ኢትዮጵያ የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሰራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ አገደች።
የኢትዮጲያ ምግብ እና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል በሚል ጥቅም ላይ ከሚውሉ ማስኮች ውስጥ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሰራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ ትዕዛዝ ማስተላፉን አስታውቋል፡፡ባስልጣኑ ከዚህ ቀደም ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮች የቫይረሱን ስርጭት ለመጨመር አስተዋፆ አላቸው በሚል ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
ነገር ግን ባለስልጣኑ ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት ህብረተሰቡ እነዚህን ማስኮች ከመጠቀም አልተቆጠበም እና ምን አይነት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው ሲል ኢትዮ ኤፍ ኤም በባለስልጠኑ የመድሀኒት ምዝገበ እና ፍቃድ ዳይሬክተር አቶ አብደላ ቃሰውን ጠይቆ እነዚህ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮችን ቫይረሱን ለመከላከል በሚል ዓላማ እናስገባ ለሚሉ ሰዎችም ሆነ ሀገር ውስጥ ለማምረት ፍቃድ ለሚጠይቁ ሰዎች ፈቃድ መስጠት አቁመናል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ቫይረሱን ለመከላል በሚል ዓላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡም ለጉምሩክ ኮሚሽን ደብዳቤ መፃፉን ነግረውናል፡፡እነዚህ ማስኮች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ሲደረግ የተሰሩበት ዓላማ በሽታውን ለመከላከል በሚል ባለመሆኑ እና ማስኮቹ በተገጠመላቸው የመተንፈሻ ቀዳዳ አማካኝነት ቫይረሱን ከመከላከል ይልቅ ለስርጭቱ ከፍተኛ አስተዋፆ ስለሚያደርጉ ማህበረሰቡ ማስኩን ከመጠቀም እንዲቆጠብ አሰጠንቅቀዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጲያ ምግብ እና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል በሚል ጥቅም ላይ ከሚውሉ ማስኮች ውስጥ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሰራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ ትዕዛዝ ማስተላፉን አስታውቋል፡፡ባስልጣኑ ከዚህ ቀደም ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮች የቫይረሱን ስርጭት ለመጨመር አስተዋፆ አላቸው በሚል ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
ነገር ግን ባለስልጣኑ ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት ህብረተሰቡ እነዚህን ማስኮች ከመጠቀም አልተቆጠበም እና ምን አይነት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው ሲል ኢትዮ ኤፍ ኤም በባለስልጠኑ የመድሀኒት ምዝገበ እና ፍቃድ ዳይሬክተር አቶ አብደላ ቃሰውን ጠይቆ እነዚህ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮችን ቫይረሱን ለመከላከል በሚል ዓላማ እናስገባ ለሚሉ ሰዎችም ሆነ ሀገር ውስጥ ለማምረት ፍቃድ ለሚጠይቁ ሰዎች ፈቃድ መስጠት አቁመናል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ቫይረሱን ለመከላል በሚል ዓላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡም ለጉምሩክ ኮሚሽን ደብዳቤ መፃፉን ነግረውናል፡፡እነዚህ ማስኮች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ሲደረግ የተሰሩበት ዓላማ በሽታውን ለመከላከል በሚል ባለመሆኑ እና ማስኮቹ በተገጠመላቸው የመተንፈሻ ቀዳዳ አማካኝነት ቫይረሱን ከመከላከል ይልቅ ለስርጭቱ ከፍተኛ አስተዋፆ ስለሚያደርጉ ማህበረሰቡ ማስኩን ከመጠቀም እንዲቆጠብ አሰጠንቅቀዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ግብጽ የህዳሴ ግድቡ ላይ በሚደረጉ ድርድሮች ወቅት “ ‘የቅኝ ግዛት ስምምነቶች ተፈፃሚ አይሆኑም’ በሚል በኢትዮጵያ ዘንድ የሚነሳው ጥያቄ አግባብ አይደለም፤ ስምምነቶቹ አሁንም ተፈፃሚ ናቸው” ስትል ከትናንት በስቲያ አርብ፤ ሰኔ 12፤2012 በድጋሚ ለጸጥታው ምክር ቤት በላከችው አቤቱታ አመለከተች።
የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ በማመመልከቻቸው አባሪ ላይ ኢትዮጵያ በ1894 ዓ.ም ከታላቋ ብሪታኒያ እና ከጣሊያን ጋር የተፈራረመችውን ስምምነት ዋቢ በማድረግ “ውሉ ተፈጻሚ ነው” ሲሉ መከራከሪያ አቅርበዋል፡፡ ሳሜህ “ኢትዮጵያ በቅኝ ተገዝታ አታውቅም። አባይን በተመለከተ የፈረመቻቸው ማንኛውም አይነት ስምምነቶች ነፃ አገር ሆና ስለፈረመቻቸው ገዢ ናቸው” ሲሉም ሞግተዋል።
“ኢትዮጵያ በአባይ ላይ የሚደረግ እና የውሃውን ፍሰት ሊይዝ የሚችል ማንኛውንም አይነት ግንባታ ላለማካሄድም ወይም እንዲካሄድ ላለመፍቀድ፤ በ1894ቱ ስምምነት ላይ ቃል ብትገባም ይህንን መቃወሟን ቀጥላለች” ስትል ግብጽ ኢትዮጵያን ወንጅላለች።ግብጽ በአጼ ምኒልክ በኩል የተፈረመውን ይህንን ስምምነትም አባሪ አድርጋም ለምክር ቤቱ ልካለች።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ በማመመልከቻቸው አባሪ ላይ ኢትዮጵያ በ1894 ዓ.ም ከታላቋ ብሪታኒያ እና ከጣሊያን ጋር የተፈራረመችውን ስምምነት ዋቢ በማድረግ “ውሉ ተፈጻሚ ነው” ሲሉ መከራከሪያ አቅርበዋል፡፡ ሳሜህ “ኢትዮጵያ በቅኝ ተገዝታ አታውቅም። አባይን በተመለከተ የፈረመቻቸው ማንኛውም አይነት ስምምነቶች ነፃ አገር ሆና ስለፈረመቻቸው ገዢ ናቸው” ሲሉም ሞግተዋል።
“ኢትዮጵያ በአባይ ላይ የሚደረግ እና የውሃውን ፍሰት ሊይዝ የሚችል ማንኛውንም አይነት ግንባታ ላለማካሄድም ወይም እንዲካሄድ ላለመፍቀድ፤ በ1894ቱ ስምምነት ላይ ቃል ብትገባም ይህንን መቃወሟን ቀጥላለች” ስትል ግብጽ ኢትዮጵያን ወንጅላለች።ግብጽ በአጼ ምኒልክ በኩል የተፈረመውን ይህንን ስምምነትም አባሪ አድርጋም ለምክር ቤቱ ልካለች።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 63 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሲሆን የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4457 የላብራቶሪ ምርመራ ስልሳ ሶስት (63) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4532 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (5 ከጤና ተቋም እና 13 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን ከአንድ የ75 ዓመት ወንድ የኦሮሚያ ክልል ነዋሪ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። ከዚህ በተጨማሪ በለይቶ በህክምና ማዕክል ውስጠ ክትትል ላይ የነበረች የ34 ዓመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወቷ ያለፈ ሲሆን በጠቅላላ ሁለት ሰዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ህይወታቸው አልፋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰባ አራት (74) ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4457 የላብራቶሪ ምርመራ ስልሳ ሶስት (63) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4532 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (5 ከጤና ተቋም እና 13 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን ከአንድ የ75 ዓመት ወንድ የኦሮሚያ ክልል ነዋሪ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። ከዚህ በተጨማሪ በለይቶ በህክምና ማዕክል ውስጠ ክትትል ላይ የነበረች የ34 ዓመት ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወቷ ያለፈ ሲሆን በጠቅላላ ሁለት ሰዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ህይወታቸው አልፋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰባ አራት (74) ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ቫይረሱ የተገኘባቸው 63 ሰዎች ሲሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው። በፆታ ሲታይ ደግሞ ወንድ(42) ሴት(21) ናቸው!
➡️ዕድሜያቸው ከ14-76 አመት የሆኑ
➡️ተጨማሪ 91 ሰዎች(67 ከአዲስ አበባ፣ 2 ከኦሮሚያ፣ 4 ከአማራ፣ 2 ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና 16 ከሶማሊ ክልሎች) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1213 ነው።
➡️የተገኙት ከአዲስ አበባ(31)፣ ከኦሮሚያ ክልል(5)፣ከአማራ ክልል(3) ፣ ከትግራይ ክልል(1)፣ከሶማሊ ክልል(9)፣ ከሀረሪ ክልል(1)፣ ከድሬዳዋ(4)፣ ከአፋር ክልል(4)፣ ከደቡብ ክልል(2) እና ከጋምቤላ ክልል(3) በድምር 63 ሰዎች ናቸው።
➡️በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 4532 ደርሷል።
➡️በጠና የታመሙት ቁጥር ደግሞ 32 ነው።
➡️በ24 ሰዓት ውስጥ 2 ሞት የተመዘገበ ሲሆን፣ እስካሁን በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 74 ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
➡️ዕድሜያቸው ከ14-76 አመት የሆኑ
➡️ተጨማሪ 91 ሰዎች(67 ከአዲስ አበባ፣ 2 ከኦሮሚያ፣ 4 ከአማራ፣ 2 ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና 16 ከሶማሊ ክልሎች) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1213 ነው።
➡️የተገኙት ከአዲስ አበባ(31)፣ ከኦሮሚያ ክልል(5)፣ከአማራ ክልል(3) ፣ ከትግራይ ክልል(1)፣ከሶማሊ ክልል(9)፣ ከሀረሪ ክልል(1)፣ ከድሬዳዋ(4)፣ ከአፋር ክልል(4)፣ ከደቡብ ክልል(2) እና ከጋምቤላ ክልል(3) በድምር 63 ሰዎች ናቸው።
➡️በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 4532 ደርሷል።
➡️በጠና የታመሙት ቁጥር ደግሞ 32 ነው።
➡️በ24 ሰዓት ውስጥ 2 ሞት የተመዘገበ ሲሆን፣ እስካሁን በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 74 ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጄኔራል መኮንኖች ጋር ተወያዩ።
ከመከላከያ ሠራዊት ጄኔራል መኮንኖች ጋር በአዲሱ የመከላከያ ግንባታ ስትራቴጂ ዝግጅት እና በተቋማዊ የግንባታ ሂደት ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
#FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ከመከላከያ ሠራዊት ጄኔራል መኮንኖች ጋር በአዲሱ የመከላከያ ግንባታ ስትራቴጂ ዝግጅት እና በተቋማዊ የግንባታ ሂደት ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
#FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ለዘመናት አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየው የጣና በለስ አየር ማረፊያ ዛሬ የሙከራ በረራውን አካሄደ።
በሙከራ የበረራ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ርዕሳነ መስተዳደሮች ተገኝተዋል።አካባቢው የተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰላጫ በመሆኑ መደበኛ የበረራ ፕሮግራሙን ለማካሄድ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚሰሩ ርዕሳነ መስተዳድሮች ገልጸዋል።የአካባቢውን ሰላም በአንጻራዊነት በማረጋጋት ቀጠናውን ወደ ልማት በሚደረገው ሂደትም የሁለቱ ክልል መንግስታት በትኩረት እንደሚሰሩ ተጠቁሟል።
ባለሃብቱ በራሳቸው ተነሳሽነት የአየር መንገዱን ለማስጀመር ያደረጉትን ተነሳሽነት በማመስገን በክልሉ ውስጥ ለሚያደርጉት የልማት እንቅስቃሴ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ አሻድሊ ሃሰን ተናግረዋል።የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በበኩላቸው የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ መንግስት ምላሽ ለመስጠት በሚደርገው ሂደት ውስጥ የባለሃብቱ ሚና የጎላ እንደሆነ ገልጸው ሌሎችም ለማገዝ መንግስት እንደሚሰራ ተናግረዋል።ተቋርጦ የነበረውን የጣና በለስ አየር ማረፊያ በአዲስ መልክ ለማስጀመር በኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ ወርቁ አይተነው እየተከናወነ ይገኛል።
ምንጭ: የመተከል ዞን ኮ/ን መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
በሙከራ የበረራ ስነ ስርዓቱ ላይ የአማራ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ርዕሳነ መስተዳደሮች ተገኝተዋል።አካባቢው የተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች መሰላጫ በመሆኑ መደበኛ የበረራ ፕሮግራሙን ለማካሄድ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚሰሩ ርዕሳነ መስተዳድሮች ገልጸዋል።የአካባቢውን ሰላም በአንጻራዊነት በማረጋጋት ቀጠናውን ወደ ልማት በሚደረገው ሂደትም የሁለቱ ክልል መንግስታት በትኩረት እንደሚሰሩ ተጠቁሟል።
ባለሃብቱ በራሳቸው ተነሳሽነት የአየር መንገዱን ለማስጀመር ያደረጉትን ተነሳሽነት በማመስገን በክልሉ ውስጥ ለሚያደርጉት የልማት እንቅስቃሴ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ አሻድሊ ሃሰን ተናግረዋል።የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በበኩላቸው የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ መንግስት ምላሽ ለመስጠት በሚደርገው ሂደት ውስጥ የባለሃብቱ ሚና የጎላ እንደሆነ ገልጸው ሌሎችም ለማገዝ መንግስት እንደሚሰራ ተናግረዋል።ተቋርጦ የነበረውን የጣና በለስ አየር ማረፊያ በአዲስ መልክ ለማስጀመር በኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ ወርቁ አይተነው እየተከናወነ ይገኛል።
ምንጭ: የመተከል ዞን ኮ/ን መምሪያ
@YeneTube @FikerAssefa
የወላይታ ዞን ምክር ቤት ራሱን ችሎ በክልልነት ለመደራጀት ባቀረበው ጥያቄ ላይ ለመወያየት አስቸኳይ ጉባኤ ጠራ።
ነገ ሰኞ ሰኔ 15፤ 2012 በሶዶ ከተማ፣ ጉተራ አዳራሽ ይካሄዳል የተባለው አስቸኳይ ጉባኤ በክልል ጥያቄ ቀጣይ አካሄዶች ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።የወላይታ ዞን የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ ኃላፊ ሶልያና አዴሎ የነገው ስብሰባ ዋነኛ አጀንዳ “የክልል አደረጃጀት የደረሰበት ደረጃ ላይ መወያየት እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ” መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። “በዋናነት አጀንዳው የክልል ጥያቄው አሁን የደረሰበትን ደረጃ መገምገም ነው። አባላቱ ናቸው ተወያይተው አቅጣጫ የሚያስቀምጡት” ብለዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
ነገ ሰኞ ሰኔ 15፤ 2012 በሶዶ ከተማ፣ ጉተራ አዳራሽ ይካሄዳል የተባለው አስቸኳይ ጉባኤ በክልል ጥያቄ ቀጣይ አካሄዶች ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።የወላይታ ዞን የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ ኃላፊ ሶልያና አዴሎ የነገው ስብሰባ ዋነኛ አጀንዳ “የክልል አደረጃጀት የደረሰበት ደረጃ ላይ መወያየት እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ” መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። “በዋናነት አጀንዳው የክልል ጥያቄው አሁን የደረሰበትን ደረጃ መገምገም ነው። አባላቱ ናቸው ተወያይተው አቅጣጫ የሚያስቀምጡት” ብለዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
የሉቴናንት ጄኔራል መሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ የአዲስ አበባ ጉብኝት "ከሱዳን ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እውቅና ውጪ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ምክር የተከናወነ ነው" በሚል የተሰራጨን መረጃ የሱዳን ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት "ሐሰት" ሲል አጣጣለ።
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa