YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኢህአዴግ ውህደት የህዝቦችን መቀራረብ ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን የሱማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ተናገሩ፡፡

@Yenetube @Fikerassefa
ኤርትራዊው ድምፃዊ በአዲስ አበባ ጥቃት ደረሰበት!

''ወዲ ማማ'' በሚል የቅጽል ስም የሚታወቀው ኤርትራዊ ሙዚቀኛ፣ ተክለ ነጋሲ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በማይታወቁ ሰዎች ጥቃት እንደተፈጸመበት ተነገረ።

ድምጻዊው ባለፈው እሁድ ከሰዓት በኋላ ገርጂ በሚገኘው አንበሳ ጋራዥ አካባቢ በእግሩ በሚጓዝበት ወቅት ማንነታቸውን በማያውቃቸው አምስት ሰዎች ጥቃቱ እንደተፈጸመበት ተክለ ለቢቢሲ ተናግሯል።

ጨምሮም ጥቃቱን ከፈጸሙበት ሰዎች ጋር ምንም አይነት ንግግር እንዳልነበረና አላማቸው ጉዳት ማድረስ እንደነበረ ገልጿል። "ምንም አይነት ንግግር አልተናገሩኝም፤ በቀጥታ ወደ ድብደባ ነበር የገቡት" ሲል ተናግሯል።

ድምጻዊው ተክለ ነጋሲ ሱዳን ውስጥ በነበረበት ጊዜ በደረሰበት የመኪና አደጋ እግሩ ተሰብሮ እንደነበር ጠቅሶ፤ እግሩ ላይ ብረት እንዳለውና ጥቃት ያደረሱበት ሰዎች በተደጋጋሚ በአደጋው ጉዳት የደረሰበት እግሩን ይመቱት እንደነበር ተናግሯል።

ከዚህም በመነሳት ከባድ አደጋን ለማድረስ ዕቅድ እንደነበራቸውና ጥቃቱ የታቀደና "በደንብ የሚያውቁኝ መሆን አለባቸው" በማለት ግምቱን አስቀምጧል።

ድማጻዊ ወዲ ማማ በደረሰበት ድብደባ ሳቢያ በቀኝ እጁ፣ በአፍንጫው፣ በጭንቅላቱና የግራ ኩላሊቱ ላይ ከባድ ጉዳት እንደደረሰበትም ለቢቢሲ ተናግሯል።

Via:- BBC News Amharic
@Yenetube @Fikerassefa
የግዮን ሆቴል ጣሪያ ወድቆ በሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ።

የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደገለጸው ከ15 ደቂቃዎች በፊት ስቴዲየም አካባቢ የሚገኘ ግዮን ሆቴል ጣሪያው መውደቁን ተናግረዋል።የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ እንዳሉት የሆቴሉ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ጣሪያው መውደቁን ተናግረዋል።በአደጋው እስካሁን የተጎዱ ሰዎች ያልተወቀ ሲሆን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ወደ ቦታው አቅንተው አደጋውን ለመቆጣጠር እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ በሴካፋ ውድድር አትሳተፍም!

ኢትዮጵያ በመጪው ቅዳሜ በሚጀመረው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የእግር ኳስ ውድድር /ሴካፋ/ እንደማትሳተፍ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።ኢትዮጵያ ከሕዳር 27 እስከ ታህሳስ 9 ቀን 2012 ዓ.ም በዩጋንዳ በሚካሄደው ውድድር እንድትሳተፍ የምድብ ድልድል ውስጥ መካተቷ ይታወቃል።ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከውድድሩ ከሚገኘው ጥቅምና ከሚወጣበት ወጪ አንጻር መሳተፉ አስፈላጊ አይደልም ብሏል። የፌዴሬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ባህሩ ጥላሁን እንደገለጹት ፌዴሬሽኑ ያለውን ውስን በጀት ለሴካፋ ውድድር ማዋሉ ጠቃሚ እንዳልሆነ ያምናል። ከዚህም ባለፈ አንድ ውድድር የሚለካው በተሳትፎ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ጥቅሞች ተገምግመው በመሆኑ በውድድሩ መሳተፉ ጠቃሚ አይደለም ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።እናም ኢትዮጵያ በምድብ ድልድል ውስጥ የተካተተች ብትሆንም በውድድሩ አትሳተፍም ሲሉ አረጋግጠዋል።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በካይሮ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የውሃ ጉዳይ የሚኒስትሮች ስብሰባ ተጠናቀቀ!

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትና አለቃቀቅ ጉዳይ ዙሪያ የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች በግብፅ ያካሄዱት የቴክኒክ ስብሰባ ተጠናቀቀ።ስብሰባው የግድቡ የውኃ ሙሌትና አለቃቀቅን በሚመለከት ህዳር 5 እና 6 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው ስብሰባ ውይይት ተደርጎባቸው የጋራ መግባባት ባልተደረሰባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን በማድረግ ነው የተካሄደው።የኢፌዴሪ ውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ስለሺ በቀለ፥ የአባይ ውሃ ለኢትዮጵያ ድህነትን ማጥፊያ እና የህልውና ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፥ የአሁኑንና የወደፊት ትውልድ የመጠቀም መብትን የማይገድብ መሆኑን ተናግረዋል።ስብሰባው በግድቡ ሙሌት እና የውኃ አለቃቀቅ ዙሪያ በአዲስ አበባ በተጀመረው ውይይት መሰረት ቀጥሎ የተካሄደ ነው።በስብሰባው ላይ የዓለም ባንክ እና የአሜሪካ መንግስት ተወካዮች በታዛቢነት መሳተፋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በአዲስ አበባው ምክክር ሶስቱ ሀገራት በግድቡ ውሃ አያያዝና አለቃቀቅ ዙሪያ አቋማቸውን አንፀባርቀው በስፋት መወያየታቸው ይታወሳል።

Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
💥ማስታወቂያ💥
School of American English

📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ

አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን

አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022


💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥

ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል

T.me/SCHOOLOFAMERICAN
ፌደራሊስት መሆናቸውን የሚገልጹ የፖለቲካ ሃይሎች በመቀሌ መሰብሰባቸውን የትግራይ ክልል ብዙኻን መገናኛ ዘግቧል፡፡ ስብሰባው ሕገ መንግሥታዊነት እና ኅብረ ብሄራዊው ፌደራላዊ ሥርዓት ባጋጠሙት ፈተናዎች እና ዕድሎች ላይ ይመክራል፡፡ የስብሰባው አዘጋጅ ትግራይ ክልል ነው፡፡ የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር ደብረ ጺዮን ገብረ ሚካዔል በሀገሪቱ የጠቅላይነት አዝማሚያ እየተንሰራፋ መምጣቱ ስጋት እንደፈጠረ በመክፈቻ ንግግራቸው አውስተዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ኦነግ በቀጣዩ ምርጫ በኦሮሚያ ክልል አብላጫውን ወንበር አገኛለሁ ብሎ እንደሚያምን ሊቀመንበሩ ኦቦ ዳውድ ኢብሳ ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል፡፡ በፌደራሉ ፓርላማም በርካታ ወንበሮችን እንደሚያገኙ ዕምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ግንባሩ ለምርጫ የሚቀርበው ባሁኑ አደረጃጀቱ ነው፡፡ ከኦሕዴድ ጋር የተጀመረውን ውይይት ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ለመቀጠል አስቸጋሪ ይሆናል ብለዋል።

Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
በመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በአሜሪካን የመጀመሪያ ቀን የመከላከያ ትብብር ውይይቱን አካሄዷል።

@YeneTube @FikerAssefa
ህወሓት የብልፅግና ፓርቲን የማትቀላቀል ከሆነ አረና ትግራይ የብልፅግና ፓርቲን በደስታ ይቀላቀላል::

አምዶም ገብረስላሴ (የአረና ትግራይ ህዝብ ግንኙነት)
@Yenetube @Fikerassefa
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ሊገጥሟት የሚችሉ አራት ሴናሪዮዎች ይፋ ተደረጉ!

አራቱ ሴናሪዎች /እጣ ፈንታ/ ይፋ የተደረጉት ህዳር 23/2012 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል "የምንፈልጋት ኢትዮጵያ በ2032" በሚል ርእስ በተደረገዉ የዉይይት መድረክ ላይ ነዉ ።
በመድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ የክልል ርእሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች ፣፣ የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ፣የሀገር ሽማግሌዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል።የዴስቲኒ ኢትዮጵያ በአገሪቱ ከሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶች፣ ክልሎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ምሑራን የተውጣጡ 50 ሰዎች በጥንቃቄ በመምረጥ ላለፉት ስድስት ወራት ዝግ ስብሰባዎችን በማካሄድ ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት አገራችን ሊገጥሟት የሚችሉ አራቱን ሴናሪዎች መቅረፁን የዴስቲኒ ኢትዮጵያ አስተባባሪ አቶ ንጉሴ አክሊሉ ተናግረዋል ።

አራቱ ሴናሪዎች አፄ በጉልበቱ ፣ ሰባራ ወንበር ፣ የፋክክር ቤት እና ንጋት ናቸዉ ።
በመድረኩ ላይ ክብርት የሰላም ሚኒስቴር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ይህን ሴናሪዮ ለማዘጋጀት የተነሱ ግለሰቦችን፣ የተለያዩ የፖለቲካ አቋም ይዘዉ በሃሳብ አንድነት ተሰባስበዉ ለሴናሪዮ ሃሳብ ያዋጡ 50 ሰዎችን አመስግነዋል።ሳይቸግረን የቸገረን ራስን በሌላዉ ቦታ አስቀምጦ መየት ነዉ ያሉት ክብርት ሚኒስትሯ ይህን ሴራኒዮ ያዘጋጁ አካላት አብሮ በመቀራረብ ዉስጥ ያለ ሃይልን አሳይተዉናል ብለዋል ።ከአራቱ ሴናሪዮ (እጣ ፈንታዎች) ውስጥ ለኢትዮጵያ “ንጋት” እንደሚመኙ የገለፁት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ለዚህም ነገን ዛሬን መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።የሴራኒዮ አባላት ያሳለፏቸዉን ዉጣ ዉረድና የቀጣይ ምኞታቸዉን ከ1-3 ደቂቃ እየተሰጣቸዉ ሃሳባቸዉን አካፍለዋል።

ምንጭ: ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
በአብን አመራሮች አባላት ላይ የተካሄደ ፓለቲካዊ እስር አስመልክቶ ከአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን ) መግለጫ።
@Yenetube @Fikerassefa
እንቦጭ በጢንዚዛዎች ሊበላ ነው።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የእንቦጭ አረም በጣና ላይ መከሰቱን የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ካሳወቁበት ጊዜ ጀምሮ አረሙን ለማስወገድ የተለያዩ ስራዎችን ዩኒቨርሲቲው ሲሰራ የቆየ ቢሆንም አረሙን ማስወገድ አልተቻለም።አረሙ በጣና ሀይቅና አዋሳኝ በሚገኙ ወረዳዎች ላይ በፍጥነት እየተዛመተ ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ችግሩ ያጋጠማቸው ሀገራት ስነ-ህይወታዊ ዘዴ/ጢንዚዛ/ በመጠቀም ውጤታማ የሆነ ስራ እንደሰሩ የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ባዮቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመሆን በስነ-ህይወታዊ ዘዴ/ጢንዚዛ/ ላይ ምርምር ሲያደርግ ቆይቶ አሁን እንቦጭን ብቻ የሚመገቡ ብሎች/ጢንዚዛዎች/ ወደ ጣና ሀይቅ ለመልቀቅ ያመች ዘንድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ወሳኝ ውይይት አድርጓል፡፡ ጢንዚዛዎችን ቀጥታ ወደ ሀይቁ ከመለቀቃቸው በፊት ግን በአባይ ረግራጋማ ቦታዎች ላይ ሙከራ ተደርጎ ውጤቱን ከታወቀ በኋላ እንቦጭ በብዛት ከተስፋፋበት የጣና ሀይቅ እንዲለቀቁ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲም የእንቦጭ አረምን በሳይንሳዊ ዘዴ ለማስወገድ በርካታ እንቦጭን ብቻ የሚመገቡ ጢንዚዛዎችን ከወንጅ ስኳር ኮርፖሬሽን የምርምር ማዕከል በማምጣት የተለያዩ የሙከራ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል፡፡

በመሆኑም ከምርምሩ በተገኘው ውጤት መሰረት እንቦጭን ለማጥፋት ጢንዚዛዎች በጣና ሀይቅ ላይ ቢለቀቁ የሀይቁ የሙቀት መጠን ከ14-18 ድግሪ ሴንቲ ግሬድ በመሆኑ ለጢንዚዛዎች መራባት ተስማሚ ስለሚሆን ውጤታማ እንደሚሆኑ በባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የብሉ ናይል ውሃ ምርምር ተቋም ተመራማሪ እንዲሁም በባዮሎጂ ት/ት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ጌታቸው በነበሩ ገልፀዋል፡፡የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ እና መምህር እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ጋሻው ጥላሁን እንዳሉት እንቦጭን ለማስወገድ ሁሉንም የማስወገጃ አማራጮችን መተግበር እንዳለ ሆኖ ነገር ግን ጊዜንም ሆነ የገንዘብ ወጭ ብዙም የማይፈልገው ብልን/ጢንዝዛንም/ መጠቀም ተገቢና አዋጭ በመሆኑ በፍጥነት ፈቃዱን አግኝቶ ወደ ትግበራ መግባት እንዳሚገባ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ:አሐዱ ሬዲዮ
@YeneTube @FikerAssefa
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች፣ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች በሙሉ የሰጠው ማሳሰቢያ!

<<በአሁኑ ስዓት በዩኒቨርስቲያችን የኩፍኝ በሽታ ምልክቶች እየታዩ ስለሆነ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ካሁን በፊት ቢከተቡም ባይከተቡም ክትባቱ በዘመቻ መልክ ይሰጣል፡፡ ስለሆነም የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ክትባቱን እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡የኩፍኝ መከላከያ ክትባቱ ህዳር 25-30/2012 ድረስ ለተከታታይ 6 ቀናት ክትባት ይሰጣል፡፡ ስለዚህ ማንኛውም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ክትባቱን በተጠቀሰው ቀንና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በተዘጋጁ የክትባት ጣቢያዎች እየመጣችሁ እንድትከተቡ እናሳስባለን፡፡
#ማሳሰቢያ ፡-ክትባቱ ለነፍሰጡሮች የተከለከለ ነው!!>>

@YeneTube @FikerAssefa
በአብን አመራሮች አባላት ላይ የተካሄደ ፓለቲካዊ እስር አስመልክቶ እና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን ) የተሰጠውን መግለጫ የኔቲዩቦች ቦታው ላይ ተገኝተን መግለጫውን ተከታትለናል እንዲሁም በካሜራችን ያስቀረነውን ቪዲዮ በዩቲዩብ ቻናላችን ከደቂቃዎች በኃላ እንለቅላችዋለን።

@Yenetube @Fikerassefa
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የእነ አቶ በረከት ስምዖንን የመከላከያ ምስክሮች ሳይሰማ ቀረ።

ችሎቱ ዛሬ የአቶ በረከት ሰምዖን እና የአቶ ታደሰ ካሳን የመከላከያ ምስክሮች ለመስማት የተሰየመ ቢሆንም 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች የሰነድና የሰው ምስክሮች ባለመቅረባቸው ለሌላ ጊዜ እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የእነ አቶ በረከት ጠበቃ “በተለይ አስፈላጊ የሆኑ የመከላከያ ሰነዶች ለዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ መድረስ ስላልቻሉ ከቀጣዩ ቀጠሮ ቀን በፊት እንድናቀርብ ይፈቀድልን” ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። አቃቤ ህግ «የተሰጠው ምክንያት ተቀባይነት የለውም» በማለት ቅሬታ ቢያቀርብም ሆኖም ግን በአጭር ጊዜ ሰነዶቹን
የሚያቀርቡ ከሆነ እንደማይቀወም ተናግሯል። የ3ኛ ተከሳሽ የአቶ ዳንኤል ግዛው ጠበቃ ባለ 150 ገፅ የሰነድ ማስረጃ እና ከ6 የሰው ምስክሮች መካከል 3ቱን አቅርበው የመከላከያ ምስክርነት ለማሰማት ቢሞክሩም አቃቤ ህግ «ምስክሮቹ በአንድ ላይ መቅረብ አለባቸው ምክንያቱም ዛሬ የተገኙና ያልተገኙ ምስክሮች ተናብበው ምስክርነት ስለሚሰጡና ትክክለኛ ፍትህን ሊያዛቡ ይችላሉ» በማለት ተቃውሞ ተከራክሯል።

የተከሳሹ ጠበቃ የአቃቤ ህግን ክርክር ባይቀበሉትም ፍርድ ቤቱ በአብላጫ ድምጽ የ3ኛ ተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮች በአንድ ላይ እንዲገኙ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ በመጨረሻ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ክስ የተመሰረተባቸው አቶ በረከት ስምዖን፣ አቶ ታደሰ ካሳና አቶ ዳንኤል ግዛው አለን የሚሏቸው የሰነድና የሰው የመከላከያ ምስክሮችን ከታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. በፊት አንዲያስመዘግቡ አዟል። ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን የመከላከያ ምስክሮች ለማድመጥ ለታህሳስ 30 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ተዘግቧል። አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሾች የጥረት ኮርፖሬት ከፍተኛ አመራሮች ሆነው ሲሰሩ የኮርፖሬቱን ንብረት ከአለአግባብ አባክነዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት ጥር 2011 ዓ.ም. ሲሆን 3ኛው ከሁለቱ ተከሳሾች ጋር በመመሳጠር በተቋሙ ሙስና ሰርተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ናቸው።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
አዲሱ የደህንነት ቀበቶ መመሪያ ከጥቅምት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል።

አዲሱ የደህንነት ቀበቶ መመሪያ ከጥቅምት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአሽከርካሪውና ለሁሉም ተሳፋሪዎች የፀና እንደሚሆን ተገለጸ።መመሪያው በመንግስትና በግል ለሰራተኞች የሰርቪስ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች፣ እስከ 150 ኪሎ ሜትር በሚጓዙ ሚኒባሶች እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ ከ5 እስከ 8 መቀመጫ ያላቸው ተሽከርካሪዎች፣ ረጅም ርቀት የሚጓዙ ልዩ ባሶችና ሀገር አቋራጭ አውቶብሶች ላይ ተግባራዊ ይሆናል።ከዚህ ባለፈም የጭነት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች፣ ከ12 እስከ 15 ሰው የሚጭኑና በከተማ ውስጥ አገልግሎት የሚሰጡ፣ የብዙሃን አገልግሎት የሚሰጡ የከተማ አውቶብሶች ለአሽከርካሪውና ፊት ወንበር ላይ ለሚቀመጡ ተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ መጠቀም ይኖርባቸዋል።

በተጨማሪም ለግል አገልግሎት የሚጠቀሙ አውቶሞቢሎች የህፃናት ደህንነት መጠበቂያ ቦርድ ያለው ማካተት ይኖርባቸዋል ነው የተባለው። በአስመጪዎች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ አዲስ የመንግስት፣ የግል፣ የህዝብና የጭነት ተሽከርካሪዎች በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሚወጣው መስፈርት መሰረት ለአሽከርካሪውና ለተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ የተገጠመላቸው መሆን አለበት።በብዙሃን ትራንስፖርት ቆመው የሚጓዙ እና አጭር ርቀት የሚጓዙ ቀበቶ እንዲያስሩ የሚያስገድደው ህግ አሁን በአዲሱ መመሪያ አስገዳጅነት እንደማይኖረው ተገልጿል።እንዲሁም በባለሁለትና በባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች፣ በግዳጅ ስራ ላይ በተሰማሩ የፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት ተሽከርካሪዎች ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም።

-መረጃው የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት ነው
@YeneTube @FikerAssefa
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግንባር(ኦብነግ) በሕወሓት ጠሪነት “ሕገ መንግሥትና ህብረ ብሄራዊ ፌዴራላዊ ሥርዓትን ማዳን" በሚል ርዕስ በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ያለው ጉባኤ ላይ እንደማይሳተፍ ለጠሪው አካል እንዳሳወቀ ጠቅሶ በማኀበራ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው ደብዳቤ ግን የሐሰት ዜና መሆኑን በትዊተር ገጹ አሳውቋል፡፡

Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa