በሽሽት ላይ የነበሩ የሶማሌ ክልል ሁለት ባለስልጣናት ሶማሊላንድ ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ።
የሶማሊላንድ ፖሊስ እንዳስታወቀው የኢትዮ ሶማሊ ክልል የፍትህ ቢሮ ሀላፊ #አብዲ ጃማ እና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ #ኢብራሒም አደን መሀድ ሀርጌሳ ውስጥ ተይዘው በፖሊስ እጅ ይገኛሉ።
ሁለቱ ሀላፊዎች የክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ መሀመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) በፌደራል መንግስት ሀይሎች መያዛቸውን ተከትሎ ከጅጅጋ ወደ ጎረቤት ሶማሊላንድ እንደሸሹ ጋሮዌ የተባለው የሶማሊላንድ ጋዜጣ ዘግቧል።
*በሌላ በኩል ለዓመታት በስደት የቆዩት የሶማሌ ክልል የመብት ተሟጋቾች የቀድሞ የፓርላማ አባል መሀመድ ድርዬ እና የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ኢሌ አማካሪ አብዱላሂ ሁሴን ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል። በሶማሌና ኦሮሞ ማህበረሰብ መካከል የነበረውን ግጭት ለመፍታት እንሰራለን ብለዋል። ለውጡን ለመደገፍም መዘጋጀታቸውን ነግረውናል።
ምንጭ ፦ ዋዜማ ራዲዮ
@yenetube @mycase27
የሶማሊላንድ ፖሊስ እንዳስታወቀው የኢትዮ ሶማሊ ክልል የፍትህ ቢሮ ሀላፊ #አብዲ ጃማ እና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ #ኢብራሒም አደን መሀድ ሀርጌሳ ውስጥ ተይዘው በፖሊስ እጅ ይገኛሉ።
ሁለቱ ሀላፊዎች የክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ መሀመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) በፌደራል መንግስት ሀይሎች መያዛቸውን ተከትሎ ከጅጅጋ ወደ ጎረቤት ሶማሊላንድ እንደሸሹ ጋሮዌ የተባለው የሶማሊላንድ ጋዜጣ ዘግቧል።
*በሌላ በኩል ለዓመታት በስደት የቆዩት የሶማሌ ክልል የመብት ተሟጋቾች የቀድሞ የፓርላማ አባል መሀመድ ድርዬ እና የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ኢሌ አማካሪ አብዱላሂ ሁሴን ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል። በሶማሌና ኦሮሞ ማህበረሰብ መካከል የነበረውን ግጭት ለመፍታት እንሰራለን ብለዋል። ለውጡን ለመደገፍም መዘጋጀታቸውን ነግረውናል።
ምንጭ ፦ ዋዜማ ራዲዮ
@yenetube @mycase27