YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ቻናል እና ዌብሳይት ጥቆማ | የሚሰራ ይበረታታል !!

ጋዜጠኛ ተስፋዬ ጌትነት ይባላል እሁድ እሁድ በእንግሊዘኛ ቋንቋ እየታተመ በሚወጣው ካፒታል ጋዜጣ ላይ ከአምስት አመታት በላይ ሰርቷል። አሁን ላይ ከካፒታል ጋዜጣ ከወጣ ብኃላ በራሱ መስራት ከጀመረ ሰነባብቷል ለኛ ለየኔቲዩብም የመረጃ ምንጫችን ከሆነ ስንበትበት ብሏል ዛሬ የራሱን ዌብሳይት ( fidelpost.com ) ላይ መስራት ጀምሯል።

fidelpost.com ላይ የምታገኙት
💥ትኩስ ዜናዎች

💥ቃለ መጠይቆችና

💥ትንታኔ ፅሁፎች በአማረኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋ ይቀርቡበታል።

የቻናላችን ቤተሰቦች የተስፋዬ ጌትነትን ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ። ⬇️

@tesfaget55 @tesfaget55
@tesfaget55 @tesfaget55
‘ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፎ የሚሰጥ ውይይት ፈጽሞ አላደረገችም፣ ወደፊትም አታደርግም’

በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ፣ የግብጽ እና የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የውሃ ሃብት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድኖቻቸው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ እኤአ ከጃንዋሪ 13 እስከ 15 ቀን 2020 በዋሽንግተን ዲሲ ሲያካሂዱት የነበረው ውይይት በጥሩ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል። የውይይቱን ውጤት እና የኢትዮጵያን አቋም አስመልክቶ ክቡር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም የተነሱ ዋና ዋና ሃሳቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል።

📌 ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድቡ ጋር በተያያዘ ትናንት በተደረገው የመግባቢያ ነጥብ ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፎ የሚሰጥ አንዳችም ውይይት ፈጽሞ አላደረገችም፣ ይሄ ወደፊትም የኢትዮጵያ ቀዳሚው መርህ ሆኖ ይቀጥላል።
📌 ከግድቡ ጋር የሚደረጉ ድርድሮች እና ውይይቶች ኢትዮጵያ ሌሎች ግድቦችን የመገንባት መብቷን የማይጋፋ ነው።
📌 ከዚህ ቀደም ለውይይቱ መጓተት እንደምክንያት ሲነሳ የነበረውን የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ከታችኛው ተፋሰስ አገራት ግድቦች የማያያዝ ውኔታ እንደቀር ማድረግ ተችሏል።
📌 የግድቡ ግንባታ በአሁኑ ወቅት በተጠናከተረ ሆኔታ ቀጥሏል፣ ግድቡ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት እየተደገፈ ነው።
📌 ግድቡ ሲጠናቀቅ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የቱሪዝምና የአሳ እርባታ ልማቶችን ይኖሩታል።
📌 የቴክኒክ ውይይቱ ብሎም ከህግ ጋር የሚያያዙት ጉዳዮች አሁንም በዘርፉ ልምድና ክህሎቱ ባላቸው፣ በሐገር ፍቅር እንዲሁም በከፍተኛ ኃላፊነት ብቁ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እየተመራ ነው።
📌 ግድቡ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ስም በከፍተኛ ደረጃ በበጎ የሚያሳድግ፣ የመደራደር አቅም እና ተደማጭነትን ያጎለብታል።
📌 ኢትዮጵያ ትክክለኛና በመርህ ላይ የተመሰረተ አቋም እስካላት ድረስ የውይይት ቦታው ተጽእኖ አያሳድርባትም።
📌 በያዝነው ዓመት መጨረሻ ግድቡን ውሃ መሙላት ይጀምራል። ሙሌቱ በጥቅሉ ከ4 እስካ 7 ዓመት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
📌 እየተደረገ ያለው ውይይት የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ ለመስጠት ሳይሆን የአባይ ወንዝ ድንበር ተሻጋሪ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከታችኛው የተፋሰሱ አገራት ጋር በትብብር ማደግ ከሚለው የኢትዮጵያ አቋም በመነሳት ነው።
📌 ከግድቡ ጋር በተያያዘ በተለይ ኢትዮጵያውያን የመገናኛ ብዙሃን አባላት፣ ተንታኞች፣ አክቲቪስቶች እና ሌሎች ጸሃፊዎች የሚያቀርቧቸው መረጃዎች ሚዛንን የጠበቁ፣ የኢትዮጵያን የመደራደር አቅም የሚገነቡ፣ ከአሉባልታ ይልቅ በጥልቅ መረጃ የታገዙና የኢትዮጵያን የመደራደር አቅም ላይ ተጨማሪ ጉልበት የሚሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን ግድቡ ላይ አሉታዊ ጥርጣሬ እንዲኖራቸው ሳይሆን ትክክለኛውን መረጃ እንዲያውቁ ድጋፋቸውም የበለጠ እንደጠናከር በማደረግ ረገድ የበኩላቸውን ከፍተኛ ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ: የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ከግብጽና ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችና የውሃ ሀብት ሚኒስትሮች ጋር በዋሽንግተን ውይይት ካደረጉ በኋላ ከሰጡት መግለጫ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድቡ ጋር በተያያዘ ትናንት በተደረገው የመግባቢያ ነጥብ ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፎ የሚሰጥ አንዳችም ውይይት ፈጽሞ አላደረገችም፣ ይሄ ወደፊትም የኢትዮጵያ ቀዳሚው መርህ ሆኖ ይቀጥላል።

• ከግድቡ ጋር የሚደረጉ ድርድሮች እና ውይይቶች ኢትዮጵያ ሌሎች ግድቦችን የመገንባት መብቷን የማይጋፋ ነው።

• ከዚህ ቀደም ለውይይቱ መጓተት እንደ ምክንያት ሲነሳ የነበረውን የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ከታችኛው ተፋሰስ አገራት ግድቦች የማያያዝ ሁኔታ እንዲቀር ማድረግ ተችሏል።

• የቴክኒክ ውይይቱ ብሎም ከህግ ጋር የሚያያዙት ጉዳዮች አሁንም በዘርፉ ልምድና ክህሎቱ ባላቸው፣ በሐገር ፍቅር እንዲሁም በከፍተኛ ኃላፊነት ብቁ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እየተመራ ነው።

• ኢትዮጵያ ትክክለኛና በመርህ ላይ የተመሰረተ አቋም እስካላት ድረስ የውይይት ቦታው ተጽእኖ አያሳድርባትም።

• በያዝነው ዓመት መጨረሻ ግድቡን ውሃ መሙላት ይጀምራል። ሙሌቱ በጥቅሉ ከ4 እስከ 7 ዓመት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

• እየተደረገ ያለው ውይይት የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ ለመስጠት ሳይሆን የአባይ ወንዝ ድንበር ተሻጋሪ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከታችኛው የተፋሰሱ አገራት ጋር በትብብር ማደግ ከሚለው የኢትዮጵያ አቋም በመነሳት ነው።

Via EBC
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ሶስት ምክትል ፕሬዚዳንቶቹን ከስራ ማገዱን አስታወቀ።

በዩኒቨርሲቲው የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ ሶስቱ ምክትል ፕሬዚዳንቶች የታገዱት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ውሳኔ መሰረት መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ካለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ጀምሮ በመማር ማስተማር ስራው ላይ አለመረጋጋት ገጥሞት መቆየቱ ይታወቃል።

የመታገዳቸው ዝርዝር ምክንያት ለጊዜው አለመገለጹን ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

Via:- EBC
@YeneTube @Fikerassefa
ረቂቁ የኤክሳይዝ ታክስ ከ 1,300 ሲሲ በታች ላሉ አዳዲስ ተሽከርካሪዎች የሚጣለውን የታክስ መጠን ከ 30% ወደ 5% አወረደ!

ይህም የአዳዲስ ቤት መኪኖችን ዋጋ እስከ 83% ይቀንሰዋል ተብሏል።

Via:- Capital newspaper / Elias Meseret
📸 አጋፔ መኪና መሸጫ
@YeneTube @Fikerassefa
#እስራዔል ተማሪዎቿ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ እንዳያደርጉ መወሰኗን ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘግቧል፡፡ ለእስራዔላዊያን በተለይ ከሱማሌ ክልል የሚነሳ የደኅንነት ስጋት (የሽብር ጥቃት) እንዳለ የእስራዔል መንግሥት ያምናል፡፡
በዚህ ዐመት ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ አየር በረራዎችም ተሰርዘዋል ብሏል ዘገባው፡፡

ምንጭ:- ዋዜማ ራዲዮ
@YeneTube @FikerAssefa
ግብጽ በዋሽንግተኑ የሕዳሴ ግድብ ቅድመ ስምምነት አስቸጋሪ አጣብቂኝ ውስጥ ገብታለች ሲል ማዳ ማስር የተሰኘ የሀገሪቱ ድረ ገጽ ዘግቧል፡፡ ግብጽ ደካማ የድርድር አቋም ላይ ናት፤ በማያዋጣት ስምምነት ውስጥ እንድትገባ አሜሪካ ግፊት እያደረገችባት ነው ሲሉ ስማቸው ያልተጠቀሰ ከፍተኛ ባለስልጣናት ነግረውኛል ብሏል፡፡ የሀገራቱ ተደራዳሪዎች መግለጫ ያወጡት በአሜሪካ ግፊት ነው፡፡

ምንጭ:- ዋዜማ ራዲዮ
@YeneTube @Fikerassefa
Audio
በደቡብ እና በሲዳማ ክልሎች መሀከል የንብረት ክፍፍል ቆጠራ መጀመሩ ተሰማ፡፡

Via Sheger Radio
@YeneTube @FikerAssefa
የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር ሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የደኅንነት ካሜራ በመግቢያ እና መውጫ በራቸው ላይ እንዲገጥሙ ማዘዙን ኢፕድ ዘግቧል፡፡ አአዩ፣ ጎንደር፣ ጅማ፣ ሀዋሳ እና ወቻሞ ዩኒቨርስቲዎች ቀደም ሲል በራሳቸው ተነሳሽነት ካሜራውን ተክለዋል፡፡

Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
  238 ኢትዮጵያዊያን ከሌባኖስ ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ በተለያዩ ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ ከጥር 6 እስከ 11 ባሉት ተከታታይ ቀናት  238 ኢትዮጵያዊያን ከሌባኖስ ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ።

መንግስት ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲን ትኩረት አድርጎ በመስራቱ  238 ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከሌባኖስ ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው በተለያዩ ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ከጥር 6 እስከ 11 ባሉት ተከታታይ ቀናት  238 ኢትዮጵያዊያን ከሌባኖስ ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ። ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ በመግለጫዉ የኢትዮ-ጅቡቲ የጠረፍ አስተዳደሮች የድንበር ደህንነት ትብብር መፍጠር፣ ሕገ ወጥ ዝውውርን መከላከል እንዲሁም በሃገራቱ መካከል የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በተመለከተ ፍሬያማ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል።

መግለጫዉ የኢትዮ- ቻይና ዲፕሎማስያዊ ግንኙንት፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተለያዩ የአፍሪካ አገራት ጉብኝት እና ዉጤቱ ፣ እንዲሁም በዋሽንግተን ዲሲ በህዳሴ ግድብ ሙሌት እና ውኃ አለቃቀቅ ላይ የተካሄደዉን ምክክር ዉጤቱን በተመለከተ ቃል- አቀባዩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ሰበር ዜና ‼️

በጎንደር ዘንድሮ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ በተኮስ የተቀናጀ ከፍተኛ ፍንዳታ ለመፈፀም በዝግጅት ላይ የነበሩ ሁለት የጥፋት ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ

በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ ዘንድሮ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ በተኮስ የተቀናጀ ከፍተኛ ፍንዳታ ለመፈፀም የሽብር ተልዕኮ ተቀብለው በዝግጅት ላይ የነበሩ ሁለት የጥፋት ቡድን አባላት ከአራት ኤፍ ዋን ቦምብ እና ከ200 ጥይቶች ጋር በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ክትትል እንዲሁም በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ክልል ፀጥታ ሀይሎች እና በአካባቢው ህብረተሰብ ትብብር በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ የጥፋት ቡድን ያሰማራውን አካል በቀጣይ ይፋ እንደሚያደርግ እና የጥፋት ሀይሎቹ ግን አደጋውን ቢያደርሱ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እና መኖሪያ ቤት በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚሰጣቸው ቃል የተገባላቸው መሆኑን እንዳረጋገጠ አስታውቋል።

የፀጥታ ሀይሎች በቅንጅት ቀን ከለሊት ደከምኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት በመጠበቃቸው በዘንድሮው የጎንደር የጥምቀት በዓል ታዳሚዎች ላይ ሽብር በመፈፀም የንፁሃንን ዜገች ህይወትለመቅጠፍና በንብረት ላይ አደጋ ለማድረስ የታለመውን አደጋ ማክሸፍ መቻሉን ነው የገለፀው።

ዘንድሮ በመላው ሀገሪቱ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ተመሳሳይ ተልዕኮ ያላቸው አካላት እኩይ ተግባራቸውን ሊፈፅሙ ስሚችሉ ህብረተሰቡ በአካባቢው ከሚገኘው የፀጥታ ሀይል ጋር በመቀናጀት ከበዓሉ ጎን ለጎን ሰላሙንም እንዲጠብቅ አሳስቧል።

ምንጭ:- FBC
@YeneTube @Fikerassefa
በቻይና በገዳይነቱ አደገኛ ነው የተባለለት ቫይረስ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎችን እንደያዘ ተገለፀ።
እስካሁን 41 ሰዎች በዚህ ቫይረስ መያዛቸው በላብራቶሪ የተረጋገጠ ሲሆን፥ ባለሙያዎች የተያዙት ሰዎች ቁጥርን 1 ሺህ 700 አድርሰውታል።

በውሃን ከተማ እስካሁን በቫይረሱ ሁለት ሰዎች ሞተዋል ተብሏል።
በጃፓንና በሆንግ ኮንግም አንድ አንድ ሰው በቫይረሱ የተያዘ ሰው እንደተገኘባቸው ነው የተገለፀው።

ከዚህች የቻይና ከተማ ቀጥታ በረራ የሚደረግባቸው ሀገራት ከከተማዋ ተነስተው በሚመጡ አውሮፕላኖች ተሳፋሪዎች ላይ በአውሮፕላን ማረፊያዎቻቸው ምርመራ ማድረግ ጀምረዋል።

ሲንጋፖርና ሆንግ ኮንግ እንዲሁም ዩናይትድ ስቴትስ መርመራውን ቀድመው ጀምረዋል።
የቻይና ባለስልጣናት ቫይረሱ ከአንድ ሰው ወደ ሌላ ሰው የመተላለፍ ባህሪ እስካሁን እንዳልታየበት ተናግረዋል።

በአውሮፓውያኑ 2002 ላይ በዚያው በቻይና የዚህ ቫይረስ ወረርሽኝ ተቀስቅሶ ከ8 ሺህ በላይ ሰዎች የተያዙ ሲሆን፥ በወቅቱ 774 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
 
ምንጭ፦ ቢቢሲ / FBC
@Yenetube @Fikerassefa
በተለያዩ አካባቢዎች የሚኖረው ያልተረጋጋ ሰላም ምርጫው ላይ ችግር እንዳይፈጥር መንግሥትን ተስፋ በማድረግ እየሰራ መሆኑን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡

የምርጫ ቦርድ አባል የሆኑት ዶክተር ጌታሁን ካሳ እንደተናገሩት፤ በአገሪቱ ያለው ሰላምና መረጋጋት እጅግ ፈታኝ ነው፡፡ በተለያዩ ጊዜያትም የተለያዩ ችግሮች በየጊዜው ይታያሉ፡፡

ስለሆነም ምርጫው እንዳይደናቀፍ መንግሥት በሚገባ መስራት አለበት፡፡ ምርጫ ቦርድ ምርጫው ሰላማዊና ነፃ እንዲሁም ፍትሃዊ እንዲሆን እየሰራ ነው፡፡ ሆኖም የጸጥታ ማስከበሩና ሰላማዊ ምርጫ እንዲካሄድ የማድረጉ ኃላፊነት የመንግሥት ነውና እርሱን ተስፋ አድርገን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ዶ/ር ጌታሁን፡፡

ሰላምን የሚያደፈርስ አካል ካለ እርምጃውንም ሆነ ሥራውን መስራት ያለበት መንግሥት ነው ያሉት ዶ/ር ጌታሁን ምርጫ ቦርድ ምርጫው ነፃ፤ ፍትሃዊና ተአማኒ እንዲሆን ከመስራት ውጪ ሊያደርገው የሚችለው ነገር እንደማይኖር ገልጸዋል፡፡

ምርጫ ቦርድ የሰላም ማስከበር ሥራን ለመስራት ኃላፊነቱ እንደማይፈቅድለት የሚያስረዱት ዶክተር ጌታሁን፤ በአገር ደረጃ ከ45ሺ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች በመኖራቸው መንግሥት በእነዚህ ጣቢያዎች ላይ ሰላማዊ ምርጫ እንዲኖር ያደርጋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል፡፡

ምንጭ፡-ኢፕድ
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በተዘጋጀው የመገናኛ ብዙሃንና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የስነ ምግባርና አሰራር ረቂቅ መመሪያ ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው

በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ተዘጋጅቶ በቀረበው የመገናኛ ብዙሃንና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የስነ ምግባርና አሰራር ረቂቅ መመሪያ ላይ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ውይይት እየተደረገበት ነው፡፡

ጋዜጠኞችና የመገናኛ ብዙሃን ከምርጫ ጣቢያዎች በ2 መቶ ሜትር ርቀት ዙሪያ ሁነው ለመዘገብ እንዲችሉ እውቅና እንዲሰጣቸው ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉም በረቂቅ መመሪያው ላይ ተመልክቷል፡፡
የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን ማንኛውም ፓርቲን ከመደገፍና ከማጥላላት የፀዱ መሆን እንዳለባቸውም ተመላክቷል፡፡

ጋዜጠኞችና መገናኛ ብዙሃን እውነተኛ በማፈላለግ ረገድ ምንጩን በሚያውቁት እውነታ ላይ ተመስርተው ዘገባዎቻቸውን መስራት እንዳለባቸው ረቂቅ መመሪያው ይገልጻል፡፡
የስነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት ፈቃድ አሰጣጥ እና ስነምግባር ለመደንገግ የወጣ ረቂቅ መመሪያም በውይይቱ ላይ ቀርቧል፡፡

በሁለቱ መመሪያዎች ላይ ውይይት ተደርጎ የሚገኙ ግብዓቶችን ለማሰባሰብ የዛውሬው መድረክ መዘጋጀቱን ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

Via:- EBC
@YeneTube @Fikerassefa
የየኔቲዩብ ቤተሰቦች የኢትዮጵያ ሙዚቃ ኢንዱስትሪ ለመርዳት የቦኩሎን ይወጡ!!

#የኔ_ዜማ የተሰኛውን የዳዊት ፅጌ አልበም ኦርጅናሉን በመግዛት በቀጥታ አርቲስቱን ይርዱ!!

ለመልካም ተግባራችሁ እናመሰግናለን!!
@YeneTube @Fikerassefa
Forwarded from YeneTube
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🎊እንኳን አደረሳችሁ🎉
ፈረስ ለበዓሉ አንድ ሙክት በግ እና ሁለት ዶሮዎች አዘጋጅቶላችኋል 🎁🎁🎁

ከዚህ ሽልማት አሽናፊ ለመሆን
1. ፈረስ ይዘዙ እና የሄዱበትን ሂሳብ ስክሪን ሻት አድርገው ይላኩልን
2. ይህንን ፓስት ላይክ እና ሼር ያድርጉ

ደንብና ግዴታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ።
Forwarded from YeneTube
Samsung Galaxy A10s
2019 Model Phone
Brand New Packed &
Original with Full Accessories
6.2inch screen size
32GB Storage
13MP camera 1080HD
4000mAh battery capacity
Dual Sim Slot

📩 @CloudMultiTrading 📩
📞 0944182119 📞

@CloudTrading @CloudTrading
🔥1
"ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊታችን የኩራታችን ምንጭ ነው"
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ
ዛሬ ከመከላከያ ሠራዊታችን አመራሮች ጋር በአዲስ አበባ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን ሂደት ተከታትለናል ሲል ዶ/ር አብይ አህመድ በfacebook ገፃቸው አስታውቋል ።

@YeneTube @Fikerassefa