን ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በለይቶ ማቆያ ክትትል ሲያደርጉ የነበሩ መሆኑንም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
➡️ሁለቱ የቱርክ፤ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ደግሞ የእንግሊዝ አገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆን፤ ሁሉም በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን አውስተዋል።
➡️የ20 ዓመቷ ህንዳዊት የአሜሪካ እንዲሁም የ40 ዓመቱ ኤርትራዊ ደግሞ የዱባይ ጉዞ ታሪክ ያላት ናቸው።
➡️በጽኑ ህሙማን ክፍል ከሚገኙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ የጤና መሻሻል በማሳየቱ ከክፍሉ መውጣቱንም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።
➡️እስካሁን ባለው ሂደትም በኢትዮጵያ ለሶስት ሺህ 232 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉን ጠቁመው፤ ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች መካከል 57ቱ የህክምና ክትትል ይገኛሉ።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
➡️ከግለሰቦቹ መካከል #ሰባቱ ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ፤ አንድ #ኤርትራዊ ቀሪዋ ደግሞ የ #ህንድ ዜግነት ያላት ናት።
➡️አራቱ ኢትዮጵያዊያን ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በለይቶ ማቆያ ክትትል ሲያደርጉ የነበሩ መሆኑንም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
➡️ሁለቱ የቱርክ፤ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ደግሞ የእንግሊዝ አገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ሲሆን፤ ሁሉም በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲያደርጉ መቆየታቸውን አውስተዋል።
➡️የ20 ዓመቷ ህንዳዊት የአሜሪካ እንዲሁም የ40 ዓመቱ ኤርትራዊ ደግሞ የዱባይ ጉዞ ታሪክ ያላት ናቸው።
➡️በጽኑ ህሙማን ክፍል ከሚገኙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ የጤና መሻሻል በማሳየቱ ከክፍሉ መውጣቱንም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።
➡️እስካሁን ባለው ሂደትም በኢትዮጵያ ለሶስት ሺህ 232 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉን ጠቁመው፤ ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች መካከል 57ቱ የህክምና ክትትል ይገኛሉ።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa