ኢትዮጵያ በወጪ ንግድ ታሪኳ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ማግኘቷ ተነገረ።
በጊዜ ማዕቀፉ ከ5.3 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ከወጪ ንግድ ተገኝቷል ተብሏል።ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ከ5.3 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ከ ወጪ ንግድ ማግኘቷ ተነግሯል።
ይህን ያህል ገቢ ሲገኝ በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሣሁን ጎፌ ተናግረዋል።በቢሾፍቱ እየተካሄደ ባለው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ዘርፍ የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ነው ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ታሪክ ከፍተኛው ገቢ ነው ያሉት።
በ2016 ሙሉ የበጀት ዓመት #ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ያገኘችው 3 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደነበር በጊዜው ተነግሯል።በቀዳሚው የ2015 ሙሉ የበጀት ዓመት ደግሞ 3.7 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር መገኘቱ ይታወሳል።ኢትዮጵያ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከወጪ ንግድ የሚገኘው ገቢ በየጊዜው ዕድገት እንዲያሳይ ማገዙ ተደጋግሞ ይጠቀሳል።
ማሻሻያውቅ የላኪዎችን የረጅም ጊዜ ጥያቄ የመለሰና በዘርፋ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው ሲል የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናግሯል።ቀደም ሲል ግን ዘርፉ የተወሳሰቡ ችግሮች ያሉበት ሆኖ ቆይቷል።
የምርት ጥራት መጓደል ፤ የመዳረሻ ቦታዎች ማነስ ፤ እሴት ተጨምሮባቸው የሚላኩ ምርቶች ብዙ አለመሆን ፤ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እና አለም አቀፍ ጉዳዮች የዘርፉ ችግሮች ተብለው በተደጋጋሚ ሲጠቀሱ የቆዩ ናቸው፡፡ህገ ወጥ ንግድና በዘርፉ የተሰማሩ አካላት የስነ ምግባር ጉድለቶችም የዘርፉ ተጨማሪ ምክንያቶች በሚል ይነሳሉ ቡና ፤ የጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች እንዲሁም የቁም እንስሳት ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ልካ ገቢ ከምታገኙባቸው መካከል ሲጠቀሱ ወርቅ እና ጫትም ሌሎቹ ናቸው፡፡
በዘጠኝ ወሩ የተገኘው ገቢ ኢትዮጵያ ከውጪ ለምትገዛቸው ምርቶች ከምታወጣው ዶላር አንጻር ሲታይ ግን አሁንም አነስተኛ የሚባል ነው፡፡ነዳጅ፣ የአፈር ማደበርያ እና የተለያዩ ምርቶች ከውጭ ለማስገባት በየዓመቱ በአማካይ 13 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደምታወጣ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
በጊዜ ማዕቀፉ ከ5.3 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ከወጪ ንግድ ተገኝቷል ተብሏል።ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ከ5.3 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ከ ወጪ ንግድ ማግኘቷ ተነግሯል።
ይህን ያህል ገቢ ሲገኝ በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሣሁን ጎፌ ተናግረዋል።በቢሾፍቱ እየተካሄደ ባለው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ዘርፍ የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ነው ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ታሪክ ከፍተኛው ገቢ ነው ያሉት።
በ2016 ሙሉ የበጀት ዓመት #ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ያገኘችው 3 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደነበር በጊዜው ተነግሯል።በቀዳሚው የ2015 ሙሉ የበጀት ዓመት ደግሞ 3.7 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር መገኘቱ ይታወሳል።ኢትዮጵያ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከወጪ ንግድ የሚገኘው ገቢ በየጊዜው ዕድገት እንዲያሳይ ማገዙ ተደጋግሞ ይጠቀሳል።
ማሻሻያውቅ የላኪዎችን የረጅም ጊዜ ጥያቄ የመለሰና በዘርፋ ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው ሲል የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናግሯል።ቀደም ሲል ግን ዘርፉ የተወሳሰቡ ችግሮች ያሉበት ሆኖ ቆይቷል።
የምርት ጥራት መጓደል ፤ የመዳረሻ ቦታዎች ማነስ ፤ እሴት ተጨምሮባቸው የሚላኩ ምርቶች ብዙ አለመሆን ፤ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እና አለም አቀፍ ጉዳዮች የዘርፉ ችግሮች ተብለው በተደጋጋሚ ሲጠቀሱ የቆዩ ናቸው፡፡ህገ ወጥ ንግድና በዘርፉ የተሰማሩ አካላት የስነ ምግባር ጉድለቶችም የዘርፉ ተጨማሪ ምክንያቶች በሚል ይነሳሉ ቡና ፤ የጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች እንዲሁም የቁም እንስሳት ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ልካ ገቢ ከምታገኙባቸው መካከል ሲጠቀሱ ወርቅ እና ጫትም ሌሎቹ ናቸው፡፡
በዘጠኝ ወሩ የተገኘው ገቢ ኢትዮጵያ ከውጪ ለምትገዛቸው ምርቶች ከምታወጣው ዶላር አንጻር ሲታይ ግን አሁንም አነስተኛ የሚባል ነው፡፡ነዳጅ፣ የአፈር ማደበርያ እና የተለያዩ ምርቶች ከውጭ ለማስገባት በየዓመቱ በአማካይ 13 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደምታወጣ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
😁33👍20❤2👀1
YeneTube
Photo
#Update
ብፁዕ አቡነ ገብርኤል በመኖሪያ ቤታቸው ተአቅበው እንዲቆዩ ቋሚ ሲኖዶስ ወሳኔ አሳለፈ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያኗ የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬ መደበኛ ጉባኤ ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት ውይይት ካደረገ በኋላ ውሳኔ አሳልፏል።
በዚህም ፦
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያኗን አባቶች፣ ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ 5 አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
ቋሚ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ ወስኗል።
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ ማርያም ቤዛዊተ ዓለም ” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያኗ የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ ወንሷል።
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ ወስኗል።
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ እንዲደረግ ወስኗል።
መረጃው የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
ብፁዕ አቡነ ገብርኤል በመኖሪያ ቤታቸው ተአቅበው እንዲቆዩ ቋሚ ሲኖዶስ ወሳኔ አሳለፈ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያኗ የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬ መደበኛ ጉባኤ ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት ውይይት ካደረገ በኋላ ውሳኔ አሳልፏል።
በዚህም ፦
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያኗን አባቶች፣ ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ 5 አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
ቋሚ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ ወስኗል።
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ ማርያም ቤዛዊተ ዓለም ” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያኗ የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ ወንሷል።
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ ወስኗል።
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ እንዲደረግ ወስኗል።
መረጃው የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
👍98😁25👎15❤4
ተከሰሱ
18 ከፍተኛ የትግራይ አመራሮች በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሰሱ
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤልን ጨምሮ 18 ከፍተኛ የትግራይ የፖለቲካ እና የጦር መሪዎች በፌደራል መንግስት በተሾሙ 64 የጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች እና ሰራተኞች ላይ ከጥቅምት 2013 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም ድረስ በነበረው የትግራይ ደም አፋሳሽ ጦርነት የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ለጠቅላይ የምርመራ መምሪያ የቀረበው የጽሁፍ ክስ እንዳመለከተው የተጠቀሱት ተከሳሾች በጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች እና ሰራተኞች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል።
ክሱ የቀረበው በአቶ አበራ ንጉስ የተባሉ የህግ ምሁር እና ጠበቃ እንዲሁም ከጥቅምት እስከ ሰኔ 2013 ዓ.ም በፌደራል መንግስት በተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ያገለገሉ ግለሰብ ናቸው።
@Yenetube @Fikerassefa
18 ከፍተኛ የትግራይ አመራሮች በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሰሱ
ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤልን ጨምሮ 18 ከፍተኛ የትግራይ የፖለቲካ እና የጦር መሪዎች በፌደራል መንግስት በተሾሙ 64 የጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች እና ሰራተኞች ላይ ከጥቅምት 2013 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም ድረስ በነበረው የትግራይ ደም አፋሳሽ ጦርነት የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ለጠቅላይ የምርመራ መምሪያ የቀረበው የጽሁፍ ክስ እንዳመለከተው የተጠቀሱት ተከሳሾች በጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች እና ሰራተኞች ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል።
ክሱ የቀረበው በአቶ አበራ ንጉስ የተባሉ የህግ ምሁር እና ጠበቃ እንዲሁም ከጥቅምት እስከ ሰኔ 2013 ዓ.ም በፌደራል መንግስት በተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ያገለገሉ ግለሰብ ናቸው።
@Yenetube @Fikerassefa
😁37👍28❤2
" እስካሁን የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል። የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል " - ፖሊስ
ዛሬ ከቀኑ 7 ሠዓት 30 ከሙከጡሪ ወደ ጂዳ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ አይሱዚ ቅጥቅጥ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከለሚ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ከነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው ከባድ የትራፊክ አደጋ መድረሱን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
አደጋው የደረሰው በኦሮሚያ ክልል፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ዋጫሌ ወረዳ ሙከጡሪ ከተማ አቅራቢያ መቼላ ቀበሌ ቄሌምቶ ላይ ነው።
እስከ አሁን የ6 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
ከሟቾች በተጨማሪ 21 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም በሌሎች 17 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱ የዞነ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ክፍል ኃላፊ ም/ ኢንስፔክተር ታከለ ቶሌራ ተናግረዋል፡፡
የአደጋ ከባድ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር አሁን ካለው ሊጨምር እንደሚችል ተጠቁሟል።
Via :- ኤፍኤምሲ
@Yenetube @Fikerassefa
ዛሬ ከቀኑ 7 ሠዓት 30 ከሙከጡሪ ወደ ጂዳ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ አይሱዚ ቅጥቅጥ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከለሚ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ከነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው ከባድ የትራፊክ አደጋ መድረሱን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
አደጋው የደረሰው በኦሮሚያ ክልል፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ዋጫሌ ወረዳ ሙከጡሪ ከተማ አቅራቢያ መቼላ ቀበሌ ቄሌምቶ ላይ ነው።
እስከ አሁን የ6 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
ከሟቾች በተጨማሪ 21 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም በሌሎች 17 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱ የዞነ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ክፍል ኃላፊ ም/ ኢንስፔክተር ታከለ ቶሌራ ተናግረዋል፡፡
የአደጋ ከባድ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር አሁን ካለው ሊጨምር እንደሚችል ተጠቁሟል።
Via :- ኤፍኤምሲ
@Yenetube @Fikerassefa
😭17👍16❤1
ከ14 አመት በፊት የሙምባይ የሽብር ጥቃት አቀናባሪ የተባለው የሀፊዝ ሰኢድን ፓኪስታን አስሬዋለው ብትልም የህንድ መገናኛ ብዙሃን ደግሞ በላሆር እጅግ የቅንጦት እና ጥብቅ ጥበቃ የሚደረግበትን ቦታ እየኖረ ነው አሉ
ፓኪስታን ሳኢድ ከእስር ቤት ውጭ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ ብትገልጽም፣ የህንድ መገናኛ ብዙሃን አገኘነው የሚሉት አዳዲስ የሳተላይት ምስሎች እና ቪዲዮዎች 24/7 ጥበቃ እየተደረገለት በምቾት እንደሚኖር ያሳያሉ።
ሙምባይ የሽብር ጥቃት ዋና አቀናባሪ እና የላሽካር ኢ ጦይባ መሪ የሆነውን እና አሁን ደግሞ ሚያዝያ 14 ቀን በፓሃልጋም 26 ንፁሀን ዜጎችን ለሞት ላበቃው የሽብር ጥቃት አቀናባሪ ተብሎ የሚጠረጠረውን የሀፊዝ ሰኢድን አሁን የሚገኝበትን መደበቂያ ቦታ በህንድ መገናኛ ብዙሃን ታይቷል ።
ኢስላማባድ በሽብር ፋይናንስ ወንጀል እስር ቤት ውስጥ ነው ከሚለው ይፋዊ አቋም በተቃራኒ ሳኢድ በፓኪስታን ላሆር በሚገኝ ከፍተኛ ህዝብ በሚኖርበት አካባቢ ጥብቅ ጥበቃ እየተደረገለት ይኖራልም ብለዋል።
ፓኪስታን ሳኢድ ከእስር ቤት ውጭ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ ብትገልጽም፣ የህንድ መገናኛ ብዙሃን አገኘነው የሚሉት አዳዲስ የሳተላይት ምስሎች እና ቪዲዮዎች 24/7 ጥበቃ እየተደረገለት በምቾት እንደሚኖር ያሳያሉ።
ሙምባይ የሽብር ጥቃት ዋና አቀናባሪ እና የላሽካር ኢ ጦይባ መሪ የሆነውን እና አሁን ደግሞ ሚያዝያ 14 ቀን በፓሃልጋም 26 ንፁሀን ዜጎችን ለሞት ላበቃው የሽብር ጥቃት አቀናባሪ ተብሎ የሚጠረጠረውን የሀፊዝ ሰኢድን አሁን የሚገኝበትን መደበቂያ ቦታ በህንድ መገናኛ ብዙሃን ታይቷል ።
ኢስላማባድ በሽብር ፋይናንስ ወንጀል እስር ቤት ውስጥ ነው ከሚለው ይፋዊ አቋም በተቃራኒ ሳኢድ በፓኪስታን ላሆር በሚገኝ ከፍተኛ ህዝብ በሚኖርበት አካባቢ ጥብቅ ጥበቃ እየተደረገለት ይኖራልም ብለዋል።
👍19
በአዲስ አበባ ከተማ የአርሶ አደር ይዞታ ይገባኛል መብት ያቀረቡ ሰባት ሺህ ገደማ አመልካቾች ጥያቄቸው ውድቅ ተደረገ!
በአዲስ አበባ ከተማ በአርሶ አደርነት እና በአርሶ አደር ልጅነት የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ሰርተፍኬት እንዲሰጣቸው ካመለከቱ 27 ሺህ ያህል አመልካቾች ውስጥ፤ 7 ሺህ የሚጠጉት ያቀረቡት ጥያቄ “ውድቅ መደረጉን” የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። የይገባኛል መብት ጥያቄዎቹ ውድቅ የተደረጉት፤ የቀረቡት ጥያቄዎች ማጣራት ከተደረገባቸው በኋላ ትክክለኛ እንዳልሆኑ በመረጋገጡ እንደሆነ ከንቲባዋ ገልጸዋል።
ከንቲባዋ ይህንን ያሉት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 22 በተካሄደው የአዲስ አበባ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ ነው። ጥያቄውን ያቀረቡት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የምክር ቤት ተመራጭ የሆኑት እሌኒ አየለ፤ ከአርሶ አደሮች የይዞታ መብት ጋር በተያያዘ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስንተዋል።
“የአገልግሎት ጥራት እና ፍጥነት በተመለከተ አንዳንድ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዳሉ ከአርሶ አደሮች እየተነሳ ነው” ያሉት እሌኒ፤ ለዚህ ችግር መፍትሔ እንደሚበጅለት ጠይቀዋል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፤ ትክክለኛ አርሶ አደሮች የይዞታ መብታቸው እንዳይነፈግ እና ሌሎችም ያለአግባብ እንዳይጠቀሙ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።
ለጥያቄው ምላሽ የሰጡት ከንቲባ አዳነች፤ እርሳቸው የሚመሩት የከተማይቱ አስተዳደር ለጥያቄዎቹ “የተሟላ ምላሽ” አለመስጠቱን አምነዋል። የእዚህ ምክንያቱ በአርሶ አደር ስም “አላግባብ ለመጠቀም” በሚደረጉ ጥረቶች፤ “ብዙ ጫናዎች የመፍጠር ሂደቶች” ስለነበሩ እንደሆነ አብራርተዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ በአርሶ አደርነት እና በአርሶ አደር ልጅነት የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ሰርተፍኬት እንዲሰጣቸው ካመለከቱ 27 ሺህ ያህል አመልካቾች ውስጥ፤ 7 ሺህ የሚጠጉት ያቀረቡት ጥያቄ “ውድቅ መደረጉን” የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። የይገባኛል መብት ጥያቄዎቹ ውድቅ የተደረጉት፤ የቀረቡት ጥያቄዎች ማጣራት ከተደረገባቸው በኋላ ትክክለኛ እንዳልሆኑ በመረጋገጡ እንደሆነ ከንቲባዋ ገልጸዋል።
ከንቲባዋ ይህንን ያሉት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 22 በተካሄደው የአዲስ አበባ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ ነው። ጥያቄውን ያቀረቡት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የምክር ቤት ተመራጭ የሆኑት እሌኒ አየለ፤ ከአርሶ አደሮች የይዞታ መብት ጋር በተያያዘ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስንተዋል።
“የአገልግሎት ጥራት እና ፍጥነት በተመለከተ አንዳንድ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዳሉ ከአርሶ አደሮች እየተነሳ ነው” ያሉት እሌኒ፤ ለዚህ ችግር መፍትሔ እንደሚበጅለት ጠይቀዋል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፤ ትክክለኛ አርሶ አደሮች የይዞታ መብታቸው እንዳይነፈግ እና ሌሎችም ያለአግባብ እንዳይጠቀሙ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።
ለጥያቄው ምላሽ የሰጡት ከንቲባ አዳነች፤ እርሳቸው የሚመሩት የከተማይቱ አስተዳደር ለጥያቄዎቹ “የተሟላ ምላሽ” አለመስጠቱን አምነዋል። የእዚህ ምክንያቱ በአርሶ አደር ስም “አላግባብ ለመጠቀም” በሚደረጉ ጥረቶች፤ “ብዙ ጫናዎች የመፍጠር ሂደቶች” ስለነበሩ እንደሆነ አብራርተዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
👍31❤5😁5😭3👀3
በ780,000 ቅድመ ክፍያ በመሀል ካዛንቺስ የቤት ባለቤት ይሁኑ ‼️
እጅግ ውብ ዕይታ ያላቸው ቤቶች
ከ 1 መኝታ እስከ ባለ 4 መኝታ
👉ባለ አንድ መኝታ 45, 55 ,60 ካ.ሜ
👉ባለ ሁለት መኝታ 80,ካ.ሜ
👉ባለ ሶስት መኝታ 95,105,115 ካ.ሜ
👉ባለ አራት መኝታ 140 ,160 ካ.ሜ
✍️ ቅድመ ክፍያ 15%
📹 (ከ780,000ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ)
➡️ እስከ 20% የዋጋ ቅናሽ አድርገናል
❇️ በ 18 ወራት የሚረከቡት ቤት💁
📍በግቢው ውስጥ
➾ ት/ቤት እና የጤና ማዕከል
➾ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ መጫወቻ
➾መዋኛ ገንዳ
➾የሳይክል እና የእግር ሽርሽር ስፍራዎች
➾ሰፊ የመኪና መቆሚያ ከ24/7 ጥበቃ ጋር
➾የመኪና ቻርጀር ስፍራዎች
📍በግቢው ዙሪያ
➾ፓርኮች ና የወንዝ ዳር ልማት
➾አለማቀፍ ት/ቤትና ሆስፒታል
➾የእምነት ተቋማ
📍የቤቶቹ እይታ
➤ ወደ ቤተ መንግስት ( ጊቢ ገብርኤል )
➤ ወደ ያካ ተራራ ጫካ
➤ ወደ ወንዝ ዳር ልማት
➤ ወደ ወዳጅነት ፓርክ
👉 ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል
❇️ ከሀገር ውጭ ያላችሁ ደንበኞች በወኪል መግዛት እንደምትችሉ እናሳውቃለን ።
ለምዝገባ 📲 0950123353 ወይም
በ whatsapp :-https://wa.me/251950123353
አሁኑ ይደውሉ
እጅግ ውብ ዕይታ ያላቸው ቤቶች
ከ 1 መኝታ እስከ ባለ 4 መኝታ
👉ባለ አንድ መኝታ 45, 55 ,60 ካ.ሜ
👉ባለ ሁለት መኝታ 80,ካ.ሜ
👉ባለ ሶስት መኝታ 95,105,115 ካ.ሜ
👉ባለ አራት መኝታ 140 ,160 ካ.ሜ
✍️ ቅድመ ክፍያ 15%
📹 (ከ780,000ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ)
➡️ እስከ 20% የዋጋ ቅናሽ አድርገናል
❇️ በ 18 ወራት የሚረከቡት ቤት💁
📍በግቢው ውስጥ
➾ ት/ቤት እና የጤና ማዕከል
➾ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ መጫወቻ
➾መዋኛ ገንዳ
➾የሳይክል እና የእግር ሽርሽር ስፍራዎች
➾ሰፊ የመኪና መቆሚያ ከ24/7 ጥበቃ ጋር
➾የመኪና ቻርጀር ስፍራዎች
📍በግቢው ዙሪያ
➾ፓርኮች ና የወንዝ ዳር ልማት
➾አለማቀፍ ት/ቤትና ሆስፒታል
➾የእምነት ተቋማ
📍የቤቶቹ እይታ
➤ ወደ ቤተ መንግስት ( ጊቢ ገብርኤል )
➤ ወደ ያካ ተራራ ጫካ
➤ ወደ ወንዝ ዳር ልማት
➤ ወደ ወዳጅነት ፓርክ
👉 ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል
❇️ ከሀገር ውጭ ያላችሁ ደንበኞች በወኪል መግዛት እንደምትችሉ እናሳውቃለን ።
ለምዝገባ 📲 0950123353 ወይም
በ whatsapp :-https://wa.me/251950123353
አሁኑ ይደውሉ
👍9❤1👎1
🌏IAT & IAIC INTERNATIONAL STUDENT FAIR🌎
✨Ready to study abroad and change your life?
🎓This is your chance to meet top university representatives from:
USA 🇺🇸 Canada 🇨🇦 Sweden 🇸🇪
Germany 🇩🇪 France 🇫🇷 Finland 🇫🇮 Denmark 🇩🇰 and more!
📆 May 3 & 4
🕐 3:00 - 10:00 (LT)
📍Ghion Hotel
Don’t forget to bring:
🪪Passport or Birth certificate
📚Transcripts or Student copy
✅Entrance Fee: FREE!!
💡Opportunities:
- Study loan options
- Learn about the scholarships offered
🏆Don’t miss this golden opportunity to take your future global!
🆓No entrance fee — just register now!
Click the link below to book your spot: 🔗
https://forms.gle/81ZueGK5d9R9Cg9P6
✨Ready to study abroad and change your life?
🎓This is your chance to meet top university representatives from:
USA 🇺🇸 Canada 🇨🇦 Sweden 🇸🇪
Germany 🇩🇪 France 🇫🇷 Finland 🇫🇮 Denmark 🇩🇰 and more!
📆 May 3 & 4
🕐 3:00 - 10:00 (LT)
📍Ghion Hotel
Don’t forget to bring:
🪪Passport or Birth certificate
📚Transcripts or Student copy
✅Entrance Fee: FREE!!
💡Opportunities:
- Study loan options
- Learn about the scholarships offered
🏆Don’t miss this golden opportunity to take your future global!
🆓No entrance fee — just register now!
Click the link below to book your spot: 🔗
https://forms.gle/81ZueGK5d9R9Cg9P6
👍3👎1
⭐️ ⭐️ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤዉ በሰላም አደረሳችሁ። ⭐️ ⭐️
የበዓል ስጦታ በማይታመን ዋጋ!!!
📍 ሳር ቤት ላይ አፖርትመንቶችን
በካሬ 64,200 ብር ብቻ
ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ታላቅ ቅናሽ
ባለ 2 እና ባለ 3 መኝታ አፖርትመንቶችን
ለመኖሪያ ምቹ እንዲሁም ለኢንቨስትመንት አዋጭ!!!
ታድያ ይህ እድል እንዳያመልጥዎ
ፈጥነዉ ይደዉሉ!!!
+251 950 05 56 55
ወይም በቴሌግራም
TG @Davehomes
What’s up https://wa.me/message/KGIM2YTYQGNYO1
የበዓል ስጦታ በማይታመን ዋጋ!!!
📍 ሳር ቤት ላይ አፖርትመንቶችን
በካሬ 64,200 ብር ብቻ
ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ታላቅ ቅናሽ
ባለ 2 እና ባለ 3 መኝታ አፖርትመንቶችን
ለመኖሪያ ምቹ እንዲሁም ለኢንቨስትመንት አዋጭ!!!
ታድያ ይህ እድል እንዳያመልጥዎ
ፈጥነዉ ይደዉሉ!!!
+251 950 05 56 55
ወይም በቴሌግራም
TG @Davehomes
What’s up https://wa.me/message/KGIM2YTYQGNYO1
👍4👎1
ሰኞ እለት በአርሲ ዞን ስሬ ወረዳ ምን ተከሰተ?
ባሳለፍነው ሰኞ፣ በቀን 20/08/2017 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን፣ ስሬ ወረዳ አንድ አስደንጋጭ ድርጊት ተከስቶ ነበር።
ወደ 'ስሬ' ከተማ ሲጓዙ የነበሩ 50 ገደማ የአካባቢው ነዋሪዎች ከአዳማ ከተማ በ40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ልዩ ቦታው 'ቀለጣ ወንዝ' ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በዚህ እለት ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ በታጣቂዎች ሀይል በተቀላቀለበት መንገድ ታግተው ተወስደዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግስት ኦነግ ሸኔ ብሎ የሚጠራው) ድርጊቱን እንደፈፀመው ሲናገሩ በመንግስት አካላት እስካሁን የተባለ ነገር የለም።
ከታገቱት ሰዎች መካከል ዕድሜው 26 ዓመት የሆነው እና የጋብቻ ስነ ስርዓቱን በመጪው እሁድ ይፈፅም የነበረው ወጣት ዮሃንስ አበራ (ዋኑ) (በምስል የተያያዘው ልጅ) በአሰቃቂ ሁኔታ በአጋቾቹ ተገድሎ አስከሬኑ በአውሬ እንዲበላ መደረጉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
"የሟች ቁርጥራጭ አካል ተሰብስቦ በዛሬው ዕለት በስሬ ከተማ የቀብር ስነ ስርዓቱ በትልቅ ሃዘንና ዋይታ ተፈፅሟል" ያሉን ነዋሪዎቹ ከታገቱት ሰዎች መካከል ነጋዴዎች፣ አረጋውያን፣ የኃይማኖት አባት፣ ወጣቶች፣ ተማሪዎችና ህፃናት ጭምር እንደሚገኙበት ጠቅሰው እስከ 2 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ እንደተጠየቁ ጠቁመዋል።
በአካባቢው በግብርና የሚተዳደረው የአርሶ አደር ማህበረሰብና የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ተከባብረው የሚኖሩበት ወረዳ ሲሆን ታጣቂዎቹ በተለያየ ጊዜ የአካባቢውን ማህበረሰብ ለማጥቃት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።
"አካባቢው በትልቅ የፀጥታ ስጋት ስር የወደቀ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብ በሰላም ወጥቶ መግባት፣ 40 ኪ.ሜ ወደ አዳማ ከተማ በነፃነት ተጉዞ መመለስ እንኳን አልቻለም" ያሉ አንድ ነዋሪ ከዚህ ቀደም እገታ የተፈፀመበት አካባቢ በደህንነት ኃይሎች ቀን ቀን ጥበቃ ይደረግ ነበረ ብለዋል።
"በቅርብ ጊዜ እገታው እስከተፈፀመበት ድረስ ጥበቃ የሚያደርጉት አካላት ቦታውን ለቀው በመውጣታቸው ምክንያት ይህ አደጋ ተከስቷል፡፡ የታገቱ አካላት በአስቸኳይ እንዲለቀቁ፣ በአሰቃቂ ሁኔታ በግፍ ለተነጠቀው ወንድማችን ፍትህ እንዲሰጠን እንዲሁም በቀጣይ የአካባቢው የፀጥታ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑና መሰል ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት መንግስት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠውና የአካባቢውን ፀጥታ እንዲያረጋግጥልን ለፌደራል መንግስትና ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አድረሱልን" ብለዋል።
በድርጊቱ ዙርያ የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽንን መረጃ ለመጠየቅ ያደረግነው መኩራ አልተሳካም። የመንግስት እና የክልል ሚድያዎች በታጣቂዎች የሚፈፀሙ እገታዎችን እና ግድያዎችን እንዳይዘግቡ መታዘዛቸውን ተያይዞ የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።
ምንጭ:- መሠረት ሚዲያ
@Yenetube @Fikerassefa
ባሳለፍነው ሰኞ፣ በቀን 20/08/2017 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን፣ ስሬ ወረዳ አንድ አስደንጋጭ ድርጊት ተከስቶ ነበር።
ወደ 'ስሬ' ከተማ ሲጓዙ የነበሩ 50 ገደማ የአካባቢው ነዋሪዎች ከአዳማ ከተማ በ40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ልዩ ቦታው 'ቀለጣ ወንዝ' ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በዚህ እለት ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ በታጣቂዎች ሀይል በተቀላቀለበት መንገድ ታግተው ተወስደዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግስት ኦነግ ሸኔ ብሎ የሚጠራው) ድርጊቱን እንደፈፀመው ሲናገሩ በመንግስት አካላት እስካሁን የተባለ ነገር የለም።
ከታገቱት ሰዎች መካከል ዕድሜው 26 ዓመት የሆነው እና የጋብቻ ስነ ስርዓቱን በመጪው እሁድ ይፈፅም የነበረው ወጣት ዮሃንስ አበራ (ዋኑ) (በምስል የተያያዘው ልጅ) በአሰቃቂ ሁኔታ በአጋቾቹ ተገድሎ አስከሬኑ በአውሬ እንዲበላ መደረጉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
"የሟች ቁርጥራጭ አካል ተሰብስቦ በዛሬው ዕለት በስሬ ከተማ የቀብር ስነ ስርዓቱ በትልቅ ሃዘንና ዋይታ ተፈፅሟል" ያሉን ነዋሪዎቹ ከታገቱት ሰዎች መካከል ነጋዴዎች፣ አረጋውያን፣ የኃይማኖት አባት፣ ወጣቶች፣ ተማሪዎችና ህፃናት ጭምር እንደሚገኙበት ጠቅሰው እስከ 2 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ እንደተጠየቁ ጠቁመዋል።
በአካባቢው በግብርና የሚተዳደረው የአርሶ አደር ማህበረሰብና የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ተከባብረው የሚኖሩበት ወረዳ ሲሆን ታጣቂዎቹ በተለያየ ጊዜ የአካባቢውን ማህበረሰብ ለማጥቃት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።
"አካባቢው በትልቅ የፀጥታ ስጋት ስር የወደቀ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብ በሰላም ወጥቶ መግባት፣ 40 ኪ.ሜ ወደ አዳማ ከተማ በነፃነት ተጉዞ መመለስ እንኳን አልቻለም" ያሉ አንድ ነዋሪ ከዚህ ቀደም እገታ የተፈፀመበት አካባቢ በደህንነት ኃይሎች ቀን ቀን ጥበቃ ይደረግ ነበረ ብለዋል።
"በቅርብ ጊዜ እገታው እስከተፈፀመበት ድረስ ጥበቃ የሚያደርጉት አካላት ቦታውን ለቀው በመውጣታቸው ምክንያት ይህ አደጋ ተከስቷል፡፡ የታገቱ አካላት በአስቸኳይ እንዲለቀቁ፣ በአሰቃቂ ሁኔታ በግፍ ለተነጠቀው ወንድማችን ፍትህ እንዲሰጠን እንዲሁም በቀጣይ የአካባቢው የፀጥታ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑና መሰል ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት መንግስት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠውና የአካባቢውን ፀጥታ እንዲያረጋግጥልን ለፌደራል መንግስትና ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አድረሱልን" ብለዋል።
በድርጊቱ ዙርያ የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽንን መረጃ ለመጠየቅ ያደረግነው መኩራ አልተሳካም። የመንግስት እና የክልል ሚድያዎች በታጣቂዎች የሚፈፀሙ እገታዎችን እና ግድያዎችን እንዳይዘግቡ መታዘዛቸውን ተያይዞ የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።
ምንጭ:- መሠረት ሚዲያ
@Yenetube @Fikerassefa
👍24😭24❤3👀1
ቲክ ቶክ በኢትዮጵያ ሴቶችን ማሸማቀቅን ጨምሮ በርካታ ችግሮችን እያባባሰ ነው፤ጥናት
የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በተለይም ቲክ ቶክ የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ችግሮች እያባባሰ መሆኑን በቅርቡ የወጣ አንድ ጥናት አመልክቷል።በቲክ ቶክ በሚደረግ ማሸማቀቅ ሀገር ጥለው የሚሰደዱ ሴቶች መኖራቸውም ተመልክቷል።የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በአገር ውስጥ ቋንቋዎች የጥላቻ ንግግሮችን መቆጣጠር አለመቻላቸው ደግሞ ጉዳቱን የከፋ አድርጎታል ተብሏል።
ተጨማሪ ለማንበብ የDW ዘገባ
https://p.dw.com/p/4tnEI?maca=amh-RED-Telegram-dwcom👉🏾
የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በተለይም ቲክ ቶክ የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ችግሮች እያባባሰ መሆኑን በቅርቡ የወጣ አንድ ጥናት አመልክቷል።በቲክ ቶክ በሚደረግ ማሸማቀቅ ሀገር ጥለው የሚሰደዱ ሴቶች መኖራቸውም ተመልክቷል።የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በአገር ውስጥ ቋንቋዎች የጥላቻ ንግግሮችን መቆጣጠር አለመቻላቸው ደግሞ ጉዳቱን የከፋ አድርጎታል ተብሏል።
ተጨማሪ ለማንበብ የDW ዘገባ
https://p.dw.com/p/4tnEI?maca=amh-RED-Telegram-dwcom👉🏾
👍17😁9❤2👀1