በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማስቆም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፍትህ እና የህግ ቋሚ ኮሚቴ ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
የሰብዓዊ መብት ኮምሽን በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በተመለከተ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ በተለያየ ጊዜያት ሪፖርት እና መግለጫዎችን ያወጣል፡፡
መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰት በዜጎች ላይ ከተፈጸመ በኃላ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ከመፈጸሙ አስቀድሞ የመከላከል ስራ መስራት እንዳለበት ለአሀዱ የተናገሩት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፎረም ዋና ዳይሬክተር አቶ ተረፈ ጠጌቲ ናቸው፡፡
የሰብዓዊ መብት ኮምሽን እና ሌሎች ተቋማትን ጨምሮ በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ የሚያወጡትን ሪፖርት ወስዶ ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ክልሎችን ጨምሮ ተቃራኒ የሆነ ምላሽ የመስጠት ሁኔታዎች ይስተዋላል ነው ያሉት፡፡
በኮምሽኑም ሆነ በመንግስት በኩል የሚወጡ የተለያዩ መግለጫዎችና ሪፖርቶች ማህበረሰቡ ላይ ግራ መጋባትን የሚፈጥር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የሰብዓዊ መብት ኮምሽን የሚያወጣው ሪፖርት በመንግስት በኩል ተግባራዊ እንዲሆን የጋራ አሰራርን ለመዘርጋት እንዲቻል የህዝብ ተወካይዎች ምክር ቤት የፍትህ እና የህግ ቋሚ ኮሚቴ መመሪያ በማዘጋጀት ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
የሰብዓዊ መብት ኮምሽን በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በተመለከተ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ በተለያየ ጊዜያት ሪፖርት እና መግለጫዎችን ያወጣል፡፡
መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰት በዜጎች ላይ ከተፈጸመ በኃላ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ከመፈጸሙ አስቀድሞ የመከላከል ስራ መስራት እንዳለበት ለአሀዱ የተናገሩት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፎረም ዋና ዳይሬክተር አቶ ተረፈ ጠጌቲ ናቸው፡፡
የሰብዓዊ መብት ኮምሽን እና ሌሎች ተቋማትን ጨምሮ በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ የሚያወጡትን ሪፖርት ወስዶ ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ክልሎችን ጨምሮ ተቃራኒ የሆነ ምላሽ የመስጠት ሁኔታዎች ይስተዋላል ነው ያሉት፡፡
በኮምሽኑም ሆነ በመንግስት በኩል የሚወጡ የተለያዩ መግለጫዎችና ሪፖርቶች ማህበረሰቡ ላይ ግራ መጋባትን የሚፈጥር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የሰብዓዊ መብት ኮምሽን የሚያወጣው ሪፖርት በመንግስት በኩል ተግባራዊ እንዲሆን የጋራ አሰራርን ለመዘርጋት እንዲቻል የህዝብ ተወካይዎች ምክር ቤት የፍትህ እና የህግ ቋሚ ኮሚቴ መመሪያ በማዘጋጀት ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ በነጩ ቤተመንግስት መገኘቱ አነጋጋሪ ሆነ!
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መኖሪያ በሆነው ነጩ ቤተመንግስት ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ መገኘቱ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
ዌስት ዊንግ በተባለው የቤተ መንግስቱ ክፍል የፕሬዝዳንቱ የሚስጥር ጥበቃዎች የተለመደ የፍተሻ ስራ ሲያከናውኑ የጎብኝዎች ስልክ ማስቀመጫ ቦታ ላይ ዕፁን ማግኘታቸው ተመላክቷል፡፡
ዕፁ በተገኘበት ወቅት ፕሬዝዳንት ባይን እና ቤተሰባቸው ሜሪላንድ በሚገኘው የፕሬዝዳንቶች ማረፊያ በሆነው ካምፕ ዴቪድ እንደነበሩም ተገልጿል፡፡
የዕፁ መገኘትን ተከትሎ ሰራተኞች ለአጭር ጊዜ ከቤተመንግስት እንዲወጡ ተደርጎ እንደነበርና በተገኘው ነጭ ዱቄት ላይ በተደረገው ምርመራ ኮኬይን ሆኖ መገኘቱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የፕሬዝዳንቱ የሚስጥር ጥበቃ አገልግሎት ዕፁ ቤተመንግስት እንዴት ሊገባ እንደቻለ የደህንነት ካሜራ እና የጎብኝዎችን መመዝገቢያ ማህደር በመጠቀም ምርመራ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ኮኬይን በአሜሪካን አገር የተከለከለ አደገኛ ዕፅ ሲሆን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁጥጥር ለህክምና አገልግሎት ካልሆነ በስተቀር ዕፁን ይዞ መገኘት በከባድ ወንጀልነት ያስቀጣል፡፡
ዌስት ዊንግ ትልቅ የቤተመንግስቱ ክፍል ሲሆን የፕሬዝዳንት ቢሮዎች፣ ኦቫል ኦፊስ፣ የስችዌሽን ክፍል፣ የምክትል ፕሬዝዳንት፣ የዋይት ሀውስ የሰራተኞች ኃላፊ፣ የፕሬስ ሴክሬታሪ እና የሌሎች ሰራተኞችን ክፍል የያዘ እንደሆነም መረጃው አመላክቷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መኖሪያ በሆነው ነጩ ቤተመንግስት ኮኬይን የተባለ አደገኛ ዕፅ መገኘቱ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
ዌስት ዊንግ በተባለው የቤተ መንግስቱ ክፍል የፕሬዝዳንቱ የሚስጥር ጥበቃዎች የተለመደ የፍተሻ ስራ ሲያከናውኑ የጎብኝዎች ስልክ ማስቀመጫ ቦታ ላይ ዕፁን ማግኘታቸው ተመላክቷል፡፡
ዕፁ በተገኘበት ወቅት ፕሬዝዳንት ባይን እና ቤተሰባቸው ሜሪላንድ በሚገኘው የፕሬዝዳንቶች ማረፊያ በሆነው ካምፕ ዴቪድ እንደነበሩም ተገልጿል፡፡
የዕፁ መገኘትን ተከትሎ ሰራተኞች ለአጭር ጊዜ ከቤተመንግስት እንዲወጡ ተደርጎ እንደነበርና በተገኘው ነጭ ዱቄት ላይ በተደረገው ምርመራ ኮኬይን ሆኖ መገኘቱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የፕሬዝዳንቱ የሚስጥር ጥበቃ አገልግሎት ዕፁ ቤተመንግስት እንዴት ሊገባ እንደቻለ የደህንነት ካሜራ እና የጎብኝዎችን መመዝገቢያ ማህደር በመጠቀም ምርመራ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ኮኬይን በአሜሪካን አገር የተከለከለ አደገኛ ዕፅ ሲሆን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ቁጥጥር ለህክምና አገልግሎት ካልሆነ በስተቀር ዕፁን ይዞ መገኘት በከባድ ወንጀልነት ያስቀጣል፡፡
ዌስት ዊንግ ትልቅ የቤተመንግስቱ ክፍል ሲሆን የፕሬዝዳንት ቢሮዎች፣ ኦቫል ኦፊስ፣ የስችዌሽን ክፍል፣ የምክትል ፕሬዝዳንት፣ የዋይት ሀውስ የሰራተኞች ኃላፊ፣ የፕሬስ ሴክሬታሪ እና የሌሎች ሰራተኞችን ክፍል የያዘ እንደሆነም መረጃው አመላክቷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
❤1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነገ ፓርላማ ቀርበው ማብራሪያ ይሰጣሉ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በነገው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ አዲስ ማለዳ ከምክር ቤቱ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ሰኔ 29/2015 ያካሂዳል፡፡
ምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2016 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን ያጸድቃል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በነገው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ አዲስ ማለዳ ከምክር ቤቱ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ሰኔ 29/2015 ያካሂዳል፡፡
ምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2016 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን ያጸድቃል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በቤኒሻንጉል ክልል የኢቦላ ቫይረስ እንዳይከሰት ስጋት መኖሩ ተነገረ!
በደቡብ ሱዳን እና በሱዳን የኢቦላ ቫይረስ ተጠርጣሪዎች መገኘት እና ሞት መመዝገቡን ተከትሎ ወደ ኢትዮጵያ ይገባል የሚል ስጋት እንዳለ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቃል።
በተለይ በሱዳን የተፈጠረውን የእርስ በእርስ ግጭት ተከትሎ የተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ ክልሉ በአጎራባች ወረዳዎች በኩል በከፈተኛ ሁኔታ ከመግባታቸው ጋር ተያይዞ በሽታው ሊገባ እንደሚችል ተገልጿል።
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ጤና ቢሮ የህብተሰብ ጤና ጣቢዎች ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ተወካይ አቶ ፍቃዱ አየለ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በሱዳን ዳባላይ በምትባል ስፍራ ከ150 በላይ በበሽታው የተጠረጠሩ ሰዎች እንዳሉ የተነገረ ሲሆን እሱን ለማጣራት ከዓለም የጤና ድርጅት እና ከሌሎች አካላት አካላት ጋር በመሆን ጥናት እየተደረገ ይገኛል።
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ሱዳን እና በሱዳን የኢቦላ ቫይረስ ተጠርጣሪዎች መገኘት እና ሞት መመዝገቡን ተከትሎ ወደ ኢትዮጵያ ይገባል የሚል ስጋት እንዳለ የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቃል።
በተለይ በሱዳን የተፈጠረውን የእርስ በእርስ ግጭት ተከትሎ የተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ ክልሉ በአጎራባች ወረዳዎች በኩል በከፈተኛ ሁኔታ ከመግባታቸው ጋር ተያይዞ በሽታው ሊገባ እንደሚችል ተገልጿል።
የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ጤና ቢሮ የህብተሰብ ጤና ጣቢዎች ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ተወካይ አቶ ፍቃዱ አየለ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በሱዳን ዳባላይ በምትባል ስፍራ ከ150 በላይ በበሽታው የተጠረጠሩ ሰዎች እንዳሉ የተነገረ ሲሆን እሱን ለማጣራት ከዓለም የጤና ድርጅት እና ከሌሎች አካላት አካላት ጋር በመሆን ጥናት እየተደረገ ይገኛል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
‹ ኢቢሲ የመንግስት አፍ መሆን የለበትም › - ዐብይ አህመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ‹ ብሔራዊው የቴሌቪዥን ጣቢያ (ኢቢሲ) የመንግስት አፍ መሆን የለበትም › ሲሉ ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም የቴሌቪዥን ጣቢያው አንድ ዓመት ከስድስት ወር ገደማ በወሰደ ጊዜ ያጠናቀቀውን ‹ የስቱዲዮ ግንባታ › መርቀው በከፈቱበት ወቅት ነው፡፡
ዐብይ ስለ ብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲናገሩ ‹ ከሰፈር ሹኩቻ የወጣ ሚዲያ፣ ለመንግስት ብቻ የሚያገለግል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን የሚያገለግል ሚዲያ እንደምታደርጉት ተስፋ ይደረጋል › ሲሉ ለተቋሙ ሰራተኞች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ይህ አንድ ዓመት ከመንፈቅ የወሰደ ግንባታ ‹ ድንቅ ስራ ነው › ያሞካሹት ዐብይ ከተቋሙ መንግስታቸው የሚጠብቀውን አብራርተዋል፡፡
‹ኢቢሲ ድምፅ ማጉያ አይደለም› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹የሚነገርን ድምፅ የሚያጎላ ሳይሆን ድምፅ የሚፈጥር መሆን አለበት› ሲሉም ተናግረዋል፡፡‹መንግስት ሲያበላሽ ቆንጠጥ አድርጎ የሚጠይቅ፣ የመንግስት አፍ ያልሆነ የኢትዮጵያን ልዕልና ከፍ የሚያደርግ መሆን አለበት› ሲሉም አሳስበዋል፡፡
‹የኢቢሲ ግንባታ የተቋማት ግንባታ መሳያ ነው› ሲሉ ያደነቁት ዐብይ ለክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ለካቢኔ አባላቶቻቸውም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመንግስት አመራሮች ባስተላለፉት መልዕክትም - የሚመሩትን ተቋማት እንደ ኢቢሲ እንዲያስውቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ለዚህም ምክንያታቸው ‹ ኢትዮጵያ በተቋማቷ ስለምትለካ ነው › ብለዋል፡፡ ተቋማቱ ካልተዋቡ ግን ‹ እነርሱን አይተው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን › እንደሚንቁ ተናግረዋል፡፡
✍Asham
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ‹ ብሔራዊው የቴሌቪዥን ጣቢያ (ኢቢሲ) የመንግስት አፍ መሆን የለበትም › ሲሉ ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም የቴሌቪዥን ጣቢያው አንድ ዓመት ከስድስት ወር ገደማ በወሰደ ጊዜ ያጠናቀቀውን ‹ የስቱዲዮ ግንባታ › መርቀው በከፈቱበት ወቅት ነው፡፡
ዐብይ ስለ ብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲናገሩ ‹ ከሰፈር ሹኩቻ የወጣ ሚዲያ፣ ለመንግስት ብቻ የሚያገለግል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን የሚያገለግል ሚዲያ እንደምታደርጉት ተስፋ ይደረጋል › ሲሉ ለተቋሙ ሰራተኞች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ይህ አንድ ዓመት ከመንፈቅ የወሰደ ግንባታ ‹ ድንቅ ስራ ነው › ያሞካሹት ዐብይ ከተቋሙ መንግስታቸው የሚጠብቀውን አብራርተዋል፡፡
‹ኢቢሲ ድምፅ ማጉያ አይደለም› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹የሚነገርን ድምፅ የሚያጎላ ሳይሆን ድምፅ የሚፈጥር መሆን አለበት› ሲሉም ተናግረዋል፡፡‹መንግስት ሲያበላሽ ቆንጠጥ አድርጎ የሚጠይቅ፣ የመንግስት አፍ ያልሆነ የኢትዮጵያን ልዕልና ከፍ የሚያደርግ መሆን አለበት› ሲሉም አሳስበዋል፡፡
‹የኢቢሲ ግንባታ የተቋማት ግንባታ መሳያ ነው› ሲሉ ያደነቁት ዐብይ ለክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ለካቢኔ አባላቶቻቸውም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመንግስት አመራሮች ባስተላለፉት መልዕክትም - የሚመሩትን ተቋማት እንደ ኢቢሲ እንዲያስውቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ለዚህም ምክንያታቸው ‹ ኢትዮጵያ በተቋማቷ ስለምትለካ ነው › ብለዋል፡፡ ተቋማቱ ካልተዋቡ ግን ‹ እነርሱን አይተው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን › እንደሚንቁ ተናግረዋል፡፡
✍Asham
@YeneTube @FikerAssefa
አባቱን እና ወንድሙን በቁማቸዉ በእሳት አቃጥሎ የገደለዉ ተጠርጣሪ ተያዘ!
"ቤተሰቦቼ ለእኔ ምንም ቦታ የላቸውም " በሚል ምክንያት ወላጅ አባቱንና ታላቅ ወንድሙን ቤንዚል በመርጨት በቁማቸዉ ያቃጠለዉ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዉሏል።
ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ክብረ ደመና ሙሉ ወንጌል አካባቢ ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
ተከሳሹ ግለሰብ ከዚህ ቀደም በሌላ ወንጀል ተከሶ ታስሮ የነበረና በፍርድ ቤት ዋስትና የተለቀቀ ሲሆን " ከእናቴ በስተቀር ለእኔ የሚያስብልኝ የለም " በሚል ምክንያት ከሳምንት በፊት በአንድ ሺህ ስድስት መቶ ብር ቤንዚል በመግዛት አባቱና ታላቅ ወንድሙ የግል ጉዳያቸውን ፈፅመው በመምጣት ቤት ውስጥ ቁጭ ባሉበት እናትዬውን ውሃ አምጭልኝ ብሎ ከቤት መውጣታቸውን ጠብቆ ቤንዚሉን አርከፍክፎባቸው ክብሪት በመለኮስ ማምለጥ እንዳይችሉ በሩን ቆልፎ ለማምለጥ ሲል በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ተጎጂዎችን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ወደ ህክምና ቢወስዱም አባትዬው ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ታላቅ ወንድሙ በህክምና ላይ ይገኛል።በተከሳሹ ላይ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
"ቤተሰቦቼ ለእኔ ምንም ቦታ የላቸውም " በሚል ምክንያት ወላጅ አባቱንና ታላቅ ወንድሙን ቤንዚል በመርጨት በቁማቸዉ ያቃጠለዉ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዉሏል።
ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ክብረ ደመና ሙሉ ወንጌል አካባቢ ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
ተከሳሹ ግለሰብ ከዚህ ቀደም በሌላ ወንጀል ተከሶ ታስሮ የነበረና በፍርድ ቤት ዋስትና የተለቀቀ ሲሆን " ከእናቴ በስተቀር ለእኔ የሚያስብልኝ የለም " በሚል ምክንያት ከሳምንት በፊት በአንድ ሺህ ስድስት መቶ ብር ቤንዚል በመግዛት አባቱና ታላቅ ወንድሙ የግል ጉዳያቸውን ፈፅመው በመምጣት ቤት ውስጥ ቁጭ ባሉበት እናትዬውን ውሃ አምጭልኝ ብሎ ከቤት መውጣታቸውን ጠብቆ ቤንዚሉን አርከፍክፎባቸው ክብሪት በመለኮስ ማምለጥ እንዳይችሉ በሩን ቆልፎ ለማምለጥ ሲል በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ተጎጂዎችን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ወደ ህክምና ቢወስዱም አባትዬው ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ታላቅ ወንድሙ በህክምና ላይ ይገኛል።በተከሳሹ ላይ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል ረሃብ 'በከፍተኛ መጠን' መጨመሩን ተመድ አስታወቀ!
በጦርነት በተጎዳው የትግራይ ክልል ለከፋ የምግብ እጥረት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን እና፣ በቅርቡ የምግብ ርዳታ መቆሙን ተከትሎ፣ ሁኔታዎች እየተባባሱ ሊሄዱ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ድጋፍ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) ፤ሰኞ ዕለት ይፋ ባደረገው ወቅታዊ ሪፖርት፣ በደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ በድርቅ ምክንያት ጉዳት ከደረሰባቸው በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች በተጨማሪ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚኖሩ 8.8 ሚሊየን ሰዎች የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አስታውቋል።
በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ለሁለት ዓመት የተካሄደውን ጦርነት ያስቆመው የሰላም ስምምነት በኅዳር ወር ከተፈረመ ወዲህ ወደ ክልሉ የሚገባው የርዳታ መጠን ቀስ በቀስ እንዲጨምር አስችሎ የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ ምግብ እጥረት ምክንያት ለውስብስብ የጤና ችግር የተጋለጡ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨምረ መሆኑን ክልሉ ይፋ አድርጓል።
"ባለፈው ዓመት በሚያዚያ ወር ከነበረው ሁኔታ ጋር ሲነፃፀር፣ በትግራይ፣ በከፍተኛ በሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች ቁጥር በ196 ከመቶ ጨምሯል" ያለው የኦቻ ሪፖርት፣ የአሃዙ መጨመር "በከፊል የተሻለ የጤና ተቋማት ተደራሽነት እና የመረጃ አሰባሰብ" በመኖሩ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክቷል።
"ለትግራይ ክልል ይሰጥ የነበረው የምግብ እርዳታ ለተረጂዎቹ እንደማይደርስ ገልፀው ድጋፍ ሰጪ ተቋማት እርዳታ ማቋረጣቸውን ተከትሎ፣ በትግራይ ለችግር ተጋላጭ በሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የምግብ ዋስትና እጦት እየተባባሰ ሄዷል" ብሏል ኦቻ በሪፖርቱ።
በተመሳሳይ ሁኔታ ባለፈው ዓመት ከጥር እስከ ሚያዚያ ወር ከነበረው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነፃፀር፣ በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ የምግብ እጥረት ምክንያት ወደ ህክምና ተቋማት የሚገቡ ሰዎች ቁጥርም በ15 ከመቶ መጨመሩን ኦቻ በሪፖርቱ አስታውቋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በጦርነት በተጎዳው የትግራይ ክልል ለከፋ የምግብ እጥረት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን እና፣ በቅርቡ የምግብ ርዳታ መቆሙን ተከትሎ፣ ሁኔታዎች እየተባባሱ ሊሄዱ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ድጋፍ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) ፤ሰኞ ዕለት ይፋ ባደረገው ወቅታዊ ሪፖርት፣ በደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ በድርቅ ምክንያት ጉዳት ከደረሰባቸው በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች በተጨማሪ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚኖሩ 8.8 ሚሊየን ሰዎች የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አስታውቋል።
በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ለሁለት ዓመት የተካሄደውን ጦርነት ያስቆመው የሰላም ስምምነት በኅዳር ወር ከተፈረመ ወዲህ ወደ ክልሉ የሚገባው የርዳታ መጠን ቀስ በቀስ እንዲጨምር አስችሎ የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ ምግብ እጥረት ምክንያት ለውስብስብ የጤና ችግር የተጋለጡ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨምረ መሆኑን ክልሉ ይፋ አድርጓል።
"ባለፈው ዓመት በሚያዚያ ወር ከነበረው ሁኔታ ጋር ሲነፃፀር፣ በትግራይ፣ በከፍተኛ በሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ወደ ሆስፒታል የሚመጡ ሰዎች ቁጥር በ196 ከመቶ ጨምሯል" ያለው የኦቻ ሪፖርት፣ የአሃዙ መጨመር "በከፊል የተሻለ የጤና ተቋማት ተደራሽነት እና የመረጃ አሰባሰብ" በመኖሩ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክቷል።
"ለትግራይ ክልል ይሰጥ የነበረው የምግብ እርዳታ ለተረጂዎቹ እንደማይደርስ ገልፀው ድጋፍ ሰጪ ተቋማት እርዳታ ማቋረጣቸውን ተከትሎ፣ በትግራይ ለችግር ተጋላጭ በሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የምግብ ዋስትና እጦት እየተባባሰ ሄዷል" ብሏል ኦቻ በሪፖርቱ።
በተመሳሳይ ሁኔታ ባለፈው ዓመት ከጥር እስከ ሚያዚያ ወር ከነበረው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነፃፀር፣ በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ የምግብ እጥረት ምክንያት ወደ ህክምና ተቋማት የሚገቡ ሰዎች ቁጥርም በ15 ከመቶ መጨመሩን ኦቻ በሪፖርቱ አስታውቋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
ምርጫ ቦርድ፤ የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔን በድጋሚ ለመሰረዝ የሚያስገድዱ ችግሮች አጋጥመውት እንደነበር የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ተናገሩ!
ድጋሚ በተደረገው የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ ላይ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሂደቱን በድጋሚ “እንዲሰረዝ” የሚያስገድዱ ተግባራት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሲፈጸሙ እንደነበር የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ተናገሩ። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በህዝበ ውሳኔው ዕለት፤ ምርጫ ቦርድ “ሌላ ውሳኔ እንደሰጠ” አድርገው መልዕክት ሲያስተላልፉ እንደነበርም አቶ ውብሸት ገልጸዋል።
የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ይህንን ያሉት፤ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 28፤ 2015 በተካሄደ የፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ ነው። አቶ ውብሸት በንባብ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ ሪፖርት፤ ምርጫ ቦርድ ህዝበ ውሳኔውን ለማካሄድ ያለፋቸውን ሂደቶች፣ የተገኘውን ውጤት እንዲሁም ያጋጠሙትን ችግሮች ዘርዝረዋል።
በ26 ገጾች በተዘጋጀው በዚሁ ሪፖርት ውስጥ በችግርነት ከተጠቀሱ ጉዳዮች ውስጥ፤ በወላይታ ዞን ተከስተው ነበር የተባሉ የህግ ጥሰቶች ይገኙበታል። በወላይታ ዞን ባለፈው ጥር ወር የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ እንዲሰረዝ ምክንያት የሆኑ የህግ ጥሰቶችን አጽንኦት ሰጥተው ያነሱት ምክትል ሰብሳቢው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 94 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12፤ 2015 በወላይታ ዞን በድጋሚ ህዝበ ውሳኔ ሲያካሄድም ችግሮች እንዳጋጠሙት አቶ ውብሸት በዛሬው ሪፖርታቸው ጠቁመዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
ድጋሚ በተደረገው የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ ላይ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሂደቱን በድጋሚ “እንዲሰረዝ” የሚያስገድዱ ተግባራት በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሲፈጸሙ እንደነበር የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ተናገሩ። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በህዝበ ውሳኔው ዕለት፤ ምርጫ ቦርድ “ሌላ ውሳኔ እንደሰጠ” አድርገው መልዕክት ሲያስተላልፉ እንደነበርም አቶ ውብሸት ገልጸዋል።
የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ይህንን ያሉት፤ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 28፤ 2015 በተካሄደ የፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ ነው። አቶ ውብሸት በንባብ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህዝበ ውሳኔ አጠቃላይ ሪፖርት፤ ምርጫ ቦርድ ህዝበ ውሳኔውን ለማካሄድ ያለፋቸውን ሂደቶች፣ የተገኘውን ውጤት እንዲሁም ያጋጠሙትን ችግሮች ዘርዝረዋል።
በ26 ገጾች በተዘጋጀው በዚሁ ሪፖርት ውስጥ በችግርነት ከተጠቀሱ ጉዳዮች ውስጥ፤ በወላይታ ዞን ተከስተው ነበር የተባሉ የህግ ጥሰቶች ይገኙበታል። በወላይታ ዞን ባለፈው ጥር ወር የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ እንዲሰረዝ ምክንያት የሆኑ የህግ ጥሰቶችን አጽንኦት ሰጥተው ያነሱት ምክትል ሰብሳቢው፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 94 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12፤ 2015 በወላይታ ዞን በድጋሚ ህዝበ ውሳኔ ሲያካሄድም ችግሮች እንዳጋጠሙት አቶ ውብሸት በዛሬው ሪፖርታቸው ጠቁመዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
🔥🔥አስቸኳይ ክፍት የስራ ቅጥር💥💥
🔴በሁሉም ስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት እንፈልጋለን።
🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።
💥ጉዳይ አስፈፃሚ/smart phone ያለው/
🔹የት/ደረጃ:10
🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ:5000+ የቀን አበል
💥ካሸር አሰልጥኖ
🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500
💥ባርማን/ባሬስታ
🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት
💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች
🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ፡ 4,500
💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000
▶ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006
👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
🔴በሁሉም ስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት እንፈልጋለን።
🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።
💥ጉዳይ አስፈፃሚ/smart phone ያለው/
🔹የት/ደረጃ:10
🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ:5000+ የቀን አበል
💥ካሸር አሰልጥኖ
🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500
💥ባርማን/ባሬስታ
🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት
💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች
🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ፡ 4,500
💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000
▶ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006
👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛውን፣ 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 28ኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡
ምክር ቤቱ በስብሰባው የ27ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡
የምክር ቤት አባላትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌደራል መንግስት የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛውን፣ 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 28ኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡
ምክር ቤቱ በስብሰባው የ27ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡
የምክር ቤት አባላትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌደራል መንግስት የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
የተከበሩ አቶ መሀመድ አህመድ " ህወሓት አሁንም ዉድቀቱ ያልተማረ መሆኑ እና ዛሬም የትግራይ ክልልን እና መላዉ ኢትዮጵያን መልሶ ጦርነት ዉስጥ ለመክተት እየተንቀሳቀሰ እንዳለ አሁንም ይነሳል።
ወቅታዊ የትግራይ ክልል ሁኔታ ማብራሪያ ይሰጥበት?" ለጠቅላይ ሚኒስትር አህመድ የቀረበ ጥያቄ።
@Yenetube @Fikerassefa
ወቅታዊ የትግራይ ክልል ሁኔታ ማብራሪያ ይሰጥበት?" ለጠቅላይ ሚኒስትር አህመድ የቀረበ ጥያቄ።
@Yenetube @Fikerassefa
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ የአብን እና የምክርቤቱ አባል ለጠ/ሚኒስትሩ ያቀረቡት ጥያቄ -
ጠ/ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ኢኮኖሚዉ ታሟል፣ ወጣቶች ሀገራቸዉ ዉስጥ ተስፋ በማጣታቸው ስደትን ምርጫቸዉ አድርገዋል ፣ ዜጎች በጠራራ ፀሀይ ይታገታሉ ፣ ብልጽግና መራሹ ፓርቲ ሀገሪቱ ከገባችበት ቅርቃር ማዉጣት ስለማይችሉ ስልጣኖን ለጊዜያዊ አስተዳደር እንዲያስረክቡ ሲሉ ጠይቀዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
ጠ/ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ኢኮኖሚዉ ታሟል፣ ወጣቶች ሀገራቸዉ ዉስጥ ተስፋ በማጣታቸው ስደትን ምርጫቸዉ አድርገዋል ፣ ዜጎች በጠራራ ፀሀይ ይታገታሉ ፣ ብልጽግና መራሹ ፓርቲ ሀገሪቱ ከገባችበት ቅርቃር ማዉጣት ስለማይችሉ ስልጣኖን ለጊዜያዊ አስተዳደር እንዲያስረክቡ ሲሉ ጠይቀዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
"ሙሉ አማራ ክልል አዲስ የጦርነት ቀጠና ሆኗል ፤ ከፊል ኦሮሚያ በተመሳሳይ የጦር ቀጠና ናቸዉ። ከ 200 ሺህ በላይ ሰዎች በመንግስት ቤታቸዉ ፈርሶ ሜዳ ላይ ወድቀዋል። እንደ ብልጽግና ሹማምንት አባባል ህጋዊ ደሃ ተደርገዋል። በሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በጦርነቱ እና በማንነት ጥቃት ተፈናቅለዋል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ለዚህ ሁሉ ቀዉስ ዋነኛ ተጠያቂው የብልጽግና መንግስት እና የእርሶ(የጠ/ሚኒስተሩ ) የወደቀ አመራር ነዉ።" የተከበሩ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለ ጠ/ሚ አብይ ካነሷቸዉ ጉዳዮች መካከል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
‹ኢትዮጵያ የደም ምድር ሆናለች - ፓርላማው ይበተን - አዲስ ምርጫ ይደረግ› - ደሳለኝ ጫኔ
የህዘብ እንደራሴዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን በማከሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የተገኙ ሲሆን ከአባላቱ በኩል በርከት ያሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡ ከእረሱም መካከል የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) አባሉ ደሳለኝ ጫኔ የጠየቋቸው ጥያቀዌች ይገኙበታል፡፡
ሰፊ ጊዜ ወስደው የዐብይን መንግስት የተቹት ደሳለኝ ‹ የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግስት የወደቀ › ሲሉ በይነውታል፡፡
ደሳለኝ በማብራሪያቸው ‹ ጠቅላይ ሚኒስትር ወደ ስልጣን ከወጡበት መጋቢት 2010 ዓመት ጀምሮ እየተወሳሰቡ የመጡት የሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ወደሁለንታዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን መሸፋፈን በማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል › ብለዋል፡፡
‹ ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት፣ ነጋዴው ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ፣ ሰርቶና ነግዶ የሚኖርበት፣ ገበሬው አርሶ የሚበላበትና ከተሜውን የሚቀልብበትን ሁኔታ መፍጠር አልቻለም › ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
‹ የኢትዮጵያ ህዝብ በችጋር እየተጠበሰ፣ በረሃብ እየተሰቃየ ነው › ሲሉም ተናግረዋል፡፡
‹ የኑሮ ውድነቱ በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ወገናችን ከእጅ ወደአፍ የሆነውን ኑሮ እንኳ መግፋት ወደማይችልበት ደረጃ ደርሷል፤ ኢኮኖሚው ታምሟል፤ መካከለኛ ነዋሪ የነበረውም ተመትቶ ወደ ድህነት ወለል ወርዷል › ሲሉ አብራርተዋል፡፡
‹ ስራ አጥነት ተስፋፍቷል፤ ወጣቶች ስደትን ምርጫ አድርጓል፤ ዜጎች በጠራራ ፀሃይ ይታገታሉ፤ ሚሊዮን ብር ይጠይቅባቸዋል የመንግስት የፀጥታ መዋቅር በተለይም ፖሊስ አማራ ዎችንና የአማራ ሊህቃንን የአማራን ህዝብ ጥያቄዎችን በመንሳታቸው መንግስትን በተለያየ መንገድ በመጠየቃቸው ብቻ የፈጠራ ወንጀል እየተሰጣቸው በማንነታቸው በጅምላ ይታሰራሉ፣ በጅምላ ይከሰሳሉ፤ ፍርድ ቤትም ነፃ ሲላቸው ፖሊስ ግለሰቦችን አስሮ ያቆያል › ሲሉ የፍትሕ ስርዓቱን ኮንነዋል፡፡
‹ የኢትዮጵያ መልዓካ ፖለቲካ በሙሉ ያደረሰ በሚባል ደረጃ ሀገራችን ሁሉም አካባቢዎች የደም ምድር ሆኗል፤ ሙሉ አማራ ክልል አዲስ የጦርነት ቀጣና ተደርጓል፤ ከፊል የኦሮሚያ ክልል ሆኖ ባጅቷል፤ ትግራይ፣ አማራና አፋር ፋይዳ ባልነበረው የብልፅግናና ህወሓት የስልጣን ጦርነት ምክንያት ደቅቋል፡፡ ቤኒሻንጉል ጋምቤላ… የተለዩ አይደሉም › ሲሉ የሀገሪቱን ሁኔታን የተረዱበትን መንገድ አስረድተዋል፡፡
‹ ከሁለት መቶሺህ በላይ ሰዎች ቤት አልባ ሆነዋል፤ በብፅልግና ሹማምንት አገላለፅ ህጋዊ ደሃ ተደርገዋል › ሲሉም ተደምጠዋል፡፡
‹ ለዚህ ቀውስና ሀገራዊ ሀገራዊ መክሸፍ ዋነኛ ተጠያቂ የብልፅግና መንግስት እና የእርስዎ የወደቀ አመራር ነው › ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የወነጀሉት ደሳለኝ ‹ መንግስትዎ ብልፅግናን አመጣለሁ ቢልም ያመጣው ግን ጉስቁልና ነው › ሲሉ ገልጸውታል፡፡
‹ ለወደቀው የእርስዎና የበልፅግና አመራር መፍሔው ምንድን ነው › ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ የእርሳቸውን መፍትሔን ግን ካማመላከትአላመነቱም፡፡
‹ እንደ አንድ ህዝብ ተወካይ ብልፅግናም ሆነ ፓርላማው ኢትዮጵያ ከገባችበት ፖለቲካ ቅርቃር ማውጣት ስለማይችሉ ስልጣኑን ለጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረከቡ፣ የሕዝብ እንደራሰዌች ምክር ቤት አባላትም በምክር ቤቱ ፍቃድ ምክር ቤቱን እንዲበተኑ ለአዲስ ምርጫ መንገዱን እንዲጠርጉ መጠየቅ እፍለጋለሁ፡፡ › ብለዋል፡፡
ደሳለኝ ይህን ጥያቄ ባቀረቡበት ወቅት የምክር ቤቱ አበላት ሲስቁ ተስተውሏል፡፡ ከዚህ ወደም በተመሳሳይ መልኩ የአብን የምክር ቤት አባል ክርስቲያን ታደለ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ‹ ስልጣን የመልቀቅ ሃሳብ እንዳላቸው › ጠይቀዋቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ በሰጡት ምላሽ ‹ ስልጣን ልቀቅ ሳይሂን አብረን እንልቀቅ ነው የሚባለው › ማለታቸው ይታወሳል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
የህዘብ እንደራሴዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን በማከሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የተገኙ ሲሆን ከአባላቱ በኩል በርከት ያሉ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡ ከእረሱም መካከል የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) አባሉ ደሳለኝ ጫኔ የጠየቋቸው ጥያቀዌች ይገኙበታል፡፡
ሰፊ ጊዜ ወስደው የዐብይን መንግስት የተቹት ደሳለኝ ‹ የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግስት የወደቀ › ሲሉ በይነውታል፡፡
ደሳለኝ በማብራሪያቸው ‹ ጠቅላይ ሚኒስትር ወደ ስልጣን ከወጡበት መጋቢት 2010 ዓመት ጀምሮ እየተወሳሰቡ የመጡት የሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ወደሁለንታዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን መሸፋፈን በማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል › ብለዋል፡፡
‹ ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት፣ ነጋዴው ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ፣ ሰርቶና ነግዶ የሚኖርበት፣ ገበሬው አርሶ የሚበላበትና ከተሜውን የሚቀልብበትን ሁኔታ መፍጠር አልቻለም › ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
‹ የኢትዮጵያ ህዝብ በችጋር እየተጠበሰ፣ በረሃብ እየተሰቃየ ነው › ሲሉም ተናግረዋል፡፡
‹ የኑሮ ውድነቱ በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ወገናችን ከእጅ ወደአፍ የሆነውን ኑሮ እንኳ መግፋት ወደማይችልበት ደረጃ ደርሷል፤ ኢኮኖሚው ታምሟል፤ መካከለኛ ነዋሪ የነበረውም ተመትቶ ወደ ድህነት ወለል ወርዷል › ሲሉ አብራርተዋል፡፡
‹ ስራ አጥነት ተስፋፍቷል፤ ወጣቶች ስደትን ምርጫ አድርጓል፤ ዜጎች በጠራራ ፀሃይ ይታገታሉ፤ ሚሊዮን ብር ይጠይቅባቸዋል የመንግስት የፀጥታ መዋቅር በተለይም ፖሊስ አማራ ዎችንና የአማራ ሊህቃንን የአማራን ህዝብ ጥያቄዎችን በመንሳታቸው መንግስትን በተለያየ መንገድ በመጠየቃቸው ብቻ የፈጠራ ወንጀል እየተሰጣቸው በማንነታቸው በጅምላ ይታሰራሉ፣ በጅምላ ይከሰሳሉ፤ ፍርድ ቤትም ነፃ ሲላቸው ፖሊስ ግለሰቦችን አስሮ ያቆያል › ሲሉ የፍትሕ ስርዓቱን ኮንነዋል፡፡
‹ የኢትዮጵያ መልዓካ ፖለቲካ በሙሉ ያደረሰ በሚባል ደረጃ ሀገራችን ሁሉም አካባቢዎች የደም ምድር ሆኗል፤ ሙሉ አማራ ክልል አዲስ የጦርነት ቀጣና ተደርጓል፤ ከፊል የኦሮሚያ ክልል ሆኖ ባጅቷል፤ ትግራይ፣ አማራና አፋር ፋይዳ ባልነበረው የብልፅግናና ህወሓት የስልጣን ጦርነት ምክንያት ደቅቋል፡፡ ቤኒሻንጉል ጋምቤላ… የተለዩ አይደሉም › ሲሉ የሀገሪቱን ሁኔታን የተረዱበትን መንገድ አስረድተዋል፡፡
‹ ከሁለት መቶሺህ በላይ ሰዎች ቤት አልባ ሆነዋል፤ በብፅልግና ሹማምንት አገላለፅ ህጋዊ ደሃ ተደርገዋል › ሲሉም ተደምጠዋል፡፡
‹ ለዚህ ቀውስና ሀገራዊ ሀገራዊ መክሸፍ ዋነኛ ተጠያቂ የብልፅግና መንግስት እና የእርስዎ የወደቀ አመራር ነው › ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የወነጀሉት ደሳለኝ ‹ መንግስትዎ ብልፅግናን አመጣለሁ ቢልም ያመጣው ግን ጉስቁልና ነው › ሲሉ ገልጸውታል፡፡
‹ ለወደቀው የእርስዎና የበልፅግና አመራር መፍሔው ምንድን ነው › ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ የእርሳቸውን መፍትሔን ግን ካማመላከትአላመነቱም፡፡
‹ እንደ አንድ ህዝብ ተወካይ ብልፅግናም ሆነ ፓርላማው ኢትዮጵያ ከገባችበት ፖለቲካ ቅርቃር ማውጣት ስለማይችሉ ስልጣኑን ለጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረከቡ፣ የሕዝብ እንደራሰዌች ምክር ቤት አባላትም በምክር ቤቱ ፍቃድ ምክር ቤቱን እንዲበተኑ ለአዲስ ምርጫ መንገዱን እንዲጠርጉ መጠየቅ እፍለጋለሁ፡፡ › ብለዋል፡፡
ደሳለኝ ይህን ጥያቄ ባቀረቡበት ወቅት የምክር ቤቱ አበላት ሲስቁ ተስተውሏል፡፡ ከዚህ ወደም በተመሳሳይ መልኩ የአብን የምክር ቤት አባል ክርስቲያን ታደለ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ‹ ስልጣን የመልቀቅ ሃሳብ እንዳላቸው › ጠይቀዋቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ በሰጡት ምላሽ ‹ ስልጣን ልቀቅ ሳይሂን አብረን እንልቀቅ ነው የሚባለው › ማለታቸው ይታወሳል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
መንግስት 2 ሚሊዮን የስራ ስምሪት ጥያቄ ከዉጭ ሀገራት እንደቀረበለት አስታወቀ!
ጠ/ሚ አብይ አህመድ የስራ እድል እና ፈጠራ ክህሎት በሚኒስቴር ደረጃ ኢትዮጵያ ውስጥ ተቋቁሞ እንደማያውቅ ለተወካዮች ምክር ቤት በሚያብራሩበት ወቅት ገልፀዋል።ከተለያዩ ዓለም ሀገራትም መንግስት 2 ሚሊየን ገደማ የሰራተኛ ስምሪት ጥያቄ ቀርቦለት እየተፈራረመ መሆኑን ጠ/ሚንስትሩ ተናግረዋል።
በዚያ ደረጃ እንዲቋቋም የተፈለገበት ደረጃ ስራ አጥነትን መቀነስ ነው ስራ አጥነትን መቀነስ ሰላም ያመጣል ብለዋል።ሰፋፉ የስራ እድል ቢፈጠር ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ይቀነሳል የሚል እምነት በመያዙ ተቋሙ በሪፎርሙ በሚኒስትር ደረጃ እንዲቋቋም መደረጉን ገልፀዋል።
ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ ካሉ የፌደራል ተቋማት አንዱ የስራ እድል እና ፈጠራ አንዱ መሆኑን አንስተዋል። በተጨማሪ የስራ ስምሪት ቁጥጥር በሀገር ውስጥ መቶ በመቶ በሚቀጥለው ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል ። ማን ስራ እንደያዘ እና የት ስራ እንደያዘ ስለሚታወቅ የውሸት ሪፖርቶችን ለማስቀረት ይረዳል ብለዋል ።
ባለፉት 11 ወራት 3.1ሚሊየን ገደማ ሰዎች ስራ መያዛቸውንም ገልፀዋል። ከነዚህም ውስጥ በግብርና 1.2ሚሊየን የሚጠጋ ሰው፣በኢንደስትሪ 600ሺ ገዳማ፣ አገልግሎት፣1.2ሚሊየን ገደማ፣ለውጭ ህጋዊ በሆነ መንገድ 100ሺ ሰው ገደማ ስራ መያዙን ጠቅሰዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ጠ/ሚ አብይ አህመድ የስራ እድል እና ፈጠራ ክህሎት በሚኒስቴር ደረጃ ኢትዮጵያ ውስጥ ተቋቁሞ እንደማያውቅ ለተወካዮች ምክር ቤት በሚያብራሩበት ወቅት ገልፀዋል።ከተለያዩ ዓለም ሀገራትም መንግስት 2 ሚሊየን ገደማ የሰራተኛ ስምሪት ጥያቄ ቀርቦለት እየተፈራረመ መሆኑን ጠ/ሚንስትሩ ተናግረዋል።
በዚያ ደረጃ እንዲቋቋም የተፈለገበት ደረጃ ስራ አጥነትን መቀነስ ነው ስራ አጥነትን መቀነስ ሰላም ያመጣል ብለዋል።ሰፋፉ የስራ እድል ቢፈጠር ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ይቀነሳል የሚል እምነት በመያዙ ተቋሙ በሪፎርሙ በሚኒስትር ደረጃ እንዲቋቋም መደረጉን ገልፀዋል።
ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ ካሉ የፌደራል ተቋማት አንዱ የስራ እድል እና ፈጠራ አንዱ መሆኑን አንስተዋል። በተጨማሪ የስራ ስምሪት ቁጥጥር በሀገር ውስጥ መቶ በመቶ በሚቀጥለው ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል ። ማን ስራ እንደያዘ እና የት ስራ እንደያዘ ስለሚታወቅ የውሸት ሪፖርቶችን ለማስቀረት ይረዳል ብለዋል ።
ባለፉት 11 ወራት 3.1ሚሊየን ገደማ ሰዎች ስራ መያዛቸውንም ገልፀዋል። ከነዚህም ውስጥ በግብርና 1.2ሚሊየን የሚጠጋ ሰው፣በኢንደስትሪ 600ሺ ገዳማ፣ አገልግሎት፣1.2ሚሊየን ገደማ፣ለውጭ ህጋዊ በሆነ መንገድ 100ሺ ሰው ገደማ ስራ መያዙን ጠቅሰዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የህዳሴ ግድብ ሙሌት እስከ መስከረም መጀመሪያ እንደማይከናወን ጠ/ሚ ዐቢይ ተናገሩ!
ኢትዮጵያ የሱዳንን እና ግብፅ ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የህዳሴ ግድብ ሙሌቱ እስከ መስከረም መጀመሪያ እንደማታከናዉን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ተናግረዋል።ከዚህ ቀደም ሀምሌ አጋማሽ የግድቡን የዉሃ ሙሌት ስናከብር ነበር ያሉት ጠ / ሚኒስትሩ ዘንድሮ ግን በቂ የዉሃ መጠን ለሁለቱ ሀገራት ከደረሰ በኋላ ሙሌቱ እንደሚከናወን መናገራቸው ተሰምቷል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሶስተኛ ዙር ሙሌት የተከናወነ ሲሆን በዘንድሮዉ ክረምት አራተኛዉ ሙሌት ለማከናወን እቅድ ተይዞ ነበር። ሆኖም ኢትዮጵያ የሁለቱ ሀገራትን ጥያቄ በማክበር ይህን እቅድ ማራዘሟን ነዉ ጠ/ሚኒስትሩ የተናገሩት።
ሱዳን እና ግብፅ በተደጋጋሚ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ አሳሪ ስምምነት እንዲፈጸም ፍላጎት እንዳላቸዉ ሲገለጽ ቆይቷል። በተለይም ግብፅ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለአረብ ሊግ፣ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ለኃያላኑ ምዕራባውያን በተደጋጋሚ ከግድቡ ጋር በተያያዘ አቤቱታዋን ስታሰማ እንደነበር ይታወቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የሱዳንን እና ግብፅ ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የህዳሴ ግድብ ሙሌቱ እስከ መስከረም መጀመሪያ እንደማታከናዉን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ተናግረዋል።ከዚህ ቀደም ሀምሌ አጋማሽ የግድቡን የዉሃ ሙሌት ስናከብር ነበር ያሉት ጠ / ሚኒስትሩ ዘንድሮ ግን በቂ የዉሃ መጠን ለሁለቱ ሀገራት ከደረሰ በኋላ ሙሌቱ እንደሚከናወን መናገራቸው ተሰምቷል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሶስተኛ ዙር ሙሌት የተከናወነ ሲሆን በዘንድሮዉ ክረምት አራተኛዉ ሙሌት ለማከናወን እቅድ ተይዞ ነበር። ሆኖም ኢትዮጵያ የሁለቱ ሀገራትን ጥያቄ በማክበር ይህን እቅድ ማራዘሟን ነዉ ጠ/ሚኒስትሩ የተናገሩት።
ሱዳን እና ግብፅ በተደጋጋሚ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ አሳሪ ስምምነት እንዲፈጸም ፍላጎት እንዳላቸዉ ሲገለጽ ቆይቷል። በተለይም ግብፅ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለአረብ ሊግ፣ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ለኃያላኑ ምዕራባውያን በተደጋጋሚ ከግድቡ ጋር በተያያዘ አቤቱታዋን ስታሰማ እንደነበር ይታወቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
‹‹በመንግስት በጀት የተሰሩ 130 ሺህ ኮንዶሚኒየሞች በዚህ ክረምት ለተጠቃሚ እናስረክባለን፡፡›› -ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
በአዲስ አበባ በመንግስት በጀት የተሰሩ 130 ሺህ ኮንዶሚኒየሞች እና 5 ሺህ ቁጠባ የኪራይ ቤቶች ተሰርተዉ ማለቃቸዉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡እነዚህን ቤቶች በዚህ ክረምት ለነዋሪዎች እናስረክባለን ነዉ ያሉት፡፡
በመንግስት የሚሰራዉ በመንግስት በጀት፣ በልመና የሚሰራዉ በልመና እንዲሁም ደግሞ በትብብር የሚሰራዉ በትብብር ይሰራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እንደዚህ ዓይነት ስራዎችን መደገፍ ካልቻልን ዝም ማለት ይሻላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከለዉጡ በፊት 3መቶ ሺህ ዳቦ ይመረት ነበር ያሉ ሲሆን አሁን ግን 4ሚሊየን ዳቦ የማምረት አቅም አለን ብለዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በቀን 2መቶ 80ሺህ እንጀራ መጋገር የሚችል ፋብሪካ ሰርተናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ቁጥሩን ብንጨምር የአዲስ አበባን 20-30 በመቶ ህዝብ እንጀራን እንደ ዳቦ በማንኛዉም ሰዓት ገዝተዉ እንዲመገቡ ማድረግ እንችላለን ሲሉ ገልጸዋል፡፡
✍Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በመንግስት በጀት የተሰሩ 130 ሺህ ኮንዶሚኒየሞች እና 5 ሺህ ቁጠባ የኪራይ ቤቶች ተሰርተዉ ማለቃቸዉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡እነዚህን ቤቶች በዚህ ክረምት ለነዋሪዎች እናስረክባለን ነዉ ያሉት፡፡
በመንግስት የሚሰራዉ በመንግስት በጀት፣ በልመና የሚሰራዉ በልመና እንዲሁም ደግሞ በትብብር የሚሰራዉ በትብብር ይሰራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እንደዚህ ዓይነት ስራዎችን መደገፍ ካልቻልን ዝም ማለት ይሻላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከለዉጡ በፊት 3መቶ ሺህ ዳቦ ይመረት ነበር ያሉ ሲሆን አሁን ግን 4ሚሊየን ዳቦ የማምረት አቅም አለን ብለዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በቀን 2መቶ 80ሺህ እንጀራ መጋገር የሚችል ፋብሪካ ሰርተናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ቁጥሩን ብንጨምር የአዲስ አበባን 20-30 በመቶ ህዝብ እንጀራን እንደ ዳቦ በማንኛዉም ሰዓት ገዝተዉ እንዲመገቡ ማድረግ እንችላለን ሲሉ ገልጸዋል፡፡
✍Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራና ትግራይ ክልሎች በይገባኛል የሚወዘገቡባቸው ስፍራዎች በህዝበ ውሳኔ መፍትሔ ሊሰጣቸው እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐበይ አህመድ ፍንጭ ሰጡ፡፡
‹የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ድግሱን አብን አብሮን ሲያፋፋም ነበር› - ዐብይ አህመድ
የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 28ኛ መደበኛ ጉባዔው እንደቀጠለ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ለእረፍት ከመውጣቱ በፊት ለተነሱት ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ምላሽ እየሰጡበት ነው፡፡ከእነዚህም መካከል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የምክር ቤት አባሉ ደሳለኛ ጫኔ ያነሱት ጥያቄ ይገኝበታል፡፡
ደሳለኝ ‹ ምክር ቤቱ እንዲበተንና አዲስ ምርጫ እንዲደረግ › በጠየቁበት ወቅት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ‹ የብልፅግናና ህወሓት የስልጣን ጦርነት › ሲል መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ ዐብይ ስለሰሜን ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ በሚሰጡበት ወቅት ለምክር ቤቱ አባል ደሳለኝ ጫኔ አገላለፅ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
‹እንደተባለው የቲ.ፒ.ኤል.ኤፍ. እና ብልፅግና ችግር ከሆነ አብኖች የት ነበራችሁ?፤ ለምን አታስታርቁም ነበር? የሚል ጥያቄ አብሮ ይነሳል › ያሉት ዐብይ ‹ አስታራቂ ሲጠፋ ነው ግጭት የሚበዛው፤ እና ድግሱን አብረን ስናፋፋም ቆይተን አሁን ለተወሰኑ ወገኖች መስጠት ሳይሆን….ማንም ይጀምረው ማን ግጭቱ ጥሩ አይደለም - ጥፋት ነው › ሲሉ መልሰዋዋል፡፡
‹ ነግር ግን ከጦርነት በኋላ ኢትዮጵያ የእፎይታ ጊዜ ትፈልጋለች › ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የጦርነቱ ቀስቃሽ ማን ነው? ለሚለው ግምገማ ይፈልጋል ያሉት ዐብይ የምክር ቤት አባሉን ፍረጃ አልተቀበሉትም፡፡‹የግምገማ ጊዜ …. አሁን እንዴት ተጀመረ?፤ እነማን ጀመሩት?፤ እነማን ደገሱት?፤ እነማን አዋጉ?፤ እነማን አስጨረሱ?፤ እነማን ደግሞ አሁን ተቀምጠው ይቀልዳሉ? የሚለውን መገምገም ይፈልጋል › ሲሉም አክለዋል፡፡
‹ ኪሳራና ጥቅሙን ለማወቅ ግምገማ ያስፈልገዋል › ያሉት ዐብይ ‹ ለነገሩ የባለፈውንም ሳንገመግም አዳዲስ ጦርነቶች ናቸው የሚታሰቡት ግን መገምገም ይፈልጋል፤ ከግምገማ በኋላ መልሶ ግንባታ ያስፈልጋል › ሲሉ አሳስበዋል፡፡ ‹ ሰላም ከፈለግህ ትርክትህን መቀየር አለብህ › ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
በሌላ በኩል የአማራና ትግራይ ክልሎች ስለሚዘገቡባቸው ቦታዎች ማብራሪያ የሰጡት ዐብይ ‹ ታላቁ › ሲሉ ያደነቋቸው ‹የአማራና ትግራይ ሕዝብ ይህን ጉዳይ በስክነት እንዲመለከቱት እመክራለሁ › ብለዋል፡፡ ‹ ቦታ የፀብ ምንጭ መሆን የለበትም › የሚሉት ዐብይ ‹ ሰዎች የትኛው ክልል መኖር እንደሚፈልጉ መወሰን ይችላሉ › ሲሉ ምልከታቸውን አጋርተዋል፡፡
የእነዚህ ቦታዎች ውዝግብ በህዝበ ውሳኔ ሊፈታ እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ለዚህ እንደ ዋቢነት የተጠቀሙት ትናንት ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲመሰረት ውሳኔ የተላለፈለትን የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች የተሰኘውን ክልል ውሳኔ በመጥቀስ ነው፡፡ዐብይ በማብራሪያቸው ‹ ይህን በሲዳማ አድርገነዋል፤ በደቡብ ምዕራብ አድርገነዋል › ብለዋል፡፡ ‹ በሰከነ መንገድ ሰው ሳይሞት ማድረግ ይቻላል፤ ከዚያ ውጭ ያለው አማራጭ ጥሩ አይደለም › ሲሉ አሳስበዋል፡፡
✍Asham
@YeneTube @FikerAssefa
‹የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ድግሱን አብን አብሮን ሲያፋፋም ነበር› - ዐብይ አህመድ
የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 28ኛ መደበኛ ጉባዔው እንደቀጠለ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ለእረፍት ከመውጣቱ በፊት ለተነሱት ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ምላሽ እየሰጡበት ነው፡፡ከእነዚህም መካከል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የምክር ቤት አባሉ ደሳለኛ ጫኔ ያነሱት ጥያቄ ይገኝበታል፡፡
ደሳለኝ ‹ ምክር ቤቱ እንዲበተንና አዲስ ምርጫ እንዲደረግ › በጠየቁበት ወቅት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ‹ የብልፅግናና ህወሓት የስልጣን ጦርነት › ሲል መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ ዐብይ ስለሰሜን ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ በሚሰጡበት ወቅት ለምክር ቤቱ አባል ደሳለኝ ጫኔ አገላለፅ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
‹እንደተባለው የቲ.ፒ.ኤል.ኤፍ. እና ብልፅግና ችግር ከሆነ አብኖች የት ነበራችሁ?፤ ለምን አታስታርቁም ነበር? የሚል ጥያቄ አብሮ ይነሳል › ያሉት ዐብይ ‹ አስታራቂ ሲጠፋ ነው ግጭት የሚበዛው፤ እና ድግሱን አብረን ስናፋፋም ቆይተን አሁን ለተወሰኑ ወገኖች መስጠት ሳይሆን….ማንም ይጀምረው ማን ግጭቱ ጥሩ አይደለም - ጥፋት ነው › ሲሉ መልሰዋዋል፡፡
‹ ነግር ግን ከጦርነት በኋላ ኢትዮጵያ የእፎይታ ጊዜ ትፈልጋለች › ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የጦርነቱ ቀስቃሽ ማን ነው? ለሚለው ግምገማ ይፈልጋል ያሉት ዐብይ የምክር ቤት አባሉን ፍረጃ አልተቀበሉትም፡፡‹የግምገማ ጊዜ …. አሁን እንዴት ተጀመረ?፤ እነማን ጀመሩት?፤ እነማን ደገሱት?፤ እነማን አዋጉ?፤ እነማን አስጨረሱ?፤ እነማን ደግሞ አሁን ተቀምጠው ይቀልዳሉ? የሚለውን መገምገም ይፈልጋል › ሲሉም አክለዋል፡፡
‹ ኪሳራና ጥቅሙን ለማወቅ ግምገማ ያስፈልገዋል › ያሉት ዐብይ ‹ ለነገሩ የባለፈውንም ሳንገመግም አዳዲስ ጦርነቶች ናቸው የሚታሰቡት ግን መገምገም ይፈልጋል፤ ከግምገማ በኋላ መልሶ ግንባታ ያስፈልጋል › ሲሉ አሳስበዋል፡፡ ‹ ሰላም ከፈለግህ ትርክትህን መቀየር አለብህ › ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
በሌላ በኩል የአማራና ትግራይ ክልሎች ስለሚዘገቡባቸው ቦታዎች ማብራሪያ የሰጡት ዐብይ ‹ ታላቁ › ሲሉ ያደነቋቸው ‹የአማራና ትግራይ ሕዝብ ይህን ጉዳይ በስክነት እንዲመለከቱት እመክራለሁ › ብለዋል፡፡ ‹ ቦታ የፀብ ምንጭ መሆን የለበትም › የሚሉት ዐብይ ‹ ሰዎች የትኛው ክልል መኖር እንደሚፈልጉ መወሰን ይችላሉ › ሲሉ ምልከታቸውን አጋርተዋል፡፡
የእነዚህ ቦታዎች ውዝግብ በህዝበ ውሳኔ ሊፈታ እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ለዚህ እንደ ዋቢነት የተጠቀሙት ትናንት ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም 12ኛ ክልል ሆኖ እንዲመሰረት ውሳኔ የተላለፈለትን የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች የተሰኘውን ክልል ውሳኔ በመጥቀስ ነው፡፡ዐብይ በማብራሪያቸው ‹ ይህን በሲዳማ አድርገነዋል፤ በደቡብ ምዕራብ አድርገነዋል › ብለዋል፡፡ ‹ በሰከነ መንገድ ሰው ሳይሞት ማድረግ ይቻላል፤ ከዚያ ውጭ ያለው አማራጭ ጥሩ አይደለም › ሲሉ አሳስበዋል፡፡
✍Asham
@YeneTube @FikerAssefa
ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ የሰሜኑ ጦርነት በተካሄደበት ወቅት ጦርነቱ እንዲቆም መግለጫ ባለመስጠቱ እና በወቅቱ በትግራይ ክልል ተገኝቶ ሕዝቡን ባለመጠየቁና ባለማጽናናቱ ይቅርታ ጠየቀ!
ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ልዩ ጉባኤ ማጠናቀቁን ተከትሎ በዛሬው ዕለት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሚዲያዎች በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በሁለት ዐበይት አጀንዳዎች መወያየቱን ገልጾ የኤጲስ ቆጶሳትን ሹመት በተመለከተ የተመረጡ ቆሞሳትን ይፋ በማድረግ የፊታችን ሐምሌ ዘጠኝ ሢመቱ እንደሚፈጸም አስታውቋል።
በሌላ በኩል በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመስጠቷ፣ በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ፣ ሊቃውንተ ቤተ
ክርስቲያንንና መላው ሕዝበ ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣ ጦርነቱ ቁሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣ በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታ መጠየቁን በንባብ ከተሰማው የቅዱስ ሲኖዶሱ መግለጫ ለመረዳት ተችሏል።
Via ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
@YeneTube @FikerAssefa
ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን ልዩ ጉባኤ ማጠናቀቁን ተከትሎ በዛሬው ዕለት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሚዲያዎች በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በሁለት ዐበይት አጀንዳዎች መወያየቱን ገልጾ የኤጲስ ቆጶሳትን ሹመት በተመለከተ የተመረጡ ቆሞሳትን ይፋ በማድረግ የፊታችን ሐምሌ ዘጠኝ ሢመቱ እንደሚፈጸም አስታውቋል።
በሌላ በኩል በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመስጠቷ፣ በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ፣ ሊቃውንተ ቤተ
ክርስቲያንንና መላው ሕዝበ ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣ ጦርነቱ ቁሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣ በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታ መጠየቁን በንባብ ከተሰማው የቅዱስ ሲኖዶሱ መግለጫ ለመረዳት ተችሏል።
Via ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
@YeneTube @FikerAssefa
የ2016 በጀት 801 ነጥብ 65 ቢሊየን ብር ሆኖ ጸደቀ!
የፌደራል መንግስት የ2016 በጀት 801 ነጥብ 65 ቢሊየን ብር ሆኖ ጸድቋል፡፡የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀት ላይ የቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡ምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2016 በጀት ዓመት በጀትን አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ ነው መርምሮ የበጀት አዋጁን ያጸደቀው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የፌደራል መንግስት የ2016 በጀት 801 ነጥብ 65 ቢሊየን ብር ሆኖ ጸድቋል፡፡የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀት ላይ የቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡ምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2016 በጀት ዓመት በጀትን አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ ነው መርምሮ የበጀት አዋጁን ያጸደቀው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa