ለረጅም ጊዜ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር የነበሩት ኦቦ ገላሳ ዲልቦ በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በገላሣ ዲልቦ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል።ርዕሰ መስተዳድሩ በሀዘን መግለጫቸው “ኦሮሚያ ጠንካራ ሰው አጥታለች” ብለዋል።
“ገላሣ ዲልቦ የኦሮሞ ነፃነት ታጋይ ነበሩ” ያሉት ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ ሙሉ ህይወታቸውን ለኦሮሞ ሕዝብ የገበሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።በሀዘን መግለጫቸው ለኦሮሞ ሕዝብ በሙሉ ብርታትን እመኛለሁ ብለዋል።ኦቦ ገላሳ ዲልቦ የ1983 ሽግግር ወቅትን ጨምሮ ለረጅም ጊዜ የኦነግ ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በገላሣ ዲልቦ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል።ርዕሰ መስተዳድሩ በሀዘን መግለጫቸው “ኦሮሚያ ጠንካራ ሰው አጥታለች” ብለዋል።
“ገላሣ ዲልቦ የኦሮሞ ነፃነት ታጋይ ነበሩ” ያሉት ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ ሙሉ ህይወታቸውን ለኦሮሞ ሕዝብ የገበሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።በሀዘን መግለጫቸው ለኦሮሞ ሕዝብ በሙሉ ብርታትን እመኛለሁ ብለዋል።ኦቦ ገላሳ ዲልቦ የ1983 ሽግግር ወቅትን ጨምሮ ለረጅም ጊዜ የኦነግ ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሚስጥራዊና አገር አፍራሽ ስብሰባ አድርጓል ተብሎ ፈቃዱ የተሰረዘው የሰላምና ልማት ማዕከል ወደ ሥራ ተመለሰ!
ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተገናኘ በኅዳር ወር ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመተላለፍ የድርጅቱ የቦርድ አባላት፣ ‹‹በድብቅ አገርን ለማፍረስ›› ተንቀሳቅሰዋል በሚል ፈቃዱ ተሰርዞበት የነበረው በእነ ኤፍሬም ይስሃቅ (ፕሮፌሰር) የሚመራው ‹‹የሰላምና ልማት ማዕከል›› የተሰኘ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት፣ ፈቃዱ ታድሶለት ወደ ሥራ መመለሱ ታወቀ፡፡
ሪፖርተር ከኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰቦች ባለሥልጣንና ከሰላምና ልማት ማዕከል ያገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው፣ የድርጅቱ ፈቃዱ ከአንድ ወር በፊት ተመልሶለት ሥራውን ጀምሯል፡፡
በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰቦች ባለሥልጣን ተመዝግቦ በዴሞክራቲክ ግንባታ ሥራዎች ላይ እንደሚሠራ የተገለጸለት ይህ ተቋም፣ እንዲዘጋ ያደረገው ዋነኛ ምክንያት፣ የድርጅቱ ኃላፊዎች አገር አፍራሽ የሆነ ሚስጥራዊ ስብሰባ እንዳካሄዱ ከተገለጸ በኋላ ነበር፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/3tPiqsp
@YeneTube @FikerAssefa
ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተገናኘ በኅዳር ወር ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመተላለፍ የድርጅቱ የቦርድ አባላት፣ ‹‹በድብቅ አገርን ለማፍረስ›› ተንቀሳቅሰዋል በሚል ፈቃዱ ተሰርዞበት የነበረው በእነ ኤፍሬም ይስሃቅ (ፕሮፌሰር) የሚመራው ‹‹የሰላምና ልማት ማዕከል›› የተሰኘ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት፣ ፈቃዱ ታድሶለት ወደ ሥራ መመለሱ ታወቀ፡፡
ሪፖርተር ከኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰቦች ባለሥልጣንና ከሰላምና ልማት ማዕከል ያገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው፣ የድርጅቱ ፈቃዱ ከአንድ ወር በፊት ተመልሶለት ሥራውን ጀምሯል፡፡
በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰቦች ባለሥልጣን ተመዝግቦ በዴሞክራቲክ ግንባታ ሥራዎች ላይ እንደሚሠራ የተገለጸለት ይህ ተቋም፣ እንዲዘጋ ያደረገው ዋነኛ ምክንያት፣ የድርጅቱ ኃላፊዎች አገር አፍራሽ የሆነ ሚስጥራዊ ስብሰባ እንዳካሄዱ ከተገለጸ በኋላ ነበር፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/3tPiqsp
@YeneTube @FikerAssefa
ለሀይማኖት ተቋማት የብሮድካስት ፈቃድ መስጠት መጀመሩን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አስታወቀ!
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ከመጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሃይማኖት ተቋማት የብሮድካስት ፈቃድ መስጠት እንደሚጀመር የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መሀመድ እድሪስ አስታዉቀዋል።በ2012 ዓ.ም ማጠናቀቂያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ የዋለው የመገናኛ ብዙሀን ፖሊሲ የሀይማኖት ድርጅቶች ከሬዲዮ ሞገድ በስተቀር በሌሎች ማሰራጫ ዘዴዎች ፈቃድ አግኝተው አስተምህሮታቸውን ለተከታያቸዉ ማድረስ እንደሚችሉ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተከትሎ ባለስልጣኑ ፈቃድ መስጠት መጀመሩ ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።ቀደም ብሎ የነበረው የብሮድካስት አዋጅ ለሀይማኖት ድርጅቶች የብሮድካስት አገልግሎት ፈቃድ መስጠትን ይከለክል እንደነበር ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ከመጋቢት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሃይማኖት ተቋማት የብሮድካስት ፈቃድ መስጠት እንደሚጀመር የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መሀመድ እድሪስ አስታዉቀዋል።በ2012 ዓ.ም ማጠናቀቂያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ የዋለው የመገናኛ ብዙሀን ፖሊሲ የሀይማኖት ድርጅቶች ከሬዲዮ ሞገድ በስተቀር በሌሎች ማሰራጫ ዘዴዎች ፈቃድ አግኝተው አስተምህሮታቸውን ለተከታያቸዉ ማድረስ እንደሚችሉ አቅጣጫ ማስቀመጡን ተከትሎ ባለስልጣኑ ፈቃድ መስጠት መጀመሩ ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።ቀደም ብሎ የነበረው የብሮድካስት አዋጅ ለሀይማኖት ድርጅቶች የብሮድካስት አገልግሎት ፈቃድ መስጠትን ይከለክል እንደነበር ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
በመቐለ የሚገኘው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በሳምንት ከ1 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች በነጻ ስልክ የማስደወል አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገለፀ!
በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሚገኘው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ቡድን በሳምንት ከ1 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች በነጻ ስልክ የማስደወል አገልግሎት በመስጠት ቤተሰቦቻቸውን ማናገር እንዲችሉ እያገዘ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ኮሚቴው ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ ከጥር 2021 እስከ ጥር 2022 ባለው ጊዜ ውስጥ በትግራይ ክልል ከቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸው ለተነጣጠሉ 41 ሺህ 326 ሰዎች ነጻ የስልክ ማስደወል አገልግሎት መስጠቱን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሚገኘው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ቡድን በሳምንት ከ1 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች በነጻ ስልክ የማስደወል አገልግሎት በመስጠት ቤተሰቦቻቸውን ማናገር እንዲችሉ እያገዘ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ኮሚቴው ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ ከጥር 2021 እስከ ጥር 2022 ባለው ጊዜ ውስጥ በትግራይ ክልል ከቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸው ለተነጣጠሉ 41 ሺህ 326 ሰዎች ነጻ የስልክ ማስደወል አገልግሎት መስጠቱን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ1,227 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ!
በኦሮሚያ ክልል በ2014 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 1,004 የትራፊክ አደጋዎች መከሰታቸውን በክልሉ ፖሊስ የትራፊክ ደህንነት እና ቁጥጥር ክፍል ባለሙያ ሳጅን የባሌወርቅ ደጀኔ በተለይ ተናግረዋል፡፡
በደረሰዉ አደጋ 1,227 ሰዎች ህይወታቸዉን ሲያጡ፣1,019 ሰዎች ላይ ከባድ እና 850 ቀላል የአካል ጉዳት ተመዝግቧል፡፡፡እንዲሁም 3,096 የንብረት ውድመት የደረሰ ሲሆን ይህም በገንዘብ ሲተመን ከ570 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚገመት ተገልፆል፡፡
ከደረሰዉ አደጋ ከፍተኛ ቁጥር የተመዘገበው በምስራቅ አርሲ፣ ምእራብ ባሌ፣ምስራቅ ሀረርጌ ፣ሰሜን ሸዋ ፣ ምስራቅ ወለጋ ዞኖች እና አዳማ፣ዱከም ፣ቡራዩ ፣ሰበታ ፣ ሱሉልታ፣ አምቦ እና ገላን ከተሞች ናቸው፡፡ 95 በመቶ የተከሰተው አደጋ የደረሰው በወንድ አሽከርካሪዎች መሆኑ ተገልፆል፡፡ እንዲሁም 90 በመቶ የሚሆነው አደጋ በቀኑ ክፍለ ጊዜ የደረሰ ሲሆን 10 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በሌሊቱ ያጋጠሙ መሆናቸው ተገልፆል።
ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት፣ከፍጥነት ወሰነ በላይ ማሽከርከር እና የአሸከርካሪዎች ጥንቃቄ ጉድለት፣ ያለ እረፍት ማሸከርከር የአደጋዎቹ መንስኤዎች ስለመሆናቸዉ ሳጅን የባሌወርቅ ደጀኔ ጨምረው ተናግረዋል፡፡
Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል በ2014 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 1,004 የትራፊክ አደጋዎች መከሰታቸውን በክልሉ ፖሊስ የትራፊክ ደህንነት እና ቁጥጥር ክፍል ባለሙያ ሳጅን የባሌወርቅ ደጀኔ በተለይ ተናግረዋል፡፡
በደረሰዉ አደጋ 1,227 ሰዎች ህይወታቸዉን ሲያጡ፣1,019 ሰዎች ላይ ከባድ እና 850 ቀላል የአካል ጉዳት ተመዝግቧል፡፡፡እንዲሁም 3,096 የንብረት ውድመት የደረሰ ሲሆን ይህም በገንዘብ ሲተመን ከ570 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚገመት ተገልፆል፡፡
ከደረሰዉ አደጋ ከፍተኛ ቁጥር የተመዘገበው በምስራቅ አርሲ፣ ምእራብ ባሌ፣ምስራቅ ሀረርጌ ፣ሰሜን ሸዋ ፣ ምስራቅ ወለጋ ዞኖች እና አዳማ፣ዱከም ፣ቡራዩ ፣ሰበታ ፣ ሱሉልታ፣ አምቦ እና ገላን ከተሞች ናቸው፡፡ 95 በመቶ የተከሰተው አደጋ የደረሰው በወንድ አሽከርካሪዎች መሆኑ ተገልፆል፡፡ እንዲሁም 90 በመቶ የሚሆነው አደጋ በቀኑ ክፍለ ጊዜ የደረሰ ሲሆን 10 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በሌሊቱ ያጋጠሙ መሆናቸው ተገልፆል።
ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት፣ከፍጥነት ወሰነ በላይ ማሽከርከር እና የአሸከርካሪዎች ጥንቃቄ ጉድለት፣ ያለ እረፍት ማሸከርከር የአደጋዎቹ መንስኤዎች ስለመሆናቸዉ ሳጅን የባሌወርቅ ደጀኔ ጨምረው ተናግረዋል፡፡
Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
የነዳጅ ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማኅበር የሥራ ማቆም አድማ ለማድረግ የጊዜ ገደብ አስቀመጠ!
የማህበሩ አባላት ዛሬ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ፣ በተደጋጋሚ መንግስት ቸልተኛ በመሆኑ የነዳጅ አመላላሽ ቦቴ ቁጥር ከ3500 በ20 እጅ ቀንሷል።ጅቡቲ ደርሶ መልስ 25000 ብር እየከሰሩ መሆኑንና ይኸም የሆነውም የብር ዋጋ በመውረዱና መለዋወጫ በመወደዱ መሆኑንም ተናግረዋል።በመሆኑም መንግስት በአስር ቀናት ውስጥ መፍትሄ የማይሰጣቸው ከሆነ የሥራ አድማ እንደሚጠሩ አስታውቀዋል።
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
የማህበሩ አባላት ዛሬ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ፣ በተደጋጋሚ መንግስት ቸልተኛ በመሆኑ የነዳጅ አመላላሽ ቦቴ ቁጥር ከ3500 በ20 እጅ ቀንሷል።ጅቡቲ ደርሶ መልስ 25000 ብር እየከሰሩ መሆኑንና ይኸም የሆነውም የብር ዋጋ በመውረዱና መለዋወጫ በመወደዱ መሆኑንም ተናግረዋል።በመሆኑም መንግስት በአስር ቀናት ውስጥ መፍትሄ የማይሰጣቸው ከሆነ የሥራ አድማ እንደሚጠሩ አስታውቀዋል።
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
ፖሊስ በኹለቱ የአሶሴትድ ፕሬስ ጋዜጠኞች ላይ የጠየቀው ይግባኝ ውድቅ ተደረገበት!
የአሶሴትድ ፕሬስ ዘጋቢ አሚር አማን እና የካሜራ ባለሙያ ቶማስ እንግዳ ላይ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን ይግባኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ። ፍርድ ቤቱ ይግባኙን ውድቅ ያደረገው “መርማሪ ፖሊስ ሥራውን በትጋት እያከናወነ ስለመሆኑ ጥርጣሬ ስላደረበት” መሆኑን ገልጿል።
የፌደራል ፖሊስ ይግባኝ የጠየቀው፤ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ መጋቢት 20 የሥር ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ነው። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ኹለቱ ጋዜጠኞች በ60 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘብ ከእስር ወጥተው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ ውሳኔ ሰጥቶ ነበር። ሆኖም ፖሊስ በውሳኔው ላይ ይግባኝ በመጠየቁ ጋዜጠኞቹ ከእስር ሳይፈቱ ቀርተዋል።
ምርመራውን እያከናወነ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ “ቀሪ ሥራዎች እያሉን ተጠርጣሪዎቹ በዋስትና እንዲወጡ መወሰኑ አግባብ አይደለም” በሚል የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲሻር ያመለከተው ትላንት ረቡዕ መጋቢት 21 ነው። ፖሊስ በዚሁ ማመልከቻው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንዲፈቅድለትም ጠይቆ ነበር።
የጋዜጠኞቹ ጠበቆች በበኩላቸው፤ ፖሊስ ለተጨማሪ የምርመራ ቀናት መጠየቂያ የሚያቀርባቸው ምክንያቶች ተመሳሳይ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። ፍርድ ቤቱም ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያጸና ጠይቀዋል።የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ይግባኝ ሰሚ ችሎት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 22 በጽህፈት ቤት በኩል በሰጠው ውሳኔ የሥር ፍርድ ቤትን ውሳኔ አጽንቷል።
“ተጠርጣሪዎቹ ከአራት ወራት በላይ በእስር ላይ ቆይተዋል ተብሎ ነው የሚታመነው” ያለው ፍርድ ቤቱ፤ ውሳኔውን የሰጠው “[በፖሊስ] ለተጨማሪ ጊዜ መጠየቂያ የሚቀርበው ምክንያት ተመሳሳይ ነው። ይህ መርማሪ ፖሊስ ሥራውን በትጋት እያከናወነ መሆኑን አጠራጣሪ ያደርገዋል” በሚል ምክንያት ነው።
ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን ከሰጠ በኋላ ጉዳዩን ከውጭ ሆነው ሲከታተሉ የነበሩ የጋዜጠኞቹ የትዳር አጋሮች እና ቤተሰቦቻቸው ደስታቸውን በእንባ ጭምር ሲገልጹ መስተዋላቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። በፍርድ ቤቱ በአካል ተገኝተው ሂደቱን የተከታተሉት ኹለቱ ጋዜጠኞችም ከውሳኔው በኋላ እርስ በእርስ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር በደስታ ስሜት ተውጠው ሲተቃቀፉ መታየታቸውንም በዘገባው ተገልጿል።
አሚር አማን እና ቶማስ እንግዳ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከአራት ወራት ህዳር 19፤ 2014 ነበር። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት “የአሸባሪውን ሸኔ ቡድንን በዓለም አቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ሥራ ሲሰሩ ነበር” በሚል ተጠርጥረው እንደሆነ ፖሊስ በወቅቱ ማስታወቁ ይታወሳል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
የአሶሴትድ ፕሬስ ዘጋቢ አሚር አማን እና የካሜራ ባለሙያ ቶማስ እንግዳ ላይ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን ይግባኝ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ አደረገ። ፍርድ ቤቱ ይግባኙን ውድቅ ያደረገው “መርማሪ ፖሊስ ሥራውን በትጋት እያከናወነ ስለመሆኑ ጥርጣሬ ስላደረበት” መሆኑን ገልጿል።
የፌደራል ፖሊስ ይግባኝ የጠየቀው፤ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ መጋቢት 20 የሥር ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ነው። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ኹለቱ ጋዜጠኞች በ60 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘብ ከእስር ወጥተው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ ውሳኔ ሰጥቶ ነበር። ሆኖም ፖሊስ በውሳኔው ላይ ይግባኝ በመጠየቁ ጋዜጠኞቹ ከእስር ሳይፈቱ ቀርተዋል።
ምርመራውን እያከናወነ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ “ቀሪ ሥራዎች እያሉን ተጠርጣሪዎቹ በዋስትና እንዲወጡ መወሰኑ አግባብ አይደለም” በሚል የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲሻር ያመለከተው ትላንት ረቡዕ መጋቢት 21 ነው። ፖሊስ በዚሁ ማመልከቻው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንዲፈቅድለትም ጠይቆ ነበር።
የጋዜጠኞቹ ጠበቆች በበኩላቸው፤ ፖሊስ ለተጨማሪ የምርመራ ቀናት መጠየቂያ የሚያቀርባቸው ምክንያቶች ተመሳሳይ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። ፍርድ ቤቱም ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያጸና ጠይቀዋል።የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ይግባኝ ሰሚ ችሎት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 22 በጽህፈት ቤት በኩል በሰጠው ውሳኔ የሥር ፍርድ ቤትን ውሳኔ አጽንቷል።
“ተጠርጣሪዎቹ ከአራት ወራት በላይ በእስር ላይ ቆይተዋል ተብሎ ነው የሚታመነው” ያለው ፍርድ ቤቱ፤ ውሳኔውን የሰጠው “[በፖሊስ] ለተጨማሪ ጊዜ መጠየቂያ የሚቀርበው ምክንያት ተመሳሳይ ነው። ይህ መርማሪ ፖሊስ ሥራውን በትጋት እያከናወነ መሆኑን አጠራጣሪ ያደርገዋል” በሚል ምክንያት ነው።
ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን ከሰጠ በኋላ ጉዳዩን ከውጭ ሆነው ሲከታተሉ የነበሩ የጋዜጠኞቹ የትዳር አጋሮች እና ቤተሰቦቻቸው ደስታቸውን በእንባ ጭምር ሲገልጹ መስተዋላቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። በፍርድ ቤቱ በአካል ተገኝተው ሂደቱን የተከታተሉት ኹለቱ ጋዜጠኞችም ከውሳኔው በኋላ እርስ በእርስ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር በደስታ ስሜት ተውጠው ሲተቃቀፉ መታየታቸውንም በዘገባው ተገልጿል።
አሚር አማን እና ቶማስ እንግዳ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከአራት ወራት ህዳር 19፤ 2014 ነበር። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት “የአሸባሪውን ሸኔ ቡድንን በዓለም አቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ሥራ ሲሰሩ ነበር” በሚል ተጠርጥረው እንደሆነ ፖሊስ በወቅቱ ማስታወቁ ይታወሳል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
በአፋር ክልል በአብኣላ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዝ ተጀምሯል!
በዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት 21 ከበድ የጭነት መኪናዎች የእርዳታ እህል በመጫን በአፋር ክልል በአብኣላ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል ማጓጓዝ መጀመሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አሰታወቀ። የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም የሰብአዊ እርዳታን ለማቅረብ እንቅስቃሴ መጀመሩ የሚታወስ ነዉ፡፡
ዉሳኔዉ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ የመድኃኒት፣ የህክምና መሳሪያዎች፣ ገንዘብና አልሚ ምግቦችን ረጂ ድርጅቶች በቻሉት መጠን በአየር ትራንስፖርት በየእለቱ መጓጓዝ መጀመራቸዉንም ማሰወቃችን ይታወሰል፡፡በዛሬዉ ዕለት ደግሞ በዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት 21 ከበድ የጭነት መኪናዎች የእርዳታ እህል በመጨን በአፋር ክልል በአብኣላ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዝ ተጀምሯል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦቱን በተሟላ ሁኔታ ለማስኬድ ከተባበረና ባለድርሻ አካላት ጋር ለመስራት ዛሬም ቁርጠኛ መሆኑን በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
@YeneTube @FikerAssefa
በዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት 21 ከበድ የጭነት መኪናዎች የእርዳታ እህል በመጫን በአፋር ክልል በአብኣላ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል ማጓጓዝ መጀመሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አሰታወቀ። የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም የሰብአዊ እርዳታን ለማቅረብ እንቅስቃሴ መጀመሩ የሚታወስ ነዉ፡፡
ዉሳኔዉ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ የመድኃኒት፣ የህክምና መሳሪያዎች፣ ገንዘብና አልሚ ምግቦችን ረጂ ድርጅቶች በቻሉት መጠን በአየር ትራንስፖርት በየእለቱ መጓጓዝ መጀመራቸዉንም ማሰወቃችን ይታወሰል፡፡በዛሬዉ ዕለት ደግሞ በዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት 21 ከበድ የጭነት መኪናዎች የእርዳታ እህል በመጨን በአፋር ክልል በአብኣላ መንገድ የሰብአዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዝ ተጀምሯል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦቱን በተሟላ ሁኔታ ለማስኬድ ከተባበረና ባለድርሻ አካላት ጋር ለመስራት ዛሬም ቁርጠኛ መሆኑን በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
#ወርቃማ_ሕጎች
የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#አእምሮህ_ማግኔት_ነው!
ሁልጊዜም አእምሮህ ማግኔት መሆኑን አስታውስ፡፡ አንተን የተቆጣጠሩህን ሃሳቦች እና በውስጥ የሰረፁትን እምነቶች የሚያምኑ እና የሚያስቡ ሌሎች ሰዎች ወዳንተ እንደሚያቀርብም ልብ በል፡፡
በትክክለኛ መንገድ የስበት ህግ (law of attraction) ብለን የምንጠራው አንድ ህግ አለ፡፡ ውሃ ከፍታውን የሚፈልግበት፣ በህዋ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ የየራሳቸውን አምሳያ የሚፈልጉበት ህግ፡፡ ፕላኔቶችን በትክክለኛ ቦታቸው ጠብቆ እንደሚያቆየው የስበት ህግ፡፡
ይህ ህግ የሚለዋወጥ ቢሆን ኖሮ የማንጎ ፍሬ ከአበባው ውስጥ በርራ በፓፓያ አበባ ውስጥ በመግባት በከፊል ማንጎ፣ በከፊል ደግሞ ፓፓያ የሆነ ዛፍ ይፈጥሩ ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ግን ሰምተን አናውቅም፡፡ ይሄንን የስበት ህግ ትንሽ በመከተል በሴቶች እና በወንዶች መካከል እንዴት እንደሚሰራ ማየት እንችላለን፡፡
ውጤታማና ሃብታም ወንዶች የሚፈልጓት ሴት የእነሱኑ አይነት ሴት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያለ ወንድም እንደዚያው፡፡ ይህ የሚሆነው በተፈጥሮ ነው - ልክ ውሃ ወደ ታች እንደሚፈሰው፡፡
“ሁሉም አምሳያውን ይስባል” የሚለው አባባል የማይገሰስ ሀቅ ነው፡፡ አንድ ወንድ የሚፈልጋት ሴት በብዙ መልኩ እሱን የምትመስለውን ሴት መሆኑ እውነት ከሆነ፣ የምትፈልጋቸውን ሰዎች ለማሰብ የእነዚህን ሰዎች ሀሳቦች እና እምነቶች በመቆጣጠር እና በማዳበር ማግኔት የመስራትን ጥቅም ማየት አትችልም?
#ወርቃማው_ሕግ መጽሐፍ
በየመጽሐፍት መደብሩና አዟሪዎች እጅ ይገኛል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram- https://tttttt.me/teklu_tilahun
የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#አእምሮህ_ማግኔት_ነው!
ሁልጊዜም አእምሮህ ማግኔት መሆኑን አስታውስ፡፡ አንተን የተቆጣጠሩህን ሃሳቦች እና በውስጥ የሰረፁትን እምነቶች የሚያምኑ እና የሚያስቡ ሌሎች ሰዎች ወዳንተ እንደሚያቀርብም ልብ በል፡፡
በትክክለኛ መንገድ የስበት ህግ (law of attraction) ብለን የምንጠራው አንድ ህግ አለ፡፡ ውሃ ከፍታውን የሚፈልግበት፣ በህዋ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ የየራሳቸውን አምሳያ የሚፈልጉበት ህግ፡፡ ፕላኔቶችን በትክክለኛ ቦታቸው ጠብቆ እንደሚያቆየው የስበት ህግ፡፡
ይህ ህግ የሚለዋወጥ ቢሆን ኖሮ የማንጎ ፍሬ ከአበባው ውስጥ በርራ በፓፓያ አበባ ውስጥ በመግባት በከፊል ማንጎ፣ በከፊል ደግሞ ፓፓያ የሆነ ዛፍ ይፈጥሩ ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ግን ሰምተን አናውቅም፡፡ ይሄንን የስበት ህግ ትንሽ በመከተል በሴቶች እና በወንዶች መካከል እንዴት እንደሚሰራ ማየት እንችላለን፡፡
ውጤታማና ሃብታም ወንዶች የሚፈልጓት ሴት የእነሱኑ አይነት ሴት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያለ ወንድም እንደዚያው፡፡ ይህ የሚሆነው በተፈጥሮ ነው - ልክ ውሃ ወደ ታች እንደሚፈሰው፡፡
“ሁሉም አምሳያውን ይስባል” የሚለው አባባል የማይገሰስ ሀቅ ነው፡፡ አንድ ወንድ የሚፈልጋት ሴት በብዙ መልኩ እሱን የምትመስለውን ሴት መሆኑ እውነት ከሆነ፣ የምትፈልጋቸውን ሰዎች ለማሰብ የእነዚህን ሰዎች ሀሳቦች እና እምነቶች በመቆጣጠር እና በማዳበር ማግኔት የመስራትን ጥቅም ማየት አትችልም?
#ወርቃማው_ሕግ መጽሐፍ
በየመጽሐፍት መደብሩና አዟሪዎች እጅ ይገኛል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram- https://tttttt.me/teklu_tilahun
በህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ባለስልጣን በአዋጅ የተሰጠውን ኃላፊነት እና ስልጣን በአግባቡ እንዳልተወጣ ገለጸ፡፡
ቋሚ ኮሚቴው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ፣ ጥራት እና ቁጥጥርን በተመለከተ የ2012 እና የ2013 በጀት ዓመት በክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ኃላፊዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል፡፡የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ክርስቲያን ታደለ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ አለመሆኑን ጠቁመው÷ መስሪያ ቤቱ እስከ ሚያዚያ 8 ቀን ድረስ የኦዲት ሪፖርት ማስተካከያ እንዲያቀርብ አሳስበዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት እና ስልጠና ዘርፍ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አቅጣጫ መቀመጡንም ሰብሳቢው አስታውሰዋል፡፡የፌዴራል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚታዩ ብልሹ አሰራሮችን መርምሮ በሁለት ወራት ውስጥ ማቅረብ እንዳለበትም ነው ማሳሰቢያ የተሰጠው፡፡የፍትህ ሚኒስቴርም ከኦዲት ሪፖርቱ አንፃር በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የወንጀል ምርምራ በማድረግ የሁሉንም አፈጻጸም ሪፖርት በሁለት ወራት ውስጥ ለቋሚ ኮሚቴው እንዲያቀርብ ተጠይቋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ወይዘሮ አራሪ ሞሲሳ በበኩላቸው÷ የባስልጣን መስሪያ ቤቱ ኃላፊዎች የኦዲት ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ምላሽ ያልሰጡ መሆኑን ገልጸው፥ የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በአግባቡ አልተወጡም ብለዋል፡፡በሌላ በኩል ትውልድን ለመቅረጽም ሆነ ለማበላሸት እድሉ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እጅ ላይ መሆኑ ታውቆ ችግሮች በትብብር እንዲፈቱ ሁለንተናዊ ጥረት መደረግ እንዳለበት ገልጸው÷ ከተቋሙ አመራሮችም ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በኩል በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ፣ ክትትልና ቁጥጥር ረገድ ችግሮች የሚታዩበት መሆኑንም የቋሚ ኮሚቴው አባላት አንስተዋል፡፡ በከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ባለስልጣን የትምህርትና ስልጠና ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱዓለም አድማሴ በበኩላቸው÷ተቋሙ የሰው ኃይል፣ የአደረጃጀት፣ የተሸከርካሪ እና የቢሮ ችግሮች እንዳሉበት መግለጻቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ቋሚ ኮሚቴው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ፣ ጥራት እና ቁጥጥርን በተመለከተ የ2012 እና የ2013 በጀት ዓመት በክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ኃላፊዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል፡፡የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ክርስቲያን ታደለ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ አለመሆኑን ጠቁመው÷ መስሪያ ቤቱ እስከ ሚያዚያ 8 ቀን ድረስ የኦዲት ሪፖርት ማስተካከያ እንዲያቀርብ አሳስበዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት እና ስልጠና ዘርፍ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አቅጣጫ መቀመጡንም ሰብሳቢው አስታውሰዋል፡፡የፌዴራል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚታዩ ብልሹ አሰራሮችን መርምሮ በሁለት ወራት ውስጥ ማቅረብ እንዳለበትም ነው ማሳሰቢያ የተሰጠው፡፡የፍትህ ሚኒስቴርም ከኦዲት ሪፖርቱ አንፃር በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የወንጀል ምርምራ በማድረግ የሁሉንም አፈጻጸም ሪፖርት በሁለት ወራት ውስጥ ለቋሚ ኮሚቴው እንዲያቀርብ ተጠይቋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ወይዘሮ አራሪ ሞሲሳ በበኩላቸው÷ የባስልጣን መስሪያ ቤቱ ኃላፊዎች የኦዲት ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ምላሽ ያልሰጡ መሆኑን ገልጸው፥ የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በአግባቡ አልተወጡም ብለዋል፡፡በሌላ በኩል ትውልድን ለመቅረጽም ሆነ ለማበላሸት እድሉ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እጅ ላይ መሆኑ ታውቆ ችግሮች በትብብር እንዲፈቱ ሁለንተናዊ ጥረት መደረግ እንዳለበት ገልጸው÷ ከተቋሙ አመራሮችም ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በኩል በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ አሰጣጥ፣ ክትትልና ቁጥጥር ረገድ ችግሮች የሚታዩበት መሆኑንም የቋሚ ኮሚቴው አባላት አንስተዋል፡፡ በከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ባለስልጣን የትምህርትና ስልጠና ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱዓለም አድማሴ በበኩላቸው÷ተቋሙ የሰው ኃይል፣ የአደረጃጀት፣ የተሸከርካሪ እና የቢሮ ችግሮች እንዳሉበት መግለጻቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ዓለም አቀፍ ለጋሾች ችግር ውስጥ ያለውን የአፋር ህዝብ አልፈው “ትግራይን እንርዳ” ማለታቸው አግባብ አይደለም-የአፋር ክልል
“የአፋር ሕዝብ እንደፍየል እና እንደዝንጀሮ በየቦታው ፈሶ እሱን ወደኋላ አድርገን የትግራይ ሕዝብ ብቻ ይረዳ የሚል ቋንቋ ትክክል” አይደለም ሲል የአፋር ክልል በዓለምአቀፍ ለጋሾች ላይ ቅረታውን አቅርቧል፡፡
የአፋር ጤና ቢሮ ኃላፊ ያሲን ሀቢብ እንደገለጹት በአፋር ክልል በርካታ ዜጎች በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው በየቦታው ነው ያሉት፡፡ የቢሮ ኃላፊው ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች በየቦታው እየወለዱ፤ ለውኃ ጥምና ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህ ባለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ ለጋሽ አካላት በአፋር አልፈው ዕርዳታ ለትግራይ ሕዝብ ማድረስ እንደሚፈልጉም የቢሮ ኃላፊ ገልጸዋል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ዕርዳታ ማግኘት እንዳለበትና መጎዳት እንደሌለበት እንደሚያምኑ የገለጹት ኃላፊው፤ አፋር ክልል ላይ በችግር ውስጥ የፈሰሰውን ህዝብ ጥሎ ማለፍ ግን አስቸጋሪ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ: https://am.al-ain.com/article/afar-region-decries-of-partiality-of-donors
@YeneTube @FikerAssefa
“የአፋር ሕዝብ እንደፍየል እና እንደዝንጀሮ በየቦታው ፈሶ እሱን ወደኋላ አድርገን የትግራይ ሕዝብ ብቻ ይረዳ የሚል ቋንቋ ትክክል” አይደለም ሲል የአፋር ክልል በዓለምአቀፍ ለጋሾች ላይ ቅረታውን አቅርቧል፡፡
የአፋር ጤና ቢሮ ኃላፊ ያሲን ሀቢብ እንደገለጹት በአፋር ክልል በርካታ ዜጎች በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው በየቦታው ነው ያሉት፡፡ የቢሮ ኃላፊው ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች በየቦታው እየወለዱ፤ ለውኃ ጥምና ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህ ባለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ ለጋሽ አካላት በአፋር አልፈው ዕርዳታ ለትግራይ ሕዝብ ማድረስ እንደሚፈልጉም የቢሮ ኃላፊ ገልጸዋል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ዕርዳታ ማግኘት እንዳለበትና መጎዳት እንደሌለበት እንደሚያምኑ የገለጹት ኃላፊው፤ አፋር ክልል ላይ በችግር ውስጥ የፈሰሰውን ህዝብ ጥሎ ማለፍ ግን አስቸጋሪ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ: https://am.al-ain.com/article/afar-region-decries-of-partiality-of-donors
@YeneTube @FikerAssefa
የተመድ የፍልሰተኞች ድርጅት አይኦኤም ከሳዑዲ ዓረቢያ በመመለስ ላይ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን መልሶ ለማቋቋም 11 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ በድረገጹ አስታውቋል። መንግሥት ተመላሾቹን መልሶ ለማቋቋም ዓለማቀፍ ለጋሾች የዕርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉ መማጸኑን ድርጅቱ ገልጧል። በሳዑዲ ዓረቢያ እንደሚኖሩ ከሚገመቱት 750 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን 450 ሺህ ያህሉ በሕገወጥ መንገድ ወደ አገሪቱ እንደገቡ ይገመታል። መንግሥት ትናንት በጀመረው ዜጎችን በአውሮፕላን የማጓጓዝ ጥረት 100 ሺህ ፍልሰተኞች ወደ አገራቸው እንደሚመለሱ ይጠበቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
#ወደ_ሀብት_ጉዞ
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች በሚለውና #አስበህ_ሐብታም_ሁን በሚል በተተረጎመው መጽሐፉ የምናውቀው የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ።
#ወደ_ሀብት_ጉዞ
ይህ ወደ ሀብት ጉዞ የተሰኘው መጽሐፍ እያንዳንዱን ሕልማችንንና ዓላማችንን ለማሳካት ያግዘናል፡፡
ብልፅግና በገንዘብና ዝና ብቻ የተገደበ ትርጉም እንደሌለው ያሳየናል፡፡ እውነተኛ ባለጸጋ ለመሆን በሁሉም የሕይወት ዘርፎች መበልፀግ ያስፈልጋል- በአካል፣ በመንፈስ፣ በገንዘብ፡፡
ለዚህም ደግሞ ከ25 ሺ በላይ ሰዎች የውድቀት ምክንያት፣ ከ500 በላይ ስኬታማ ሰዎች ምስጢርና የሀያ አምስት አመታት የምርምር ውጤት... ወደ #ሀብት_ጉዞ መጽሐፍን ፈጥሯል።
ከ60 ሚሊየን ኮፒ በላይ ከተሸጠው አስበህ ሀብታም ሁን መጽሐፍ ቀጥሎ ከፍተኛ ሽያጭን የተቀዳጀ መጽሐፍ።
እነሆ በሁሉም መልክ ወደ ሀብት ጉዞ!!
የናፖሊዮን ሂልን መጽሐፍ ይዞ!!!
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች በሚለውና #አስበህ_ሐብታም_ሁን በሚል በተተረጎመው መጽሐፉ የምናውቀው የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ።
#ወደ_ሀብት_ጉዞ
ይህ ወደ ሀብት ጉዞ የተሰኘው መጽሐፍ እያንዳንዱን ሕልማችንንና ዓላማችንን ለማሳካት ያግዘናል፡፡
ብልፅግና በገንዘብና ዝና ብቻ የተገደበ ትርጉም እንደሌለው ያሳየናል፡፡ እውነተኛ ባለጸጋ ለመሆን በሁሉም የሕይወት ዘርፎች መበልፀግ ያስፈልጋል- በአካል፣ በመንፈስ፣ በገንዘብ፡፡
ለዚህም ደግሞ ከ25 ሺ በላይ ሰዎች የውድቀት ምክንያት፣ ከ500 በላይ ስኬታማ ሰዎች ምስጢርና የሀያ አምስት አመታት የምርምር ውጤት... ወደ #ሀብት_ጉዞ መጽሐፍን ፈጥሯል።
ከ60 ሚሊየን ኮፒ በላይ ከተሸጠው አስበህ ሀብታም ሁን መጽሐፍ ቀጥሎ ከፍተኛ ሽያጭን የተቀዳጀ መጽሐፍ።
እነሆ በሁሉም መልክ ወደ ሀብት ጉዞ!!
የናፖሊዮን ሂልን መጽሐፍ ይዞ!!!
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
በጂዳ እና አካባቢዋ ባሉ እስር ቤቶች ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ወደ አገር ቤት የመመለስ ሥራ ዛሬ ይጀመራል!
ከጂዳ እና አካባቢ ባሉ እስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ወደ አገር ቤት የመመለስ ሥራ ዛሬ እንደሚመለሱ ተገለፀ።በተጨማሪም 1 ሺህ 831 በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የነበሩ ዜጎች ዛሬ ኢትዮጵያ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገር ቤት ለመመለስ ከታቀደው 102 ሺህ ዜጎች መካከል ከ80 ሺህ የማያንሱት የሚገኙት በጂዳ እና አካባቢ በሚገኙ እስር ቤቶች እና የማቆያ ማዕከላት ነው።
ዛሬ በሚደረጉ አራት በረራዎች ከጅዳ 1438 በሳኡዲ አረቢያ በእስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የነበሩ ዜጎች ኢትዮጵያ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።ከትላንት በስቲያ በጀመረው በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤቶች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ሥራ፤ በአንድ ቀን ከሪያድ 936 ኢትዮጵያዊን ማምጣት የተቻለ ሲሆን ዛሬ ማለዳም 393 ዜጎች ወደ አገራቸው መመለሳቸውም ታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ከጂዳ እና አካባቢ ባሉ እስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ወደ አገር ቤት የመመለስ ሥራ ዛሬ እንደሚመለሱ ተገለፀ።በተጨማሪም 1 ሺህ 831 በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የነበሩ ዜጎች ዛሬ ኢትዮጵያ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገር ቤት ለመመለስ ከታቀደው 102 ሺህ ዜጎች መካከል ከ80 ሺህ የማያንሱት የሚገኙት በጂዳ እና አካባቢ በሚገኙ እስር ቤቶች እና የማቆያ ማዕከላት ነው።
ዛሬ በሚደረጉ አራት በረራዎች ከጅዳ 1438 በሳኡዲ አረቢያ በእስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የነበሩ ዜጎች ኢትዮጵያ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።ከትላንት በስቲያ በጀመረው በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤቶች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ሥራ፤ በአንድ ቀን ከሪያድ 936 ኢትዮጵያዊን ማምጣት የተቻለ ሲሆን ዛሬ ማለዳም 393 ዜጎች ወደ አገራቸው መመለሳቸውም ታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ 1,200 በላይ ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው አልተመለሱም ተባለ፡፡
ኢንዱስትሪ ፓርኩ በሕወሃት ታጣቂ ቡድን ከደረሰበት ውድመት ሙሉ በሙሉ ባለማገገሙ እና የአጎአ እድል በመሰረዙ በሥሩ ያሉ ኢንዱስትሪዎች በቀደመው አቅማቸው ልክ እያመረቱ አይደለም ተብሏል፡፡
በመሆኑም 1,214 የፓርኩ ሰራተኞች አሁንም ወደ ሥራ ገበታቸው እንዳልተመለሱ የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ሰኢድ ተናግረዋል፡፡
በፓርኩ ውስጥ ሥራ ላይ ካሉ ሼዶች መካከል በተለይ ካልሲ እያመረተ ወደ አሜሪካ ገበያ ይልክ የነበረው ፍአንላይ የተባለ የቻይና ኩባንያ ከጦርነቱ በኋላ አገግሞ ሥራ ቢጀምርም በጥቂቱ ብቻ እየሰራ በመሆኑ በርካታ ሰራተኞቹ ወደ ሥራቸው እንዳልተመለሱ ተሰምቷል፡፡
የወንዶች ሙሉ ልብስ እያመረተ ለአሜሪካ ገበያ የሚልክ የቻይና አሜሪካ ኩባንያ እና የሴቶች ቦርሳ እያመረተ እንዲሁ 95 በመቶ ለአሜሪካ ገበያ የሚያቀርብ ኩባንያ ሥራቸውን የተሻለ እየከወኑ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ይሁንና አሜሪካ ለአፍሪካ አገራት ከሰጠቸው የቀረጥና ኮታ ነፃ እድል ኢትዮጵያን ማስወጣቷ ተከትሎ ሁለቱ ኩባንያዎች የገበያ ችግር እንደገጠማቸው ሸገር ከኩባንያዎቹ የስራ ኃላፊዎች ሰምቷል፡፡
የገበያው ሁኔታ ሲስተካከልና በፓርኩ ውስጥ እየሰሩ ያሉ ኩባንያዎች በህወሃት አማካኝነት ከደረሰባቸው ውድመት አገግመው በሙሉ አቅማቸው ማምረት ሲጀምሩ አሁን የተቀነሱ ከ1,200 በላይ ሰራተኞች ወደ ስራቸው ይመለሳሉ ተብሏል፡፡
Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
ኢንዱስትሪ ፓርኩ በሕወሃት ታጣቂ ቡድን ከደረሰበት ውድመት ሙሉ በሙሉ ባለማገገሙ እና የአጎአ እድል በመሰረዙ በሥሩ ያሉ ኢንዱስትሪዎች በቀደመው አቅማቸው ልክ እያመረቱ አይደለም ተብሏል፡፡
በመሆኑም 1,214 የፓርኩ ሰራተኞች አሁንም ወደ ሥራ ገበታቸው እንዳልተመለሱ የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ሰኢድ ተናግረዋል፡፡
በፓርኩ ውስጥ ሥራ ላይ ካሉ ሼዶች መካከል በተለይ ካልሲ እያመረተ ወደ አሜሪካ ገበያ ይልክ የነበረው ፍአንላይ የተባለ የቻይና ኩባንያ ከጦርነቱ በኋላ አገግሞ ሥራ ቢጀምርም በጥቂቱ ብቻ እየሰራ በመሆኑ በርካታ ሰራተኞቹ ወደ ሥራቸው እንዳልተመለሱ ተሰምቷል፡፡
የወንዶች ሙሉ ልብስ እያመረተ ለአሜሪካ ገበያ የሚልክ የቻይና አሜሪካ ኩባንያ እና የሴቶች ቦርሳ እያመረተ እንዲሁ 95 በመቶ ለአሜሪካ ገበያ የሚያቀርብ ኩባንያ ሥራቸውን የተሻለ እየከወኑ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ይሁንና አሜሪካ ለአፍሪካ አገራት ከሰጠቸው የቀረጥና ኮታ ነፃ እድል ኢትዮጵያን ማስወጣቷ ተከትሎ ሁለቱ ኩባንያዎች የገበያ ችግር እንደገጠማቸው ሸገር ከኩባንያዎቹ የስራ ኃላፊዎች ሰምቷል፡፡
የገበያው ሁኔታ ሲስተካከልና በፓርኩ ውስጥ እየሰሩ ያሉ ኩባንያዎች በህወሃት አማካኝነት ከደረሰባቸው ውድመት አገግመው በሙሉ አቅማቸው ማምረት ሲጀምሩ አሁን የተቀነሱ ከ1,200 በላይ ሰራተኞች ወደ ስራቸው ይመለሳሉ ተብሏል፡፡
Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራና አፋር ክልሎች የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችና የኦፕቲካል ፋይበር የጥገና ሥራ መጠናቀቁ ተገለፀ!
በአማራና አፋር ክልሎች በህወሃት ቡድን ከፍተኛ ውድመት አጋጥሞት የነበረውን የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችና የኦፕቲካል ፋይበር ገመዶች የመጠገን ሥራ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰታወቀ።
በክልሎች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ለመጠገን ለመለዋወጫ አቅርቦት የወጣውን ወጪ ሳይጨምር ለሥራው ብቻ ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉም ተገልጿል።
የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ጥገናው በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ለተወሰኑ ሰዓታት ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ሲሠራ ቆይቶ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገልጿል፡፡
ከደብረሲና – ሸዋሮቢት – ከሚሴ – ኮምቦልቻ – አቀስታ – ዓለም ከተማ ባለ132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር፤ ከደብረብርሃን – ኮምቦልቻ – ሠመራ እና ከኮምቦልቻ – አላማጣ እስከ ቆቦ ድረስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር እንዲሁም ከደብረታቦር እስከ ጋሸና ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በሚያልፍበት አካባቢ የሚገኙ ከተሞችና መንደሮች ላይ ከህዳር 24/2014 ጀምሮ በተደረገው ጥገና አካባቢዎቹ ኤሌክትሪክ መልሰው እንዲያገኙ መደረጉ ይታወሳል፡፡
ከደሴ – ወልዲያ የ ባለ 66 ኪሎ ቪልት መስመር ጥገና በማካሄድ የወልዲያና አካባቢው ኃይል እንዲያገኙ ተደርገዋል፡፡
የመልሶ ጥገና ሥራውን ከተቋሙ ስምንት ሪጅኖች የተውጣጣ የጥገና ቡድን በከፍተኛ ርብርብ ሲያከናውን መቆየቱም ተገልጿል፡፡
በአማራና አፋር ክልል የደረሰውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ለመጠገን ለመለዋወጫ አቅርቦት የወጣውን ወጪ ሳይጨምር ለሥራው ብቻ ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራና አፋር ክልሎች በህወሃት ቡድን ከፍተኛ ውድመት አጋጥሞት የነበረውን የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችና የኦፕቲካል ፋይበር ገመዶች የመጠገን ሥራ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰታወቀ።
በክልሎች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ለመጠገን ለመለዋወጫ አቅርቦት የወጣውን ወጪ ሳይጨምር ለሥራው ብቻ ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉም ተገልጿል።
የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ጥገናው በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ለተወሰኑ ሰዓታት ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ሲሠራ ቆይቶ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገልጿል፡፡
ከደብረሲና – ሸዋሮቢት – ከሚሴ – ኮምቦልቻ – አቀስታ – ዓለም ከተማ ባለ132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር፤ ከደብረብርሃን – ኮምቦልቻ – ሠመራ እና ከኮምቦልቻ – አላማጣ እስከ ቆቦ ድረስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር እንዲሁም ከደብረታቦር እስከ ጋሸና ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በሚያልፍበት አካባቢ የሚገኙ ከተሞችና መንደሮች ላይ ከህዳር 24/2014 ጀምሮ በተደረገው ጥገና አካባቢዎቹ ኤሌክትሪክ መልሰው እንዲያገኙ መደረጉ ይታወሳል፡፡
ከደሴ – ወልዲያ የ ባለ 66 ኪሎ ቪልት መስመር ጥገና በማካሄድ የወልዲያና አካባቢው ኃይል እንዲያገኙ ተደርገዋል፡፡
የመልሶ ጥገና ሥራውን ከተቋሙ ስምንት ሪጅኖች የተውጣጣ የጥገና ቡድን በከፍተኛ ርብርብ ሲያከናውን መቆየቱም ተገልጿል፡፡
በአማራና አፋር ክልል የደረሰውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ለመጠገን ለመለዋወጫ አቅርቦት የወጣውን ወጪ ሳይጨምር ለሥራው ብቻ ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ከማለዳው ጀምሮ በተደረጉ ሶስት በረራዎች በጠቅላላው 1173 ዜጎች አዲስ አበባ እስካሁን ገብተዋል።
የጅዳ ተመላሾች ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱም የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በርኦ፣ የስደት እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ም /ዋና ዳይሬክተር ጠይባ ሃሰን፣ የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳ፣ የዜግነት እና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ም/ ዋና /ዳይሬክተር አቶ ታምሩ ገምበቶ እና ሌሎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የጅዳ ተመላሾች ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱም የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በርኦ፣ የስደት እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ም /ዋና ዳይሬክተር ጠይባ ሃሰን፣ የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳ፣ የዜግነት እና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ም/ ዋና /ዳይሬክተር አቶ ታምሩ ገምበቶ እና ሌሎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa