በሶማሌ ክልል የተከሰተውን ድርቅ መቋቋም እንደተቻለ የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡
በሶማሌ ክልል ላለፉት ወራት በዝናብ እጥረት ምክንያት በተከሰተው ድርቅ በተለይ በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ የክልሉ መንግስት ድርቁን ለመቋቋምና ህዝብና እንስሳትን ለመታደግ በሰራው ስራ ድርቁን መቋቋም እንደቻለ ገልጿል፡፡
አሁን ላይ የድርቅ አደጋ ጊዜ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝና በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች የበልግ ዝናብ መጣል መጀመሩን የገለጸው የክልሉ መንግስት፤ ድርቁን ለመቋቋም እንደተሰራው ሁሉ፣ በድህረ ድርቁ ወቅትም ጠንካራ ዝግጅት አድርጎ ወደ ስራ መግባቱን ትላንት አመሻሹን ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል፡፡
በክልሉ አካባቢዎች መዝነብ ከጀመረው የበልግ ዝናም በድርቁ የተጎዱ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግና በወንዞችና ተፋሰስ አከባቢዎች ሊከሰቱ የሚችሉ የጎርፍ አደጋዎች፣ ወረርሽኝና ተዛማጅ ጉዳዮች ለመከላከል ጠንካራ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውንም አክሏል፡፡
የክልሉ አደጋ ስጋት አመራርና የጤና ቢሮ አመራሮች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በመውረድ አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ እንዲሰጡ የክልሉ መንግሥት ኮሚቴዎችን አዋቅሮ ማሰማራቱም በመግለጫው ተመልክቷል፡፡
የድርቅ አደጋውን ለመቋቋም ከክልሉ መንግሥትና ህዝብ ጎን በመሆን የክልል መንግስታትና ህዝቦች፤ ባለሀብቶች፣ ግብረሰናይ ድርጅቶች እንዲሁም የፌዴራል መንግሥት ላደረጉት ድጋፍና ትብብር የክልሉ መንግሥት ምስጋና ማቅረቡን ከክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሌ ክልል ላለፉት ወራት በዝናብ እጥረት ምክንያት በተከሰተው ድርቅ በተለይ በእንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ የክልሉ መንግስት ድርቁን ለመቋቋምና ህዝብና እንስሳትን ለመታደግ በሰራው ስራ ድርቁን መቋቋም እንደቻለ ገልጿል፡፡
አሁን ላይ የድርቅ አደጋ ጊዜ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝና በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች የበልግ ዝናብ መጣል መጀመሩን የገለጸው የክልሉ መንግስት፤ ድርቁን ለመቋቋም እንደተሰራው ሁሉ፣ በድህረ ድርቁ ወቅትም ጠንካራ ዝግጅት አድርጎ ወደ ስራ መግባቱን ትላንት አመሻሹን ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል፡፡
በክልሉ አካባቢዎች መዝነብ ከጀመረው የበልግ ዝናም በድርቁ የተጎዱ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግና በወንዞችና ተፋሰስ አከባቢዎች ሊከሰቱ የሚችሉ የጎርፍ አደጋዎች፣ ወረርሽኝና ተዛማጅ ጉዳዮች ለመከላከል ጠንካራ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውንም አክሏል፡፡
የክልሉ አደጋ ስጋት አመራርና የጤና ቢሮ አመራሮች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በመውረድ አስፈላጊው ትብብርና ድጋፍ እንዲሰጡ የክልሉ መንግሥት ኮሚቴዎችን አዋቅሮ ማሰማራቱም በመግለጫው ተመልክቷል፡፡
የድርቅ አደጋውን ለመቋቋም ከክልሉ መንግሥትና ህዝብ ጎን በመሆን የክልል መንግስታትና ህዝቦች፤ ባለሀብቶች፣ ግብረሰናይ ድርጅቶች እንዲሁም የፌዴራል መንግሥት ላደረጉት ድጋፍና ትብብር የክልሉ መንግሥት ምስጋና ማቅረቡን ከክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል በጦርነቱ ጉዳት በደረሰባቸው አራት ዞኖች የሚገኙ ከ60 ሺህ በላይ ህጻናትን መንከባከብ የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ!
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ፣ ሰሜን ሸዋና ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞኖች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ከ60 ሺህ በላይ ህጻናትን መንከባከብ የሚያስችል ፕሮጀክት በደሴ ከተማ ይፋ ተደርጓል።ፕሮጀክቱ የአንድ ዓመት መርሃ ግብር ሲሆን፤ በአራቱ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ላይ ይተገበራል ተብሏል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ባደረገው የዳሰሳ ጥናት በአማራ ክልል ነፍሰ ጡርና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ህጻናት በጦርነቱ ሳቢያ ክፉኛ መጎዳታቸውን ማረጋገጡን የፓዝ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ትርሲት ግርሻው ተናግረዋል። በአካባቢዎቹ የተደረገው ጦርነት በበርካታ ህጻናትና እናቶች ላይ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረሱን የጠቆሙት ዳይሬክተሯ፤ መርሃ ግብሩ ከሰሜን ወሎ ዞን ግዳንና ራያ ቆቦ ወረዳዎች፣ ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ፣ ከዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞን ሰቆጣ ዙሪያና ዳህና ወረዳዎች እንዲሁም ከሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ የሚተገበር መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም 60 ሺህ የሚደርሱ ህጻናትና ከ15 ሺህ በላይ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች በቀጥታ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ከ446 ሺህ በላይ ህዝብ ደግሞ በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።ይህ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤ መርሃ ግብር 500 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፤ የገንዘብ ድጋፉን ያደረገው ቢግ ዊን ፊላንትሮፊ የተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ነው።
በመሆኑም በአማራ ክልል የከፋ ጉዳት የደረሰባቸው በአራት ዞኖችና ስድስት ወረዳዎች የሚገኙ ህፃናትና እናቶች በዚሁ የክብካቤ በመርሐ ግብር መካተታቸውን ተናግረዋል።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ ፍቃዱ ያደታ፤ በኢትዮጵያ 59 በመቶ የሚሆኑ ህፃናት በዕድሜያቸው ልክ መድረስ ከሚገባቸው አካላዊና አዕምሯዊ ዕድገት ያልደረሱ ስለመሆናቸው ገልጸዋል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የጀመረው የቅድመ ልጅነት ዘመን፣ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች ክብካቤ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ መጠቆማቸውን ከደቡብ ወሎ ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ ተስፋ ዳኛው በበኩላቸው፤ ፓዝ ኢትዮጵያ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤው ህፃናት በአካላቸው የጠነከሩ በአዕምሯቸው የጎለበቱ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችል በመሆኑ፤ በሚመለከታቸው የመንግስት መዋቅሮች ተገቢው ድጋፍና ክትትል ይደረጋለታል ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ፣ ሰሜን ሸዋና ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞኖች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ከ60 ሺህ በላይ ህጻናትን መንከባከብ የሚያስችል ፕሮጀክት በደሴ ከተማ ይፋ ተደርጓል።ፕሮጀክቱ የአንድ ዓመት መርሃ ግብር ሲሆን፤ በአራቱ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ላይ ይተገበራል ተብሏል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ባደረገው የዳሰሳ ጥናት በአማራ ክልል ነፍሰ ጡርና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ህጻናት በጦርነቱ ሳቢያ ክፉኛ መጎዳታቸውን ማረጋገጡን የፓዝ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ትርሲት ግርሻው ተናግረዋል። በአካባቢዎቹ የተደረገው ጦርነት በበርካታ ህጻናትና እናቶች ላይ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረሱን የጠቆሙት ዳይሬክተሯ፤ መርሃ ግብሩ ከሰሜን ወሎ ዞን ግዳንና ራያ ቆቦ ወረዳዎች፣ ከደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ፣ ከዋግ ኽምራ ብሄረሰብ ዞን ሰቆጣ ዙሪያና ዳህና ወረዳዎች እንዲሁም ከሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ የሚተገበር መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም 60 ሺህ የሚደርሱ ህጻናትና ከ15 ሺህ በላይ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች በቀጥታ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል። ከ446 ሺህ በላይ ህዝብ ደግሞ በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።ይህ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤ መርሃ ግብር 500 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፤ የገንዘብ ድጋፉን ያደረገው ቢግ ዊን ፊላንትሮፊ የተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ነው።
በመሆኑም በአማራ ክልል የከፋ ጉዳት የደረሰባቸው በአራት ዞኖችና ስድስት ወረዳዎች የሚገኙ ህፃናትና እናቶች በዚሁ የክብካቤ በመርሐ ግብር መካተታቸውን ተናግረዋል።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ ፍቃዱ ያደታ፤ በኢትዮጵያ 59 በመቶ የሚሆኑ ህፃናት በዕድሜያቸው ልክ መድረስ ከሚገባቸው አካላዊና አዕምሯዊ ዕድገት ያልደረሱ ስለመሆናቸው ገልጸዋል።
ፓዝ ኢትዮጵያ የጀመረው የቅድመ ልጅነት ዘመን፣ የሚያጠቡና ነፍሰ ጡር እናቶች ክብካቤ መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ መጠቆማቸውን ከደቡብ ወሎ ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ወሎ ዞን ም/ አስተዳዳሪ ተስፋ ዳኛው በበኩላቸው፤ ፓዝ ኢትዮጵያ የቅድመ ልጅነት ዘመን እንክብካቤው ህፃናት በአካላቸው የጠነከሩ በአዕምሯቸው የጎለበቱ ሆነው እንዲያድጉ የሚያስችል በመሆኑ፤ በሚመለከታቸው የመንግስት መዋቅሮች ተገቢው ድጋፍና ክትትል ይደረጋለታል ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በሱማሌ ክልል በቦምባስ ከተማ በተፈጠረ ግጭት ሰዎች መሞታቸው ኢዜማ አስታወቀ!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መጋቢት 12/2014 በሱማሌ ክልል በቦምባስ ከተማ በተፈጠረው ግጭት የሰው ህይወት መጥፋቱንና በዜጎች ላይም የአካል ጉዳት ማጋጠሙን ታማኝ ከሆኑ ምንጮች መረጃ ደርሶኛል ሲል አስታውቋል፡፡
ፓርቲው በቦምባስ ከተማ ሊካሄድ በነበረው የአኪሾ የጎሳ መሪ ምርጫ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት፤ የጸጥታ ኃይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል በመጠቀማቸው የሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን፤ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል፡፡
በክልሉ በተለያዩ ጊዜ ማኅበረሰቡን ያሳተፈ የጎሳ ምርጫ የሚደረግ ሲኾን፤ በቅርቡ ሊደረግ የነበረው የአኪሾ ጎሳ መሪ ምርጫ ድብቅ የፖለቲካ አላማ ያላቸው አካላት ፍላጎታቸውን ለማሳካት ባደረጉት ጥረት በጸጥታ አካላትና በሕዝቡ መሀከል ግጭት እንዲነሳ በዛም ደግሞ ንጹሃንን ተጎጂ ያደረገ ጉዳት ደርሷል፡፡
በሱማሌ ክልል በተለያየ ጊዜ የሰውና የመንግሥትን ንብረት ያወደመ፣ የሰውን ሕይወት የቀጠፈ ግጭት ከተፈጠረ በኋላ የግጭቱ መነሻ ምን እንደሆነ ሳይጣራ፣ አጥፊዎች ተለይተው ለህግ ሳይቀርቡ፣ የፍትህ ሥርዓቱ አስተማሪ የሆነ ቅጣት ሳያስተላልፍ፤ በመንግሥት ኃላፊዎች እገዛ ጭምር ግልፅ ያልሆነ የእርቅ ሂደት መከናወኑ ግጭቶች እንዲደጋገሙ መንገድ ከመክፈቱ በተጨማሪ የክልሉን ሰላም ከቀን ወደ ቀን አስተማማኝ እንዳይሆን እያደረገው ይገኛል ሲልም ኢዜማ ገልጿል፡፡
የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከዚህ ድርጊት በስተጀርባ እጃቸው ያለበትና የሚመለከታቸውን አካላት ማንነት በማጣራት አፋጣኝ ፍትህ እንዲሰጥ ያሳሰበው ፓርቲው፤ ግጭቱን ተከትሎ የቆሰሉ አካላት ተገቢ ሕክምና እንዲያገኙ፣ የሟች ቤተሰቦችም ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ ጠይቋል፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መጋቢት 12/2014 በሱማሌ ክልል በቦምባስ ከተማ በተፈጠረው ግጭት የሰው ህይወት መጥፋቱንና በዜጎች ላይም የአካል ጉዳት ማጋጠሙን ታማኝ ከሆኑ ምንጮች መረጃ ደርሶኛል ሲል አስታውቋል፡፡
ፓርቲው በቦምባስ ከተማ ሊካሄድ በነበረው የአኪሾ የጎሳ መሪ ምርጫ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት፤ የጸጥታ ኃይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል በመጠቀማቸው የሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን፤ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል፡፡
በክልሉ በተለያዩ ጊዜ ማኅበረሰቡን ያሳተፈ የጎሳ ምርጫ የሚደረግ ሲኾን፤ በቅርቡ ሊደረግ የነበረው የአኪሾ ጎሳ መሪ ምርጫ ድብቅ የፖለቲካ አላማ ያላቸው አካላት ፍላጎታቸውን ለማሳካት ባደረጉት ጥረት በጸጥታ አካላትና በሕዝቡ መሀከል ግጭት እንዲነሳ በዛም ደግሞ ንጹሃንን ተጎጂ ያደረገ ጉዳት ደርሷል፡፡
በሱማሌ ክልል በተለያየ ጊዜ የሰውና የመንግሥትን ንብረት ያወደመ፣ የሰውን ሕይወት የቀጠፈ ግጭት ከተፈጠረ በኋላ የግጭቱ መነሻ ምን እንደሆነ ሳይጣራ፣ አጥፊዎች ተለይተው ለህግ ሳይቀርቡ፣ የፍትህ ሥርዓቱ አስተማሪ የሆነ ቅጣት ሳያስተላልፍ፤ በመንግሥት ኃላፊዎች እገዛ ጭምር ግልፅ ያልሆነ የእርቅ ሂደት መከናወኑ ግጭቶች እንዲደጋገሙ መንገድ ከመክፈቱ በተጨማሪ የክልሉን ሰላም ከቀን ወደ ቀን አስተማማኝ እንዳይሆን እያደረገው ይገኛል ሲልም ኢዜማ ገልጿል፡፡
የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከዚህ ድርጊት በስተጀርባ እጃቸው ያለበትና የሚመለከታቸውን አካላት ማንነት በማጣራት አፋጣኝ ፍትህ እንዲሰጥ ያሳሰበው ፓርቲው፤ ግጭቱን ተከትሎ የቆሰሉ አካላት ተገቢ ሕክምና እንዲያገኙ፣ የሟች ቤተሰቦችም ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ ጠይቋል፡፡
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ከፍተኛ ስርቆት በመዲናችን አዲስ አበባ ተፈጽሟል ተባለ!
- ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ተብሏል!
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጎሮ ሰፈራ ልዩ ቦታው ፖስታ ቤት መቲ ጋራዥ አካባቢ በቀን 11፣ 2014 ዓ.ም የቻይና ነጋዴዎች ተከራይተው ይሰሩበት የነበረው መጋዘን ላይ ከፍተኛ ስርቆት የተፈጸመው፡፡በዚህ ስርቆት 418 ያህል ቴሌቪዥኖች የተሰረቁ ሲሆን ቁጥራቸው የማይታወቅ ላፕቶፕ ኮምፒተሮች የመኪና ባትሪዎች እንደዚሁም 63ሺህ ጥሬ ገንዘብ አብሮ መሰረቁን ነው ኢትዮ ኤፍ ኤም አገኘሁት ያለው መረጃ የሚጠቁመው፡፡
እነዚህ ነጋዴዎች መጋዘኑን የተከራዩት ከአንድ ወር በፊት የነበረ ሲሆን ከቻይና በርካታ እቃዎችን እያስመጡ ለነጋዴዎች ያከፋፍሉበታል የነበረ መጋዘን ነው፡፡አቶ መኮንን ድርጊቱን ያቀነባበሩት የጥበቃ ሰራተኞች ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ያላቸውን ግምት ያስቀመጡ ሲሆን አሁን ላይ እነዚህ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል ብለዋል፡፡
ቃላቸውን ለፖሊስ የሰጡት የጥበቃ ሰራተኞች በበኩላቸው ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ያሉት አቶ መኮነን ፣ከድርጊቱ መፈጸም በላይ የጸጥታ አካላት የሰጡት ምላሽ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡
የቤት አከራዩ አቶ መኮንን ስርቆቱ በተፈጸመበት እለት መብራት ጠፍቶ እንደነበረ እና የአይሱዚ መኪና መጋዘን ውስጥ ገብቶ መጫኑን በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ጥቆማቸውን እንዳደረሱዋቸው ተናግረዋል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
- ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ተብሏል!
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጎሮ ሰፈራ ልዩ ቦታው ፖስታ ቤት መቲ ጋራዥ አካባቢ በቀን 11፣ 2014 ዓ.ም የቻይና ነጋዴዎች ተከራይተው ይሰሩበት የነበረው መጋዘን ላይ ከፍተኛ ስርቆት የተፈጸመው፡፡በዚህ ስርቆት 418 ያህል ቴሌቪዥኖች የተሰረቁ ሲሆን ቁጥራቸው የማይታወቅ ላፕቶፕ ኮምፒተሮች የመኪና ባትሪዎች እንደዚሁም 63ሺህ ጥሬ ገንዘብ አብሮ መሰረቁን ነው ኢትዮ ኤፍ ኤም አገኘሁት ያለው መረጃ የሚጠቁመው፡፡
እነዚህ ነጋዴዎች መጋዘኑን የተከራዩት ከአንድ ወር በፊት የነበረ ሲሆን ከቻይና በርካታ እቃዎችን እያስመጡ ለነጋዴዎች ያከፋፍሉበታል የነበረ መጋዘን ነው፡፡አቶ መኮንን ድርጊቱን ያቀነባበሩት የጥበቃ ሰራተኞች ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ያላቸውን ግምት ያስቀመጡ ሲሆን አሁን ላይ እነዚህ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል ብለዋል፡፡
ቃላቸውን ለፖሊስ የሰጡት የጥበቃ ሰራተኞች በበኩላቸው ስርቆቱ የተፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በለበሱ ሰዎች ነው ያሉት አቶ መኮነን ፣ከድርጊቱ መፈጸም በላይ የጸጥታ አካላት የሰጡት ምላሽ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡
የቤት አከራዩ አቶ መኮንን ስርቆቱ በተፈጸመበት እለት መብራት ጠፍቶ እንደነበረ እና የአይሱዚ መኪና መጋዘን ውስጥ ገብቶ መጫኑን በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ጥቆማቸውን እንዳደረሱዋቸው ተናግረዋል፡፡
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
“መንግስት ከታጠቁ ሃይሎች ጋር ድርድር መጀመር አለበት ”የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ)
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) 2 መደበኛ ጉባዔ ከመጋቢት 17-18 ማካሄዱን ተከትሎ በሀገሪቱና በህዝቡ ያጋጠሙ ፈተናዎች ላይ በመወያየት የፓርቲውን ቀጣይ የትግል መዕራፍ እና እስትራቲጂ አቅጣጫውን አስቀምጧል።
ከ 4 ዓመታተ በፊት የመጣው ለውጥ ሀገራችን ወደአዲስ የሰላም እና ዲሞክራሲ ያሸጋገራል የሚል ተስፋ ቢኖርም የለውጡ ሂደት ተቀልብሶ ወደ ዲሞክራሲ የነበርው ሽግግር እድል ባክኖ የእርስ በርስ ጦርነትና የሀገር መፍረስ አደጋ ተጋርጦብናል ሲል የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) የመደበኛው ግባዔ መጠናቀቁን ተከትሎ ባውጣው መግለጫ አስታውቋል ።
በቅርቡም የፌደራሉ እና የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጦርነትን ለማቆም ያሳለፉት ውሳኔ በፍጥነት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲለውጥ ጥሪውን አስተላልፏል ኦፌኮ።
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋርም የገባበትን ጦርነት በሰላማዊ መንግድ ለመፍታት ቁርጠኝነቱን ሊያሳይ እንደሚገባም ፓርቲው አሳስቧል።
በሁሉም የአገሪት አካባቢዎች ግጭት እንዲቆም ፤ መንግስት ከታጠቁ ሃይሎች ጋር ድርድር እንዲጀምር እና ብሔራዊ ምክክሩ ላይ እንዲሳትፉ ፤ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች በተለይም የኦፌኮ እና ኦነግ አባለት ከእስር እንዲፈቱ የሚሉት ጉዳዮዎች ኦፌኮ በአቋም መግልጫው አጽኖት የሰጠባቸው ጉዳዮች ናቸው።
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) 2 መደበኛ ጉባዔ ከመጋቢት 17-18 ማካሄዱን ተከትሎ በሀገሪቱና በህዝቡ ያጋጠሙ ፈተናዎች ላይ በመወያየት የፓርቲውን ቀጣይ የትግል መዕራፍ እና እስትራቲጂ አቅጣጫውን አስቀምጧል።
ከ 4 ዓመታተ በፊት የመጣው ለውጥ ሀገራችን ወደአዲስ የሰላም እና ዲሞክራሲ ያሸጋገራል የሚል ተስፋ ቢኖርም የለውጡ ሂደት ተቀልብሶ ወደ ዲሞክራሲ የነበርው ሽግግር እድል ባክኖ የእርስ በርስ ጦርነትና የሀገር መፍረስ አደጋ ተጋርጦብናል ሲል የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ(ኦፌኮ) የመደበኛው ግባዔ መጠናቀቁን ተከትሎ ባውጣው መግለጫ አስታውቋል ።
በቅርቡም የፌደራሉ እና የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጦርነትን ለማቆም ያሳለፉት ውሳኔ በፍጥነት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲለውጥ ጥሪውን አስተላልፏል ኦፌኮ።
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋርም የገባበትን ጦርነት በሰላማዊ መንግድ ለመፍታት ቁርጠኝነቱን ሊያሳይ እንደሚገባም ፓርቲው አሳስቧል።
በሁሉም የአገሪት አካባቢዎች ግጭት እንዲቆም ፤ መንግስት ከታጠቁ ሃይሎች ጋር ድርድር እንዲጀምር እና ብሔራዊ ምክክሩ ላይ እንዲሳትፉ ፤ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች በተለይም የኦፌኮ እና ኦነግ አባለት ከእስር እንዲፈቱ የሚሉት ጉዳዮዎች ኦፌኮ በአቋም መግልጫው አጽኖት የሰጠባቸው ጉዳዮች ናቸው።
@YeneTube @FikerAssefa
አዲስ አበባ በአፍሪካ ለኑሮ ውዷ ከተማ ተባለች!
ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ የተባለ ድህረገጽ ይዞ በወጣው መረጃ መዲናችን አዲስ አበባ በአፍሪካ ለኑሮ ውዷ ከተማ ተብላለች። ድህረገጹ ባወጣው አሃዛዊ ኢንዴክስ(index) አዲስአበባ በ58.92 በአንደኛ ደረጃ ተቀምጣለች። በሁለተኛ እና በሶስተኛ ደረጃ የተቀመጡት የኮትዲቯሯ አቢጃን እና የዚምባቡዌዋ ሃራሬ ሲሆኑ 55.73 እና 52.33 በቅድመ ተከተል የተሰጣቸው ኢንዴክስ ነዉ።
https://africa.businessinsider.com/local/lifestyle/15-african-cities-with-the-highest-cost-of-living-index-scores/11ghkpw
@YeneTube @FikerAssefa
ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ የተባለ ድህረገጽ ይዞ በወጣው መረጃ መዲናችን አዲስ አበባ በአፍሪካ ለኑሮ ውዷ ከተማ ተብላለች። ድህረገጹ ባወጣው አሃዛዊ ኢንዴክስ(index) አዲስአበባ በ58.92 በአንደኛ ደረጃ ተቀምጣለች። በሁለተኛ እና በሶስተኛ ደረጃ የተቀመጡት የኮትዲቯሯ አቢጃን እና የዚምባቡዌዋ ሃራሬ ሲሆኑ 55.73 እና 52.33 በቅድመ ተከተል የተሰጣቸው ኢንዴክስ ነዉ።
https://africa.businessinsider.com/local/lifestyle/15-african-cities-with-the-highest-cost-of-living-index-scores/11ghkpw
@YeneTube @FikerAssefa
#ወርቃማ_ሕጎች
የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#አእምሮህ_ማግኔት_ነው!
ሁልጊዜም አእምሮህ ማግኔት መሆኑን አስታውስ፡፡ አንተን የተቆጣጠሩህን ሃሳቦች እና በውስጥ የሰረፁትን እምነቶች የሚያምኑ እና የሚያስቡ ሌሎች ሰዎች ወዳንተ እንደሚያቀርብም ልብ በል፡፡
በትክክለኛ መንገድ የስበት ህግ (law of attraction) ብለን የምንጠራው አንድ ህግ አለ፡፡ ውሃ ከፍታውን የሚፈልግበት፣ በህዋ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ የየራሳቸውን አምሳያ የሚፈልጉበት ህግ፡፡ ፕላኔቶችን በትክክለኛ ቦታቸው ጠብቆ እንደሚያቆየው የስበት ህግ፡፡
ይህ ህግ የሚለዋወጥ ቢሆን ኖሮ የማንጎ ፍሬ ከአበባው ውስጥ በርራ በፓፓያ አበባ ውስጥ በመግባት በከፊል ማንጎ፣ በከፊል ደግሞ ፓፓያ የሆነ ዛፍ ይፈጥሩ ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ግን ሰምተን አናውቅም፡፡ ይሄንን የስበት ህግ ትንሽ በመከተል በሴቶች እና በወንዶች መካከል እንዴት እንደሚሰራ ማየት እንችላለን፡፡
ውጤታማና ሃብታም ወንዶች የሚፈልጓት ሴት የእነሱኑ አይነት ሴት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያለ ወንድም እንደዚያው፡፡ ይህ የሚሆነው በተፈጥሮ ነው - ልክ ውሃ ወደ ታች እንደሚፈሰው፡፡
“ሁሉም አምሳያውን ይስባል” የሚለው አባባል የማይገሰስ ሀቅ ነው፡፡ አንድ ወንድ የሚፈልጋት ሴት በብዙ መልኩ እሱን የምትመስለውን ሴት መሆኑ እውነት ከሆነ፣ የምትፈልጋቸውን ሰዎች ለማሰብ የእነዚህን ሰዎች ሀሳቦች እና እምነቶች በመቆጣጠር እና በማዳበር ማግኔት የመስራትን ጥቅም ማየት አትችልም?
#ወርቃማው_ሕግ መጽሐፍ
በየመጽሐፍት መደብሩና አዟሪዎች እጅ ይገኛል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram- https://tttttt.me/teklu_tilahun
የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#አእምሮህ_ማግኔት_ነው!
ሁልጊዜም አእምሮህ ማግኔት መሆኑን አስታውስ፡፡ አንተን የተቆጣጠሩህን ሃሳቦች እና በውስጥ የሰረፁትን እምነቶች የሚያምኑ እና የሚያስቡ ሌሎች ሰዎች ወዳንተ እንደሚያቀርብም ልብ በል፡፡
በትክክለኛ መንገድ የስበት ህግ (law of attraction) ብለን የምንጠራው አንድ ህግ አለ፡፡ ውሃ ከፍታውን የሚፈልግበት፣ በህዋ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ የየራሳቸውን አምሳያ የሚፈልጉበት ህግ፡፡ ፕላኔቶችን በትክክለኛ ቦታቸው ጠብቆ እንደሚያቆየው የስበት ህግ፡፡
ይህ ህግ የሚለዋወጥ ቢሆን ኖሮ የማንጎ ፍሬ ከአበባው ውስጥ በርራ በፓፓያ አበባ ውስጥ በመግባት በከፊል ማንጎ፣ በከፊል ደግሞ ፓፓያ የሆነ ዛፍ ይፈጥሩ ነበር፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ግን ሰምተን አናውቅም፡፡ ይሄንን የስበት ህግ ትንሽ በመከተል በሴቶች እና በወንዶች መካከል እንዴት እንደሚሰራ ማየት እንችላለን፡፡
ውጤታማና ሃብታም ወንዶች የሚፈልጓት ሴት የእነሱኑ አይነት ሴት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያለ ወንድም እንደዚያው፡፡ ይህ የሚሆነው በተፈጥሮ ነው - ልክ ውሃ ወደ ታች እንደሚፈሰው፡፡
“ሁሉም አምሳያውን ይስባል” የሚለው አባባል የማይገሰስ ሀቅ ነው፡፡ አንድ ወንድ የሚፈልጋት ሴት በብዙ መልኩ እሱን የምትመስለውን ሴት መሆኑ እውነት ከሆነ፣ የምትፈልጋቸውን ሰዎች ለማሰብ የእነዚህን ሰዎች ሀሳቦች እና እምነቶች በመቆጣጠር እና በማዳበር ማግኔት የመስራትን ጥቅም ማየት አትችልም?
#ወርቃማው_ሕግ መጽሐፍ
በየመጽሐፍት መደብሩና አዟሪዎች እጅ ይገኛል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram- https://tttttt.me/teklu_tilahun
በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎች ከነገ በስቲያ ጀምሮ ወደ አገር ቤት ይመለሳሉ!
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና በማዕከላት ውሰጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።16 የመንግስት ተቋማትን በአባልነት የያዘው ኮሚቴው ዜጎችን መመለስ ለመጀመር የተደረጉ የመጨረሻ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ዛሬ የገመገመ ሲሆን ከመጪው ረቡዕ ጀምሮ ዜጎችን መመለሱ እንደሚጀምር ይፋ ሆኗል።
በውይይቱ እንደተገለፀው የበረራ፣ የማቆያ ማዕከላት ዝግጅት፣ የመገልገያ ቁሳቁስ፣ የምግብ እና መጠጥ አቅርቦት፣ የአልባሳት፣ የትራንስፖርት እንዲሁም የህክምና አገልግሎትን ለተመላሾች በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ በመቻል ረገድ የተደረጉ ዝግጅቶች በግብረ ሃይሉ አባላት ውይይት ተደርጎባቸዋል።የኮሚቴው ሰብሳቢ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንዳሉት የመመለሱ ተግባር ተመላሽ ዜጎችን ካሉበት አምጥቶ እስከ መኖሪያ ቀያቸው የማድረስ ስራን የሚሸፍን ነው።
ይህንኑ ከመነሻው እስከ መድረሻው በተሳለጠ ቅብብሎሽ ለመፈፀም ተቋማት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አምባሳደር ብርቱካን አሳስበዋል።ተመላሾች አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ ክልሎች ከየማዕከላቱ ቶሎ በማንሳት ወደ መኖሪያቸው መውሰድ ያለባቸው በመሆኑ ያደረጉት ዝግጅትም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ክልሎቹ ያልተጠናቀቁ የዝግጅት ስራዎችን በቀሪ ቀናት እንዲያጠናቅቁ አሳስበዋል።በየጊዜው የቅበላ አቅምን በማሳደግ ዜጎችን ካሉበት አስቸጋሪ ሁኔታ ለማውጣት መንግሥት የተቻለውን ጥረት ማድረጉን እንደሚቀጥልም አምባሳደሯ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና በማዕከላት ውሰጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ብሄራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።16 የመንግስት ተቋማትን በአባልነት የያዘው ኮሚቴው ዜጎችን መመለስ ለመጀመር የተደረጉ የመጨረሻ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ዛሬ የገመገመ ሲሆን ከመጪው ረቡዕ ጀምሮ ዜጎችን መመለሱ እንደሚጀምር ይፋ ሆኗል።
በውይይቱ እንደተገለፀው የበረራ፣ የማቆያ ማዕከላት ዝግጅት፣ የመገልገያ ቁሳቁስ፣ የምግብ እና መጠጥ አቅርቦት፣ የአልባሳት፣ የትራንስፖርት እንዲሁም የህክምና አገልግሎትን ለተመላሾች በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ በመቻል ረገድ የተደረጉ ዝግጅቶች በግብረ ሃይሉ አባላት ውይይት ተደርጎባቸዋል።የኮሚቴው ሰብሳቢ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንዳሉት የመመለሱ ተግባር ተመላሽ ዜጎችን ካሉበት አምጥቶ እስከ መኖሪያ ቀያቸው የማድረስ ስራን የሚሸፍን ነው።
ይህንኑ ከመነሻው እስከ መድረሻው በተሳለጠ ቅብብሎሽ ለመፈፀም ተቋማት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አምባሳደር ብርቱካን አሳስበዋል።ተመላሾች አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ ክልሎች ከየማዕከላቱ ቶሎ በማንሳት ወደ መኖሪያቸው መውሰድ ያለባቸው በመሆኑ ያደረጉት ዝግጅትም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ክልሎቹ ያልተጠናቀቁ የዝግጅት ስራዎችን በቀሪ ቀናት እንዲያጠናቅቁ አሳስበዋል።በየጊዜው የቅበላ አቅምን በማሳደግ ዜጎችን ካሉበት አስቸጋሪ ሁኔታ ለማውጣት መንግሥት የተቻለውን ጥረት ማድረጉን እንደሚቀጥልም አምባሳደሯ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የኢትዮጵያ ኮምንኬሽን ባለሥልጣን ሁለተኛውን የቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ ጨረታ በመጭው መስከረም እንደገና እንደሚጀምር ካፒታል ጋዜጣ ከባለሥልጣኑ መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል። ባለሥልጣኑ ጨረታውን ለማውጣት የሚያስችለውን ቅድመ ጥናት እንዳጠናቀቀ ዘገባው ገልጧል። ባለሥልጣኑ ለሁለተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ በተያዘው ዓመት መግቢያ ላይ ጀምሮት የነበረውን የጨረታ ሂደት ባለፈው ታኅሳስ ላልተወሰነ ጊዜ አቋርጫለሁ ማለቱ ይታወሳል።የሁለተኛው ቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ ጨረታ ሂደት የተቋረጠው፣ በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ኩባንያዎች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት እንደሆነ በወቅቱ ተገልጧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በጉራጌ ዞን ቆሴ ከተማ ያለው ችግር ምንድን ነው?
ቆሴ በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ወደከተማ አስተዳደርነት ለማደግ እንቅስቃሴ ላይ ያለች መለስተኛ ከተማ ናት።አካባቢው ሁለት የጉራጌ እና የሃድያ ብሔረሰቦች የሚዋሰኑበት ነው። በዚህ አካባቢ ከዚህ ቀደም ግጭት ተከስቶ ነበር። አካባቢው በህዝበ ውሳኔ ወደ ጉራጌ ዞን ተጠቃሎ ከቆየ ከረዥም ዓመታት በኋላ አሁን ደግሞ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለዶይቸ ቬለ እንደገለፁት ግጭት እንደ አዲስ ተነስቷል። » ለውጡ ከመጣ በኋላ በሀዲያ ዞን የሚኖሩ ወጣቶች ከተማው ለኛ ይገባል በሚል መነሳሳት ውዝግብ ተነስቷል።
እና አሁንም ድረስ ከፍተኛ የሆነ የአካል ጉድለት እና የንብረት ጉድለት እየተፈፀ ነው። ብዙ ቤቶች ተቃጥለዋል። »እንደ የአካባቢው ነዋሪ ከሆነ ችግሩ በውይይት ተፈታ በተባለ እለትም ቤቶች ተቃጥለዋል ንብረትም ወድሟል። « እስከዛሬ ድረስ ውጥረት ላይ ነው ያለው። ምንም መፍትሄ አላገኘም። ከተማዋ ላይ ትልቅ ገበያ ነበር። ግን እየተካሄደበት አይደለም» እናም ከመንግሥት አካላት መፍትሄ እንፈልጋለን ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች። ጉዳዩን አስመልክቶ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሃመድ ጀማል በመሠረተ ልማቶች ላይ በተደራጀ መልኩ ጥቃት የሚፈፅሙ ሰዎች እንደነበሩ ገልፀው «ዘግይተንም ቢሆን» በቅርቡ ችግሩን ለመፍታት ችለናል ይላሉ።
ባለፉት ሁለት ወራት በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም ይታያል ያሉን የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሁንም ግን አንዳንድ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሱና በቁጥጥር ስር ያልዋሉ ተጠርጣሪ ሰዎች መኖራቸውን ገልፀዋል።ቆሴ ከ 16 በላይ ብሔር ብሔረሰቦች አብረው የሚኖሩበት ከተማ እንደሆነች የገለፁልን የድቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዴ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምክንያት አለመግባባቶች የነበሩ ቢሆንም እነዚህ ጥያቄዎች አሁን በምክክር እና በውይይት ተፈተዋል ይላሉ። ይሁንና አሁንም የህዝቡን እንድነት ለመሸርሸር የሚሞክሩ ውስን ግለሰቦች አሉ ብለዋል። አቶ አለማየሁ አክለውም እንደዚህ አይነት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሰዎችን ህዝቡ ጠይቀዋል። ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ ሰዎችም በህግ እንደሚጠየቁ ገልጸዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ቆሴ በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ወደከተማ አስተዳደርነት ለማደግ እንቅስቃሴ ላይ ያለች መለስተኛ ከተማ ናት።አካባቢው ሁለት የጉራጌ እና የሃድያ ብሔረሰቦች የሚዋሰኑበት ነው። በዚህ አካባቢ ከዚህ ቀደም ግጭት ተከስቶ ነበር። አካባቢው በህዝበ ውሳኔ ወደ ጉራጌ ዞን ተጠቃሎ ከቆየ ከረዥም ዓመታት በኋላ አሁን ደግሞ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለዶይቸ ቬለ እንደገለፁት ግጭት እንደ አዲስ ተነስቷል። » ለውጡ ከመጣ በኋላ በሀዲያ ዞን የሚኖሩ ወጣቶች ከተማው ለኛ ይገባል በሚል መነሳሳት ውዝግብ ተነስቷል።
እና አሁንም ድረስ ከፍተኛ የሆነ የአካል ጉድለት እና የንብረት ጉድለት እየተፈፀ ነው። ብዙ ቤቶች ተቃጥለዋል። »እንደ የአካባቢው ነዋሪ ከሆነ ችግሩ በውይይት ተፈታ በተባለ እለትም ቤቶች ተቃጥለዋል ንብረትም ወድሟል። « እስከዛሬ ድረስ ውጥረት ላይ ነው ያለው። ምንም መፍትሄ አላገኘም። ከተማዋ ላይ ትልቅ ገበያ ነበር። ግን እየተካሄደበት አይደለም» እናም ከመንግሥት አካላት መፍትሄ እንፈልጋለን ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች። ጉዳዩን አስመልክቶ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሃመድ ጀማል በመሠረተ ልማቶች ላይ በተደራጀ መልኩ ጥቃት የሚፈፅሙ ሰዎች እንደነበሩ ገልፀው «ዘግይተንም ቢሆን» በቅርቡ ችግሩን ለመፍታት ችለናል ይላሉ።
ባለፉት ሁለት ወራት በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም ይታያል ያሉን የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሁንም ግን አንዳንድ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሱና በቁጥጥር ስር ያልዋሉ ተጠርጣሪ ሰዎች መኖራቸውን ገልፀዋል።ቆሴ ከ 16 በላይ ብሔር ብሔረሰቦች አብረው የሚኖሩበት ከተማ እንደሆነች የገለፁልን የድቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዴ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምክንያት አለመግባባቶች የነበሩ ቢሆንም እነዚህ ጥያቄዎች አሁን በምክክር እና በውይይት ተፈተዋል ይላሉ። ይሁንና አሁንም የህዝቡን እንድነት ለመሸርሸር የሚሞክሩ ውስን ግለሰቦች አሉ ብለዋል። አቶ አለማየሁ አክለውም እንደዚህ አይነት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሰዎችን ህዝቡ ጠይቀዋል። ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ ሰዎችም በህግ እንደሚጠየቁ ገልጸዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
https://tttttt.me/sabinaadvisor
የስራ ጉዞ ወደ # Europe
#Schengen_visa
👉 የሚሰራበት አገር - geneva, Swaziland
👉 የስራው አይነት :- accounting
👉 የስራ ቀናት - 6 ቀናት/ week
👉 የወር ደሞዝ - €10000_13000 and more
👉 ፆታ - አይጠይቅም
👉 ዕድሜ - 25እስከ 45
👉 መኖሪያ ቤት - በነፃ
👉 ፕሮሰሱ የሚፈጀው ግዜ ከ 2 - 3 ወር ነው
#10 persons
#Requirements
👉 Passport
👉photo
👉Degree documents
👉Work experience
Contact:
@Sabinavisa
+251118683939
0936363639
0936363680
የስራ ጉዞ ወደ # Europe
#Schengen_visa
👉 የሚሰራበት አገር - geneva, Swaziland
👉 የስራው አይነት :- accounting
👉 የስራ ቀናት - 6 ቀናት/ week
👉 የወር ደሞዝ - €10000_13000 and more
👉 ፆታ - አይጠይቅም
👉 ዕድሜ - 25እስከ 45
👉 መኖሪያ ቤት - በነፃ
👉 ፕሮሰሱ የሚፈጀው ግዜ ከ 2 - 3 ወር ነው
#10 persons
#Requirements
👉 Passport
👉photo
👉Degree documents
👉Work experience
Contact:
@Sabinavisa
+251118683939
0936363639
0936363680
Forwarded from Teklu Tilahun - ተክሉ ጥላሁን
#ወደ_ሀብት_ጉዞ
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች በሚለውና #አስበህ_ሐብታም_ሁን በሚል በተተረጎመው መጽሐፉ የምናውቀው የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ።
#ወደ_ሀብት_ጉዞ
ይህ ወደ ሀብት ጉዞ የተሰኘው መጽሐፍ እያንዳንዱን ሕልማችንንና ዓላማችንን ለማሳካት ያግዘናል፡፡
ብልፅግና በገንዘብና ዝና ብቻ የተገደበ ትርጉም እንደሌለው ያሳየናል፡፡ እውነተኛ ባለጸጋ ለመሆን በሁሉም የሕይወት ዘርፎች መበልፀግ ያስፈልጋል- በአካል፣ በመንፈስ፣ በገንዘብ፡፡
ለዚህም ደግሞ ከ25 ሺ በላይ ሰዎች የውድቀት ምክንያት፣ ከ500 በላይ ስኬታማ ሰዎች ምስጢርና የሀያ አምስት አመታት የምርምር ውጤት... ወደ #ሀብት_ጉዞ መጽሐፍን ፈጥሯል።
ከ60 ሚሊየን ኮፒ በላይ ከተሸጠው አስበህ ሀብታም ሁን መጽሐፍ ቀጥሎ ከፍተኛ ሽያጭን የተቀዳጀ መጽሐፍ።
እነሆ በሁሉም መልክ ወደ ሀብት ጉዞ!!
የናፖሊዮን ሂልን መጽሐፍ ይዞ!!!
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
ቲንክ ኤንድ ግሮው ሪች በሚለውና #አስበህ_ሐብታም_ሁን በሚል በተተረጎመው መጽሐፉ የምናውቀው የናፖሊዮን ሂል አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ።
#ወደ_ሀብት_ጉዞ
ይህ ወደ ሀብት ጉዞ የተሰኘው መጽሐፍ እያንዳንዱን ሕልማችንንና ዓላማችንን ለማሳካት ያግዘናል፡፡
ብልፅግና በገንዘብና ዝና ብቻ የተገደበ ትርጉም እንደሌለው ያሳየናል፡፡ እውነተኛ ባለጸጋ ለመሆን በሁሉም የሕይወት ዘርፎች መበልፀግ ያስፈልጋል- በአካል፣ በመንፈስ፣ በገንዘብ፡፡
ለዚህም ደግሞ ከ25 ሺ በላይ ሰዎች የውድቀት ምክንያት፣ ከ500 በላይ ስኬታማ ሰዎች ምስጢርና የሀያ አምስት አመታት የምርምር ውጤት... ወደ #ሀብት_ጉዞ መጽሐፍን ፈጥሯል።
ከ60 ሚሊየን ኮፒ በላይ ከተሸጠው አስበህ ሀብታም ሁን መጽሐፍ ቀጥሎ ከፍተኛ ሽያጭን የተቀዳጀ መጽሐፍ።
እነሆ በሁሉም መልክ ወደ ሀብት ጉዞ!!
የናፖሊዮን ሂልን መጽሐፍ ይዞ!!!
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል።
*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
በእስራኤል ከሚፈጸሙ ዘር ተኮር ጥቃቶች አብዛኞቹ ቤተ-እስራኤላውያን ላይ እንደሚያነጣጥሩ ሪፖርት ጠቆመ!
እስራኤል ውስጥ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ከተመዘገቡት የዘረኝነት ጥቃቶች ግማሽ ያህሉ ቤተ-እስራኤላውያን እንዲሁም አረቦች ላይ ያነጣጠሩ እንደነበሩ በመንግሥት የወጣ ሪፖርት አመለከተ።የእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር ባወጣውን ሪፖርት መሠረት እንደ አውሮፓውያኑ በ2021 እስራኤል ውስጥ ከተፈጸሙ 458 ዘር ተኮር ጥቃቶች መካከል 48 በመቶው ያህሉ የደረሱት ከኢትዮጵያ በሄዱ ቤተ-እስራኤላውያን እና በአረቦች ላይ ነው።
በእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር ሥር የሚገኘው የዘር ተኮር ጥቃቶች መከላከል ክፍል እንዳለው እነዚህ ጥቃቶች በአገልግሎት ዘርፍ የሚስተዋል መድልዎ፣ የሥራ ቅጥር መድልዎ፣ ዘረኛ ንግግሮች እና ዘረኛ ማስታወቂያዎችን ያካትታሉ።አምና ለእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት ኢትዮጵያዊ የዘር ሐረግ ያላቸው እስራኤላውያን ዘረኛ መድልዎ ይደርስባቸዋል፣ ይገለላሉም።
በመሥሪያ ቤቱ ከተመዘገቡ ዘረኛ ጥቃቶች መካከል 24 በመቶው በቀጥታ ቤተ-እስራኤላውያን ላይ ሲያነጣጥሩ፣ ቀሪው 24 በመቶ አረቦች፣ 10 በመቶው ደግሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የዘር ግንድ ያላቸው አይሁዳውያን ላይ የተቃጡ ናቸው።የእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር ባወጣውን ሪፖርት መሠረት፤ እአአ በ2019፤ 497 ዘር ተኮር ጥቃቶች ተመዝግበዋል። በ2020 ደግሞ 506 እንዲሁም አምና የተመዘገቡት 458 ጥቃቶች ናቸው።እነዚህ ጥቃቶች በፍትሕ ሚኒስቴር የተመዘገቡ ብቻ ሲሆኑ፣ በመላው አገሪቱ ያለው እውነታ ከዚህ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ዘገባዎች ይጠቁማሉ።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
እስራኤል ውስጥ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ከተመዘገቡት የዘረኝነት ጥቃቶች ግማሽ ያህሉ ቤተ-እስራኤላውያን እንዲሁም አረቦች ላይ ያነጣጠሩ እንደነበሩ በመንግሥት የወጣ ሪፖርት አመለከተ።የእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር ባወጣውን ሪፖርት መሠረት እንደ አውሮፓውያኑ በ2021 እስራኤል ውስጥ ከተፈጸሙ 458 ዘር ተኮር ጥቃቶች መካከል 48 በመቶው ያህሉ የደረሱት ከኢትዮጵያ በሄዱ ቤተ-እስራኤላውያን እና በአረቦች ላይ ነው።
በእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር ሥር የሚገኘው የዘር ተኮር ጥቃቶች መከላከል ክፍል እንዳለው እነዚህ ጥቃቶች በአገልግሎት ዘርፍ የሚስተዋል መድልዎ፣ የሥራ ቅጥር መድልዎ፣ ዘረኛ ንግግሮች እና ዘረኛ ማስታወቂያዎችን ያካትታሉ።አምና ለእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት ኢትዮጵያዊ የዘር ሐረግ ያላቸው እስራኤላውያን ዘረኛ መድልዎ ይደርስባቸዋል፣ ይገለላሉም።
በመሥሪያ ቤቱ ከተመዘገቡ ዘረኛ ጥቃቶች መካከል 24 በመቶው በቀጥታ ቤተ-እስራኤላውያን ላይ ሲያነጣጥሩ፣ ቀሪው 24 በመቶ አረቦች፣ 10 በመቶው ደግሞ የመካከለኛው ምሥራቅ የዘር ግንድ ያላቸው አይሁዳውያን ላይ የተቃጡ ናቸው።የእስራኤል የፍትሕ ሚኒስቴር ባወጣውን ሪፖርት መሠረት፤ እአአ በ2019፤ 497 ዘር ተኮር ጥቃቶች ተመዝግበዋል። በ2020 ደግሞ 506 እንዲሁም አምና የተመዘገቡት 458 ጥቃቶች ናቸው።እነዚህ ጥቃቶች በፍትሕ ሚኒስቴር የተመዘገቡ ብቻ ሲሆኑ፣ በመላው አገሪቱ ያለው እውነታ ከዚህ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ዘገባዎች ይጠቁማሉ።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ፌደራል መንግሥቱ እና የትግራይ ክልል አስተዳደር በተናጥል ግጭት ማቆማቸውን ባለፈው ሳምንት ካሳወቁ ወዲህ ወደ ትግራይ ዕርዳታ አልገባም በማለት የሕወሃት ባለሥልጣናት አማረዋል። የመንግሥት ቃል አቀባይ ለገሠ ቱሉ ግን ሕወሃት ታጣቂዎቹን ከአፋር ክልል ካላስወጣ ዕርዳታውን ለማጓጓዝ እንደማይቻል ለቪኦኤ ተናግረዋል። ባሁኑ ወቅት 43 ዕርዳታ የጫኑ ካሚዮኖች በሠመራ ከተማ ዝግጁ ሆነው የታጣቂዎችን መልቀቅ እየተጠባበቁ እንደሆነ ለገሠ ገልጸዋል። ሕወሃት ግን ግጭት የማቆም ቃሌን የማከብረው ዕርዳታ ከገባ ብቻ ነው ይላል።
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
በቤንች ሸኮ ዞን የጉራ ፈርዳ ወረዳ የጸጥታ ችግሮች ከዞኑ አቅም በላይ መሆናቸው ተገለጸ!
በቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ እና በአጎራባች አካባቢዎች በየወቅቱ የሚከሠቱ የጸጥታ መደፍረሶች ከዞኑ አቅም በላይ መሆናቸውን የቤንች ሸኮ ዞን መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ደቡብ ክልል በቤንች ሸኮ ዞን ቤንች ሸኮ ወረዳ፣ ሸካ ወረዳ፣ ጉራ ፈርዳ ወረዳ እና በአጎራባች ቦታዎች በየወቅቱ የሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮችን ለመቆጣጠር የጸጥታ ግብረ ኃይል እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም፣ ከዞኑ አቅም በላይ መሆኑን ተከትሎ በአከባቢው ያለውን የፀጥታ ችግር ሙሉ ለሙሉ ለማጥራት መቸገሩን የዞን ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ተስፋየ ጊታር ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በቤንች ሸኮ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ እና በአጎራባች አካባቢዎች በየወቅቱ የሚከሠቱ የጸጥታ መደፍረሶች ከዞኑ አቅም በላይ መሆናቸውን የቤንች ሸኮ ዞን መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ደቡብ ክልል በቤንች ሸኮ ዞን ቤንች ሸኮ ወረዳ፣ ሸካ ወረዳ፣ ጉራ ፈርዳ ወረዳ እና በአጎራባች ቦታዎች በየወቅቱ የሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮችን ለመቆጣጠር የጸጥታ ግብረ ኃይል እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም፣ ከዞኑ አቅም በላይ መሆኑን ተከትሎ በአከባቢው ያለውን የፀጥታ ችግር ሙሉ ለሙሉ ለማጥራት መቸገሩን የዞን ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ተስፋየ ጊታር ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በሀገር ውስጥ የዲ ኤን ኤ ምርመራ ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ!
ከዚህ ቀደም ወደ ዉጭ ሀገር በመላክ ይሰጥ የነበረዉን አገልግሎት በሀገር ዉስጥ ለመስጠት ያስችላል የተባለለት ለወንጀል ምርመራ የሚያግዝ የዘረ-መል (ዲ ኤን ኤ) ምርመራ በሀገር ዉስጥ ለመጀመር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።አገልግሎቱ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ስለሚጀምረዉ ቴክኖሎጂው አተገባበር እና ስለሙከራው ውጤታማነት በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ለህዝብ መረጃ እንደሚሰጥ የፌደራል ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄላን ኢብራሂም ተናግረዋል።
ለወንጀል ምርመራ ስራ የሚያግዙ አዳዲስ የፎረንሲክ ምርመራ ማሽኖችን ወደ ሀገር አስገብቶ ጥቅም ላይ እያዋለ መሆኑን የገለጸዉ ፖሊስ ሌሎች አሰራሮቹንም በቴክኖሎጂ እያዘመነ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።ከዚህ በተጨማሪም የአቪየሽን ፖሊስ፣ የምድር ባቡር ፖሊስ፣ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ እንዲሁም በኢንዱስትሪ እና ቱሪዝም ላይ ትኩረት አድርጎ የሚከታተል የፖሊስ ክፍሎች በአዲስ መልክ ተደራጅተዋል ነዉ የተባለው።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
ከዚህ ቀደም ወደ ዉጭ ሀገር በመላክ ይሰጥ የነበረዉን አገልግሎት በሀገር ዉስጥ ለመስጠት ያስችላል የተባለለት ለወንጀል ምርመራ የሚያግዝ የዘረ-መል (ዲ ኤን ኤ) ምርመራ በሀገር ዉስጥ ለመጀመር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።አገልግሎቱ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ስለሚጀምረዉ ቴክኖሎጂው አተገባበር እና ስለሙከራው ውጤታማነት በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ለህዝብ መረጃ እንደሚሰጥ የፌደራል ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄላን ኢብራሂም ተናግረዋል።
ለወንጀል ምርመራ ስራ የሚያግዙ አዳዲስ የፎረንሲክ ምርመራ ማሽኖችን ወደ ሀገር አስገብቶ ጥቅም ላይ እያዋለ መሆኑን የገለጸዉ ፖሊስ ሌሎች አሰራሮቹንም በቴክኖሎጂ እያዘመነ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።ከዚህ በተጨማሪም የአቪየሽን ፖሊስ፣ የምድር ባቡር ፖሊስ፣ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ እንዲሁም በኢንዱስትሪ እና ቱሪዝም ላይ ትኩረት አድርጎ የሚከታተል የፖሊስ ክፍሎች በአዲስ መልክ ተደራጅተዋል ነዉ የተባለው።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
ዘመን ባንክ የማስተር ካርድ የክፍያ ሲስተምን መተግበር የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ!
ዘመን ባንክ ኤም ፒ ጂ ኤስ የተባለ የማስተር ካርድ ሲስተምን በማስጀመር ክፍያዎችን በቀጥታ መክፈል የሚያስችል ቴክኖሎጂን አስተዋውቋል።ይህንን ቴክኖሎጂ ያስተዋወቀው ከማስተር ካርድ ጋር በመሆን ነው።ይህ የክፍያ ሲስተም ለአየር መንገድ እንዲሁም ለሆቴሎች ቅድሚያ አገልግሎት ክፍያ መፈጸም የሚያስችል ነው ተብሏል።
ከዚህ በተጨማሪም የኦንላየን ግብይቶችን በቀጥታ መክፈል የሚያስችል ነው።ይህ የክፍያ ሲስተም በኢትዮጵያ ብርም መገበያየት የሚያስችልና የቀጥታ ክፍያ ንክኪን የሚቀንስ ነው።ኢኮሜርስ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ የመጣ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት ቴክኖሎጂ ግብይቱን በአንድ ቦታ በመጨረስ እንዲቀላጠፍ ያደርጋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ዘመን ባንክ ኤም ፒ ጂ ኤስ የተባለ የማስተር ካርድ ሲስተምን በማስጀመር ክፍያዎችን በቀጥታ መክፈል የሚያስችል ቴክኖሎጂን አስተዋውቋል።ይህንን ቴክኖሎጂ ያስተዋወቀው ከማስተር ካርድ ጋር በመሆን ነው።ይህ የክፍያ ሲስተም ለአየር መንገድ እንዲሁም ለሆቴሎች ቅድሚያ አገልግሎት ክፍያ መፈጸም የሚያስችል ነው ተብሏል።
ከዚህ በተጨማሪም የኦንላየን ግብይቶችን በቀጥታ መክፈል የሚያስችል ነው።ይህ የክፍያ ሲስተም በኢትዮጵያ ብርም መገበያየት የሚያስችልና የቀጥታ ክፍያ ንክኪን የሚቀንስ ነው።ኢኮሜርስ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ የመጣ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት ቴክኖሎጂ ግብይቱን በአንድ ቦታ በመጨረስ እንዲቀላጠፍ ያደርጋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በ2014 የሙያ ብቃት ምዘና ከወሰዱ መምራን መካከል 1,600ዎቹ ማለፋቸው ተነገረ፡፡
ምዘናው ሁለት ዓይነት እንደሆነ የከተማዋ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዛሬ ባዘጋጀው መርኃ ግብር ላይ ሲነገር ተሰምቷል።የመጀመሪያው የጽሑፍ ምዘና ሲሆን ይህን ምዘና 1,835 መምህራን በዚህ ዓመት ወስደዋል ተብሏል።
የጽሑፍ ፈተናውን ከወሰዱ 1,835 መምህራን መካከል 1,600ዎቹ ለማህደረ ተግባር ፈተና መቅረባቸው ተጠቅሷል።እነዚህ በሙሉ የማህደረ ተግባር ፈተናውን አልፈው የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሠርተፊኬት ማግኘታቸው ተነግሯል።የማህደረ ተግባር ምዘና የመምህሩን አጠቃላይ የተግባር እንቅስቃሴ የሚያሳይ ስርዓት እንደሆነ ተሰምቷል።
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
ምዘናው ሁለት ዓይነት እንደሆነ የከተማዋ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዛሬ ባዘጋጀው መርኃ ግብር ላይ ሲነገር ተሰምቷል።የመጀመሪያው የጽሑፍ ምዘና ሲሆን ይህን ምዘና 1,835 መምህራን በዚህ ዓመት ወስደዋል ተብሏል።
የጽሑፍ ፈተናውን ከወሰዱ 1,835 መምህራን መካከል 1,600ዎቹ ለማህደረ ተግባር ፈተና መቅረባቸው ተጠቅሷል።እነዚህ በሙሉ የማህደረ ተግባር ፈተናውን አልፈው የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሠርተፊኬት ማግኘታቸው ተነግሯል።የማህደረ ተግባር ምዘና የመምህሩን አጠቃላይ የተግባር እንቅስቃሴ የሚያሳይ ስርዓት እንደሆነ ተሰምቷል።
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa